26.07.2013 Views

መፈንቅለ መንግስት...

መፈንቅለ መንግስት...

መፈንቅለ መንግስት...

SHOW MORE
SHOW LESS

Create successful ePaper yourself

Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.

አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />

መልካም<br />

ዓዲስ ዓመት<br />

መልካም ዓዲስ ዓመት<br />

የምንሻው<br />

አጋርነት<br />

በባራክ ኦባማ<br />

/ፕሬዝዳንት/<br />

‹‹በአዲሱ ዓመት ‘አሸባሪ’<br />

ከመባል ይጠብቃችሁ››<br />

ሰሞነኛ ምርቃት<br />

ከታች ሰፈር ልጆች ጋር በኮሪያ- ዴጉ ተካሂዶ የነበረውን የአትሌቲክስ ሻምፒዮና<br />

ፍፃሜ እየተመለከትን እያለ ምነው አትሌቶቻችን ውጤት ራቃቸው ብል እየተቀባበሉ<br />

‹‹የሚወራውን አልሰማህም እንዴ?… ‘እያንጓለለ ካልተፈታ’ ብለው አድማ ላይ እኮ<br />

4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5 2003 ዋጋ 7፡00 ብር<br />

•<br />

•<br />

•<br />

‹‹በቴሌቪዥን በሚሰሩት ‘ድራማ’ ሀቅ ሊወጣ አይችልም››<br />

ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ<br />

ለቢቢሲ ያወራነው በአደባባይ ነጋ ጠባ ስናወራው የነበረ ነው<br />

የኢቴቪ ዘገባ ላይ የትርጉም ስህተቶች ነበሩ<br />

አባሎቻችሁ ናቸው የተባሉ ሰዎችን አላውቃቸውም<br />

የደርግ ከፍተኛ ባለስልጣን የነበሩትና ኋላ ላይም ስርአቱን በመክዳት ወደ ውጭ ያቀኑት<br />

ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ ከሁለት አስርት አመታት በኋላ ሰሞኑን የመጀመሪያ<br />

የሆነውን ይፋዊ ቃለምልልስ ሰጥተዋል። ግንቦት 8 ቀን 1981 ዓ.ም ስለተደረገው<br />

መንፈንቅለ <strong>መንግስት</strong>፣ደርግን ሥርዓት ለመጣል ይፋለሙ የነበሩትን ሻዕቢያና ህወሀትን<br />

በማግባባት ረገድ ምን ሚና እንደተጫወቱ፣ በወቅታዊው የኢትዮጵያ ፖለቲካና<br />

እስካሁን ይፋ ባልተደረጉ በርካታ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ በዝርዝር ይናገራሉ፡<br />

“የ1981 <strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong><br />

ለማድረግ ከሻዕቢያና ከወያኔ ጋር ተስማምተን ነበር”<br />

በ ገፅ 16<br />

በውስጥ ገፅ በውስጥ ገፅ በውስጥ ገፅ<br />

እንቁጣጣሽ<br />

Vs<br />

ቅዱስ ዮሐንስ<br />

በ ገፅ 20<br />

ደበበ እሸቱ እንዲፈታ አንድነት/መድረክ ጠየቀ<br />

• ‹‹<strong>መንግስት</strong> ሕዝቡን እያሸበረ ነው››<br />

•<br />

‹‹ኢህአዴግ ሁለት ሰዎች ድንበር አቋረጡ ብሎ ሊጨነቅ ቀርቶ አገር ገንጥሎ የሚሰጥ ድርጅት ነው››<br />

በሱራፍኤል ግርማ<br />

<strong>መንግስት</strong> በአሸባሪነት ከፈረጀው ግንቦት ሰባት ጋር ‹‹የሕቡዕ ግንኙነት አለው›› በሚል ምክንያት ለእስር<br />

የተዳረገው አንጋፋው አርቲስትና ፖለቲከኛ ደበበ እሸቱ እንዲፈታ የመድረክ አመራር አባላት ጠየቁ።<br />

ምንም እንኳን የአቶ ደበበን መታሰር አስመልክቶ ለብሉም በርግ አስተያየታቸውን የሰጡት የ<strong>መንግስት</strong><br />

ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ሽመልስ ከማል ‹‹ከአሸባሪው ግንቦት ሰባት ጋር ግንኙነት አለው፤<br />

የሚስ አብዮታዊ ዴሞክራሲ<br />

ልማታዊ ውበት ምስጢር<br />

አንባብያን ሆይ! የተያያዝነውን የሀገር ገፅታ ግንባታ በማስቀጠሉ ረገድ ጉልህ ሚና<br />

እንደሚጫወት የታመነበት ታላቅ ውድድር በቅርቡ መካሄዱ ይታወቃል። በውድድሩም<br />

በታሪካችን ለመጀመሪያ ጊዜ የብሔር ብሔረሰቦችን እኩል ተሳትፎ ባረጋገጠ መልኩ ከተለያዩ<br />

የኅብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጣ የልማታዊ ዳኞች ቡድን፣ የልማታዊ ውበትን እሳቤ የተላበሰች<br />

