መፈንቅለ መንግስት...
መፈንቅለ መንግስት...
መፈንቅለ መንግስት...
Create successful ePaper yourself
Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />
መልካም<br />
ዓዲስ ዓመት<br />
መልካም ዓዲስ ዓመት<br />
የምንሻው<br />
አጋርነት<br />
በባራክ ኦባማ<br />
/ፕሬዝዳንት/<br />
‹‹በአዲሱ ዓመት ‘አሸባሪ’<br />
ከመባል ይጠብቃችሁ››<br />
ሰሞነኛ ምርቃት<br />
ከታች ሰፈር ልጆች ጋር በኮሪያ- ዴጉ ተካሂዶ የነበረውን የአትሌቲክስ ሻምፒዮና<br />
ፍፃሜ እየተመለከትን እያለ ምነው አትሌቶቻችን ውጤት ራቃቸው ብል እየተቀባበሉ<br />
‹‹የሚወራውን አልሰማህም እንዴ?… ‘እያንጓለለ ካልተፈታ’ ብለው አድማ ላይ እኮ<br />
4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5 2003 ዋጋ 7፡00 ብር<br />
•<br />
•<br />
•<br />
‹‹በቴሌቪዥን በሚሰሩት ‘ድራማ’ ሀቅ ሊወጣ አይችልም››<br />
ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ<br />
ለቢቢሲ ያወራነው በአደባባይ ነጋ ጠባ ስናወራው የነበረ ነው<br />
የኢቴቪ ዘገባ ላይ የትርጉም ስህተቶች ነበሩ<br />
አባሎቻችሁ ናቸው የተባሉ ሰዎችን አላውቃቸውም<br />
የደርግ ከፍተኛ ባለስልጣን የነበሩትና ኋላ ላይም ስርአቱን በመክዳት ወደ ውጭ ያቀኑት<br />
ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ ከሁለት አስርት አመታት በኋላ ሰሞኑን የመጀመሪያ<br />
የሆነውን ይፋዊ ቃለምልልስ ሰጥተዋል። ግንቦት 8 ቀን 1981 ዓ.ም ስለተደረገው<br />
መንፈንቅለ <strong>መንግስት</strong>፣ደርግን ሥርዓት ለመጣል ይፋለሙ የነበሩትን ሻዕቢያና ህወሀትን<br />
በማግባባት ረገድ ምን ሚና እንደተጫወቱ፣ በወቅታዊው የኢትዮጵያ ፖለቲካና<br />
እስካሁን ይፋ ባልተደረጉ በርካታ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ በዝርዝር ይናገራሉ፡<br />
“የ1981 <strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong><br />
ለማድረግ ከሻዕቢያና ከወያኔ ጋር ተስማምተን ነበር”<br />
በ ገፅ 16<br />
በውስጥ ገፅ በውስጥ ገፅ በውስጥ ገፅ<br />
እንቁጣጣሽ<br />
Vs<br />
ቅዱስ ዮሐንስ<br />
በ ገፅ 20<br />
ደበበ እሸቱ እንዲፈታ አንድነት/መድረክ ጠየቀ<br />
• ‹‹<strong>መንግስት</strong> ሕዝቡን እያሸበረ ነው››<br />
•<br />
‹‹ኢህአዴግ ሁለት ሰዎች ድንበር አቋረጡ ብሎ ሊጨነቅ ቀርቶ አገር ገንጥሎ የሚሰጥ ድርጅት ነው››<br />
በሱራፍኤል ግርማ<br />
<strong>መንግስት</strong> በአሸባሪነት ከፈረጀው ግንቦት ሰባት ጋር ‹‹የሕቡዕ ግንኙነት አለው›› በሚል ምክንያት ለእስር<br />
የተዳረገው አንጋፋው አርቲስትና ፖለቲከኛ ደበበ እሸቱ እንዲፈታ የመድረክ አመራር አባላት ጠየቁ።<br />
ምንም እንኳን የአቶ ደበበን መታሰር አስመልክቶ ለብሉም በርግ አስተያየታቸውን የሰጡት የ<strong>መንግስት</strong><br />
ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ሽመልስ ከማል ‹‹ከአሸባሪው ግንቦት ሰባት ጋር ግንኙነት አለው፤<br />
የሚስ አብዮታዊ ዴሞክራሲ<br />
ልማታዊ ውበት ምስጢር<br />
አንባብያን ሆይ! የተያያዝነውን የሀገር ገፅታ ግንባታ በማስቀጠሉ ረገድ ጉልህ ሚና<br />
እንደሚጫወት የታመነበት ታላቅ ውድድር በቅርቡ መካሄዱ ይታወቃል። በውድድሩም<br />
በታሪካችን ለመጀመሪያ ጊዜ የብሔር ብሔረሰቦችን እኩል ተሳትፎ ባረጋገጠ መልኩ ከተለያዩ<br />
የኅብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጣ የልማታዊ ዳኞች ቡድን፣ የልማታዊ ውበትን እሳቤ የተላበሰች<br />
ቆንጆ መርጦ “ሚስ አብዩታዊት ዴሞክራሲ” ሲል ሰይሟል። ወርቃማው የአሸናፊነት ዘውድ<br />
በክብር ከተጫነላት ወጣት ጋር ልማታዊው ጋዜጠኛችን ቀጣዩን አጭር ቆይታ አድርጓል።<br />
ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ<br />
ናቸው›› አሉኝ። ምን ለማለት ፈልገው እንደሆነ ግን አልገባኝም፡፡<br />
በ ገፅ 9<br />
በ ገፅ 21<br />
በ ገፅ 9<br />
በ ገፅ 7<br />
ማብቂያ የለሹ የኢትዮጵያዊያን ሰቆቃ<br />
በመካከለኛው ምስራቅ?!<br />
አሜሪካ ስለኢትዮጵያ<br />
ምን ታስባለች?<br />
አዳዲስ የዊክሊክስ<br />
መረጃዎች ይናገራሉ<br />
ጠ/ሚኒስትሩ የወታደራዊ ኃይል<br />
የበላዩ ጄኔራል ሳሞራ እና የደህንነት<br />
ክፍሉ ሃላፊ አቶ ጌታቸው አሰፋ<br />
አሜሪካ የኢትዮጵያን የደህንነት<br />
አሳሳቢ ጉዳዮች ጉዳዬ ትላቸው<br />
እንደሆን እምነቱ ተመናምኖባቸዋል<br />
እስከማለት ደርሰዋል። እነዚህ<br />
ሁለቱ ባለሥልጣናት ጦረኛ ነገር<br />
ግን በውጭ ፖሊሲ ጉዳይ ላይ<br />
እጅግ ተፅዕኖ ፈጣሪ የገዢው<br />
ፓርቲ አባላት ናቸው።<br />
5<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ
2<br />
የካቲት 2000 ዓ.ም ተመሠረተ<br />
አውራምባ ታይምስ፡- በብሉ<br />
ኤርዝ ጀነራል ቢዝነስ ኃላ/የተ/<br />
የግል/ማህበር ስር የሚታተም፤<br />
በፖለቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ<br />
የሚያተኩር፤ በንግድ ሚኒስቴር<br />
በቁጥር 020/2/6572/2001<br />
የተመዘገበ ሳምንታዊ ጋዜጣ ነው፡፡<br />
T’@Í=”Ó ›?Ç=}`<br />
Ç©ƒ ŸuÅ<br />
ª“ ›²ÒÏ<br />
õì
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />
መልካም ዓዲስ ዓመት<br />
በባራክ ኦባማ<br />
/ፕሬዝዳንት/<br />
በዚህ የመስከረም<br />
1፣ 1993 የሽብርተኞች ጥቃት<br />
10ኛ ዓመት መታሰቢያ፣ የሽብር<br />
ጥቃቱ በዩናይትድ ስቴትስ<br />
ላይ ብቻ ሳይሆን፣ በዓለም<br />
እንዲሁም በሰብዓዊነት እና<br />
በጋራ ተስፋዎቻችን ላይ የተቃጣ<br />
መሆኑን እናስታውሳለን።<br />
በዚያን ዕለት<br />
ሕይወታቸውን ካጡት ወደ<br />
3ሺህ የሚጠጉ ንፁሀን ሰዎች<br />
ውስጥ በመቶዎች የሚቆጠሩት<br />
ከ90 የሚበልጡ አገራት ዜጎች<br />
እንደነበሩም እናስታውሳለን።<br />
በርካታ ዘሮች እና እምነቶች<br />
ያሏቸው ወንዶችና ሴቶች፣<br />
ወጣትና አዛውንትም ነበሩ። በዚህ<br />
የሐዘን መታሰቢያ የእነርሱን<br />
ትውስታ ከቤተሰቦቻቸው እና<br />
ከየአገሮቻቸው ጋር በመሆን<br />
በአክብሮት እንዘክራለን።<br />
የዛሬ አሥር ዓመት<br />
ዓለም እንደ አንድ የተሰባሰበበትን<br />
ሁኔታ ከምስጋና ጋር<br />
እናስታውሰዋለን። በዓለም ዙርያ<br />
ያሉ ከተሞች በሙሉ ለደቂቃ<br />
በሕሊና ፀሎት እረጭ ብለው ነበር።<br />
ሰዎች በአብያተ-ክርስቲያናት፣<br />
በመስጊዶች፣ በምኩራቦችና<br />
የምንሻው<br />
አጋርነት<br />
በሌሎችም የአምልኮ ሥፍራዎች<br />
ፀሎታቸውን አድርሰዋል። እኛም<br />
በዩናይትድ ስቴትስ የምንገኝ፣<br />
በመላው የዓለም ዳርቻ የሚገኙ<br />
ሕዝቦች ባከበሯቸው የሻማ<br />
ምሽቶችና በየኤምባሲዎቻችን<br />
ደጃፎች ባስቀመጧቸው አበቦች<br />
በአንድነት መንፈስ ከጎናችን<br />
መቆማቸውን ያሳዩበትን ሁኔታ<br />
ከቶም አንረሳውም።<br />
ከመስከረም 1፣<br />
1993 በኋላ ባሉት ሳምንታት<br />
እንደ ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ<br />
መንቀሳቀሳችንንም እናስታውሳለን።<br />
የመጠነ ሰፊው ጥምረታችን አካል<br />
በሆነ እንቅስቃሴ አል-ቃኢዳን<br />
በአፍጋኒስታን ከሚገኙ የማሰልጠኛ<br />
ሠፈሮቹ አባረነዋል፤ ታሊባንን<br />
ከሥልጣን አስወግደናል፤<br />
እንዲሁም ለአፍጋን ሕዝቦች<br />
ከሽብር ነፃ ሆነው የሚኖሩበትን<br />
ዕድል ሰጥተናቸዋል። ነገር<br />
ግን ቀጣዮቹ ዓመታት ቀላል<br />
አልነበሩም፤ በመስከረም 1፣ 1993<br />
ማግስት ተጋርተነው የነበረው<br />
የዓለም አቀፍ አጋርነት መንፈስም<br />
ፈተና ገጥሞት ነበር።<br />
እንደ አሜሪካ<br />
ፕሬዝዳንትነቴ፣ የተጋረጡብንን<br />
ዓለማቀፋዊ ተግዳሮቶች<br />
ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ለመቋቋም<br />
የሚያስፈልገንን ዓለምአቀፋዊ<br />
ትብብር ለማደስ የሚያስችሉ<br />
ተግባራትን አከናውኛለሁ። አብሮ<br />
የመሥራት አዲስ ዘመንን ይፋ<br />
በማድረግ፣ ከአገራትና ከሕዝቦች<br />
ጋር በጋራ ፍላጎትና በመከባበር<br />
ላይ የተመሠረተ አጋርነትን<br />
መሥርተናል።<br />
እንደ ዓለም አቀፍ<br />
ማኅበረሰብ፣ ሽብርተኞች ከዜጎቻችን<br />
ጋር የሚነጻጸር ጥንካሬና ፅናት<br />
እንደሌላቸው አሳይተናል።<br />
ዩናይትድ ስቴትስ ከኢስላም ጋር<br />
ጦርነት ውስጥ እንዳልሆነችና<br />
ወደፊትም እንደማትሆን ግልጽ<br />
አድርጌአለሁ። ከዚያ ይልቅ፣<br />
CITY TECH TRADING<br />
New Arrival Surveying Equipment<br />
Leica Total Stations<br />
Sokkia Totalstation<br />
Sokkia Automatic Level<br />
Come and Visit Our Shop to Get All<br />
Surveying Equipment with Affordable Price<br />
Address:-Bole DH Geda Tower 1st floor, No 1-09<br />
Tell: +251911 229906 ,+251 16628452 +251 16628052<br />
ከተባባሪዎቻችንና ከአጋሮቻችን ጋር<br />
አል-ቃኢዳን ለመዋጋት በአንድነት<br />
ቆመናል። አል-ቃኢዳ በበርካታ<br />
አገራት በፈፀማቸው ጥቃቶች<br />
በአሥር ሺህዎች የሚቆጠሩ<br />
ንፁኃን ወንዶች፣ ሴቶችና ሕፃናትን<br />
የገደለ ሲኾን፣ ከሰለባዎቹ ውስጥ<br />
እጅግ የሚበዙት ሙስሊሞች<br />
ናቸው። እናም በዚህ ሳምንት፣<br />
ከመካከለኛው ምስራቅ እስከ<br />
አውሮፓ፣ ከአፍሪካ እስከ ኢሲያ<br />
ሁሉንም የአል-ቃኢዳ ሰለባዎች፣<br />
እንዲሁም ቤተሰቦቻቸውና<br />
ዜጎቻቸው በፈታኝ ሁኔታዎች<br />
ውስጥ ለማለፍ ያሳዩትን ድፍረትና<br />
ፅናት እናስታውሳለን።<br />
በጋራ በመንቀሳቀሳችን<br />
የአል-ቃኢዳ ሴራዎችን አክሽፈናል፤<br />
ኦሳማ ቢን ላደንንና ብዙዎቹን<br />
የአመራሩ አባላት አስወግደናል፤<br />
እናም አል-ቃኢዳን በሽንፈት<br />
ጎዳና ላይ እንዲጓዝ ዳርገነዋል።<br />
ይህ በዚህ እንዳለ፣ በመካከለኛው<br />
ምስራቅና በሰሜን አፍሪካ<br />
የሚገኙ ሕዝቦች ፍትኅና ሰብዓዊ<br />
ክብርን ለመቀዳጀት የሚያበቃው<br />
እርግጠኛ መንገድ፣ አዕምሮ-አልቦ<br />
ሽብርተኝነትና ነውጥ ሳይሆን፣<br />
ከነውጥ አልባነት የሚመነጭ<br />
የሞራል ኃይል (የበላይነት)<br />
መሆኑን እያሳዩ ይገኛሉ። ይህ<br />
ሁኔታ ነውጠኛ ጽንፈኞች<br />
ሰሚ እያጡ መምጣታቸውንና<br />
መጪው ዘመን የእነዚያ ለማፍረስ<br />
የሚተጉት ሽብርተኞች ሳይሆን<br />
መገንባትን ለሚሹት መሆኑን<br />
በግልጽ አመላክቷል።<br />
የሰላምና የብልጽግና<br />
መጻዒ ዘመንን ለሚሹ አገራትና<br />
ሕዝቦች - ዩናይትድ ስቴትስ<br />
ከእነርሱ ጋር በአጋርነት<br />
ትቆማለች። በአገር ውስጥ<br />
ኢኮኖሚያዊ ተግዳሮቶች እያሉብን<br />
እንኳ፣ ዩናይትድ ስቴትስ በዓለም<br />
ላይ የተለየ የአመራር ሚና<br />
መጫወቷን ትቀጥላለች። ከኢራቅ<br />
ቀሪ ወታደሮቻችንን ስናስወጣና<br />
በአፍጋኒስታንም ፀጥታ የማስከበር<br />
ኃላፊነቱን ስናስተላልፍ፣<br />
ኢራቃውያንና አፍጋኖች<br />
የሕዝቦቻቸውን ደኅንነት ለማስከበር<br />
እና የዕድሎች ተጠቃሚነትን<br />
ለማረጋገጥ የሚያደርጉትን<br />
ጥረት መደገፋችንን እንቀጥላለን።<br />
በአረቡ ዓለምና ከዚያም ባሻገር፣<br />
ለመላው የሰው ልጆች ክብር እና<br />
ሁለንተናዊ መብቶች መከበር<br />
በጽናት እንቆማለን።<br />
በዓለም ዙርያ ሰላምን<br />
ለማስፈን፣ ሕዝቦችን ከድህነት<br />
የሚያወጡ የልማት ተግባራትን<br />
ለማገዝ፣ እንዲሁም የምግብ<br />
ዋስትናን፣ ጤናንና የዜጎችና<br />
የኅብረተሰብን እምቅ አቅም ጥቅም<br />
ላይ ለማዋል የሚያስችለውን<br />
መልካም አስተዳደር ለማራመድ<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
3<br />
የሚጠይቀውን ከባድ ሥራ<br />
መስራታችንን እንቀጥላለን።<br />
ከዚሁ ጎን ለጎን፣<br />
በአገር ውስጥ እሴቶቻችንን<br />
ጠብቀን ለመኖር የራሳችንን<br />
ቃል-ኪዳን እናድሳለን፡፡ ዩናይትድ<br />
ስቴትስ የስደተኞች አገር<br />
እንደመሆኗ ከየትኛውም አገርና<br />
ባህል የሚመጡ ሕዝቦችን እጆቿን<br />
ዘርግታ ትቀበላለች። እኒህ አዳዲስ<br />
አሜሪካውያን - የዛሬ አሥር ዓመት<br />
እንዳጣናቸው ንፁኃን የሽብር<br />
ሰለባዎች ሁሉ - የቱንም ያህል<br />
የዘር ወይም የጎሳ፣ የአስተዳደግ<br />
ወይም የእምነት ልዩነቶች<br />
ቢኖሩን እንኳ ሁላችንም ይህችን<br />
ዓለም ለዛሬውም ሆነ ለመጪው<br />
ትውልድ የተሻለች የመኖርያ<br />
ስፍራ ለማድረግ እንችላለን<br />
በሚል የጋራ ተስፋ የተሳሰርን<br />
መሆናችንን ያስታውሱናል።<br />
እነዚያን ያጣናቸውን ሰዎችም<br />
ከዚህ ታላቅ እሴት ጋር ልናስባቸው<br />
ግድ ይለናል።<br />
እነዚያ መስከረም 1<br />
ቀን 1993 ጥቃት የፈፀሙብን<br />
ሰዎች በዩናይትድ ስቴትስ እና<br />
በተቀረው ዓለም መካከል የጥላቻ<br />
ንፋስ እንዲነፍስ ፈልገው ነበር።<br />
አልተሳካላቸውም። እነሆ በጥቃቱ<br />
የአሥረኛ ዓመት መታሰቢያ<br />
ከወዳጆቻችንና ከአጋሮቻችን ጋር<br />
በአንድነት ቆመን እነዚያን በዚህ<br />
ትግል ውስጥ ያጣናቸውን በሙሉ<br />
እናስታውሳለን። እነርሱንም<br />
በማስታወስ፣ ሕዝቦች ሁሉ<br />
በክብር፣ በነፃነትና በሰላም<br />
የሚኖሩባትን ዓለም ዕውን<br />
ለማድረግ የሚያስፈልገንን<br />
የአጋርነትና የመከባበር መንፈስ<br />
ዳግም እናረጋግጣለን።<br />
/ባራክ ኦባማ የዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ ፕሬዝዳንት ናቸው።<br />
ይህ ጽሑፍ፣ የመስከረም አንዱ የሽብርተኞች ጥቃት 10ኛ ዓመት<br />
መታሰቢያን አስመልክተው ያስተላለፉት መልእክት ሲሆን አዲስ አበባ<br />
በሚገኘው የአሜሪካን ኤምባሲ በኩል ለዝግጅት ክፍላችን የተላከ ነው።/
4<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
ፊ ቸ ር<br />
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />
መልካም ዓዲስ ዓመት<br />
ማብቂያ የለሹ የኢትዮጵያዊያን ሰቆቃ<br />
በመካከለኛው ምስራቅ?!<br />
ኢትዮጵያዊያን ወደ መካከለኛው ምስራቅ የሚያደርጉት ስደት እና የሚደርስባቸው ኢ-ሰብዓዊ ጥቃት የጭንቅ ዜና አብሳሪነቱ ቀጥሏል። አቤል ዓለማየሁ እና<br />
ሱራፍኤል ግርማ ባሰናዱት ቀጣይ ሀተታዊ ፅሁፋቸው የህግ ባለሙያዎች፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፣ በጉዳዩ ላይ ሰፊ ጥናት ያካሄዱ ኢትዮጵያዊያንንና<br />
ዕድሜያቸው በ60ዎቹ መባቻ ላይ የሚገመተው<br />
ወ/ሮ ኩሪ ወልዱ በትካዜ ተውጠው ዕንባቸው መንታ<br />
መንታ ሆኖ ይወርዳል። በጎረቤቶቻቸውና በንስሐ<br />
አባታቸው ጭምር ቢለመኑ፣ ቢገዘቱ ማንባታቸውን<br />
ማቆም አልቻሉም። ስለልጃቸው መልካም ፀባይና ቅን<br />
አሳቢነት ሳይታክቱ ደግመው ደጋግመው በማያባራው<br />
እንባቸው በመታጀብ ይናገራሉ። ‹‹ልጄን የማጎርስበት<br />
አቅም እንኳን የለኝም፤ እንዲያሳክምልኝ <strong>መንግስት</strong>ን<br />
እና የኢትዮጵያን ሕዝብ እለምናለሁ›› የሚል<br />
ተማፅኗቸውን ያቀርባሉ። አዛውንቷ ወ/ሮ በሞሐመድ<br />
ጋዳፊ ቤተሰብ ኢ-ሰብዓዊ ጥቃት የደረሰባት የሸዋዬ<br />
ሞላ እናት ናቸው።<br />
ሊቢያን ለ42 ዓመታት እንደግል ድርጅታቸው<br />
ባሻቸው መንገድ ሲዘውሯት እንደኖሩና የአምባገነኖች<br />
አርአያ መሆናቸው ከሚነገርላቸው ጋዳፊ ልጆች<br />
አንዱ የሆነው ሐኒባል ጋዳፊ ሚስት የሆነችው<br />
አሊያን፤ እንጀራ ፍለጋ በተሰደደችው ሸዋዬ ሞላ<br />
ላይ ያደረሰችው ዘግናኝ ድርጊት ልብ አድሚም፣<br />
አነጋጋሪም ሆኗል። አሊያን ‹‹ያለ ምግብና ውኃ ለሶስት<br />
ቀናት እንድትቆዪ የሰጠኹሽን ትዕዛዝ ተላልፈሻል››<br />
በሚል ምክንያት የወጣቷን እጅና እግር በሌሎች<br />
የቤት ሠራተኞች አሳስራ የፈላ ውኃ በጭንቅላቷ<br />
ላይ በማፍሰስ ከባድ ጉዳት ከማድረሷ በላይ፣ ወጣቷ<br />
ሕክምና እና በቂ ምግብና ውኃ እንዳታገኝ በጠባብ<br />
ከፍል ውስጥ ለወራት ዘግታባት መቆየቷ የጥቃቱን<br />
ከፍተኛነት አጉልቶታል።<br />
የሚመለከታቸው የ<strong>መንግስት</strong> ባለስልጣናትን በማነጋገር ‹‹ይህ ችግር ማብቂያው መቼ ይሆን?›› ሲሉ ይጠይቃሉ።<br />
ኃላፊ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ሴቶችም ሆኑ ወንዶች<br />
እድላቸውን ለመሞከር በዓለም አቀፍ መድረክ ሙከራ<br />
ማድረጋቸውን (መጓዛቸውን) እንደ ችግር መውሰድ<br />
እንደሌለበት ጠቁመው ‹‹ግን›› ይላሉ፣ ‹‹ግን ዜጎች<br />
በሄዱበት የዜግነት ክብራቸው እንዳይነካ <strong>መንግስት</strong><br />
ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል። <strong>መንግስት</strong> ያለውም ዜጎች<br />
ጥቅም ለማስጠበቅ ነውና›› ይላሉ።<br />
‹‹እዚህ አገር ያለው አማራጭ ውስጥ ስለሆነ ዜጎች<br />
በሕገ-ወጥ መንገድ ከአገር ወጥተዋል ብሎ በቸልታ<br />
ሊታዩ አይገባም። ራስን ለመለወጥ እንደሚደረግ<br />
ሰዋዊ ባህሪ ማየት ይገባል። ስለሁሉም ኢትዮጵያዊ<br />
ዜጋ ኃላፊነት አለበት›› በማለት ፕሮፌሰር በየነ<br />
ጴጥሮስ ለሁሉም ዜጎች ከለላ መሆን እንዳለበት<br />
<strong>መንግስት</strong>ን ያሳስባሉ።<br />
የኢትዮጵያ <strong>መንግስት</strong><br />
ለዜጎቹ ከለላ እየሆነ ነውን?<br />
የደነደነ ልብ ያለውን ሰው እንኳን ስሜት<br />
የሚሰብረው መካከለኛው ምስራቅ እና አንዳንድ<br />
የአፍሪካ አገራት የሚጓዙ ኢትዮጵያውያን ሴቶች<br />
መብት ጥሰት የዘወትር ጩኸት ቢሆንም የሸዋዬ<br />
ሞላ ጉዳት የሲ.ኤን.ኤን፣ አልጀዚራና አል አረቢያ<br />
በግርድፉም ቢሆን የሌሎች ብዙዎች የሚከታተሏቸው<br />
መገናኛ ብዙሐንን ከወትሮው የተለየ ትኩረት ስላገኘ<br />
ዓለም አቀፍ መነጋገሪያ ሆኗል። አጋጣሚውን በአረብ<br />
አገራቱ ላሉ ዜጎች መታደግ የሚቻልበት ጊዜ ‹‹አሁን››<br />
መሆኑን ይበልጥ ስለመጠቆሙ እየተገለፀ ነው።<br />
ሸዋዬ ላይ የተፈፀመው በደል በሊቢያ ከተፈጠረው<br />
አመፅ ተንተርሶ በጋዳፊ ቤተሰብ መሆኑ ዓለም አቀፍ<br />
ትኩረትን ስቦ ለመነጋገሪያነት በቃ እንጂ፣ በሌሎች<br />
አረብ አሰሪዎቻቸው ከፍተኛ ስቃይ የሚደርስባቸው<br />
አያሌ ‹‹ሸዋዬዎች›› መኖራቸው የዘወትር ሐቅ ነው።<br />
‹‹የአረብ አገር ሕይወት መሯት ራሷን ከፎቅ ወርውራ<br />
ሞተች››፣ ‹‹መርዝ በመጠጣት ራሷን የማጥፋት<br />
ሙከራ አደረገች›› እንዲሁም ‹‹አሰሪዋን ገደለች››<br />
የሚሉ ዜናዎች ለኢትዮጵያውያን አዲስ አይደሉም።<br />
‹‹የሸዋዬ ጉዳይ የሚዲያዎችን ሰፊ ትኩረት<br />
ስላገኘ አረቦች ደንግጠዋል። መንግስታቱም የዜጎችን<br />
መብት ያከብሩ ዘንድ ከዓለም አቀፍ ሰብዓዊ መብት<br />
ጠባቂዎች ወቀሳ ለማምለጥ የተቻላቸውን ያህል<br />
የሰብዓዊ መብት ጥበቃ ያደርጋሉ የሚል እምነት<br />
አለኝ›› የሚለው ነብዩ ሲራክ አጋጣሚው (የሸዋዬ<br />
ጉዳት) አሳዛኝ ቢሆንም ችግሩ እንዲጎላና ዓለማቀፋዊ<br />
እውቅና እንዲኖረው የሚያደርግ መልካም አጋጣሚ<br />
መፈጠሩን ያምናል። አምባሳደር ዲና ሙፍቲም<br />
ክስተቱ ንቃትን እንደሚጨምር ይስማማሉ።<br />
‹‹በየኤምባሲው ያሉ ሰዎች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ<br />
መወጣት አለባቸው። በትክክል ውጪ የሚገኙ<br />
ኢትዮጵያውያን ለሚያቀርቧቸው ጥያቄዎች ተገቢውን<br />
ምላሽ ሊሰጥ ይገባል›› ይላሉ።<br />
ተቀድቶ ‹‹በማያልቅ›› የነዳጅ ሀብት አቅማቸው<br />
ወደዳበሩት የአረብ አገራት ከቤት ሰራተኝነት ብቻ<br />
ሳይሆን በተለያየ የሙያ መስኮች ሥራ ፈላጊዎች<br />
ይተማሉ። በቤት ሰራተኝነት ወደ አገራቱ ከሚደርሱ<br />
ዜጎች መካከል የሩቅ ምስራቅ አገሮች ቁጥራቸው<br />
ያይላል፤ ኢንዶኔዥያ፣ ስሪላንካ፣ ፊሊፒንስ፣<br />
ሕንድ፣ ፓኪስታን፣ ባንግላዴሽ…። የኢትዮጵያውያኑ<br />
ቁጥርም ከፍተኛ ሲሆን በተለይ የቅርብ መረጃዎች<br />
እንደሚያሳዩት ከሆነ እንደ አትሌቲክሱ ሁሉ በቤት<br />
ሠራተኝነት ፍልሰትም የኢትዮጵያውያኑ ቁጥር<br />
በልጠው ኬኒያዊያን በአገራቱ እየተነሰነሱ ነው፡፡<br />
ሸዋዬ ሞላ፣<br />
ዜጎች ለምን ይፈልሳሉ?<br />
የኢትዮጵያ ሕገ-<strong>መንግስት</strong>፣ አንቀጽ 32 የመዘዋወር<br />
ነፃነት በሚል ርዕስ ንዑስ አንቀፅ አንድ እና ሁለት<br />
ላይ በሰፈረው መሠረት፣ ‹‹ማንኛውም ኢትዮጵያዊ<br />
በሕጋዊ መንገድ የመዘዋወር፣ በፈለገው ጊዜ ከአገር<br />
የመውጣት ነፃነት እና ወደ አገሩ የመመለስ መብት<br />
እንዳለው ይደነግጋል።<br />
ብዙ ዜጎች ግን ይህን መብት በመጠቀም ወደ<br />
ሌላ አገር የሚሻገሩት በሰራተኛና ማሕበራዊ ጉዳይ<br />
ሚኒስቴር አማካኝነት ዋስትና ተገብቶላቸው እና<br />
ዓለም አቀፋዊ ሕግጋትን በተከተለ ሁኔታ አይደለም።<br />
በዋነኛነት ችግር የሚያጋጥማቸውም ሕገ-ወጥ<br />
ተጓዦቹ መሆኑን የውጪ ጉዳይ ቃል አቀባይ<br />
የሆኑት አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ይገልፃሉ። ‹‹ትልቅ<br />
ይህቺ ኢንዶኔዥያዊት የቤት ሠራተኛ በ50ዎቹ የእድሜ ክልል በሚገኙ አሰሪዋ በተፈፀመባት<br />
ችግር የሚያጋጥማቸው በሕገ-ወጥ ደላላ አማካኝነት<br />
ከባድ ድብደባ ከሸዋዬ የማይተናነስ ጉዳት ደርሶባት መዲና ውስጥ በሚገኝ ፍ/ቤት ቀርባ<br />
ባዶ ተስፋ ተሞልተው የሚሄዱ ናቸው። አሰሪዎቹም<br />
አሰሪዋ ላይ ፍርድ ከመሰጠቱም በላይ የኢንዶኔዥያ እና የሳውዲ አረቢያ የሠራተኛ አቅርቦት<br />
ምንም ዋስትና እንደሌላቸው ስለሚያውቁ እጃቸው<br />
ስምምነት እንዲቋረጥ አንዱ ምክንያት ሆኗል። አገራችን ከዚህ ምን ትማራለች?<br />
ለገባው ኢትዮጵያዊ ደህንነት አይጨነቁም›› ሲሉ<br />
ሕጋዊ ጉዞ አለመኖሩ ችግሩን እንደሚያጎላው<br />
ከአሰራር ጋር በሚፈጠር አለመግባባት የሰብዓዊ<br />
ቢያሰምሩበትም ከቦታው የሚወጡ መረጃዎች<br />
ተልዕኮውን በደንብ ያልተረዳ ነው›› ይላሉ።<br />
መብት ጥሰቶች በሁሉም አገር ሰራተኞች ላይ<br />
የሚጠቁሙት በሕጋዊ ኤጀንሲ በኩል በሰራተኛ እና<br />
በተለያየ ወቅት እንደ አሜሪካ ያሉ የበለፀጉ አገራት<br />
የሚፈፀም ቢሆንም ሌሎች አገራት ለዜጎቻቸው<br />
ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ‹‹ታውቀው›› ድንበር<br />
በሌላ አገር የሚገኙ ዜጎቻቸው በጥፋት ተሳታፊ ቢሆኑ<br />
ከለላ እንደሚቆሙ በምርመራ ጋዜጠኝነት መረጃ<br />
የሚሻገሩትም ከጣጣ ነፃ አለመሆናቸውን ነው።<br />
እንኳን ሰብዓዊ መብታቸው እንዳይደፈር እንቅልፍ<br />
የሰበሰበው የጀርመን ድምፅ ዘጋቢ ነብዩ ሲራክ<br />
ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ይህ ችግር መኖሩን በሳውዲ<br />
አለመተኛታቸው አርያነት ያደርጋቸዋል። [ሕግን<br />
ያስረዳል። ‹‹የተጠቀሱት አገር ዜጎች ችግር<br />
አረቢያ ታዝቧል። ‹‹በሥራ እና አሰሪ ኤጀንሲዎች<br />
የተላለፈ ኢ-ሰብዓዊ አያያዝ እንዲኖረው የሚደነግግ<br />
ከመፈጠሩ አስቀድሞም ሆነ ከተፈጠረ በኋላ<br />
የሚላኩ የኮንትራት ሰራተኞች ተቀባይ አጥተው<br />
ሕግ ስለሌለ] በኢትዮጵያ ውስጥም ሆነ በውጪ<br />
በ<strong>መንግስት</strong> ተወካዮቻቸው አማካኝነት ክትትልና<br />
ለሳምንታት ሲንገላቱ ተመልክቻለሁ። አሰሪዎቻቸውን<br />
አገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ደህንነት እና ዋስትና<br />
ጥበቃ ይደረግላቸዋል። ሲበደሉ ይብዛም ይነስ ፍትህን<br />
አግኝተው ወደ ሥራ የተሰማሩትም በምግብ አቅርቦት፣<br />
እንዲረጋገጥ የኢትዮጵያ <strong>መንግስት</strong> የተቻለውን<br />
ሳያገኙ የሚቀሩበት አጋጣሚ አናሳ ነው›› የሚለው<br />
በሥራ ብዛትና ለተመሳሳይ ችግሮች በመዳረጋቸው<br />
ማድረግ እንዳለበት የሚጠቅሱት ዶ/ር ሼክስፒር<br />
ጋዜጠኛው በቅርቡ አንዲት ኢንዶኔዥያዊት የቤት<br />
አሁን ድረስ ስልክ እየደወሉ የሚገልፁልኝ እህቶች<br />
የአሜሪካን ተሞክሮ በመጥቀስ <strong>መንግስት</strong> እንዲነቃ<br />
ሰራተኛ በ50ዎቹ የእድሜ ክልል በሚገኙ አሰሪዋ<br />
አጋጥመውኛል›› የሚለው ነብዩ የቅርብ ጊዜ<br />
ይጠይቃሉ። ‹‹በአሜሪካ ሴናተሮች እና የኮንግረስ<br />
በተፈፀመባት ከባድ ድብደባ ከሸዋዬ የማይተናነስ<br />
ተሞክሮው ይህን ሀቅ ፍንትው አድርጎ እንደሚገልፅ<br />
አባላት የዜጎች መብቶች፣ ደህንነትና ዋስትናን<br />
ጉዳት ደርሶባት እንደነበር ገልጾ፣ ‹‹ጉዳዩ መዲና<br />
ማሳያውን ይዘረዝራል። ‹‹ከጥቂት ሳምንታት በፊት<br />
ለማረጋገጥ ከሌላ አገር ጋር አብረው በመስራት<br />
ውስጥ በሚገኝ ፍ/ቤት ቀርቦ አሰሪዋ ላይ ፍርድ<br />
ያነጋገርኳት እህት ሳውዲ አረቢያ ጅዳ ለአንድ ሳምንት<br />
ንቁ ተሳትፎ ያደረጋሉ። ይህንንም በተደጋጋሚ<br />
ከመሰጠቱም በላይ የኢንዶኔዥያ እና የሳውዲ<br />
በማቆያ/ እስር ቤት ሆና አሰሪዎቿን ስትጠባበቅ<br />
ተመልክተናል። በእህቶቻችን ላይ የደረሰው በአንድ<br />
አረቢያ የሰራተኛ አቅርቦት ስምምነት እንዲቋረጥ<br />
ብርድ መትቷት የከፋ የጤና መታወክ ገጥሟታል።<br />
አሜሪካዊ ዜጋ ላይ ተፈፅሞ ከሆነ፣ የአሜሪካ<br />
ምክንያት ከሆኑ ጉዳዩች መካከል አንዱ ሆኗል›› ሲል<br />
አሰሪዎቿም መጥተው ቢወስዷትም ግማሽ ጎኗ<br />
<strong>መንግስት</strong> ጉዳቱን በቀላሉ አይመለከተውም። ለዜጋው<br />
በምሳሌነት በሳውዲ አረቢያ መገናኛ ብዙሃን ሳይቀር<br />
‹‹ሽባ›› የመሆን የጤና እክል እንዳጋጠማት በተማፅኖ<br />
ፍትህን ለማሰጠት የተቻለውን ሁሉ ያደርጋል።››<br />
ስለተዘገበው ጉዳይ ተናግሯል፤ ጉዳዩ ኢትዮጵያውያን<br />
ገልፃልኛለች። ከእሷ ባገኘሁት አድራሻ መሠረት<br />
ላይ ሲያጠነጥን ግን ትኩረቱ የተገላቢጦሽ እንደሆነ<br />
አዲስ አበባ ወደሚገኘው ያመጣት የሥራ አገናኝ<br />
የዲፕሎማቶች ግንዛቤ ሲመዘን<br />
በመጠቆም።<br />
ኤጀንሲ በተደጋጋሚ ብደውልም ስልኩ አይመልስም።<br />
የኢትዮጵያ <strong>መንግስት</strong> በአረቡ ዓለም ላሉት ዜጎቹ<br />
ነዋሪነታቸውን በአሜሪካ ሲያትል ከተማ ያደረጉት<br />
ወደ አገሬ የምገባበትን መንገድ ፈልጉልኝ ስትል<br />
ከለላና ጥበቃ ስለማድረጉ ችግሮች በተነሱ ቁጥር<br />
የሕግ ባለሙያው ዶ/ር ሼክስፒር ፈይሳም የኢትዮጵያ<br />
የድረሱልኝ ጥሪዋን ማሰማቷን በጀርመን ሬዲዮ ላይ<br />
ሁሌም ጥያቄ ያጭራል። በመካከለኛው ምስራቅ<br />
<strong>መንግስት</strong> ከፍተኛ ትኩረት የሚያሻው ጉዳይ ላይ<br />
አቅርቤዋለሁ›› ይላል።<br />
የጀርመን ድምፅ ሬዲዮ ዘጋቢ የሆነው ነቢዩ ሲራክ<br />
ቸልታ እንደመረጠ ከሚያምኑት ውስጥ ናቸው።<br />
ዜጎች በሕጋዊ መንገድ በሠራተኛ እና አሰሪዎች<br />
ጉዳዩን አስመልክቶ ለአውራምባ ታይምስ በሰጠው<br />
<strong>መንግስት</strong> አስቀድሞ ዲፕሎማሲያዊ፣ ፖለቲካዊና<br />
አማካኝነት ስራ አግኘተው ወደ አገራቱ ቢላኩም<br />
ምስክርነት፣ በአካባቢው ያሉ የኢትዮጵያ <strong>መንግስት</strong><br />
ኢኮኖሚያዊ ግንኙነቶቹን ስለሚያስብ በቸልታ<br />
ችግር ሲደርስባቸው የሚያማክሯቸውን የኤምባሲ<br />
ተወካይ ዲፕሎማቶች የዜጎችን መብት ለማስከበር<br />
ለመዋጡ በምክንያትነት ያቀርቡታል። ‹‹<strong>መንግስት</strong><br />
እና ቆንስላ መስሪያ ቤቶች እንዳይገናኙ ያደርጓቸዋል።<br />
እርባና ያለው ሥራ ባለመሥራታቸው እንደሚወቀሱ<br />
ለዜጎቹ የጥበቃና የመቆርቆር ሚናውን ከተወጣ<br />
እንደውም የአሰሪዎች የሴራ ትብታብ የሚጀምረው<br />
ያረጋግጣል።<br />
ያለውን የጠቀስኳቸውን ግንኙነቶች ማጣትን<br />
ኤምባሲ እና ቆንስላ መ/ቤቶችን እንዳያውቁ በማድረግ<br />
‹‹በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ባሉባቸው አረብ<br />
ያስከትልበታል። ለዚህም ነው በተደጋጋሚ ጊዜ ዜጎቹ<br />
ነው፤ በተለይ ሕገ-ወጥ ተጓዦችን።<br />
ሀገራት የሚላኩት በጣት የሚቆጠሩ ዲፕሎማቶች<br />
ሰብዓዊ ባልሆኑ በችግር ውስጥ ሲሰቃዩ ዝምታን<br />
ሴቶቹ በሥራ ቦታ ላይ መድረሳቸውን ‹‹ሃሎ››<br />
በዲፕሎማሲ የጠለቀ ዕውቀት የሌላቸውና<br />
የሚመርጠው›› ይላሉ።<br />
ይበሉ እንጂ ስለ አሰሪዎቻቸው ፀባይ፣ የስራቸው<br />
የሚላኩባቸውን ሐገራት ህግና ስርዓቶች ከራሳቸው<br />
የኢትዮጵያን ልማት፣ ዴሞክራሲና ሰላም ሊደግፉ<br />
አይነት፣ ተገቢ መጠለያ እና ሕክምና ስለማግኘታቸው<br />
ጋር በቶሎ አዋህደው መሥራት ስለሚከብዳቸው<br />
የሚችሉ ስራዎችን መስራት፣ ኢንቨስትመንት እና<br />
በወል አይታወቅም። ይህንን መሰል የችግሮች መነባበር<br />
የዜጎችን መብት ማስከበርም ሆነ ችግሮች ሲከሰቱ<br />
ቱሪዝም መሳብ፣ የውጪ ገበያ ማፈላለግ ብቻ<br />
የተሰላቹ ሰራተኞች በተስፋ መቁረጥ ወንጀል ውስጥ<br />
በአፋጣኝ ለመፍታት ይቸገራሉ›› የሚለው ነቢዩ፣<br />
ሳይሆን የዜጎችን መብት ማስጠበቅም የውጪ ጉዳይ<br />
ተዘፍቀው ይታያሉ። የዜጎች መብት ጠባቂው፤<br />
ያስተዋላቸውን ችግሮች ዘርዝሯል።<br />
ሚኒስቴር በኤምባሲዎች አማካኝነት የሚከውነው<br />
<strong>መንግስት</strong> ተቀዳሚ ግዴታውን መወጣት ያለበት ይህ<br />
በቅርቡ በኩዌት ከ400 በላይ የኮንትራንት<br />
ተልዕኮ እንደሆነ የሚናገሩት አምባሳደር ዲና<br />
ሁሉ ከመከሰቱ በፊት መሆኑን ዶ/ር ሼክስፒር ፈይሳ<br />
ሠራተኞች በአሠሪዎቻቸው የሚደርስባቸውን<br />
ሙፍቲ፣ ‹‹ዋነኛው የስራችን ትኩረት ኢኮኖሚክ<br />
ያሰምሩበታል።<br />
ድብደባና በቂ ምግብ አለመኖር፣ ለአንድ ሥራ ሄደው<br />
ዲፕሎማሲ ነው። ይህ ለማሳካት ውጪ የሚገኙ<br />
ዓለም ለሁሉም ዓለማቀፋዊ ቤት መሆኗ<br />
በተለያዩ ቤቶች እንዲሠሩ በመደረጉ የተፈጠረባቸውን<br />
ኢትዮጵያውያንን መብት ማስከበር የግድ ነው።<br />
ተፈጥሯዊ ሂደት የፈጠረው መሆኑን የሚገልፁት ‹የኢትዮጵያን <strong>መንግስት</strong> ኃላፊነት እየተወጣ ነው›<br />
ባለበት አገር ሆኖ ‘እዚህ ያለሁት ኢንቨስተር ለመሳብ<br />
የመድረክ ምክትል ሊቀ መንበር እና የህዝብ ግንኙነት ተብሎ የሚሞካሸው ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ<br />
ብቻ ነው’ የሚል ዲፕሎማት ካለ ‹‹ያልገባው እና<br />
በ ገፅ 22
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />
መልካም ዓዲስ ዓመት<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
5
6 ኮመንትሪ<br />
በታዲዎስ ጌታሁን<br />
“<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
“እኚህ ነበሩ”<br />
... የሰው ልጅ<br />
የሚሞተው፣ ዕድሜው<br />
ሲንዘላዘል አብሮ የሚዝረከረክ<br />
እንቅስቃሴውን ሥርዓት ለማስያዝ<br />
የሚደክሙ ወዳጅ ዘዶቹን ሥራ<br />
አስፈትቶ (ያልቀናቸው) በረሀብ<br />
እንዳይገላቸው ‹‹ይመስለኛል››።<br />
አንድ ሰው ወይም<br />
ደግሞ እኔ ብሞት ይህቺ ሀገር<br />
የሚጎድልባት ገፀ-በረከት አለ<br />
ብዬ አላምንም። ይኸን ስሜት<br />
የማይሰጥ ጉዳይ ከማመን ይልቅ፣<br />
የአንድ ግለሰብ ቦርጭ ተደርምሶ/<br />
ፈንድቶ አንዲት ቀበሌን አጥለቀለቀ<br />
የሚል “ስጥ እንግዲህ” ወሬ ባምን<br />
ይቀለኛል።<br />
በእርግጥ አልጋ<br />
ላይ ሲውሉ ቀርቶ ሲያስነጥሱ<br />
እንኳን ክፉ እንዳይገጥማቸው<br />
የምንንሰፈሰፍላቸው አያሌ የሰው<br />
ሰው ኢትዮጵያውያን አሉ።<br />
ሰዎች፣ መቼ<br />
እንደሚሞቱ አይወቁ እንጂ<br />
ከሚያውቋቸው ቀናት በአንዱ<br />
እንደሚሞቱ ያውቃሉ።<br />
እንደሚሞቱ የሚያውቁ ብዙዎች<br />
(ሁሉም) ሲሆኑ፣ “ሞታቸውን”<br />
ጠቀም ላለ ጉዳይ (ለሀገር እና<br />
ለወገን) የሚያውሉ ግን በጣም<br />
ጥቂት ናቸው።<br />
ሙቅ ሲጠጣ ‘ትን’<br />
ብሎት የሞተም ሆነ ለነፃነት<br />
(፬)<br />
/መጠቅለያ/<br />
ሰላም ለእናንተ ለአንባቢዎቼ!<br />
ለሶሰት ሳምንታት የዛሬው<br />
ርዕሳችን መቆያ ሆኖን ሰንብቷል።<br />
ዛሬ መጠቅለያ ያክል ይህንን<br />
እፀፋለሁ።<br />
ውድ አንባቢያን በሁለተኛው<br />
ክፍል ጽሑፍ እንዳልኩት ይህ<br />
ጽሑፍ እንደተናጋሪ እንጅ እንደ<br />
አጥኚ አለዚያም እንደተመራማሪ<br />
የሰራሁት አይደለም። በሌላ<br />
አባባል እንደ አንድ ፀሐፊ<br />
እያየሁና እየሰማሁ ከታዘብኳቸው<br />
ነገሮች እናንተም ከምታዩአቸውና<br />
ከምትሰሟቸው ተነስቼ ነው<br />
የፃፍኩት።<br />
መሰንበቻዬን ሕፃን፣ ወጣት፣<br />
ምሁር፣ ካህን፣ መሪ፣ ሰራተኛ<br />
እያልኩ በርዕስ እየከፋፈልኩ<br />
በአንድ የሞራል ኪሳራ መገለጫው<br />
በሆነ ሰው የሚታዩ ባህሪያትን<br />
ገልጫለሁ። ለመሆኑ ግን ለዚህ<br />
ሁሉ የሞራል ዝቅጠት ተጠያቂው<br />
ማነው? እኔ እንዲህ ይማሰኛል።<br />
ሰዎች በጎ አእምሯዊ<br />
አስተሳሰብን ማዳበር ይችሉ ዘንድ<br />
ትልቁን ሚና የሚወስደው መማር<br />
ነው። መማር ደግሞ ደብተር<br />
ይዞ ትምህርት ቤት መመላለስን<br />
ብቻ ሳይሆን የሚገልፀው፣<br />
ከሃይማኖት /ከእምነት ተቋም/<br />
ከሰፈር፣ ከቤተሰብ፣ ከአካባቢ፣<br />
ሲፋለም የሞተ አንድ ዓይነት<br />
ስም ነው የሚሰጠው - ‘ሞተ’<br />
የሚል። ነገር ግን፣ ሞቱን<br />
ለአንድ ብር ገመድ አሳልፎ<br />
የሰጠ ሰውና ለማኅበረሰብ ነፃነት<br />
የሰጠ፣ በታሪክም ሆነ በትውልድ፣<br />
በሰማይም ሆነ በምድር ‘እኩል’<br />
ክብር አያገኝም።<br />
… ሰዎች፣ ኑሮ<br />
የሚያቀርብላቸውን ጥያቄ<br />
ለመመለስ ብዙ ቦታዎች ይገባሉ<br />
- መሥሪያ ቤቶችን ጨምሮ።<br />
አንድ ሰው ወይም ባለጉዳይ<br />
ከመንግሥትም ሆነ ከግል<br />
መሥሪያ ቤቶች የሚሰጠው<br />
ምላሽ የማያሳምነው ከሆነ<br />
‘ለምን?’ ብሎ መጠየቅ አለበት።<br />
አለበለዚያ በተጠያቂነትና በግል<br />