ቆንጆ መርጦ “ሚስ አብዩታዊት ዴሞክራሲ” ሲል ሰይሟል። ወርቃማው የአሸናፊነት ዘውድ<br />

በክብር ከተጫነላት ወጣት ጋር ልማታዊው ጋዜጠኛችን ቀጣዩን አጭር ቆይታ አድርጓል።<br />

ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ<br />

ናቸው›› አሉኝ። ምን ለማለት ፈልገው እንደሆነ ግን አልገባኝም፡፡<br />

በ ገፅ 9<br />

በ ገፅ 21<br />

በ ገፅ 9<br />

በ ገፅ 7<br />

ማብቂያ የለሹ የኢትዮጵያዊያን ሰቆቃ<br />

በመካከለኛው ምስራቅ?!<br />

አሜሪካ ስለኢትዮጵያ<br />

ምን ታስባለች?<br />

አዳዲስ የዊክሊክስ<br />

መረጃዎች ይናገራሉ<br />

ጠ/ሚኒስትሩ የወታደራዊ ኃይል<br />

የበላዩ ጄኔራል ሳሞራ እና የደህንነት<br />

ክፍሉ ሃላፊ አቶ ጌታቸው አሰፋ<br />

አሜሪካ የኢትዮጵያን የደህንነት<br />

አሳሳቢ ጉዳዮች ጉዳዬ ትላቸው<br />

እንደሆን እምነቱ ተመናምኖባቸዋል<br />

እስከማለት ደርሰዋል። እነዚህ<br />

ሁለቱ ባለሥልጣናት ጦረኛ ነገር<br />

ግን በውጭ ፖሊሲ ጉዳይ ላይ<br />

እጅግ ተፅዕኖ ፈጣሪ የገዢው<br />

ፓርቲ አባላት ናቸው።<br />

5<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ


2<br />

የካቲት 2000 ዓ.ም ተመሠረተ<br />

አውራምባ ታይምስ፡- በብሉ<br />

ኤርዝ ጀነራል ቢዝነስ ኃላ/የተ/<br />

የግል/ማህበር ስር የሚታተም፤<br />

በፖለቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ<br />

የሚያተኩር፤ በንግድ ሚኒስቴር<br />

በቁጥር 020/2/6572/2001<br />

የተመዘገበ ሳምንታዊ ጋዜጣ ነው፡፡<br />

T’@Í=”Ó ›?Ç=}`<br />

Ç©ƒ ŸuÅ<br />

ª“ ›²ÒÏ<br />

õì


አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />

መልካም ዓዲስ ዓመት<br />

በባራክ ኦባማ<br />

/ፕሬዝዳንት/<br />

በዚህ የመስከረም<br />

1፣ 1993 የሽብርተኞች ጥቃት<br />

10ኛ ዓመት መታሰቢያ፣ የሽብር<br />

ጥቃቱ በዩናይትድ ስቴትስ<br />

ላይ ብቻ ሳይሆን፣ በዓለም<br />

እንዲሁም በሰብዓዊነት እና<br />

በጋራ ተስፋዎቻችን ላይ የተቃጣ<br />

መሆኑን እናስታውሳለን።<br />

በዚያን ዕለት<br />

ሕይወታቸውን ካጡት ወደ<br />

3ሺህ የሚጠጉ ንፁሀን ሰዎች<br />

ውስጥ በመቶዎች የሚቆጠሩት<br />

ከ90 የሚበልጡ አገራት ዜጎች<br />

እንደነበሩም እናስታውሳለን።<br />

በርካታ ዘሮች እና እምነቶች<br />

ያሏቸው ወንዶችና ሴቶች፣<br />

ወጣትና አዛውንትም ነበሩ። በዚህ<br />

የሐዘን መታሰቢያ የእነርሱን<br />

ትውስታ ከቤተሰቦቻቸው እና<br />

ከየአገሮቻቸው ጋር በመሆን<br />

በአክብሮት እንዘክራለን።<br />

የዛሬ አሥር ዓመት<br />

ዓለም እንደ አንድ የተሰባሰበበትን<br />

ሁኔታ ከምስጋና ጋር<br />

እናስታውሰዋለን። በዓለም ዙርያ<br />

ያሉ ከተሞች በሙሉ ለደቂቃ<br />

በሕሊና ፀሎት እረጭ ብለው ነበር።<br />

ሰዎች በአብያተ-ክርስቲያናት፣<br />

በመስጊዶች፣ በምኩራቦችና<br />

የምንሻው<br />

አጋርነት<br />

በሌሎችም የአምልኮ ሥፍራዎች<br />

ፀሎታቸውን አድርሰዋል። እኛም<br />

በዩናይትድ ስቴትስ የምንገኝ፣<br />

በመላው የዓለም ዳርቻ የሚገኙ<br />

ሕዝቦች ባከበሯቸው የሻማ<br />

ምሽቶችና በየኤምባሲዎቻችን<br />

ደጃፎች ባስቀመጧቸው አበቦች<br />

በአንድነት መንፈስ ከጎናችን<br />

መቆማቸውን ያሳዩበትን ሁኔታ<br />

ከቶም አንረሳውም።<br />

ከመስከረም 1፣<br />

1993 በኋላ ባሉት ሳምንታት<br />

እንደ ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ<br />

መንቀሳቀሳችንንም እናስታውሳለን።<br />

የመጠነ ሰፊው ጥምረታችን አካል<br />

በሆነ እንቅስቃሴ አል-ቃኢዳን<br />

በአፍጋኒስታን ከሚገኙ የማሰልጠኛ<br />

ሠፈሮቹ አባረነዋል፤ ታሊባንን<br />

ከሥልጣን አስወግደናል፤<br />

እንዲሁም ለአፍጋን ሕዝቦች<br />

ከሽብር ነፃ ሆነው የሚኖሩበትን<br />

ዕድል ሰጥተናቸዋል። ነገር<br />

ግን ቀጣዮቹ ዓመታት ቀላል<br />

አልነበሩም፤ በመስከረም 1፣ 1993<br />

ማግስት ተጋርተነው የነበረው<br />

የዓለም አቀፍ አጋርነት መንፈስም<br />

ፈተና ገጥሞት ነበር።<br />

እንደ አሜሪካ<br />

ፕሬዝዳንትነቴ፣ የተጋረጡብንን<br />

ዓለማቀፋዊ ተግዳሮቶች<br />

ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ለመቋቋም<br />

የሚያስፈልገንን ዓለምአቀፋዊ<br />

ትብብር ለማደስ የሚያስችሉ<br />

ተግባራትን አከናውኛለሁ። አብሮ<br />

የመሥራት አዲስ ዘመንን ይፋ<br />

በማድረግ፣ ከአገራትና ከሕዝቦች<br />

ጋር በጋራ ፍላጎትና በመከባበር<br />

ላይ የተመሠረተ አጋርነትን<br />

መሥርተናል።<br />

እንደ ዓለም አቀፍ<br />

ማኅበረሰብ፣ ሽብርተኞች ከዜጎቻችን<br />

ጋር የሚነጻጸር ጥንካሬና ፅናት<br />

እንደሌላቸው አሳይተናል።<br />

ዩናይትድ ስቴትስ ከኢስላም ጋር<br />

ጦርነት ውስጥ እንዳልሆነችና<br />

ወደፊትም እንደማትሆን ግልጽ<br />

አድርጌአለሁ። ከዚያ ይልቅ፣<br />

CITY TECH TRADING<br />

New Arrival Surveying Equipment<br />

Leica Total Stations<br />

Sokkia Totalstation<br />

Sokkia Automatic Level<br />

Come and Visit Our Shop to Get All<br />

Surveying Equipment with Affordable Price<br />

Address:-Bole DH Geda Tower 1st floor, No 1-09<br />

Tell: +251911 229906 ,+251 16628452 +251 16628052<br />

ከተባባሪዎቻችንና ከአጋሮቻችን ጋር<br />

አል-ቃኢዳን ለመዋጋት በአንድነት<br />

ቆመናል። አል-ቃኢዳ በበርካታ<br />

አገራት በፈፀማቸው ጥቃቶች<br />

በአሥር ሺህዎች የሚቆጠሩ<br />

ንፁኃን ወንዶች፣ ሴቶችና ሕፃናትን<br />

የገደለ ሲኾን፣ ከሰለባዎቹ ውስጥ<br />

እጅግ የሚበዙት ሙስሊሞች<br />

ናቸው። እናም በዚህ ሳምንት፣<br />

ከመካከለኛው ምስራቅ እስከ<br />

አውሮፓ፣ ከአፍሪካ እስከ ኢሲያ<br />

ሁሉንም የአል-ቃኢዳ ሰለባዎች፣<br />

እንዲሁም ቤተሰቦቻቸውና<br />

ዜጎቻቸው በፈታኝ ሁኔታዎች<br />

ውስጥ ለማለፍ ያሳዩትን ድፍረትና<br />

ፅናት እናስታውሳለን።<br />

በጋራ በመንቀሳቀሳችን<br />

የአል-ቃኢዳ ሴራዎችን አክሽፈናል፤<br />

ኦሳማ ቢን ላደንንና ብዙዎቹን<br />

የአመራሩ አባላት አስወግደናል፤<br />

እናም አል-ቃኢዳን በሽንፈት<br />

ጎዳና ላይ እንዲጓዝ ዳርገነዋል።<br />

ይህ በዚህ እንዳለ፣ በመካከለኛው<br />

ምስራቅና በሰሜን አፍሪካ<br />

የሚገኙ ሕዝቦች ፍትኅና ሰብዓዊ<br />

ክብርን ለመቀዳጀት የሚያበቃው<br />

እርግጠኛ መንገድ፣ አዕምሮ-አልቦ<br />

ሽብርተኝነትና ነውጥ ሳይሆን፣<br />

ከነውጥ አልባነት የሚመነጭ<br />

የሞራል ኃይል (የበላይነት)<br />

መሆኑን እያሳዩ ይገኛሉ። ይህ<br />

ሁኔታ ነውጠኛ ጽንፈኞች<br />

ሰሚ እያጡ መምጣታቸውንና<br />

መጪው ዘመን የእነዚያ ለማፍረስ<br />

የሚተጉት ሽብርተኞች ሳይሆን<br />

መገንባትን ለሚሹት መሆኑን<br />

በግልጽ አመላክቷል።<br />

የሰላምና የብልጽግና<br />

መጻዒ ዘመንን ለሚሹ አገራትና<br />

ሕዝቦች - ዩናይትድ ስቴትስ<br />

ከእነርሱ ጋር በአጋርነት<br />

ትቆማለች። በአገር ውስጥ<br />

ኢኮኖሚያዊ ተግዳሮቶች እያሉብን<br />

እንኳ፣ ዩናይትድ ስቴትስ በዓለም<br />

ላይ የተለየ የአመራር ሚና<br />

መጫወቷን ትቀጥላለች። ከኢራቅ<br />

ቀሪ ወታደሮቻችንን ስናስወጣና<br />

በአፍጋኒስታንም ፀጥታ የማስከበር<br />

ኃላፊነቱን ስናስተላልፍ፣<br />

ኢራቃውያንና አፍጋኖች<br />

የሕዝቦቻቸውን ደኅንነት ለማስከበር<br />

እና የዕድሎች ተጠቃሚነትን<br />

ለማረጋገጥ የሚያደርጉትን<br />

ጥረት መደገፋችንን እንቀጥላለን።<br />

በአረቡ ዓለምና ከዚያም ባሻገር፣<br />

ለመላው የሰው ልጆች ክብር እና<br />

ሁለንተናዊ መብቶች መከበር<br />

በጽናት እንቆማለን።<br />

በዓለም ዙርያ ሰላምን<br />

ለማስፈን፣ ሕዝቦችን ከድህነት<br />

የሚያወጡ የልማት ተግባራትን<br />

ለማገዝ፣ እንዲሁም የምግብ<br />

ዋስትናን፣ ጤናንና የዜጎችና<br />

የኅብረተሰብን እምቅ አቅም ጥቅም<br />

ላይ ለማዋል የሚያስችለውን<br />

መልካም አስተዳደር ለማራመድ<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

3<br />

የሚጠይቀውን ከባድ ሥራ<br />

መስራታችንን እንቀጥላለን።<br />

ከዚሁ ጎን ለጎን፣<br />

በአገር ውስጥ እሴቶቻችንን<br />

ጠብቀን ለመኖር የራሳችንን<br />

ቃል-ኪዳን እናድሳለን፡፡ ዩናይትድ<br />

ስቴትስ የስደተኞች አገር<br />

እንደመሆኗ ከየትኛውም አገርና<br />

ባህል የሚመጡ ሕዝቦችን እጆቿን<br />

ዘርግታ ትቀበላለች። እኒህ አዳዲስ<br />

አሜሪካውያን - የዛሬ አሥር ዓመት<br />

እንዳጣናቸው ንፁኃን የሽብር<br />

ሰለባዎች ሁሉ - የቱንም ያህል<br />

የዘር ወይም የጎሳ፣ የአስተዳደግ<br />

ወይም የእምነት ልዩነቶች<br />

ቢኖሩን እንኳ ሁላችንም ይህችን<br />

ዓለም ለዛሬውም ሆነ ለመጪው<br />

ትውልድ የተሻለች የመኖርያ<br />

ስፍራ ለማድረግ እንችላለን<br />

በሚል የጋራ ተስፋ የተሳሰርን<br />

መሆናችንን ያስታውሱናል።<br />

እነዚያን ያጣናቸውን ሰዎችም<br />

ከዚህ ታላቅ እሴት ጋር ልናስባቸው<br />

ግድ ይለናል።<br />

እነዚያ መስከረም 1<br />

ቀን 1993 ጥቃት የፈፀሙብን<br />

ሰዎች በዩናይትድ ስቴትስ እና<br />

በተቀረው ዓለም መካከል የጥላቻ<br />

ንፋስ እንዲነፍስ ፈልገው ነበር።<br />

አልተሳካላቸውም። እነሆ በጥቃቱ<br />

የአሥረኛ ዓመት መታሰቢያ<br />

ከወዳጆቻችንና ከአጋሮቻችን ጋር<br />

በአንድነት ቆመን እነዚያን በዚህ<br />

ትግል ውስጥ ያጣናቸውን በሙሉ<br />

እናስታውሳለን። እነርሱንም<br />

በማስታወስ፣ ሕዝቦች ሁሉ<br />

በክብር፣ በነፃነትና በሰላም<br />

የሚኖሩባትን ዓለም ዕውን<br />

ለማድረግ የሚያስፈልገንን<br />

የአጋርነትና የመከባበር መንፈስ<br />

ዳግም እናረጋግጣለን።<br />

/ባራክ ኦባማ የዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ ፕሬዝዳንት ናቸው።<br />

ይህ ጽሑፍ፣ የመስከረም አንዱ የሽብርተኞች ጥቃት 10ኛ ዓመት<br />

መታሰቢያን አስመልክተው ያስተላለፉት መልእክት ሲሆን አዲስ አበባ<br />

በሚገኘው የአሜሪካን ኤምባሲ በኩል ለዝግጅት ክፍላችን የተላከ ነው።/


4<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

ፊ ቸ ር<br />

አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />

መልካም ዓዲስ ዓመት<br />

ማብቂያ የለሹ የኢትዮጵያዊያን ሰቆቃ<br />

በመካከለኛው ምስራቅ?!<br />

ኢትዮጵያዊያን ወደ መካከለኛው ምስራቅ የሚያደርጉት ስደት እና የሚደርስባቸው ኢ-ሰብዓዊ ጥቃት የጭንቅ ዜና አብሳሪነቱ ቀጥሏል። አቤል ዓለማየሁ እና<br />

ሱራፍኤል ግርማ ባሰናዱት ቀጣይ ሀተታዊ ፅሁፋቸው የህግ ባለሙያዎች፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፣ በጉዳዩ ላይ ሰፊ ጥናት ያካሄዱ ኢትዮጵያዊያንንና<br />

ዕድሜያቸው በ60ዎቹ መባቻ ላይ የሚገመተው<br />

ወ/ሮ ኩሪ ወልዱ በትካዜ ተውጠው ዕንባቸው መንታ<br />

መንታ ሆኖ ይወርዳል። በጎረቤቶቻቸውና በንስሐ<br />

አባታቸው ጭምር ቢለመኑ፣ ቢገዘቱ ማንባታቸውን<br />

ማቆም አልቻሉም። ስለልጃቸው መልካም ፀባይና ቅን<br />

አሳቢነት ሳይታክቱ ደግመው ደጋግመው በማያባራው<br />

እንባቸው በመታጀብ ይናገራሉ። ‹‹ልጄን የማጎርስበት<br />

አቅም እንኳን የለኝም፤ እንዲያሳክምልኝ <strong>መንግስት</strong>ን<br />

እና የኢትዮጵያን ሕዝብ እለምናለሁ›› የሚል<br />

ተማፅኗቸውን ያቀርባሉ። አዛውንቷ ወ/ሮ በሞሐመድ<br />

ጋዳፊ ቤተሰብ ኢ-ሰብዓዊ ጥቃት የደረሰባት የሸዋዬ<br />

ሞላ እናት ናቸው።<br />

ሊቢያን ለ42 ዓመታት እንደግል ድርጅታቸው<br />

ባሻቸው መንገድ ሲዘውሯት እንደኖሩና የአምባገነኖች<br />

አርአያ መሆናቸው ከሚነገርላቸው ጋዳፊ ልጆች<br />

አንዱ የሆነው ሐኒባል ጋዳፊ ሚስት የሆነችው<br />

አሊያን፤ እንጀራ ፍለጋ በተሰደደችው ሸዋዬ ሞላ<br />

ላይ ያደረሰችው ዘግናኝ ድርጊት ልብ አድሚም፣<br />

አነጋጋሪም ሆኗል። አሊያን ‹‹ያለ ምግብና ውኃ ለሶስት<br />

ቀናት እንድትቆዪ የሰጠኹሽን ትዕዛዝ ተላልፈሻል››<br />

በሚል ምክንያት የወጣቷን እጅና እግር በሌሎች<br />

የቤት ሠራተኞች አሳስራ የፈላ ውኃ በጭንቅላቷ<br />

ላይ በማፍሰስ ከባድ ጉዳት ከማድረሷ በላይ፣ ወጣቷ<br />

ሕክምና እና በቂ ምግብና ውኃ እንዳታገኝ በጠባብ<br />

ከፍል ውስጥ ለወራት ዘግታባት መቆየቷ የጥቃቱን<br />

ከፍተኛነት አጉልቶታል።<br />

የሚመለከታቸው የ<strong>መንግስት</strong> ባለስልጣናትን በማነጋገር ‹‹ይህ ችግር ማብቂያው መቼ ይሆን?›› ሲሉ ይጠይቃሉ።<br />

ኃላፊ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ሴቶችም ሆኑ ወንዶች<br />

እድላቸውን ለመሞከር በዓለም አቀፍ መድረክ ሙከራ<br />

ማድረጋቸውን (መጓዛቸውን) እንደ ችግር መውሰድ<br />

እንደሌለበት ጠቁመው ‹‹ግን›› ይላሉ፣ ‹‹ግን ዜጎች<br />

በሄዱበት የዜግነት ክብራቸው እንዳይነካ <strong>መንግስት</strong><br />

ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል። <strong>መንግስት</strong> ያለውም ዜጎች<br />