ፅናት የመገልገል (የመስተናገድ)<br />
መብቱን በገዛ ፈቃዱ አሳልፎ<br />
እንደሰጠ ይቆጠራል።<br />
ሁሉም የየራሱን<br />
መብትና ነፃነት በራሱ ጉልበትና<br />
ወዝ ማስከበር አለበት። ተጠያቂነት<br />
በጎደለው አሰራር መብቱን የተቀማ<br />
ኢትዮጵያዊ፣ የተነጠቀውን ነፃነት<br />
አልያም መብት የሚያስመልስለት<br />
የፈረንሳይ ፓርላማ ሳይሆን ራሱ<br />
ኢትዮጵያዊው ባለጉዳይ ነው።<br />
እያንዳንዱ ሰው የየራሱ<br />
ነፃ አውጪ መሆን አለበት። ለእኔ<br />
ነፃነት ወይም እኔ ነፃ እንድወጣ፣<br />
በዬትም ሀገር ያለፈው ትውልድ ድል የተቀዳጀበትን ስልት አሊያም ተነሳሽነት ይሔ<br />
ትውልድ መድገም ካቃተው ቀስ በቀስ የታሪክ ሞት ይከሰታል። የአንድ ተራ ሰው ሞት፣<br />
ከቤተሰቡና ወዳጆቹ አልፎ ለብሔራዊ ሐዘን የሚበቃበት ጉልበት የለውም። የታሪክ ሞት<br />
ግን ከሀገር አልፎ ጎረቤት ሀገሮችን ጨምር ለሐዘን ይዳርጋል።<br />
በደሳለኝ ስዩም<br />
“<br />
ከባህል፣ ከኑሮ፣ ከስልጣኔ ደረጃ<br />
ወዘተ የሚገኙ ትምህርቶችንም<br />
ይገልፃል።<br />
እንግዲህ ትምህርት የንቃተ-<br />
ኅሊና እና የበጎ አስተሳሰብ ምንጭ<br />
መሆኑን ከተስማማን፣ የትምህርት<br />
ምንጭም ከላይ የዘረዘርነው ሁሉ<br />
መሆኑን ከተስማማን ነገራችን<br />
ያለው “ከትምህርት” ይሆናል<br />
ማለት ነው።<br />
፩. ባሕላዊ ትምህርት<br />
በመሠረቱ ባህላዊ ትምህርት ስል<br />
የየባህሉ፣ የየሚዛኑ፣ የየሰፈሩ፣<br />
የየሃይማኖቱ ወዘተ ታሪኮች፣<br />
አፈ-ታሪኮች፣ እንቆቅልሾች፣<br />
የልጆች ጨዋታዎች፣ አለባበሶች፣<br />
ሰላምታዎች፣ እንቅስቃሴዎች፣<br />
ዜማዎች ወዘተ ሁሉ<br />
ያጠቃልላል።<br />
አንድ ዜጋ በስብዕና ደረጃ<br />
የተሟላና በአወንታዊነት<br />
የበለፀገ ሞራል መላበስ ይችል<br />
ዘንድ ከመነጨበት ማኅበረሰብ<br />
ውስጥ ያሉ ባህላዊ ትምህርቶች<br />
ያስፈልጉታል። ያለዚያ የማንነት<br />
ቀውሱ ከዚሁ ከልጅነቱ ጀምሮ<br />
ይጠናወታል።<br />
በእያንዳንዱ ባህላዊ ትምህርት<br />
ውስጥ እንዴት መልካም ስብዕናን<br />
ማጎልበት እንደሚችል በቀጥታም<br />
ይሁን በተዘዋዋሪ ትምህርቶችን<br />
ያገኛል።<br />
እነዚህን ባህላዊ ትምህርቶች<br />
በነፃነት አግኝቶ የማደግ አጋጣሚው<br />
በጠበበ ቁጥር ማን ነህ? ከየት<br />
የሌላ (ሀገር) ሰው ደም የሚፈስ<br />
አሊያም ጥይት የሚፈነዳ ከሆነ<br />
የነፃነት ጣዕም ሳይገባኝ ነው<br />
የምኖረው።<br />
በራሴ ፍላጎትና<br />
ተነሳሽነት ነፃነቴን እና መብቴን<br />
ካልጨበጥኩ፣ ሌላ ወገን<br />
ያስጨበጠኝን ነፃነት በቀላሉ<br />
ለማንም አሳልፌ የምሰጥ ተራ<br />
ሰው እሆናለሁ። ምክንያቱም፣<br />
ለነፃነቴ ዋጋም ሆነ ግብር<br />
አልከፈልኩበትምና።<br />
ሌሎች በልካቸው<br />
አስጠብበው የሚሰጡንን<br />
የነፃነት ካባ መልበስ፣ ሕይወት<br />
በምትፈቅደው አቅጣጫ ሁሉ<br />
አለመንቀሳቀስ ማለት ነው።<br />
የቻይና የነፃነት ካባ፣ ለኢትዮጵያ<br />
ይጠባታል ወይም ያጥራታል<br />
አሊያም ይሰፋታል። ስለዚህ ካባው<br />
የተመጣጠነ እንዲሆን ሲንጀሩ<br />
(ፍላጎቱና ተነሳሽነቱ) የራስ መሆን<br />
አለበት።<br />
ዜጎች፣ ራሳቸውን<br />
ነፃ ማውጣት እንደሚችሉ<br />
ካመኑ፣ ለታመነው የነፃነት<br />
መጀመሪያ የራሳቸውን ፊሽካ<br />
ይነፋሉ፤ አሊያም ነፃነታቸውን<br />
ለቀሙት ገዢዎቻቸው ወደው<br />
ሳይሆን ተገደው (ተረግጠው)፣<br />
ለማያምኑበት ሕግ ታምነው<br />
ይኖራሉ።<br />
የነፃነት ፀሐይ እንደ<br />
ተፈጥሮ ፀሐይ በምስራቅ በኩል<br />
ብቻ አትገኝም። የሰው ልጆች<br />
ባሉበት በአራቱም አቅጣጫዎች<br />
አለች። ነፃ መሆን የሚፈልጉ<br />
ሰዎች ፀሐይቱን የማያወጧት<br />
ከሆነ፣ ለረዥም ዘመናት በጨለማ<br />
ውስጥ ለመኖር በራሳቸው ላይ<br />
እንደፈረዱ ማወቅ አለባቸው።<br />
ተፈጥሮ በነፃ<br />
የሰጠችውን ነፃነቱንና መብቱን<br />
በየስርቻው ለማርመጥመጥ<br />
ነህ? ወዴት ነህ? ወዘተ ለሚሉ<br />
ጥያቄዎች ቀጥተኛና አወንታዊ<br />
መልስ መስጠት የማይችል ብኩን<br />
ዜጋ እየበረከተ ይመጣል።<br />
በዚህ ደረጃ የምስራቅ ሀገራት<br />
/ቻይና፣ ጃፓን፣ ህንድ/ በጎ<br />
ምሳሌ መሆን የሚችሉ<br />
ይመስለኛል። ዘመናቸው<br />
እየረቀቀ፣ ቴክኖሎጂያቸው<br />
እየመጠቀ ቢመጣም እንኳ ባህላዊ<br />
ትምህርቶቻቸው እንደ ተጠበቁ<br />
የልጆች ማሳደጊያ ናቸው።<br />
ሰላምታ፣ አለባበስ፣ አመጋገብ፣<br />
ስፖርታዊ እንቅስቃሴአቸው ሁሉ<br />
ለዚህ ማሳያ ሊሆን ይችላል።<br />
ባንፃሩ ገና ታድጋለች ብለን<br />
በመንጠብቃት ሀገራችን ግብረ-ወጥ<br />
የሆኑ የሰለጠኑ የሚመስሉ ግን<br />
የሰየጠኑ ልማዶች እንደፋሽስት<br />
ወረዋት ባህላዊ ትምህርቶቿ<br />
የአላዋቂነት መገለጫ ሆነው<br />
መቆጠር ጀምረዋል።<br />
እስኪ አዲስ አበባ ውስጥ ለልጆቹ<br />
ኢትዮጵያዊ ተረት እየነገረ ባህሉን<br />
እያስተማረ ልጀቹን የሚያሳድግ<br />
ወላጅ ምንያክል ይሆናል?<br />
መሠረታዊ እና ታላቁ የሞራል<br />
ቀውስ ከዚህ ይጀምራል።<br />
፪. ዘመናዊ ትምህርት<br />
ባለንበት የሉላዊነት ዘመን /<br />
ዘመነ ግሎባላይዜሽን የዘመናዊ<br />
ትምህርት መስፋፋት የስልጣኔና<br />
የሳይንስ ምንጭ ተደርጎ<br />
ይወሰዳል። በመሆኑም ይህንን<br />
ዘመናዊ ትምህርት ለማስፋፋት<br />
ብዙ ጥረት ይደረጋል።<br />
ዘመናዊ ትምህርት ብዙ አማራጭ<br />
የኑሮ ዘዴዎችን፣ አቋርጭ የኑሮ<br />
መስመሮችን ውበትንና ስልትን<br />
የተላበሱ የአኗኗር ልማዶችን<br />
ለማበጀት ይጠቅማል።<br />
“ሰው ማኅበራዊ እንስሳ ነው”<br />
የሚለውን ፍቱንነቱ ያልተረጋገጠ<br />
አባባል ውድቅ ሊያደርጉ የሚችሉ<br />
ፍቱን ስልጣኔዎችን ያመጣል -<br />
ዘመናዊ ትምህርት።<br />
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />
መልካም ዓዲስ ዓመት<br />
የሚነሳሳበትን ኃይል በመመከት<br />
ራሱን በራሱ ነፃ ማውጣት አለበት<br />
- ማንኛውም ዜጋ።<br />
አንድ ኢትዮጵያዊ<br />
ሰው ኢትዮጵያ ውስጥ ያገኘውን<br />
መብትና ነፃነት ማስከበር ያለበት<br />
በኢትዮጵያ መፈክር እንጂ በራስ<br />
ወዳዶች የጥቀመኝ ልጥቀምህ<br />
ፖሊሲ አይደለም።<br />
ኢትዮጵያውያን፣ በሰበብ<br />
አስባቡ በፖለቲካ ደዌ የሚገመት<br />
ነፃነታቸውን የሚያክሙላቸው<br />
የባንኮክ ስፔሻሊስቶች አይደሉም።<br />
የስኳር ታማሚ ወደ ታይላንድ<br />
ሊላክ ይችላል። የነፃነት በሽተኛ<br />
(በቂ ነፃነት የሌለው) ኢትዮጵያዊ<br />
ሪፈር የሚያደረገው ግን ወደ<br />
አድዋ ተራራ ነው።<br />
በተራራው ስር<br />
የተከናወነው የነፃነት ተጋድሎ<br />
የልብ ልብ ስለሚሰጥ፣ ዛሬ<br />
ነፃነት የጎደላቸው ወይም<br />
ነፃነታቸውን የተቀሙ ዜጎች<br />
ያለፈው ታሪካቸውን ሊጠቀሙበት<br />
ይችላሉ። የትላንት የድል ታሪኮች<br />
ተመዝግበው የሚቀመጡት የዛሬ<br />
ሰዎች ከሚደነቀርባቸው ፈተናዎች<br />
የሚያመልጡበትን መንገድ<br />
ለማመላከት ጭምር ነው።<br />
ሰዎች ነፃነት አልባ<br />
የሚሆኑት፣ ፖለቲካ ጨጓራ<br />
በሽታ የሚሸመትበት የህመም ገበያ<br />
ሲሆን ነው። የገዢዎች የፖለቲካ<br />
አካሔድ መዳረሻውና ዓላማው<br />
ሀገርን ወደተሻለ አንድነትና<br />
ዕድገት ማድረስ ከሆነ ማንም ሰው<br />
ፈሪ አይሆንም። ደግሞም ፖለቲካ<br />
ሀገርን ከማልማት ውጭ ሌላ<br />
ዓላማ ሊኖረው አይገባም።<br />
አንዳንድ ጊዜ፣<br />
የፖለቲካ ትርጉም ያልገባው<br />
ፖለቲከኛ በልጅነቱ የመታውን<br />
ጉልቤ ዛሬ አስታውሶ ለማሰር፣<br />
ሥልጣኑን ተጠቅሞ አፈንጋጭ<br />
ባንፃሩ ቅደም ተከተሉ ተጠብቆ<br />
አለማና ግቡ ተለይቶ ግልፅና<br />
ሊዳሰስ የሚችል ሆኖ ትምህርቱ<br />
መስፋፋት ካልቻለ በተቀራኒው<br />
ኪሳራን ውድቀትን ሊያመጣ<br />
እንደሚችል የታመነ ነው።<br />
በትምህርት ስርአት ውስጥ<br />
የመጀሪያም የመጨረሻም አላማና<br />
ግብ ቢኖር የሰውን ልጅ አእምሮ<br />
ማልማት እንጂ ቁስ አካላዊነትን<br />
ማስፋፋት አይደለም።<br />
የዘመናዊ ትምህርት አላማ ሊሆን<br />
የሚገባው በጎ ስብዕና መላበስን<br />
ሰብአዊነትን ርህራሄን አሳቢነትን<br />
ቅንነትን በጠቅላላው በሞራል<br />
መበልፀግን ማስቻል ነው።<br />
ገንዘብ ማግኘት መኪና መግዛት<br />
ቤት መስራት ጠፈር ላይ<br />
መዝናናት ወዘተ በተደራቢነት<br />
ማለትም የሞራል ግንባታው<br />
እየተካሄደ ሞራሉ የበለፀገ ሰው<br />
የሚሰራው እንጂ እንደመጀመሪያ<br />
አላማ ተደርጎ በዘመናዊ ትምህርት<br />
ውስጥ ከተቀመጠ ጥፋቱ ብዙ<br />
ነው።<br />
ቁጥር መደመር መቀነስ የጦር<br />
ስትራቴጅ መቀየስ የንድፈ ሐሳቦችን<br />
ሽኩቻ መቀላቀል ገንዘብን ማጋበስ<br />
ቅድሚያ አለማዎቹ ከሆኑ ዘመናዊ<br />
ትምህርት የሚያፈራው ሞራሉ<br />
የዘቀጠ ዜጋ ብቻ ይሆናል። ራስ<br />
ወዳድነት ጨካኝነት የሀገር ፍቅር<br />
ማጣት ወዘተ ይነግሳሉ።<br />
በመሆኑም ከእያንዳንዱ የሳይንስና<br />
የቁጥር ትምህርት በቅድሚያ<br />
ግብረ-ገባዊነት (ኤቲካል) ሥነ-<br />
ልቦናዊ /ሳይኮሎጂካል/ ትህርቶች<br />
ቅድሚያ ሊሰጣቸው ይገባል።<br />
፫. ሃይማኖታዊ<br />
ትምህርቶች<br />
የሰው ልጅ በተፈጥሮው<br />
የአማኝነት ባህርይን የታለበሰ<br />
ነው። በዚህ ማመኑ ውስጥ ያሉ<br />
ስርዓቶችን ህገ ደንቦችን እና<br />
የአኗኗር ዘይቤዎችን ማክበር<br />
ህግ የሚያወጣ ይመስለኛል።<br />
አንዲት ሀገር ያለ<br />
በቂ ነፃነት መኖር ትችላለች<br />
የሚል ፖለቲከኛ በተዘዋዋሪ፣<br />
ያለ ፓራሹት ከአውሮፕላን ላይ<br />
መዝለል እችላለሁ እያለ መሆኑን<br />
ማወቅ አለበት።<br />
በተለይ፣ ባለፉት<br />
ዘመናት ለነፃነትና ለመብት ትልቅ<br />
ቦታ ይሰጡ የነበሩ ህዝቦች፣ ዛሬ<br />
ዛሬ ነፃነታቸው አጣብቂኝ ውስጥ<br />
ሲገባ ‹ዝም› ካሉ ከታሪካቸው<br />
ጋር እየተጣሉ ነው ማለት ነው።<br />
አሊያም የነፃነታቸውን ታሪክ<br />
በገዛ ፈቃዳቸው ገንዘብ ለመቅበር<br />
እየተዘጋጁ ነው።<br />
በዬትም ሀገር ያለፈው<br />
ትውልድ ድል የተቀዳጀበትን ስልት<br />
አሊያም ተነሳሽነት ይሔ ትውልድ<br />
መድገም ካቃተው ቀስ በቀስ የታሪክ<br />
ሞት ይከሰታል። የአንድ ተራ ሰው<br />
ሞት፣ ከቤተሰቡና ወዳጆቹ አልፎ<br />
ለብሔራዊ ሐዘን የሚበቃበት<br />
ጉልበት የለውም። የታሪክ ሞት<br />
ግን ከሀገር አልፎ ጎረቤት ሀገሮችን<br />
ጨምር ለሐዘን ይዳርጋል።<br />
ምክንያቱም ብዙ ሀገሮች ነፃነት<br />
ያገኙት ከጎረቤቶቻቸው የነፃነት<br />
ታሪክና እንቅስቃሴ ልምድ ወስደው<br />
ነው።<br />
ዜጎች፣ በየወቅቱ<br />
ለሚያስመዘግቡት የነፃነት ድል<br />
ሻማ ሲያበሩ ደስ ይላል። ነገር<br />
ግን ነፃ መሆን አቅቷቸው ያለፈው<br />
ወገናቸው ያስመዘገበውን ድል<br />
ለመዘከር ‹ብቻ› ሻማ የሚያበሩ<br />
ከሆነ ደስ አይልም።<br />
አንድ ትውልድ በገነባው<br />
የታሪክና የድል ማማ ላይ ሰላሳና<br />
አርባ ትውልድ እየወጣ ሊሸልልና<br />
ሊምነሸነሽ አይገባም። ሁሉም<br />
ትውልድ የየራሱን ታሪክና ድል<br />
ማስመዝገብ አለበት። ያለበለዚያ<br />
‹‹የድል ታሪክ ማስመዝገብ<br />
ያቃታቸው ትውልዶች እኚህ<br />
ነበሩ›› ከሚል ጥቅስና የፎቶ<br />
ኤግዚቢሽን የሚያመልጥ ሰው<br />
አይኖርም።<br />
የድል ታሪክ፣ መኪና<br />
በመንዳትና ትላልቅ ቤቶችን<br />
በመስራት የሚከሰት /የሚመዘገብ<br />
የሚመስላቸው ደሀ ሰዎች፣ ሽሮ<br />
እየበሉ ጮማ ታሪክ ማስመዝገብ<br />
እንደሚችሉ ሊያውቁና ሊያምኑ<br />
ይገባል።<br />
ለሞራል ዝቅጠት ተጠያቂው ማን ነው?<br />
<strong>መንግስት</strong> ወይም መንግስታዊ አሰራር በባህላዊና በሃይማኖታዊ<br />
ጉዳዮች መደናገሩ ቀርቶ ይልቁንም ዘመናዊ ትምህርትን ሊሆን<br />
በሚገባው መልኩ ማስፋፋት ከተቻለ ሁሉም ሰላም ይሆናል<br />
ደግሞ ያስደስተዋል።<br />
በዓለም ያሉ ሃይማኖቶች<br />
በዝርዝር ጉዳዮችና በአንዳንድ<br />
መሰረታዊ ነጥቦች ይለያዩ እንጂ<br />
የጋራ መገለጫዎቻቸው የሆኑ ብዙ<br />
ነጥቦች አሉ። ከእነዚህም ውስጥ<br />
ሰላማዊ መሆን፣ ፍቅር መሰጠት፣<br />
ግብረ-ገባዊ መሆን፣ ለደንቦች<br />
መገዛት ወዘተ ይጠቀሳሉ።<br />
የአንድ ዜጋ ሞራል የበለፀገ<br />
ይሆን ዘንደ አስተሳሰቡም<br />
በአወንታዊነት የተቃኘ ይሆን<br />
ዘንድ ሃይማኖታዊ ትምህርቶች<br />
ታላቅ አስተዋጽኦ አላቸው። አንድ<br />
ሀገር፣ የአንድ ሀገር ህዝብ ወይም<br />
የአንድ ሀገር <strong>መንግስት</strong> ከአንድ<br />
ዜጋ የሚፈልጉትን አስተዋፅኦ<br />
ሊያገኙ የሚችሉት ዜጋው<br />
ከመሠረቱ በተስተካከለ የሞራል<br />
መሠረት ላይ የቆመ ሲሆን ነው።<br />
ባንፃሩ ሃይማኖቶች ለእውነታዊነት<br />
ይህንን ያክል ተፅኖ ያላቸው<br />
የመሆናቸውን ያክል ለጥፋትም<br />
ይህንኑ ያክል ተፅኖ ይኖራቸዋል።<br />
መከፋፈልን፣ ዘረኝነትን፣<br />
ወገናዊነትን፣ ግላዊነትን መስበክ<br />
የየሃይማኖቶች የዕለት ከዕለት<br />
ተግባር ከሆነ የዜጎች የሞራል<br />
ኪሳራ ቃላት የማይገልጠው<br />
ይሆናል።<br />
በእርግጥ የአንድ ሀገር ዜጎች<br />
የሞራል ግንባታ ሥርዓቱን ሁሉ<br />
በእጁ የያዘው <strong>መንግስት</strong> ላይ<br />
ይንጠልጠል እንጂ አስተዋጽኦው<br />
የሁሉም ነው።<br />
በመሆኑም <strong>መንግስት</strong> ወይም<br />
መንግስታዊ አሰራር በባህላዊና<br />
በሃይማኖታዊ ጉዳዮች መደናገሩ<br />
ቀርቶ ይልቁንም ዘመናዊ<br />
ትምህርትን ሊሆን በሚገባው<br />
መልኩ ማስፋፋት ከተቻለ ሁሉም<br />
ሰላም ይሆናል።<br />
ሰላም ለእናንተ!
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />
መልካም ዓዲስ ዓመት<br />
በአናንያ ሶሪ<br />
“<br />
በአብርሃም ተስፋዬ<br />
“<br />
ከቀደመው ዘመን አንስቶ<br />
እስካሁን ስለግሪክ ፍልስፍናዎች<br />
ይነገራል። የግሪክ ህዝቦች በክርክርና<br />
በውይይት ከፍተኛ እምነት<br />
እንደነበራቸው ይወሳል። ለዚህም<br />
ይመስላል በርካታ ፍልስፍናዎች<br />
ከምድረ-ግሪክ መነሳታቸው።<br />
የፍልስፍናዎቹ መነሻ ደግሞ እኒሁ<br />
የአመለካከት ልዩነቶች እንደሆኑ<br />
ይታመናል። ናቸውም። በልዩነቶች<br />
ውስጥ የሚፋጭ እውነት ይኖራል።<br />
በልዩነቶች ውስጥ ማመንና ማሳመን<br />
ይኖራል። በልዩነቶች ውስጥ<br />
የሚወጡ የሚወርዱ ጉዳዮች<br />
ይኖራሉ። በዚህ መሀከል ደግሞ<br />
የበሰለ ነገር ይገኛል።<br />
በግሪክ የነበሩ ፈላስፎችም<br />
ታዲያ በአመለካከቶቻቸው ዙሪያ<br />
ይወያዩ ይከራከሩ እንደነበር ይነገራል።<br />
በተለይም ህዝብ ወደተሰበሰበበት<br />
ቦታ በመሄድ አመለካከቶቻቸውን<br />
ያንጸባርቃሉ። እነዚህ አመለካከቶች<br />
በደንብ ይብላላሉ። ህዝቡም<br />
የወደደውን፣ ያመነበትን ይቀበላል።<br />
ለነገሩ እነዚህ<br />
የአመለካከት “አባቶች” ስላመኑበት<br />
አተያይ በአደባባይ በድንጋይ<br />
ተወግረዋል፤ ስለእምነታቸው<br />
በአደባባይ ተሰቅለዋል፤ ተገቢ ነው<br />
ላሉት ምልከታ ከህዝብ መሀከል<br />
እንደ ባዕድ ተቆጥረዋል፤ “የለም!<br />
እንዲህ ነው” ብለው ለማሳመን በጣሩ<br />
“አብደዋል፣ አቅላቸውን ስተዋል”<br />
ተብለዋል፤ ስለአመለካከታቸው<br />
የሚደርስባቸውን አሜን ብለው<br />
ተቀብለዋል።<br />
ትናንት ከትናንት ወዲያ<br />
የተገፉትን የአመለካከት ባለቤቶች፤<br />
ዛሬ የመርህ ሁሉ መነሻ፤ የተግባር<br />
ሁሉ መዳረሻ እነርሱ እንደሆኑ<br />
እናነሳለን። ዓለምም ያወድሳቸዋል።<br />
“እከሌ እንዳለው” እያልን ያን ጊዜ<br />
ህዝቡ ያልተቀበለውን አመለካከት<br />
ለእራሳችን እምነት ማስኬጃ<br />
እንደመጀመሪያ ምዕራፍ አድርገን<br />
እንነሳለን። ዛሬ ላይ ስለበርካቶቹ<br />
ስናነሳም “ከጊዜያቸው ቀድመው<br />
የተፈጠሩ” እስከማለት እንደርሳለን።<br />
ስለኢትዮጵያ ስናነሳ ስለአጼ<br />
ቴዎድሮስ እንደምናነሳው ሁሉ።<br />
እኔ ግን በዚህ<br />
አልስማማም። ማንም ፍጡር<br />
ወደዚህ ምድር በጊዜው ይመጣል።<br />
ለዛውም መምጣት ባለበት ጊዜ።<br />
ባይሆን ኖሮ የግሪክ ፈላስፎችንም፤<br />
ኢትዮጵያውያኑንም ጀግኖች<br />
አናያቸውም ነበር። ለነገሩ<br />
ስለፍልስፍናዎቹ መነሻ ሲነሳ<br />
የፈላስፎቹ አመለካከት ይነሳል።<br />
ክርክራቸው ልዩ ነው። እርስበእርስ<br />
ለመተማመን የማይፈነቅሉት<br />
ድንጋይ የለም። ነገር ሲመረምሩ<br />
ይከርማሉ። ብዙም ነገር ይፈትሻሉ።<br />
ምክንያቱን ለህዝቡ የሚያቀብሉትን<br />
ነገር በቅድሚያ ሊያምኑበት<br />
እንደሚገባ ጠንቅቀው ያውቃሉ።<br />
ይህንን ሳያደርጉ ወደህዝብ /<br />
መድረክ/ ብቅ ማለት የማይታሰብ፣<br />
እንደውርደትም ተደርጎ የሚቆጠር<br />
ነገር ነው። ስለሆነም ከባድ ኃላፊነት<br />
እንዳለባች ያስባሉ። ከዚህ ሁሉ<br />
ዝግጅት በ|ላ ታዲያ የሚሆነው<br />
እንዲሆን ከመድረኩ ብቅ ይላሉ<br />
- የአቴና የድሮ ልጆች። ክብbን<br />
ዳግም ለዘመናት እያስጠሩ ይኸው<br />
ዛሬም ድረስ በየመዛግብቱ ሰፍረው<br />
ይታያሉ። በርካታ ፍልስፍናዎች<br />
ከዚህች የአመለካከት ልዩነቶች<br />
ሲስተናገዱባት ከነበረች ምድር ከተፍ<br />
ብለዋል።<br />
በኢትዮጵያም በርካቶች<br />
ስለአመለካከታቸው ብዙ ዋጋ<br />
ከፍለዋል። ቀድሞ በተማሪዎች<br />
ንቅናቄ ውስጥ ከፍተኛ እንቅስቃሴ<br />
የነበራቸው፤ የዚያ ዘመን ሰዎች<br />
ስማቸው ዛሬም ይጠቀሳል። በርካቶቹ<br />
ዛሬ ላይ ሆነን ትንቢት ተናጋሪ አይነት<br />
እንደነበሩ መገመት አያቅተንም።<br />
ግን ብዙዎችን አጥተናል። እንዲህ<br />
ያሉትን ትንቢተኞች በማጣታችን<br />
ደግሞ እነርሱ ስለአመለካከታቸው<br />
ከከፈሉት ዋጋ በላቀ፣ ኢትዮጵያ<br />
እነርሱን ስላጣች የከፈለችው<br />
እንደሚብስ እሙን ነው።<br />
እንደኢትዮጵያ ባለ ሀገር<br />
ደግሞ የአመለካከት ልዩነቶች ሊኖሩ<br />
ግድ ነው። ይህንን ማስተናገድ<br />
ኮመንትሪ<br />
አሜሪካ ስለኢትዮጵያ ምን ታስባለች?<br />
የአሜሪካ <strong>መንግስት</strong> ስለኢትዮጵያ<br />
እና ስለገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ምን<br />
ያስባል? በፀረ ሽብርተኝነት ዘመቻው<br />
ውስጥ ኢትዮጵያን በምስራቅ አፍሪካ<br />
ያለች እውነተኛና አስተማማኝ<br />
አጋር አድርጎስ ያያታል? አልያስ<br />
ከኤርትራ፣ ሱዳን፣ ሶማሊያና<br />
ጅቡቲ ጋር ሲነፃፀር የተሻለ ወዳጅ<br />
ኢትዮጵያ ናት ከሚል የአቅርቦት<br />
እጥረት የተነሳ ሻል ካለው ጋር<br />
የመቀጠል አዝማሚያ ይሆን? ዋርካ<br />
በሌለበት አንቧጮ አድባር ይሆናል!<br />
እንዲል ተረቱ። የአሜሪካ <strong>መንግስት</strong><br />
ብሔራዊ ጥቅሙን ከማስጠበቅ<br />
አንፃርስ የጠ/ሚኒስትር መለስን<br />
አብዮታዊ ዲሞክራሲ እንዴት<br />
ይቃኘዋል? በተለይ ደግሞ ኢህአዴግ<br />
እከተለዋለሁ ከሚለው የቻይና ፈለግ<br />
እና ተዛማጅ የ<strong>መንግስት</strong> ጣልቃ-<br />
ገብ ፖሊሲዎቹ አኳያ፣ እንዲሁም<br />
የቻይና ኩባንያዎች በኢትዮጵያ<br />
ውስጥ ያለጨረታ እና ተፎካካሪ<br />
በ‹‹ድርድር›› ስለሚያገኙት ከፍተኛ<br />
የወታደራዊና የንግድ አትራፊ<br />
ሥራዎች አሜሪካ ምን ታስባለች?<br />
በዛሬው የዊክሊክስ ገመና አጋላጭ<br />
ጽሁፍ ውስጥ የተዘረዘሩት ጉዳዮች<br />
በዋናነት የሚያጠነጥኑት የአሜሪካ<br />
ኤምባሲና የአሜሪካ <strong>መንግስት</strong><br />
ስለኢትዮጵያ፣ ኢህአዴግ፣ እና<br />
ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ያላቸው<br />
አመለካከት ምን እንደሚመስል<br />
በጥቂቱም ቢሆን ለመቃኘት<br />
በሚያስችል መልኩ ሲሆን ትንሽ<br />
ግርም የሚያሰኘው ነገር ቢኖር ግን ይህ<br />
ለአደባባይ የበቃ ገመና ስለኢትዮጵያና<br />
ገዢዎቿ ከሚናገረውም በላይ<br />
ወይም እኩል ስለአሜሪካ <strong>መንግስት</strong><br />
መንታ አካሄዶች እና የተሰላ ጥበባዊ<br />
አቀራረብ በመስመሮቹ መሐል<br />
ማንበብ ለሚችል ሁሉ የሚገልፀው<br />
አያሌ ምስጢራት ይዟል።<br />
አዎ እነዚህን ሁሉ ጉዳዮች በቅርበት<br />
እየተከታተለ ዋሽንግተን ለሚገኘው<br />
ነጩ ቤተ<strong>መንግስት</strong> (White House)<br />
ሪፖርት የሚያደርገው በኢትዮጵያ<br />
ያለው የአሜሪካ ኤምባሲ ሲሆን<br />
አብዛኞቻችን የማንገምተውን<br />
ነገር ግን ውስጥ ውስጡን ሲነገሩ<br />
የምንሰማቸውን የአደባባይ<br />
ሹክሹክታዎች የአሜሪካ ኤምባሲም<br />
ጭምር የሚጋራቸው የዲፕሎማሲክ<br />
ማህበረሰቡ የኮሪዶር ላይ ወጎች<br />
እንደሆኑ ስንቶቻችን እናውቅ<br />
ይሆን? ታዲያ እነዚህን የአሜሪካ<br />
ኤምባሲ አመለካከቶች፣ ትዝብቶች፣<br />
ምልከታዎች እና ግንዛቤዎች ለህዝብ<br />
ይፋ በማድረግ የሚታወቀው የድረ-<br />
ገፅ ገመና አጋላጭ ዊክሊክስ ሰሞኑን<br />
ባሰራጫቸው ቱባ ቱባ ሰነዶቹ<br />
የኢትዮጵያን <strong>መንግስት</strong> እብድ<br />
የጠ/ሚ/መለስን ያልተስተካከሉ እይታዎች ማረም ብንችልም፤<br />
እንዲሁም በሰብዓዊ መብት ሪፖርቱ ዙሪያ ለመወያየትና የታዩት<br />
ችግሮችን ለማረም ጥረት እያደረግን እንደሆነ ብናስታውቃቸውም፤<br />
አሁንም እየቀጠለ ያለው የእነዚህ ጉዳዮች መነሳት የጠ/ሚኒስትሩንና<br />
የመንግስታቸውን ጭንቀት ያመለክታል።<br />
አዳዲስ የዊክሊክስ መረጃዎች ይናገራሉ<br />
እብድ የሚያካክሉ ሚስጥራት ፀሐይ<br />
አስመትቷቸዋል።<br />
አሜሪካ የአቶ መለስን<br />
ልማት ‹‹ገድላዊ የኢኮኖሚ<br />
ዕድገት›› በማለት<br />
ገልፃዋለች<br />
ከሴናተር ኢንሆፍ እና ልዑካኖቹ<br />
ጋር በApril 7 ከተደረገ አጭር ስብሰባ<br />
በኋላ ጠ/ሚ መለስ አምባሳደሩን<br />
ነጠል አርገው ወደ ጎን ወሰዱና<br />
በግል ሦስት ጉዳዮችን አነሱላቸው።<br />
1ኛ) በስህተቶች የተሞላ ነው<br />
ብለው የሚያምኑበትን የስቴት<br />
ዲፓርትመንት የሰብዓዊ መብቶች<br />
ሪፖርት ‹‹ማሻሻል›› ስለማስፈለጉ<br />
2ኛ) የአሜሪካ ኤምባሲ<br />
የኢትዮጵያን ረቂቅ የፀረ-ሽብርተኝነት<br />
ህግ ለሂውማን ራይትስ ዎች አሳልፎ<br />
ሰጥቷል ስለሚባለው ውንጀላ እና<br />
3ኛ) የተፈጠሩትን አለመግባባቶች<br />
ለመፍታት እና የኢትዮ-አሜሪካ<br />
ግንኙነትን ለማዳበር በከፍተኛ ደረጃ<br />
ባለው እርከን የሁለትዮሽ ስብሰባዎች<br />
መካሄድ ስለማስፈለጉ ነበር።<br />
ከቅርብ ወራት ወዲህ የሚስተዋሉና<br />
የአሜሪካ <strong>መንግስት</strong> እርምጃዎችን<br />
ተከትለው እየባሰባቸው የመጡ<br />
መረር ያሉ የአቶ መለስ ምላሾች<br />
በርግጠኝነት የሚመነጩት የኦባማ<br />
አስተዳደር ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን<br />
ግንኙነቱን በምን መልኩ ይቃኘው<br />
ይሆን? ከሚል የመንግስታቸው<br />
ጭንቀት ነው።<br />
ከዚሁ ጋር በተጓዳኝ የጠቅላይ<br />
ሚኒስትሩ ምክንያተ-ቢስ ግትርነት<br />
የሚንፀባረቅባቸው የብርቱካን<br />
ጉዳይ፣ የመ.ያ.ድ.ዎች ህግ፣ ገድላዊ<br />
የኢኮኖሚ ዕድገትና የኢትዮጵያ<br />
የሰብዓዊ መብት አያያዞች ከብዙ<br />
በጥቂቱ ለመጥቀስ መንግስታቸው<br />
አገሪቱን በአሁን ሰዓት እያለፈችባቸው<br />
ባሉ ጉዳዮች ላይ ከአሜሪካ ፖለቲካ<br />
እና ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች እንዲሁም<br />
እሴቶች በተፃራሪ የቆመን የመከላከያ<br />
ስለአመለካከት ልዩነት<br />
የሚከፈል ዋጋ እስከምን?<br />
የውዴታ ግዴታ ይሆናል። ተወደደም<br />
ተጠላ እንደብዛታችን ልዩነታችንን<br />
ተረድቶ አስተሳሰባችንንም<br />
እንድናራምድ የሚፈቅድ አይነት<br />
ምህዳር ያስፈልጋል። ከምንም ነገር<br />
በላይ በአንድ እሳቤ ከመታጠር<br />
የተሻለ እንደሆነም ይታየኛል።<br />
ዛሬ ግን ይህንን<br />
የሚያበረታታ ነገር መመልከት ከባድ<br />
እንደሆነ ይሰማኛል። ስለበርካታ<br />
ጉዳዮች ለመወያያትም የሚሻ ማግኘት<br />
ከባድ እየሆነ ነው። በመሠረቱ<br />
በዚህ ረገድ የትምህርት ማዕከላት<br />
የሚጫወቱት ሚና ከምንምና<br />
ከማንም ይልቃል። ልዩነቶች<br />
እንዲስተናገዱ እድሉንና መንገዱን<br />
ሁሉ ማመቻቸት፣ በልዩነቶቹ<br />
ውስጥ የሚንቀለቀሉ እሳቤዎችን<br />
እንዲፋፋሙ፣ ሌሎችም ያሻቸውን<br />
እንዲመርጡና እንዲቀበሉ። የሀሳብ<br />
አቅራቢዎቹም ምልከታ በተደራጀ<br />
መልኩ እንዲቀመጥ ማስቻል<br />
ይጠበቅባቸዋል - የትምህርት<br />
አምባዎቻችን።<br />
እንዲህ ያሉ ሀሳባቸውን<br />
እንዳሻቸው መግለጽ የሚችሉና<br />
የሚፈልጉ፣ ብሎም የሚደፍሩ<br />
ዜጎችን ለማፍራት ደግሞ ተsማቱ<br />
መድረኮችን መፍጠር ይኖርባቸዋል።<br />
መድረኩን ከመፍጠርም ባሻገር<br />
እንዲህ ያሉትን ዜጎች /ግለሰቦች/<br />
ማወደስ ያስፈልጋል። ዕውቅናም<br />
ሊቸራቸው ግድ ነው። ጠቃሚና<br />
አሳማኝ አጀንዳ ይዞ ለሚመጣ<br />
ማንኛውም ዜጋ በአንድም ይሁን<br />
በሌላ፣ ብቻ ማኅበረሰቡን የሚጠቅም<br />
ነገር እስከሆነ ድረስ፤ ማኅበረሰቡ<br />
በአንድ አይነት አጀንዳ ላይ ብቻ<br />
ማተኮር አለበት ከሚል ብሒል<br />
ተላቀን፣ የሌሎችንም ምልከታ<br />
ጠቀሜታ ሊኖረው ይችላል ብሎ<br />
ማሰብ በጣም ጠቃሚ ይመስለኛል።<br />
በማንኛውም ነገር<br />
ላይ የሚነሱ ሀሳቦች በምሁራን<br />
ውይይቶች ቢዳብሩ፤ ሀገራዊ የሆኑ<br />
አጀንዳዎች ላይም ልዩነቶች ቢኖሩ<br />
እንኳን የልዩነቶቹን መነሻ ለህዝቡ<br />
በደንብ በማሳየት ህዝቡም እንዲወያይ<br />
ግንብ እየገነባ እንደሆነ አመላካች<br />
ነው። በመሆኑም ልክ የአፍሪካ<br />
ጉዳዮች ረዳት ፀሐፊ እንደተመደበ<br />
በከፍተኛ ደረጃ ባለው እርከን (senior<br />
level) የሁለትዮሽ ስብሰባዎች<br />
እንዲካሄዱ አሁንም እናሳስባለን።<br />
ይህ እርምጃ የኢትዮጵያን ጭንቀቶች<br />
ጋብ ለማድረግ ከመርዳቱም በላይ<br />
ያሳሰቡንን ጉዳዮች አፅንኦት ለመስጠት<br />
እና ለግንኙነቱ የምንሰጠውን ድጋፍ<br />
ለማጠናከር ይረዳል።<br />
አሜሪካ ኢትዮጵያን<br />
እንደአስፈላጊ አጋር<br />
አታያት ይሆን?<br />
የጠ/ሚ/መለስን ያልተስተካከሉ<br />
እይታዎች ማረም ብንችልም፤<br />
እንዲሁም በሰብዓዊ መብት ሪፖርቱ<br />
ዙሪያ ለመወያየትና የታዩት<br />
ችግሮችን ለማረም ጥረት እያደረግን<br />
እንደሆነ ብናስታውቃቸውም፤<br />
አሁንም እየቀጠለ ያለው የእነዚህ<br />
ጉዳዮች መነሳት የጠ/ሚኒስትሩንና<br />
የመንግስታቸውን ጭንቀት<br />
ያመለክታል። ይህም አሜሪካ<br />
በኢትዮጵያ ላይ ያላት አቋም<br />
እየጠነከረና እየባሰ ይሄድ ይሆን?<br />
ከሚል እና አሜሪካ ከእንግዲህ<br />
ኢትዮጵያን በቀጠናው እንዳለ ወሳኝ<br />
አጋሯ አድርጋ ላታያት ትችል<br />
ይሆናል ከሚል ጭንቀት የሚመነጭ<br />
ነው።<br />
አቶ መለስ ከዚህ የተሻሉ<br />
መልካም ግንኙነቶችን እንደሚሹ<br />
ግልፅ ቢሆንም እነዚህ የሁለትዮሽ<br />
ግንኙነቶች ግን በርሳቸው መርህዎች<br />
እንዲመሠረቱና ኢትዮጵያ የሰብዓዊ<br />
መብቶችን፣ ዴሞክራሲን ብሎም<br />
የኢኮኖሚ ልማትን በራሷ የፖሊሲ<br />
ግቦች ተመስርታ በምታካሂድበት<br />
ወቅት አሜሪካ ለአገራቸው<br />
የመተናፈሻ እና የመፈናፈኛ ቦታ<br />
እንድትሰጣት ይፈልጋሉ።<br />
ማድረግ ተገቢ ነው።<br />
<strong>መንግስት</strong>ም ቢሆን<br />
እንዲህ ላለው ነገር ትኩረት ሊሰጥ<br />
ግድ ነው። ሁሌም አንድ ዓይነት<br />
አስተሳሰብና አመለካከት ይዘን<br />
እስከመቼ፤ እንዴትስ እንÕዛለን?<br />
የነገዋን ኢትዮጵያ የሚረከበው ዜጋ<br />
ዛሬ ላይ ባላንሸራሸረው አስተሳሰቡ<br />
ነገን ማየት ይቻለዋልን? እውነት<br />
ኢትዮጵያስ ህዳሴዋ እንዲሰምር<br />
አማራጮች አያሿትም? እና ሌሎችም<br />
ጥያቄዎች በውስጤ ይመላለሳሉ።<br />
ምንም እንኳን እንደ<br />
ግሪኮቹ ህዝብ ሰብስበን የምንወያይበት<br />
ቦታ ባይኖርም፣ ሁኔታዎችን ግን<br />
ማመቻቸት ተገቢም አስፈላጊም<br />
ነው። ብዙ ጊዜ እንደውም ከዚሁ<br />
የራስን አመለካከት በነጻነት ከመግለጽ<br />
ጋር በተያያዘ በተለይም ከመንግሥት<br />
ወገን ነን የሚሉት ግለሰቦች ቃላቸው<br />
አንድ አይነት እየሆነ አግራሞት<br />
ይፈጥርብኛል። ከላይ በመንግሥት<br />
የሥልጣን መዋቅር ውስጥ ያሉት<br />
ምናልባትም በውይይት ወቅት<br />
ልዩነቶቻቸውን እያነሱ ይማEገቱ<br />
ይሆናል። ይሆናል ነው ያልኩት።<br />
ከዚህ ባለፈ የማስፈጸም ጉዳይ<br />
እያነሱ ምላሽ ይሰጡ ይሆናል።<br />
ሌላውን “ወገን ነኝ” ባይ ግን ምን<br />
ይሉታል?<br />
መግባባት እየቻልን<br />
አይደለም። መደማመጥ አቁመናል።<br />
የምናነሳውን ሀሳብ ለማስረዳት<br />
ሳይሆን ለማዘዝ ይቀናናል። የተለየ<br />
ነገር ለመቀበል ዝግጅቱ ያንሰናል።<br />
ለነገሩ ልዩነት ያለው ነገር<br />
የሚያመጣም ከጠፋ ሰንበት እያለ<br />
ነው። ለዚህ ደግሞ በልዩነት መÕዝ<br />
አለመቻላችን ወይም አለመፈለጋችን<br />
በምክንያትነት ሊጠቀስ ይችላል።<br />
በእርግጥም ልዩነቶችን<br />
ያለማስተናገዳችን ነገር ዋጋ<br />
እያስከፈለን ነው። “የተለየ ሀሳብ<br />
አለን” ያሉ ዜጎችም በየዘመኑ<br />
አጥተናቸዋል። መሪዎቻችንም<br />
እንደልዩ ፍጡር እያዩዋቸው ዳግም<br />
እንዳይደርሱባቸው አርቀዋቸዋል።<br />
ትንቢት ተናጋሪ ምርጥ ዜጎች<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
7<br />
አቶ መለስ የአሜሪካ<br />
ፖሊሲ እንዲቀየር<br />
ተፅዕኖ ለመፍጠር<br />
ሞከሩ<br />
ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ በFebruary 25<br />
አምባሳደሩን ጠርተው በኢትዮጵያ<br />
እይታ አሜሪካ ከጋራ ዓላማቸው<br />
ውስጥ ከተካተቱት ከክልላዊ<br />
መረጋጋት፣ ፀረ ሽብርተኝነት እና<br />
ከልማት ጉዳዮች ይልቅ ለሰብዓዊ<br />
መብቶች የበለጠ ትኩረት በመስጠት<br />
ጠንከር ያለ የፖሊሲ ለውጥ<br />
እያደረገች እንደሆነ እንደሚሰማቸው<br />
ገለፁ። ይህ አባባል የውጭ ጉዳይ<br />
ሚኒስትር አቶ ስዩም በ February<br />
20 ለአምባሳደሩ የተናገሩትን<br />
የቃላት ተቃውሞ የሚያጠናክር<br />
ነበር። አቶ ስዩም የአሜሪካ ኮንግረስ<br />
ኢትዮጵያን ልማትና መሰል እርዳታ<br />
ከማግኘታቸው በፊት የኮንግረሱን<br />
ማስገንዘቢያ ከሚፈልጉ እንደሱዳን፣<br />
ዚምባቡዌ፣ እና ኢራን ያሉ 20<br />
አገራት ዝርዝር ውስጥ ማካተቱን<br />
አጥብቀው ተቃውመዋል።<br />
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲናገሩ<br />
‹‹ኢትዮጵያ በሁለትዮሽ ግንኙነቱ<br />
ውስጥ ከወዲሁ የሚታወቅ አካሄድን<br />
(predictability) እና ኢትዮጵያ<br />
ለአሜሪካ ምን ዓይነት ስፍራ ላይ<br />
የቆመች አገር መሆኗን በግልፅ<br />
ማስቀመጥ እንደሚያስፈልግ››<br />
ገልፀዋል። እንደውም ጠ/ሚኒስትሩ<br />
የወታደራዊ ኃይል የበላዩ ጄኔራል<br />
ሳሞራ እና የደህንነት ክፍሉ<br />
ሃላፊ አቶ ጌታቸው አሰፋ አሜሪካ<br />
የኢትዮጵያን የደህንነት አሳሳቢ<br />
ጉዳዮች ጉዳዬ ትላቸው እንደሆን<br />
እምነቱ ተመናምኖባቸዋል<br />
እስከማለት ደርሰዋል። እነዚህ ሁለቱ<br />
ባለሥልጣናት ጦረኛ ነገር ግን<br />
በውጭ ፖሊሲ ጉዳይ ላይ እጅግ<br />
በ ገፅ 23<br />
የነበራት/ያላት ኢትዮጵያ ብርታት<br />
በሌላቸው ምክንያቶች ለዘመናት<br />
ልጆቿን አጥታለች። ምናልባትም<br />
ዛሬ ላይ ለጠፋው አመለካከትን<br />
ጥርት አድርጎ ለማቅረብ ያለመቻል<br />
ችግር በእነዚህ ዜጎች ላይ የተወሰደው<br />
አሰቃቂና አሳዛኝ ግፍ የተሞላበት<br />
እርምጃ እንደ ምክንያትነት ሊጠቀስ<br />
ይችል ይሆናል።<br />
በያለንበት አጋጣሚዎች<br />
እንደሚፈጠሩበት ብርቱ<br />
የምክንያታዊነት ጥያቄዎች ምላሽ<br />
የሌለን ብዙዎች ነን። ለምን ብሎ<br />
መጠየቅ እንደወንጀል የሚቆጠርብንም<br />
እልፎች። በጣም አሳዛኙ ነገር<br />
ኢትዮጵያ ላጣቻቸው ምርጥ ልጆቿ<br />
መጥፋት ወይም መሸሽ ምክንያቱ<br />
አሳማኝ አይደለም። ሞትን የተቀበሉ<br />
በርካታ ኢትዮጵያውያን ነበሩ።<br />
ልዩነቶችን እንደጦር<br />
ከመፍራት ይልቅ፣ አቅርቦ<br />
ማዳመጥና መመርመር ለመንግሥት<br />
ኃላፊነትም ጭምር ነው። በዚህ<br />
ረገድ ከመንግሥት ወዲያ ማን<br />
የአንበሳውን ድርሻ መውሰድ<br />
ይቻለዋል? ዜጎችም ከተጫናቸው<br />
ፍርሃት ተላቀው አመለካከቶቻቸውን<br />
በነጻነት የሚያንጸባርቁበትን ዘመን<br />
ከመናፈቅ ይልቅ፣ ጊዜው አሁን<br />
ነው ማለት ይገባቸዋል። መድረኩን<br />
ማመቻቸት ደግሞ የሁላችንም<br />
ድርሻ ነው። ለኢትዮጵያ ከእኛ<br />
ወዲህ ማን እንዲመጣላት እንሻለን?<br />
ለዘመናትስ ከዜጎቿ ይልቅ ሌሎች<br />
ሲንሰፈሰፉላት ይታያል እየተባለች<br />
እስከመቼ? አመለካከቶቻችንስ<br />
ሳናወጣቸው ለመቼ? ፍርሃታችንስ<br />
የሚለቀን፤ ስለአመለካከቶቻችንስ<br />
የምንከፍለው ዋጋ እስከምን<br />
ይደርሳል? እስከምንስ መድረስ<br />
ይኖርበታል?<br />
እኒያ የግሪክ ሰዎች<br />
ብዙ ከፍለዋል። ስማቸውም ዛሬ<br />
ድረስ ይወሳል። ኢትዮጵያውያኑም<br />
በሚገባቸውም ደረጃ ባይሆንም<br />
አንዳንድ ጊዜ ይነሳሉ። ልንዘክራቸው<br />
ግድ ይላል። ምናልባትም ስለእነርሱ<br />
ብርታት ማንሳታችን ሌሎች<br />
ጀግኖች ይፈጥርልን ይሆናል።<br />
እነርሱ ስለምልከታቸው የከፈሉትን<br />
ዋጋ እያነሳን ማወደሳችን ሌሎች<br />
እንደነሱ ላሉቱ ብርታት ይሆናል።<br />
ስለሆነም “እናንተ ስለሀገራችሁ<br />
ብላችሁ በቅን ልቡና ያነሳች|ቸው<br />
አመለካከቶቻችሁ ዋጋ ያስከፈላDችሁ<br />
ኢትዮጵያውያን ሆይ! ሰላማችሁ<br />
ይብዛ፤ ጽናታችሁን በአሁኗ<br />
ኢትዮጵያ ላለነው ያውርሰን”<br />
እላለሁ።
8<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />
መልካም ዓዲስ ዓመት
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />
መልካም ዓዲስ ዓመት<br />
‹‹በአዲሱ ዓመት ‘አሸባሪ’<br />
ከመባል ይጠብቃችሁ››<br />
በወጋየሁ ታምራት<br />
ጤና ይስጥልኝ! እንዴት ናችሁሳ? ዓመቷን<br />
እንደቀልድ ፉት አልናትም አይደል?። በርግጥ ዓመቱ<br />
ማለቂያው ደረሰ እንጂ ማለቁን እርግጠኛ መሆን<br />
አይቻልም። እንዴ! መንግስታችን ጳጉሜ ከተመቸው<br />
ዓመቱ ይራዘም ቢልስ? ‹‹ሽብርተኛ›› በመያዝም እኮ<br />
በዚህ ወር ስኬታማ ሆኗል…አይደል እንዴ?<br />
አርቲስት ደበበ እሸቱም ‹‹ከአሸባሪው የግንቦት 7<br />
አመራሮች ጋር በህቡ ሲያሴር በመገኘቱ ታሰረ››<br />
መባሉን ሰምተናል። ‹‹ኧረ ደቤ ህብር መፍጠር እንጂ<br />
ሽብር አያውቅም!›› ሲሉ አንዳንድ ተቆርቋሪዎችን<br />
ብሰማ ‹‹እናንተ ውሳኔውን ለነፃው ፍ/ቤት ስጡ››<br />
በማለት ገስጫቸዋለሁ። የተከሰሰ ፖለቲከኛ ሁሉ<br />
ጥፋተኛ ሳይባል በነጣ መለቀቅ እኛ አገር እንብዛም<br />
ስላልተለመደ ነው መሰል ሰዉ እስር ሲመጣ ይሰጋል።<br />
‹‹ደግሞ እወቁ እኛ ማንንም ተቃወመን ብለን በፖለቲካ<br />
አቋሙ የምናስር ሰዎች አይደለንም!›› የሚለውን<br />
የትምህርት አይነት ሰሞኑን በደንብ እያስጠኑን ስለሆነ<br />
በቀጣይ ጊዜ በደንብ አድርገን ለጠርጣሪዎች ለማስረዳት<br />
ዝግጁ ነን። ግን ጥያቄ ያለው አለ?<br />
ዓመቱ ለእርስዎ እንዴት ነበር? በዓመቱ ምን<br />
ያላየነው አለ? እንደ ኑሮ ውድነት እደግመዋለሁ እንደ<br />
ኑሮ ውድነት ኮሜዲ እና ትራጄዲ ፊልም የሰራብን<br />
ግን አልነበረም። [ለነገሩ ማን ያልቀለደብን አለ?]<br />
ዓመቱን እንደ ሩጫ ማቋረጥ የሚቻል ቢሆን እንደ<br />
ገ/እግዚአብሄር የዴጉ ውሎ 38 ደቂቃ ድረስስ ማን<br />
ይሮጥ ነበር? ያው እንግዲህ እየተደረቡም ቢሆን የኑሮ<br />
ሩጫውን መቀጠል ነውና ይበርቱ የአገር ሰው!!!<br />
እኔ ሰሞነኛ አገልጋይዎ የወግ ማዕዴ የፍስክ ወግ<br />
ብትሉ፣ የጾም በየአይነቱ እዚህ ድረስ ነው ስላችሁ<br />
[በአውራ ጣቴ አገጬን ነክቻለሁ።] ይሄውላችሁማ<br />
አንዱ ፍንዳታ ብጤ… ‹‹የሚሰራውን የማያውቅ እብድ<br />
ነው›› አለኝ። በጄ! አልኩት ቀጠለናም ‹‹መንግስታችንም<br />
እኮ የሚሰራውን አያውቅም፡፡ ‘ቁርጥ የዋጋ ተመን’ አለ<br />
አልተሳካለትም፣ ‘የታክሲ ስምሪት’ አለ ችግሩ ያው<br />
ነው…›› ሲል ትክን ብዬ እና መንግስታችን እብድ ነው<br />
ልትል ነው? ብለው አስቀያሚ ሳቅ ከሳቀ በኋላ ‹‹ያው<br />
ነው…›› ብሎ ወሬውን ሊቀጥል ሲል በግልምጫ<br />
ሰማይ አድርሼ ብመልሰው ቱር ብሎ ከአጠገቤ<br />
ጠፋ፡፡ [የማትፈልጉት ነገር ሁሉ እንዲህ ቱር ብሎ<br />
ከአጠገባችሁ ይጥፋላችሁ፤ አሜን! በሉ]<br />
ግራ የገባው ሁሌም ቀኙ አይታየውም፡፡ እውነቴን<br />
ነዋ! ለዚህ የሆዱን አውርቶ ቱር ብሎ ጠፊ የሚታየው<br />
የተገነባው ዴሞክራሲ፣ መንገድና ህንፃ ሳይሆን ቤቱ<br />
የፈረሰበት ብሶተኛ፣ ‹‹ምህረት›› የተደረገለት ሳይሆን<br />
ግብር የተጫነበት ምላሰኛ ነው። እንደዚህ አይነቶቹን<br />
ይዘን አገሪቱን እንዴት ለአቅመ አገር ማብቃት<br />
ይቻላል?<br />
ሌላ ወዳጄን አገኘሁትና ስለ እዚህ ቱር ብሎ ጠፊ<br />
እና ንግግሩ ከአወራሁት በኋላ ለእርስዎ ከላይ<br />
እንዳጫወትኮት እንደዚህ አይነቶቹን ይዘን አገሪቱን<br />
እንዴት ለአቅመ አገር ማብቃት ይቻላል? ብለው ወደ<br />
እኔ ዞሮ ቁጭ አለ። ‹‹አንተ እና መሰል ካድሬዎች<br />
የምትናገሩትን የማታውቁ፤ በቀቀኖች፣ ህሊና እና<br />
ሞራላችሁን የቀበራችሁ፣ ኢትዮጵያ በቀዳዳ ወንፊት<br />
እያነፈሰች የአብዮታዊ ዴሞክራሲን ጠበል ካልጋትን<br />
በኃይለየሱስ ካሳ<br />
ልማታዊ ጋዜጠኛ (ል.ጋ)<br />
ፉክክሩ በተመሳሳይ ሂደት ውስጥ ያለፉ እንስቶችን<br />
ብቻ ቢመለከትም፣ ፍትሐዊና ዓለም አቀፍ<br />
መለኪያዎችን ያሟላ እንደነበር የአፍሪካ ኅብረት<br />
ታዛቢዎች ማረጋገጫ ሰጥተዋል። አንቺስ ማሸነፌ<br />
ተገቢ ነው ትያለሽ?<br />
ልማታዊ ቆንጆ (ል.ቆ)<br />
ያለ ጥርጥር። ኦልሞስት ሁሉም ዳኞች ድምፃቸውን<br />
ሰጥተውኛል። ወሳኞቹ እነሱ ናቸው። ባልፈልግም<br />
እንኳ ምርጫቸውን የመቀበል አብዩታዊ ግዴታ<br />
አለብኝ። በእርግጥ ለዚህ በመብቃቴ ደስታዬ አንድና<br />
አንድ የለውም። ለህዳሴው መሳለጥ ማበርከት<br />
የምችለውን አስተዋጽኦ ሳስብ ሀሴት ያናውጠኛል።<br />
ል.ጋ<br />
ባለድል መሆንሽ እንደማይቀር የውድድሩ አዘጋጆች<br />
አስቀድመው ሲተነብዩ ነበር። የትንቢቱ መስመር<br />
በእቅድና ጥናት ላይ ተመስርተው መንቀሳቀሳቸውን<br />
አመላካች ነው። ተተኪ የልማት አርበኛ የመኮትኮት<br />
ዓላማቸውንም በአንቺ አሳክተዋል። እስኪ እስካሁን<br />
የመጣሽበትን ጎዳናና የወደፊት አቅጣጫሽን<br />
ግለጪልን?<br />
ል.ቆ<br />
ሲጀመር መድረኩ የተዘጋጀው ማንም እንዳሻው<br />
እየገባ እንዲፈነጭበት አይደለም። በጭራሽ። ይህ<br />
ለድርድር አይቀርብም። ረጅም ርቀት ተጉዘን<br />
የሚፈለግብንን ያሟላን ጥቂቶች ነን ለእጩነት<br />
የደረስነው። “የተመረጡ ምርጦች” ይሉናል። ክበቡን<br />
ለመቀላቀል ብዙ ትጋት ይጠይቃል። ጥቂት ጥቅም<br />
ትላላችሁ፡፡ አሁን አንተ የምርጫ ሰሞን ስብሰባ፣<br />
ስብሰባ ትል ነበር፡፡ ያኔ ትንሽ ግንባርህ ወዝቶ ነበር፡<br />
፡ አሁን ግን እንዳለቀ የውሃ እቃ የሚፈልግህ አለ?››<br />
ብሎ በጥያቄ ሀሳቡን ሲቋጭ እንደዚህ አይነቱን ሰው<br />
እንዴት መመልከት እንዳለብን ከፓርቲዬ በተነገረኝ<br />
መሰረት ‹‹አላዋቂ ነህ›› በሚመስል እና በሀዘኔታ<br />
አስተያየት ‹‹ዝም ብለህ አትንጫጫ ሳይኖርህ<br />
ማሳለጫ›› አላልኩት መሰሎት። ኤጭ! አሉ እኒያ<br />
የማላውቃቸው ሴትዮ… ስንቱን እንዲህ ብዬ<br />
እንደምችለው ግን አልገባኝም፡፡ ሰዉ እኮ እህ ብለው<br />
ካዳመጡት ተበድሮ ያወራል።<br />
ከእሱ ይልቅ የገረመኝ ይሄ IMF የሚባው ሰውዬ<br />
ይሁን ሴትዮ ይቅርታ ዳታው ለጊዜው ቢጠፋብኝም<br />
ግን… ለምን ከራሳችን ላይ አይወርድም? ‹‹የማክሮ<br />
ኢኮኖሚያችሁ ሚዛኑ የተዛባ ነው። ነጋዴውም<br />
እምነት እያጣ ነው›› የሚለው ማን ንገረን አለው?<br />
ንገሩኝ ባይ! በእርግጥ ለትራንስፎርሜሽናችን ሩጫ<br />
ላይ በመሆናችን ሻይ ቡና አላልነውም። በዚህም ደንፉ<br />
(ንዴት) ጋማ ሲለው ጊዜ ‹‹ሚዛኑ የተዛባ ነው›› አላ!<br />
እኔምለው ሚዛኑ በሻይና ቡና ነውንዴ የሚሰራው<br />
ብል ታች ሰፈር ያለው አደገኛ ቦዘኔ አደገኛ ቃላት<br />
ወረወረብኝ፡፡ ቀላል ይናገራልንዴ? ‹‹ለችግራችን ፔስ<br />
ሜከር እየሆናችሁ ረሀብ ራሱ ሀትሪክ ሰርቶብናል…<br />
ምዕራባውያኑ ጓዳችን ፈትሸው ለዓለም ሲያወሩ<br />
እውነቱ አልጥማችሁ እያለ ለ‘አይናችሁን ጨፍኑ’<br />
ጨዋታችሁ ቀይ ካርድ የሚመዝ አጥተናል …››<br />
ቢለኝ ጀርባውን ሳላስጠና ምንም መናገር አያስፈልግም<br />
ብዬ ዝቅ ብዬ አሳለፍኩት ልክ ነኛ! እንዲህ አይነት<br />
ሰው ወይ ሽብርተኛ፣ ወይ ፅንፈኛ፣ ወይ ጨለምተኛ<br />
ወይ ሌላ በ ‹‹ኛ›› የሚያልቅ ነገር እንደሆነ እኛ መች<br />
እናጣዋለን?<br />
እህሳ! ይች ክረምት ትንሽ ከበድ አለች አይደል?<br />
‹‹ሊነጋ ሲል ይጨልማል›› እንዲሉ ነዋ! እኛም<br />
አውቃንበታል ድህነታችንን ቀቅለን እየበላን፣<br />
ቴሌቪዥን ላይ እናፈጣለን። እዚያ ደግሞ ጥጋብ ስላለ<br />
ሚሊየነር ገበሬዎችን እያየሁ ‹‹ተመስገን›› ስል የሰማኝ<br />
<strong>መንግስት</strong>ን ማመስገን አላርጂክ የሆነበት አንድ ወዳጄ<br />
‹‹ፓ! ወገኛ ነህ የታለ ስኳር ድንች? የት እንደጠፋ<br />
ታውቃለህ? አታውቅም ምርጥ ምርጡን ለፈረንጆች<br />
ሲባል አልሰማህም? እኛ ሳንጠግብ ኤክስፖርት<br />
አድርገውታል›› ቢለኝ እንዴት በ‹‹አድርገውታል››<br />
ይገደባል? ‹‹አድርጋችሁታል›› ባለማለቱ እኔን እንደ<br />
ነጭ ለባሽ ነው እንዴ የሚያየኝ? ብዬ በገደምዳሜ<br />
በጭላንጭል አይተው የተከተሉን ድንኳን ሰባሪዎች<br />
ተንጠባጥበው ቀርተዋል። አካሄዳቸው ኪራይ<br />
ሰብሳቢነት ነበርና። በበኩሌ ነፍስ ካወቅሁበት ጊዜ<br />
አንስቶ ተሳትፎዬ ተስተጓጉሎ አያውቅም። ካምፓስ<br />
ሳለሁ የተማሪዎች ህዋስ መሪ ሆኜ አገልግያለሁ።<br />
ተመርቄ ከወጣሁ በኋላ ደግሞ የሴቶች ሊግ<br />
ሊቀመንበር፣ የወጣቶች ፎረም ጸሐፊና ያላገቡ<br />
ወጣት ሴቶች ፌዴሬሽን አቃቤ ነዋይ ነኝ። የሀገሪቱ<br />
ታሪክ ተስተካክሎ እንዲፃፍ የተዋቀረው ኮሚቴ<br />
ውስጥ በአባልነት አለሁበት። የምጣኔ ኃብታችንን<br />
ምጥቀት የሚያስተነትኑ ቁጥሮች በተንኳሾች<br />
ተዛብተው እንዳይዘገቡ ጠንክሬ እከታተላለሁ።<br />
ከዚህም በላይ በቻይናዋ ዋንግ ዡ ከተማ የሶስት<br />
ወር ሥልጠና ወስጃለሁ። “ወ/ሪት ልማት” መባል<br />
ከማኩራትም ባለፈ በቀላሉ የማይገኝ ዕድል ነው።<br />
እርሱን ተጠቅሜ የምሰራቸው ተግባራት ይኖራሉ።<br />
ለአብነት ያህል ታዳጊዎች ምን ማሰብ እና እንዴት<br />
ማሰብ እንዳለባቸው የሚነግር ተቋም ለመክፈት ጫፍ<br />
ደርሻለሁ። በተጨማሪም “ኃይማኖት ለልማት” በሚል<br />
ማዕቀፍ ላከናውነው የምሻው ውጥን አለኝ። አንተም<br />
በሚገባ እንደምትረዳው በፈጣሪ ማመን ያን ያህልም<br />
የሚያስፈልግ ጉዳይ አይደለም። የእኛ መንፈሳዊ<br />
መጽሐፍ ትግላችን ያስገኘለን አምላክ-አካል ግለሰቦች<br />
ቃላት ናቸው። እነርሱን ጠንቅቆ ማወቅና ማነብነቡ<br />
ይበቃል። ሆኖም የእምነት ተቋማትን ልንገለገልባቸው<br />
እንችላለን ብዬ አምናለሁ። በተረፈ የዘወትር ምኞቴ<br />
ሁሌም የማልማትን ታላቋን ሀገር ሰሜን ኮሪያን<br />
መጎብኘት ነው። እንደሚሳካ አልጠራጠርም። ዋነኛ<br />
ሥራው ንግድን መቆጣጠርና ነጋዴዎችን ማውገዝ<br />
የሆነ ቡድን አለ። የእሱ አካል መሆን ከቻልኩ<br />
እርካታዬ የትየሌሌ ይሆናል።<br />
ል.ጋ<br />
የኢራንና የኩባ ተመራማሪዎች እንደደረሱበት<br />
ሰሞነኛ ምርቃት<br />
ከታች ሰፈር ልጆች ጋር በኮሪያ- ዴጉ ተካሂዶ የነበረውን የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ፍፃሜ እየተመለከትን እያለ<br />
ምነው አትሌቶቻችን ውጤት ራቃቸው ብል እየተቀባበሉ ‹‹የሚወራውን አልሰማህም እንዴ?… ‘እያንጓለለ<br />
ካልተፈታ’ ብለው አድማ ላይ እኮ ናቸው›› አሉኝ። ምን ለማለት ፈልገው እንደሆነ ግን አልገባኝም፡፡<br />
ብነግረው ‹‹ምርጥ ምርጡ ጉዳይ ለትልልቆቹ ዓሳዎች<br />
እንጂ ለትንንሾቹ በሰሚ ሰሚ ካልሆነ መረጃውን<br />
ስለማይነግሯችሁ ከእኛ እኩል ናችሁ ብዬ ነው››<br />
በማለት የሆዴን ስለነገረኝ በፀጥ ማርሽ ኩምሽሽ<br />
አደረገኝ እላችኋለሁ። እኔንማ ሲጠራኝ ‹‹አትርሱኝ››<br />
እያለ ነው፤ አትርሱኝ ካላልካቸው በቀር ለምርጫ<br />
ሰሞን ካልሆነ እንዳንተ ያለው ካድሬ ትዝ አይላቸውም<br />
ለማለት ነው።<br />
[ውድ አንባብያን አሁን የዜና ሰዓታችን ስለደረሰ<br />
ከዜናው በኋላ እንደገና እናወጋን]<br />
ጤና ይስጥልኝ ዜና እናሰማለን ምክንያቱም ከማን<br />
እናንሳለን፡፡<br />
ሁሉም በኢህአዴግ ፊት እኩል ነው የሚለውን<br />
‘እውነታ’ ሽሮ ‹‹አይደለም ታጋይ እና አባል የሚሉ<br />
ልዩነቶች አሉ›› በማለት በቅምቀማ ቤት ሲያወራ<br />
የተገኘው እንደልቡ ባሻዬ የተባለ ግለሰብ እንዲህ<br />
ሊያናግረው የቻለው ምን ጠጥቶ ነው፣ ምንስ ተመግቦ<br />
ነበር በሚል ሊካሄድ የነበረው ጥናት ትክክለኛ ቀኑ<br />
ባይገለፅም ለሚቀጥለው ዓመት ጠዋት ተላልፏል<br />
ተብሎ በየመሸታው ቤት እየተወራ ነው።<br />
የውጪ ዜና፡- ትሪፖሊን በሚስጥር ለቀው አልጀሪያ<br />
የገቡት የጋዳፊ ባለቤት ሰሞኑን በሚስጥር ቅኔ አዘል<br />
ነጠላ ዚማ መልቀቃቸውን ከአልጀርስ ሰምተናል።<br />
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት አቶ ኦባማም ይህን ቅኔ<br />
ለፈታ ኢትዮጵያዊ እስረኛ(ሰው) ከስራቱ ይፈታል<br />
[አሜሪካ ይሄዳል ለማለት ከሆነ አገራችንን መዘባበቻ<br />
ማድረጋቸው ያሳዝናል] ሲሉ ሀሳብ ሰንዝረዋል<br />
በማለት የዘገበው ነቆራ.com ነው አዝማቹ እንዲህ<br />
ይነበባል።<br />
አሻግሬ ሳየው ከማዶ ከጎራው<br />
በዝናር ያጌጠው እሱ ነው ያ ጀግናው<br />
ከዜናው ተመልሰናል ስራችንን እንቀጥል። ወግም ስራ<br />
ሆነንዴ? ይላሉ የታች ሰፈር ልጆች። አልቀረባችሁም<br />
እላቸዋለኋ! ስራ ስል ምን ትዝ አለኝ መሰላችሁ ሁለት<br />
የቀድሞ ወዳጆቻችን አግኝቼ ምን እየሰራችሁ ነው?<br />
ብላቸው ‹‹ስፖርት›› አሉኛ! ኧረ ሳቄ ናልኝ ካልኩ<br />
በኋላ ሌላውን ከተመረቀ ሁለት ዓመት ያለፈውን ልጅ<br />
አንተስ ምንድን ነው የምትሰራው? ብለው ጨዋና<br />
ታታሪ የሚባሉትን የላይ ሰፈር ልጆች ጠርቶ ‹‹እነሱ<br />
እንኳን አልያዙም›› ሲል በሾርኒ ዋልጌነቱን ነገረኝ።<br />
በራሱ የሚያሽሟጥጥም አለ ለካ!<br />
እኔምለው! ኮሌጅ ማስበጠሱ ብቻ ምን ዋጋ አለው?<br />
የበጠሱትን መልሰው መቋጠር ካልቻሉ ኮሌጅ እንደ<br />
በኒዩሊበራል ሀገራት ውበት ሴቶችን የመጨቆኛና<br />
ወንዶችን የማሽመድመጃ ሴራ አካል ነው። ሥርዓቱም<br />
እየተንኮታኮተ ከመሆኑ አንፃር በልማታዊ አስተሳሰብ<br />
ውበት እንዴት ይገለፃል?<br />
ል.ቆ<br />
ዋናው ነገር የገላ መለምለም ወይም የመልክ ስልክክ<br />
ማለት አይደለም። ከሁሉ በላይ በማንነት መኩራት<br />
ያሻል። ኩራትህን ለመግለፅ ደግሞ መግደርደር<br />
የለብህም። ለእኔ ፈታኝ የነበረው አጋጣሚ በደሜ<br />
ውስጥ የበርካታ ዘሮች ጠብታ መኖሩ ነው። የምልህ<br />
ገብቶሃል? የትኛውን ብሔር መወከል እንዳለብኝ<br />
እርግጠኛ አልነበርኩም። አለባበሱ፣ ጭፈራው፣ ታሪክ<br />
ነገራው አምታታኝ። የአባቴ አባት ወገኖቼ የእናቴን<br />
እናት ወገኖች መጨቆናቸውን፣ የአባቴ እናት ወገኖች<br />
ከእናቴ አባት ወገኖች ጋር መፋለማቸውን ተረዳሁ።<br />
ግን ልማታዊነት ከጭቁኖች ጎን መቆም መሆኑን<br />
አልዘነጋሁም። ያደረግሁትም ያንን ነው። ቁንጅና<br />
ዝም ብሎ አይን ከማማለል ባለፈ የራሱ ግብና ፋይዳ<br />
አለው። እርሱን ለመገንዘብ በቅድሚያ ሚናን መለየት<br />
ግድ ነው። ዓለም ጥቁርና ነጭ ነች። ወይ ከጥቁሩ<br />
ጋር ሁን ወይም ከነጩ ጋር ሁን። ልማታዊ ውበትን<br />
ከተጎናፀፍክ የሚሉህን ትሰማለህ። የሰማኸውን<br />
ታሰማለህ። በተቀደደልህ ቦይ ትፈሳለህ። በተመተረልህ<br />
መንገድ ትነጉዳለህ። ዞር ዞር ብለህ ዙሪያህን መቃኘት<br />
የለብህም። ጥያቄዎችን በማሰላሰልና በመሰንዘር<br />
አትቸገርም። በእውነቱ አስደሳች ነው።<br />
ል.ጋ<br />
አንዳንድ የአዲስ አበባ ከተማ ኗሪዎች ውድድሩን<br />
ማሸነፍሽ ከምስራቅ አፍሪካ መረጋጋት ጋር ቀጥተኛ<br />
ተዛምዶ እንዳለው የገለፁበት ሁኔታ ነው ያለው።<br />
ፊታቸውን ቅጭም አድርገውም ቢሆን ደስታቸውን<br />
በሰላማዊ ሰልፍ ሊያሳዩ እየተሰናዱ ናቸው።<br />
ሞባይል ካርድ መሸጫ ሱቅ መፍላቱ በእርግጥ<br />
እንደ አካሄድ ከአገር ገፅታ ግንባታ አንፃር ሙድ<br />
አለው። በየመንደሩ፣ በየኩሽናው፣ መከፈቱ ቁልፍ<br />
ጥንካሬያችንን ያሳያል፡፡ [ሳቄ መጣብኝ፡፡ እናንተዬ<br />
የብርድ ሳቅ ለካ ስትራፖ አለው።] ለማንኛውም ከሳቁ<br />
ተመልሻለሁ።<br />
ጠቅላይ ሚኒስትራችን አልናፈቁዎትም? ፈቃዱን<br />
የሰጣቸው መድረክ ወይም ቅንጅት ይመስል ‹‹እነዚህ<br />
የሠርተፍኬት መሸጫ ሱቆች…›› እያሉ በራሳቸው<br />
እና በእኛ ላይ ፓርላማው ተከፍቶ ሲቀልዱ ማየት<br />
ነው ያማረኝ። ይህን የትምህርት ‹‹አብዮት››<br />
እና የሠርተፍኬት መሸጫ ሱቆች ሰሞኑን አይን<br />
በዝቶባቸዋል። <strong>መንግስት</strong> እንደ ምርጫ ፈተና ኮሌጆቹን<br />
ሀ፣ ለ፣ ሐ 1 እና 2 እያለ መክፈል ጀመረ አሉ።<br />
በቀይ ካርድ የተባረሩም አሉ። ኢንቨስት ካደረጉ በኋላ<br />
ከማባረር ቀድሞ ነበር እንጂ መደቆስ አትሉም?<br />
መንጌን የሚያስታውሰን ነገር… የጠ/ሚኒስትራችን<br />
ፎቶ በየቢሮው እና በአደባባዩ መሰቀል ከተጀመረ<br />
ከራርሟል አይደለም? አንድ ወዳጄ ይህን ሲያነሳብኝ<br />
‹‹እወደድ ባዩ ሰቀለው እንጂ እሳቸው ይህንን<br />
አልደግፍምም፣ አላየሁም፣ አልሰማሁም፣ ብለዋል<br />
አራት ነጥብ›› ብለው ‹‹በየሚኒስትሮቻችሁ፣<br />
በየኮሚሽነሮቻችሁ ቢሮ ፎቶው ተሰቅሏል። ሰዎቹ<br />
ወይ አይሰሙም፣ ወይ አይታዘዙም ማለት ነው።<br />
የማይታዘዝ ደግሞ ነገ…›› ብሎ ሳይጨርስ እኔም<br />
ቱር ብዬ ጠፋሁ፡፡ የቀረውን አሞራ ትጨርስላችሁ።<br />
በሞቴ ሳልረሳው ልንገራችሁማ ኢቴቪ በሰከንድ<br />
የማስታወቂያውን ክፍያ ጣራ ላይ ሰቀለውኮ<br />
አሃ! ለእኛም ይታሰብልና ማስታወቂያ ባናሰራም<br />
ማስታወቂያ እናያለና! ልክ ነኛ! በማስታወቂያው<br />
ካልተዝናናን ታዲያ በምኑ ልንዝናና ነው…[በርግጥ<br />
ማስታወቂያ ሰሪዎቹ ሁለት ብቻ መስለዋል፡፡ እነሱም<br />
ጣሪያ ወጥተው ሲወርዱ አልቆባቸዋል እያሉ ታች<br />
ሰፈር ያወራሉ] እኛ ሰፈር ቴሌቪዥን ድምፅ ተቀንሶ<br />
ይከፈታል። ማስታወቂያ ሲመጣ ‹‹ከፍ አድርገው<br />
ይባላል›› ሲያልፍ ይቀነሳል እንዲህ ነው ኢቴቪ ጋር<br />
ተስማምተን የምንኖረዋ! ምን ላድርግ ታዲያ ከታች<br />
ሰፈሮች ጋር ሲኖሩ ተስማምቶ ካልሆነ ስለማይቻል<br />
ችያቸዋለሁ።<br />
መቼም የእኔ ነገር አንዱን ጥዬ አንዱን አንጠልጥዬ<br />
ሆነብኝ እንጂ ኢቴቪ ‹‹በኤሌክትሪክ የሚሰራ ባስ<br />
ደብረ ማርቆስ ሊገጣጣም ነው። በቅርቡ ለሙከራ<br />
ከጊዮርጊስ አዲሱ ገበያ ይጀምራል›› ብሎ ካስደሰተን<br />
ይኸው ፀሀይዋ ስንት ጊዜ ገብታ ወጣች መሰላችሁ፡፡<br />
‹‹ከምን ደረሰ ብለው አጣርተዋል?›› አሃ! ከማስደሰት<br />
የገፅታ ግንባታ አንፃር ከሆነማ ይሄ የባቡር ዝርጋታው<br />
ጉዳይስ እንዴት ነው?<br />
ከታች ሰፈር ልጆች ጋር በኮሪያ- ዴጉ ተካሂዶ<br />
የነበረውን የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ፍፃሜ እየተመለከትን<br />
እያለ ምነው አትሌቶቻችን ውጤት ራቃቸው ብል<br />
እየተቀባበሉ ‹‹የሚወራውን አልሰማህም እንዴ?…<br />
‘እያንጓለለ ካልተፈታ’ ብለው አድማ ላይ እኮ<br />
ናቸው›› አሉኝ። ምን ለማለት ፈልገው እንደሆነ ግን<br />
አልገባኝም፡፡ ለማንኛውም ሳምንት በሰላም እንገናኝ<br />
ዘንድ ከስንብቴ በፊት ከተማ ውስጥ የሚወራውን<br />
ሰሞነኛ ምርቃት ቱቱ ብዬ ላድርስዎ። ‹‹በአዲሱ<br />
ዓመት ‘አሸባሪ’ ከመባል ይጠብቅዎ!›› ሰላም!!!<br />
የሚስ አብዮታዊ ዴሞክራሲ ልማታዊ ውበት ምስጢር<br />
አንባብያን ሆይ! የተያያዝነውን የሀገር ገፅታ ግንባታ በማስቀጠሉ ረገድ ጉልህ ሚና እንደሚጫወት የታመነበት ታላቅ ውድድር በቅርቡ መካሄዱ ይታወቃል። በውድድሩም በታሪካችን<br />
ለመጀመሪያ ጊዜ የብሔር ብሔረሰቦችን እኩል ተሳትፎ ባረጋገጠ መልኩ ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጣ የልማታዊ ዳኞች ቡድን፣ የልማታዊ ውበትን እሳቤ የተላበሰች ቆንጆ<br />
መርጦ “ሚስ አብዩታዊት ዴሞክራሲ” ሲል ሰይሟል። ወርቃማው የአሸናፊነት ዘውድ በክብር ከተጫነላት ወጣት ጋር ልማታዊው ጋዜጠኛችን ቀጣዩን አጭር ቆይታ አድርጓል።<br />
ለአድናቂዎችሽ ምን መልዕክት ታስተላልፊያለሽ?<br />
ል.ቆ<br />
ምልክታችሁ እሆን ዘንድ ስለፈቀዳችሁ<br />
አመሰግናለሁ። ይህ ለእኔ የኮንትራት ውል ነው።<br />
ስሜን በተግባር ካላስከበርኩ ህዝቡ ውሉን ያለማደስ<br />
መብቱ ተከብሮለታል። አልፈልግሽም ብሎ ቀይ<br />
ካርድ ሊመዝብኝ ይችላል። ስለዚህ አሁን የምለው<br />
እኔ ለልማት ተግቻለሁ፣ ከጎኔ ቁሙና እጅ ለእጅ<br />
ተያይዘን የአምስት ዓመቱ - አራት ሆነ’ንዴ? -<br />
የእድገት ትራንስሚውቴሽን እቅድ ... ማለቴ እድገትና<br />
ተራንስፊክሴሽን ... ኤጭ! ምን ዕዳ ነው’ቴ ...<br />
የአምስት ዓመቱ የእድገትና ትራንስግሬሽን . . .<br />
ል.ጋ<br />
ትራንስፎርሜሽን<br />
ለ.ቆ<br />
አዎ። እርሱ እንዲሳካ የበኩላችንን እንወጣ።<br />
ል.ጋ<br />
በጣም ጥሩ። በመጨረሻ ከየወረዳ ኃላፊዎች<br />
የሰበሰብኩት ዳታ አለ። ቁጥራቸው እዚህ ግቡ<br />
ማይባልና ግራፉ እንደሚያሳየን ቁልቁል እየወረደ ያለ<br />
ነቃፊዎች አላጣሽም። ምን ትያቸዋለሽ?<br />
ል.ቁ<br />
ወየውላችሁ!<br />
ል.ጋ<br />
አመሰግናለሁ ሚስ አብዮታዊት ዴሞክራሲ። ልማታዊ<br />
ስኬትና አብዮታዊ ደስታ እንዲገጥምሽ እመኛለሁ።<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
9
10<br />
በንፍታሌም<br />
የመፅሐፉ ርዕሥ፡- ፒያሳ (መሐሙድ ጋ ጠብቂኝ)<br />
የመፅሐፉ ደራሲ፡- መሐመድ ሰልማን<br />
የመፅሐፉ አይነት፡- ወግ፣ መጣጠፍ እና የጉዞ<br />
ማስታወሻ<br />
የገፅ ብዛት፡- 181 ገፅ<br />
የመፅሐፉ ዋጋ፡- 29 ብር<br />
ፒያሳን የትውልድ መንደሬ ያህል<br />
አብጠርጥሬ አውቃታለሁ። ለድፍን 15 ዓመታት<br />
በውስጧ ተመላልሼባታሁ። ከእግር እስከ ራሷ ልቅም<br />
አድርጌ አይቻታለሁ ብዬ አምናለሁ። በመሀመድ<br />
ሙዚቃ ቤት ወረድ ብዬ ተረት ሰፈር ውስጥ ወግ<br />
ሰልቄአለሁ። ሸቅብ ተመልሼ በዶሮ ማነቂያ ጉራንጉር<br />
ተሹለክልኬአለሁ። ሰራተኛ ሰፈርን በቀን በለሊትም<br />
ቃኝቻለሁ። ውቤ በረሃን፣ ገዳም ሰፈርን፣ አትክልት<br />
ተራን ወዘተ በየተራ ውዬባቸዋለሁ፤አምሽቼባዋለሁ።<br />
ሁሉንም የፒያሳ ‹‹መዳረሻ››ዎች እስኪበቃኝ ድረስ<br />
አዳርሻቸዋለሁ። እንዲያው በአጭሩ፣ ከአጭሩም<br />
በአጭሩ አውቃቸዋለሁ ባይ ነኝ።<br />
ግን ደግሞ ከእኔ በላይ ፒያሳን የሚያሳየኝ<br />
ሲገኝ ገረመኝ። ምን መገረም ብቻ? ደነቀኝ። ዕለት<br />
በዕለት የምጎበኛትን ፒያሳ እንደ አዲስ በአይነ<br />
ህሊናዬ እየቃኘሁ ሳቅኩ። አንድም በራሴ፣ አንድም<br />
በሁላችንም፣ አንድም በማንነታችን እየሳቅሁ ከራሴ<br />
ጋር ሙግት ገጠምኩ። እየሳቅኩ አዘንኩ። ‹‹እያነቡ<br />
እስክስታ›› እንዲሉ።<br />
እንዲህ ያለ ጥልቅና መንታ ሥሜት<br />
ውስጥ የከተተኝ በቅርቡ ለአንባቢያን የቀረበውና<br />
‹‹ፒያሳ›› የሚል ርዕስ የተሰጠው መፅሐፍ ነው።<br />
‹‹ፒያሳ›› ከሚል ጉልህ ርዕሥ ሥር ‹‹ማሕሙድ<br />
ጋር ጠብቂኝ›› የሚል ንዑስ ርዕሥ በድራቢነት<br />
ተሰጥቶታል። ደራሲው ደግሞ መሐመድ ሰልማን<br />
ይባላል።<br />
ደራሲው መሐመድ ሰልማን ‹‹ፒያሳ››<br />
(መሐሙድ ጋ ጠብቂኝ) የሚል ርዕሥ የሰጠው<br />
ይህ መፅሐፍ ወጎችን፣ መጣጥፎችን እና የጉዞ<br />
ማስታወሻዎችን በአንድነት አጣምሮ ይዟል። በ14<br />
ክፍሎች (ርዕሶች) የተሰደሩት የመሐመድ ሰልማን<br />
በረከቶች በፒያሳ ‹‹ምህዳር›› ብቻ የተከበቡ ይደሉም።<br />
የሀገርን ዳር የሚያካልሉ፣ የሀገርን ሁለንተና ቁልጭ<br />
አድርገው የሚያሳዩ የብዕር ትሩፋቶች ናቸው። በሌላ<br />
አነጋገር የሀገር ዕውነት፣ የሐገር እብደት፣ የሐገር<br />
ንቅዘት፣ የሀገር ዝቅጠት፣ የሀገር እምነት ወዘተ<br />
እንደዘበት የታቀኙባቸው ናቸው። እንደገና በሌላ<br />
አነጋገር የእኛ ማንነት፣ የእኛ ምንነት፣ የእኛ ዕምነት፣<br />
የእኛ ሥነ ምግባር ልኬት ወዘተ በሚጥም ቋንቋ<br />
የተመዘነበት ድንቅ የሥነ ፅሁፍ በረከት ነው።<br />
ለዚህም ይመስለኛል የቀድሞው አዲስ<br />
ነገር ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ መስፍን ነጋሽ ፣ ካለበት<br />
ከሀገረ- ስዊድን የሚከተለውን አስተያየት በመፅሐፉ<br />
መቅድም እንዲህ ሲል ያሰፈረው፡-<br />
‹‹በፀሐፊው እይታ ፖለቲካ/ፖሊሲ፣ ባህል፣<br />
ኢኮኖሚና ጊዜ ተጣምረው የሰሩትን ኢትዮጰያዊ<br />
ህይወት፣ አኗኗር፣ ህልም፣ ብሶት ወዘተ በጋዜጠኛ<br />
አይን ከትቦልናል። ፅሁፎቹ የግለሰቦችንና የቡድኖችን<br />
የቀን ተቀን አኗኗርና ትዝብት የሚያንፀባርቁ<br />
እንደመሆናቸው የዘመኑ ‹ዜና መዋዕል› አካል<br />
ተደርገው ሊታዩ የሚገባቸው ናቸው።…››<br />
ይህ አስተያየት የመፅሐፉን ይዘት ብቻ<br />
ሳይሆን፣ የደራሲውን ላቅ ያለ ችሎታ የሚጠቁም<br />
ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ የሥነ ፅሁፍ አጥኚዎች<br />
(ተመራማሪዎች) አንድ ደራሲ የድርሰቱ ምንጭ<br />
የሆነውን ማህበረሰብ በሚገባ ማወቅ እንዳለበት<br />
ነው ለደራሲነት ክህሎት ቅድሚያ የሚሰጡት።<br />
ደራሲ ማህበረሰቡን የኑሮ ገፅታ፣ የኢኮኖሚውን፣<br />
የፖለቲካውን፣ የማህበራዊ ህይወቱን ሁኔታ፣<br />
ከእነዚህ ጋር ተያያዥ የሆኑ ታሪካዊ ክስተቶችን<br />
ልቅም አድርጎ ማወቅ አለበት ይላሉ። ምክንያቱም<br />
‹‹በሥነ ፅሁፍና በማህበረሰብ መካከል ጥብቅ ትስስር<br />
አለ፤ ትስስሩና የእውኑ ህይወት ገፅታዎች የድርሰቱ<br />
መሠረቶች ናቸውና›› ሲሉ ያሰምሩበታል።<br />
የ‹‹ፒያሳ›› (መሐሙድ ጋ ጠብቂኝ) ደራሲ<br />
መሐመድ ሰልማን፣ ይህንን የማህበረሰብን እና የሥነ-<br />
ፅሁፍን ጥልቅ ትስስር በድንቅ ብቃትና ክህሎት ነው<br />
ያስመሰከረው። ‹‹ዐደይ መቀሌ››፣ ‹‹በኤርትራ ሙዚቃ<br />
የምትደንስ ከተማ››፣ ‹‹የመመረቂያ ፅሁፎች ጥቁር<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
ፒያሳ<br />
በ‹‹ ››<br />
ገበያ››፣ ‹‹ሼ መንደፈር በመርካቶ››፣ ‹‹ከአዲግራት<br />
እስከ ዛል አንበሳ›› ወዘተ በተሰኙ ርዕሶች ያቀረበልን<br />
ታሪኮች ለዚህ አባባል አይነተኛ ማሳያዎች ናቸው።<br />
በነገራችን ላይ በመፅሐፉ ውስጥ<br />
ከተካተቱት ትረካዎች ስምንት ያህሉ በቀድሞዋ<br />
‹‹አዲስ ነገር›› ጋዜጣ ለንባብ የበቁ ናቸው። ቢሆኑስ?<br />
ዛሬም እንደ አዲስ እየተገረምን፣ እየተደመምን፣<br />
በራሳችን እያዘንን እና እየተከዝን እናነባቸዋለን።<br />
ራሳችንን እንፈትሽባቸዋለን። የት እንዳለንና ወዴት<br />
እየሄድን እንደሆነ እናይባቸዋለን። ለማንኛውም ወደ<br />
ዋና ጉዳይ እንመለስ። ወደ ደራሲው።<br />
በ‹‹ፒያሳ›› መፅሐፍ የምናስተውለው<br />
የደራሲውን የላቀ ችሎታ ነው፡፡ ደራሲው መሐመድ<br />
ሰልማን በመማር ብቻ ሳይሆን፣ በተፈጥሮ<br />
የተጎናፀፈው ድንቅ ችሎታ አለው ብንል ማጋነን<br />
አይሆንም። መሐመድ በእርግጥ ይፅፋል። ይፅፋል<br />
ብቻ ሳይሆን በቃላት መሳልን ተክኖበታል። በቃላቶች<br />
ህብረ ነገሮችን አጉልቶ ያሳየናል። አንድን ነገር<br />
በአንባቢያን ልቦናና አዕምሮ ውስጥ ለመቅረፅ ብዙም<br />
አይጨነቅም። በቀላል ቋንቋ፣ በአጭርና በቁጥብ<br />
ዓረፍተ ነገር፣ በተዋበ ስልትና ፍሰት መጥኖ በቀላሉ<br />
ይገልፅልናል።<br />
አገላለፁ ልክ እንደ ልጅነት ልብና አዕምሮ<br />
ንፁህ ነው። ለዚህ አባባል አስረጂ ይሆን ዘንድ<br />
የሚከተለውን መጥቀስ እንችላለን፡-<br />
‹‹ትልቁ የአገራችን የህዝብ ሽንት ቤት<br />
‹ማህሙድ ሙዚቃ ቤት› ማዶ ነው። ግርማዊነታቸው<br />
የፈረንሳይ ህንፃ ባለሙያዎች አስመጥተው ነው<br />
ይህንን የህዝብ ሽንት ቤት ያሰሩት። እውነቴን ነው።<br />
ካላመንክ አቶ ፍቅሩ ኪዳኔ የጻፉትን ‹የፒያሳ ልጅ›<br />
መፅሐፍ አንብብ…›› (ገፅ 7)<br />
መሐመድ ሰልማን አስረጅ ከማቅረቡ<br />
በፊት ‹‹እመነኝ›› ይላል። ‹‹‹ከላማንክ እነ እከሌን<br />
ጠይቅ፣ የእከሌን መፅሐፍ አንብብ›› ይልና ወደ ሌላ<br />
ጉዳይ ያመራል። ህፃን ሆናችሁ ‹‹ካላመንክ እከሌን<br />
እንጠይቅ›› ያላችሁበት የዕውቀት ማስረገጫ እማኝ<br />
የጠራችሁበትን የቅንነት ዘመን አስታወሳችሁ?።<br />
መሐመድ ሰልማን የተከተለው የአተራረክ<br />
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />
መልካም ዓዲስ ዓመት<br />
p Ç T@<br />
ሽንቁር ሀገር ሲመተር<br />
ስልትና ዘይቤ መራሩን የሚያጣፍጥ፣ ጠፋጩን<br />
የሚያመር ነውና የአንባቢያንን ስሜት ሰቅዞ የመያዝ<br />
ኃይል ደርቧል፡፡<br />
‹‹ፒያሳ ፎቅ አልባ ናት ካልን ‹ገመናዋን<br />
ማን ሸፈነላት?› የሚለው ጥያቄ ይከተላል።<br />
በፒያሳ ወርቅ ወርቁን ስታይ ከጀርባ ምን እንዳለ<br />
ትረሳለህ። በፒያሳ ቆንጆ ኮረዶች ሽው እልም ሲሉ<br />
ስታይ ማሰቢያህ ይሰለባል። ደፈር ብለህ አንዷን<br />
የፒያሳ ቆንጆ ዳሌዋን እያየህ በ‹ብሪቲሽ ካውንስል›<br />
ወይ በ‹አምፒር› ወይ በ‹ሰራተኛ ሠፈር› በኩል ባለ<br />
ቀጭን ቅያስ ውስጥ ትገባለች። መጨረሻዋን ልይ<br />
ብለህ አሁንም ትከተላለህ። እስከ ውስጥ። ድንገት<br />
ትሰለብብሃለች። በዚህ ቅፅበት ምን ሰወራት ብለህ<br />
ለራስህ ስታንሾካሹክ ከጭርንቁስ ቤቷ በመስኮት<br />
ወጥታ ‹ምን አልክ› ልትልህ ትችላለች። ስለዚህ<br />
የፒያሳ ልጅ አትከተል። ከተከተልክም እጇን ይዘህ<br />
ተከተላት፡፡…›› (ገፅ 10)<br />
ይኼኔ ነው የዘይቤን ምንነት ማጠየቅ<br />
የሚገባው። ዘይቤ የአንድን ሀሳብ፣ ድርጊት፣ የአንድን<br />
ነገር ቅርፅ ወይም ሁኔታ፤ እንዲሁም የሰውን ባህርይ<br />
ስሜትና መልክ አጉልቶና አድምቆ ለተመልካችም ሆነ<br />
ለሰሚው ፍስሃ በመስጠት የሚቀርብ የአነጋገር ስልት<br />
መሆኑን ነው የዘርፉ ምሁራን የሚያስረዱት።<br />
ይህ ስልት ግዑዙ ነፍስ እንዲዘራ፣ ደብዛዛው<br />
ብሩህ እንዲሆን፣ ረቂቁ እንዲገዝፍ ከመርዳቱም<br />
በላይ ተገላጩ የስሜት ህዋሳትን ነክቶ ብሩህ ምስል<br />
በመፍጠር በዓይነ ህሊና እንዲታይ፣ በእዝነ ህሊና<br />
እንዲሰማ፣ ጣዕምና ለዛው እንዲታወቅ የማድረግ<br />
ኅይል እንዳለው ነው ምሁራኑ የሚያስረግጡት።<br />
ከዚህ አንፃር መሀመድ ሰልማን በሚያስገርም<br />
ሁኔታ ተሳክቶለታል። ከላይ ለአብነት የጠቀስናትን<br />
የፒያሳ ቆንጆ ታሪክ ልብ በሉ፡፡ የሚከተላትን<br />
ወጣት ሹክሹክታ ብቻ ሰምታ ‹ምን አልክ› ስትል<br />
ትታያችሁ። ያ ቤት በጭቃ ግድግዳ ነው የተሰራው<br />
ወይስ በካርቱን? በካርቱንስ ቢሆን ሹክሹክታን እንዴት<br />
ያሰማል? አይታያችሁም በመሐመድ ብዕር ውስጥ<br />
የዚያች ቆንጆ ልጅ ሰፈር ጉስቁልና? ቤቶች እንዴት<br />
ችምችም ብለው እንደተሰሩ?<br />
ይህ ብቻ አይደለም፤ መለመድ በእያንዳንዱ<br />
ታሪክ ውሰጥ በስላቁ ያስቀናል። እያሳቀን ስቃይና<br />
ሰቆቃን ያሳየናል። እናም ከራሳችን ጋር እንዋቀሳለን።<br />
ከአስተሳሰባችን ንቅዘት ጋር እንብሰለሰላለን። በትካዜና<br />
በቁጭት እንትከነከናለን። የወደፊት ህይወታችንን<br />
በሥጋት እናስተውላለን።<br />
መሀመድ ሰልማን በትረካው ከሚያሳየን<br />
ዕውነታ ውጪ ለማንም ለምንም አይወግንም።<br />
እንዲያም ይበል እንጂ በፍፁም ቅንነትና ጨዋነት<br />
ለኢትዮጵያዊነትና ለመልካም እሴቶቿ ከመወገን<br />
ወደኋለ አይልም። ግን ደግሞ ውግንናው ንፅህናውን<br />
የጠበቀ ነው። ‹‹ሼ መንደፈር በመርካቶ››ን ሊነቅሱ<br />
ይችሏል። እነሆ፡-<br />
‹‹… በየአጋጣሚው የማነባቸው አዳዲስ<br />
መንፈሳዊ መፅሐፍትም ስለፍቅር የሚሰብኩት<br />
ቃላት ጎድለውባቸዋል። ይልቁንም መጪው ዘመን<br />
በኃይማኖቴ ላይ አደጋ የሚያንዣብብበት እንደሚሆን<br />
የሚተነብዩና ነቅቼ እንድጠብቅም የሚያስጠነቅቁ<br />
ናቸው። በተቀራኒው ጎራ የሚፃፉ መፅህፍትም<br />
በተመሳሳይ መልኩ ተናዳፊ ናቸው።… ከቤተ ሙከራው<br />
ሲወጡም ብዙ አማኝን የሚያስቀይም ውጤት ይዘው<br />
እኛን ብቻ ስሙ ሲሉ ይንጎራደዳሉ። ያንኑ በመፅሐፍ፣<br />
በሲዲ፣ በቲ-ሸርት ካልታተመልን ይላሉ። የእኔዋ<br />
የአሁኗ መርካቶ በዚህ ሁሉ ተቃርኖ የተሞላች ናት።<br />
በዚህ ዓመት በጋራ የተጀመሩት የፍልሰታና የረመዳን<br />
ጾሞች ደግሞ ተቃርኖውን አጉልተው እያሳዩኝ ነው።<br />
በመርካቶው ሼ መንደፈር።…›› (ገፅ 146)<br />
መሐመድ ሳልማን ከኃይማኖት ሥነ<br />
ምግባር አልባነት እስከ ትምህርት ጥራት ውድቀት፣<br />
ከፖለቲካ ግራ መጋባት እስከ ማህበራዊ ህይወት<br />
ዝቅጠት፣ ወዘተ ያልዳሰሰው ጉዳይ የለም። በዚህ<br />
ትረካው ስለ ትግራይ ህዝብ ታዝናላችሁ። ስለ<br />
አዲግራት ታዝናላችሁ። ስለ ትግራይ እናቶች<br />
ታለቅሳላችሁ።<br />
‹‹…በአዲግራት የሰማሁት የአፈሣ<br />
ታሪክ አስደንቆልኛል። ለምሳሌ ሰርግ ላይ የነበሩ<br />
ወንድማማቾች ከታደሙበት ሰርግ ድንኳን ታፍሰው<br />
ተወስደዋል። ታላቅ በጦርነቱ ህይወቱ ሲያልፍ፣<br />
ታናሽ ህይወቱ ተርፏል። ይህንን ታሪክ የነገሩኝን<br />
ወዳጆቼን ይህ የሆነው በደርግ ጊዜ ነው? እያልኩ<br />
ሞግቻቸዋለሁ። አይደለም። … መቀሌ ላይ ደግሞ<br />
ዘወትር ማለዳ የቀበሌ ወታደር መልማዮች በየስርቻው<br />
በየመንደሩ ይዞሩ ነበር፡፡ ያገኙትን ኮበሌ ቀብ<br />
አድርገው ስልጠና ያስገቡታል። በየጎዳናው ወጣት<br />
ሲጠፋ ደግሞ ቤት ለቤት አሰሳና አፈሳ ተጀመረ። …<br />
እናቶች ልጆቻቸውን ለመሸሸግ ተገደዱ። ይህ ታሪክ<br />
የደርግ አይደለም። … ‹ደብሪ›ን (ጎተራ) በጦርነቱ ጊዜ<br />
እናቶች ልጆቻቸውን ለመደበቅ ተጠቅመውበታል…››<br />
(ገፅ 167)<br />
መሐመድ ስልማን መራሩን የህይወት<br />
ዕውነታ በቀላል አገላለፅ ቁልጭ አድርገን እንድንጋት<br />
ግድ ይለናል። ያላየነውን የቅንጦት የሚመስል የዘቀጠ<br />
እና መረን የለቀቀን ብልግና እያሳየን እንድንጠየፍ<br />
ያደርገናል። ‹‹የጀሚላ መዳፎች›› (ከገፅ 119-129)<br />
ለዚህ ከበቂ በላይ አስረጅ ናቸው። ውቦቹ የጀሚላ<br />
መዳፎች ፀያፍ ተግባራት የማህበረሰባችንን ብልሹነት<br />
ለመግለፅ በእርግጥም ከበቂ በላይ ናቸው።<br />
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሶሲዮሎጂ<br />
ዲፓርትመንት ሌክቸረር የሆኑት አቶ ደረሰ ጌታቸው<br />
በመፅሐፉ መግቢያ ‹‹መሿለኪያ›› በሚል ርዕሥ<br />
ባሰፈሩት አስተያየት የሚከተለውን ያሉት ለዚህ<br />
ይመስለኛል።<br />
‹‹አዲስ አበባን ሰንገው የያዙ ችግሮችንም<br />
መሐመድ በሰላ ፅሁፉ ነቅሶ አውጥቷቸዋል።<br />
ሥራ አጥነት፣ የኑሮ ውድነት፣ ሴተኛ አዳሪነትን<br />
የመሳሰሉትን የኑሮ ችግሮች ላይ የራሱን ቁዘማ<br />
(ሪፍሌክሽን) ያስነብበናል። አዲስ አበባን ሲያስስ<br />
የከተማ አውቶብስ አይቀረውም። ከዚያ ወጣ ብሎም<br />
የደረሰባቸውን የሀገሪቱ ክፍሎች በከተሜ ዕይታ<br />
ታዝቧቸዋል። ‹ገጠርን ማዕከል ባደረገ› የልማት<br />
ስትራቴጂና የሰው ኃይል ስብስብ የሚታወቀው<br />
<strong>መንግስት</strong>ና የከተማው ባለስልጣኖች ይህን መፅሐፍ<br />
ቢያነቡት ጥሩ ነው…››<br />
ምን ባሥልጣናት ብቻ? የሀገሪቷ<br />
ህዝብ በሙሉ ቢያነበው ጥሩ ነው እንጂ። መቼም<br />
ባለሥልጣናቱ ያነበንባሉ እንጂ አያነቡም። ህዝቡ ነው<br />
ማንበብ ያለበት። ምክንያቱም ‹‹ፒያሳ›› (መሀሙድ<br />
ጋ ጠብቂኝ) መፅሐፍ ውስጥ የሁሉም ህይወት አለ።<br />
በጥበብና በጥበበኛ ብዕር የተኳለ። ያ ብዕር የመሐመድ<br />
ሠልማን ብዕር ነው። የምናየውን ዕውነት፣ ባላየነው<br />
መንገድና ዕይታ አሳምሮ፣ እንደዋዛ አዋዝቶ ልክ<br />
ልካችንን የሚነግረን ድንቅ ብዕር። አቦ! ‹‹እጅ በነክ››<br />
ብዬ ባሳርግ ነው የሚሻለው። እጅ በነክ!!!