ጥቅም ለማስጠበቅ ነውና›› ይላሉ።<br />

‹‹እዚህ አገር ያለው አማራጭ ውስጥ ስለሆነ ዜጎች<br />

በሕገ-ወጥ መንገድ ከአገር ወጥተዋል ብሎ በቸልታ<br />

ሊታዩ አይገባም። ራስን ለመለወጥ እንደሚደረግ<br />

ሰዋዊ ባህሪ ማየት ይገባል። ስለሁሉም ኢትዮጵያዊ<br />

ዜጋ ኃላፊነት አለበት›› በማለት ፕሮፌሰር በየነ<br />

ጴጥሮስ ለሁሉም ዜጎች ከለላ መሆን እንዳለበት<br />

<strong>መንግስት</strong>ን ያሳስባሉ።<br />

የኢትዮጵያ <strong>መንግስት</strong><br />

ለዜጎቹ ከለላ እየሆነ ነውን?<br />

የደነደነ ልብ ያለውን ሰው እንኳን ስሜት<br />

የሚሰብረው መካከለኛው ምስራቅ እና አንዳንድ<br />

የአፍሪካ አገራት የሚጓዙ ኢትዮጵያውያን ሴቶች<br />

መብት ጥሰት የዘወትር ጩኸት ቢሆንም የሸዋዬ<br />

ሞላ ጉዳት የሲ.ኤን.ኤን፣ አልጀዚራና አል አረቢያ<br />

በግርድፉም ቢሆን የሌሎች ብዙዎች የሚከታተሏቸው<br />

መገናኛ ብዙሐንን ከወትሮው የተለየ ትኩረት ስላገኘ<br />

ዓለም አቀፍ መነጋገሪያ ሆኗል። አጋጣሚውን በአረብ<br />

አገራቱ ላሉ ዜጎች መታደግ የሚቻልበት ጊዜ ‹‹አሁን››<br />

መሆኑን ይበልጥ ስለመጠቆሙ እየተገለፀ ነው።<br />

ሸዋዬ ላይ የተፈፀመው በደል በሊቢያ ከተፈጠረው<br />

አመፅ ተንተርሶ በጋዳፊ ቤተሰብ መሆኑ ዓለም አቀፍ<br />

ትኩረትን ስቦ ለመነጋገሪያነት በቃ እንጂ፣ በሌሎች<br />

አረብ አሰሪዎቻቸው ከፍተኛ ስቃይ የሚደርስባቸው<br />

አያሌ ‹‹ሸዋዬዎች›› መኖራቸው የዘወትር ሐቅ ነው።<br />

‹‹የአረብ አገር ሕይወት መሯት ራሷን ከፎቅ ወርውራ<br />

ሞተች››፣ ‹‹መርዝ በመጠጣት ራሷን የማጥፋት<br />

ሙከራ አደረገች›› እንዲሁም ‹‹አሰሪዋን ገደለች››<br />

የሚሉ ዜናዎች ለኢትዮጵያውያን አዲስ አይደሉም።<br />

‹‹የሸዋዬ ጉዳይ የሚዲያዎችን ሰፊ ትኩረት<br />

ስላገኘ አረቦች ደንግጠዋል። መንግስታቱም የዜጎችን<br />

መብት ያከብሩ ዘንድ ከዓለም አቀፍ ሰብዓዊ መብት<br />

ጠባቂዎች ወቀሳ ለማምለጥ የተቻላቸውን ያህል<br />

የሰብዓዊ መብት ጥበቃ ያደርጋሉ የሚል እምነት<br />

አለኝ›› የሚለው ነብዩ ሲራክ አጋጣሚው (የሸዋዬ<br />

ጉዳት) አሳዛኝ ቢሆንም ችግሩ እንዲጎላና ዓለማቀፋዊ<br />

እውቅና እንዲኖረው የሚያደርግ መልካም አጋጣሚ<br />

መፈጠሩን ያምናል። አምባሳደር ዲና ሙፍቲም<br />

ክስተቱ ንቃትን እንደሚጨምር ይስማማሉ።<br />

‹‹በየኤምባሲው ያሉ ሰዎች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ<br />

መወጣት አለባቸው። በትክክል ውጪ የሚገኙ<br />

ኢትዮጵያውያን ለሚያቀርቧቸው ጥያቄዎች ተገቢውን<br />

ምላሽ ሊሰጥ ይገባል›› ይላሉ።<br />

ተቀድቶ ‹‹በማያልቅ›› የነዳጅ ሀብት አቅማቸው<br />

ወደዳበሩት የአረብ አገራት ከቤት ሰራተኝነት ብቻ<br />

ሳይሆን በተለያየ የሙያ መስኮች ሥራ ፈላጊዎች<br />

ይተማሉ። በቤት ሰራተኝነት ወደ አገራቱ ከሚደርሱ<br />

ዜጎች መካከል የሩቅ ምስራቅ አገሮች ቁጥራቸው<br />

ያይላል፤ ኢንዶኔዥያ፣ ስሪላንካ፣ ፊሊፒንስ፣<br />

ሕንድ፣ ፓኪስታን፣ ባንግላዴሽ…። የኢትዮጵያውያኑ<br />

ቁጥርም ከፍተኛ ሲሆን በተለይ የቅርብ መረጃዎች<br />

እንደሚያሳዩት ከሆነ እንደ አትሌቲክሱ ሁሉ በቤት<br />

ሠራተኝነት ፍልሰትም የኢትዮጵያውያኑ ቁጥር<br />

በልጠው ኬኒያዊያን በአገራቱ እየተነሰነሱ ነው፡፡<br />

ሸዋዬ ሞላ፣<br />

ዜጎች ለምን ይፈልሳሉ?<br />

የኢትዮጵያ ሕገ-<strong>መንግስት</strong>፣ አንቀጽ 32 የመዘዋወር<br />

ነፃነት በሚል ርዕስ ንዑስ አንቀፅ አንድ እና ሁለት<br />

ላይ በሰፈረው መሠረት፣ ‹‹ማንኛውም ኢትዮጵያዊ<br />

በሕጋዊ መንገድ የመዘዋወር፣ በፈለገው ጊዜ ከአገር<br />

የመውጣት ነፃነት እና ወደ አገሩ የመመለስ መብት<br />

እንዳለው ይደነግጋል።<br />

ብዙ ዜጎች ግን ይህን መብት በመጠቀም ወደ<br />

ሌላ አገር የሚሻገሩት በሰራተኛና ማሕበራዊ ጉዳይ<br />

ሚኒስቴር አማካኝነት ዋስትና ተገብቶላቸው እና<br />

ዓለም አቀፋዊ ሕግጋትን በተከተለ ሁኔታ አይደለም።<br />

በዋነኛነት ችግር የሚያጋጥማቸውም ሕገ-ወጥ<br />

ተጓዦቹ መሆኑን የውጪ ጉዳይ ቃል አቀባይ<br />

የሆኑት አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ይገልፃሉ። ‹‹ትልቅ<br />

ይህቺ ኢንዶኔዥያዊት የቤት ሠራተኛ በ50ዎቹ የእድሜ ክልል በሚገኙ አሰሪዋ በተፈፀመባት<br />

ችግር የሚያጋጥማቸው በሕገ-ወጥ ደላላ አማካኝነት<br />

ከባድ ድብደባ ከሸዋዬ የማይተናነስ ጉዳት ደርሶባት መዲና ውስጥ በሚገኝ ፍ/ቤት ቀርባ<br />

ባዶ ተስፋ ተሞልተው የሚሄዱ ናቸው። አሰሪዎቹም<br />

አሰሪዋ ላይ ፍርድ ከመሰጠቱም በላይ የኢንዶኔዥያ እና የሳውዲ አረቢያ የሠራተኛ አቅርቦት<br />

ምንም ዋስትና እንደሌላቸው ስለሚያውቁ እጃቸው<br />

ስምምነት እንዲቋረጥ አንዱ ምክንያት ሆኗል። አገራችን ከዚህ ምን ትማራለች?<br />

ለገባው ኢትዮጵያዊ ደህንነት አይጨነቁም›› ሲሉ<br />

ሕጋዊ ጉዞ አለመኖሩ ችግሩን እንደሚያጎላው<br />

ከአሰራር ጋር በሚፈጠር አለመግባባት የሰብዓዊ<br />

ቢያሰምሩበትም ከቦታው የሚወጡ መረጃዎች<br />

ተልዕኮውን በደንብ ያልተረዳ ነው›› ይላሉ።<br />

መብት ጥሰቶች በሁሉም አገር ሰራተኞች ላይ<br />

የሚጠቁሙት በሕጋዊ ኤጀንሲ በኩል በሰራተኛ እና<br />

በተለያየ ወቅት እንደ አሜሪካ ያሉ የበለፀጉ አገራት<br />

የሚፈፀም ቢሆንም ሌሎች አገራት ለዜጎቻቸው<br />

ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ‹‹ታውቀው›› ድንበር<br />

በሌላ አገር የሚገኙ ዜጎቻቸው በጥፋት ተሳታፊ ቢሆኑ<br />

ከለላ እንደሚቆሙ በምርመራ ጋዜጠኝነት መረጃ<br />

የሚሻገሩትም ከጣጣ ነፃ አለመሆናቸውን ነው።<br />

እንኳን ሰብዓዊ መብታቸው እንዳይደፈር እንቅልፍ<br />

የሰበሰበው የጀርመን ድምፅ ዘጋቢ ነብዩ ሲራክ<br />

ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ይህ ችግር መኖሩን በሳውዲ<br />

አለመተኛታቸው አርያነት ያደርጋቸዋል። [ሕግን<br />

ያስረዳል። ‹‹የተጠቀሱት አገር ዜጎች ችግር<br />

አረቢያ ታዝቧል። ‹‹በሥራ እና አሰሪ ኤጀንሲዎች<br />

የተላለፈ ኢ-ሰብዓዊ አያያዝ እንዲኖረው የሚደነግግ<br />

ከመፈጠሩ አስቀድሞም ሆነ ከተፈጠረ በኋላ<br />

የሚላኩ የኮንትራት ሰራተኞች ተቀባይ አጥተው<br />

ሕግ ስለሌለ] በኢትዮጵያ ውስጥም ሆነ በውጪ<br />

በ<strong>መንግስት</strong> ተወካዮቻቸው አማካኝነት ክትትልና<br />

ለሳምንታት ሲንገላቱ ተመልክቻለሁ። አሰሪዎቻቸውን<br />

አገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ደህንነት እና ዋስትና<br />

ጥበቃ ይደረግላቸዋል። ሲበደሉ ይብዛም ይነስ ፍትህን<br />

አግኝተው ወደ ሥራ የተሰማሩትም በምግብ አቅርቦት፣<br />

እንዲረጋገጥ የኢትዮጵያ <strong>መንግስት</strong> የተቻለውን<br />

ሳያገኙ የሚቀሩበት አጋጣሚ አናሳ ነው›› የሚለው<br />

በሥራ ብዛትና ለተመሳሳይ ችግሮች በመዳረጋቸው<br />

ማድረግ እንዳለበት የሚጠቅሱት ዶ/ር ሼክስፒር<br />

ጋዜጠኛው በቅርቡ አንዲት ኢንዶኔዥያዊት የቤት<br />

አሁን ድረስ ስልክ እየደወሉ የሚገልፁልኝ እህቶች<br />

የአሜሪካን ተሞክሮ በመጥቀስ <strong>መንግስት</strong> እንዲነቃ<br />

ሰራተኛ በ50ዎቹ የእድሜ ክልል በሚገኙ አሰሪዋ<br />

አጋጥመውኛል›› የሚለው ነብዩ የቅርብ ጊዜ<br />

ይጠይቃሉ። ‹‹በአሜሪካ ሴናተሮች እና የኮንግረስ<br />

በተፈፀመባት ከባድ ድብደባ ከሸዋዬ የማይተናነስ<br />

ተሞክሮው ይህን ሀቅ ፍንትው አድርጎ እንደሚገልፅ<br />

አባላት የዜጎች መብቶች፣ ደህንነትና ዋስትናን<br />

ጉዳት ደርሶባት እንደነበር ገልጾ፣ ‹‹ጉዳዩ መዲና<br />

ማሳያውን ይዘረዝራል። ‹‹ከጥቂት ሳምንታት በፊት<br />

ለማረጋገጥ ከሌላ አገር ጋር አብረው በመስራት<br />

ውስጥ በሚገኝ ፍ/ቤት ቀርቦ አሰሪዋ ላይ ፍርድ<br />

ያነጋገርኳት እህት ሳውዲ አረቢያ ጅዳ ለአንድ ሳምንት<br />

ንቁ ተሳትፎ ያደረጋሉ። ይህንንም በተደጋጋሚ<br />

ከመሰጠቱም በላይ የኢንዶኔዥያ እና የሳውዲ<br />

በማቆያ/ እስር ቤት ሆና አሰሪዎቿን ስትጠባበቅ<br />

ተመልክተናል። በእህቶቻችን ላይ የደረሰው በአንድ<br />

አረቢያ የሰራተኛ አቅርቦት ስምምነት እንዲቋረጥ<br />

ብርድ መትቷት የከፋ የጤና መታወክ ገጥሟታል።<br />

አሜሪካዊ ዜጋ ላይ ተፈፅሞ ከሆነ፣ የአሜሪካ<br />

ምክንያት ከሆኑ ጉዳዩች መካከል አንዱ ሆኗል›› ሲል<br />

አሰሪዎቿም መጥተው ቢወስዷትም ግማሽ ጎኗ<br />

<strong>መንግስት</strong> ጉዳቱን በቀላሉ አይመለከተውም። ለዜጋው<br />

በምሳሌነት በሳውዲ አረቢያ መገናኛ ብዙሃን ሳይቀር<br />

‹‹ሽባ›› የመሆን የጤና እክል እንዳጋጠማት በተማፅኖ<br />

ፍትህን ለማሰጠት የተቻለውን ሁሉ ያደርጋል።››<br />

ስለተዘገበው ጉዳይ ተናግሯል፤ ጉዳዩ ኢትዮጵያውያን<br />

ገልፃልኛለች። ከእሷ ባገኘሁት አድራሻ መሠረት<br />

ላይ ሲያጠነጥን ግን ትኩረቱ የተገላቢጦሽ እንደሆነ<br />

አዲስ አበባ ወደሚገኘው ያመጣት የሥራ አገናኝ<br />

የዲፕሎማቶች ግንዛቤ ሲመዘን<br />

በመጠቆም።<br />

ኤጀንሲ በተደጋጋሚ ብደውልም ስልኩ አይመልስም።<br />

የኢትዮጵያ <strong>መንግስት</strong> በአረቡ ዓለም ላሉት ዜጎቹ<br />

ነዋሪነታቸውን በአሜሪካ ሲያትል ከተማ ያደረጉት<br />

ወደ አገሬ የምገባበትን መንገድ ፈልጉልኝ ስትል<br />

ከለላና ጥበቃ ስለማድረጉ ችግሮች በተነሱ ቁጥር<br />

የሕግ ባለሙያው ዶ/ር ሼክስፒር ፈይሳም የኢትዮጵያ<br />

የድረሱልኝ ጥሪዋን ማሰማቷን በጀርመን ሬዲዮ ላይ<br />

ሁሌም ጥያቄ ያጭራል። በመካከለኛው ምስራቅ<br />

<strong>መንግስት</strong> ከፍተኛ ትኩረት የሚያሻው ጉዳይ ላይ<br />

አቅርቤዋለሁ›› ይላል።<br />

የጀርመን ድምፅ ሬዲዮ ዘጋቢ የሆነው ነቢዩ ሲራክ<br />

ቸልታ እንደመረጠ ከሚያምኑት ውስጥ ናቸው።<br />

ዜጎች በሕጋዊ መንገድ በሠራተኛ እና አሰሪዎች<br />

ጉዳዩን አስመልክቶ ለአውራምባ ታይምስ በሰጠው<br />

<strong>መንግስት</strong> አስቀድሞ ዲፕሎማሲያዊ፣ ፖለቲካዊና<br />

አማካኝነት ስራ አግኘተው ወደ አገራቱ ቢላኩም<br />

ምስክርነት፣ በአካባቢው ያሉ የኢትዮጵያ <strong>መንግስት</strong><br />

ኢኮኖሚያዊ ግንኙነቶቹን ስለሚያስብ በቸልታ<br />

ችግር ሲደርስባቸው የሚያማክሯቸውን የኤምባሲ<br />

ተወካይ ዲፕሎማቶች የዜጎችን መብት ለማስከበር<br />

ለመዋጡ በምክንያትነት ያቀርቡታል። ‹‹<strong>መንግስት</strong><br />

እና ቆንስላ መስሪያ ቤቶች እንዳይገናኙ ያደርጓቸዋል።<br />

እርባና ያለው ሥራ ባለመሥራታቸው እንደሚወቀሱ<br />

ለዜጎቹ የጥበቃና የመቆርቆር ሚናውን ከተወጣ<br />

እንደውም የአሰሪዎች የሴራ ትብታብ የሚጀምረው<br />

ያረጋግጣል።<br />

ያለውን የጠቀስኳቸውን ግንኙነቶች ማጣትን<br />

ኤምባሲ እና ቆንስላ መ/ቤቶችን እንዳያውቁ በማድረግ<br />

‹‹በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ባሉባቸው አረብ<br />

ያስከትልበታል። ለዚህም ነው በተደጋጋሚ ጊዜ ዜጎቹ<br />

ነው፤ በተለይ ሕገ-ወጥ ተጓዦችን።<br />

ሀገራት የሚላኩት በጣት የሚቆጠሩ ዲፕሎማቶች<br />

ሰብዓዊ ባልሆኑ በችግር ውስጥ ሲሰቃዩ ዝምታን<br />

ሴቶቹ በሥራ ቦታ ላይ መድረሳቸውን ‹‹ሃሎ››<br />

በዲፕሎማሲ የጠለቀ ዕውቀት የሌላቸውና<br />

የሚመርጠው›› ይላሉ።<br />

ይበሉ እንጂ ስለ አሰሪዎቻቸው ፀባይ፣ የስራቸው<br />

የሚላኩባቸውን ሐገራት ህግና ስርዓቶች ከራሳቸው<br />

የኢትዮጵያን ልማት፣ ዴሞክራሲና ሰላም ሊደግፉ<br />

አይነት፣ ተገቢ መጠለያ እና ሕክምና ስለማግኘታቸው<br />

ጋር በቶሎ አዋህደው መሥራት ስለሚከብዳቸው<br />

የሚችሉ ስራዎችን መስራት፣ ኢንቨስትመንት እና<br />

በወል አይታወቅም። ይህንን መሰል የችግሮች መነባበር<br />

የዜጎችን መብት ማስከበርም ሆነ ችግሮች ሲከሰቱ<br />

ቱሪዝም መሳብ፣ የውጪ ገበያ ማፈላለግ ብቻ<br />

የተሰላቹ ሰራተኞች በተስፋ መቁረጥ ወንጀል ውስጥ<br />

በአፋጣኝ ለመፍታት ይቸገራሉ›› የሚለው ነቢዩ፣<br />

ሳይሆን የዜጎችን መብት ማስጠበቅም የውጪ ጉዳይ<br />

ተዘፍቀው ይታያሉ። የዜጎች መብት ጠባቂው፤<br />

ያስተዋላቸውን ችግሮች ዘርዝሯል።<br />

ሚኒስቴር በኤምባሲዎች አማካኝነት የሚከውነው<br />

<strong>መንግስት</strong> ተቀዳሚ ግዴታውን መወጣት ያለበት ይህ<br />

በቅርቡ በኩዌት ከ400 በላይ የኮንትራንት<br />

ተልዕኮ እንደሆነ የሚናገሩት አምባሳደር ዲና<br />

ሁሉ ከመከሰቱ በፊት መሆኑን ዶ/ር ሼክስፒር ፈይሳ<br />

ሠራተኞች በአሠሪዎቻቸው የሚደርስባቸውን<br />

ሙፍቲ፣ ‹‹ዋነኛው የስራችን ትኩረት ኢኮኖሚክ<br />

ያሰምሩበታል።<br />

ድብደባና በቂ ምግብ አለመኖር፣ ለአንድ ሥራ ሄደው<br />

ዲፕሎማሲ ነው። ይህ ለማሳካት ውጪ የሚገኙ<br />

ዓለም ለሁሉም ዓለማቀፋዊ ቤት መሆኗ<br />

በተለያዩ ቤቶች እንዲሠሩ በመደረጉ የተፈጠረባቸውን<br />

ኢትዮጵያውያንን መብት ማስከበር የግድ ነው።<br />

ተፈጥሯዊ ሂደት የፈጠረው መሆኑን የሚገልፁት ‹የኢትዮጵያን <strong>መንግስት</strong> ኃላፊነት እየተወጣ ነው›<br />

ባለበት አገር ሆኖ ‘እዚህ ያለሁት ኢንቨስተር ለመሳብ<br />

የመድረክ ምክትል ሊቀ መንበር እና የህዝብ ግንኙነት ተብሎ የሚሞካሸው ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ<br />