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />
መልካም ዓዲስ ዓመት<br />
S ´ “ —<br />
‹‹አሰብ የማን ናት?››<br />
መፅሐፍ ለንባብ በቃ<br />
አለም አቀፍ የህግ ባለሙያ የሆኑት እና በኢትዮጵያ ፖለቲካ<br />
ውስጥ ጉልህ ሚና የነበራቸው ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማርያም<br />
አሰብ የማን ናት? በሚል ርዕስ መፅሐፍ ፃፉ፡፡ ዶ/ር ያዕቆብ<br />
የመፅሐፉን ዋና አላማ ሲገልፁም ታሪክን፣ አለም አቀፍ ሕግን፤<br />
የቀይ ባህር አፋሮች አንድነትና መብትን ከግንዛቤ አግብቶ የአሰብ<br />
ወደብ ሕጋዊ ባለቤት ኤርትራ ወይስ ኢትዮጵያ ነች ለሚለው<br />
ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት መሞከር እንደሆነ ነው፡፡ በተለያዩ<br />
ዘመናት አሰብን ለማስመለስ የተደረጉ ትግሎችን፤ ስለ አልጀርሱ<br />
ስምምነት እንዲሁም የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን አስተያየት<br />
ከመያዙም በተጨማሪ ወደብ ለአንድ አገር ያለውን ኢኮኖሚያዊ<br />
ፋይዳም አካቶ ይዟል፡፡<br />
መፅሐፉ በ13 ምዕራፎች የተከፋፈለ ሲሆን 260 ገፆች አሉት፡<br />
፡ በመፅሐፉ የተወሰነ ገፅ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ያቀረቡ ሲሆን<br />
ይህንንም በመግቢያቸው አሰብን ወደ ኢትዮጵያ ለማስመለስ<br />
የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ድጋፍ ስለሚያስፈልግ ለእነሱ መጠነኛ<br />
ግንዛቤ ለማስጨበጥ እንደተዘጋጀ ገልፀዋል፡፡<br />
መፅሐፉ በ45 ብር በመሸጥ ላይ ሲሆን ከሽያጩ የሚገኘው<br />
ገቢ ለበጐ አድራጐት ድርጅቶች እንደሚውልና መታሰቢያነቱን<br />
ለዴሞክራሲ፤ ለፍትህና ለአንድነት ሲታገሉ ለወደቁ<br />
ኢትዮጵያዊያን አድርገዋል፡፡<br />
በኳንተም ፊዚክስ ላይ<br />
ውይይት ተካሄደ<br />
በዶክተር አቡሽ አያሌው በተፃፈው ‹‹አልፋና ኦሜጋ››<br />
መፅሀፍና በውስጡ ስለተገለፃው ‹‹ኳንተም ፊዚክስ›› ምንነትና<br />
አጠቃላይ ሀሳብ ላይ ውይይት ተካሄደ። ውይይቱ የተካሄደው<br />
ባለፈው ሳምንት እሁድ ረፋድ ላይ በጥቁር አንበሳ ት/ቤት<br />
የስብሰባ አዳራሽ ውስጥ ሲሆን የእኛና የዩኒቨርስ ማንነት<br />
በኳንተም ፊዚክስ መነጽር ሲታይ ምን ገጽታ እንዳለው፣<br />
ሳይንሱ በህይወታችን ስኬታማነት፣ ሰላምና ፍቅር እንዲሁም<br />
ም ብልፅግና በኩል የሚጫወተውን ሚና እና ተያያዥ ነገሮች<br />
ለህብረተሰቡ ግልፅ ለማድረግ ውይይቱ መካሄድን የመፀሀፉ<br />
ደራሲና አዘጋጅ ዶ/ር አቡሽ አያሌው ገልጿል። የሳይንሱን<br />
ትክክለኛነት በህዝቡ አስተሳሰብ ውስጥ ለማስረፅ ተከታታይ<br />
ውይይቶች እንደሚካሄዱም ነው የተገለፀው።<br />
“የትሮይ ፈረስ” እና ‹‹ገንዘብና<br />
ፍቅር›› ፊልሞች ተመረቁ<br />
በአስቴር ፊልም ፕሮዳክሽን የተዘጋጀውና 1 ሰዓት ከ40 ደቂቃ<br />
የሚፈጀው ‹‹የትሮይ ፈረስ›› ፊልም ባለፈው ሰኞ ነሐሴ 30 ቀን<br />
2003 ዓ.ም በብሔራዊ ቲያትር አዳራሽ በይፋ ተመረቀ።<br />
በቤተሰብ ተፅዕኖ ምክንያት ወንድ ቀርባ የማታውቅ አንዲት<br />
ቆንጆን ለመርታት በሚደረግ ጥረት ላይ የታሪኩን ጨብጥ<br />
የመሠረተው ይህ ፊልም፣ በ1994 ዓ.ም ለህትመት ከበቃው<br />
‹‹የትሮይ ፈረስና ሎሎች አጫጭር ታሪኮች›› ከተሰኘ መፅሐፍ<br />
መነሻ ሀሳቡ የተወሰደ መሆኑ በምርቃት ሥነ ሥርዓቱ ወቅት<br />
ተገልጿል። ይህም የሀገራችንን የአጫጭር ልብ ወለድ ደራሲዎች<br />
ሥራ በማግዘፍ፣ ደራሲዎችን ሊያበረታታ ይችላል ተብሏል።<br />
የፊልሙ ደራሲ አሳምነው ባርጋ ሲሆን፣ ዳይሬክተሩ ደግሞ<br />
አርቲስት ቢንያም ወርቁ ነው።<br />
አርቲስት ሰለሞን ቦጋለ፣ ጌታሁን ሰለሞን፣ ሸዋፈራሁ<br />
ደሳለኝ፣ ይገረም ደጀኔ፣ እፀህይወት አበበና ሎሎች ታዋቂና<br />
አዳዲስ ተዋናዮችም ተሳትፈውበተል። ፊልሙን ሰርቶ<br />
ለማጠናቀቅም 580 ሺህ ብር ወጪ መጠየቁም ታውቋል።<br />
እንዲሁም በኤሊያስ ወርቅነህ ፕሮዲዩስ ተደርጎ በጋላክሲ<br />
ፊልም ፕሮዳክሽን የቀረበው ‹‹ገንዘብና ፍቅር›› ፊልም ሀሙስ<br />
በ8፡00 ሰዓት በሀገር ፍቅር ቲያትር ቤት የኪነ-ጥበብ አፍቃሪያን<br />
ታዋቂ ሰዎችና ጥሪ የተደረገላቸው አንግዶች በተገኙበት<br />
ተመርቋል። አስቂኝ የሆነው ይህ የፍቅር ፊልም 1፡40 ሰዓት<br />
ርዝመት ያለው ሲሆን በርካታ ተዋንያን እንደተሳተፉበትም<br />
ተገልጿል።<br />
‹‹ንቃት›› ፊልም ዛሬ ይመረቃል<br />
በደራሲና አዘጋጅ ዮናስ ጌታቸው ተሰርቶ በሰርድ አይ ፊልም<br />
ፕሮዳክሽን የቀረበው ‹‹ንቃት›› ፊልም ዛሬ በአዲስ አበባ ቴአትርና<br />
ባህል አዳራሽ ይመረቃል። ፊልሙን ሰርቶ ለማጠናቀቅ ከአንድ<br />
ሚሊዮን ብርና ከሁለት አመት በላይ መፍጀቱን አዘጋጆች<br />
ለአውራምባ ታይምስ በላኩት መግለጫ አስታውቀዋል። ልብ<br />
አንጠልጣይ የፍቅር ፊልም እንደሆነ የተነገረው ‹‹ንቃት›› ህዝቡ<br />
ስለ ኤች. አይ. ቪ ግንዛቤ ቢኖረውም ችግሩ ባለመቀረፉ ላይ<br />
እንደሚያጠነጥን እንዲሁም ሙሉ በሙሉ በአሜሪካ አገር<br />
መሠራቱን ጨምረው ገልፀዋል።<br />
ፋንቱ ማንዶዬ 60ኛ የልደትና<br />
44ኛ የሞያ ቆይታውን አከበረ<br />
አንጋፋው የጥበብ ሰው አርቲስት ፋንቱ ማንዶዬ 60ኛ<br />
የልደት በአሉንና 44ኛ የኪነ-ጥበብ ቆይታውን ባለፈው ማክሰኞ<br />
በደማቅ ሁኔታ አከበረ። ጳጉሜ 1 ቀን በአዲስ አበባ ቲያትርና<br />
ባህል አዳራሽ ከቀኑ 8ሰዓት ጀምሮ በተዘጋጀው በዚህ ፕሮግራም<br />
ላይ እጅግ በርካታ የሙያ አጋሮቹ ተገኝተው እንኳን አደሰረህ<br />
ብለውታል። በእለቱ በአርቲስት ተስፋዬ አበበ (ፋዘር) የተፃፈ<br />
‹‹እሱ ማን ነው›› የተሰኘ ህብረ ዝማሬ በተስፋዬ ቲያትር<br />
ማደራጃ አባላት የቀረበ ሲሆን የተለያዩ ስጦታዎችና ሽልማቶች<br />
ለአርቲስት ፋንቱ ተበርክተውለታል። በኪ- ጥበብ ቆይታው<br />
33 የመድረክ ቴአትሮችን፣ 11 የቴሌቪዥን እንዲሁም ሁለት<br />
ተከታታይ የሬዲዮ ድራማዎችን መስራቱ ተገልጿል።<br />
ጥበብ ሀበሻ በልዩ ፕሮግራም<br />
በአሉን ሊያከብር ነው<br />
በሀበሻ ሚዲያና ፕሮሞሽን ሰርቪስ የሚቀርበው ‹‹ጥበብ<br />
ሀበሻ›› የሬዲዮ ፕሮግራም አውድ አመቱን አስመልክቶ ልዩ<br />
የኪነ-ጥበብ ፕሮግራም አዘጋጀ። ዘወትር አርብ ከ9-11 ሰዓት<br />
እና ዘወትር እሁድ ከ6-8 ሰዓት በኪነ-ጥበብ፣ በቤተሰብና በፍቅር<br />
ዙሪያ የመረጃ ፕሮግራሞችን በ96.3 ኤፍ ኤም የሚያቀርበው<br />
ጥበብ ሀበሻ በበዓሉ ዋዜማ ምሽት ከ3-6 ሰዓት የተለያዩ ታዋቂ<br />
ሰዎችን፣ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎችንና አዝማሪዎችን በመጋበዝ<br />
በቀጥታ ሥርጭት እንደሚያስተላልፍ የፕሮግራሙ አዘጋጅ<br />
አብርሀም ግዛው ገልጿል።<br />
እንኳን አደረሰህ ግዛቸው!<br />
እንኳን አብሮ አደረሰን! ሰላም ነው?<br />
በአሉን ለመቀበል ምን ምን ዝግጅቶች እያደረክ ነው?<br />
እርግጥ ብዙ ዝግጅት አላደርግም። ግን ያው<br />
እንደማንኛውም ሰው ማድረግ የሚገባኝን<br />
አደርጋለሁ።<br />
ዘመን መለወጫ ሲመጣ ምን ምን የምታስታውሰው ነገር አለህ?<br />
አዲስ ዓመት ሲመጣ ከሌሎቹ በአላት ለየት<br />
የሚልበት የራሱ ድባብ አለው፡፡ በውስጥሽ<br />
የአዲስነትና የተስፋ ስሜት ያጭራል፡፡ እንደገና<br />
ደግሞ በዓሉ በየትኛውም በሳምንቱ ቀናት ሊሆን<br />
ይችላል። እስከዛሬ ለዋዜማው ስንሰራ ኢቭ እሁድ<br />
ቀን ውሎ አላስታውስም። የዘንድሮው ኢቭ እሁድ<br />
መሆኑ በራሱ ደስ ይላል። አመት በዓል ሲመጣ<br />
ቤት ውስጥ የሚደረገው ሽርጉድ ድባቡ ሁሌም<br />
ይታወሰኛል። ከዛ በተረፈ የተለየ የማስታውሰው<br />
ነገር የለም። በእያንዳንዱ አመት እቅዶች ስላሉኝ<br />
እነሱን አስታውሳለሁ።<br />
በ2003 ምን አቅደህ ምን ተሳካልህ?<br />
የተወሰኑ ነገሮች አቅጀ ነበር። በእቅዴ ያልተካተቱ<br />
በርካታ ነገሮችም ተሳክተውልኛል። ራሴን አንደ<br />
እድለኛ እቆጥራለሁ። ይሄ ነው ያ ነው ከማለት<br />
ተቆጥቤያለሁ። ይህ የእግዚአብሔር ስራ ነውና።<br />
ለበዓል በግ የመግዛት ልማድ አለህ?<br />
አዎ። እገዛለሁ።<br />
ለዚህ በዓል በግ ገዝተህ ቢጠፋ፣ ቢሞት፤ አሊያም በመኪና ቢገጭ<br />
ደግመህ ትገዛለህ ወይስ ለእኔ ባይለው ነው ብለህ ትተወዋለህ?<br />
[በጣም እየሳቀ] ይሄ ከባድ ጥያቅ ነው፡፡ ግን በጉ<br />
ባልሽው መንገድ አደጋ ቢደርስበት ከእኔም ሆነ<br />
ከቤተሰቦቼ ደስታ አይበልጥምና ደግሜ እገዛለሁ<br />
እንጂ አይገርመኝም። ዋናው እኔ ደህና ልሁን<br />
እንጂ ምናባቱ።<br />
ኃብታም ነኝ ለማለት ነው?<br />
እንደዛ ሳይሆን የበጉ መሞት ወይም መጥፋት<br />
ከደስታዬ አይበልጥም ለማለት እንጂ ዋጋው ቀላል<br />
ነው ለማለት አይደለም።<br />
ዶሮ መገነጣጠል ትችላለህ?<br />
እኔ ኧረ አልችልም! እንዴት አይነት ነገር ነው<br />
ባካችሁ?! ምን መሰለሽ፤ በአል ሲሆን ቄጤማው፣<br />
የቡና ስነ-ስርዓቱ፣ ሬዲዩው የሚዘፍነው የበዓል<br />
ዘፈን . . . ሁሉ ነገር ደስ ስለሚለኝ እቤት ዶሮ<br />
ሲሰራ፣ ሲገነጣጠል አያለሁ፤ አብሬም እሆናለሁ፡፡<br />
ግን ዶሮ መገነጣጠልን አስቤው አላውቅም።<br />
በበዓል ብዙ ምግብ በልተህ ታውከህ ታውቃለህ?<br />
የባሠ አታምጣ! [ረዥም ሳቅ] በመጀመሪያ ደረጃ<br />
የምግብ ፍላጎቴ ጥርቅም ብሎ የሚዘጋው በበዓል<br />
ጊዜ ነው። እንኳን ብዙ በልቼ ልታወክ ይቅርና።<br />
በልጅነትህ አበባ ስለህ እየዞርክ ትሰጥ ነበር?<br />
አዎ በጣም! አበባ ስዬ መስጠት ብቻ ሳይሆን<br />
ከየህፃናቱ በ10 ሳንቲም እየገዛሁ እኔ በ15ና<br />
በ25 ሳንቲም የመሸጥ ቢዝነስ ጀምሬ አትራፊ<br />
የነበርኩበትን ጊዜ አስታውሳለሁ። ይሄ እንደውም<br />
ለዚህ በዓል መታሰቢያ ይሁንልኝ፡፡ የሚገርምሽ<br />
አበባ በመሳልም በኩል የሚስተካከለኝ አልነበረም።<br />
ዲዛይነር ነበርኩ ማለት ይቻላል።<br />
የምትስላቸውን ነገሮች ታስታውሳለህ?<br />
አደይ አበባ፣ የሚካኤልን ሥዕል፣ አደይ አበባ ላይ<br />
መስቀል በመሳል መልካም አዲስ ዓመት የሚል<br />
እፅፍና አመተ-ምህረቱን ከጎኑ አድርጌ እስል ነበር።<br />
ቀለም የምገዛው ወይዘሮ ማሚቱ ከሚባሉ የልብስ<br />
ቀለም ከሚሸጡ ሴትዮ ነበር። ቀጨኔ የታወቁ<br />
የልብስ ቀለም ሻጭ ነበሩ። [ቀጨኔ የሽመና ሥራ<br />
የሚካሄድበት አካባቢ መሆኑን ልብ ይሏል።]<br />
ቀለሙን ከገዛሁ በኋላ መጀመሪያ ሸንበቆ እፈልግና<br />
እዛ ላይ ጥጥ እጠመጥማለሁ። ከዛም መቀባት ነው<br />
አልኩሽ።<br />
ስኬች ያደረከው ላይ ማለት ነው?<br />
እንዴ! ተይ እንጂ! ሀበሽኛ አድርጊው እንጂ።<br />
‘ዲዛይን ያደረግከው ላይ’ ለማለት ነው። [‘ዲዛይን’ም<br />
እኮ ግን . . . ???]<br />
1<br />
አፍታ<br />
“እኔ ጋር ሥራ እንጂ ውበት<br />
የሚባል ነገር የለም”<br />
ድምፃዊ ግዛቸው ተሾመ<br />
በባህል ዘፈኖቹ በዙዎች ጎጃም ተወልዶ እንዳደገ ቢገመቱም እሱ ግን የአዲስ አበባ ልጅ መሆኑን ይገልፃል። ከተለያዩ ድምፃውን ጋር በጋራ አልበም በማውጣት ወደሙዚቃው ጠልቆ የገባ ሲሆን<br />
በ2001 ዓ.ም ‹‹ይሁና›› የሚል የራሱን አልበም በመልቀቅ ተደማጭነትን አግኝቷል። ውበቴ ሥራዬ ነው ከሚለው ድምፃዊ ግዛቸው ተሾመ ጋር ናፍቆት ዮሴፍ አዝናኝ ቆይታ አድርጋለች።<br />
እሺ ‘ዲዛይን’ ያደረከው [የነደፍከው]ላይ? ሂሴን ውጫለሁ<br />
እና እልሻለሁ አበባ ገዝቶ በመሸጥም በመሳልም<br />
አንደኛ ነበርኩ።<br />
የሠርግ ሥራ ሽቀላው እንዴት ይዞሀል?<br />
ኧረ በጣም አሪፍ ነው! በነገራችን ላይ ከሽቀላ አንፃር<br />
ብቻ አትይው፡፡ በተለይ ሰዎች በሠርጋቸው እለት<br />
ሲደሰቱ ማየት ምን ያህል እንደሚያረካ ልነግርሽ<br />
አልችልም። ሽቀላው እንዳለ ሆኖ ማለት ነው። እናም<br />
እኔ ራሱ የሠርግ ካሴት ሰርቼ አጠናቅቄያለሁ።<br />
ከ2004 እቅዴ አንዱ እሱን ማሳካት ነው።<br />
ቢሰራም ባይሰራም በአዲስ አመት ዕቅዶች ይታቀዳሉ። ከካሴቱ ውጭ<br />
ምን ያቀድከው ነገር አለ?<br />
ከላይ የለገፅኩት የሰርጉን ካሴት ለአድማጭ ማድረስ<br />
አንዱ ነው። ሌላው በ2004 ካቀድኩት ውስጥ የራሴን<br />
ባንድ አቋቁሜ በራሴ ባንድ ሰርግ መስራት ነው።<br />
የእግዚአብሔር ፈቃዱ ይሁን።<br />
አንዳንድ ሰዎች መጠጥ የማይወዱ ቢሆኑም እንኳን በአል ሲመጣ<br />
ከተለያዩ መጠጦች ይቀማምሳሉ። ከቢራውም፣ ከጠጁም፣<br />
ከጠላውም፣ ከውስኪውም . . . ። አንተ በበአል ምን መጠጣት<br />
ያስደስትሀል?<br />
እኔ የማልዋሽሽ ነገር፣ እናቴ ቤት ሁሌም በበአል ጠጅ<br />
አለ። ጠጁ ልስልስ ያለና ለተማሪ የሚሰራ አይነት<br />
ነው። ወደ ብርዝ የሚያደላ ማለት ነው። እናቴ ቤት<br />
እሱን ቁጭ ብዬ ስጠጣ ትክክለኛ የአመት በአል<br />
ስሜት ይሰማኛል። በተረፈ ከዚህ በላይ ለመጠጥ ብዙ<br />
ፍላጎት የለኝም።<br />
እንጉርጉሮህን የሰሙ ብዙዎች ግዛቸው ጎጃሜ ነው እንደሚሉ<br />
ታውቃለህ?<br />
በመጀመሪያ እኔ ጎጃሜ ብሆን ደስ ነው የሚለኝ።<br />
ከዛ በላይ ግን ኢትዮጵያዊ ነኝ። ይህ ደግሞ በጣም<br />
ያኮራኛል፡፡ እንደዛም ሆኖ ተወልጄ ያደግኩት<br />
አዲስ አበባ ውስጥ ቀጨኔ መድኃኒያለም<br />
አካባቢ ነው።<br />
ከመልክና ከቁመና ጋር በተያያዘ የግዛቸው ውበቱ<br />
አንገቱ ነው ይባላል፡፡ ትስማማለህ?<br />
የእኔ ውበቴ ወንድነቴ ነው።<br />
ወንድነቴ ስትል?<br />
ወንድ መሆኔ ነዋ!<br />
የአንገትህንስ ነገር ብዙ አትስማማበትም?<br />
እኔ አላውቅውም። እኔ ጋር ውበት<br />
የሚባል ነገር የለም። ሥራ ብቻ ነው።<br />
፡ ግን በጉ ባልሽው መንገድ አደጋ<br />
ቢደርስበት ከእኔም ሆነ ከቤተሰቦቼ ደስታ<br />
አይበልጥምና ደግሜ እገዛለሁ<br />
እንጂ አይገርመኝም።<br />
ዋናው እኔ ደህና<br />
ልሁን እንጂ<br />
ምናባቱ።<br />
በመጀመሪያ ወንድነቴ ነው ውበቴ ያልከኝ ወንድነት ብቻውን<br />
ውበት ነው ማለትህ ነው?<br />
ወዴት ወዴት! እኔ እንደዚህ ወጣኝ? ወንድ<br />
አሁን ቆንጆ ሆነ አልሆነ ለእኔ ግድ የለኝም።<br />
ሴት ልጅ ግን ውበትን በመቀባባትና በተለያዩ<br />
ዘዴዎች ታመጣዋለች። እኔ በግሌ ግን ቆንጆ<br />
ሆንኩ አልሆንኩ ግድ የለኝም። አላስበውምም።<br />
ስራ ላይ ነው ትኩረቴ።<br />
እናስ ቆንጆ ነኝ ብለህ ታምናለህ?<br />
ቆይ በናትሽ . . . ይሄ የሚያስጠላ ጥያቄ<br />
አይመስልሽም? [መመለስ አልፈለገም።]<br />
እስከዛሬ ፊት ለፊት ያላገኘኸው ግን ደግሞ የምታደንቀውና<br />
በዚህ አጋጣሚ እንኳን አደረሰህ ማለት የምትፈልገው ካለ?<br />
እኔ በጣም ደስ የሚሉኝና በጣም የማደንቃቸው<br />
ጠቅላይ ሚኒስትሩን ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር<br />
መለስ ዜናዊን፣ “እንኳን ለ2004 ዓ.ም አዲስ<br />
አመት ከነቤተሰብዎ በሰላም አደረሰዎት! አመቱ<br />
የጤና፣ የሰላምና መልካም የአመራር ጊዜ<br />
እንዲሆንልዎ እመኝልዎታለሁ!” በይልኝ።<br />
ለኢትዮጵያ ህዝብ የትኛውን ዘፈንህን ልጋብዝልህ?<br />
በመጀመሪያ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ እንኳን<br />
ለአዲሱ አመት በሰላም አደረሳችሁ በይልኝ። ከዛም<br />
‹‹አውዳመቱ›› የተሰኘውን ዘፈን ጋብዣቸዋለሁ።<br />
አመሰግናለሁ።<br />
11<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ
12<br />
በኤልያስ ገብሩ<br />
ከተቋቋመ ሦስት ዓመታትን ያስቆጠረው<br />
ጃካራንዳ ኢንተግሬትድ አግሮ ኢንዱስትሪ<br />
አ.ማ በተለያዩ ጊዜያቶች ለሀገር ውስጥ<br />
መገናኛ ብዙሃን የሚያዘጋጃቸውን የመስክ<br />
ጉብኝቶች መሠረት በማድረግ የአውራምባ<br />
ታይምስ ዝግጅት ክፍል እሁድ ነሐሴ<br />
29/2003 ዓ.ም ድርጅቱ ተግባራዊ ሥራውን<br />
እያከናወነ በሚገኝበት በአዋሽ መልካሳ<br />
የግብርና መስክ ላይ ከቀትር ጀምሮ ተገኝቶ<br />
ነበር፡፡ ምንም እንኳን ያለነው በክረምት ወራት<br />
መገባደጃ ላይ ቢሆንም፣ በወቅቱ በአዋሽ<br />
መልካሳ የከረረ ፀሀይ ሳይኖር የሙቀት ወበቁ<br />
ግን ከላይ የተደረበ ልብስን የማስወለቅ አቅም<br />
ነበረው፡፡<br />
አዋሽ መልካሳ ደርሰን ከናዝሬት ወደ አሰላ<br />
በሚወስደው ዋና መንገድ በስተቀኝ በኩል<br />
በሚገኝ ኮረኮንጅ መንገድ ወደ ውስጥ ጥቂት<br />
መቶ ሜትሮች በመኪና ከገባን በኋላ አንድ<br />
አነስተኛ ድልድይ ጋር ደርሰን በመቆም<br />
ከመኪና ወረድን። ቀጥሎም፣ ለመስክ ጉብኝቱ<br />
በስፍራው ለነበርነው ለዚህ ፅሁፍ አቅራቢና<br />
ለአውራምባ ታይምስ ማኔጂንግ ኤዲተር<br />
ዳዊት ከበደ፣ የአክሲዮን ማሕበሩ የቦርድ<br />
ሊቀመንበርና ዋና ሥራ አስኪያጅ የሆኑት<br />
አቶ ደምመላሽ ወጋየሁ ገለፃ ያደርጉልን<br />
ጀመር<br />
ጥናትን መሠረት<br />
ያደረገ የውኃ ጠለፋ<br />
በጠባቧ ድልድይ ሥር 400 ኩንታል<br />
ክብደት ያለው ኮንክሪት ድንጋይ ተቀብሯል፡<br />
- ወደ ወንጂ ስኳር ፋብሪካ የሚሄዱ ከባድ<br />
ተሽከርካሪዎችን መሸከም እንዲችል ታስቦ፡፡<br />
ከድልድዩ በስተቀኝ የተወሰኑ ሜትሮች ራቅ<br />
ብሎ የአዋሽ ወንዝ እንደደፈረሰ በእርጋታ<br />
ተፈጥሯዊ ጉዞውን ሲያደርግ ይታያል፡፡<br />
የውሃ ሥራዎች ዲዛይንና ቁጥጥር ባለስልጣን<br />
መ/ቤት በወንዙ ላይ በቂ ጥናት አድርጎ<br />
ጃካራንዳ ኢንተግሬትድ አግሮ ኢንዱስትሪ<br />
አ.ማ እያካሄደ ለሚገኘው የልማት ሥራ<br />
አገልግሎት እንዲሰጥ ሁለት ኪሎ ሜትር<br />
የውሃ መስመር ጠለፋና የቦይ ግንባታ<br />
መሥራቱን አቶ ደምመላሽ ይናገራሉ፡፡<br />
በሚፈልገው አቅም ውሃ እንዲያመጣ ተደርጎ<br />
በግንብ በተሰራው ቦይ ውስጥ የሚያልፈው<br />
ውሃ በተገቢ የውሃ ፍሰት ቀመር የተስተካከለ<br />
በመሆኑ በአካባቢው የሚገኙትን የሕብረተሰብ<br />
የግብርና ማሳዎች ከጎርፍ ለመከላከል ትልቅ<br />
ድጋፍ ይሰጣል።<br />
በተፈጥሮ የስበት ኃይል አማካኝነት<br />
አንድ ኪሎ ሜትር ያህል የሚጓዘው ይኼ<br />
የተጠለፈው ውሃ ጃካራንዳ በሰራው መጠነኛ<br />
ግድብ ውስጥ ለመጠራጠም ይገደዳል።<br />
[ሌላው አንድ ኪሎ ሜትር በግፊት ኃይል<br />
የሚንቀሳቀስ ነው] በውሃው መሄጃ ግራና<br />
ቀኝ፣ በተለይም በስተግራ በኩል ያሉት<br />
እንደ ዝግባ፣ ግራርና ባህር ዛፍን የመሳሰሉ<br />
ዛፎች፣ ቁጥቋጦዎችና ሳሮች ከሌላው በተለየ<br />
መልኩ ለምልመው ይታያሉ። …‹‹እነዚህ<br />
በፊት ውሃ በአጠገባቸው በማያልፍበት ጊዜ<br />
የመቅላትና የመድረቅ ባህሪ ነበራቸው››<br />
በማለት ስለሁኔታው በንፅፅሮሽ የገለፁት አቶ<br />
ደምመላሽ፣ በጥናት ተመርኩዞ የተካሄደው<br />
የውሃ ጠለፍ ሥራ በአካባቢው ሥነ-ምህዳር<br />
ላይ አዎንታዊ ለውጥ ማምጣቱን በአፅንዎት<br />
ይናገራሉ። በእርግጥም ለዚህ ጥሩ ምስክር<br />
የሚሆን ነገር ወዲያው ተመለከትን፡፡<br />
በግድቡ አጠገብ ቅርንጫፎቻቸው ተንዥርግጎ<br />
አንገታቸውን ወደ መሬት ዳፋ ባደረጉት<br />
የግራር ዛፎች ላይ በሕብረ-ቀለማት ያሸበረቁ<br />
ወፎች ጎጇቸውን ቀልሰው በነፃነት እየዘመሩ<br />
ነበር።<br />
ጥቅመ- ብዙዋ ትንሿ ግድብ<br />
በአጠቃላይ 300 ሜትር ርዝመትና 10<br />
ሜትር የጎን ስፋት ያላት ትንሿ ግድብ ከጥቂት<br />
ወራቶች በኋላ ለመስኖ ልማት፣ ለከብቶችና<br />
ፍየሎች መጠጥ ውሃና ለሌሎች አገልግሎቶች<br />
ጥቅም ለመስጠት ተዘጋጅታለች። በግድቢ<br />
ውስጥም 11 ሺህ አሳዎች በመርባት ላይ<br />
ሲገኙ ከእነዚህም መካከል አንድ ሺህ ያህሉ<br />
ለቻይናዊያኖች ተሽጠዋል፡፡ በቀጣዩ ዓመት<br />
መስከረም ወር ደግሞ የሚረቡት አሳዎች<br />
ቁጥር 40 ሺህ እንደሚደርስ የሚናገሩት<br />
አቶ ደምመላሽ፣ ይህንን በተመለከተ የሰበታ<br />
አሳ ምርምር ድርጅት ተመራማሪዎች ጥናት<br />
ማካሄዳቸውን ይገልፃሉ። ከግድቡም በላይ<br />
ትንሽ ሞልቶ የሚፈስሰው ውሃ ተመሳሳይ<br />
መንገድን ተከትሎ ወደ ሌላኛው የአካባቢ ስፍራ<br />
በአነስተኛ መጠን ሲጓዝ ይታያል፡፡ ሆኖም<br />
ግን፣ እንደ አክስዮን ማህበሩ ኃላፊ ንግግር<br />
ከሆነ ጃካራንዳ ይኼንን የውሃ መስመር 300<br />
ሜትር ያህል አስተካክሎ በማዘጋጀት ሌላ<br />
ተመሳሳይ የአሳ ማርቢያ ግድብ ለመስራት<br />
የአጭር ጊዜ ዕቅድ ነድፏል።<br />
ከግድቡ ጎን ከፍ ብሎ ደግሞ አዲስ<br />
የተሰራ የውሃ መሳቢያ ፓምፕ የሞተር<br />
ክፍል የሚገኝ ሲሆን፣ በኤሌክትሪክ ኃይል<br />
የሚሰራው ይኼ ፓምፕ 90 ኪሎ ዋት<br />
ኃይል ሲኖረው በሰኮንድ 75 ሊትር ውሃ<br />
የመሳብ አቅመ አለው። ይኼም በ45 ሜትር<br />
ርቀት ላይ ተሰርቶ ሙሉ በሙሉ ሊጠናቀቅ<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
ለተቃረበውና ሲያልቅ አምስት ሺህ ኪውቢክ<br />
ሊትር ውሃ የመያዝ አቅም ላለው የውሃ<br />
ማጠራቀሚያ ገንዳ (Reservoir) ውሃን<br />
በፍጥነት ያቀብላል። አንዴ በገንዳው ውስጥ<br />
የሚጠራቀመው ውሃ ለአንድ ሳምንት<br />
ያህል ለካምፓኒው የተለያዩ ስራዎች<br />
አገልግሎት በቂ እንደሆነ የተናገሩት አቶ<br />
ደምመላሽ፣ የውሃ መስመሮች ተዘርግተው<br />
መጠናቀቃቸውንና የኤሌክትሪክ ኃይል<br />
አቅርቦት ለማግኘት ደግሞ ትራንስፎርመር<br />
በጥሩ ሁኔታ መተከሉን ያስረዳሉ፡፡<br />
ሕብረተሰብን ያማከለ ልማት<br />
እስከ ግድቡ ድረስ ባሉት መሬቶች ግራና<br />
ቀኝ ከሚገኙት ቦታዎች መካከል ሁለት<br />
ሁለት ሜትር ብቻ ለጃካራንዳ የሥራና<br />
የመንገድ አገልግሎት በመተው በቁጥቋጦ<br />
በተለይም፣ በቁልቋል የተሸፈኑትን መሬቶች<br />
በመመንጠር በአካባቢው ለሚገኙ 500 ያህል<br />
ወጣቶች ለግብርና ልማት እንዲጠቀሙበት<br />
በዕቅድ ተነድፎ ወደ ሥራ እየተገባ ያለበት<br />
ሁኔታ መኖሩን ኃላፊው ይገልፃሉ። በጉዳዩ<br />
ዙሪያም፣ ከፌዴራል <strong>መንግስት</strong> የኦሮሚያ<br />
ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት ም/ኮሚሽነር<br />
አቶ ሳሙኤል ገዳ ጋር በአካል ተገናኝቶ<br />
በመምከርና አካባቢውን በማስጎብኘት ጥሩ<br />
መግባባት ላይ ተደርሶ ይሁንታ ሊገኝበት<br />
ችሏል። ለወጣቶቹም የተለያዩ የአትክልት<br />
ችግኞችን፣ ዘሮችንና የውሃ አቅርቦትን<br />
የሚሰጣቸው ጃካራንዳ ነው፡፡ ‹‹በአሁን<br />
ወቅት የአካባቢው ሕብረተሰብ ለድርጅታችን<br />
ያለው አመለካከት በጣም መልካም ነው፡<br />
፡ ሕብረተሰብን ያላማከለ ልማት ውጤታማ<br />
አይሆንም፡፡ ከሥራችን ጎን ለጎን ሕብረተሰቡ<br />
ተጠቃሚ እንዲሆን እንፈልጋለን›› ሲሉ<br />
የገለፁልን አቶ ደምመላሽ፣ ከዚህ ቀደም<br />
ተሰርቆባቸው የነበረውን የውሃ መሳቢያ<br />
ፓምፕ ሕብረተሰቡ ተከታትሎ ማስመለሱን<br />
በመልካም አርያነት ያስታውሱታል፡፡<br />
እንደመሬቱ አመቺነት መስራት<br />
የጃካራንዳ ኢንተግሬትድ አግሮ ኢንዱስትሪ<br />
አ.ማ ለሥራ የተሰጠው አብዛኛው መሬት<br />
ለግብርና ልማት በጣም የማያመች መሆኑ<br />
ይገለፃል፡፡ በዓይን አይቶ ምስክርነት<br />
ለመስጠትም ቀላል ነው። አክሲዩን ማሕበሩን<br />
በመጀመሪያዎቹ ወራት ከገጠሙት ችግሮች<br />
መካከል ተፈጥሯዊ የሆኑት ተጠቃሽ ናቸው።<br />
አካባቢው ቀደም ብሎ በቁጥቋጦ ተሸፍኖ<br />
የነበረ ሲሆን የአካባቢው ቀደምት ‹ነዋሪዎች›<br />
የነበሩትን ጅብ፣ ዘንዶ፣ ጊንጥ፣ እና እባብን<br />
ለማባረር ፈታኝ መሆኑ ይታወሳል።<br />
ነገር ግን፣ ቁጥቋጦዎቹ እየተመነጠሩ፣<br />
አካባቢውን የተቆጣጠሩት የእሳት ጎመራ<br />
ውጤት ድንጋዮች ተለቅመው እየተቆሩ<br />
ለግንባታ፣ ለሽያጭና ለቋሚ አትክልትና<br />
ፍራፍሬ ተክሎች ምርት አካባቢው ምቹ<br />
ወደመሆን እየመጣ ነው - ባላሰለሰ የሥራ<br />
ጥረትና ትጋት። ይኼንንም አስመልክቶ<br />
አቶ ደምመላሽ እንዲህ ሲሉ ይገልፃሉ፡<br />
- ‹‹እንደሥራው አመቺነት ሳይሆን እንደ<br />
መሬቱ አመቺነት እየተሰራ ነው።››<br />
አትክልትና ፍራፍሬዎችና<br />
ችግኝ ጣቢያ<br />
ከጃካራንዳ ሳይት አቅራቢያ በኢትዮጵያ<br />
ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የመልካሳ<br />
ግብርና ምርምር ማዕከል ይገኛል። የማዕከሉ<br />
ተመራማሪዎች በሙያ ነክ ጉዳዩች ዙሪያ<br />
የጃካራንዳ አጋሮች ናቸው። ለዚህም ነው<br />
የተሻለ ምርት ሊሰጡ የሚችሉ የቋሚ<br />
አትክልትና ፍራፍሬ ዝርያዎችን ማዕከሉ<br />
ለጃካራንዳ ሰጥቶ በማዳቀል የተወሰኑ<br />
ፍራፍሬዎች በጥሩ ሁኔታ አፍርተው ማየት<br />
የተቻለው።<br />
ቀደም ሲል በ2500 ካሬ ሜትር መሬት<br />
ላይ 250 እግር ማንጎዎች ተተክለው ነበር።<br />
በአሁን ወቅት እነዚህ በግንዶቻቸው ላይ<br />
በርካታ ፍሬዎችን አፍርተዋል። እንዲሁም<br />
ተጨማሪ 750 እግር ያህል ማንጎዎች በቅርቡ<br />
የተተከሉ ሲሆን፣ በአጠቃላይ የሚተከሉት<br />
ማንጎዎች ለአምስት ዓመታት ያህል<br />
በጥራትና በብቃት ተመርተው እንደሚለቀሙ<br />
የአቶ ደምመላሽ ሀሳብ ነው። አቦካዶና ሙዝን<br />
የመሳሰሉ የፍራፍሬ ተክሎችም የጃካራንዳ<br />
ሌሎች የልማቱ ፍሬዎች ናቸው።<br />
በሌላ በኩል ደግሞ፣ 150 ሜትር ርዝመትና<br />
መጠነኛ የጎን ስፋት ባላት አነስተኛ ችግኝ<br />
ጣቢያ (Nursery) ውስጥ ፓፓዬ 200 ሺህ፣<br />
አቦካዶ አንድ ሺህና ማንጎ 400 እግር<br />
ያህል ችግኞች በመፍላት ላይ ይገኛሉ።<br />
የችግኝ ጣቢያው ዋና ዓላማም የከብቶች<br />
ፍግና ተረፈ ምርቶችን (Waste product)<br />
በተፈጥሮ ማዳበሪያነት በመጠቀም ለችግኞቹ<br />
አመቺ ሁኔታን በመፍጠር በቅድሚያ<br />
ለድርጅቱ ልማት፣ ሲተርፍ ደግሞ ለሌሎች<br />
አልሚዎችና ገበሬዎች ችግኞችን መሸጥ<br />
መሆኑን ኃላፊው ይገልፃሉ።<br />
ከብቶች፣ ፍየሎችና ዛፎች<br />
አክስዩን ማሕበሩ ከዚህ ቀደም<br />
እንደሚያደርገው ሁሉ የሚደልቡ ከብቶችን<br />
ከቦረናና ሞያሌ ገዝቶ በማምጣት ሰንጋዎቹ<br />
ተገቢው ክብደት ላይ ሲደርሱ ከነቁማቸው<br />
ወደ ውጭ ሀገራት (ግብፅና አረብ ሀገራት)<br />
ለሽያጭ ይቀርባሉ። በጥር ወር 2003<br />
ዓ.ም ላይ ይኼንን አስመልክቶ አውራምባ<br />
ታይምስ በሰራው ዘገባ ላይ ሰንጋዎቹ ወደ<br />
ማደለቢያው ጣቢያው ሲገቡ ክብደታቸው<br />
ከ270 ኪ.ግ እንደማይበልጥ፣ ለሶስት<br />
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />
መልካም ዓዲስ ዓመት<br />
እንደ ስሙ በማበብ ላይ ያለው<br />
ጃካራንዳ<br />
ወራት በየቀኑ አስር ሊትር ውሃ እየተቀለቡ<br />
ለሽያጭ ብቁ እንደሚሆኑና ክብደታቸው<br />
እስከ 400 ኪ.ግ እንደሚመዝን፣ እንዲሁም<br />
እነዚህን ለውጭ ገቢያ ብቁ ለማድረግ ሶስት<br />
ወራት እንደሚፈጅ አስፍሯል። በዕለቱ<br />
ያገኘናት የሥራ ተቆጣጣሪም ደልበው<br />
ወደ ውጪ ሃገራት የሚሸጡት ሰንጋዎች<br />
ዋጋቸው ከ6500-8000 ብር ድረስ መሆኑን<br />
ነግራናለች። በመስክ ጉብኝቱ ወቅት በቁጥር<br />
430 ያህል ሰንጋዎችና 213 ያህል ፍየሎች<br />
ነበሩ። የበረቶቹ ቁጥርም ከአራት ወደ ስድስት<br />
ከፍ ብሏል።<br />
በተጨማሪም፣ ድርጅቱ ከአዳማ ወረዳ<br />
ግብርና ፅ/ቤት ጋር በመመካከር የአካባቢውን<br />
የአግሮ-ኢኮሎጂካል ሥነ-ምህዳር ለመጠበቅና<br />
የሙቀቱን መጠን ለመቀነስ በማሰብ<br />
2800 ያህል የጃካራንዳና የድሬዳዋ ዛፎችን<br />
አሰበጣጥሮ በመትከል እየተንከባከቡ<br />
እንደሚገኙ አቶ ደምመላሽ ያስረዳሉ።<br />
ቀጣይ ዕቅዶችና ትግበራዎች<br />
አምስት ሺህ ኪውቢክ ሊትር ውሃ የመያዝ<br />
አቅም ካለው የውሃ ማጠራቀሚያ ገንዳ<br />
በስተቀኝ በኩል አምስት ሄክታር ቦታ ላይ<br />
መሬቱን አመቺ በማድረግ የዶሮ እርባታ<br />
በቀጣይ ወራት ለመጀመር መታቀዱን<br />
የአክስዮን ማሕበሩ የቴክኒክ ክፍል ኃላፊ<br />
የሆነው ወጣት ይስሃቅ ገ/እግዚያብሔር<br />
ገልፀዋል። እንዲሁም ማሕበሩ አሁን ከያዘው<br />
38 ሔክታር መሬት ውጪ ተጨማሪ 15<br />
ሔክታር መሬትን ለመጨመር ተገቢውን<br />
ነገር በማድረግ ከሚመለከተው የ<strong>መንግስት</strong><br />
አካልና የሕብረተሰብ ክፍል ጋር ተነጋግሮ<br />
የግል ይዞታው አድርጓል፡- በመሬቱ ላይ<br />
የተተከሉ አትክልትና ፍራፍሬ እና የተዘሩ<br />
ሰብሎች እስኪነሱ ከመጠበቅ ውጪ። የከብት<br />
ሥጋ እርድና ማቀነባበሪያ ሥራ ግንባታም<br />
የቀጣይ ዕቅዶች አንዱ አካል ነው።<br />
በግማሽ ቀን የነበረንን የመስክ ጉብኝት<br />
አጠናቅቀን በአካባቢው የነበረውን ሁኔታ<br />
በእርጋታ ስንመለከት ጃካራንዳ በእርግጥም<br />
በለውጥ ጎዳና ላይ መሆኑን በቀላሉ መገንዘብ<br />
ችለናል። የአክሲዮን ማሕበሩ የቦርድ<br />
ሊቀመንበርና ዋና ሥራ አስኪያጅ በሆኑት<br />
አቶ ደምመላሽ ላይ የተመለከትነው ጠንካራ<br />
የሥራ ፍላጎትና፣ ተነሳሽነትና የለውጥ ራዕይ<br />
ትልቅ ስሜትን የሚፈጥር ነበር። በመጨረሻም<br />
አቶ ደምመላሽ በአጋጣሚ ፈገግ የሚያደርግ<br />
ንግግርን ተናገሩ። የዚህ ፅሁፍ አቅራቢ<br />
የግብርና ባለሙያ እንደነበረ ሰሙና ትንሽ<br />
ኮስተርና ሳቅ በማለት፣‹‹ በጋዜጠኝነት ሙያ<br />
ወሬ እየፈለክ ወረቀት ከምትቀዳድ ይልቅ<br />
በሙያህ ገበሬ ሆነህ ብትሰራ ይሻልሃል፣<br />
የሚያዋጣው እሱ ነው።›› ሲሉ ተናገሩ።<br />
ቀደም ሲል በ2500 ካሬ ሜትር<br />
መሬት ላይ 250 እግር ማንጎዎች<br />
ተተክለው ነበር። በአሁን ወቅት<br />
እነዚህ በግንዶቻቸው ላይ በርካታ<br />
ፍሬዎችን አፍርተዋል። እንዲሁም<br />
ተጨማሪ 750 እግር ያህል<br />
ማንጎዎች በቅርቡ የተተከሉ ሲሆን፣<br />
በአጠቃላይ የሚተከሉት ማንጎዎች<br />
ለአምስት ዓመታት ያህል በጥራትና<br />
በብቃት ተመርተው እንደሚለቀሙ<br />
የአቶ ደምመላሽ ሀሳብ ነው።
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />
መልካም ዓዲስ ዓመት<br />
13<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ
14<br />
በዓለም አቀፍ ሕግ በውጭ ሀገራት ለሚገኙ ዜጎች ሚኒስቴር መ/ቤቱ<br />
የሚያደርገው ከለላ ምንድን ነው?<br />
ወደ ዓለም አቀፍ ሕግ ከመሄዳችን በፊት የውጭ<br />
ጉዳይ ሚኒስቴር ካሉት የውጭ ተልዕኮዎች መካከል<br />
አንዱና ዋንኛው በውጭ ያሉ ዜጎችን መጠበቅ ነው።<br />
በውጭ ያሉ ኢትዮጵያውያንን መጠበቅ ሲባል ብዙ<br />
ጉዳዮች አብረው ይነሳሉ። አንደኛ እዛ ያሉ ዜጎች<br />
የሚፈልጓቸውን ሕጋዊ ሰነዶች ማዘጋጀትና ችግር<br />
ሲገጥማቸው ማገዝ ነው።<br />