ብቻ ነው’ የሚል ዲፕሎማት ካለ ‹‹ያልገባው እና<br />

በ ገፅ 22


አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />

መልካም ዓዲስ ዓመት<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

5


6 ኮመንትሪ<br />

በታዲዎስ ጌታሁን<br />

“<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

“እኚህ ነበሩ”<br />

... የሰው ልጅ<br />

የሚሞተው፣ ዕድሜው<br />

ሲንዘላዘል አብሮ የሚዝረከረክ<br />

እንቅስቃሴውን ሥርዓት ለማስያዝ<br />

የሚደክሙ ወዳጅ ዘዶቹን ሥራ<br />

አስፈትቶ (ያልቀናቸው) በረሀብ<br />

እንዳይገላቸው ‹‹ይመስለኛል››።<br />

አንድ ሰው ወይም<br />

ደግሞ እኔ ብሞት ይህቺ ሀገር<br />

የሚጎድልባት ገፀ-በረከት አለ<br />

ብዬ አላምንም። ይኸን ስሜት<br />

የማይሰጥ ጉዳይ ከማመን ይልቅ፣<br />

የአንድ ግለሰብ ቦርጭ ተደርምሶ/<br />

ፈንድቶ አንዲት ቀበሌን አጥለቀለቀ<br />

የሚል “ስጥ እንግዲህ” ወሬ ባምን<br />

ይቀለኛል።<br />

በእርግጥ አልጋ<br />

ላይ ሲውሉ ቀርቶ ሲያስነጥሱ<br />

እንኳን ክፉ እንዳይገጥማቸው<br />

የምንንሰፈሰፍላቸው አያሌ የሰው<br />

ሰው ኢትዮጵያውያን አሉ።<br />

ሰዎች፣ መቼ<br />

እንደሚሞቱ አይወቁ እንጂ<br />

ከሚያውቋቸው ቀናት በአንዱ<br />

እንደሚሞቱ ያውቃሉ።<br />

እንደሚሞቱ የሚያውቁ ብዙዎች<br />

(ሁሉም) ሲሆኑ፣ “ሞታቸውን”<br />

ጠቀም ላለ ጉዳይ (ለሀገር እና<br />

ለወገን) የሚያውሉ ግን በጣም<br />

ጥቂት ናቸው።<br />

ሙቅ ሲጠጣ ‘ትን’<br />

ብሎት የሞተም ሆነ ለነፃነት<br />

(፬)<br />

/መጠቅለያ/<br />

ሰላም ለእናንተ ለአንባቢዎቼ!<br />

ለሶሰት ሳምንታት የዛሬው<br />

ርዕሳችን መቆያ ሆኖን ሰንብቷል።<br />

ዛሬ መጠቅለያ ያክል ይህንን<br />

እፀፋለሁ።<br />

ውድ አንባቢያን በሁለተኛው<br />

ክፍል ጽሑፍ እንዳልኩት ይህ<br />

ጽሑፍ እንደተናጋሪ እንጅ እንደ<br />

አጥኚ አለዚያም እንደተመራማሪ<br />

የሰራሁት አይደለም። በሌላ<br />

አባባል እንደ አንድ ፀሐፊ<br />

እያየሁና እየሰማሁ ከታዘብኳቸው<br />

ነገሮች እናንተም ከምታዩአቸውና<br />

ከምትሰሟቸው ተነስቼ ነው<br />

የፃፍኩት።<br />

መሰንበቻዬን ሕፃን፣ ወጣት፣<br />

ምሁር፣ ካህን፣ መሪ፣ ሰራተኛ<br />

እያልኩ በርዕስ እየከፋፈልኩ<br />

በአንድ የሞራል ኪሳራ መገለጫው<br />

በሆነ ሰው የሚታዩ ባህሪያትን<br />

ገልጫለሁ። ለመሆኑ ግን ለዚህ<br />

ሁሉ የሞራል ዝቅጠት ተጠያቂው<br />

ማነው? እኔ እንዲህ ይማሰኛል።<br />

ሰዎች በጎ አእምሯዊ<br />

አስተሳሰብን ማዳበር ይችሉ ዘንድ<br />

ትልቁን ሚና የሚወስደው መማር<br />

ነው። መማር ደግሞ ደብተር<br />

ይዞ ትምህርት ቤት መመላለስን<br />

ብቻ ሳይሆን የሚገልፀው፣<br />

ከሃይማኖት /ከእምነት ተቋም/<br />

ከሰፈር፣ ከቤተሰብ፣ ከአካባቢ፣<br />

ሲፋለም የሞተ አንድ ዓይነት<br />

ስም ነው የሚሰጠው - ‘ሞተ’<br />

የሚል። ነገር ግን፣ ሞቱን<br />

ለአንድ ብር ገመድ አሳልፎ<br />

የሰጠ ሰውና ለማኅበረሰብ ነፃነት<br />

የሰጠ፣ በታሪክም ሆነ በትውልድ፣<br />

በሰማይም ሆነ በምድር ‘እኩል’<br />

ክብር አያገኝም።<br />

… ሰዎች፣ ኑሮ<br />

የሚያቀርብላቸውን ጥያቄ<br />

ለመመለስ ብዙ ቦታዎች ይገባሉ<br />

- መሥሪያ ቤቶችን ጨምሮ።<br />

አንድ ሰው ወይም ባለጉዳይ<br />

ከመንግሥትም ሆነ ከግል<br />

መሥሪያ ቤቶች የሚሰጠው<br />

ምላሽ የማያሳምነው ከሆነ<br />

‘ለምን?’ ብሎ መጠየቅ አለበት።<br />

አለበለዚያ በተጠያቂነትና በግል<br />

ፅናት የመገልገል (የመስተናገድ)<br />

መብቱን በገዛ ፈቃዱ አሳልፎ<br />

እንደሰጠ ይቆጠራል።<br />

ሁሉም የየራሱን<br />

መብትና ነፃነት በራሱ ጉልበትና<br />

ወዝ ማስከበር አለበት። ተጠያቂነት<br />

በጎደለው አሰራር መብቱን የተቀማ<br />

ኢትዮጵያዊ፣ የተነጠቀውን ነፃነት<br />

አልያም መብት የሚያስመልስለት<br />

የፈረንሳይ ፓርላማ ሳይሆን ራሱ<br />

ኢትዮጵያዊው ባለጉዳይ ነው።<br />

እያንዳንዱ ሰው የየራሱ<br />

ነፃ አውጪ መሆን አለበት። ለእኔ<br />

ነፃነት ወይም እኔ ነፃ እንድወጣ፣<br />

በዬትም ሀገር ያለፈው ትውልድ ድል የተቀዳጀበትን ስልት አሊያም ተነሳሽነት ይሔ<br />

ትውልድ መድገም ካቃተው ቀስ በቀስ የታሪክ ሞት ይከሰታል። የአንድ ተራ ሰው ሞት፣<br />

ከቤተሰቡና ወዳጆቹ አልፎ ለብሔራዊ ሐዘን የሚበቃበት ጉልበት የለውም። የታሪክ ሞት<br />

ግን ከሀገር አልፎ ጎረቤት ሀገሮችን ጨምር ለሐዘን ይዳርጋል።<br />

በደሳለኝ ስዩም<br />

“<br />

ከባህል፣ ከኑሮ፣ ከስልጣኔ ደረጃ<br />

ወዘተ የሚገኙ ትምህርቶችንም<br />

ይገልፃል።<br />

እንግዲህ ትምህርት የንቃተ-<br />

ኅሊና እና የበጎ አስተሳሰብ ምንጭ<br />

መሆኑን ከተስማማን፣ የትምህርት<br />

ምንጭም ከላይ የዘረዘርነው ሁሉ<br />

መሆኑን ከተስማማን ነገራችን<br />

ያለው “ከትምህርት” ይሆናል<br />

ማለት ነው።<br />

፩. ባሕላዊ ትምህርት<br />

በመሠረቱ ባህላዊ ትምህርት ስል<br />

የየባህሉ፣ የየሚዛኑ፣ የየሰፈሩ፣<br />

የየሃይማኖቱ ወዘተ ታሪኮች፣<br />

አፈ-ታሪኮች፣ እንቆቅልሾች፣<br />

የልጆች ጨዋታዎች፣ አለባበሶች፣<br />

ሰላምታዎች፣ እንቅስቃሴዎች፣<br />

ዜማዎች ወዘተ ሁሉ<br />

ያጠቃልላል።<br />

አንድ ዜጋ በስብዕና ደረጃ<br />

የተሟላና በአወንታዊነት<br />

የበለፀገ ሞራል መላበስ ይችል<br />

ዘንድ ከመነጨበት ማኅበረሰብ<br />

ውስጥ ያሉ ባህላዊ ትምህርቶች<br />

ያስፈልጉታል። ያለዚያ የማንነት<br />

ቀውሱ ከዚሁ ከልጅነቱ ጀምሮ<br />

ይጠናወታል።<br />

በእያንዳንዱ ባህላዊ ትምህርት<br />

ውስጥ እንዴት መልካም ስብዕናን<br />

ማጎልበት እንደሚችል በቀጥታም<br />

ይሁን በተዘዋዋሪ ትምህርቶችን<br />

ያገኛል።<br />

እነዚህን ባህላዊ ትምህርቶች<br />

በነፃነት አግኝቶ የማደግ አጋጣሚው<br />

በጠበበ ቁጥር ማን ነህ? ከየት<br />

የሌላ (ሀገር) ሰው ደም የሚፈስ<br />

አሊያም ጥይት የሚፈነዳ ከሆነ<br />

የነፃነት ጣዕም ሳይገባኝ ነው<br />

የምኖረው።<br />

በራሴ ፍላጎትና<br />

ተነሳሽነት ነፃነቴን እና መብቴን<br />

ካልጨበጥኩ፣ ሌላ ወገን<br />

ያስጨበጠኝን ነፃነት በቀላሉ<br />

ለማንም አሳልፌ የምሰጥ ተራ<br />

ሰው እሆናለሁ። ምክንያቱም፣<br />

ለነፃነቴ ዋጋም ሆነ ግብር<br />

አልከፈልኩበትምና።<br />

ሌሎች በልካቸው<br />

አስጠብበው የሚሰጡንን<br />

የነፃነት ካባ መልበስ፣ ሕይወት<br />

በምትፈቅደው አቅጣጫ ሁሉ<br />

አለመንቀሳቀስ ማለት ነው።<br />

የቻይና የነፃነት ካባ፣ ለኢትዮጵያ<br />

ይጠባታል ወይም ያጥራታል<br />

አሊያም ይሰፋታል። ስለዚህ ካባው<br />

የተመጣጠነ እንዲሆን ሲንጀሩ<br />

(ፍላጎቱና ተነሳሽነቱ) የራስ መሆን<br />

አለበት።<br />

ዜጎች፣ ራሳቸውን<br />

ነፃ ማውጣት እንደሚችሉ<br />

ካመኑ፣ ለታመነው የነፃነት<br />

መጀመሪያ የራሳቸውን ፊሽካ<br />

ይነፋሉ፤ አሊያም ነፃነታቸውን<br />

ለቀሙት ገዢዎቻቸው ወደው<br />

ሳይሆን ተገደው (ተረግጠው)፣<br />

ለማያምኑበት ሕግ ታምነው<br />

ይኖራሉ።<br />

የነፃነት ፀሐይ እንደ<br />

ተፈጥሮ ፀሐይ በምስራቅ በኩል<br />

ብቻ አትገኝም። የሰው ልጆች<br />

ባሉበት በአራቱም አቅጣጫዎች<br />

አለች። ነፃ መሆን የሚፈልጉ<br />

ሰዎች ፀሐይቱን የማያወጧት<br />

ከሆነ፣ ለረዥም ዘመናት በጨለማ<br />

ውስጥ ለመኖር በራሳቸው ላይ<br />

እንደፈረዱ ማወቅ አለባቸው።<br />

ተፈጥሮ በነፃ<br />

የሰጠችውን ነፃነቱንና መብቱን<br />

በየስርቻው ለማርመጥመጥ<br />

ነህ? ወዴት ነህ? ወዘተ ለሚሉ<br />

ጥያቄዎች ቀጥተኛና አወንታዊ<br />

መልስ መስጠት የማይችል ብኩን<br />

ዜጋ እየበረከተ ይመጣል።<br />

በዚህ ደረጃ የምስራቅ ሀገራት<br />

/ቻይና፣ ጃፓን፣ ህንድ/ በጎ<br />

ምሳሌ መሆን የሚችሉ<br />

ይመስለኛል። ዘመናቸው<br />

እየረቀቀ፣ ቴክኖሎጂያቸው<br />

እየመጠቀ ቢመጣም እንኳ ባህላዊ<br />

ትምህርቶቻቸው እንደ ተጠበቁ<br />

የልጆች ማሳደጊያ ናቸው።<br />

ሰላምታ፣ አለባበስ፣ አመጋገብ፣<br />

ስፖርታዊ እንቅስቃሴአቸው ሁሉ<br />

ለዚህ ማሳያ ሊሆን ይችላል።<br />

ባንፃሩ ገና ታድጋለች ብለን<br />

በመንጠብቃት ሀገራችን ግብረ-ወጥ<br />

የሆኑ የሰለጠኑ የሚመስሉ ግን<br />

የሰየጠኑ ልማዶች እንደፋሽስት<br />

ወረዋት ባህላዊ ትምህርቶቿ<br />

የአላዋቂነት መገለጫ ሆነው<br />

መቆጠር ጀምረዋል።<br />

እስኪ አዲስ አበባ ውስጥ ለልጆቹ<br />

ኢትዮጵያዊ ተረት እየነገረ ባህሉን<br />

እያስተማረ ልጀቹን የሚያሳድግ<br />