ወደ ዓለም አቀፍ ሕጉ ስንመጣ፤ እያንዳንዱ ሕግ<br />
ከዓለም አቀፍ ሕግጋት እና ድንጋጌዎች ጋር ተጣጥሞ<br />
ነው መስራት ያለበት። ስለዚህ በዓለም አቀፍ ደረጃ<br />
ለሚንቀሳቀሱ ሰዎች የሚሰጡ ከለላዎች አሉ።<br />
ለምሳሌ ለስደተኞች የሚሰጥ መብት አለ። የተባበሩት<br />
መንግስታት ድርጅት ስለስደተኞች ያፀደቀው ድንጋጌ<br />
አለ። የእኛ ሕግጋትም ከእዛ ጋር የሚጣጣሙ ናቸው።<br />
ስለዚህ ዞሮ ዞሮ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ተልዕኮዎች<br />
ውስጥ አንዱ በውጭ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ከለላ<br />
መስጠት ነው።<br />
ተግባራዊነቱስ ምን ያክል ነው? ምክንያቱም ‹‹ችግር በገጠመን ጊዜ<br />
የሚሰማን የለም›› የሚሉ ቅሬታዎች አረብ ሀገራት ከሚገኙ ዜጎች<br />
ዘንድ በስፋት ይደመጣልና።<br />
እንግዲህ በተቻለ መጠን በውጭ በርካታ ኤምባሲዎችና<br />
ቆንፅላ ጽ/ቤቶች አሉ፡፡ አንዱም የችግሩ ምንጭ<br />
የሚመስለኝ [ከለላ ላለማግኘታቸው] ኤምባሲዎቻችን<br />
በሌሉባቸው ሀገራት ያሉ ዜጎቻችን ጉዳይ ነው።<br />
ይሄ መዋቅራዊ ችግር ነው። አቅም ስንገነባ<br />
ሊቀረፍ የሚችል ነው። ሁለተኛው የችግሩ ምንጭ<br />
ዜጎች ራሳቸው መከተል የሚገባቸውን አካሄዶች<br />
ስለማይከተሉ ነው። ለምሳሌ ኤምባሲዎች ባሉባቸው<br />
ሀገራት ያሉት ኤምባሲ ሄደው አይመዘገቡም።<br />
አድራሻቸውን አለማሳወቅና ችግር ሲከሰት ብቻ ወደ<br />
ኤምባሲ የመሄድ ነገር አለ።<br />
ዜጎችን እየወቀስኩ አይደለም፤ እነሱ ጋር የሚስተዋለው<br />
ችግር የሚመነጨው ምናልባት ከግንዛቤ እጥረት<br />
ይሆናል፤ አሊያም ኤምባሲ ሄዶ የመመዝገብን ጥቅም<br />
አሳንሶ ከማየት የመነጨ ይመስለኛል።<br />
ሶስተኛው አንተም እንዳልከው … እንግዲህ<br />
ኤምባሲዎች ውስጥ የሚሰሩት ሰዎች ናቸውና<br />
ከእነሱም ስህተት አይጠፋም። ከኤምባሲው ፖሊሲ<br />
በተቃራኒ እዛ የሚሠሩ ግለሰቦች ለዜጎች ተገቢውን<br />
ምላሽ ላይሰጡ ይችላሉ።<br />
በጋዳፊ ቤተሰቦች አስከፊ ጥቃት የደረሰባትን የሸዋዬ ጉዳይ <strong>መንግስት</strong><br />
እንዴት አየው?<br />
ይሄ በጣም አሰቃቂ ነው። ማንም <strong>መንግስት</strong><br />
በዜጋው ላይ እንዲህ ዓይነት ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት<br />
አንዲፈፀም አይፈልግም። መረጃው እንደደረሰንም<br />
ፈጥነን የልጅቱን ቤተሰቦች አነጋግረናል። ስለማንነቷ<br />
እና ስለአካሄዷ መረጃዎችን ተቀብለናል። ከዛም<br />
በዚህ ጉዳይ ላይ ተባብረን ልንሰራ የምንችላቸውን<br />
ወገኖች አነጋግረናል። አዲስ አበባ በሚገኘው የሊቢያ<br />
ኤምባሲ ካሉት አምባሳደር ጋርም ተነጋግረናል።<br />
አሁን የደረስንበት ውጤት ልጅቱ የተሻለ ሕክምና<br />
የምታገኝበት ሁኔታ መመቻቸት እንዳለበት ነው።<br />
በዚህ ረገድ የተያዙ አማራጮች አሉ፤ አንደኛው፣<br />
የማልታ <strong>መንግስት</strong> የሕክምና ወጪዋን ችሎ<br />
እንደሚያሳክማት እየገለፀ ነው። ሁለተኛው፣<br />
እንግሊዝና አሜሪካ ለማሳከም ጥያቄ አቅርበዋል።<br />
የትኛውን አማራጭ እንደምትጠቀም ልጅቷ ነች<br />
የምትወስነው። ሌላው የጉዞ ሰነድ በእጇ ስለሌለ<br />
የሚያስፈልጓት ሰነዶች እየተዘጋጁላት ነው።<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
ለሽግግር መንግስቱ ኢትዮጵያ ዕውቅና እንደመስጠቷ መጠን የጋዳፊን<br />
ቤተሰቦች ለመክሰስ <strong>መንግስት</strong> አስቧል?<br />
እንዳልከው ለሽግግር ካውንስሉ ዕውቅና ከሰጡ<br />
የአፍሪካ አገሮች አንዷ ኢትዮጵያ ነች። ጦርነቱ ገና<br />
አልተጠናቀቀም፣ የተረጋጋ ሁኔታም አልተፈጠረም።<br />
እንግዲህ ሁሉም ነገር ሲረጋጋ ነው ይሄን ጉዳይ<br />
ማንሳት የሚቻለው። ጉዳዩ በጣም ትኩረት የሚሰጠው<br />
ነው። ልጅቷ/ቤተሰቦቿ ካሳ የጠየቁበት ሁኔታ አለ ግን<br />
በ<strong>መንግስት</strong> ደረጃ ይሄን ለማድረግ መረጋጋት የግድ<br />
ነው።<br />
እዚህ ካለው የሊቢያ ኤምባሲ ጋር ‹‹ተነጋግረናል›› ብላችኋል …<br />
እነሱ ጉዳዩን እንዴት ነው ያዩት?<br />
በጣም ነው ያዘኑት። ሰውየውና ቤተሰቦቹ [ጋዳፊ]<br />
እንኳንና በሌላ ሀገር ዜጋ ቀርቶ በራሳቸው ዜጎች<br />
ላይም ከእዚህ የበለጠ ግፍ የሚፈፅሙ መሆናቸውን<br />
በመግለፅ አፅናንተውናል።<br />
በሌሎች አረብ ሀገራትም ያሉ ኢትዮጵያውያን ተመሳሳይ ወይም<br />
ከዚህ የባሰ ጥቃት ይፈፀምባቸዋል፤ ለዚህ ምክንያቱ ምንድን ነው?<br />
በተደጋጋሚ የምንናገረው ነገር አለ። አንደኛ፣<br />
ከአካሄዳቸው ጀምሮ ሊታዩ የሚገቡ ጉዳዮች አሉ።<br />
በሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አማካኝነት<br />
ዋስትና ተይዞላቸው የሥራው ሁኔታ ታውቆ፣<br />
ሰብዓዊነት በተከተለና ዓለም አቀፍ ሕግጋትን<br />
በተከተለ ሁኔታ ብዙዎች ሲሄዱ አይስተዋልም።<br />
ለዚህ ነው እንግዲህ በሕገ-ወጥ ደላላ አማካኝነት<br />
ያልሆነ ባዶ ተስፋ ተሞልተው የሚሄዱትና ትልቅ<br />
ችግር የሚያጋጥማቸው። አሰሪዎቹም በሕገ-ወጥ<br />
መንገድ የሚሄዱት ምንም ዋስትና እንደሌላቸው<br />
ስለሚያውቁ እጃቸው ለገባው ኢትዮጵያዊ ደህንነት<br />
አይጨነቁም።<br />
አረብ ሀገራት ያሉ ኢትዮጵያውያን ችግር ደርሶባቸው ለኤምባሲ<br />
በሚያመለክቱበት ጊዜ ‹‹ዞር በል፤ እኛ የመጣነው ኢንቨስተር<br />
ለመሳብ እንጂ ለአሽከር አይደለም›› የሚል መልስ እንደሚሰጣቸው<br />
ይገልፃሉ። በሌላ በኩል ደግሞ የኤምባሲዎች ዋና ዓላማ የኢህአዴግ<br />
ደጋፊ ዳያስፖራዎችን ማሰባሰብ መሆኑን የሚገልጹ አሉ … ዋና<br />
ተልዕኳቸው ምንድን ነው?<br />
በነገራችን ላይ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተሰጠው<br />
ተልዕኮ በውጭ የሚተገበረው በኤምባሲዎች<br />
አማካኝነት ነው። ለመ/ቤቱ ከተሰጠው ተልዕኮ<br />
አንዱ የኢትዮጵያን ልማት፣ ዴሞክራሲ እና ሰላም<br />
ሊደግፉ የሚችሉ ሥራዎችን በውጭ መስራት ነው።<br />
እነዚህም ኢንቨስትመንትን መሳብ፣ የውጭ ገበያ<br />
ማፈላለግና ጎብኚዎችን መሳብ ናቸው፡፡ ነገር ግን<br />
የዜጎችን መብቶች ማስጠበቅም ከዚሁ እኩል ትኩረት<br />
ተሰጥቶት የሚሰራ ነው።<br />
ስለዚህ ‹‹እኔ እዚህ ያለሁት ኢንቨስተር ለመሳብ ብቻ<br />
ነው›› የሚል ዲፕሎማት ካለ ያልገባው ነገር አለ ማለት<br />
ነው። ተልዕኮውን በደንብ አልተረዳም ማለት ነው።<br />
በእርግጥ የሥራችን ዋንኛው ትኩረት ኢኮኖሚያዊ<br />
ዲፕሎማሲ ነው። ሆኖም ኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲን<br />
በደንብ ለማሳካት ውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን<br />
መብቶች ማስከበር የግድ ነው። ለሚሺነሪዎቻችንም<br />
በየጊዜው ስለተልዕኳቸው ሥልጠናዎች የሚሰጠው<br />
ለዚህ ነው።<br />
እዚህ ጋር አንድ ጥያቄ ላንሳ … አሁን ባለው ሁኔታ በውጭ የሚገኙ<br />
ኢትዮጵያውያን መብቶች አጥጋቢ በሆነ ደረጃ ተከብረዋል?<br />
ቅድም ባነሳናቸው ምክንያቶች ክፍተቶች የግድ<br />
ይኖራሉ። ወደ ኤምባሲ ሄዶ መመዝገብ አነስተኛ<br />
ግምት ስለተሰጠው ዜጎች ሄደው የመመዝገባቸው<br />
ሁኔታ በጣም አነስተኛ ነው። እንዲሁም በአቅም<br />
ውስንነት የተነሳ ኤምባሲ ባልከፈትንባቸው ሀገራት<br />
ያሉ ዜጎችን መብቶች ማስጠበቅ አዳጋች ነው።<br />
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />
መልካም ዓዲስ ዓመት<br />
‹‹ከተፈፀመ ቆይቷል ግን ሲ.ኤን.ኤን እስኪዘግበው ድረስ<br />
እኛም ቤተሰቦቿም ምንም መረጃ አልነበረንም››<br />
ሸዋዬ ሞላ በተባለች ኢትዮጵያዊት ላይ በጋዳፊ ቤተሰቦች<br />
የተፈጸመው ኢ-ሰብዐዊ ጥቃት አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ ሱራፍኤል ግርማ<br />
ለወጣቷ እየተደረገ ስላለው ድጋፍና በአጠቃላይ በአረብ አገራት<br />
ስላሉ ኢትዮጵያዊያን ሁኔታ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ<br />
የሆኑትን አምባሳደር ዲና ሙፍቲን አነጋግሯል፡፡<br />
አምባሳደር ዲና ሙፍቲ<br />
በመሠረቱ ከሆነ አንድ ሥራ መቶ በመቶ ይከናወናል<br />
ብሎ መጠበቅ አዳጋች ነው። የዳያስፖራ ፖሊሲ<br />
ተዘጋጅቶ በውጭ ያሉ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገር<br />
ቤት መጥተው በልማት እንዲሳተፉ አንዳንድ ጥቅማ<br />
ጥቅሞችን በመስጠት ሁሉ እየጣርን ነው።<br />
‹‹ዳያስፖራ›› ሲባል የትኛው ዳያስፖራ ነው?<br />
በሁሉም ሀገራት የሚገኙ የኢትዮጵያ ዳያስፖራዎች<br />
አንድ ዓይነት ሁኔታ ላይ አይደለም ያሉት። ለምሳሌ<br />
ሰሜን አሜሪካና አውሮፓ ያሉ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ<br />
ያሉበትን ሀገር ዜግነት ይወስዳሉ። ስለዚህ እነዚህ<br />
ኢትዮጵያውያን ሳይሆኑ ‹‹ትውልደ ኢትዮጵያውያን››<br />
ነው የሚባሉት። ለእነሱ የሚሰጠው ድጋፍ እንደ<br />
ዜጋ አይደለም። ሌላው በአፍሪካ እና በኢሲያ ያሉ<br />
ዳያስፖራዎች ያሉበትን ሀገር ዜግነት ስለማያገኙ<br />
ኢትዮጵያውያን ናቸው። የሚያገኙት ጥቅምም<br />
እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ነው። ስለዚህ ፖሊሲው<br />
ሁለቱንም የሚመለከት ነው።<br />
የቆንፅላ ጽቤቶች ሥራ ምንድን ነው?<br />
የቆንፅላ ጽ/ቤቶች ከኤምባሲ ዝቅ ያሉ ሲሆን፣ ኤምባሲ<br />
በሌለበት ሀገር ውስጥ ሥራዎችን የሚያከናውኑ<br />
አካላት ናቸው፤ በተለይም ሕጋዊ ሰነዶችን ማዘጋጀትና<br />
ማረጋገጫ መስጠት። በነገራችን ላይ የኤምባሲና<br />
ቆንፅላ ጽ/ቤት አከፋፈት እንደየሀገራት ሁኔታ<br />
ይለያያል። የበለፀጉት ሀገራት በመላው ዓለም በሚገኙ<br />
ሀገራት ኤምባሲዎች ሊኖራቸው ይችላል። በእኛ ደረጃ<br />
ግን ‹‹ወሳኝ›› ተብለው በሚታመኑ ሀገራት ብቻ ነው<br />
ኤምባሲ የሚያስፈልገው። የመን አሁን ኤምባሲ ነው<br />
ያለን። ሳዑዲ አረቢያ ጅዳ ቆንፅላ ጽ/ቤት ነው ያለው።<br />
ዱባይና ቤይሩት ቆንፅላ ነው ያለው።<br />
የሸዋዬ ጉዳይ የማንቂያ ደወል ነውና ከዚህ በኋላ ወደ አረብ ሀገራት<br />
የሚሄዱ ኢትዮጵያውያን ምን ከለላ ይደረግላቸዋል?<br />
‹‹ማንቂያ ደወል›› ያልከው በጣም ትክክለኛ ቃል<br />
ነው። ይሄ ነገር ከተፈፀመ ቆይቷል ግን ሲ.ኤን.ኤን<br />
እስኪዘግበው ድረስ እኛም ቤተሰቦቿም ምንም መረጃ<br />
አልነበረንም። ሌሎች ከዚህ መማር ያለባቸው ነገር<br />
በየሄዱባቸው ሀገራት ሄደው መመዝገብ ያለባቸው<br />
መሆኑን ነው። አካሄደቸውን ሕጋዊ ማድረግ<br />
አለባቸው። የጉዳዩ ትልቁ ባለቤት ተጓዦች ናቸው።<br />
ስለዚህ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው።<br />
ጥሩ . . . ወደ ውጭ የሚሄዱት የጠቀሷቸውን ቅድመ-ሁኔታዎች<br />
ማሟላት አለባቸው። መንግሥትስ ከዚህ በኋላ ለዜጎቹ እንዴት ነው<br />
ከለላ የሚያደርገው?<br />
በየኤምባሲው ያሉ ሰዎች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ<br />
መወጣት አለባቸው። ውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን<br />
ለሚያቀርቧቸው ጥያቄዎች ትክክለኛና ተገቢው ምላሽ<br />
ሊሰጣቸው ይገባል።<br />
በተለያዩ እስር ቤቶች ውስጥም የሚገኙ በርካታ ኢትዮጵያውያን አሉ፤<br />
ለምን አስፈትታችኋቸው ወደ ሀገር ቤት እንዲመጡ አታደርጉም?<br />
የተመዘገቡ ስላልሆኑ የመረጃ ዕጥረት አለ።<br />
የሚደርሱን መረጃዎች የግምት ናቸው። ‹‹የት<br />
እስር ቤት? ብዛታቸውስ?›› የሚለውን ነገር በደንብ<br />
የሚመልስ አይደለም። የሚመጡ ሰዎችም የሚሰጡን<br />
መረጃ አጥጋቢ አይደለም።<br />
የአረቡ ዓለም አብዮት በተቀሰቀሰበት ወቅት ኢትዮጵያውያንን ወደ<br />
ሀገር ቤት የመመለስ ሥራ በ<strong>መንግስት</strong>ና በዓለም አቀፍ ተቋማት በኩል<br />
ይከናወን ነበር። በአንፃሩ ደግሞ ወደዛው የሚሄዱ ሰዎች ነበሩ።<br />
ለምንድን ነው ዝም የሚባለው?<br />
ትክክል። ከየመን ሸሽተው የሚመጡትን ለመቀበል<br />
አየር ማረፊያ ቆመን ወደ የመን የሚሄዱ ሰዎችን<br />
ተመልክተናል። ‹‹ይኸው እነዚህ የሚመለሱት እዛ<br />
ችግር ሆኖ ነው፤ ለምን ትሄዳላችሁ?›› ስንላቸው<br />
ሊሰሙን ፈቃደኞች አልነበሩም። በዚህ ላይ ማንም<br />
ሰው ወደ ፈለገበት ቦታ የመሄድ ሕገ-መንግስታዊ<br />
ነፃነት አለው። ያንን ጥሰን ማስቆም አንችልም።<br />
ግን ከሄዱስ በኋላ ከለላ ማድረግ አይቻልም?<br />
ከሄዱ በኋላ ሌላ ሀገር ነው ያሉት። በሄዱበት ሀገር<br />
ሕግ መሰረት ነው የሚተዳደሩት። <strong>መንግስት</strong> ጣልቃ<br />
መግባት የሚችለው ችግር ሲደርስ ነው። ችግሮች<br />
ሲከሰቱ ከዛ ሀገር <strong>መንግስት</strong> ጋር በመነጋገር ለጉዳዩ<br />
ዕልባት ይሻል እንጂ ለእያንዳንዱ እንቅስቃሴ ከለላ<br />
መስጠት አይችልም።<br />
በርካታ ኢትዮጵያውያን ከሚገኙባት ኳታር ጋር ዲፕሎማሲያዊ<br />
ግንኙነት ተቋርጧል። እዛ ያሉ ኢትዮጵያውያንን ጉዳይ እንዴት ነው<br />
የምትከታተሉት?<br />
እስካሁን ድረስ ያጋጠመ ችግር የለም። ግን እንደ<br />
ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት [IOM] እና በተባበሩት<br />
መንግስታት ድርጅት [UNHCR] ባሉ ዓለም አቀፍ<br />
ተቋማት በኩል መብቶቻቸውን ማስጠበቅ ይቻላል።
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />
መልካም ዓዲስ ዓመት<br />
15<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ
16<br />
ደርግ ወደ ሥልጣን ሲመጣ እርስዎ የትና በምን<br />
ኃላፊነት ላይ ነበሩ?<br />
ደርግ ወደ ስልጣን ሲመጣ እኔ አሜሪካን<br />
ሀገር ትምህርት ላይ ነበርኩ። ከዚያ<br />
እንማንኛውም በዘመኑ እንደነበሩ ወጣት<br />
ተማሪዎች ለውጡን ደግፌ ተሰለፍኩ።<br />
በነገራችን ላይ ከዚያ በፊት ከውትድርናው<br />
ዓለም ወጥቼ ነበር። የለውጡ እንቅስቃሴ<br />
ሲጀመር ነው እንደገና ወደ ወታደርነት<br />
የተመለስኩት። እናም ለውጡን የበለጠ<br />
ለማንቀሳቀስ ከሌሎች መኮንኖች ጋር<br />
ተባብሬ ተሰለፍኩ፡፡ በደርግ ውስጥ<br />
በሰራሁባቸው ዓመታት ውስጥ የሚቻለንን<br />
ያህል በኢትዮጵያ እውነተኛና መሠረታዊ<br />
ለውጥ ለማምጣት፣ ከድህነት ወደ<br />
ዕድገት፣ ከጦርነት ወደ ሰላም መሸጋገር<br />
የምንችልበትን መንገድ ለመቀየስ<br />
ሞክረናል።<br />
ወደ አሜሪካ ለትምህርት ከመውጣትዎ በፊት የት<br />
ነበር የሚሰሩት?<br />
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ትምህርት ላይ<br />
ነበርኩ። የመጀመሪያ ዲግሪዬን ያገኘሁትም<br />
እዛው ነው። ከዛ በኋላ ወደ አሜሪካ አገር<br />
ወጥቼ ኮሎምቢያ ዩኒቨርስቲ ትምህርት<br />
ጀመርኩ። ኮሎምቢያ ዩኒቨርስቲ ስማር<br />
የሻለቅነት ማዕረግ ማግኘት የምችልበት<br />
ወቅት ነበር። በዚህ የተነሳ ወደ ሀገር<br />
ቤት ስመለስ የሻለቅነት ማዕረግ ሰጡኝ።<br />
ቢሆንም በሻለቅነት ማዕረግ ብዙ ጊዜ<br />
አልሰራሁበትም።<br />
በሐረር ጦር አካዳሚ 2ኛ ኮርስ ሰልጣኝ ነበሩ።<br />
2ኛ ኮርስ መኮንኖች ደግሞ እስከ ጀኔራል ማዕረግ<br />
ደርሰዋል። እርስዎ ታዲያ ለምን እስከ ጄኔራል ማዕረግ<br />
ማግኘት አልቻሉም?<br />
ወደ ወታደርነት ሥራ አልተመለስኩም።<br />
አብዮቱን እንደተቀላቀልኩ በሲቪልነት<br />
ነው ያገለገልኩት።<br />
ከአሜሪካ ወደ አገርዎ የተመለሱት ደርግ ሥልጣን<br />
ከያዘ ከስንት ጊዜ በኋላ ነው?<br />
ንጉሱ መስከረም 2 ቀን ከሥልጣን ወረዱ<br />
ሲባል፣ እኔና ኒውዮርክ አካባቢ የምንገኝ<br />
ሰዎች ወዲያው ነው ጓዛችንን ጠቅልለን<br />
ወደ ሀገር ቤት የገባነው፡፡ በዚያው<br />
በመስከረም ወር ማለት ነው።<br />
መልካም። ለህትመት ባበቁት አንድ መፅሐፍ፣<br />
እርስዎ የሐረር ጦር አካዳሚ፣ ኮ/ል መንግስቱ<br />
ደግሞ የሆለታ ጦር አካዳሚ ሰልጣኝ እንደነበራችሁ፣<br />
ሁለታችሁም በማዕረግ ደረጃ አቻ እንደሆናችሁ<br />
ጠቅሰው፣ ሀገር ቤት እንደገቡ ኮ/ል መንግስቱን<br />
ለማነጋገር ወደ ቤተ<strong>መንግስት</strong> በሄዱ ጊዜ ‹‹አንተ ብዬ<br />
ነው የማነጋግረው›› ብለው ፣ ‹‹ወዲያው ሳላስበው<br />
አንቱ ማለት ጀመርኩ›› ሲሉ የተረኩት ክፍል አለ።<br />
እስቲ ይህ ሊሆን የቻለበትን ሁኔታ መለስ ብለው<br />
ያጫውቱኝ?<br />
ተፈሪ መኮንን ትምህርቴን ከጨረስኩ<br />
በኋላ ወደ ሐረር ጦር አካዳሚ የገባሁት<br />
በግል ፍላጎቴ አይደለም። ተመልምለን ነው<br />
የግድ ወደ ጦር ት/ቤት የተላክነው። እና<br />
የ2ኛ ኮርስ ሰልጣኝ ነኝ። ሐረር ሚሊቴር<br />
አካዳሚ፣ የታወቀ ሚሊተሪ አካዳሚ ነው።<br />
ህንዶች ያቋቋሙት ነው። እዚያ 3 ዓመት<br />
ሰልጥኛለሁ። በእነዚያ ሶስት ዓመታት<br />
በየቀኑ የምንማረው፣ የምንዘጋጀው እና<br />
አዕምሮአችንን የምናሰለጥነው ከራስ<br />
በላይ ሀገርን (ኢትዮጵያን) ማስቀደምን<br />
ነው። ከራስ በፊት ሀገር፣ ከራስ በፊት<br />
ሀገር፣ ከራስ በፊት ሀገር በሚል መርህ<br />
ተኮትኩተን ነው የሰለጠንነው።<br />
ከስልጠና በኋላ አየር ወለድ ገባሁ። የኛ<br />
ኮርስ ሁለተኛው ቡድን ነበር ወደ አየር<br />
ወለድ ሲገባ። ከዚያ ኤርትራ ሄድኩ።<br />
በኤርትራ ለሰራዊቱ የተለያየ ስልጠና<br />
በመስጠት ለብዙ ዓመታት አገለገልኩ።<br />
ከዚያ ደግሞ በአሜሪካን ሀገር (አድቫንስ)<br />
ከፍተኛ የእግረኛ ወታራዊ ትምህርት<br />
ሥልጠና ለ11 ወራት ተማርኩ። እንደገና<br />
ደግሞ ወደ አገር ቤት ተመልሼ ወደ<br />
ምድብ ሥራዬ ኤርትራ አቆናሁ። ውጊያ<br />
ላይ ቆሰልኩ። በመቁሰሌ ምክንያት<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
ከወታደር ቤት ተሰናበትኩና አዲስ አበባ<br />
ዩኒቨርስቲ ገባሁ።<br />
በእነዚህ ወቅቶች ሁሉ እኔ መንግስቱ<br />
ኃ/ማርያምን አላውቀውም። እሱ ግን<br />
ኤርትራ መጥቶ በነበረበት ጊዜ አይቶኛል፤<br />
ያስታውሰኛል። እሱ ከሆለታ ጦር ት/ቤት<br />
ነው የወጣው። የእኔ ሲኒየር ነው። ከአሜሪካ<br />
ለውጡን ደግፈን ወደ ሀገር ቤት ስንመለስ<br />
መንግስቱ የደርግ ምክትል ሊቀመንበር<br />
ነበር። በወቅቱ ማንኛውም መኮንን እንደ<br />
ጓድ “አንተ” ነበር የምንባባለው። እንደ<br />
ጓደኛ ነበር የምንነጋገረው።<br />
እና አሁን አንተ የጠየቅከኝ ፍርሀትና<br />
“አንቱታ” የተፈጠረው በአንድ ጊዜ<br />
ሳይሆን ቀስ በቀስ ነው። መጀመሪያ<br />
“አንቱ” በሉ ተባልን። ማለት ጀመርን።<br />
ከዚያ እጃችሁን ኪሳችሁ ውስጥ አትክተቱ<br />
ተባልን፣ እጃችንን ከኪሳችን ማውጣት<br />
ጀመርን። ከዚያ ቀረብ ብሎ ማነጋገር<br />
ቀረ። በመጨረሻ የምንነጋገረው በ20<br />
ሜትር ርቀት ሆነ። እንዲህ እንዲህ እያለ<br />
ሰውየው የሚያስፈራ ድባብ ፈጠረ። ከዚያ<br />
ትጥቅ ፈትተን እንድንገባ ተደረገ። ያ<br />
ሁኔታ ፍርሃት አሳደረብን። ክብር ሳይሆን<br />
ፍርሀት። እነዚህ ሁኔታዎች ተደምረው<br />
ነው በመፅሐፉ ያልኩት የሆነው።<br />
በነገራችን ላይ ይህንን ሁኔታ የፃፉት ከሀገር ከወጡና<br />
ከደርግ ከተለዩ በኋላ ቢሆንም፣አተራረክ ግን ኮሎኔል<br />
መንግስቱን ያደንቋቸው እንደነበር የሚያሳይ ነው<br />
የሆነብኝ። መፅሐፍዎን ሳነብ እንደተረዳሁት፣ ኮ/ል<br />
መንግስቱን ለማነጋገር ወደ ቤተ <strong>መንግስት</strong> ሲገቡ ተራ<br />
ሰው ጠብቀው በአስተሳሰቡ ላቅ ያለ ሰው እንዳገኙ<br />
አድርገው ነው የገለፁት። ይህ አገላለፅዎ አሁን<br />
ከሚናገሩት ጋር አይጋጭም?<br />
የፍርሃት ስሜት ከየትና እንዴት እንደመጣ<br />
ነው ቀደም ብዬ የነገርኩህ። እንጂ መቼም<br />
ጊዜ ቢሆን ብናገረው የማላፍርበት፣ ከደረግ<br />
ጋር መስራት ከጀመርኩበት ጊዜ አንስቱ<br />
ለተወሰነ ጊዜ ያህል ለኮ/ል መንግስቱ<br />
ታላቅ አክብሮት ነበረኝ።<br />
አብዮቱ ሲጀመር ያየሁበት የኢትዮጵያዊነት<br />
ስሜት ከምጠብቀው በላይ ነው የሆነብኝ።<br />
የመናገር ችሎታው፤ የማዳመጥ<br />
ችሎታው፣ የመምራት ችሎታው በጣም<br />
ነበር ያስደነቀኝ። ትዝ ይለኛል ያኔ እኔ<br />
የዕድገት በህብረት ምክትል አዝማች<br />
ነበርኩ። በእሱ ፊት ዘማች ተማሪዎችን<br />
አሰልፈን ‹‹ቪቫ መንግስቱ›› እያልን<br />
ስናልፍ፣ እኔ ነበርኩ የመጀመሪያው<br />
‹‹ቪቫ መንግስቱ›› ባይ። ከተፈሪ ባንቲ እና<br />
አጥናፉ አባተ እሱን ለይተን ነበር ‹‹ቪቫ››<br />
ስንል የነበረው።<br />
በዚያ ጊዜ የነበረውን ሁኔታ መለስ ብለህ<br />
ከተመለከትከው በኢትዮጵያ ውስጥ ለውጥ<br />
ስንል ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ሳይሆን፣<br />
ህብረተሰባዊ (የህብረተሰብ) ለውጥ ነው።<br />
ፊውዳሊዝምን የማጥፋትና አዲሲቱን<br />
ኢትዮጵያ የመገንባት ህልም ነበርን።<br />
እና የመንግስቱ ኃ/ማርያም ከአናሳ<br />
ብሔረሰብ የመምጣቱ ጉዳይ፣ ከበታች<br />
መኮንንነት የመምጣቱ ጉዳይ፣ ባህርይው፣<br />
ከጀርባውም ሆነ ከፊቱ ያለው ሌላ ሌላ<br />
ነገር ተደማምሮ እንደለውጥ ተምሳሌት<br />
ተወሰደ። በጠቅላላው እሱ የሚያሳው<br />
የለውጥ ምልክት ነበር የኢትዮጵያን<br />
ለውጥ ያሳያል በሚል ደገፍነው፡ ከዚህ<br />
በተጨማሪ በጣም ጎበዝ አርበኛ ነበር።<br />
ሲናገር፣ ሲያሳምን፣ ሲያዳምጥ በጣም<br />
አደንቀው ነበር። በዚያን ጊዜ ያለ ምንም<br />
ማመንታት እሱን ደግፌአለሁ። ለተወሰነ<br />
ጊዜም አመራሩን ተቀብያለሁ።<br />
በደርግ ውስጥ በየትኛው የኃላፊነት ሥልጣን ላይ ነው<br />
የሰሩት?<br />
በመጀመሪያ የዕድገት በህብረት ምክትል<br />
አዝማች ሆኜ ነው የሰራሁት። ዋና<br />
አዝማቹ ኪሮስ አለማየሁ ይባል ነበር።<br />
በኢትዮጵያውያን ዘንድ በስፋት የታቅሁት<br />
ያኔ ነው። ምንም እንኳን ዘመቻውን<br />
<strong>መንግስት</strong> የኋላ ኋላ ለሌላ ነገር<br />
ቢጠቀምበትም በኢትዮጵያ አዲስ ዕይታን፣<br />
አዲስ ዕውቀትን የፈነጠቀ ነበር። ዓላማው<br />
ጥሩ ነበር።<br />
ከዚያ በኋላ የዕርዳታ ማስተባበሪያና<br />
ማቋቋሚያ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር<br />
ነው የሆንኩት። በወቅቱ በኢትዮጵያ<br />
ከፍተኛ ድርቅ ችግር ነበር። ያ ድርቅ<br />
ለደርግ ውድቀት እንደ አንድ ምክንያት<br />
ነው።<br />
የሆነ ሆኖ በረሃብ ለተጎዳው ኢትዮጵያዊ<br />
የተቻለኝን ድጋፍ ለመስጠት ዕድል<br />
ያገኘሁበትም ነው። ከዚያ በኋላ ውጭ<br />
ጉዳይ ሚኒስቴር መ/ቤት ምክትል<br />
ሚኒስትር ሆኜ ተሾምኩ። ኮ/ል ፈለቀ ወ/<br />
ጊዎርጊስ ሚኒስትር፣ እኔ ምክትል ሆኜ<br />
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />
መልካም ዓዲስ ዓመት<br />
“የ1981 <strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> ለማድረግ<br />
ከሻዕቢያና ከወያኔ ጋር ተስማምተን ነበር”<br />
ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ<br />
ግንቦት 8 ቀን 1981 ዓ.ም በኮሎኔል መንግስቱ ኃ/ማርያም ላይ የተቃጣው መንፈንቅለ <strong>መንግስት</strong> የከሸፈበት ዕለት መሆኑ በኢትዮጵያውያን ዘንድ የሚረሳ አይደለም። የዛሬ 22 ዓመት የተካሄደው ያ የ<strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> ሙከራ ሀገሪቷ በረዥም<br />
ዓመታት ያፈራቻቸውን ምርጥ የጦር ባለሟሎች ያጣችበት ነውና። ኮሎኔል መንግስቱ ወደ ምሥራቅ ጀርመን ለጉብኝት መጓዛቸውን ተከትሎ የተሞከረውና የከሸፈው የግንቦት 8ቱ <strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ ሰፊ ዝግጅት<br />
የተደረገበት፣ በዚያ ወቅት የደርግን ሥርዓት ለመጣል የትጥቅ ትግል ሲያካሂዱ ከነበሩት ሻዕቢያና ህወሀት ጋር ሥምምነት የተደረሰበት ነበር ይላሉ፡- ሻለቃ ዳዊት ወ/ጊዎርጊስ። ሻለቃ ዳዊት፣ በሀገር ውስጥ የ<strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> ሙከራ ያደረጉትን<br />
ጄኔራል መኮንኖችንና የደርግ ጦር አዛዦችን፣ እንዲሁም የደርግን ሥርዓት ለመጣል ይፋለሙ የነበሩትን ሻዕቢያና ህወሀትን በማግባባት ወሳኝ ሚና መጫወታቸውን በተመለከተ በይፋ ቃለምልልስ ሰጥተዋል። ሻለቃ ዳዊት ወ/ጊዎርጊስ ሥርዓቱን<br />
ከድተው የወጡ የመጀመሪያው የደርግ ከፍተኛ ባለሥልጣን መሆናቸው ይታወቃል። ከእሳቸው ቀጥሎ ደርግን ከድተው ከሀገር የወጡት ኮ/ል ጎሹ ወልዴ ናቸው። እነዚህ ሁለት ከፍተኛ የደርግ ሹማምንቶች የሐረር ጦር አካዳሚ ምሩቆችም ነበሩ።<br />
ሁለቱም፣ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን የያዙት ከአሜሪካን ሀገር የል ዩኒቨርስቲ እና ኮሎምቢያ ዩኒቨርስቲ ነው። ከድተው ከሀገር የወጡት እነዚህ ሁለት የሥርዓቱ ባለሥልጣናት አገዛዙን ለመጣል ውጭ ሀገር ሆነው ሲታገሉ፣ ሌሎቹ የደርግ ጄኔራሎች ደግሞ<br />
በሀገር ውስጥ <strong>መፈንቅለ</strong> መንግሥት ለማካሄድ ተስማምተው የግንቦት 8ቱ ሙከራን መታቀዱን ሻለቃ ዳዊት ይተርኩልናል። ኮ/ል መንግስቱ ያንን የ<strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> ሙከራ ይሻገሩ እንጂ፣ ከዚያ በኋላ በሥልጣናቸው ላይ የቆዩት ለሁለት ዓመት<br />
ከ5 ቀናት ብቻ ነበር። ይሁን እንጂ ሻለቃ ዳዊት፣ ከግንቦት 8ቱ በኋላም በኮሎኔሉ ላይ <strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> ታቅዶ ነበር ሲሉም አስገራሚ ቃለምልልስ ሰጥተዋል። በአሁኑ ወቅት በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ውስጥ በመስራት ላይ የሚገኙት ሻለቃ<br />
ዳዊት ወ/ጊዎርጊስ፣ ሰሞኑን ወደዋሽንግተን ዲሲ ለሥራ ብቅ ባሉበት ወቅት ለአንጋፋው ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና የሰጡት ቃለ-ምልልስ እስካሁን ያልተሰሙና ተደብቀው የቆዩ ታሪኮችን የያዘ ሆኖ አግኝተነዋል። ስለዚህም ለአንባቢዎቻችን ግንዛቤ ይረዳ<br />
ዘንድ፣ የሻለቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስን ቃለምልልስ እንደሚከተለው አቅርበነዋል።<br />
ለ3 ዓመት አገለገልኩ።<br />
ውጭ ጉዳይ ም/ሚኒስትር የሆንኩት<br />
በመጥፎ ጊዜ ነበር። የሱማሌ ወረራ<br />
ነበር በወቅቱ። ያኔ የኢትዮጵያ ድንበር<br />
እንደተደፈረ፣ ህልውናዋ እንደተነካ<br />
በየክፍለ ዓለማቱ እየተዘዋወሩ ለማሳማን<br />
የደከምንበትና ከፍተኛ ትግል የገጠምንበት<br />
ወቅት ነበር።<br />
በዚያ ጊዜ ኢትዮጵያ ማርክስሲት ርዕዮትን<br />
እየተከተለች እንደገና ደግሞ ወደ ምዕራቡ<br />
አገር ሄዳ ዕርዳታና ድጋፍ ለመጠየቅ<br />
የተገደደችበት ወቅት ነበር። በአንድ<br />
በኩል በድርቅ ለተጎዳው ህዝባችን ዕርዳታ<br />
ሰጡን፣ በሌላ በኩል ግሞ ሀገራችን<br />
ስለተወረረች የፖለቲካ ድጋፍ ስጡን<br />
ብሎ ዓለምን መጠየቅና የፈለግነውን ነገር<br />
ማግኘት ቀላል ነገር አልነበረም። ያንን<br />
ሁኔታ አስታርቆና ሚዛን ጠብቆ ተጠቃሚ<br />
መሆን መቻል ፈታኝ ነበር፡፡<br />
ከዚያ በኋላ ደግሞ የኤርትራ ዋና ተጠሪ<br />
ሆኜ ተሾምኩ። ኤርትራን የማስተዳደር<br />
ኃላፊነት የኔ ነበር። በመስክ ያለው ወታደራዊ<br />
ጉዳይ የኔ ኃላፊነት አልነበረም። ህዝቡን<br />
ማስተዳደርን፣ ፀጥታውን ማስጠበቅ፣<br />
የኤርትራ ህዝብ በኢትዮጵያዊነቱ ፀንቶ<br />
እንዲቆይ ማድረግ የእኔ ኃላፊነት ነበር።<br />
ኤርትራ በአስተዳደሪነት 3 ዓመት<br />
ሰርቻለሁ። በጣም ደስተኛ የሆንኩበትን<br />
ፍሬያማ ሥራ አከናውኛለሁ። በወቅቱ<br />
የኤርትራ ህዝብ ሁሉ የሚመሰክረው<br />
ተግባር ተወጥቻለሁ።<br />
እርስዎ በቀይ ኮከብ ዘመቻ ጊዜ የኤርትራ አስተዳዳሪ<br />
ነበሩ?<br />
አዎ! ከ74-76 ዓ.ም ማለት ነው። በዓሉ<br />
ግርማ ኦሮማይን ሲፅፍ ማለት ነው።<br />
አብረን ኤርትራ ነበርን።<br />
ለህትመት ካበቋቸው መፅሐፎች የአንዱን ገቢ<br />
‹‹ለኤርትራና ኢትዮጵያ ህዝቦች ወዳጅነት<br />
ማህበር›› መስጠትዎን አንብቤአለሁ። ከዚህ በኋላ<br />
የኤርትራና የኢትዮጵያ ህዝብ እንደገና አብሮ ይኖራል<br />
የሚል ተስፋ አለዎት ማለት ነው? የመፅሐፍዎን<br />
ሽያጭ የለገሱት ማህበር ዓላማስ ምንድን ነው? ምንስ<br />
እየሰራ ነው?<br />
ምን መሰለህ? አሁን ኤርትራን መገንጠል<br />
የመጀመሪያው አማራጭ ከሆነ፣ ቀጥሎ<br />
መምጣት ያለት አማራጭ የኢትዮጵያ እና<br />
የኤርትራ ህዝብ አንድ መሆን ይገባዋል<br />
የሚል መሆን አለበት። ህዝቡ በጠላትነት<br />
መተያየት የለበትም። ሁለቱ ህዝቦች<br />
ሰላማቸው፣ ኢኮኖሚያቸው፣ አኗኗራቸው<br />
ወዘተ አንድ አይነት ነው። ሁሉም ነገር<br />
የሚያገናኛቸው ናቸው። ኤርትራ ላይ<br />
የመጣ ነገር ኢትዮጵያንም ይነካል።<br />
ኢትዮጰያ ላይ የመጣ ነገር ሁሉ ኤርትራን<br />
ይነካል።<br />
ባለፉት 150 ዓመታት በኢትዮጵያ ወደ<br />
90 ያህል ጦርነቶች ተደርገዋል። ከእነዚህ<br />
ጦርነቶች ውስጥ 95 በመቶ ያህሉ<br />
የመጣው በኤርትራ ባህር በኩል ነው።<br />
አሁንም የእስልምና አክራሪነት ቢከሰት፣<br />
የሶማሌ ጦርነት ቢመጣ፣ የኢኮኖሚ<br />
ችግር ወዘተ ቢፈጠር፣ የሚመጣው<br />
በኤርትራ በኩል ነው። ልክ እንደዚያው<br />
ሁሉ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚፈጠር<br />
ችግር ሁሉ ኤርትራ ውስጥ ይሰማል።<br />
ስለዚህ አብረን መኖር የሚገባን ህዝቦች<br />
ነን። በሁሉም ነገር ተሳስረን ያለን እና<br />
የምንኖር ነን። ይህንን ዕውነታ በፖለቲካ<br />
ማሰር ባይቻልም፣ አብረን በሰላም መኖር<br />
አለብን በሚል መርህ ነው ማህበሩን<br />
የመሰረትነው።ማህበሩ በሁለቱ ሕዝቦች<br />
መሀከል ያለውን የጋራ ትስስርና ታሪክ<br />
የሚያጎላ፣ ህዝቡን የሚያነቃቃ ስለሆነ<br />
ነው የመፅሀፌን ገቢ ያበረከትኩት።<br />
ማህበሩን የመሠረታችሁት ኢትዮጵያውያንና<br />
ኤርትራውያን በጋራ ሆናችሁ ነው?<br />
አዎ! በመሀሉ ግን እኔ የማህበር ሥራ<br />
መስራት አልቻልኩም። አሁን በአሜሪካ<br />
ሳንሆዜ ያሉ ሌሎች ድርጅቶች ናቸው<br />
ዓላማውን የሚያራምዱት።<br />
እርስዎ ግን ኢትዮጵያና ኤርትራ አንድ ቀን<br />
በኮንፌዴሬሽንም ሆነ በሌላ መልክ አብረው መኖር<br />
ይችላሉ ብለው ይገምታሉ?<br />
አዎ ይችላሉ። ግን በመጀመሪያ ደረጃ<br />
መሠረቱ አሁን መጣል አለበት።<br />
መልካም። እርስዎ የእርዳታ ማስተባበሪያ ኮሚሽን<br />
ኮሚሽነር በነበሩበት ጊዜ ስለተከሰተው ረሃብና<br />
ስለሆነው ነገር በጥቂቱ ሊነግሩኝ ይችላሉ?<br />
እ.አ.አ ከ82-85 ዓ.ም ማለት ነው<br />
እኔ በእርዳታ ኮሚሽን ኮሚሽነርንት<br />
ያገለገልኩት። ያኔ ኢትዮጵያ ውስጥ<br />
የተከሰተውን ከባድ የድርቅ ችግር<br />
ለመታደግ ዓለም በሙሉ የተንቀሳቀሰበት<br />
ዘመን ነው።<br />
አሁን በሶማሌ፣ በኢትዮጵያና በኬንያ<br />
የተፈጠረውን የድርቅ ችግር ከዚያ ዘመን<br />
ጋር ይወዳደራል የሚሉ አሉ። ቢሆንም፣<br />
ያኔ የተከሰተው የድርቅ ችግር ግን እጅግ<br />
የከፋ ነበር። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት<br />
ወዲህ መላውን ዓለም ያስተባበረ የድርቅ<br />
ችግር ነበር የተከሰተው።<br />
የአጋጣሚ ነገር ሆኖ፣ ያኔ የደርግ<br />
<strong>መንግስት</strong> የፖለቲካ አሰላለፍ ከምስራቁ<br />
ዓለም ጋር ነበር። ዕርዳታ ለመስጠት<br />
የተዘጋጀው ደግሞ ምዕራቡ ዓለም ነው።<br />
ይህንን ሁለቱን ጉዳይ ማስታረቅ ከባድ<br />
ፈተና ነበር። ከዚህ ሌላ የደርግ <strong>መንግስት</strong><br />
10ኛውን የአብዮት በዓል አከብራለሁ<br />
ብሎ የተነሳበት ነበርና ድርቅ አለ ብሎ<br />
ማመን አልፈለገም። ኢትዮጵያ በሀብት<br />
በለፀገች፣ አደገች፣ በሀብት ተጥለጠለቀች<br />
ተብሎ ፕሮፓጋንዳ የሚነዛበት ወቅት<br />
ነበር። ዕውነታው አፍጥጦ የሚታይ<br />
ነበር። ምዕራቡ ዓለም ዕርዳታ ለመስጠት<br />
ቢዘጋጅም፣ ደርግ መቀበል አልፈለገም።<br />
‹‹ችግር የለም፤ ድርቅ የለም፤ ችግሩን<br />
የፈጠራችሁት እናንተ ናችሁ›› ባይ<br />
ነው። ይህንን ማስታርቆ ህዝቡን ከችግር<br />
መታደግ ለእኔ እጅግ ከባድ ፈተና ነበር።<br />
ያም ሆነ ይህ፣ የዓለም ዕውቅ አርቲስቶች<br />
‹‹We are the World›› የተሰኘ ኮንሰርት<br />
አዘጋጁ። ያንን ዘፈን ሲያዘጋጁ አማክረን<br />
ብለው ወደ አሜሪካ ጠርተውኝ ነበር።<br />
በ ገፅ 18
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />
መልካም ዓዲስ ዓመት<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
17
18<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
ሴ ት<br />
ሴበመቅደስ<br />
ፍስሐ<br />
tigi.vip@gmail.com<br />
ኪራይ ሰብሳቢዎቹ<br />
በ2002 ዓ.ም ለ2003 መባቻ፣ ‹‹አዲስ›› ብለን ልንቀበለው<br />
የጥቂት ቀናት ልዩነት ሲቀረን፣ በዚሁ ዓምድ<br />
ያቀረብነው አንድ ጽሁፍ ነበር - ኪራይ ሰብሳቢ ሕፃናትን<br />
በማስመልከት።<br />
ለማስታወስ ያህል፡-<br />
ሴቶቹ፣ በአዲስ ዓመት ወቅት የሚጨፍሩበት መንገድና<br />
ወንዶቹ የሚጨፍሩበት መንገድ አንድ እንዳልሆነ ያወዳደርንበት ሁኔታ<br />
ነበር። ባህል እየተበረዘ ነው (ኧረ እንደውም እየጠፋ ነው!) ብለን ነበር።<br />
ልክ ነው። ባህል አጥፊዎቹ ራሳቸው ባህልን ናፋቂዎቹ ሆነው ተቸገርን<br />
እንጂ።<br />
የወንዶቹ ማስጠንቀቂያ አይሉት ‹‹ሆያ-ሆዬ›› አስቂኝም፣<br />
አሳቃቂም ነው። እስቲ በደጅዎ የቆሙ ታዳጊ ሆያ-ሆዬ ጨፋሪ ህፃናት<br />
ሲጨፍሩ እንዳልሰሙአቸው ሆነው ዝም ይበሏቸው፤ ድካማቸው ከንቱ<br />
እንዳይሆን የሰጉት ህፃናት፣ ‹‹ኧረ በቃ በቃ ጉሮሮአችን ነቃ›› ብለው<br />
ሊገስፁዎት ይሞክራሉ። ‹‹እምቢኝ›› ካሉም ወንዶቹ ለእርስዎ የሚሆን<br />
የስድብ ግጥም አያጡም።<br />
አንዳንዴም እነሱ በምን ገንዘብ እንደሚያገኙ ይገባቸዋልና<br />
እንዲገጥምላቸው ብቻ የሚጠቀሙት ንግግርም አጀብ ያሰኛል። የሰማንያ<br />
ዓመቱን ሽማግሌ ‹‹የኔ’ማ አባባ ኢትዮጵያዊው ሩኒ›› ሊሉም ይችላሉ -<br />
ታዲያ ይሄን ምን ይሉታል?<br />
የሴቶቹም ከዚህ በብዙ ይለያል ማለት አይደለም። ነገር ግን<br />
‘የአለማመን’ ዘይቤአቸው ይለያል። የእነሱ እንደወንዶቹ ትዕዛዛዊና<br />
ሽንገላዊ አይደለም። ልምምጥ ነው። ሌላውን ሰው የሚያሳዝን፣<br />
የሚያራራና ሆድ የሚያባባ አይነት ነው። ሴቶቹ እንደወንዶች ‹‹ኧረ<br />
በቃ በቃ ጉሮሮአችን ነቃ›› ላይልዎት ይችላሉ።<br />
የሴቶቹ የጭፈራ ስርዓት ልምምጥንና የሌላውን ሰው<br />
ሩሁሩነት መፈለግ መሆኑን በዚህ ማረጋገጥ እንችላለን፡-<br />
‹‹ . . . እንኳን ቤትና የለኝም አጥር፣<br />
እደጅ አድራለሁ ኮከብ ስቆጥር።<br />
ኮከብ ቆጥሬ ስገባ ቤቴ፣<br />
ትቆጣኛለች የእንጀራ እናቴ።››<br />
በማለት እርስዎ የማያገባዎትን፣ ነገር ግን እነርሱ የእርስዎን ልብ<br />
ያራራል ያሉበትን መንገድ ይጠቀማሉ።<br />
የሴቶቹ ምርቃት ከወንዶቹ ይለያል። ወንዶቹ፡-<br />
‹‹…ክበር በስንዴ ክበር በጤፍ፣<br />
ምቀኛ ይርገፍ፣ እንደቆላ ጤፍ።››<br />
ሊልዎት ይችላሉ። በስንዴና በጤፍ መክበር እንደሚቻል ያገናዘቡ<br />
የሚመስሉት ህፃናቱ፣ ለጭፈራቸው ክፍያ ያበረከቱት ሽልማት በስንዴ<br />
የተጋገረ ዳቦ ቢሆን ይሄ ምርቃት ላይደርስዎም ይችላል።<br />
ሴቶቹ፡- የዛሬ ባለውለታቸውን ለዛሬ ዓመትም እንዲያገኙት<br />
በመመኘት፡-<br />
‹‹ከብረው ይቆዩኝ ከብረው፣<br />
ባ’መት ወንድ ልጅ ወልደው፣<br />
ሰላሳ ጥጆች አስረው።›› ብለው መልካም ምኞትን<br />
ይገለፃሉ።<br />
አንዳንዴ በወንዶች የ‹‹ሆያ-ሆዬ›› በዓል ሴቶች እንደ ወንድ<br />
ሲጨፍሩ ገጥሞዎት ያውቃል? ለምን ይሆን? የሚል ጥያቄ ውስጤ<br />
ያጭራል። እንደ ወንድ መሆን የመመኘት ሀሳቡ የመጣው ከምን<br />
ይሆን? እኔ መልስ የለኝም።<br />
ነጥቡ ከላይ ለትውስታ ያነሳነው ነገር ብቻም አይደለም።<br />
ከዓመት ዓመት ይሄው ጉዳይ እየተቀየረና በሚገርም ሁኔታ ከትክክለኛ<br />
ባህሉ እያፈነገጠ መሆኑ እንጂ። ጠያቂዎቹ ህፃናት እንዳሉ ሆነው<br />
ሰጪዎቹ ምን ነካቸው የሚያስብል ነው።<br />
‹‹ዮንዜና ዮንዜ ሳቢሳ፣ ጠላትህ ይበሳ እንደ አሮጌ ጣሳ።›› .<br />
. . የተባለው አባወራ ምናልባትም ፀበኛ ጎረቤት ካለው የልቡ ደርሷልና<br />
ግጥም አድርጎ ይሸልም ይሆናል። ነገር ግን መሆን ያለበት ያ አልነበረም።<br />
እኛ እንዲህ እያደረግን ተመልሰን ደግሞ ‹‹ወይ ጊዜ!›› ብንል ምን ዋጋ<br />
ይኖረዋል። ባህል ስለመበላሸቱ ተጠያቂው ተረካቢው ትውልድ ሳይሆን<br />
አስረካቢው ትውልድም እንደሆነ ልብ ይሏል። እናስብበት።<br />
ወደአዲስ ዓመት ስንመጣስ? እንዲህ ነው፡- ‹‹አዲስ›› ብለን<br />
አንድ ነገር ስንገዛ ቀድሞ የነበረንን አሮጌ ነገር በአግባቡ ተጠቅመንበት<br />
ሲያልቅ (ተጠቅመንበታል ብለን ስናስብ) ነው። በዚህ ሊያልቅ የቀናት<br />
ልዩነት በቀረው ‹‹አሮጌ›› ዓመት የፈፀምነውን በጎ ተግባር ብቻ በማሰብ<br />
ዓመቱን በጥሩ ሁኔታ ተጠቅመንበታል ብለን የምናስብ ከሆነ ስህተት<br />
ሰርተናል።<br />
ከወንዶቹ በመቀጠል ዓመቱን በመልካም ምኞት ያስጀመሩን<br />
ሴት ህፃናት ለእነሱ የተሳካ ላይሆን ይችላል።<br />
‹ከብረው ይቆዩኝ› ብለው የመረቁዎትና መልካም ምኛታቸውን<br />
የገለፁልዎ ሴት ህፃናት በዓመቱ ያለ እድሜያቸው ወልደው የኃላፊነት<br />
ሸክም ተከምሮባቸው ያገኙዋቸውም ይሆናል። አሊያም ያለአቅማቸው<br />
በተሰጣቸው የስራ ኃላፊነት ላይ ሲዳክሩ፤ አሊያም የትምህርት እድል<br />
ተነፍጓቸው ቤት ውስጥ ቁጭ ብለው … ይህ ሁሉ የሚሆነውና<br />
የሚለወጠው በእርስዎ ነው። ያኔ - ‹‹አዲስ›› አስተሳሰብ ያመጡ ቀን -<br />
ሁሌም ለእርስዎ ዓመቱ አዲስ ይሆናል።<br />
ከብረው ይቆዩኝ!<br />
መልካም አዲስ ዓመት!<br />
የአፍሪካ ዜናዎች<br />
እነ ማይክል ጃክሰን፣ እነ ሊየንል<br />
ሪቼ ወዘተ ሁሉ አግኝቼ<br />
አነጋገርኳቸው። የዘፈኑን ግጥም<br />
ሁሉ አየሁ። ሙዚቃውን ሰሩት።<br />
ብዙ የዕርዳታ ገንዘብ አሰባሰቡ።<br />
ከዛ በኋላ ደግሞ ኢትዮጵያ መጡ።<br />
አክብረን ተቀበልናቸው። ቦብ<br />
ጊልዶፍ ደግሞ ከእንግሊዘ አንዲሁ<br />
ለዕርዳታ ተነሳሳ። ላይቭ ኤይድ<br />
አደረገ። በአሜሪካ ፊያደልፊያ<br />
በተካሄደው ‹‹ባንድ ኤይድ›› ላይ<br />
ብርሃነ ደሬሳ ምክትል ኮሚሽነር<br />
ስለነበር በስፍራው ተገኝቶ ነበር።<br />
እንዲህ እንዲህ ባለ ሁኔታ<br />
በታቻለ መጠን እርዳታ እንዲገባ<br />
አድርገናል።<br />
ነገር ግን ጥረታችንን ከምስራቁ<br />
ዓለም ፖለቲካ ጋር ሊታረቅ<br />
አልቻለም። ‹‹ኮሚኒዝም ተበረዘ፤<br />
በዕርዳታ ሰበብ ምዕራቦች ሰርገው<br />
እየገቡ ነው፤ አብዮቱ ተቀለበሰ››<br />
ተባለ። ያኔ የኢትዮጰያን ገፅታ<br />
በማሳየት ረገድ ፊት ለፊት<br />
የነበርኩት እኔ ስለሆንኩ ክፉኛ<br />
እወቀስ ጀመር።<br />
መወቀስ ማለት? ዕርዳታ ለምን ገባ ነው?<br />
አዎ! ለምን ችግር አለ ብላችሁ<br />
ኢትዮጵያን አጋለጣችሁ ነው<br />
የተባለው። ወቅቱ 10ኛው<br />
አብዮት በአል የሚከበርበት ነው።<br />
መንግስቱ ኃ/ማርያም 6 ሰዓት<br />
ሙሉ ንግግር አደረገ።6 ሰዓት<br />
ሙሉ ንግግር ሲያደርግ የአንጎላው<br />
ፕ/ት ዶ ሳንቶስ፣ የዛምቢያ ፕ/ት<br />
ኬኔት ካውንዳ፣ የዚምባቡዌው<br />
ሙጋቤ፣ የደቡብ የመኑ ፕ/ት እና<br />
ሌሎችም እዚያው አዳራሽ ውስጥ<br />
ነበሩ። በስድስት ሰዓት ንግግሩ<br />
ስለዚያ አስከፊ ድርቅ አንድ<br />
ገፅ አልተናገረም። ብቻ ግን፣<br />
ዕርዳታ እንዲገባ እኔ ምዕራቡን<br />
አለም ስለወተወትኩ ‹‹የሲ.<br />
አይ. ኤ ኤጀንት ነው፤ አብዮቱን<br />
ለማስቀልበስ የተቀጠረ ነው››<br />
ስባል ለህይወቴ ፈራሁ። ያኔ<br />
ጠፋሁ፤ አሜሪካ ገባሁ።<br />
አወጣጥዎ ለሥራ ነበር?<br />
አዎ! ለሥራ ነው የወጣሁት።<br />
ምክንያቱም በግልፅ ነው<br />
የተወገዝኩት። ፖሊት ቢሮ<br />
ተጠርቼ ‹‹የኢትዮጵያን አብዮት<br />
ለመቀልበስ ሞክረሀል፤ በዕርዳታ<br />
ሰበብ የኃይማኖት ሰዎች እየገቡ<br />
አይዲዮሎጂውን እንዲበርዙ<br />
አድርገሀል፤ የምዕራባውያን<br />
ወኪሎች ገብተው በኢትዮጵያ ላይ<br />
ሳቦታጅ እንዲፈፅሙ ተባብረሃል።<br />
ከምሥራቁ ዓለም ጋር እንድንጣላ<br />
አድርገሀል››… ወዘተ ተባልኩ።<br />
ለማንኛውም ዛቻ ሲበዛብኝ ከአገር<br />
እንደወጣሁ ቀረሁ።<br />
በዚያ ረሀብ የተነሳ ምን ያህል ሰው እንደሞተ<br />
ይታወቃል? የተገኘውስ ዕርዳታ ህይወት<br />
በማትረፍ ረገድ ምን ያህል አግዟል?<br />
በእውነቱ መገመት በጣም<br />
አስቸጋሪ ነው። የቁጥር ነገር<br />
አስቸጋሪ ይመስለኛል። በእኔ<br />
ግምት 2 ሚለየን ሕዝብ በረሃብ<br />
ህይወቱን አጥቷል። በወቅቱ<br />
ቤት ይቁጠረው ነው ያልነው።<br />
የውጭው ዓለም ዕርዳታ ባይደርስ<br />
ኖሮ ከዚያም በከፋ መጠን ሕዝብ<br />
ያልቅ ነበር። የእኛ መ/ቤት እና<br />
ሌሎች ምግባረ ሰናይ ድርጅቶች<br />
በመተባበር ነው ዕርዳታ እንዲገኝ<br />
ያደረገው። በእውነቱ እኔ በወቅቱ<br />
ሕዝብን ለመታደግ ብርቱ ጥረት<br />
አድርጌያለሁ። ይህንን ጥረቴ<br />
ደግሞ በዚያ ወቅት የተ.መ.ድ<br />
ባለስልጣን የነበሩ ሰው ለሕትመት<br />
ባበቁት መፅሐፍ ‹‹ዳዊት ወ/<br />
ጊዎርጊስ ብርቱ ጥረት ባያደርግ<br />
ኖሮ ከ1 ሚሊዮን የበለጠ ህዝብን<br />
ህይወት ማትረፍ አይቻልም<br />
ነበር›› ሲሉ ምስክርነታቸውን<br />
ሰጥተውበታል። ማዘር ቴሬዛም<br />
እንዲሁ።<br />
ግን እንደው በሚሊየን የሚቆጠር ሕዝብ<br />
ለዕልቂት ከመዳረጉ በፊት መርዳት<br />
አይቻልም ነበር?<br />
በዚያ ወቅት ደርግ በትግራይ<br />
ከወያኔ፣ በኤርትራ ከሻዕቢያ ጋር<br />
ጦርነት ላይ ነበር። እና የደርግ<br />
<strong>መንግስት</strong> የጦርነቱን ቀጠና ክፍት<br />
አድርጎ ሕዝቡ ይረዳ ማለት<br />
በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ሽምቅ<br />
ተዋጊዎችን መርዳት ነው በሚል<br />
አልተቀበለውም። ሕዝቡን ነጥሎ<br />
መርዳት ደግሞ አይቻልም።<br />
የከፋው ረሀብ ያለው ደግሞ<br />
በጦርነቱ ቀጠና ያለው ሕዝብ<br />
ነው። ይሁን እንጂ የእኛ መ/ቤትና<br />
ሌሎች ምግባረ ሰናይ ድርጅቶች<br />
ከሰብዓዊነት አንፃር ሕዝቡ መረዳት<br />
አለበት የሚል ዕምነት ነበረን።<br />
የደርግ መግስት ጭራሽ ረሃብን<br />
መኖሩንም ለመቀበል ፈቃደኛ<br />
ሊሆን አልቻለም። ረሐብ መኖሩን<br />
ቢያምን ይከበራል እንጂ አይናቅም<br />
ነበር። ባለማመሪ የበለጠ ተናቀ።<br />
ሕዝብን ያስጨረሰ <strong>መንግስት</strong><br />
የሚል ስም አተረፈ።<br />
እናንተ ያለውን ሁኔታ ለ<strong>መንግስት</strong> ማስረዳት<br />
አትችሉም ነበር?<br />
እኛማ ተናገርን። እኔ ራሴ በግሌ<br />
ችግሩን ዘርዝሬ ገልጬ ነበር።<br />
‹‹የለም፤ <strong>መንግስት</strong> በአቅሙ<br />
ይረዳል፤ የውጭው ዓለም<br />
አይስማ›› የሚል ምላሽ ነው<br />
ያገኘሁት። እንዲያም ሆኖ ማይክል<br />
በርግ እና መሀመድ ዓሊ (ጋዜጠኛ)<br />
ኮረም ገብተው ሁኔታውን<br />
በፊልም እንዲቀርፁ አደረግን።<br />
ያ ፊልም በቢ.ቢ.ሲ 24 ደቂቃ፣<br />
በአሜሪካው ቢ.ኤን.ሲ ቴሌቪዥን<br />
ደግሞ 4 ደቂቃ ታየ። ዓለም<br />
በሙሉ ለእርዳታ ተንቀሳቀሰ።<br />
የብዙ ሰዎችንም ህይወት ማትረፍ<br />
ተቻለ።<br />
እርስዎ ህይወትዎን ለማትረፍ ከሀገር<br />
እንደወጡ ቢናገሩም፣ በአሜሪካ የተደላደለ<br />
ህይወት እንደገጠመዎት ነው በወቅቱ<br />
ሲነገር የነበረው። ይህ ሁኔታ ደግሞ የደርግ<br />
<strong>መንግስት</strong> ‹‹ዳዊት የሲ.አይ.ኤ ኤጀንት<br />
ነው›› ሲል ያወጣውን መግለጫ ተዓማኒ<br />
ያደርገዋል የሚሉ አሉ። በዚህ ጉዳይ ላይ<br />
የእርስዎ አስተያየት ምንድነው? ለመሆኑ<br />
አሜሪካ እንደደረሱ ወዴት ሄዱ? ምንስ<br />
አደረጉ?<br />
እንዳልከው ደርግ ‹‹ዘርፎ ከሀገር<br />
ወጣ፤ የሲአይኤ ኤጀንት ነው››<br />
ወዘተ የሚል የሥም ማጥፋት<br />
ዘመቻ አካሂዶብኛል። እኔ ግን<br />
እንደማንኛውም ሰው አሜሪካ<br />
እንደገባሁ የፖለቲካ ጥገኝነት<br />
ነው የጠየቅሁት። በዚያ ወቅት<br />
በዕርዳታ ሰጪ ድርጅቶችና<br />
በውጪ መንግስታት ዘንድ<br />
ዕውቅና ስለነበረኝ ብዙም ችግር<br />
አልገጠመኝም።<br />
አሜሪካ ከገባሁ በኋላ ወዲያውኑ<br />
ለደርግ <strong>መንግስት</strong> ሶስት ደብዳቤ<br />
አከታትዬ ፃፍኩ። እነዚያን<br />
ደብዳቤዎች ደበበ እሸቱ አፈላልጎ<br />
በመፅሐፉ ውስጥ አትሞታል።<br />
ደብዳቤዎቹ በፖለቲካውም ሆነ<br />
በኢኮኖሚው መስክ ደርግ ምን<br />
ማድረግ እንደሚገባው የሚመክሩና<br />
<strong>መንግስት</strong>ን የሚያቃኑ ነበሩ። እኔ<br />
የደርግን <strong>መንግስት</strong> በይፋ መኮነን<br />
እና መውገዝ የጀመርኩት የሥም<br />
ማጥፋት ዘመቻ ከተከፈተብኝ<br />
በኋላ ነው። በዚያው ወደ ፖለቲካ<br />
ትግል ገባሁ። ፖለቲካ ውስጥ<br />
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />
መልካም ዓዲስ ዓመት<br />
አወዛጋቢው የዙማ ተሿሚ<br />
ስለአስገድዶ መድፈር እንዲሁም በተመሳሳይ ጾታዎች መካከል<br />
ስለሚደረግ ወሲባዊ ግንኙነት ወይም ግብረ-ሰዶማዊነት በተመለከተ<br />
በሚሰነዝሯቸው አነጋጋሪ አስተያየቶች ይታወቃሉ - ሞጎንግ ሞጎንግ።<br />
እኝህን ግለሰብ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ጃኮብ ዙማ ዋና ዳኛ (ቺፍ<br />
ጀስቲስ) አድረገው በቅርቡ መሾማቸው ጠንካራ ትችት እያስሰነዘረባቸው<br />
ይገኛል።<br />
ከሹመቱ አስቀድሞ የሀገሪቱ ቀንደኛ የሚባሉ ጎትጓች<br />
ቡድኖች ጃኮብ ዙማ ዳኛ ሞጎንግን ዋና ዳኛ አድርገው እንዳይሾሟቸው<br />
ቢጎተጉቷቸውም የሚሰማ ጆሮ አላገኙም። ለጉትጎታቸው ዋነኛ ምክንያት<br />
ብለው የሚያነሱት ተሿሚው በአስገድዶ ደፋሪዎች ላይ ያላቸው አቋም<br />
ጠንካራ አይደለም የሚል ነው።<br />
ውንጀላውን በፍጹም የማይቀበሉት ዋና ዳኛ ሞጎንግ፣ ፈጣሪ<br />
ዋና ዳኛ እንዲሆኑ እንደሚፈልግ መግለፃቸውን ባለፈው ሳምንት ቢቢሲ<br />
ዘግቦ ነበር። ከ2009 አንስቶ በሀገሪቱ ሕገመንግሥታዊ ፍርድ ቤት<br />
ያገለገሉት ዳኛ ሞጎንግ፣ ከዚህ ቀደምም በሀገሪቱ ‹‹ኖርዝ ዌስት›› ግዛት<br />
<strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong>...<br />
በሚገኝ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሆነው አገልግለዋል።<br />
ታዋቂ የደቡብ አፍሪካ የሕግ ባለሙያዎች፣ የሰብዓዊ መብት<br />
ተሟጋች ቡድኖች እና የደቡብ አፍሪካ የሰራተኞች ማኅበር፣ ሹመቱን በይፋ<br />
ከተቃወሙ አካላት መካከል ይጠቀሳሉ። ከዚህም በተጨማሪ፣ የኖቤል የሰላም<br />
ሎሬቶችን - የኢራኗ ሽሪን ኢባዲ፣ የአየርላንዷ ሜይሪድ ማጉዌር እና<br />
አሜሪካዊቷ ጆዲ ዊሊያምስ - ያቀፈው ሴት የኖቤል ተሸላሚዎች ቡድን (The<br />
Nobel Women’s Initiative) ዋና ዳኛ ሞጎንግን በመቃወም በደተረገው ዘመቻ<br />
ድጋፋቸውን ለግሰዋል።<br />
‹‹እንደዚህ አይነት ኃለፊት ሲመጣ፣ ሳልፀልይና ኃላፊቱንም<br />
እንድወስድ እግዚአብሔር መፈለጉን ውስጤ ሳያረጋግጥ አልቀበለውም››<br />
ያሉት አዲሱ ተሿሚ ዋና ዳኛ ሞጎንግ ናቸው። ጃኮብ ዙማም በአዲሱ ተሿሚ<br />
ኃላፊነት ሥር የፍትህ ሥርዓቱ በአስተማማኝ መዳፎች ውስጥ እንደሆን<br />
ያላቸውን እምነት ገልፀዋል።<br />
በ2004 ውስጥ ዳኛ ሞጎንግ አንድ የሰባት ዓመት ሴት አስገድዶ<br />
የደፈረ ግለሰብ የተፈረደበትን የዕድሜ ልክ እስራት ወደ 18 ዓመት ዝቅ እንዲል<br />
ከገባህ ደግሞ ጠንካራ ቆዳ<br />
ሊኖርህ ይገባል። እኔም ጠንካራ<br />
ቆዳ ያለኝ ነኝና ከትግል ወደ ኋላ<br />
አላልኩም።<br />
አሜሪካ እንደተራ ስደተኛ ነው የገባሁት<br />
እያሉኝ ነው?<br />
አዎ እንደማንኛውም ተራ ስደተኛ<br />
ነው የገባሁት።<br />
እሺ፤ መቼ ነው የተባበሩት መንግስታት<br />
ድርጅት ውስጥ ሥራ የጀመሩት?<br />
ወያኔ አዲስ አበባ ከገባ በኋላ<br />
ነው።<br />
ከተሰደዱ በኋላ ወደ ፖለቲካው ትግል<br />
የገቡት እንዴት ነው? ምንስ አደረጉ?<br />
እንደነገርኩህ ደርግን በፅሁፍ<br />
በማጋለጥ ነው የፖለቲካ ትግል<br />
የጀመርኩት። ከዚያ በኋላ ደርግን<br />
ከሥልጣን ለመጣል መጠቀም<br />
የሚገባን አማራጭ ጦርነት<br />
ሳይሆን፣ በውስጡ ባሉ ኃይሎች<br />
መፈንቀል ነው በሚል ከጓደኞቼ<br />
ጋር ‹‹ነፃ የወታደሮች ንቅናቄ››ን<br />
አቋቋምን። እናም ተራማጅ በሆኑ፣<br />
ለፍትህ በቆሙና በደርግ ውስጥ<br />
ባሉ ከፍተኛ መኮንንኖች <strong>መፈንቅለ</strong><br />
<strong>መንግስት</strong> ለማድረግ ሞከርን።<br />
የ1981 ዓ.ምን ማለት ነው።በዚያ<br />
<strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> ሙከራ ውስጥ<br />
ከሀገር ውጪ ያለውን ሁኔታ<br />
የምናስተባብረው እኔ እና ጓደኞቼ<br />
ነበርን። ያንን ያደረግነው ደርግን<br />
በ<strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> አስወግዶ፣<br />
በኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ የሽግግር<br />
<strong>መንግስት</strong> ማቋቋም አለብን በሚል<br />
ነው።በዚህ መሰረት ከሻዕቢያ ጋር<br />
ብዙ ከተወያየን በኋላ ሥምምነት<br />
ላይ ደርሰን ተፈራረምን።<br />
ምን የሚል ሥምምነት ላይ ደርሳችሁ<br />
ተፈራረማችሁ?<br />
በ<strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> ደርግ<br />
ከስልጣን ከተወገደ፣ ሻዕቢያ<br />
ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የሽግግር<br />
መንግስቱ አባል ሆኖ፣ ስለኤርትራ<br />
ሁኔታ ይወያያል የሚል ስምምነት<br />
ላይ ደርሰን ነው የተወዳደርነው።<br />
የት ተገናኝታችሁ ነው የተወያያችሁት?<br />
ኤርትራ መሬት። እኔ ራሴ ናቅፋ<br />
ገብቼ ነው የተፈራረምነው።<br />
ፊርማው ከመፈንቅል መንግስቱ ሙከራ<br />
ቀደም ብሎ ነው የተከናወነው?<br />
አዎ። የ<strong>መፈንቅለ</strong> መንግስቱ<br />
ዋነኛ ዓላማ ጦርነቱን ማቆም<br />
ነው። ጦርነት የማይቆም ከሆነ<br />
<strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> ማድረግ<br />
ጥቅም የለውም። በጥቅሉ ጦርነት<br />
እናቆማለን፤ ሠላም እንፈጥራለን፤<br />
ከዚያ ሁሉን አቀፍ የሽግግር<br />
<strong>መንግስት</strong> እንመሰርታለን የሚል<br />
ነው ስምምነቱ። ለዚህ ሁኔታ<br />
መሳካት ደግሞ በቅድሚያ<br />
ከሻዕቢያና ህወሀት፣ ከኢህአፓ፣<br />
ከኦነግ ጋር መስማማት ያስፈልግ<br />
ነበር።<br />
ከህወሀት ጋር የት ተነጋገራችሁ?<br />
ዋሽንተን ውስጥም ተነጋግረናል።<br />
በዋናነት ከህወሀትጋር<br />
የተነጋገርነው ግን በሻዕቢያ በኩል<br />
ነው።<br />
ከሁሉም ተቃዋሚዎች ጋር በእኩልነት<br />
የሽግግር <strong>መንግስት</strong> ለመመስረት ማለት<br />
ነው?<br />
እንደዛ ነበር የተስማማነው።<br />
ከዚያስ?<br />
በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ <strong>መፈንቅለ</strong><br />
<strong>መንግስት</strong> ለማካሄድ በከፍተኛ<br />
መኮንኖችና ባለሥልጣናት<br />
መሀከል ሙሉ ስምምነት ተደርጎ<br />
አያውቅም። ሀገር ውስጥ በሁሉም<br />
ደረጃ ያሉ፣ ሁሉም መኮንኖች<br />
በሃሳቡ ተስማሙ። የፖሊስ፣ የጦር<br />
ሰራዊት፣ የአየር ኃይል፣ የባሕር<br />
ኃይል አዛዦች፣ ምክትል አዛዦች<br />
በሙሉ ጉዳዩን ተስማምተውበት<br />
ነው እዚያ ደረጃ የደረሱት። ችግር<br />
መሆን የነበረበት እዚያ ስምምነት<br />
ላይ መድረስ ነበር። እንጂ <strong>መፈንቅለ</strong><br />
መንግሱትን ማካሄድ ችግር መሆን<br />
አልነበረበትም።<br />
እርስዎ ሁሉም ተስማሙ ቢሉም<br />
ሜ/ጄ/ል ኃብተጊዎርጊስ ሀብተማሪያም<br />
ባለመስማማታቸው እኮ ነው በ<strong>መፈንቅለ</strong><br />
<strong>መንግስት</strong> አድራጊዎቹ እንደተገደሉ<br />
የሚታወቀው። እና…<br />
ሁሉም ተስማሙ ስልህ፣ እዚያ<br />
ጉዳይ ውስጥ መታቀፍ የሌለባቸው<br />
መጀመያውኑም አልተነገራቸውም።<br />
ለደርግ ሙሉ ድጋፍ የነበራቸው<br />
እነ ጄ/ል ኃብተጊዎርጊስ ኃ/ማሪያም<br />
አልተነገራቸውም። ሌሎቹ ግን<br />
ተነግሯቸዋል። ለምሳሌ ጄኔራል<br />
መርዕድን ውሰድ። የታወቁ የጦር<br />
መኮንን ናቸው፤ ኮንጎና ኮርያ<br />
የዘመቱ ትልቅ ዕውቀት የነበራቸው<br />
የጦር ሰው ናቸው። ጄ/ል ደምሴ<br />
ቡልቶ ለኢትዮጵያ ጦር ከፍተኛ<br />
አስተዋጽኦ ያደረጉ ናቸው። የባህር<br />
ኃይል አዛዥ ኮሞደር ተስፋዬም<br />
እንዲሁ። እነዚህ ሁሉ ከፍተኛ<br />
የጦር አዛዦች የተስማሙበት<br />
<strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> ነው<br />
የተካሄደው።<br />
እነዚህ ምርጥ የጦር መኮንኖች በእናንተ<br />
ስምምነት መሰረት የሽግግር <strong>መንግስት</strong><br />
በመመስረቱ ጉዳይ ላይ ተስማምተው ነበር?<br />
<strong>መፈንቅለ</strong> መንግስቱ ቢሳካ እንኳ፣ እነሱ<br />
እርስ በርስ ለሥልጣን ሊሻኮቱ ይችላሉ<br />
የሚል ሥጋት የነበራቸው ብዙ ሰዎች አሉ።<br />
ያ ሁኔታ ላለመከሰቱ ምን ማስተማመኛ<br />
ነበራችሁ?<br />
በዋናነት <strong>መፈንቅለ</strong> መንግስቱ<br />
ከተደረገ በኋላ በ15 ቀን ወይም<br />
3 ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ<br />
የሽግግር መንግሰት ይቋቋማል<br />
የሚል ስምምነት ነው የደረስነው።<br />
ሀገር ቤት የጦሩ ኃላፊነት ያቺን<br />
<strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> ማካሄድ ብቻ<br />
ነበር። ሻዕቢያ፣ ህወሀት፣ ኦነግ፣<br />
ኢህአፓ ወዘተ ወዲያው ሀገር<br />
ቤት ገብተው 15 ቀን ባልሞላ<br />
ጊዜ ውስጥ ሽግግር <strong>መንግስት</strong><br />
ለመመስረት ተስማምተው ነበር።<br />
እዚያ አዲስ አበባ <strong>መፈንቅለ</strong><br />
<strong>መንግስት</strong> ማድረግ የተስማሙት<br />
ሰዎች ሌላ ዓላማ ይኑራቸው<br />
አይኑራቸው አላውቅም። ነገር ግን<br />
ከእኛ ጋር የተደረገው ስምምነትና<br />
ዝግጅት እንደነገርኩህ ነው።<br />
ግን የሽግግር መንግስቱን ለማካሄድ የሆነ<br />
ኮማቴ መኖር አለበት። ኮሚቴ ካለ፣ ያንን<br />
ኮሚቴ ማን እንደሚመራው ይታወቃል?<br />
እኔ በውጭ ሀገር በኩል ያለውን<br />
ሁኔታ ነው የማውቀው። ሀገር<br />
ውስጥ እስከመጨረሻዋ ደረጃ<br />
ድረስ የሆነውን የሰማሁት ልክ<br />
እንደእናንተው ነው። እኛ አርብ<br />
ዕለት ካርቱም ገባን። ስምምነት<br />
ላይ ደረስን። ማክሰኞ <strong>መፈንቅለ</strong><br />
<strong>መንግስት</strong> ይደረጋል አሉን።<br />
ማክሰኞ ዕለት ይሳካል ብለን<br />
ለተባበሩት መንግሰታት አንዳንድ<br />
ነገር ስናደርግ <strong>መፈንቅለ</strong> መንግስቱ<br />
ከሸፈ ተባለ። ሌላውን ነገር እኔ<br />
አላውቅም። የሚያውቁት ሀገር<br />
ውስጥ የነበሩት ናቸው። እኔ<br />
‹‹አሉ››ን ነው የምሰማው።<br />
<strong>መፈንቅለ</strong> መንግስቱ ከከሸፈ በኋላ፣ እናንተ<br />
የመሠረታችሁት ነፃ የወታደሮች ንቅናቄ<br />
ተበተነ ወይስ?<br />
አይ… ሌላ ሁተኛና ሶስተኛ<br />
የ<strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> ሙከራ<br />
ለማድግ ሞክረናል።<br />
(ሻለቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ ለዚህና ለሌሎች<br />
አነጋጋሪ ጥያቄዎች የሰጡትን ምላሽ<br />
በሚቀጥለው ሳምንት ይዘን እንቀርባለን።
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />
መልካም ዓዲስ ዓመት<br />
አድርገው ነበር። ከዓመት በኋላም የሰባት ዓመት ዕድሜ<br />
ሴትን ለመድፈር ሙከራ ያደረገ ግለሰብ የተፈረደበትን<br />
የአምስት ዓመት እስራት ወደ ሁለት ዓመት ዝቅ አድርገው<br />
ወስነዋል። በሌላ ውሳኔያቸው ደግሞ ለአንድ ባለቤቱን/<br />
ሚስቱን ለደፈረ ባል ይቅረታቸውን አጎናፅፈውታል።<br />
የተዘገበው ምክንያታቸውም በወቅቱ ባለቤቱ የምሽት ልብስ<br />
እና የውስጥ ሱሪ ለብሰው የነበረ መሆኑ ነው።<br />
በባልና በሚስት መሀከል የሚደረግ ወሲባዊ<br />
ግንኙነትን እንደ አስገድዶ ደፈራ እንደማይቆጥሩ<br />
በሶስየትድ ፕሬስ የተዘገበላቸው ዋና ዳኛ ሞጎንግ ግን<br />
ይህ ሁሉ ተቃውሞ ቢሰነዘርባቸውም፣ የደቡብ አፍሪካን<br />
ሕገመንግሥት እንደሚያስፈጽሙ እና በሀገሪቱም ላዕላይ<br />
ሕግ መሰረት እንደሚገዙ በመግለጽ ሹመቱን በጸጋ<br />
ተቀብለዋል።<br />
በዓለም አቀፍ ደረጃ የአስገድዶ ደፈራ ወንጀሎች<br />
በተደጋጋሚ ከሚፈፀሙባቸው ሀገራት መካከል ደቡብ<br />
አፍሪካ ከቀዳሚ ተሰላፊዎች መካከል ግንባር ቀደሟ<br />
ናት። በኢንተርፖል መረጃ መሰረት፣ በደቡብ አፍሪካ<br />
በየ17 ሰከንዶች ውስጥ አንድ የአስገድዶ ደፈራ ወንጀል<br />
ይፈፀማል።<br />
/ምንጭ - ቢ.ቢ.ሲ/<br />
በኤልያስ ገብሩ<br />
ከታህሳስ 1953 ዓ.ም. ጀምሮ የኢትዮጵያ<br />
ሕዝብ የሉዓላዊ ስልጣኑ ባለቤት ለመሆን የጀመረው<br />
ሁሉን አቀፍ ትግል ሳይሳካ ሃምሳ ዓመታት<br />
እንደሞላው በመጥቀስ፣ ‹‹ቀጣዩ ዓመት የጨለማ<br />
ጊዜ ሆኖ መቀጠል የለበትም›› ሲል አንድነት<br />
ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ትናንት<br />
መግለጫ አወጣ።<br />
ቀጣዩ 2004 ዓ.ም. ለሁለንተናዊ ነፃነት<br />
ሁሉን አቀፍ የነፃነት ትግል የሚደረግበት ዓመት<br />
ሊሆን እንደሚገባ የገለፀው አንድነት ‹‹የሚደረገው<br />
የነፃነት ትግልም ለኢትዮጵያውያን ሁሉ ለኢህአዴግ<br />
አባላትም ጭምር ነፃነትን የሚያጎናፅፍ ሊሆን<br />
ይገባዋል። ትግሉ ከዘረኝነት ከበቀልና ከቁርሾ የፀዳ<br />
ሁላችንንም ኢትዮጵያውያንን ከሊቅ -እስከ ደቂቅ<br />
በደቡብ ምስራቃዊ አፍሪካ የምትገኘው ማላዊ መሪ የሆኑት ፕሬዝዳንት ቢንጉ<br />
ዋ ሙታሪካ፣ ባቤታቸውን የመንግሥታቸው የሥራ አስፈፃሚ አካል አባል<br />
ማድረጋቸው፣ እና እንዲሁም ወንድማቸውን በፊት ከነበሩበት መንግሥታዊ<br />
ሥልጣን አንስተው ከፍ ላለ ኃላፊነት መሾማቸው አነጋጋሪ አድርጓቸዋል።<br />
ባለፈው ረቡዕ ነበር ባለቤታቸውን ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ እና የሴቶች ጉዳዮች ሚኒስትር<br />
አድርገው የሾሟቸው። ባለፈው ሀምሌ ወር ውስጥ በመንግሥታቸው ላይ በተካሄደ<br />
የተቃውሞ ሰልፍ በተፈጠረ ግጭት 19 ሰዎች ከሞቱ በኋላ በተከተለው የካቢኒ<br />
ብፕወዛ፣ ከባለቤታቸው ካሊስታ ሹመት በተጨማሪ ወንድማቸው ፒተር ሙታሪካ<br />
በሚኒስትርነት ማዕረግ ወደ ሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ተዘዋውረዋል።<br />
የዚያ የሰው ህይወት የጠፋበት ሰልፍ አደራጆች ለፕሬዝዳንት ሙታሪካ አንድ<br />
ጠንካራና ቆራጥ የተባለ ቀነ-ገደብ አስቀምጠውላቸዋል - እስከ መስከረም 21 ድረስ<br />
መንግሥታዊ ማሻሻያዎችን እንዲወስዱ።<br />
ያም ሆኖ፣ ቀነ-ገደቡ ተከበረም አልተከበረም፣ ሚር. ሙታሪካ የሚመሩትን<br />
መንግሥት የቤተ-ዘመድ መሰብሰቢያ አድርገዋል የሚል ውንጀላ በይፋ ከመሰንዘሩ<br />
በፊት ሚስታቸውንና ወንድማቸውን የካቢኔ አባል ለማድረጋቸው አሳማኝ ምክንያት<br />
ማቅረብ እንደሚጠብቅባቸው ማሳሰቢያ ያስተላፉት የአገሪቱ ተቃዋሚ የፖለቲካ<br />
ድርጅት - የማላዊ ኮንግሬስ ፓርቲ - መሪ ጆን ቴምቦ ናቸው።<br />
እንቅስቃሴዎቹንም በቅርበት ስንከታተል ቆይተናል››<br />
ቢሉም የመድረክ አመራሮች ውድቅ አድርገውታል።<br />
መድረኩ ትናንት በሰጠው ጋዜጣዊ<br />
መግለጫ ላይ ‹‹የደበበ እሸቱን መታሰር መድረክ<br />
በተለይም አንድነት ፓርቲ እንዴት ያየዋል?›› የሚል<br />
ጥያቄ ከአውራምባ ታይምስ ቀርቦ የነበረ ሲሆን፣ ባለው<br />
የፖለቲካ አቋም የተነሳ በኢህአዴግ እንደማይወደድ<br />