ወላጅ ምንያክል ይሆናል?<br />

መሠረታዊ እና ታላቁ የሞራል<br />

ቀውስ ከዚህ ይጀምራል።<br />

፪. ዘመናዊ ትምህርት<br />

ባለንበት የሉላዊነት ዘመን /<br />

ዘመነ ግሎባላይዜሽን የዘመናዊ<br />

ትምህርት መስፋፋት የስልጣኔና<br />

የሳይንስ ምንጭ ተደርጎ<br />

ይወሰዳል። በመሆኑም ይህንን<br />

ዘመናዊ ትምህርት ለማስፋፋት<br />

ብዙ ጥረት ይደረጋል።<br />

ዘመናዊ ትምህርት ብዙ አማራጭ<br />

የኑሮ ዘዴዎችን፣ አቋርጭ የኑሮ<br />

መስመሮችን ውበትንና ስልትን<br />

የተላበሱ የአኗኗር ልማዶችን<br />

ለማበጀት ይጠቅማል።<br />

“ሰው ማኅበራዊ እንስሳ ነው”<br />

የሚለውን ፍቱንነቱ ያልተረጋገጠ<br />

አባባል ውድቅ ሊያደርጉ የሚችሉ<br />

ፍቱን ስልጣኔዎችን ያመጣል -<br />

ዘመናዊ ትምህርት።<br />

አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />

መልካም ዓዲስ ዓመት<br />

የሚነሳሳበትን ኃይል በመመከት<br />

ራሱን በራሱ ነፃ ማውጣት አለበት<br />

- ማንኛውም ዜጋ።<br />

አንድ ኢትዮጵያዊ<br />

ሰው ኢትዮጵያ ውስጥ ያገኘውን<br />

መብትና ነፃነት ማስከበር ያለበት<br />

በኢትዮጵያ መፈክር እንጂ በራስ<br />

ወዳዶች የጥቀመኝ ልጥቀምህ<br />

ፖሊሲ አይደለም።<br />

ኢትዮጵያውያን፣ በሰበብ<br />

አስባቡ በፖለቲካ ደዌ የሚገመት<br />

ነፃነታቸውን የሚያክሙላቸው<br />

የባንኮክ ስፔሻሊስቶች አይደሉም።<br />

የስኳር ታማሚ ወደ ታይላንድ<br />

ሊላክ ይችላል። የነፃነት በሽተኛ<br />

(በቂ ነፃነት የሌለው) ኢትዮጵያዊ<br />

ሪፈር የሚያደረገው ግን ወደ<br />

አድዋ ተራራ ነው።<br />

በተራራው ስር<br />

የተከናወነው የነፃነት ተጋድሎ<br />

የልብ ልብ ስለሚሰጥ፣ ዛሬ<br />

ነፃነት የጎደላቸው ወይም<br />

ነፃነታቸውን የተቀሙ ዜጎች<br />

ያለፈው ታሪካቸውን ሊጠቀሙበት<br />

ይችላሉ። የትላንት የድል ታሪኮች<br />

ተመዝግበው የሚቀመጡት የዛሬ<br />

ሰዎች ከሚደነቀርባቸው ፈተናዎች<br />

የሚያመልጡበትን መንገድ<br />

ለማመላከት ጭምር ነው።<br />

ሰዎች ነፃነት አልባ<br />

የሚሆኑት፣ ፖለቲካ ጨጓራ<br />

በሽታ የሚሸመትበት የህመም ገበያ<br />

ሲሆን ነው። የገዢዎች የፖለቲካ<br />

አካሔድ መዳረሻውና ዓላማው<br />

ሀገርን ወደተሻለ አንድነትና<br />

ዕድገት ማድረስ ከሆነ ማንም ሰው<br />

ፈሪ አይሆንም። ደግሞም ፖለቲካ<br />

ሀገርን ከማልማት ውጭ ሌላ<br />

ዓላማ ሊኖረው አይገባም።<br />

አንዳንድ ጊዜ፣<br />

የፖለቲካ ትርጉም ያልገባው<br />

ፖለቲከኛ በልጅነቱ የመታውን<br />

ጉልቤ ዛሬ አስታውሶ ለማሰር፣<br />

ሥልጣኑን ተጠቅሞ አፈንጋጭ<br />

ባንፃሩ ቅደም ተከተሉ ተጠብቆ<br />

አለማና ግቡ ተለይቶ ግልፅና<br />

ሊዳሰስ የሚችል ሆኖ ትምህርቱ<br />

መስፋፋት ካልቻለ በተቀራኒው<br />

ኪሳራን ውድቀትን ሊያመጣ<br />

እንደሚችል የታመነ ነው።<br />

በትምህርት ስርአት ውስጥ<br />

የመጀሪያም የመጨረሻም አላማና<br />

ግብ ቢኖር የሰውን ልጅ አእምሮ<br />

ማልማት እንጂ ቁስ አካላዊነትን<br />

ማስፋፋት አይደለም።<br />

የዘመናዊ ትምህርት አላማ ሊሆን<br />

የሚገባው በጎ ስብዕና መላበስን<br />

ሰብአዊነትን ርህራሄን አሳቢነትን<br />

ቅንነትን በጠቅላላው በሞራል<br />

መበልፀግን ማስቻል ነው።<br />

ገንዘብ ማግኘት መኪና መግዛት<br />

ቤት መስራት ጠፈር ላይ<br />

መዝናናት ወዘተ በተደራቢነት<br />

ማለትም የሞራል ግንባታው<br />

እየተካሄደ ሞራሉ የበለፀገ ሰው<br />

የሚሰራው እንጂ እንደመጀመሪያ<br />

አላማ ተደርጎ በዘመናዊ ትምህርት<br />

ውስጥ ከተቀመጠ ጥፋቱ ብዙ<br />

ነው።<br />

ቁጥር መደመር መቀነስ የጦር<br />

ስትራቴጅ መቀየስ የንድፈ ሐሳቦችን<br />

ሽኩቻ መቀላቀል ገንዘብን ማጋበስ<br />

ቅድሚያ አለማዎቹ ከሆኑ ዘመናዊ<br />

ትምህርት የሚያፈራው ሞራሉ<br />

የዘቀጠ ዜጋ ብቻ ይሆናል። ራስ<br />

ወዳድነት ጨካኝነት የሀገር ፍቅር<br />

ማጣት ወዘተ ይነግሳሉ።<br />

በመሆኑም ከእያንዳንዱ የሳይንስና<br />

የቁጥር ትምህርት በቅድሚያ<br />

ግብረ-ገባዊነት (ኤቲካል) ሥነ-<br />

ልቦናዊ /ሳይኮሎጂካል/ ትህርቶች<br />

ቅድሚያ ሊሰጣቸው ይገባል።<br />

፫. ሃይማኖታዊ<br />

ትምህርቶች<br />

የሰው ልጅ በተፈጥሮው<br />

የአማኝነት ባህርይን የታለበሰ<br />

ነው። በዚህ ማመኑ ውስጥ ያሉ<br />

ስርዓቶችን ህገ ደንቦችን እና<br />

የአኗኗር ዘይቤዎችን ማክበር<br />

ህግ የሚያወጣ ይመስለኛል።<br />

አንዲት ሀገር ያለ<br />

በቂ ነፃነት መኖር ትችላለች<br />

የሚል ፖለቲከኛ በተዘዋዋሪ፣<br />

ያለ ፓራሹት ከአውሮፕላን ላይ<br />

መዝለል እችላለሁ እያለ መሆኑን<br />

ማወቅ አለበት።<br />

በተለይ፣ ባለፉት<br />

ዘመናት ለነፃነትና ለመብት ትልቅ<br />

ቦታ ይሰጡ የነበሩ ህዝቦች፣ ዛሬ<br />

ዛሬ ነፃነታቸው አጣብቂኝ ውስጥ<br />

ሲገባ ‹ዝም› ካሉ ከታሪካቸው<br />

ጋር እየተጣሉ ነው ማለት ነው።<br />

አሊያም የነፃነታቸውን ታሪክ<br />

በገዛ ፈቃዳቸው ገንዘብ ለመቅበር<br />

እየተዘጋጁ ነው።<br />

በዬትም ሀገር ያለፈው<br />

ትውልድ ድል የተቀዳጀበትን ስልት<br />

አሊያም ተነሳሽነት ይሔ ትውልድ<br />

መድገም ካቃተው ቀስ በቀስ የታሪክ<br />

ሞት ይከሰታል። የአንድ ተራ ሰው<br />

ሞት፣ ከቤተሰቡና ወዳጆቹ አልፎ<br />

ለብሔራዊ ሐዘን የሚበቃበት<br />

ጉልበት የለውም። የታሪክ ሞት<br />

ግን ከሀገር አልፎ ጎረቤት ሀገሮችን<br />

ጨምር ለሐዘን ይዳርጋል።<br />

ምክንያቱም ብዙ ሀገሮች ነፃነት<br />

ያገኙት ከጎረቤቶቻቸው የነፃነት<br />

ታሪክና እንቅስቃሴ ልምድ ወስደው<br />

ነው።<br />

ዜጎች፣ በየወቅቱ<br />

ለሚያስመዘግቡት የነፃነት ድል<br />

ሻማ ሲያበሩ ደስ ይላል። ነገር<br />

ግን ነፃ መሆን አቅቷቸው ያለፈው<br />

ወገናቸው ያስመዘገበውን ድል<br />

ለመዘከር ‹ብቻ› ሻማ የሚያበሩ<br />

ከሆነ ደስ አይልም።<br />

አንድ ትውልድ በገነባው<br />

የታሪክና የድል ማማ ላይ ሰላሳና<br />

አርባ ትውልድ እየወጣ ሊሸልልና<br />

ሊምነሸነሽ አይገባም። ሁሉም<br />

ትውልድ የየራሱን ታሪክና ድል<br />

ማስመዝገብ አለበት። ያለበለዚያ<br />

‹‹የድል ታሪክ ማስመዝገብ<br />

ያቃታቸው ትውልዶች እኚህ<br />

ነበሩ›› ከሚል ጥቅስና የፎቶ<br />

ኤግዚቢሽን የሚያመልጥ ሰው<br />

አይኖርም።<br />

የድል ታሪክ፣ መኪና<br />

በመንዳትና ትላልቅ ቤቶችን<br />

በመስራት የሚከሰት /የሚመዘገብ<br />

የሚመስላቸው ደሀ ሰዎች፣ ሽሮ<br />

እየበሉ ጮማ ታሪክ ማስመዝገብ<br />

እንደሚችሉ ሊያውቁና ሊያምኑ<br />

ይገባል።<br />

ለሞራል ዝቅጠት ተጠያቂው ማን ነው?<br />

<strong>መንግስት</strong> ወይም መንግስታዊ አሰራር በባህላዊና በሃይማኖታዊ<br />

ጉዳዮች መደናገሩ ቀርቶ ይልቁንም ዘመናዊ ትምህርትን ሊሆን<br />

በሚገባው መልኩ ማስፋፋት ከተቻለ ሁሉም ሰላም ይሆናል<br />

ደግሞ ያስደስተዋል።<br />

በዓለም ያሉ ሃይማኖቶች<br />

በዝርዝር ጉዳዮችና በአንዳንድ<br />

መሰረታዊ ነጥቦች ይለያዩ እንጂ<br />

የጋራ መገለጫዎቻቸው የሆኑ ብዙ<br />

ነጥቦች አሉ። ከእነዚህም ውስጥ<br />

ሰላማዊ መሆን፣ ፍቅር መሰጠት፣<br />

ግብረ-ገባዊ መሆን፣ ለደንቦች<br />

መገዛት ወዘተ ይጠቀሳሉ።<br />

የአንድ ዜጋ ሞራል የበለፀገ<br />

ይሆን ዘንደ አስተሳሰቡም<br />

በአወንታዊነት የተቃኘ ይሆን<br />

ዘንድ ሃይማኖታዊ ትምህርቶች<br />

ታላቅ አስተዋጽኦ አላቸው። አንድ<br />

ሀገር፣ የአንድ ሀገር ህዝብ ወይም<br />

የአንድ ሀገር <strong>መንግስት</strong> ከአንድ<br />

ዜጋ የሚፈልጉትን አስተዋፅኦ<br />

ሊያገኙ የሚችሉት ዜጋው<br />

ከመሠረቱ በተስተካከለ የሞራል<br />

መሠረት ላይ የቆመ ሲሆን ነው።<br />

ባንፃሩ ሃይማኖቶች ለእውነታዊነት<br />

ይህንን ያክል ተፅኖ ያላቸው<br />

የመሆናቸውን ያክል ለጥፋትም<br />

ይህንኑ ያክል ተፅኖ ይኖራቸዋል።<br />

መከፋፈልን፣ ዘረኝነትን፣<br />

ወገናዊነትን፣ ግላዊነትን መስበክ<br />

የየሃይማኖቶች የዕለት ከዕለት<br />

ተግባር ከሆነ የዜጎች የሞራል<br />

ኪሳራ ቃላት የማይገልጠው<br />

ይሆናል።<br />

በእርግጥ የአንድ ሀገር ዜጎች<br />

የሞራል ግንባታ ሥርዓቱን ሁሉ<br />

በእጁ የያዘው <strong>መንግስት</strong> ላይ<br />

ይንጠልጠል እንጂ አስተዋጽኦው<br />

የሁሉም ነው።<br />

በመሆኑም <strong>መንግስት</strong> ወይም<br />

መንግስታዊ አሰራር በባህላዊና<br />

በሃይማኖታዊ ጉዳዮች መደናገሩ<br />

ቀርቶ ይልቁንም ዘመናዊ<br />

ትምህርትን ሊሆን በሚገባው<br />

መልኩ ማስፋፋት ከተቻለ ሁሉም<br />

ሰላም ይሆናል።<br />

ሰላም ለእናንተ!


አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />

መልካም ዓዲስ ዓመት<br />

በአናንያ ሶሪ<br />

“<br />

በአብርሃም ተስፋዬ<br />

“<br />

ከቀደመው ዘመን አንስቶ<br />

እስካሁን ስለግሪክ ፍልስፍናዎች<br />

ይነገራል። የግሪክ ህዝቦች በክርክርና<br />

በውይይት ከፍተኛ እምነት<br />

እንደነበራቸው ይወሳል። ለዚህም<br />

ይመስላል በርካታ ፍልስፍናዎች<br />

ከምድረ-ግሪክ መነሳታቸው።<br />

የፍልስፍናዎቹ መነሻ ደግሞ እኒሁ<br />

የአመለካከት ልዩነቶች እንደሆኑ<br />

ይታመናል። ናቸውም። በልዩነቶች<br />

ውስጥ የሚፋጭ እውነት ይኖራል።<br />

በልዩነቶች ውስጥ ማመንና ማሳመን<br />

ይኖራል። በልዩነቶች ውስጥ<br />

የሚወጡ የሚወርዱ ጉዳዮች<br />

ይኖራሉ። በዚህ መሀከል ደግሞ<br />

የበሰለ ነገር ይገኛል።<br />

በግሪክ የነበሩ ፈላስፎችም<br />

ታዲያ በአመለካከቶቻቸው ዙሪያ<br />

ይወያዩ ይከራከሩ እንደነበር ይነገራል።<br />

በተለይም ህዝብ ወደተሰበሰበበት<br />

ቦታ በመሄድ አመለካከቶቻቸውን<br />

ያንጸባርቃሉ። እነዚህ አመለካከቶች<br />

በደንብ ይብላላሉ። ህዝቡም<br />

የወደደውን፣ ያመነበትን ይቀበላል።<br />

ለነገሩ እነዚህ<br />

የአመለካከት “አባቶች” ስላመኑበት<br />

አተያይ በአደባባይ በድንጋይ<br />

ተወግረዋል፤ ስለእምነታቸው<br />

በአደባባይ ተሰቅለዋል፤ ተገቢ ነው<br />

ላሉት ምልከታ ከህዝብ መሀከል<br />

እንደ ባዕድ ተቆጥረዋል፤ “የለም!<br />

እንዲህ ነው” ብለው ለማሳመን በጣሩ<br />

“አብደዋል፣ አቅላቸውን ስተዋል”<br />

ተብለዋል፤ ስለአመለካከታቸው<br />

የሚደርስባቸውን አሜን ብለው<br />

ተቀብለዋል።<br />

ትናንት ከትናንት ወዲያ<br />

የተገፉትን የአመለካከት ባለቤቶች፤<br />

ዛሬ የመርህ ሁሉ መነሻ፤ የተግባር<br />

ሁሉ መዳረሻ እነርሱ እንደሆኑ<br />

እናነሳለን። ዓለምም ያወድሳቸዋል።<br />

“እከሌ እንዳለው” እያልን ያን ጊዜ<br />

ህዝቡ ያልተቀበለውን አመለካከት<br />

ለእራሳችን እምነት ማስኬጃ<br />

እንደመጀመሪያ ምዕራፍ አድርገን<br />

እንነሳለን። ዛሬ ላይ ስለበርካቶቹ<br />

ስናነሳም “ከጊዜያቸው ቀድመው<br />

የተፈጠሩ” እስከማለት እንደርሳለን።<br />

ስለኢትዮጵያ ስናነሳ ስለአጼ<br />

ቴዎድሮስ እንደምናነሳው ሁሉ።<br />

እኔ ግን በዚህ<br />

አልስማማም። ማንም ፍጡር<br />

ወደዚህ ምድር በጊዜው ይመጣል።<br />

ለዛውም መምጣት ባለበት ጊዜ።<br />

ባይሆን ኖሮ የግሪክ ፈላስፎችንም፤<br />

ኢትዮጵያውያኑንም ጀግኖች<br />

አናያቸውም ነበር። ለነገሩ<br />

ስለፍልስፍናዎቹ መነሻ ሲነሳ<br />

የፈላስፎቹ አመለካከት ይነሳል።<br />

ክርክራቸው ልዩ ነው። እርስበእርስ<br />

ለመተማመን የማይፈነቅሉት<br />

ድንጋይ የለም። ነገር ሲመረምሩ<br />

ይከርማሉ። ብዙም ነገር ይፈትሻሉ።<br />

ምክንያቱን ለህዝቡ የሚያቀብሉትን<br />

ነገር በቅድሚያ ሊያምኑበት<br />

እንደሚገባ ጠንቅቀው ያውቃሉ።<br />

ይህንን ሳያደርጉ ወደህዝብ /<br />

መድረክ/ ብቅ ማለት የማይታሰብ፣<br />

እንደውርደትም ተደርጎ የሚቆጠር<br />

ነገር ነው። ስለሆነም ከባድ ኃላፊነት<br />

እንዳለባች ያስባሉ። ከዚህ ሁሉ<br />

ዝግጅት በ|ላ ታዲያ የሚሆነው<br />

እንዲሆን ከመድረኩ ብቅ ይላሉ<br />

- የአቴና የድሮ ልጆች። ክብbን<br />

ዳግም ለዘመናት እያስጠሩ ይኸው<br />

ዛሬም ድረስ በየመዛግብቱ ሰፍረው<br />

ይታያሉ። በርካታ ፍልስፍናዎች<br />

ከዚህች የአመለካከት ልዩነቶች<br />

ሲስተናገዱባት ከነበረች ምድር ከተፍ<br />

ብለዋል።<br />

በኢትዮጵያም በርካቶች<br />

ስለአመለካከታቸው ብዙ ዋጋ<br />

ከፍለዋል። ቀድሞ በተማሪዎች<br />

ንቅናቄ ውስጥ ከፍተኛ እንቅስቃሴ<br />

የነበራቸው፤ የዚያ ዘመን ሰዎች<br />

ስማቸው ዛሬም ይጠቀሳል። በርካቶቹ<br />

ዛሬ ላይ ሆነን ትንቢት ተናጋሪ አይነት<br />

እንደነበሩ መገመት አያቅተንም።<br />

ግን ብዙዎችን አጥተናል። እንዲህ<br />

ያሉትን ትንቢተኞች በማጣታችን<br />

ደግሞ እነርሱ ስለአመለካከታቸው<br />

ከከፈሉት ዋጋ በላቀ፣ ኢትዮጵያ<br />

እነርሱን ስላጣች የከፈለችው<br />

እንደሚብስ እሙን ነው።<br />

እንደኢትዮጵያ ባለ ሀገር<br />

ደግሞ የአመለካከት ልዩነቶች ሊኖሩ<br />

ግድ ነው። ይህንን ማስተናገድ<br />

ኮመንትሪ<br />

አሜሪካ ስለኢትዮጵያ ምን ታስባለች?<br />

የአሜሪካ <strong>መንግስት</strong> ስለኢትዮጵያ<br />

እና ስለገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ምን<br />

ያስባል? በፀረ ሽብርተኝነት ዘመቻው<br />

ውስጥ ኢትዮጵያን በምስራቅ አፍሪካ<br />

ያለች እውነተኛና አስተማማኝ<br />

አጋር አድርጎስ ያያታል? አልያስ<br />

ከኤርትራ፣ ሱዳን፣ ሶማሊያና<br />

ጅቡቲ ጋር ሲነፃፀር የተሻለ ወዳጅ<br />

ኢትዮጵያ ናት ከሚል የአቅርቦት<br />

እጥረት የተነሳ ሻል ካለው ጋር<br />

የመቀጠል አዝማሚያ ይሆን? ዋርካ<br />

በሌለበት አንቧጮ አድባር ይሆናል!<br />

እንዲል ተረቱ። የአሜሪካ <strong>መንግስት</strong><br />

ብሔራዊ ጥቅሙን ከማስጠበቅ<br />

አንፃርስ የጠ/ሚኒስትር መለስን<br />

አብዮታዊ ዲሞክራሲ እንዴት<br />

ይቃኘዋል? በተለይ ደግሞ ኢህአዴግ<br />

እከተለዋለሁ ከሚለው የቻይና ፈለግ<br />

እና ተዛማጅ የ<strong>መንግስት</strong> ጣልቃ-<br />

ገብ ፖሊሲዎቹ አኳያ፣ እንዲሁም<br />

የቻይና ኩባንያዎች በኢትዮጵያ<br />

ውስጥ ያለጨረታ እና ተፎካካሪ<br />

በ‹‹ድርድር›› ስለሚያገኙት ከፍተኛ<br />

የወታደራዊና የንግድ አትራፊ<br />

ሥራዎች አሜሪካ ምን ታስባለች?<br />

በዛሬው የዊክሊክስ ገመና አጋላጭ<br />

ጽሁፍ ውስጥ የተዘረዘሩት ጉዳዮች<br />

በዋናነት የሚያጠነጥኑት የአሜሪካ<br />

ኤምባሲና የአሜሪካ <strong>መንግስት</strong><br />

ስለኢትዮጵያ፣ ኢህአዴግ፣ እና<br />

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ያላቸው<br />

አመለካከት ምን እንደሚመስል<br />

በጥቂቱም ቢሆን ለመቃኘት<br />

በሚያስችል መልኩ ሲሆን ትንሽ<br />

ግርም የሚያሰኘው ነገር ቢኖር ግን ይህ<br />

ለአደባባይ የበቃ ገመና ስለኢትዮጵያና<br />

ገዢዎቿ ከሚናገረውም በላይ<br />

ወይም እኩል ስለአሜሪካ <strong>መንግስት</strong><br />

መንታ አካሄዶች እና የተሰላ ጥበባዊ<br />

አቀራረብ በመስመሮቹ መሐል<br />

ማንበብ ለሚችል ሁሉ የሚገልፀው<br />

አያሌ ምስጢራት ይዟል።<br />

አዎ እነዚህን ሁሉ ጉዳዮች በቅርበት<br />

እየተከታተለ ዋሽንግተን ለሚገኘው<br />

ነጩ ቤተ<strong>መንግስት</strong> (White House)<br />

ሪፖርት የሚያደርገው በኢትዮጵያ<br />

ያለው የአሜሪካ ኤምባሲ ሲሆን<br />

አብዛኞቻችን የማንገምተውን<br />

ነገር ግን ውስጥ ውስጡን ሲነገሩ<br />

የምንሰማቸውን የአደባባይ<br />

ሹክሹክታዎች የአሜሪካ ኤምባሲም<br />

ጭምር የሚጋራቸው የዲፕሎማሲክ<br />

ማህበረሰቡ የኮሪዶር ላይ ወጎች<br />

እንደሆኑ ስንቶቻችን እናውቅ<br />

ይሆን? ታዲያ እነዚህን የአሜሪካ<br />

ኤምባሲ አመለካከቶች፣ ትዝብቶች፣<br />

ምልከታዎች እና ግንዛቤዎች ለህዝብ<br />

ይፋ በማድረግ የሚታወቀው የድረ-<br />

ገፅ ገመና አጋላጭ ዊክሊክስ ሰሞኑን<br />

ባሰራጫቸው ቱባ ቱባ ሰነዶቹ<br />

የኢትዮጵያን <strong>መንግስት</strong> እብድ<br />

የጠ/ሚ/መለስን ያልተስተካከሉ እይታዎች ማረም ብንችልም፤<br />

እንዲሁም በሰብዓዊ መብት ሪፖርቱ ዙሪያ ለመወያየትና የታዩት<br />

ችግሮችን ለማረም ጥረት እያደረግን እንደሆነ ብናስታውቃቸውም፤<br />

አሁንም እየቀጠለ ያለው የእነዚህ ጉዳዮች መነሳት የጠ/ሚኒስትሩንና<br />

የመንግስታቸውን ጭንቀት ያመለክታል።<br />

አዳዲስ የዊክሊክስ መረጃዎች ይናገራሉ<br />

እብድ የሚያካክሉ ሚስጥራት ፀሐይ<br />

አስመትቷቸዋል።<br />

አሜሪካ የአቶ መለስን<br />

ልማት ‹‹ገድላዊ የኢኮኖሚ<br />

ዕድገት›› በማለት<br />

ገልፃዋለች<br />

ከሴናተር ኢንሆፍ እና ልዑካኖቹ<br />

ጋር በApril 7 ከተደረገ አጭር ስብሰባ<br />

በኋላ ጠ/ሚ መለስ አምባሳደሩን<br />

ነጠል አርገው ወደ ጎን ወሰዱና<br />

በግል ሦስት ጉዳዮችን አነሱላቸው።<br />

1ኛ) በስህተቶች የተሞላ ነው<br />

ብለው የሚያምኑበትን የስቴት<br />

ዲፓርትመንት የሰብዓዊ መብቶች<br />

ሪፖርት ‹‹ማሻሻል›› ስለማስፈለጉ<br />

2ኛ) የአሜሪካ ኤምባሲ<br />

የኢትዮጵያን ረቂቅ የፀረ-ሽብርተኝነት<br />

ህግ ለሂውማን ራይትስ ዎች አሳልፎ<br />

ሰጥቷል ስለሚባለው ውንጀላ እና<br />

3ኛ) የተፈጠሩትን አለመግባባቶች<br />

ለመፍታት እና የኢትዮ-አሜሪካ<br />

ግንኙነትን ለማዳበር በከፍተኛ ደረጃ<br />

ባለው እርከን የሁለትዮሽ ስብሰባዎች<br />

መካሄድ ስለማስፈለጉ ነበር።<br />

ከቅርብ ወራት ወዲህ የሚስተዋሉና<br />

የአሜሪካ <strong>መንግስት</strong> እርምጃዎችን<br />

ተከትለው እየባሰባቸው የመጡ<br />

መረር ያሉ የአቶ መለስ ምላሾች<br />

በርግጠኝነት የሚመነጩት የኦባማ<br />

አስተዳደር ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን<br />

ግንኙነቱን በምን መልኩ ይቃኘው<br />

ይሆን? ከሚል የመንግስታቸው<br />

ጭንቀት ነው።<br />

ከዚሁ ጋር በተጓዳኝ የጠቅላይ<br />

ሚኒስትሩ ምክንያተ-ቢስ ግትርነት<br />

የሚንፀባረቅባቸው የብርቱካን<br />

ጉዳይ፣ የመ.ያ.ድ.ዎች ህግ፣ ገድላዊ<br />

የኢኮኖሚ ዕድገትና የኢትዮጵያ<br />

የሰብዓዊ መብት አያያዞች ከብዙ<br />

በጥቂቱ ለመጥቀስ መንግስታቸው<br />

አገሪቱን በአሁን ሰዓት እያለፈችባቸው<br />

ባሉ ጉዳዮች ላይ ከአሜሪካ ፖለቲካ<br />

እና ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች እንዲሁም<br />

እሴቶች በተፃራሪ የቆመን የመከላከያ<br />

ስለአመለካከት ልዩነት<br />

የሚከፈል ዋጋ እስከምን?<br />

የውዴታ ግዴታ ይሆናል። ተወደደም<br />

ተጠላ እንደብዛታችን ልዩነታችንን<br />

ተረድቶ አስተሳሰባችንንም<br />

እንድናራምድ የሚፈቅድ አይነት<br />

ምህዳር ያስፈልጋል። ከምንም ነገር<br />

በላይ በአንድ እሳቤ ከመታጠር<br />

የተሻለ እንደሆነም ይታየኛል።<br />

ዛሬ ግን ይህንን<br />

የሚያበረታታ ነገር መመልከት ከባድ<br />

እንደሆነ ይሰማኛል። ስለበርካታ<br />

ጉዳዮች ለመወያያትም የሚሻ ማግኘት<br />

ከባድ እየሆነ ነው። በመሠረቱ<br />

በዚህ ረገድ የትምህርት ማዕከላት<br />

የሚጫወቱት ሚና ከምንምና<br />

ከማንም ይልቃል። ልዩነቶች<br />

እንዲስተናገዱ እድሉንና መንገዱን<br />

ሁሉ ማመቻቸት፣ በልዩነቶቹ<br />

ውስጥ የሚንቀለቀሉ እሳቤዎችን<br />

እንዲፋፋሙ፣ ሌሎችም ያሻቸውን<br />

እንዲመርጡና እንዲቀበሉ። የሀሳብ<br />

አቅራቢዎቹም ምልከታ በተደራጀ<br />

መልኩ እንዲቀመጥ ማስቻል<br />

ይጠበቅባቸዋል - የትምህርት<br />

አምባዎቻችን።<br />

እንዲህ ያሉ ሀሳባቸውን<br />

እንዳሻቸው መግለጽ የሚችሉና<br />

የሚፈልጉ፣ ብሎም የሚደፍሩ<br />

ዜጎችን ለማፍራት ደግሞ ተsማቱ<br />

መድረኮችን መፍጠር ይኖርባቸዋል።<br />

መድረኩን ከመፍጠርም ባሻገር<br />

እንዲህ ያሉትን ዜጎች /ግለሰቦች/<br />

ማወደስ ያስፈልጋል። ዕውቅናም<br />

ሊቸራቸው ግድ ነው። ጠቃሚና<br />

አሳማኝ አጀንዳ ይዞ ለሚመጣ<br />

ማንኛውም ዜጋ በአንድም ይሁን<br />

በሌላ፣ ብቻ ማኅበረሰቡን የሚጠቅም<br />

ነገር እስከሆነ ድረስ፤ ማኅበረሰቡ<br />

በአንድ አይነት አጀንዳ ላይ ብቻ<br />

ማተኮር አለበት ከሚል ብሒል<br />

ተላቀን፣ የሌሎችንም ምልከታ<br />

ጠቀሜታ ሊኖረው ይችላል ብሎ<br />

ማሰብ በጣም ጠቃሚ ይመስለኛል።<br />

በማንኛውም ነገር<br />

ላይ የሚነሱ ሀሳቦች በምሁራን<br />

ውይይቶች ቢዳብሩ፤ ሀገራዊ የሆኑ<br />

አጀንዳዎች ላይም ልዩነቶች ቢኖሩ<br />

እንኳን የልዩነቶቹን መነሻ ለህዝቡ<br />