ያስታወሱት የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ<br />
ጊዳዳ፣ ‹‹እንደ አንድ የኢትዮጵያ ታጋይ እንዲለቀቅ<br />
አንድነትና መድረክ ይጠይቃሉ›› ብለዋል። የፓርቲው<br />
ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆኑት አቶ አንዷለም አራጌም<br />
ደበበ እሸቱን በደንብ እንደሚያውቁትና ‹‹በሽብር<br />
ተግባር ይሰማራል›› የሚል ዕምነት እንደሌላቸው<br />
ተናግረዋል።<br />
የቀድሞው ቅንጅት የላዕላይ ም/ቤት<br />
አባልና የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ የነበረው አርቲስት<br />
ደበበ፣ ምርጫ 97ን ተከትሎ ከሌሎች የቅንጅት<br />
አመራር አባላት ጋር የዕድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበት<br />
ዜናዎች<br />
ፕሬዝዳንቱ ሚስታቸውን ሾሙ<br />
የአፍሪካ ዜናዎች<br />
እንደተንታኞች እይታ ከሆነ፣ ፕሬዝዳንቱ ወንድማቸውን የሾሙበት ዋነኛ ዓላማ<br />
እየተንገዳገደች ላለችው ሀገር ‹‹አዲስ›› መሪ (ወይም ወራሻቸውን) አስቀድመው ለማዘጋጀት<br />
እና በዚህም መንገድ የዓለማቀፋዊ ግንኙቶች ተሞክሮአቸውን ማዳበር ነው።<br />
በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት መግቢያ አካባቢ የሙታሪካ መንግሥት በሙስና ተጨማልቋል፣<br />
ኢኮኖሚውን አመሳቅሏል በሚሉ ዋነኛ ምክንያቶች ዮናይትድ ኪንግደም ለማላዊ ትሰጥ<br />
የነበረውን እርዳታ ማቋረጧ ይታወሳል።<br />
ይህ የኢኮኖሚ ጉዳይ ባለፈው ወር ለተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ ተጠቃሽ ምክንያት ነበር -<br />
በሀገሪቱ ተቃዋሚዎች። ተቃዋሚዎቹ እንደሚሉት፣ ማላዊ ከእንግሊዝ የ73 ዓመታት የቅኝ<br />
አገዛዝ በኋላ በሀምሌ 6/1964 (እ.አ.አ) ነፃነቷን ከተቀዳጀች በኋላ ካጋጠሟት ኢኮኖሚያዊ<br />
ቀውሶች መካከል ይሄኛው በአስከፊነቱ ቀዳሚው ነው።<br />
ከፍተኛ የነዳጅ፣ የኤሌክትሪክ ኃይል እና የውጭ የመገበያያ ገንዘብ እጥረት በአሁኑ ወቅተ<br />
ሀገሪቱን እያመሷት ይገኛሉ። ባለፈው ወር የፕሬዝዳንት ሙታሪካ መንግሥት የሀገሪቱ<br />
የመገበያያ ገንዘብ (‘ዋቻ’) ከዶላር (የአሜሪካ) ጋር ያለውን የምንዛሬ ተመን/ዋጋ ዋጋ ዝቅ<br />
ለማድረግ ተገዶ ነበር።<br />
ከዓለም እጅግ ደሃ ሀገራት ተርታ የምትሰለፈው ማላዊ፣ 75 በመቶ የሚሆነው ሕዝቧ በቀን<br />
ከአንድ ዶላር ባነሰ ገቢ ነው የሚኖረው፤ መኖር ከተባለ።<br />
/ምንጭ - ቢ.ቢ.ሲ/<br />
ሲፒጄ፣ <strong>መንግስት</strong> በጋዜጠኞች ላይ<br />
ያቀረበው ክስ ፍሬ ቢስ መሆኑን ገለፀ<br />
በሱራፍኤል ግርማ<br />
ማድረጋቸውን ላይወድ ይችላል። ግን ጋዜጠኞቹ ርምጃ ነው›› ያለው ጋዜጠኛ ዳዊት፣ <strong>መንግስት</strong> ጋዜጠኞች በተመሳሳይ ሁኔታ የሽብርተኝነት ክስ<br />
ከሥራቸው ፀባይ አኳያ ሁሉንም ወገኖች ማግኘት ጋዜጠኞችን ‹‹በሽብር ተጠርጥረዋል›› እያለ ማሰሩ ተመስርቶባቸዋል።<br />
ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬና ርዕዮት ዓለሙን ግድ ይላቸዋል›› ሲል የ<strong>መንግስት</strong>ን ‹‹ከአሸባሪዎች የ<strong>መንግስት</strong> ጥገኛ ያልሆኑና ተቺ የሚዲያ ተቋማትን<br />
ብሉምበርግ በድረ ገፁ፣ የ<strong>መንግስት</strong><br />
ጨምሮ በሽብርተኝነት ክስ የቀረበባቸውን የስዊዲን<br />
ጋዜጠኞች <strong>መንግስት</strong> በአፋጣኝ እንዲፈታ የጋዜጠኞች<br />
መብቶች ተሟጋች የሆነው ሲፒጄ ጠየቀ። ባወጣው<br />
መግለጫ የኢትዮጵያ <strong>መንግስት</strong> የፀረ ሽብርተኝነት<br />
ሕጉን ለነፃ ፕሬስ ማፈኛነት እየተጠቀመበት መሆኑን<br />
ያስታወቀ ሲሆን፣ ‹‹<strong>መንግስት</strong> ይሄን ፍሬ ቢስ ክሱን<br />
በመተው ጋዜጠኞቹን ሊፈታ ይገባል›› ብሏል።<br />
የሲፒጄ በአፍሪካ አስተባባሪ የሆነው<br />
ሞሐመድ ኪየታም ‹‹የኢትዮጵያ <strong>መንግስት</strong> ‹ሽብርተኛ›<br />
ብሎ ከፈረጃቸው ወገኖች ጋር ጋዜጠኞቹ ግንኙነት<br />
ጋር ንክኪ አላቸው›› የሚል ክስ ውድቅ አድርጓል።<br />
የአውራምባ ታይምስ ም/ዋና አዘጋጅ<br />
በአሸባሪነት መከስስን አስመልክቶ ለተለያዩ ዓለም<br />
አቀፍ የሚዲያ ተቋማት አስተያየቱን የሰጠው<br />
የአውራምባ ታይምስ ማኔጂንግ ኤዲተር ዳዊት ከበደም<br />
በባልደረባው ላይ የቀረበውን ክስ እንደማይቀበል<br />
አስታውቋል።<br />
ለአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ የእንግሊዘኛ<br />
አገልግሎት ዘጋቢ ፒተር ሄንሌ በስልክ በሰጠው ቃለ<br />
መጠይቅ ‹‹ይህ ክስ ነፃውን ፕሬስ ለማሸማቀቅ የተወሰደ<br />
ለማጥፋት የተቀነባበረ ሴራ መሆኑን ተናግሯል።<br />
የ<strong>መንግስት</strong>ን ፖሊሲዎች መተቸት<br />
በአሸባሪነት እየተተረጎመ መሆኑን ያስገነዘበው<br />
የአውራምባ ታይምስ ማኔጅንግ ኤዲተር፣ ለብሉም<br />
በርግ የዜና አውታርም ‹‹የባልደረባችን በሽብር መከሰስ<br />
ጋዜጣው ላይ ተፅዕኖ የማሳረፊያ አንዱ መንገድ ነው››<br />
ሲል ሁኔታውን አብራርቷል።<br />
በሌላ በኩል ከወራት በፊት ፓርላማ<br />
በአሸባሪነት ከፈረጀው ኦብነግ ታጣቂዎች ጋር<br />
ጂጂጋ ከተማ አካባቢ የተያዙት ስዊዲናያዊያን<br />
ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚኒስትር ዲኤታ አቶ<br />
ሽመልስ ከማል ‹‹ግለሰቦቹ ወደ አገር ውስጥ የገቡት<br />
በሕገ ወጥ መንገድ ነው፡፡ ከጋዜጠኝነት ሥራ ውጪ<br />
የጦር መሳሪያ አጠቃቀም ስልጠና ወስደዋል፤ የጦር<br />
መሳሪያ ይዘው የሚያሳይ የቪዲዮ ቴፕም አቃቤ ሕግ<br />
አለው›› ማለታቸውን አስነብቧል።<br />
ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬና ርዕዮት ዓለሙ<br />
ክስ ከተመሰረተባቸው በኋላ በፖሊስ ምርመራ ላይ<br />
ከነበሩበት ‹‹ማዕከላዊ›› ወደ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት<br />
የተዛወሩ ሲሆን፣ ለጥቅምት ዘጠኝ ቀን 2004ዓ.ም<br />
ተቀጥረዋል።<br />
‹‹የኢትዮጵያ ሕዝብ የተነጠቀው ነፃነቱን ለመቀዳጀት ዛሬውኑ ለትግል ይነሳ››<br />
አንድነት ፓርቲ<br />
የሚያስተባብር አንድነታችንን ከመቼውም ጊዜ በላይ<br />
ጎልቶ የሚወጣበት ሊሆን ይገባዋል።›› ብሏል።<br />
የነፃነት ትግሉም መጀመሪያ ፍርሃትን<br />
ድል መንሳት መሆኑን በመጥቀስም፣ በአሁኑ ወቅት<br />
በአረቡ ዓለም እየተካሄደ ያለው የነፃነት ትግልና<br />
ውጤቱም ተግባራዊ ተሞክሮውን ማጠናከሩን፣<br />
ሕዝቡ ነፃ አውጪዎችን ቁጭ ብሎ የሚጠብቅበት<br />
ጊዜ ማብቃቱንና እያንዳንዱ የኢትዮጵያ ሕዝብም<br />
የነፃነቱ ባለቤት ለመሆን አበክሮ ሊታገል እንደሚገባው<br />
መግለጫው አትቷል።<br />
‹‹የወደፊቷን የበለፀገችና ዴሞክራሲያዊት<br />
ኢትዮጵያን መፍጠር ላለበት ኢትዮጵያዊ ወጣት ግን<br />
አምባገነን አገዛዝን ተሸክሞ መኖር ፈፅሞ አማራጭ<br />
ሊሆን አይችልም። በመሆኑም የነፃነት ህልምን እውን<br />
ለማድረግ በ2004 ዓ.ም. የመጀመሪያው እርምጃ<br />
ፍርሃትን ድል መንሳት ነው›› በማለት ፓርቲው<br />
ለኢትዮጵያዊ ወጣት ጥሪውን አስተላልፏል።<br />
ደበበ እሸቱ እንዲፈታ አንድነት...<br />
እንዲሁም በገዥው ፓርቲ ቡራኬ<br />
የሚተዳደሩና ለገዥው ፓርቲ የጭቆና አገዛዝ<br />
ድጋፋቸውን ቀጥተኛ በሆነና ባልሆነ መንገድ እየሰጡ<br />
የሚገኙ “ተቃዋሚ ፓርቲዎች” ሳይረፍድ ከሕዝብ ጎን<br />
እንዲቆሙ አንድነት ሀሳቡን ሰንዝሯል።<br />
የኢትዮጵያ ዲያስፖራም ትኩረቱ የነፃነት<br />
ጥያቄ ላይ መሆን ስለሚገባው ለጥያቄው ተጠናክኖና<br />
ተደራጅቶ መውጣት እንደሚገባው፣ ዓለም አቀፍ<br />
ማሕበረሰብም የኢትዮጵያ ሕዝብ አሁን ካለበት<br />
የጭቆናና የችጋር አዘቅት ራሱን ነፃ ለማውጣት<br />
ለሚያደርገው ትግል ከመቼውም ጊዜ በላቀ መልኩ<br />
ድጋፍ እንዲሰጥ ፓርቲው ጠይቋል።<br />
በመጨረሻም ለኢህአዴግ ጥሪውን<br />
ያስተላለፈው አንድነት፣ አገዛዙ ለሕዝብ ሰላማዊ<br />
የለውጥ እንቅስቃሴ ሰላማዊ ምላሽ ቢሰጥ ከምንም<br />
በላይ ለራሱ፣ ለሕዝብ፣ ለሀገርና ለትውልድ ጠቃሚና<br />
ክቡር ውጤት ማስመዝገብ ይችላል ብሎ እንደሚያምን<br />
በይቅርታ መፈታቱና ከእስር ከተፈታ በኋላ<br />
በመስራችነት ባቋቋመው አንድነት ለዴሞክራሲና<br />
ለፍትሕ ፓርቲ ውስጥ በተፈጠረው የሀሳብ ልዩነት<br />
የተነሳ ‹‹መርህ ይከበር›› በሚል አቋሙ ከፓርቲው<br />
መሰናበቱ ይታወሳል።<br />
ከፖለቲካዊ እንቅስቃሴው በተጨማሪ<br />
በተለያዩ ኪነ-ጥበባዊና ማህበራዊ ክንዋኔዎች ላይ<br />
ተሳታፊ የነበረው አርቲስት ደበበ፣ በሸገር ኤፍ.ኤም<br />
ላይ የመጽሀፍት ትረካ ሲያቀርብ ቆይቷል።<br />
ከመታሰሩ ጥቂት ሠዓታትን ቀደም ብሎ<br />
ለፍትሕ ጋዜጣ የአዲስ ዓመት መልካም ምኞቱን<br />
የሚገልፅ ፅሁፍ ያስገባው ደበበ እሸቱ፣‹‹አዲሱ ዓመት<br />
ከሰቀቀን ኑሮ ተላቀን እፎይ የምንልበት፣በፍራቻ<br />
ሳይሆን በመምረጥ የምንኖርበት እንዲሆን እመኛለሁ››<br />
ብሎ ነበር።<br />
‹‹ረሐብን ማጋለጥ በሽብርተኝነት<br />
ሊያስወነጅል አይገባም›› በሚል ርዕስ የኢትዮጵያ<br />
ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ በሰጠው<br />
ከመታሰሩ ጥቂት ሠዓታትን ቀደም ብሎ ለፍትሕ ጋዜጣ የአዲስ<br />
ዓመት መልካም ምኞቱን የሚገልፅ ፅሁፍ ያስገባው ደበበ እሸቱ፣‹‹አዲሱ<br />
ዓመት ከሰቀቀን ኑሮ ተላቀን እፎይ የምንልበት፣በፍራቻ ሳይሆን<br />
በመምረጥ የምንኖርበት እንዲሆን እመኛለሁ›› ብሎ ነበር።<br />
19<br />
ገልጿል።<br />
በተያያዘ ዜናም ነሐሴ 29 ቀን 2003<br />
ዓ.ም በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ከዜና እወጃ በኋላ ፕ/ር<br />
በየነ ጴጥሮስ በኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰተውን ድርቅ<br />
ምክንያት በማድረግ ተዘጋጅቶ የነበረውን አንድ<br />
የማስተባበያ ፕሮግራም አንድነት ተችቶታል። በዚህ<br />
ፕሮግራም ላይ ቀርበው ከተናገሩት ሰዎች መካከል<br />
በተለይ ሁለቱ ‹‹የመድረክ አባላት ነን›› በማለት<br />
ያቀረቡት አስተያየት የተሳሳተ መሆኑ በመጥቀስ፣<br />
አንደኛ አቶ አበበ ታምራት ከሀምሌ 13/2003 ዓ.ም<br />
ጀምሮ በሥነ-ምግባር ችግር ምክንያት ከፓርቲው<br />
መታገዳቸውን ተገልጿል። ሁለተኛ አቶ አጥናፉ<br />
የተባለው ግለሰብ ደግሞ በሥነ-ምግባር ብልሹነት<br />
የሚታወቅና የመድረክ አባል አለመሆኑን መድረክ<br />
ትናንት በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።<br />
መግለጫ ዋና ርዕሰ ጉዳይ የነበረው በቅርቡ የታሰሩት<br />
የመድረክ አመራር አባላት ጉዳይ ነበር። ለአቶ በቀለ<br />
ገርባ አና ለአቶ ኦልባና ሌሊሳ መታሰር <strong>መንግስት</strong><br />
‹‹ከኦነግ ጋር ሲያሴሩ ነበር›› የሚል ምክንያት<br />
ቢያቀርብም፣ መድረኩ ይህን ውድቅ አድርጎታል፡፡<br />
በመግለጫው መሠረት ለሁለቱ ግለሰቦች<br />
መታሰር ዋንኛው ምክንያት በኢትዮጵያ ስላለው<br />
አጠቃላይ ሁኔታ ለአምንስቲ ኢንተርናሽናል መረጃ<br />
በመስጠታቸውና የኢህአዴግ <strong>መንግስት</strong> የእርዳታ<br />
እህልን ለፖለቲካ መሳሪያነት እያዋለው መሆኑን<br />
ለዘገቡት የቢቢሲ ጋዜጠኞች ጥቆማ በመስጠታቸው<br />
ነው።<br />
ፖለቲከኞቹ የምር የኦነግ አባላት ቢሆኑ<br />
ኖሮ ከኦነግ የሚፃረር የፖለቲካ ፕሮግራም ባለው<br />
መድረክ ውስጥ አባል ከመሆን ይልቅ መገንጠልን<br />
በሚደግፈው ኢህአዴግ ውስጥ መታቀፍ ይችሉ<br />
እንደነበር አቶ ጥላሁን እንዳሻው የተባሉ የመድረክ<br />
አመራር አስገንዝበዋል።<br />
የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ደሞክራሲያዊ<br />
አንድነት መድረክ ሽብርተኝነትን በምንም መልኩ<br />
እንደማይደግፍ አፅንኦት የሰጡት አቶ ገብሩ አስራት<br />
ደግሞ በበኩላቸው፣ ኢህአዴግ ተቃዋሚዎቹንና<br />
ተቺዎቹን በማሰር አጠቃላይ ሕዝቡን እያሸበረ<br />
መሆኑን ገልፀዋል።<br />
በሽብርተኝነት ክስ ስለተመሰረተባቸው<br />
ስዊዲናዊያን ጋዜጠኞች ጉዳይም በመግለጫው ላይ<br />
ተነስቷል። ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ‹‹ሁለቱ ጋዜጠኞች<br />
በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ በመግባት<br />
ሉዓላዊነታችን መደፈሩን እንዴት ያዩታል?›› የሚል<br />
ጥያቄ ለአቶ አንዷለም አራጌ ቀርቦ የነበረ ሲሆን፣<br />
አቶ አንዷለምም ‹‹ኢህአዴግ ሁለት ሰዎች ድንበር<br />
አቋረጡ ብሎ ሊጨነቅ ይቅርና አገር ገንጥሎ የሚሰጥ<br />
ድርጅት ነው›› የሚል መልስ ሰጥተዋል።<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ
20<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />
መልካም ዓዲስ ዓመት<br />
‹‹በቴሌቪዥን በሚሰሩት ‘ድራማ’<br />
ሀቅ ሊወጣ አይችልም››<br />
ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ<br />
/የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ ሊቀ-መንበር እና የመድረክ ምክትል ሊቀ-መንበር/<br />
በአንድ ወር በፊት ቢቢሲ ኒውስ ናይት በተሰኘው ፕሮግራሙ ላይ የኢትዮጵያ <strong>መንግስት</strong> የሚሰጠውን እርዳታ ለፖለቲካ ፍጆታ እንደሚያውለው፣ የተደበቀ<br />
ረሀብ በኢትዮጵያ እንደሚገኝና ሌሎች ሀሳቦችን የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችን እና ቦታው ድረስ ተገኝቶ ተጎጂ ያላቸውን ዜጎች በማነጋገር ዘገባ<br />
ካቀረበ በኋላ የኢትዮጵያ <strong>መንግስት</strong> በተለያየ መንገድ ዘገባው የተሳሳተ መሆኑን መግለፁ ይታወሳል። ባለፈው እሁድ ምሽት በኢትዮጵያ ፈርስት ድረ-ገጽ<br />
ኤዲተር ቢኒያም ከበደ ተዘጋጅቶ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የቀረበው ‹‹ዶክመንተሪ›› ፊልምም በዋነኛነት ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ላይ ባጠነጠነ መልኩ<br />
ለቢቢሲ የሰጡት አስተያየት እውነትነት እንደሌለው የገለፀ ነበር። በዚህና በመሰል ጉዳዮች ዙሪያ የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ ሊቀ-መንበር፣<br />
የመድረክ ምክትል ሊቀ-መንበርና የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆኑት ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስን አቤል ዓለማየሁ አነጋግሯቸዋል።<br />
ኒውስ ናይት በተሰኘው የቢቢሲ ፕሮግራም ላይ <strong>መንግስት</strong> አገር ውስጥ የሚገባ የእርዳታ እህልን ለፖለቲካ ጥቅም እያዋለው እንደሆነ፣ የሚረዱትም<br />
የኢህአዴግ አባላት (ደጋፊዎች) መሆናቸውን ገልፀዋል። ይህን ሀሳብ የሰነዘሩት ከምን ተነስተው ነው?<br />
ኢህአዴግ አባላቱ በሆኑና ‹‹ተቃዋሚ›› በሚላቸው መሀከል አድሎ እንደሚያደርግ ባለፈው 20 ዓመት ስንናገረው የነበረ<br />
ነው። አሁን እነሱን ለምን እንዲህ እንዳርበተበታቸው እኔ’ንጃ። ጉዳዩ ለንደን ደርሶ በቢቢሲ በኩል ተመልሶ ስለመጣ ነው?<br />
በየቀኑ ለጋዜጠኛ ጋዜጣዊ መግለጫ ስንሰጥ የምንናገረው ነው።<br />
በተራቡት ዜጎች ላይ ሞራል የሚነካ ሥራ እንደሚሠራ በአደባባይ ነጋ ጠባ ስናወራው የነበረ ነው። ፓርላማ ውስጥ<br />
በነበርንበት ጊዜም ስንገልፀው የኖርነው ነው። ስም ዝርዝር ሰብስበን ለእርዳታ ለጋሾች ሰጥተን እናውቃለን። ለኢፒጂ<br />
(Ethiopian Partners Group)፣ ዓለም ባንክና ለሌሎችም ሰጥተናል።<br />
ስም ዝርዝራቸው የተገለፀው ሰዎች ምንድን ናቸው?<br />
በምርጫ ሰሞን ባለ ሽኩቻ ሰዎች ማንን እንደሚደግፉ በሚያደረጉት እንቅስቃሴ ወረዳ አመራሮች ተለይተው ይታወቃሉ።<br />
የተቃዋሚ ደጋፊዎችን ምርጫው እንዳለቀ ከሴፍቲ ኔት ዝርዝር ያስወጧቸዋል። እውነታውን ለመደበቅ የሚጠቀሙበት<br />
ቃል ‹‹እናንተ ጨርሳችኋል›› የሚል ነው። የእነዚህ ሰዎች ስም እና የቦታቸውን ስም ዝርዝር ለጠቀስኳቸው ድርጅቶች<br />
ሰጥተናል።<br />
ይህ ችግር በቀድሞ ጊዜም ሆነ አሁን ድረስ አለ ነው የሚሉት?<br />
ይሄ ችግር ድሮም ሆነ አሁንም ያለ ነው። ኢህአዴግ በበቂ መረጃ ማስተባበል የቻለበትን ሁኔታ እስከዛሬ አልተመለከትኩም።<br />
ይህንን አድበስብሶ ማለፍ አይቻልም። የተራበውን ህዝብ [በተለይ የእኛ ደጋፊውን] ‹‹ይህ የመጣው ለኢህአዴግ አባላት<br />
እና ደጋፊዎች ነው። ለእናንተ በየነ ጴጥሮስ ሲያመጣ ትበላላችሁ›› ይሏቸዋል። ይህ የተለመደ አባባል ነው። ጨዋታው<br />
ያለው እነሱ ካምፕ ነው። ለሁሉም እየሰጡ መሆኑን በተግባር ካየን እኛም ወቀሳችንን እናቆማለን። በቴሌቪዥን<br />
በሚሰሩት ድራማ ሀቅ ሊወጣ አይችልም።<br />
‹‹ኢህአዴግ እርዳታን ለፖለቲካ ጥቅም ያውለዋል›› ሲሉ እውን ፖለቲካ ልዩነትን ከማንፀባረቅ በፀዳ መልኩ ነው?<br />
በምርጫ ሰሞን በከባድ መኪና የእርዳታ እህል ሞልቶ የምግብ እጥረት አለ ወደሚባልበት ቦታ መሄዱ ሲሄዱ ለማን<br />
ድምፅ መስጠት እንዳለባቸውም መመሪያ ይሰጧቸዋል።<br />
ዳቦ በጆንያ ይዘው አድለው ከጨረሱ በኋላ ‹‹አባል ሁኑ›› የሚሉበት ሁኔታ መኖሩን እናውቃለን። ሩቅ ሳትሄድ እዚህ<br />
አዲስ አበባ ለኢህአዴግ ድምፅ ይሰጣል ለተባለ ጎረምሳ ሁሉ ሰላሳ እና ሃምሳ ብር ሲያድሉ ይውሉ አልነበር እንዴ?<br />
አድልዎ ማለት ይሄ ነው፤ በገንዘብ ድምፅ መግዛት።<br />
የትም ቀበሌ ያለ ወጣት ሥራቸውን ይንቃል። ገንዘቧን ግን ‹‹እፈልጋታለሁ›› ብሎ ይወስዳል። ይህን የሚያደርጉት የቀን<br />
የውሎ አበል የሚከፈላቸው ካድሬዎቻቸው ናቸው። በአንድ የምርጫ ክልል ብቻ ሰዎች [የእኛ ደጋፊዎች] ‹‹እህላችን<br />
ሳይደርስ ቀርቶ እርዳታ ብንጠይቅም ተገለልን እናም ተቸግረናል›› ብለው ፅፈው ፈርመው የላኩልን መረጃዎች እጃችን<br />
ላይ አሉ።<br />
ይህ ከሆነ እርዳታ ለጋሾች ሊያውቁ አይችሉም ብለው ያስባሉ?<br />
እርዳታ ሰጪዎች ‹‹እርዳታ የሚገባው ለእነዚህ ነው›› የሚል ሚና የላቸውም። ከወረዳ/ከቀበሌ ተጣርቶ በተላለፈላቸው<br />
ስም ዝርዝር መሰረት ይሰጣሉ። ተመርጠው የመጡት ሰዎች የኢህዴግ ሰዎች ይሁኑ/አይሁኑ የሚያውቁት ነገር<br />
የለም።<br />
መድልዎ እየፈፀመ ያለው ስም ዝርዝር የሚሰጠው አካል ነው። የእኛ አባላት ‹‹በሴፍቲ ኔት አንታቀፍም፣ እርዳታ<br />
ሲመጣ ስም ዝርዝራችን የለም›› ይሉናል። እንደውም መታወቂያ ሁሉ እየታደለ ነው። ለእኛ ሰዎች ግን ያንን መታወቂያ<br />
እሺ ብለው አይሰጡም። እኛ መረጃ ሳይኖረን ዝም ብለን አንናገርም።<br />
ቢቢሲ ዘገባውን ካስተናገደ በኋላ <strong>መንግስት</strong> ላይ ተቺ ሀሳብ የሰነዘራችሁ ተቃዋሚ ፖለቲከኞችን በምርጫ ድምፅ ህዝብ ስለቀጣችሁና ተስፋ ስለቆረጣችሁ<br />
ባገኛችሁት አጋጣሚ ውሸትን (ጥላቻን) እንደምትሰብኩ በ<strong>መንግስት</strong> መገናኛ ብዙሐን ላይ ስሞታ ቀርቦባችኋል። ይስማማሉ?<br />
ይህ በራሱ በጣም ሰፊ አወያይ ርዕስ ነው። መድረክ ከምርጫው በኋላ ‹‹ኢህአዴግ አዳፍኖት ለማለፍ ያቀደው የአገራችን<br />
የዴሞክራሲ ሂደት ግንባታ በህዝባችን ሰላማዊ ሂደት ይከሽፋል›› የሚል መግለጫ መስጠቱ ይታወሳል። እዚያ ላይ<br />
የነበሩትን ችግሮች ዘርዝረናቸዋል። ‹‹ምርጫው ድራማ እንጂ ፍትሃዊ አልነበረም፣ የምር’ኮ ውጤት ነው›› ብለናል።<br />
እኔ ከማንም በላይ ፓርላማ የቆየሁ ሰው ነኝ፤ ከሽግግሩ ወቅት ጀምሮ። ያኔ ሁሉ የምናቀርበው ክስ ነው። በምርጫ<br />
ባሸነፍኩባቸው ጊዜያት ‹‹በየነ ጴጥሮስን መርጣችሁ ምን አገኛችሁ? እሱ ያመጣውን እርዳታ ብሉ›› እያሉ ይዘባበቱባቸው<br />
ነበር። ይሄ እውነታ እንጂ ከምርጫ መሸነፍና ማሸነፍ ጋር የሚያያዝ አይደለም።<br />
ለምሳሌ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ወደሃድያ አካባቢ፤ ሆሳዕና ድረስ ስንት ጊዜ ሄዱ? ድሮ የትኛው ቦታ ሄደው ያውቁ<br />
ነበር? ጨርሶ ታይተው አይታወቁም። በምርጫ ስለተሸነፉ ግን ተመላለሱ። በተወሰነ መንገድ ተሳክቶላቸዋል። የህዝቡን<br />
ልብ ግን መቼም አያገኙትም። ሰዉ በተወሰነ መልኩ ዲፕሎማት ሆኗል። በቀጥታ መቃወም ትቷል። እኔ ብሄድ ግን<br />
‹‹ሆ›› ብሎ እንደሚቀበለኝ አውቃለሁ። የገለፅኳቸው ነገሮች ሁሉ ያሉና የማምንባቸው ናቸው።<br />
ቢቢሲ ላይ የእናንተ ሀሳብ (ክስ) መስተናገዱን ማጣጣል ላይ መሰረት ያደረገ ‹‹ዶክመንተሪ›› ፊልም ባለፈው እሁድ ምሽት በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን<br />
ቀርቧል። እንደተመለከቱት ነግረውኛልና በዚህ ዙሪያ ምን ይላሉ? አዘጋጁ በእርስዎ የትውልድ መንደር ባደዋቾ ድረስ ሄዶ…<br />
እኔ የተናገርኩት በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው የተደበቀ ረሃብ እንጂ ስለተወለድኩበት አካባቢ የተለየ ሁኔታ<br />
ያነሳሁት ነገር የለም። እንዳለኝ መረጃም ከሆነ የቢቢሲ ዘጋቢዎች እኔ የተወለድኩበት አካባቢም አልሄዱም። እነሱ<br />
በጠቋሚዎቻቸው አማካኝነት ማየት የፈለጉት ኢትዮጵያ ውስጥ የተደበቀ ረሃብ እንዳለ፣ ርዳታ የፖለቲካ አንድምታ<br />
ስላለው በፍትሃዊነት እንደማይዳረስ መረጃ ይዘው ነው የመጡት።<br />
ያወራነው ዋሻ ውስጥ ሳይሆን የሚታወቅ ሆቴል ውስጥ ነው። የአቶ ቢኒያም (የዶክመንተሪው አዘጋጅ እና ኢትዮጵያ<br />
ፈርስት ድረ-ገጽ ኤዲተር) አካሄድ ነገር ፍለጋ እንጂ የሚገናኝም ነገር የለውም፤ ‹‹ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ›› ዓይነት<br />
ነው። እኔ በኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው ነገር እያወራሁ እኔ አካባቢ መሄድ ምን ማለት ነው? የእሱን (የቢኒያምን) ጥበት<br />
ነው የሚያሳየው። የፈለገው እኔን በአካባቢዬ ብቻ ሊገድበኝ ነው። [ሳቅ እያሉ] የእኔ የመረጃ ምንጮች በመላው ኢትዮጵያ<br />
ይገኛሉ። ኃላፊነቴም በዚያው ያህል ነው።<br />
እንደዚህ ዓይነት ነገር ውስጥ የሚገባው ቅጥረኛ ሰው ነው። እውነት እና ሀቅ ፈላጊ ቢሆን ‹‹አንተ የምርጫ ጣቢያ<br />
(የትውልድ አካባቢ) እየሄድኩ ስለሆነ የማናግራቸውን ሰዎች ስጠኝ›› ማለት ነበረበት። ቢቢሲ ቢያናድደውም ስለ ቢቢሲ<br />
የሚታመን የመረጃ አካል መሆንና/አለመሆን እሱ ክሬዲት የመስጠት አቅም ያለው አይመስለኝም። ‹‹የአገራችንን ስም<br />
አጎደፉ›› የሚል ‹‹አርበኛ ነኝ›› ባይ ነው። ምክንያታዊ ሆኖ ‹‹አርበኛ›› ቢሆን እኔ ችግር የለብኝም። ‹‹ጋዜጠኛ (መረጃ<br />
ሰብሳቢ ነኝ)›› ካለ አካሄዱ ጤናማ/ሚዛናዊ አልነበረም። የሄደው ለአንድ ወገን የሚሆን መረጃ ይዞ ለመምጣት ብቻ ነው።<br />
ነገር የማይገባው የዋህ ነው።<br />
ያነጋገራቸው ሰዎች የኢህአዴግ ጥቅም ተካፋዮች ይሆናሉ ብሎ ሳይጠረጥር ቀርቶ ነው? ያነጋገራቸው በአጋጣሚ ደርሶ<br />
ያገኛቸውን ሰዎች ናቸው? [እየሳቁ] አይደለም። የማውቀው የወረዳ ሊቀ-መንበር የቆመበት መሀከል ነው ሲያዋራቸው<br />
የነበረው። እናስ ‹‹ረሃብ፣ ችግር፣ አድሎ አለ›› እንዲሉ ይጠብቃል?<br />
የእርስዎ አጎት ሚስት በግብዓትነት ቀርበው ክስዎ ውሸት መሆኑን ‹‹<strong>መንግስት</strong> ለተቃዋሚ/ለደጋፊ ብሎ ለያይቶ እርዳታ እንደማያከፋፍል ተናግረዋል።<br />
ይህስ ማረጋገጫ መሆን አይችልም?<br />
በ ገፅ 23
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />
መልካም ዓዲስ ዓመት<br />
በናፍቆት ዮሴፍ<br />
የዘመን መለወጫ<br />
( እ ን ቁ ጣ ጣ ሽ )<br />
በ ሀ ገ ራ ች ን<br />
ከሚከበሩ ሀገራዊና<br />
ሀ ይ ማ ኖ ታ ዊ<br />
በዓላት አንዱ<br />
ከመሆኑም ሌላ<br />
ከሌሎች በዓላት<br />
የሚለይበት በርካታ ገጽታዎች<br />
አሉት።<br />
አሮጌው አልፎ አዲስ ዓመት<br />
ሲተካ ብዙዎች የአዲስነት<br />
ስሜት የሚላበሱበት፤ በአሮጌው<br />
አመት ያላሳኩትን ለመከወን<br />
የሚያቅዱበት፤ ሱሰኞች ከሱስ<br />
ነፃ ለመውጣት፣ ብቸኞች በጋብቻ<br />
ለመጣመር፣ ሌሎች ለመማር<br />
(ከስህተትም ሆነ የቀለም<br />
ትምህርት) የሚያቅዱበት፤<br />
በአጠቃላይ ብሩህ ተስፋ<br />
የሚሰነቅበት በዓል ነው።<br />
በበዓሉ መቃረቢያ ልጃገረዶች<br />
‹‹እንቁጣጣሽ እንኳን መጣሽ››<br />
እያሉ ሲጨፍሩ ልጅነት<br />
የሚታወስበትም ነው - የዘመን<br />
መለወጫ። ከዚያም አልፎ በዓመት<br />
አንድ ጊዜ ብቻ የሚበቅለው ደማቅ<br />
ቢጫ አደይ አበባ የሚታይበትም<br />
ስለሆነ በዓሉ ልዩ ስሜትን<br />
ያላብሳል።<br />
‹‹እንቁጣጣሽ›› ማለት?<br />
በዓሉ ሁለት መጠሪያዎች<br />
እንዳሉት - ‹‹እንቁጣጣሽ›› እና<br />
‹‹ቅዱስ ዮሀንስ››። በዚህ ፅሁፍ<br />
በዓሉ ለምን ቅዱስ ዮሀንስና<br />
እንቁጣጣሽ እንደተባለና ታሪካዊ<br />
ዳራውን ለማስቃኘት ወደናል።<br />
ቅዱስ ዩሀንስ<br />
ሀመር መፅሄት በመስከረም<br />
1996 ዓ.ም እትሙ፣ የአይሁድ<br />
ንጉስ የነበረው ንጉስ ሄሮድስ<br />
የወንድሙ የፊልጶስ ሚስት<br />
የሆነችውንና ‹‹ሄሮዲያደን››<br />
የተባለችውን ሴት ባገባ ጊዜ<br />
መጥምቁ ዮሀንስ ‹‹የወንድምህ<br />
ሚስት ለአንተ እንድትሆን<br />
አልተፈቀደም›› ብሎ በማስተማሩ<br />
ጳጉሜ አንድ ቀን ታስሮ መስከረም<br />
ሁለት ቀን አንገቱ በሰይፍ ተቀልቶ<br />
ሞተ። ይህ ቅዱስ የህግ አዲስ<br />
ካህን፣ ነቢይና ሐዋሪያ በመሆኑ<br />
መታሰቢያው የአዲስ ዘመን<br />
መባቻ ተደርጎ በእስክንድሪያና<br />
በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር<br />
በዓላት የሚከበሩበት፣ እንዲሁም<br />
አፅዋማት የሚገቡበት ተደርጎ<br />
መወሰዱን፣ እናም ቀኑም በስሙ<br />
ቅዱስ ዮሀንስ ተብሎ መሰየሙን<br />
ይገልፃል። ዘመኑም በዚሁ እለት<br />
ይታደሳል፣ ይለወጣል።<br />
መፅሄቱ ሁለት ዮሐንሶች እንዳሉ<br />
ይገልፃል፡- መጥምቀ መለኮት<br />
ቅዱስ ዮሐንስ እና ሐዋሪያውና<br />
ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሀንስ። ዘመኑ<br />
የተሰየመው አራተኛውን ወንጌል<br />
በፃፈው በዮሀንስ ወልደ-ነጎድጓድ<br />
ሲሆን፣ ቃለ-ነቢይ ልዑል ዮሀንስ<br />
መስከረም አንድ ቀን በ1979 ዓ.ም<br />
ለኢትዮጵያ ሬዲዮ የሰጡትን ቃለ-<br />
ምልልስ ጠቅሶ ዘግቧል።<br />
መፅሄቱ፣ ዘመኑ በስሙ<br />
ስለተሰየመለት ቅዱስ ዮሀንስ<br />
ሌላም ተጨማሪ መረጃ<br />
አጣቅሷል።<br />
‹‹ዘመን አልፎ ዘመን ሲተካ<br />
የመሸጋገሪያው ዕለት በየአመቱ<br />
ቅዱስ ዮሀንስ እየተባለ ይጠራል።<br />
ይህም የነቢዩ የዘካሪያስ ልጅ<br />
መጥምቁ ዮሀንስ ነው፡፡ በዘመነ-<br />
ብሉይ መጨረሻና በዘመነ<br />
ሀዲስ መጀመሪያ ላይ ተነስቶ<br />
‹መንግስተ-ሰማያት ቀርባለችና<br />
ንስሀ ግቡ› እያለ ስለክርስቶስ<br />
አዳኝነት ስላስተማረ በየአመቱ<br />
የዘመን መጀመሪያ በእርሱ ሥም<br />
እንዲጠራ ተደርጓል›› ሲሉ ቀሊኃ<br />
ልሳኑ በዛብህ ‹‹ልሳነ-ተዋህዶ ዘ<br />
ኦርቶዶክስ” በተሰኘ፣ በ1987<br />
ዓ.ም በቁጥር ሰባት መፅሀፍ<br />
መፃፋቸውን ያትታል።<br />
ልዩ ቅኝት<br />
እንቁጣጣሽ<br />
Vs<br />
ቅዱስ ዮሐንስ<br />
‹‹እንቁጣጣሽ››<br />
አንዳንዶች ስለ እንቁጣጣሽ በቃል<br />
የተነገረ አንጂ በፅሁፍ የሰፈረ ነገር<br />
አንደሌለ ሲናገሩ፣ ሌሎች ደግሞ<br />
የተጻፈ ታሪካዊ ዳራ እንዳለው<br />
ይከራከራሉ። ሆኖም ከዘመን<br />
ዘመን ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ<br />
ከግዕዝ የተወሰደ ቃል አንደሆነ<br />
መዛግብት ያስረዳሉ። ‹‹እንቁ›<br />
የግዕዝ ቃል ሆኖ ለነጠላ ቁጥር<br />
የሚያገለግል ሲሆን፣ ‹‹አዕናቁ››<br />
የሚለው ለብዙ ቁጥር ያለግላል።<br />
‹‹ጣጣሽ›› የሚለው ‹‹ፃዕፃዕ››<br />
ከሚለው የግዕዝ ቃል የተወረሰ<br />
እንደሆነና የአማርኛ ትርጓሜውም<br />
ጣጣ፣ መባዕ፣ ግብር፣ መፍቀድ፣<br />
ገፀ-በረከት (በረከተ-ገፅ) ማለት<br />
አንደሆነ ከላይ በገለፅነው ዓ.ም<br />
ለንባብ የበቃው ሀመር የተባለው<br />
መንፈሳዊ መፅሄት መረጃዎችን<br />
ጠቅሶ አስፍሯል። በአጠቃላይ<br />
እንቁጣጣሽ ማለት የእንቁጣጣሽ<br />
ግብር፣ የእንቁጣጣሽ ገፀ-በረከት<br />
ማለት እንደሆነ የታሪክ ድርሳናት<br />
ያስረዳሉ። በመፅሀፍ ብሉያትም<br />
ቢሆን ለመባዕ የሚገባውን ግብር<br />
‹‹ፃዕፃዕ›› ይሉት እንደነበር ነው<br />
መረጃዎች የሚጠቁሙት።<br />
መነን መፅሄት በ1965 ዓ.ም<br />
‹‹እንቁጣጣሽ ምንድን ነው›› በሚል<br />
ርዕስ እንዳስነበበው፣ በሀገራችን<br />
ለመጀመሪያ ጊዜ እንቁጣጣሽ (ገፀ-<br />
በረከት) የተበረከተው ለቀዳማዊ<br />
ምኒልክ እናት ለንግስት ማክዳ<br />
እንደነበርና ንግስቲቱ ምኒልክን<br />
በወለደች ጊዜ ህዝቡ ንጉስ<br />
ተወለደ ብሎ እልል በማለት<br />
የአበባ እንቁጣጣሽ ለንግስት ማክዳ<br />
አበረከተ።<br />
ታዲያ እንቁጣጣሽ የተባለው<br />
በመጀመሪያ ለንግስቲቱ ስለተበረከተ<br />
እንጂ ለንጉሱ ተበርክቶ ቢሆን<br />
ኖሮ ‹‹ዕንቁ ፃፃሁ›› ይባል ነበር።<br />
ከዚህም በተጨማሪ ንጉስ ሰለሞን<br />
ከደስታው ብዛት ለንግስቲቱ<br />
ለጣትሽ መታሰቢያ ይሁንሽ ሲል<br />
የዕንቁ ቀለበት ሰጥቷት እንደነበር<br />
ሊቃውንት ያስረዳሉ።<br />
በ1951 ዓ.ም ብርሀንና ሰላም<br />
ጋዜጣ ላይ በዓሉን አስመልክቶ<br />
‹‹ርዕሰ አውደ ዓመት›› በሚል ርዕስ<br />
የሰፈረው ጽሁፍ ንግስት አዜብ<br />
ለንጉስ ሰለሞን ‹‹ተንካራ›› የተሰኘ<br />
እንቁ ወስዳ ገፀ-በረከት በሰጠችው<br />
ጊዜ ‹‹እንቁጣጣሽ ይሁን›› ብሏት<br />
እንደነበር ያስረዳል።<br />
ጋዜጣው ጨምሮ እንደገለፀው፣<br />
በኢትዮጵያ ስለ ሕግ የተሰበከው<br />
በንግስት አዜብ በምኒልክ እናት<br />
በመሆኑ ሲታሰብ እንደሚኖር፣<br />
በዚህም ቀን የቅድስ ዮሀንስ<br />
መጥምቅ በዓል እንደሚከበር ነው፡፡<br />
ታዲያ የኢትዮጵያ ሴቶች ለምለም<br />
ሳርና አበባ በእጃቸው ይዘው<br />
በዓሉን የሚያከብሩት ለምለም<br />
ሳርና አበባው በኖህ ጊዜ ‹‹ማየ<br />
አይህ›› (የጥፋት ውሀ) መጉደሉን<br />
ለማብሰር እርግብ በአፏ ቅጠል<br />
ይዛ ታይታ ስለነበር ነው። ምንም<br />
እንኳን ‹‹ማየ አይህ›› የጥፋት<br />
ቢሆንም፣ ክረምት አለፈ የሚለውን<br />
ሀሳብ እንደሚወክል ብርሀንና<br />
ሰላም ጋዜጣ ከላይ በገለፅነው ዓ.ም<br />
እትሙ አስፍሮታል።<br />
በሌላ በኩል ስለ ዘመን መለወጫ<br />
(እንቁጣጣሽ በዓል) አለቃ አያሌው<br />
ታምሩ በ1953 ዓ.ም ባሳተሙት<br />
‹‹የኢትዮጵያ እምነት በሶስቱ<br />
ህግጋት›› በተሰኘው መፅሀፋቸው<br />
የዘመን መለወጫ በሶስት መንገድ<br />
መታወቁን አስፍረዋል። አንደኛ፣<br />
እስራኤላውያን በብሉይ ኪዳን<br />
ያከብሩት የነበረው ሚያዚያ 1<br />
ቀን፤ ሁለተኛ፣ የአለም ክርስቲያን<br />
የክርስቶስን ልደት ተቀዳሚ<br />
በማድረግ የሚያከብሩት ጥር 1<br />
ቀን፤ ሶስተኛ፣ ኢትዮጵያ ከጥንት<br />
መሠረት አውቃ የምታከብረው<br />
መስከረም 1 ቀን ናቸው።<br />
እስራኤላውያን የዘመን መለወጫ<br />
በአልን ሚያዚያ 1 ቀን ማድረጋቸው<br />
በዚሁ ወር ከግብፅ ባርነት ነፃ<br />
በመውጣተቸው፣ እንዲሁም<br />
እግዚአብሔር ይህንን የነፃነት በአል<br />
በየአመቱ እዲያከብሩ ስላዘዛቸውና<br />
የአለም ክርስቲያን ጥር 1 ቀን<br />
ማክበራቸው የክርስቶስን ልደት<br />
ምክንያት በማድረግ መሆኑ ግልፅ<br />
ነው፡፡ የኢትዮጵያ መስከረም 1 ቀን<br />
አውድ አመት (ዘመን መለወጫ)<br />
ስላደረገችበት ጥቂት እንበል።<br />
ኢትዮጵያ ይህንን በዓል<br />
የተቀበለችው ከ‹‹ካም›› ነው፡<br />
፡ የተጀመረበትም ካም እና ልጁ<br />
ኩሣ ወደ ኢትዮጵያ የገቡበትና<br />
አኩስም (አክሱም) በኩሳ ስም<br />
የተመሰረተችበት ጊዜ ነው።<br />
ዘመኑም በኢትዮጵያ ከ4900<br />
ዓመት በላይ ሲሆን፣ ጊዜውም<br />
ከጥፋት ውሀ በኋላ መሆኑን<br />
የአለቃ አያሌው መጽሀፍ ያስረዳል፡<br />
፡<br />
ስለ ዘመን መለወጫ ስያሜዎች<br />
ማለትም ስለ ቅዱስ ዮሀንስና<br />
እንቁጣጣሽ አለቃ አያሌው<br />
ታምሩ በ2001 ዓ.ም ባሳተሙት<br />
‹‹ትምህርተ-ሀይማኖት›› በተሰኘ<br />
መጽሐፋቸው ‹‹እንቁጣጣሽ››<br />
የሚለው ቃል ከግብር፣ ከመባዕ፣<br />
ከገፀ-በረከት ጋር የተቆራኘ ትርጓሜ<br />
በየዘመኑ የመጡ ምሁራን<br />
ያመጡት እንጂ እውነታው ወዲህ<br />
ነው ይላሉ። ይሁን እንጂ ‹‹ቅዱስ<br />
ዮሀንስ›› ስለተባለው የዘመን<br />
መለወጫ ስያሜ እላይ ከሰፈረው<br />
ጋር ብዙ የሚያመሳስለው ነገር<br />
አለ።<br />
‹‹ቅዱስ ዮሀንስ› አለቃ<br />
አያሌው እንደገለፁት<br />
አለቃ አያሌው ታምሩ ዘመኑ<br />
በአራቱ ወንጌላውያን የተሰየመ<br />
ነው ይላሉ። የዘመን መለወጫው<br />
‹‹ቅዱስ ዮሐንስ›› የሚባልበትንም<br />
ምክንያት ሲያስረዱ፣ ወንጌልን<br />
የሚቀበሉ ሁሉ በአራቱ<br />
ወንጌላዊያን (በዩሀንስ፣ በማቲዎስ፣<br />
በማርቆስና በሉቃስ) የዘመን ቁጥር<br />
መስመራቸውን እንደሚያሳርፉ<br />
ገልጸው፣ ኢትዮጵያ ዘመን<br />
መለወጫን ‹‹ቅዱስ ዮሃንስ››<br />
የምትልበት ሁለት ዋና ዋና<br />
ምክንያቶች አንዳሏት ያብራራሉ፡<br />
፡ አንደኛ፣ ቅዱስ ዮሀንስ ወንጌላዊ<br />
ወንጌሉን የጀመረው በዜና<br />
ፍጥረት መሆኑን እንደሚከተለው<br />
ገልጾታል፡-<br />
‹‹ቃል ቀዳማዊ፣ ቃል<br />
በእግዚአብሔር ዘንድ ነበር።<br />
እግዚአብሔር ቃል ነበር፣ እርሱ<br />
በእግዚአብሔር ዘንድ ነበር። ሁሉ<br />
በእርሱ ሆነ›› ብሎ ሙሴ ‹‹ቀዳማዊ<br />
ገብረእግዛብሔር ሰማየ ወምድረ<br />
(እግዚአብሔር መጀመሪያ ሰማይና<br />
ምድርን ፈጠረ ሲል በቀዳማዊ<br />
ቃሉ በኢየሱስ ክርስቶስ አለሙን<br />
መፍጠሩን ያስረዳ በመሆኑና<br />
ቅዱስ ዮሀንስም የወንጌልን<br />
ትምህርት ከሙሴ ስብከት ጋር፣<br />
የወንጌልን ፅህፈት ከሙሴ አፃፃፍ<br />
ጋር እንዲሁም የወንጌልን ጥንት<br />
ከሙሴ አነሳስ ጋር በማስተባበር<br />
(ቃል ቀዳማዊ ነው) ሁሉ በእርሱ<br />
ሆነ) በማለት ስላጠናቀቀው፣<br />
ቤተክርስቲያንም በቅዱስ ዮሀንስ<br />
ወንጌል መሠረት እለቱን ‹‹ቅዱስ<br />
ዮሀንስ›› ብላ ትጠራለች” ካሉ<br />
በኋላ በተጨማሪም በቁጥር<br />
ስርአት አንድ ጊዜ ወደ ፊት<br />
አንድ ጊዜ ወደኋላ ነው ብለን<br />
ካመንን ዘንድ ወደኋላ ተመልሰን<br />
አሁን ባለው በአራቱ ወንጌላውያን<br />
መስፈሪያ ያለውን ዘመን ስንለካ<br />
ስነ-ፍጥረት ጥንተ-ፍጥረት በዘመነ<br />
ዮሀንስ ሆኖ ይገኛል። እናም ከቃሉ<br />
አፃፃፍ ጋር ተስማምቶ ስላገኘችው<br />
ቤተ-ክርስቲያን ቅዱስ ዮሀንስ ብላ<br />
ትጠራለች።<br />
ሁለተኛው ደግሞ ‹‹ወንጌላውያን<br />
ሁሉ የተባበሩት በቅዱስ ዮሀንስ<br />
መጥምቅ ዜና ነው። ወንጌላውያን<br />
ሁሉ ወንጌልን የጀመሩት በቅዱስ<br />
ዮሀንስ ስብከት ነው፡፡ ይህም<br />
ማቴዎስ ምዕራፍ 3፣ ማርቆስ<br />
መዕራፍ1፣ ሉቃስ ምዕራፍ 3፣<br />
ቅዱስ ዮሀንስ በምዕራፍ 1 ሁሉም<br />
ለወንጌል ትምህርት መሠረት<br />
መግቢያ ያደረጉት የቅዱስ ዮሀንስን<br />
መጥምቅ ትምህርት ነው›› ሲሉ<br />
አስፍረዋል።<br />
አለቃ አያሌው በመፅሀፋቸው<br />
‹‹ከዚህም ጋር ቅዱስ ዮሀንስ<br />
በንጉስ ሄሮድስ ትዕዛዝ ጳጉሜ<br />
1 ቀን ታስሮ መስከረም 2 ቀን<br />
በሰማዕትነት ሞቷል›› ሲሉ<br />
አስፍረዋል።<br />
እንቁጣጣሽ በአለቃ አያሌው ገለፃ<br />
አለቃ አያሌው የእንቁጣጣሽን<br />
ትርጉሜ በተመለከተ እዳሰፈሩት<br />
የቃሉ ትርጓሜና ታሪኩ ከምድርና<br />
ከኢትዮጵያ አመሰራረት ጋር<br />
የተያያዘ እንደሆነ ገልፀው<br />
‹‹እግዚአብሄር ፍጥረትን መፍጠር<br />
በጀመረ በሶስተኛው ቀን ‹ምድር<br />
ሳርም ቡቃያም ታውጣ›› ብሎ<br />
ሲናገር ሰማዩን በከዋክብት<br />
ከማስጌጡ አስቀድሞ ምድርን<br />
በአበባ አስጊጧል›› ሲሉ በመፅሀፉ<br />
ያሰፈሩት ሲሆን በዚህም ምክንያት<br />
“ምድር ተንቆጠቆጠች ማለት<br />
እንቁጣጣሽ መሰለች፣ አበበች፣<br />
ለመለመች አጌጠች ለማለት<br />
ነው። እንቁጣጣሽ የሚባለው<br />
በአሁኑ ጊዜ በየአመቱ መጀመሪያ<br />
ላይ ከሌሎች አበቦች አስቀድሞ<br />
የሚታየው በአማርኛ ቋንቋ ‹‹አደይ<br />
አበባ›› የተባለው ቢጫ አበባ ነው።<br />
ይሄ ነው እንቁጣጣሽ ያሰኘው”<br />
ሲሉ በትምህርተ-ሃይማኖት<br />
መጽሃፋቸው ላይ አስፍረውታል።<br />
አለቃ አያሌው እንደፃፉት፣<br />
ስለእንቁጣጣሽ ተራኪዎች የተለያየ<br />
ቋንቋ እንደሰጡት ጠቁመው<br />
በተለይም ‹‹የሠለሞንን ዘር<br />
መመኪያ እናደርጋለን የሚሉ<br />
ተራኪዎች›› ያሏቸው ንጉስ<br />
ሰለሞን ከንግስት ሳባ ጋር በተገናኘ<br />
ጊዜ ስለክብሯ አንቁጣጣሽ ብሎ<br />
የዕንቁ ቀለበት ሰጥቷት ነበር።<br />
ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ነው እንቁጣጣሽ<br />
የተባለው” ብለው ይተርካሉ። ግን<br />
“ትክክለኛ ታሪክ አይደለም›› ሲሉ<br />
ያጣጥሉታል፡፡<br />
የሆነ ሆኖ እንደ ግዕዙ ቃል<br />
እንቁጣጣሽ ‹‹ጣጣ›› ከሚለው ቃል<br />
መጥቶ ግብር፣ ገፀ-በረከት፣ ጣጣ<br />
የሚለውን ትርጉሜ አግኝቶም<br />
ከሆነ በአሉ በርካታ ግብርን<br />
(ወጪን) የሚጠይቅ በመሆኑ<br />
ጥንቃቄ ማድረግ ይጠበቅብናል፡፡<br />
› እንደአለቃ አያሌው ገለፃ ምድር<br />
ለመለመች፣ አጌጠች፣ አበበች<br />
ማለትም ከሆነ ለሀገራችን አሜን<br />
ያድርግለን፡፡ ስለዘመን መለወጫ<br />
ካነሳን አይቀር በዚሁ አጋጣሚ ስለ<br />
ጳጉሜም ትንሽ እንበል።<br />
ይህቺ የሀገራችን 13ኛ ወር<br />
(ጳጉሜ) ትርጓሜዋ ‹‹ጭማሪ››<br />
ማለት ነው፡፡ በመሆኑም ጭማሪ<br />
ወጪም ትሆናለችና ልብ ልንላት<br />
ይገባል፤ ዘንድሮ ደግሞ ስድስት<br />
ቀን ሆና ትውላለችና።<br />
መልካም ቅዱስ ዮሀንስ! መልካም<br />
የእንቁጣጣሽ በዓል!<br />
21<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ
22<br />
በኤልያስ ገብሩ<br />
በአዲስ<br />
elias.gebru32@gmail.com<br />
ዓመት አዲስ መንፈስ<br />
ኢትዮጵያኖች የፊታችን<br />
ሰኞ አዲስ ዓመትን<br />
የ ም ን ጀ ም ር በ ት<br />
ዕለት ነው። አዲስ<br />
ዓመት ብዙዎቻችን<br />
አዲስ እንዲሆንልን<br />
እ ና ስ ባ ለ ን ፣<br />
እንመኛለን። በአዲስ ዓመት ለውጥ<br />
ለማየትና ስኬትን ለመቀዳጀት ዕቅድ<br />
ነድፈውና ለራሳቸው ቃል ገብተው በአዲስ<br />
የመንፈስ ሀይል ለመንቀሳቀስ የሚሹና<br />
እንዳሰቡትም የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦችና<br />
አካሎች መኖራቸው እሙን ነው። በአንፃሩ<br />
ደግሞ፣ አዲስ ዓመት ስለመጣ ብቻ አዲስ<br />
ነገር ማድረግ እንዳለባቸው በማሰብ<br />
ስሜታዊ ሃሳብ ላይ በመመርኮዝ እርጋታ<br />
የጎደለው ስሜታዊ ዕቅድን ይነድፋሉ።<br />
እነዚህም በአዲሱ ዓመት ብዙም<br />
ሳይጓዙ ከእቅዳቸው ውጪ እንደሚሆኑ<br />
አያጠራጥርም። ለማንኛውም…… አዲስ<br />
ዓመት እንዴት ነው የምናከብረው?<br />
እንዲሁ በቀላሉ እቤት ውስጥ በመቀመጥ<br />
እና ዓመቱን አቅልሎ በመመልከት? ብዙ<br />
ሕዝብ በዓሉን ለማክበር በተሰበሰበበት<br />
ቦታ በመገኘት ወይስ ወዳልለመድነው ቦታ<br />
በመጓዝ? የበዓሉስ አከባበር የጠበቅነውን<br />
ያህል ይሆንልን ይሆን?<br />
ጠቃሚ ነገሮች ላይ<br />
የፀባይ ውሳኔዎች ላይ ነው። በሕይወት<br />
ውስጥ የሚገኙ የፀባይ ውሳኔዎች የሰዎችን<br />
ስኬት ይወስኑታል። የሚፈልጉትን<br />
ወይም ማድረግ የሚሹትን ለማሟላት<br />
ሰዎች ለራሳቸው ሕይወት ተጠያቂዎች<br />
መሆናቸው ይገለፃል።<br />
የተለየ ነገር ምን<br />
እናድርግ?<br />
የቢዝነስ ባለቤቶች፣ የድርጅት ማናጀሮች<br />
ወይም አስፈፃሚዎች የራሳቸውን የሥራ<br />
ዕቅድ የማስፈፀም ኃላፊነት እንዳለባቸው<br />
ሁሉ ሠራተኞቻቸውም የሚጠበቅባቸውን<br />
ነገሮች ማሳካት እንዲችሉ የመደገፍ<br />
ኃላፊነት ሊኖራቸው ይገባል፡፡<br />
በአሜሪካ ሀገር በአዲስ ዓመት መግቢያ<br />
ሰሞን በአንድ ትምህርት ቤት መግቢያ<br />
በር ላይ እንዲህ የሚል መርህ ቃል<br />
ተፅፎ በትልቁ ተለጥፏል፡- ‹‹High<br />
Expectation = High Achievement››<br />
(ከፍተኛ ግምት = ከፍተኛ ውጤት)፡፡<br />
በዚህም በአካባቢው ለሚገኙ መምህራን<br />
እንዲደርስ ታስቦ መዘጋጀቱን የሚገልፀው<br />
መረጃው፣ መምህራኖች ከተማሪዎቻቸው<br />
ከፍተኛ ውጤት የሚጠብቁ ከሆነ እነሱም<br />
ከራሳቸው የሚጠብቁት ነገር ከፍ ያለ<br />
ይሆናል። መምህራኖች ከራሳቸው የላቀ<br />
ነገር እንደሚጠበቅ ሲያስቡ ደግሞ<br />
ተማሪዎቻቸውን በዕውቀትና በሥነ-ምግባር<br />
ሊያሳድግ የሚችል ጥራት ያለው ትምህርት<br />
ለመስጠት ያስችላቸዋል፡፡ ይኼንንም<br />
ተከትሎ ተማሪዎች የሚጠበቅባቸው<br />
ደረጃ ላይ ይገኛሉ። ‹‹የቢዝነስ ባለቤቶች፣<br />
የድርጅት ማናጀሮች ወይም አስፈፃሚዎች<br />
ራሳቸውን እንደአስተማሪ፣ ሰራተኞቻቸውን<br />
ደግሞ እንደተማሪ ሊያስቧቸው ይገባል።››<br />
በማለት በአሜሪካን ሀገር የወጣ አንድ<br />
መረጃ ዘግቧል፡፡<br />
አዲስ ዓመት በመጣ ቁጥር አዲስ<br />
የባህሪ ውሳኔ ለማድረግ ከፍተኛ እድልን<br />
ይፈጥራል። ሽግግሩ ሥነ-አዕምሯዊ<br />
ለውጥን ለማድረግ በጣም ቀላል<br />
የሚያደርግ ሲሆን፣ ሰብኮንሺየስ የሆነው<br />
የሠው የአንጎል ክፍል አዲሱን ውሳኔ<br />
በቀላሉ ይቀበላል። ምን አይነት አዲስ<br />
የፀባይ ለውጥ ውሳኔ ማድረግ አለብን?<br />
በዋነኝነት እርስ በእርስ በመተባበር ትስስር<br />
እና ቁርኝትን መፍጠር ነው። ለምሳሌ፣<br />
በቢዝነስ ሥራ ውስጥ የሚጠበቀውን<br />
ውስጣዊና ውጫዊ ስኬቶችን ለመጎናፀፍ<br />
አዲስ የፀባይ ለውጥ ውሳኔ ለማድረግ<br />
ሚናው የጎላ ነው። እንዲሁም አንድ<br />
ሰው በውስጡና ከእሱ ውጪ እንዲሆኑ<br />
የሚጠብቃቸው ነገሮች እንዲለወጡ ድጋፍ<br />
ይሰጣል። በቢዝነስ ዓለምም አንድ ድርጅት<br />
በአዲስ ዓመት ከእሱ ውጭ ካሉ ሸሪኮች<br />
ጋር ለውጤት የሚያበቃ ስትራቴጂን<br />
በመንደፍ ሕብረት መፍጠር አለበት፡<br />
፡ ቅድሚያ ግን፣ ለካምፓኒው/ ለድርጅቱ<br />
ስኬት አጋር መሆን የሚችሉ ሸሪኮችን<br />
መምረጥ ተገቢ ነው።<br />
የድርጅቱን ምርጥ<br />
ታሪክ መምረጥ<br />
በካምፓኒው ወይንም በድርጅቱ ውስጥ<br />
ስላለው መልካም ነገር ሰራተኞች አዎንታዊ<br />
አመለካከትን ይዘው የባለቤትነት ስሜት<br />
እንዲሰማቸው አዲስ ስትራቴጂን መንደፍ<br />
ወሳኝነት እንዳለው መረጃዎች ያስረዳሉ።<br />
የድርጅት ባለቤቶች ወይንም የተቋም<br />
ኃላፊዎች ደግሞ ለሥራቸው እድገት<br />
ዕውቀትና ጥበብን ያማከለ ኃላፊነትንና<br />
የተጠና ሪስክን ሊወስዱ ይገባቸዋል።<br />
ሰራተኞች ከድርጅቱ ራዕይ ጋር ራሳቸውን<br />
ማስማማት እንዲችሉ የድርጅቱን ያለፈ<br />
ታሪክ እንዲያውቁ ማድረግ ብልህነት<br />
ነው፡፡ በድርጅቱ ታሪክ ውስጥም ጥሩ<br />
የሚባለውን መርጦ በመለየት በሰራተኞቹ<br />
እንዲደገም ደጋግሞ መናገር የባለቤቶች<br />
ወይም የኃላፊዎች ድርሻ ሲሆን<br />
ሰራተኞችም በዚህ ተገቢውን የፀባይ ለውጥ<br />
ውሳኔ እንዲያመጡ ማድረግ ያስፈልጋል።<br />
ትኩረት ማድረግ<br />
በአዲስ ዓመት ከግዢ ጋር ለተገናኙ<br />
የተለያዩ ነገሮች ይበልጥ ትኩረት ሰጥቶ<br />
ከማክበር ይልቅ በአዲስ ዓመት ለራስና<br />
ከራስ ውጪ ትልቅ ለውጥ ሊያመጡ<br />
በሚችሉ ቅድመ-ዕቅዶች ላይ የላቀ ትኩረት<br />
የኢትዮጵያዊያን ሰቆቃ...<br />
መስጠቱ በጣም ጠቀሜታ እንዳለው<br />
መረጃዎች ያስረዳሉ። ለምሳሌ በብዙ<br />
የአዲስ ዓመት ወቅቶች ላይ፣ ሁሌም<br />
ለማለት በሚያስችል መልኩ በርካታ<br />
ሕፃናት ልጆች፣ ታዳጊዎችና ወጣቶች<br />
ከቤተሰቦቻቸው አዳዲስ አልባሳትና<br />
ጫማዎች ተገዝተው እንዲበረከትላቸው<br />
ይፈልጋሉ፣ ይጠብቃሉም። ብዙዎች<br />
እንዳሰቡት ሆኖ ሊያገኙት ይችላሉ። ነገር<br />
ግን፣ በአጋጣሚም ይሁን በሌላ [ቤተሰብ<br />
በብር እጥረት ምክንያት መግዛት ካልቻለ]<br />
በየዓመቱ ለልጆች ያስለመዳቸውን ነገር<br />
በሚያስቀርበት ጊዜ አዳዲስ አልባሳትና<br />
ጫማዎችን ይጠብቁ የነበሩ ሕፃናት፣<br />
ታዳጊና ወጣት ልጆች ራሳቸውን<br />
ከጓደኞቻቸው/ ከጎረቤት ልጆች ጋር<br />
በማነፃፀር መከፋታቸውና መበሳጨታቸው<br />
አይቀሩ ነው፡- የቤተሰብን ችግር በበቂ<br />
ምክንያት ካለተረዱት በስተቀር።<br />
አለበለዚያ ያ የአዲስ ዓመት ትውስታ<br />
ሁሌም በአዕምሯቸው ውስጥ ተቀምጦ<br />
ይረብሻቸዋል። በአሉታዊ መንገድ<br />
የተቀረፀው ትዝታ ልጆቹን ማንቀሳቀስ<br />
ካልቻለ ደግሞ ትዝታው አሁንም ድረስ<br />
በውስጣቸው መኖሩን ጠቋሚ ምልክት ነው።<br />
ይኼ ከላይ ልጆችን መሠረት በማድረግ<br />
የተጠቀሰው ምሳሌ በአዋቂ ሰዎች፣<br />
በድርጅቶች፣ በአካባቢዎችና በዝግጅቶች<br />
ላይ የሚሰራ መሆኑ ይገለፃል። በአዲስ<br />
ዓመት የሆነ ነገር እንደሚደረግላቸው<br />
የሚጠብቁ ሰዎችም ሆኑ ድርጅቶች<br />
የሚጠብቁት ነገር ካልተደረገላቸው በቀላሉ<br />
ስሜታቸው ሊነካ፣ የመስራት አቅማቸው<br />
ሊቀንስ፣ ብሎም ለውድቀት ሊዳረጉ<br />
እንደሚችሉ በጉዳዩ ላይ ጥናት ያደረጉ<br />
ምሁራን ያስረዳሉ። የሚጠበቀው ነገር<br />
አንዳንዴ እውነት ላይሆን እንደሚችልም<br />
ጠቁመዋል። በአጠቃላይ ሕፃናት፣<br />
አዋቂዎች፣ ድርጅቶች…አዲስ ዓመት<br />
በመጣ ቁጥር የሆነ ጥቅም ነክ-ነገር ከሰዎች<br />
ወይም ከሌላ አካል እንዲደረግላቸው<br />
አብዝቶ ከመፈለግ ይልቅ በሕይወታቸው<br />
ላይ በመሰረታዊ ሁኔታ ትልቅ ሊያመጡ<br />
በሚችሉ እውነተኛ ዕቅዶች ላይ ትኩረት<br />
ማድረግ እንደሚገባቸው አፅንዎት<br />
ሰጥተውታል፡- የዘርፉ ተመራማሪዎች።<br />
ያልተሟላ የፍላጎት ስሜታችንን<br />
ወደ ውስጣችን እንዲገባ ከፈቀድንለት<br />
ሕይወታችንን ውስብስብ የማድረግ አቅም<br />
አለው። ፍላጎታችን ካልሟላ ሕይወት<br />
ይበልጥ አስቸጋሪ ትሆናለች። ከእኛነታችን<br />
ውጪ የምንጠብቀው ነገር በተለያየ<br />
መልኩ ይመጣል። በገንዘብና በቢዝነስ፣<br />
በሥራ፣ በትምህርት፣ በፍቅርና በትዳር<br />
ሕይወት፣ በመንፈሳዊ ሕይወት …<br />
እነዚህን ነገሮች ለማግኘት የቁጥጥር ስራ<br />
ወሳኝ ነው። ይኼንን መስራት ካልተቻለ<br />
ደግሞ ብዙ ኃይልን ውጤት በማያመጣ<br />
ነገር ላይ ማዋሉ ተገቢ አለመሆኑን<br />
በዘርፉ የምርምር ጥናት ያደረጉ ምሁራን<br />
ይናገራሉ። ቁጥጥሩ የሚደረገው በሰዎች<br />
የሥራ ጫና መቋቋም አቅቷቸው የሸሹ ኢትዮጵያውያን በድብቅ እንዳነጋገሩት<br />
የሚያስታውሰው ነቢዩ፤ በሊባኖስ፣ በባሕሬን፣ በዱባይና አቡዳቢ ዜጎች በተመሳሳይ<br />
ሁኔታ ለችግር ቢዳረጉም በ<strong>መንግስት</strong> ተወካዮች ምንም ዓይነት የመብት ጥበቃ<br />
እንዳልተደረገላቸው አረጋግጧል።<br />
በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ሰቆቃ የተለያዩ መገናኛ ዘዴዎችን<br />
በመጠቀም ይፋ በማድረጉ ‹‹<strong>መንግስት</strong> ሊሰራ ይገባ የነበረውን ሥራ እየከወነ ነው››<br />
ተብሎ የሚሞካሸው ይህ ጋዜጠኛ በአካባቢው ያሉ ዲፕሎማቶች የኢትዮጵያውያንን<br />
ጩኸት ሰምቶ ምላሽ ለመስጠት ለምን እንደከበዳቸው ጥያቄ ማቅረቡ አልቀረም።<br />
ቀደም ሲል የጅዳ ቆንፅላ ጽ/ቤት ኃላፊ የነበሩት አምባሳደር ተክለአብ ከበደና<br />
ሌሎች ሠራተኞች ሲሰጡት የቆየው መልስ ‹‹የበጀትና የሰው ኃየል ዕጥረት አለብን››<br />
የሚል ነበር፡፡ ሆኖም ፕሬዝደንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ ጅዳ በሄዱ ጊዜ ተመሳሳዩን<br />
ጥያቄ አቅርቦላቸው ‹‹የበጀትና የሰው ኃይል እጥረት ስለመኖሩ ጥያቄ አልቀረበልንም፡<br />
፡ ሲቀርብልን ምላሽ እንሰጥበታለን›› ማለታቸው ችግሩ የቅንጅትና የበሰለ አመራር<br />
እጥረት እንደሆነ መመስከሩን ያስታውሳል።<br />
‹‹አለ›› የተባለውን የገንዘብና የሰው ኃይል ዕጥረት ለመቅረፍ ከልብ ስላልታሰበበት<br />
እንጂ የጅዳው ቆንፅላ ጽ/ቤት በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን ፓስፖርት በማደስና<br />
የውክልና ወረቀት በመስጠት በሚያስገባው ከፍተኛ ገቢ ችግሩን ማቃለል<br />
እንደሚቻልም መረጃዎች ይጠቁማሉ። በውጭ አገራት በተለይም በአረብ አገራት<br />
የሚገኙ ዲፕሎማሲያዊ ሚሲዮኖች በስፍራው የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ችግር<br />
ከመፍታት ይልቅ የኢህአዴግ ደጋፊ ዲያስፖራዎችን በማሰባሰቡ ላይ እንደሚያተኩሩ<br />
የሚያስገነዝቡ ወቀሳዎች ሲቀርቡ ይስተዋላል።<br />
ካለፈው አራት ዓመት ወዲህ በጅዳና አካባቢው ያሉ ኢትዮጵያውያንን እንዲያገለግሉ<br />
ተመድበው በነበሩት አቶ ሙክታር መሐመድ ላይም ተመሳሳይ ትችት ተሰንዝሯል።<br />
ምንም እንኳን የዲፕሎማቱ ዋና ተልዕኮ ለኢትዮጵያውያን አንገብጋቢ ጥያቄዎች<br />
ምላሽ መስጠት ቢሆንም እሳቸው ግን ብሔር ተኮር ‹‹የልማት ማህበሮችን››<br />
በማደራጀት ላይ ተጠምደው የሥራ ጊዜያቸውን እንዳገባደዱ ምንጮች ለአውራምባ<br />
ታይምስ ገልፀዋል።<br />
በየዕለቱ በርካታ ኢትዮጵያውያን በሚጎርፉባት የመን ያሉ ኢትዮጰያውያንም እዚያ<br />
ያለው ኤምባሲ ጩኸታቸውን ለመስማት ፈቃደኛ አለመሆኑን ሲገልጹ ቆይተዋል።<br />
በተለይም የዘመናት ብሶት የወለደው የዓረብ አብዮት በየመንም መቀጣጠሉን ተከትሎ<br />
ኢትዮጵያውያን ከፍተኛ ስጋት ውስጥ እንደነበሩ በአንድ ወቅት ግሩም ተ/ኃይማኖት<br />
የተባሉ ስደተኛ አውራምባ ታይምስ ላይ ባሰፈሩት ፅሁፍ መግለፃቸው አይዘነጋም።<br />
ምንም እንኳን የኢትዮጵያ <strong>መንግስት</strong> /የመን የሚገኘው ኤምባሲ/ ከ IOM ጋር<br />
በመተባበር በየመን ሊቀሰቀስ በሚችለው ጦርነት ዜጎች እንዳይጎዱ ኢትዮጵያውያንን<br />
ወደ ኢትዮጵያ ሲመልስ የነበረ ቢሆንም፣ ‹‹የመን ባለው ኤምባሲ አንተማመንም››<br />
ያሉት ኢትዮጵያውያን በርካታ ናቸው።<br />
ግፍ ተፈፅሞባቸው ወደ ኤምባሲው በመሄድ ጥያቄ የሚያቀርቡ ወገኖችን<br />
‹‹እኛ ለገረድ አልመጣንም›› በሚል ዲፕሎማቶቹ ሲገፏቸው እንደነበር አቶ<br />
ግሩም በፅሁፋቸው ከማስታወሳቸው ባሻገር፣ በ<strong>መንግስት</strong>ና በIOM አማካኝነት ወደ<br />
ሐገራቸው የተመለሱትም ለአውራምባ ታይምስ ይህንኑ ተናግረዋል። በወቅቱ<br />
ተመላሾቹ በሰው ሀገር ከደረሰባቸው ግፍና መከራ የተነሳ እንባ እየተናነቃቸው<br />
‹‹ኤምባሲው ከሰውም አይቆጥረንም። እንደምንም ገንዘብ አግኝተን ስልክ ስንደውል<br />
‹ጠግበህ ነው የመጣኸው፤ ይበልህ የራስህ ጉዳይ ነው› ይሉናል›› ሲሉ ነበር በአረብ<br />
አገራት የሚገኙ ኤምባሲዎች ከኢትዮጵያውያን ጋር ሆድና ጀርባ መሆናቸውን<br />
ያመለከቱት።<br />
ከአውራምባ ታይምስ ጋር ቆይታ ያደረጉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ<br />
አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፣ ‹‹መቼም ኤምባሲዎች ውስጥ የሚሠሩት ሰዎች ናቸውና<br />
ከኤምባሲዎች ፖሊሲ በተጻራሪ ስህተት መሥራታቸው አይቀርም›› በማለት<br />
አቤቱታውን በከፊል ቢጋሩትም <strong>መንግስት</strong> በውጭ አገራት ለሚገኙ ዜጎች ከለላ<br />
በማድረግ ላይ መሆኑን በመግለጽ በፅኑ ሞግተዋል፡፡<br />
‹‹ልጆቻችን እና እህቶቻችን ላይ የሚደርስ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት አገራችንንም ሆነ<br />
የሚመሩትን ሰዎች የሚያስከብር ካለመሆኑም በላይ የዲፕሎማቲክ እንቅስቃሴ<br />
ውድቀት ማሳያ ነው›› የሚሉት ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ‹‹ኤምባሲው ከመኖር<br />
መዝለል አለበት›› ሲሉ ይወቅሳሉ።<br />
ዲና ሙፍቲ በአቅም ውስንነት የተነሳ ኤምባሲ ባልተከፈተባቸው አገራት ያሉ<br />
ዜጎች መብት ማስጠበቅ አዳጋች ነው ቢሉም በየነ በዚህ አይስማሙም። ‹‹ሁሉ አገር<br />
ኤምባሲና ቆንስላ አይኖርም። በሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና በሌሎች አገሮች<br />
በኩል የቅርብ የጎንዮሽ ክትትል ያደርጋሉ›› ሲሉ የኤምባሲ እና ቆንስላ አለመኖር<br />
ሁሌ እንደ ችግር መታየት እንደሌለበት ጠቁመዋል።<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
ጤ ና<br />
አዲስ ዓመት በመጣ ቁጥር አዲስ የባህሪ ውሳኔ ለማድረግ ከፍተኛ እድልን ይፈጥራል። ሽግግሩ ሥነ-አዕምሯዊ ለውጥን<br />
ለማድረግ በጣም ቀላል የሚያደርግ ሲሆን፣ ሰብኮንሺየስ የሆነው የሠው የአንጎል ክፍል አዲሱን ውሳኔ በቀላሉ ይቀበላል<br />
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />
መልካም ዓዲስ ዓመት<br />
አንድን ድርጅት ስኬታማ ወደሆነ የሥራ<br />
ባህል መውሰድ ጊዜ ስለሚጠይቅ በተቻለ<br />
መጠን ትግስተኛ መሆን ይመከራል፡፡<br />
ለዚህ ምን ማድረግ ያስፈልጋል?<br />
ከአሮጌው ዓመት ራስን መነጠል<br />
አንድ ድርጅት በአዲስ ዓመት ስኬታማ<br />
ለመሆን የተሻሉ ሰራተኞችን መምረጥ<br />
መቻል ወሳኝና ቁልፍ ተግባሩ ማድረግ<br />
አለበት፡፡ አንድ የሥራ ኃላፊ ከራሱ<br />
ጋር በውስጡ የሚነጋገረው ነገር በፀባይ<br />
ለውጥ ውሳኔዎች ላይ ጫና የመፍጠር<br />
አቅም አለው። ከእሱ በሚጠበቀው ነገር<br />
ላይ ውጤታማ ለመሆን ኃላፊው ግለሰባዊ<br />
ባህሪውን በመጀመሪያ መቆጣጠር አለበት።<br />
በአካላዊ ሰውነቱ ላይ የኬሚካል ወይንም<br />
የሆርሞኖች አለመመጣጠት ካልኖረ<br />
በስተቀር ፀባዩን መቆጣጠር ይችላል።<br />
ግለሰቡ የሥነ-አዕምሮ ችግር ካለ ደግሞ<br />
የሕክምና ባለሙያ ጋር በመሄድ ሕክምና<br />
መውሰድ እና ስላለበት ችግር በዙሪያው<br />
ላሉት ሰዎችና የሥራ ባልደረቦቹ ማሳወቁ<br />
መልካም መሆኑን መረጃዎች ያስረዳሉ።<br />
በዚህ ወቅት ሰራተኞች ለኃላፊው በጣም<br />
ቅን ሊያስቡለት፣ በቀላሉ ሊረዱትና እና<br />
ትዕግስተኛ ሊሆኑለት የሚችሉበት ዕድል<br />
ከፍተኛ ነው፡፡ … የሆነ ሆኖ፣ በተቻለ<br />
መጠን ስላለፈው አሮጌ ዓመት ከማሰብ<br />
መታቀብ ብልህነት መሆኑ ይገለፃል።<br />
ስለዚህ ሰዎች ለስኬታማ ሥራቸውና<br />
ሕይወታቸው ያላቸውን ሙሉ ኃይል<br />
እና አቅም በአዲሱ ዓመት ላይ ማድረግ<br />
እንደሚገባቸው በዘርፉ ጥናት ያደረጉ<br />
ባለሙያዎች ይመክራሉ፡፡ ይኼም ማለት<br />
ብዙ ጊዜን ለእውነተኛ ዕቅድ በመስጠት<br />
ስኬት ላይ ማነጣጠር ሲሆን ባለፈ ጊዜ<br />
ውድቀት እና ስኬት አልባነት ላይ እያሰቡ<br />
ጊዜ ማባከኑ ዋጋ የለውም።<br />
መልካም አዲስና የጤና ዓመት<br />
ይሁንላችሁ!<br />
ተስፋ እና ስጋት<br />
ከወራት በፊት ም/ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ኃ/ማርያም<br />
ደሳለኝ ሳዑዲ አረቢያን ከጎበኙ በኋላ፣ ሳዑዲ አረቢያ ወደ 30 ሺህ የሚጠጉ ኢትዮጵያዊ<br />
የኮንትራት ሠራተኞችን እንደምትፈልግ ይፋ ማድረጋቸውን ተከትሎ ከ15 ሺህ በላይ<br />
የሚገመቱ ዜጎች ወደ ሳዑዲ መግባታቸውን መረጃዎች ይጠቁማሉ።<br />
30 ሺህ ሠራተኞች በሳዑዲ አረቢያ መፈለጋቸው አገር ውስጥ በሥራ አጥነትና<br />
በድህነት ለሚማቅቀው ወጣት አስደሳች ዜና ቢሆንም ስጋቶችም አብረው መከሰታቸው<br />
አልቀረም። ለዚህ ሐተታዊ ፅሁፍ ሰፊና በማስረጃ የተደገፉ ማብራሪያዎችን በመስጠት<br />
ተባባሪ የሆነው ጋዜጠኛ ነቢዩ ሲራክ፣ ስጋቱ የሚመነጨው በሁለቱ ሀገራት መካከል<br />
ስለተደረገው ስምምነት የተፈረመ ሰነድ ይፋ ካለመደረጉ መሆኑን ያስገነዝባል።<br />
በኮንትራት ስለሚሄዱ ሠራተኞች ደመወዝ፣ የሥራ ሠዓት ህክምናና ተዛማጅ<br />
መብቶችን በሚመለከት የሚነሱ ጥያቄዎችን መመለስ የሚችል ሰነድ ይፋ አለመሆኑ<br />
ኢትዮጵያውያንን ለብዝበዛ ሊዳርግ እንደሚችል በመግለፅ ትዝብቱን አካፍሏል።<br />
በአዲሱ የሥራ ዕድል ‹‹ተጠቃሚ›› ሆነው ሳዑዲ አረቢያ ከገቡ ኢትዮጵያውያን<br />
መካከል አንዳንዶች ተቀባይ አጥተው ሲንገላቱ መመልከቱን ለአውራምባ ታይምስ<br />
የገለፀው የመካከኛው ምስራቅ የጀርመን ሬዲዮ ዘጋቢ፣ አሠሪዎቻቸውን አግኝተው<br />
ወደ ሥራ የተሰማሩትም በምግብ እጦትና በሥራ ብዛት ለከፋ ችግር መዳረጋቸውን<br />
አልሸሸገም።<br />
ይህንንም ችግር ለመቅረፍ ያሉት አማራጮች ለሠራተኛና አሠሪ አገናኝ ኤጀንሲዎች<br />
ፍቃድ በሚሰጠው የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴርና በየሀገሩ በሚገኙት<br />
ዲፕሎማቲክ መሥሪያ ቤቶች መካከል ያለውን የመረጃ ክፍተት ማጥበብና ዜጎችን<br />
ወደ ባዕድ አገር ከላኩ በኋላ ችግር ሲደርስ ዝም የሚሉ ሥራ አገናኝ ኤጀንሲዎች ላይ<br />
ጥብቅ ቁጥጥር የማያደርግ መሆኑን የሚያስገነዝቡ አሉ። ‹‹ውል ገብተው እስከላኩ<br />
ድረስ ሠራተኞችን በሚመለከት ማናቸውም ጉዳይ ከኃላፊነትና ከተጠያቂነት ማምለጥ<br />
እንደማይችሉ <strong>መንግስት</strong> እርምጃ በመውሰድ ትምህርት ሊሰጥ ይገባል›› በማለት<br />
ሀሳቡን ያጠናክራል፤ ነብዩ።<br />
ሸዋዬ - የማንቂያ ደወል?<br />
‹‹ዘመናዊ ባርነትን ለማስፋፋት የሚሯሯጡትን ጥጋጥግ ላይ ያሉትን ሕገ-ወጥ<br />
ደላሎች ተከታትሎ መቆጣጠር <strong>መንግስት</strong> አቅቶት ነውን?›› ሲሉ የሚጠይቁት<br />
ፕሮፌሰር በየነ መረጃው ጠፍቶት ሳይሆን ኃላፊነት ያለመስማት ችግር ነው ካሉ<br />
በኋላ ይህን ችግር መቅረፍ የችግሩን ግማሽ ያህል መቅረፍ መሆኑን ይስማማሉ።<br />
‹‹ሸዋዬ ሞላ ለደረሰባት ጉዳቶች፣ ሕመምና ስቃይ ካሳ ይገባታል›› የሚል አመለካከት<br />
አለኝ›› የሚሉት ዶ/ር ሼክስፒር ፈይሳ ‹‹የደረሱባት ከባድ ጉዳቶች በቀጥታ ከጋዳፊ<br />
ቤተሰብ እርምጃዎች የመነጩ ናቸውና ጋዳፊንና ቀንደኛ ጋሻግሬዎቻውን በፍትሐ<br />
ብሔርም ብቻ ሳይሆን በወንጀል ሕግም ተጠያቂ ሊያደርጋቸው ስለሚችል ካሳ<br />
ለማስከፈል የኢትዮጵያ <strong>መንግስት</strong>ን ትጋት ይሻል›› ይላሉ።<br />
በሸዋዬ ሞላ ላይ የተፈፀመው ድርጊት እጅግ አስከፊና በኢትዮጰያዊነት ብሔራዊ ኩራት<br />
ላይ የተቃጣ ቢሆንም፣ የተገለፁትን ችግሮች ለመቅረፍ እንደማንቂያ ደወል ሊወሰድ<br />
እንደሚገባ እየተገለፀ ነው። ወጣቷ የተሻለ ኑሮ ፍለጋን ሲንከራተቱ በየበረኻውና<br />
በየባሕሩ ድምፃቸው ዳግም ላይሰማ ጠፍቶ የቀረ እንዲሁም በአሠሪዎቻቸው ግፍ<br />
ለሚፈፀምባቸው ሌሎች የአገሯ ልጆች ሁሉ ማሳያ ተደርጋ እየተወሰደች ነው። የወጣቷ<br />
ጉዳይ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሰፊ ሽፋን ተሰጥቶት በመዘገቡ የተነሳ የእርዳታ እጆች<br />
እንዲዘረጉ የተማፅኖ ጥሪዎች እየቀረቡ ሲሆን፣ በተመሳሳይ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ<br />
ኢትዮጵያውያን ዕልፍ አዕላፍ መሆናቸውን በመግለፅ ‹‹እነሱንም እንታደጋቸው››<br />
የሚሉ ድምጾች ሊበረክቱ እንደሚገባ የሚወተውቱ ወገኖች መደመጥ ጀምረዋል።<br />
ሌሎች ደግሞ ይህ ወቅት የኢትዮጵያ <strong>መንግስት</strong> መፈተኛው መሆኑን<br />
በመግለፅ ላይ ናቸው። ‹‹<strong>መንግስት</strong> የድርጊቱን ፈፃሚዎች በዓለም አቀፍ ፍ/<br />
ቤት በመክሰስ ተመጣጣኙን ቅጣት ሊያስወስንባቸው ይገባል›› የሚሉት እነዚህ<br />
ወገኖች፣ ኢትዮጵያውያን በርክተው ከሚገኙባቸው የአረብ አገራት መንግስታት ጋር<br />
የዜጎቹን ሁኔታ አስመልክቶ ከእስካሁኑ ‹‹ኮስተር›› ባለ መልኩ ሊነጋገር እንደሚገባ<br />
አስገንዝበዋል።<br />
‹‹‘የማንቂያ ደወል’ የሚለው አገላለፅ ትክክለኛ ነው›› የሚሉት አምባሳደር ዲና<br />
ሙፍቲ ደግሞ በበኩላቸው፣ ከዚህ በኋላ ወደ አረብ ሐገራት ለመጓዝ የሚያስቡ<br />
አካሄዳቸውን ሕጋዊ በማድረግና በአቅራቢያቸው ወዳለ ኤምባሲ አሊያም ቆንጽላ<br />
ጽ/ቤት ሄደው በመመዝገብ ለራሳቸው ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚኖርባቸው<br />
አስገንዝበዋል፡፡<br />
ዞሮ ዞሮ በአረብ ሐገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን መብት ስለማስከበር ሲነሳ<br />
ዓይኖች ወደ ኤምባሲዎች ማነጣጠራቸው አይቀርምና ወደ አካባቢው የሚላኩት<br />
ዲፕሎማቶች ከፖለቲካ ታማኝነታቸው ባለፈ በሰብዓዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸው በቂ<br />
የሥራ ልምድና ፍላጎት ግምት ውስጥ ሊገባ እንደሚገባ የበርካቶች መስማሚያ ነጥብ<br />
ነው።
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />
መልካም ዓዲስ ዓመት<br />
}SdeK¨< Ÿ}c\ ð×” ¾h¨` ¨