በደንብ በማሳየት ህዝቡም እንዲወያይ<br />

ግንብ እየገነባ እንደሆነ አመላካች<br />

ነው። በመሆኑም ልክ የአፍሪካ<br />

ጉዳዮች ረዳት ፀሐፊ እንደተመደበ<br />

በከፍተኛ ደረጃ ባለው እርከን (senior<br />

level) የሁለትዮሽ ስብሰባዎች<br />

እንዲካሄዱ አሁንም እናሳስባለን።<br />

ይህ እርምጃ የኢትዮጵያን ጭንቀቶች<br />

ጋብ ለማድረግ ከመርዳቱም በላይ<br />

ያሳሰቡንን ጉዳዮች አፅንኦት ለመስጠት<br />

እና ለግንኙነቱ የምንሰጠውን ድጋፍ<br />

ለማጠናከር ይረዳል።<br />

አሜሪካ ኢትዮጵያን<br />

እንደአስፈላጊ አጋር<br />

አታያት ይሆን?<br />

የጠ/ሚ/መለስን ያልተስተካከሉ<br />

እይታዎች ማረም ብንችልም፤<br />

እንዲሁም በሰብዓዊ መብት ሪፖርቱ<br />

ዙሪያ ለመወያየትና የታዩት<br />

ችግሮችን ለማረም ጥረት እያደረግን<br />

እንደሆነ ብናስታውቃቸውም፤<br />

አሁንም እየቀጠለ ያለው የእነዚህ<br />

ጉዳዮች መነሳት የጠ/ሚኒስትሩንና<br />

የመንግስታቸውን ጭንቀት<br />

ያመለክታል። ይህም አሜሪካ<br />

በኢትዮጵያ ላይ ያላት አቋም<br />

እየጠነከረና እየባሰ ይሄድ ይሆን?<br />

ከሚል እና አሜሪካ ከእንግዲህ<br />

ኢትዮጵያን በቀጠናው እንዳለ ወሳኝ<br />

አጋሯ አድርጋ ላታያት ትችል<br />

ይሆናል ከሚል ጭንቀት የሚመነጭ<br />

ነው።<br />

አቶ መለስ ከዚህ የተሻሉ<br />

መልካም ግንኙነቶችን እንደሚሹ<br />

ግልፅ ቢሆንም እነዚህ የሁለትዮሽ<br />

ግንኙነቶች ግን በርሳቸው መርህዎች<br />

እንዲመሠረቱና ኢትዮጵያ የሰብዓዊ<br />

መብቶችን፣ ዴሞክራሲን ብሎም<br />

የኢኮኖሚ ልማትን በራሷ የፖሊሲ<br />

ግቦች ተመስርታ በምታካሂድበት<br />

ወቅት አሜሪካ ለአገራቸው<br />

የመተናፈሻ እና የመፈናፈኛ ቦታ<br />

እንድትሰጣት ይፈልጋሉ።<br />

ማድረግ ተገቢ ነው።<br />

<strong>መንግስት</strong>ም ቢሆን<br />

እንዲህ ላለው ነገር ትኩረት ሊሰጥ<br />

ግድ ነው። ሁሌም አንድ ዓይነት<br />

አስተሳሰብና አመለካከት ይዘን<br />

እስከመቼ፤ እንዴትስ እንÕዛለን?<br />

የነገዋን ኢትዮጵያ የሚረከበው ዜጋ<br />

ዛሬ ላይ ባላንሸራሸረው አስተሳሰቡ<br />

ነገን ማየት ይቻለዋልን? እውነት<br />

ኢትዮጵያስ ህዳሴዋ እንዲሰምር<br />

አማራጮች አያሿትም? እና ሌሎችም<br />

ጥያቄዎች በውስጤ ይመላለሳሉ።<br />

ምንም እንኳን እንደ<br />

ግሪኮቹ ህዝብ ሰብስበን የምንወያይበት<br />

ቦታ ባይኖርም፣ ሁኔታዎችን ግን<br />

ማመቻቸት ተገቢም አስፈላጊም<br />

ነው። ብዙ ጊዜ እንደውም ከዚሁ<br />

የራስን አመለካከት በነጻነት ከመግለጽ<br />

ጋር በተያያዘ በተለይም ከመንግሥት<br />

ወገን ነን የሚሉት ግለሰቦች ቃላቸው<br />

አንድ አይነት እየሆነ አግራሞት<br />

ይፈጥርብኛል። ከላይ በመንግሥት<br />

የሥልጣን መዋቅር ውስጥ ያሉት<br />

ምናልባትም በውይይት ወቅት<br />

ልዩነቶቻቸውን እያነሱ ይማEገቱ<br />

ይሆናል። ይሆናል ነው ያልኩት።<br />

ከዚህ ባለፈ የማስፈጸም ጉዳይ<br />

እያነሱ ምላሽ ይሰጡ ይሆናል።<br />

ሌላውን “ወገን ነኝ” ባይ ግን ምን<br />

ይሉታል?<br />

መግባባት እየቻልን<br />

አይደለም። መደማመጥ አቁመናል።<br />

የምናነሳውን ሀሳብ ለማስረዳት<br />

ሳይሆን ለማዘዝ ይቀናናል። የተለየ<br />

ነገር ለመቀበል ዝግጅቱ ያንሰናል።<br />

ለነገሩ ልዩነት ያለው ነገር<br />

የሚያመጣም ከጠፋ ሰንበት እያለ<br />

ነው። ለዚህ ደግሞ በልዩነት መÕዝ<br />

አለመቻላችን ወይም አለመፈለጋችን<br />

በምክንያትነት ሊጠቀስ ይችላል።<br />

በእርግጥም ልዩነቶችን<br />

ያለማስተናገዳችን ነገር ዋጋ<br />

እያስከፈለን ነው። “የተለየ ሀሳብ<br />

አለን” ያሉ ዜጎችም በየዘመኑ<br />

አጥተናቸዋል። መሪዎቻችንም<br />

እንደልዩ ፍጡር እያዩዋቸው ዳግም<br />

እንዳይደርሱባቸው አርቀዋቸዋል።<br />

ትንቢት ተናጋሪ ምርጥ ዜጎች<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

7<br />

አቶ መለስ የአሜሪካ<br />

ፖሊሲ እንዲቀየር<br />

ተፅዕኖ ለመፍጠር<br />

ሞከሩ<br />

ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ በFebruary 25<br />

አምባሳደሩን ጠርተው በኢትዮጵያ<br />

እይታ አሜሪካ ከጋራ ዓላማቸው<br />

ውስጥ ከተካተቱት ከክልላዊ<br />

መረጋጋት፣ ፀረ ሽብርተኝነት እና<br />

ከልማት ጉዳዮች ይልቅ ለሰብዓዊ<br />

መብቶች የበለጠ ትኩረት በመስጠት<br />

ጠንከር ያለ የፖሊሲ ለውጥ<br />

እያደረገች እንደሆነ እንደሚሰማቸው<br />

ገለፁ። ይህ አባባል የውጭ ጉዳይ<br />

ሚኒስትር አቶ ስዩም በ February<br />

20 ለአምባሳደሩ የተናገሩትን<br />

የቃላት ተቃውሞ የሚያጠናክር<br />

ነበር። አቶ ስዩም የአሜሪካ ኮንግረስ<br />

ኢትዮጵያን ልማትና መሰል እርዳታ<br />

ከማግኘታቸው በፊት የኮንግረሱን<br />

ማስገንዘቢያ ከሚፈልጉ እንደሱዳን፣<br />

ዚምባቡዌ፣ እና ኢራን ያሉ 20<br />

አገራት ዝርዝር ውስጥ ማካተቱን<br />

አጥብቀው ተቃውመዋል።<br />

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲናገሩ<br />

‹‹ኢትዮጵያ በሁለትዮሽ ግንኙነቱ<br />

ውስጥ ከወዲሁ የሚታወቅ አካሄድን<br />

(predictability) እና ኢትዮጵያ<br />

ለአሜሪካ ምን ዓይነት ስፍራ ላይ<br />

የቆመች አገር መሆኗን በግልፅ<br />

ማስቀመጥ እንደሚያስፈልግ››<br />

ገልፀዋል። እንደውም ጠ/ሚኒስትሩ<br />

የወታደራዊ ኃይል የበላዩ ጄኔራል<br />

ሳሞራ እና የደህንነት ክፍሉ<br />

ሃላፊ አቶ ጌታቸው አሰፋ አሜሪካ<br />

የኢትዮጵያን የደህንነት አሳሳቢ<br />

ጉዳዮች ጉዳዬ ትላቸው እንደሆን<br />

እምነቱ ተመናምኖባቸዋል<br />

እስከማለት ደርሰዋል። እነዚህ ሁለቱ<br />

ባለሥልጣናት ጦረኛ ነገር ግን<br />

በውጭ ፖሊሲ ጉዳይ ላይ እጅግ<br />

በ ገፅ 23<br />

የነበራት/ያላት ኢትዮጵያ ብርታት<br />

በሌላቸው ምክንያቶች ለዘመናት<br />

ልጆቿን አጥታለች። ምናልባትም<br />

ዛሬ ላይ ለጠፋው አመለካከትን<br />

ጥርት አድርጎ ለማቅረብ ያለመቻል<br />

ችግር በእነዚህ ዜጎች ላይ የተወሰደው<br />

አሰቃቂና አሳዛኝ ግፍ የተሞላበት<br />

እርምጃ እንደ ምክንያትነት ሊጠቀስ<br />

ይችል ይሆናል።<br />

በያለንበት አጋጣሚዎች<br />

እንደሚፈጠሩበት ብርቱ<br />

የምክንያታዊነት ጥያቄዎች ምላሽ<br />

የሌለን ብዙዎች ነን። ለምን ብሎ<br />

መጠየቅ እንደወንጀል የሚቆጠርብንም<br />

እልፎች። በጣም አሳዛኙ ነገር<br />

ኢትዮጵያ ላጣቻቸው ምርጥ ልጆቿ<br />

መጥፋት ወይም መሸሽ ምክንያቱ<br />

አሳማኝ አይደለም። ሞትን የተቀበሉ<br />

በርካታ ኢትዮጵያውያን ነበሩ።<br />

ልዩነቶችን እንደጦር<br />

ከመፍራት ይልቅ፣ አቅርቦ<br />

ማዳመጥና መመርመር ለመንግሥት<br />

ኃላፊነትም ጭምር ነው። በዚህ<br />

ረገድ ከመንግሥት ወዲያ ማን<br />

የአንበሳውን ድርሻ መውሰድ<br />

ይቻለዋል? ዜጎችም ከተጫናቸው<br />

ፍርሃት ተላቀው አመለካከቶቻቸውን<br />

በነጻነት የሚያንጸባርቁበትን ዘመን<br />

ከመናፈቅ ይልቅ፣ ጊዜው አሁን<br />

ነው ማለት ይገባቸዋል። መድረኩን<br />

ማመቻቸት ደግሞ የሁላችንም<br />

ድርሻ ነው። ለኢትዮጵያ ከእኛ<br />

ወዲህ ማን እንዲመጣላት እንሻለን?<br />

ለዘመናትስ ከዜጎቿ ይልቅ ሌሎች<br />

ሲንሰፈሰፉላት ይታያል እየተባለች<br />

እስከመቼ? አመለካከቶቻችንስ<br />

ሳናወጣቸው ለመቼ? ፍርሃታችንስ<br />

የሚለቀን፤ ስለአመለካከቶቻችንስ<br />

የምንከፍለው ዋጋ እስከምን<br />

ይደርሳል? እስከምንስ መድረስ<br />

ይኖርበታል?<br />

እኒያ የግሪክ ሰዎች<br />

ብዙ ከፍለዋል። ስማቸውም ዛሬ<br />

ድረስ ይወሳል። ኢትዮጵያውያኑም<br />

በሚገባቸውም ደረጃ ባይሆንም<br />

አንዳንድ ጊዜ ይነሳሉ። ልንዘክራቸው<br />

ግድ ይላል። ምናልባትም ስለእነርሱ<br />

ብርታት ማንሳታችን ሌሎች<br />

ጀግኖች ይፈጥርልን ይሆናል።<br />

እነርሱ ስለምልከታቸው የከፈሉትን<br />

ዋጋ እያነሳን ማወደሳችን ሌሎች<br />

እንደነሱ ላሉቱ ብርታት ይሆናል።<br />

ስለሆነም “እናንተ ስለሀገራችሁ<br />

ብላችሁ በቅን ልቡና ያነሳች|ቸው<br />

አመለካከቶቻችሁ ዋጋ ያስከፈላDችሁ<br />

ኢትዮጵያውያን ሆይ! ሰላማችሁ<br />

ይብዛ፤ ጽናታችሁን በአሁኗ<br />

ኢትዮጵያ ላለነው ያውርሰን”<br />

እላለሁ።


8<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />

መልካም ዓዲስ ዓመት


አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />

መልካም ዓዲስ ዓመት<br />

‹‹በአዲሱ ዓመት ‘አሸባሪ’<br />

ከመባል ይጠብቃችሁ››<br />

በወጋየሁ ታምራት<br />

ጤና ይስጥልኝ! እንዴት ናችሁሳ? ዓመቷን<br />

እንደቀልድ ፉት አልናትም አይደል?። በርግጥ ዓመቱ<br />

ማለቂያው ደረሰ እንጂ ማለቁን እርግጠኛ መሆን<br />

አይቻልም። እንዴ! መንግስታችን ጳጉሜ ከተመቸው<br />

ዓመቱ ይራዘም ቢልስ? ‹‹ሽብርተኛ›› በመያዝም እኮ<br />

በዚህ ወር ስኬታማ ሆኗል…አይደል እንዴ?<br />

አርቲስት ደበበ እሸቱም ‹‹ከአሸባሪው የግንቦት 7<br />

አመራሮች ጋር በህቡ ሲያሴር በመገኘቱ ታሰረ››<br />

መባሉን ሰምተናል። ‹‹ኧረ ደቤ ህብር መፍጠር እንጂ<br />

ሽብር አያውቅም!›› ሲሉ አንዳንድ ተቆርቋሪዎችን<br />

ብሰማ ‹‹እናንተ ውሳኔውን ለነፃው ፍ/ቤት ስጡ››<br />

በማለት ገስጫቸዋለሁ። የተከሰሰ ፖለቲከኛ ሁሉ<br />

ጥፋተኛ ሳይባል በነጣ መለቀቅ እኛ አገር እንብዛም<br />

ስላልተለመደ ነው መሰል ሰዉ እስር ሲመጣ ይሰጋል።<br />

‹‹ደግሞ እወቁ እኛ ማንንም ተቃወመን ብለን በፖለቲካ<br />

አቋሙ የምናስር ሰዎች አይደለንም!›› የሚለውን<br />

የትምህርት አይነት ሰሞኑን በደንብ እያስጠኑን ስለሆነ<br />

በቀጣይ ጊዜ በደንብ አድርገን ለጠርጣሪዎች ለማስረዳት<br />

ዝግጁ ነን። ግን ጥያቄ ያለው አለ?<br />

ዓመቱ ለእርስዎ እንዴት ነበር? በዓመቱ ምን<br />

ያላየነው አለ? እንደ ኑሮ ውድነት እደግመዋለሁ እንደ<br />

ኑሮ ውድነት ኮሜዲ እና ትራጄዲ ፊልም የሰራብን<br />

ግን አልነበረም። [ለነገሩ ማን ያልቀለደብን አለ?]<br />

ዓመቱን እንደ ሩጫ ማቋረጥ የሚቻል ቢሆን እንደ<br />

ገ/እግዚአብሄር የዴጉ ውሎ 38 ደቂቃ ድረስስ ማን<br />

ይሮጥ ነበር? ያው እንግዲህ እየተደረቡም ቢሆን የኑሮ<br />

ሩጫውን መቀጠል ነውና ይበርቱ የአገር ሰው!!!<br />

እኔ ሰሞነኛ አገልጋይዎ የወግ ማዕዴ የፍስክ ወግ<br />

ብትሉ፣ የጾም በየአይነቱ እዚህ ድረስ ነው ስላችሁ<br />

[በአውራ ጣቴ አገጬን ነክቻለሁ።] ይሄውላችሁማ<br />

አንዱ ፍንዳታ ብጤ… ‹‹የሚሰራውን የማያውቅ እብድ<br />

ነው›› አለኝ። በጄ! አልኩት ቀጠለናም ‹‹መንግስታችንም<br />

እኮ የሚሰራውን አያውቅም፡፡ ‘ቁርጥ የዋጋ ተመን’ አለ<br />

አልተሳካለትም፣ ‘የታክሲ ስምሪት’ አለ ችግሩ ያው<br />

ነው…›› ሲል ትክን ብዬ እና መንግስታችን እብድ ነው<br />

ልትል ነው? ብለው አስቀያሚ ሳቅ ከሳቀ በኋላ ‹‹ያው<br />

ነው…›› ብሎ ወሬውን ሊቀጥል ሲል በግልምጫ<br />

ሰማይ አድርሼ ብመልሰው ቱር ብሎ ከአጠገቤ<br />

ጠፋ፡፡ [የማትፈልጉት ነገር ሁሉ እንዲህ ቱር ብሎ<br />

ከአጠገባችሁ ይጥፋላችሁ፤ አሜን! በሉ]<br />

ግራ የገባው ሁሌም ቀኙ አይታየውም፡፡ እውነቴን<br />

ነዋ! ለዚህ የሆዱን አውርቶ ቱር ብሎ ጠፊ የሚታየው<br />

የተገነባው ዴሞክራሲ፣ መንገድና ህንፃ ሳይሆን ቤቱ<br />

የፈረሰበት ብሶተኛ፣ ‹‹ምህረት›› የተደረገለት ሳይሆን<br />

ግብር የተጫነበት ምላሰኛ ነው። እንደዚህ አይነቶቹን<br />

ይዘን አገሪቱን እንዴት ለአቅመ አገር ማብቃት<br />

ይቻላል?<br />

ሌላ ወዳጄን አገኘሁትና ስለ እዚህ ቱር ብሎ ጠፊ<br />

እና ንግግሩ ከአወራሁት በኋላ ለእርስዎ ከላይ<br />

እንዳጫወትኮት እንደዚህ አይነቶቹን ይዘን አገሪቱን<br />

እንዴት ለአቅመ አገር ማብቃት ይቻላል? ብለው ወደ<br />

እኔ ዞሮ ቁጭ አለ። ‹‹አንተ እና መሰል ካድሬዎች<br />

የምትናገሩትን የማታውቁ፤ በቀቀኖች፣ ህሊና እና<br />

ሞራላችሁን የቀበራችሁ፣ ኢትዮጵያ በቀዳዳ ወንፊት<br />

እያነፈሰች የአብዮታዊ ዴሞክራሲን ጠበል ካልጋትን<br />

በኃይለየሱስ ካሳ<br />

ልማታዊ ጋዜጠኛ (ል.ጋ)<br />

ፉክክሩ በተመሳሳይ ሂደት ውስጥ ያለፉ እንስቶችን<br />

ብቻ ቢመለከትም፣ ፍትሐዊና ዓለም አቀፍ<br />

መለኪያዎችን ያሟላ እንደነበር የአፍሪካ ኅብረት<br />

ታዛቢዎች ማረጋገጫ ሰጥተዋል። አንቺስ ማሸነፌ<br />

ተገቢ ነው ትያለሽ?<br />

ልማታዊ ቆንጆ (ል.ቆ)<br />

ያለ ጥርጥር። ኦልሞስት ሁሉም ዳኞች ድምፃቸውን<br />

ሰጥተውኛል። ወሳኞቹ እነሱ ናቸው። ባልፈልግም<br />

እንኳ ምርጫቸውን የመቀበል አብዩታዊ ግዴታ<br />

አለብኝ። በእርግጥ ለዚህ በመብቃቴ ደስታዬ አንድና<br />

አንድ የለውም። ለህዳሴው መሳለጥ ማበርከት<br />

የምችለውን አስተዋጽኦ ሳስብ ሀሴት ያናውጠኛል።<br />

ል.ጋ<br />

ባለድል መሆንሽ እንደማይቀር የውድድሩ አዘጋጆች<br />

አስቀድመው ሲተነብዩ ነበር። የትንቢቱ መስመር<br />

በእቅድና ጥናት ላይ ተመስርተው መንቀሳቀሳቸውን<br />

አመላካች ነው። ተተኪ የልማት አርበኛ የመኮትኮት<br />

ዓላማቸውንም በአንቺ አሳክተዋል። እስኪ እስካሁን<br />

የመጣሽበትን ጎዳናና የወደፊት አቅጣጫሽን<br />

ግለጪልን?<br />

ል.ቆ<br />

ሲጀመር መድረኩ የተዘጋጀው ማንም እንዳሻው<br />

እየገባ እንዲፈነጭበት አይደለም። በጭራሽ። ይህ<br />

ለድርድር አይቀርብም። ረጅም ርቀት ተጉዘን<br />

የሚፈለግብንን ያሟላን ጥቂቶች ነን ለእጩነት<br />

የደረስነው። “የተመረጡ ምርጦች” ይሉናል። ክበቡን<br />

ለመቀላቀል ብዙ ትጋት ይጠይቃል። ጥቂት ጥቅም<br />

ትላላችሁ፡፡ አሁን አንተ የምርጫ ሰሞን ስብሰባ፣<br />

ስብሰባ ትል ነበር፡፡ ያኔ ትንሽ ግንባርህ ወዝቶ ነበር፡<br />

፡ አሁን ግን እንዳለቀ የውሃ እቃ የሚፈልግህ አለ?››<br />

ብሎ በጥያቄ ሀሳቡን ሲቋጭ እንደዚህ አይነቱን ሰው<br />

እንዴት መመልከት እንዳለብን ከፓርቲዬ በተነገረኝ<br />

መሰረት ‹‹አላዋቂ ነህ›› በሚመስል እና በሀዘኔታ<br />

አስተያየት ‹‹ዝም ብለህ አትንጫጫ ሳይኖርህ<br />

ማሳለጫ›› አላልኩት መሰሎት። ኤጭ! አሉ እኒያ<br />

የማላውቃቸው ሴትዮ… ስንቱን እንዲህ ብዬ<br />

እንደምችለው ግን አልገባኝም፡፡ ሰዉ እኮ እህ ብለው<br />

ካዳመጡት ተበድሮ ያወራል።<br />

ከእሱ ይልቅ የገረመኝ ይሄ IMF የሚባው ሰውዬ<br />

ይሁን ሴትዮ ይቅርታ ዳታው ለጊዜው ቢጠፋብኝም<br />

ግን… ለምን ከራሳችን ላይ አይወርድም? ‹‹የማክሮ<br />

ኢኮኖሚያችሁ ሚዛኑ የተዛባ ነው። ነጋዴውም<br />

እምነት እያጣ ነው›› የሚለው ማን ንገረን አለው?<br />

ንገሩኝ ባይ! በእርግጥ ለትራንስፎርሜሽናችን ሩጫ<br />

ላይ በመሆናችን ሻይ ቡና አላልነውም። በዚህም ደንፉ<br />

(ንዴት) ጋማ ሲለው ጊዜ ‹‹ሚዛኑ የተዛባ ነው›› አላ!<br />

እኔምለው ሚዛኑ በሻይና ቡና ነውንዴ የሚሰራው<br />

ብል ታች ሰፈር ያለው አደገኛ ቦዘኔ አደገኛ ቃላት<br />

ወረወረብኝ፡፡ ቀላል ይናገራልንዴ? ‹‹ለችግራችን ፔስ<br />

ሜከር እየሆናችሁ ረሀብ ራሱ ሀትሪክ ሰርቶብናል…<br />

ምዕራባውያኑ ጓዳችን ፈትሸው ለዓለም ሲያወሩ<br />

እውነቱ አልጥማችሁ እያለ ለ‘አይናችሁን ጨፍኑ’<br />

ጨዋታችሁ ቀይ ካርድ የሚመዝ አጥተናል …››<br />

ቢለኝ ጀርባውን ሳላስጠና ምንም መናገር አያስፈልግም<br />

ብዬ ዝቅ ብዬ አሳለፍኩት ልክ ነኛ! እንዲህ አይነት<br />

ሰው ወይ ሽብርተኛ፣ ወይ ፅንፈኛ፣ ወይ ጨለምተኛ<br />

ወይ ሌላ በ ‹‹ኛ›› የሚያልቅ ነገር እንደሆነ እኛ መች<br />

እናጣዋለን?<br />

እህሳ! ይች ክረምት ትንሽ ከበድ አለች አይደል?<br />

‹‹ሊነጋ ሲል ይጨልማል›› እንዲሉ ነዋ! እኛም<br />

አውቃንበታል ድህነታችንን ቀቅለን እየበላን፣<br />

ቴሌቪዥን ላይ እናፈጣለን። እዚያ ደግሞ ጥጋብ ስላለ<br />

ሚሊየነር ገበሬዎችን እያየሁ ‹‹ተመስገን›› ስል የሰማኝ<br />

<strong>መንግስት</strong>ን ማመስገን አላርጂክ የሆነበት አንድ ወዳጄ<br />

‹‹ፓ! ወገኛ ነህ የታለ ስኳር ድንች? የት እንደጠፋ<br />

ታውቃለህ? አታውቅም ምርጥ ምርጡን ለፈረንጆች<br />

ሲባል አልሰማህም? እኛ ሳንጠግብ ኤክስፖርት<br />

አድርገውታል›› ቢለኝ እንዴት በ‹‹አድርገውታል››<br />

ይገደባል? ‹‹አድርጋችሁታል›› ባለማለቱ እኔን እንደ<br />

ነጭ ለባሽ ነው እንዴ የሚያየኝ? ብዬ በገደምዳሜ<br />

በጭላንጭል አይተው የተከተሉን ድንኳን ሰባሪዎች<br />

ተንጠባጥበው ቀርተዋል። አካሄዳቸው ኪራይ<br />

ሰብሳቢነት ነበርና። በበኩሌ ነፍስ ካወቅሁበት ጊዜ<br />

አንስቶ ተሳትፎዬ ተስተጓጉሎ አያውቅም። ካምፓስ<br />

ሳለሁ የተማሪዎች ህዋስ መሪ ሆኜ አገልግያለሁ።<br />

ተመርቄ ከወጣሁ በኋላ ደግሞ የሴቶች ሊግ<br />

ሊቀመንበር፣ የወጣቶች ፎረም ጸሐፊና ያላገቡ<br />

ወጣት ሴቶች ፌዴሬሽን አቃቤ ነዋይ ነኝ። የሀገሪቱ<br />

ታሪክ ተስተካክሎ እንዲፃፍ የተዋቀረው ኮሚቴ<br />

ውስጥ በአባልነት አለሁበት። የምጣኔ ኃብታችንን<br />

ምጥቀት የሚያስተነትኑ ቁጥሮች በተንኳሾች<br />

ተዛብተው እንዳይዘገቡ ጠንክሬ እከታተላለሁ።<br />

ከዚህም በላይ በቻይናዋ ዋንግ ዡ ከተማ የሶስት<br />

ወር ሥልጠና ወስጃለሁ። “ወ/ሪት ልማት” መባል<br />

ከማኩራትም ባለፈ በቀላሉ የማይገኝ ዕድል ነው።<br />

እርሱን ተጠቅሜ የምሰራቸው ተግባራት ይኖራሉ።<br />

ለአብነት ያህል ታዳጊዎች ምን ማሰብ እና እንዴት<br />

ማሰብ እንዳለባቸው የሚነግር ተቋም ለመክፈት ጫፍ<br />

ደርሻለሁ። በተጨማሪም “ኃይማኖት ለልማት” በሚል<br />

ማዕቀፍ ላከናውነው የምሻው ውጥን አለኝ። አንተም<br />

በሚገባ እንደምትረዳው በፈጣሪ ማመን ያን ያህልም<br />

የሚያስፈልግ ጉዳይ አይደለም። የእኛ መንፈሳዊ<br />

መጽሐፍ ትግላችን ያስገኘለን አምላክ-አካል ግለሰቦች<br />

ቃላት ናቸው። እነርሱን ጠንቅቆ ማወቅና ማነብነቡ<br />

ይበቃል። ሆኖም የእምነት ተቋማትን ልንገለገልባቸው<br />

እንችላለን ብዬ አምናለሁ። በተረፈ የዘወትር ምኞቴ<br />

ሁሌም የማልማትን ታላቋን ሀገር ሰሜን ኮሪያን<br />

መጎብኘት ነው። እንደሚሳካ አልጠራጠርም። ዋነኛ<br />

ሥራው ንግድን መቆጣጠርና ነጋዴዎችን ማውገዝ<br />

የሆነ ቡድን አለ። የእሱ አካል መሆን ከቻልኩ<br />

እርካታዬ የትየሌሌ ይሆናል።<br />

ል.ጋ<br />

የኢራንና የኩባ ተመራማሪዎች እንደደረሱበት<br />

ሰሞነኛ ምርቃት<br />

ከታች ሰፈር ልጆች ጋር በኮሪያ- ዴጉ ተካሂዶ የነበረውን የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ፍፃሜ እየተመለከትን እያለ<br />

ምነው አትሌቶቻችን ውጤት ራቃቸው ብል እየተቀባበሉ ‹‹የሚወራውን አልሰማህም እንዴ?… ‘እያንጓለለ<br />

ካልተፈታ’ ብለው አድማ ላይ እኮ ናቸው›› አሉኝ። ምን ለማለት ፈልገው እንደሆነ ግን አልገባኝም፡፡<br />

ብነግረው ‹‹ምርጥ ምርጡ ጉዳይ ለትልልቆቹ ዓሳዎች<br />

እንጂ ለትንንሾቹ በሰሚ ሰሚ ካልሆነ መረጃውን<br />

ስለማይነግሯችሁ ከእኛ እኩል ናችሁ ብዬ ነው››<br />

በማለት የሆዴን ስለነገረኝ በፀጥ ማርሽ ኩምሽሽ<br />

አደረገኝ እላችኋለሁ። እኔንማ ሲጠራኝ ‹‹አትርሱኝ››<br />

እያለ ነው፤ አትርሱኝ ካላልካቸው በቀር ለምርጫ<br />

ሰሞን ካልሆነ እንዳንተ ያለው ካድሬ ትዝ አይላቸውም<br />

ለማለት ነው።<br />

[ውድ አንባብያን አሁን የዜና ሰዓታችን ስለደረሰ<br />

ከዜናው በኋላ እንደገና እናወጋን]<br />

ጤና ይስጥልኝ ዜና እናሰማለን ምክንያቱም ከማን<br />

እናንሳለን፡፡<br />

ሁሉም በኢህአዴግ ፊት እኩል ነው የሚለውን<br />

‘እውነታ’ ሽሮ ‹‹አይደለም ታጋይ እና አባል የሚሉ<br />

ልዩነቶች አሉ›› በማለት በቅምቀማ ቤት ሲያወራ<br />

የተገኘው እንደልቡ ባሻዬ የተባለ ግለሰብ እንዲህ<br />

ሊያናግረው የቻለው ምን ጠጥቶ ነው፣ ምንስ ተመግቦ<br />

ነበር በሚል ሊካሄድ የነበረው ጥናት ትክክለኛ ቀኑ<br />

ባይገለፅም ለሚቀጥለው ዓመት ጠዋት ተላልፏል<br />

ተብሎ በየመሸታው ቤት እየተወራ ነው።<br />

የውጪ ዜና፡- ትሪፖሊን በሚስጥር ለቀው አልጀሪያ<br />

የገቡት የጋዳፊ ባለቤት ሰሞኑን በሚስጥር ቅኔ አዘል<br />

ነጠላ ዚማ መልቀቃቸውን ከአልጀርስ ሰምተናል።<br />

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት አቶ ኦባማም ይህን ቅኔ<br />

ለፈታ ኢትዮጵያዊ እስረኛ(ሰው) ከስራቱ ይፈታል<br />

[አሜሪካ ይሄዳል ለማለት ከሆነ አገራችንን መዘባበቻ<br />

ማድረጋቸው ያሳዝናል] ሲሉ ሀሳብ ሰንዝረዋል<br />

በማለት የዘገበው ነቆራ.com ነው አዝማቹ እንዲህ<br />

ይነበባል።<br />

አሻግሬ ሳየው ከማዶ ከጎራው<br />

በዝናር ያጌጠው እሱ ነው ያ ጀግናው<br />

ከዜናው ተመልሰናል ስራችንን እንቀጥል። ወግም ስራ<br />

ሆነንዴ? ይላሉ የታች ሰፈር ልጆች። አልቀረባችሁም<br />

እላቸዋለኋ! ስራ ስል ምን ትዝ አለኝ መሰላችሁ ሁለት<br />

የቀድሞ ወዳጆቻችን አግኝቼ ምን እየሰራችሁ ነው?<br />

ብላቸው ‹‹ስፖርት›› አሉኛ! ኧረ ሳቄ ናልኝ ካልኩ<br />

በኋላ ሌላውን ከተመረቀ ሁለት ዓመት ያለፈውን ልጅ<br />

አንተስ ምንድን ነው የምትሰራው? ብለው ጨዋና<br />

ታታሪ የሚባሉትን የላይ ሰፈር ልጆች ጠርቶ ‹‹እነሱ<br />

እንኳን አልያዙም›› ሲል በሾርኒ ዋልጌነቱን ነገረኝ።<br />

በራሱ የሚያሽሟጥጥም አለ ለካ!<br />

እኔምለው! ኮሌጅ ማስበጠሱ ብቻ ምን ዋጋ አለው?<br />

የበጠሱትን መልሰው መቋጠር ካልቻሉ ኮሌጅ እንደ<br />

በኒዩሊበራል ሀገራት ውበት ሴቶችን የመጨቆኛና<br />

ወንዶችን የማሽመድመጃ ሴራ አካል ነው። ሥርዓቱም<br />

እየተንኮታኮተ ከመሆኑ አንፃር በልማታዊ አስተሳሰብ<br />

ውበት እንዴት ይገለፃል?<br />

ል.ቆ<br />

ዋናው ነገር የገላ መለምለም ወይም የመልክ ስልክክ<br />

ማለት አይደለም። ከሁሉ በላይ በማንነት መኩራት<br />

ያሻል። ኩራትህን ለመግለፅ ደግሞ መግደርደር<br />

የለብህም። ለእኔ ፈታኝ የነበረው አጋጣሚ በደሜ<br />

ውስጥ የበርካታ ዘሮች ጠብታ መኖሩ ነው። የምልህ<br />

ገብቶሃል? የትኛውን ብሔር መወከል እንዳለብኝ<br />

እርግጠኛ አልነበርኩም። አለባበሱ፣ ጭፈራው፣ ታሪክ<br />

ነገራው አምታታኝ። የአባቴ አባት ወገኖቼ የእናቴን<br />

እናት ወገኖች መጨቆናቸውን፣ የአባቴ እናት ወገኖች<br />

ከእናቴ አባት ወገኖች ጋር መፋለማቸውን ተረዳሁ።<br />

ግን ልማታዊነት ከጭቁኖች ጎን መቆም መሆኑን<br />

አልዘነጋሁም። ያደረግሁትም ያንን ነው። ቁንጅና<br />

ዝም ብሎ አይን ከማማለል ባለፈ የራሱ ግብና ፋይዳ<br />

አለው። እርሱን ለመገንዘብ በቅድሚያ ሚናን መለየት<br />

ግድ ነው። ዓለም ጥቁርና ነጭ ነች። ወይ ከጥቁሩ<br />

ጋር ሁን ወይም ከነጩ ጋር ሁን። ልማታዊ ውበትን<br />

ከተጎናፀፍክ የሚሉህን ትሰማለህ። የሰማኸውን<br />

ታሰማለህ። በተቀደደልህ ቦይ ትፈሳለህ። በተመተረልህ<br />

መንገድ ትነጉዳለህ። ዞር ዞር ብለህ ዙሪያህን መቃኘት<br />

የለብህም። ጥያቄዎችን በማሰላሰልና በመሰንዘር<br />

አትቸገርም። በእውነቱ አስደሳች ነው።<br />

ል.ጋ<br />

አንዳንድ የአዲስ አበባ ከተማ ኗሪዎች ውድድሩን<br />

ማሸነፍሽ ከምስራቅ አፍሪካ መረጋጋት ጋር ቀጥተኛ<br />

ተዛምዶ እንዳለው የገለፁበት ሁኔታ ነው ያለው።<br />

ፊታቸውን ቅጭም አድርገውም ቢሆን ደስታቸውን<br />

በሰላማዊ ሰልፍ ሊያሳዩ እየተሰናዱ ናቸው።<br />

ሞባይል ካርድ መሸጫ ሱቅ መፍላቱ በእርግጥ<br />

እንደ አካሄድ ከአገር ገፅታ ግንባታ አንፃር ሙድ<br />

አለው። በየመንደሩ፣ በየኩሽናው፣ መከፈቱ ቁልፍ<br />

ጥንካሬያችንን ያሳያል፡፡ [ሳቄ መጣብኝ፡፡ እናንተዬ<br />

የብርድ ሳቅ ለካ ስትራፖ አለው።] ለማንኛውም ከሳቁ<br />

ተመልሻለሁ።<br />

ጠቅላይ ሚኒስትራችን አልናፈቁዎትም? ፈቃዱን<br />

የሰጣቸው መድረክ ወይም ቅንጅት ይመስል ‹‹እነዚህ<br />

የሠርተፍኬት መሸጫ ሱቆች…›› እያሉ በራሳቸው<br />

እና በእኛ ላይ ፓርላማው ተከፍቶ ሲቀልዱ ማየት<br />

ነው ያማረኝ። ይህን የትምህርት ‹‹አብዮት››<br />

እና የሠርተፍኬት መሸጫ ሱቆች ሰሞኑን አይን<br />

በዝቶባቸዋል። <strong>መንግስት</strong> እንደ ምርጫ ፈተና ኮሌጆቹን<br />

ሀ፣ ለ፣ ሐ 1 እና 2 እያለ መክፈል ጀመረ አሉ።<br />

በቀይ ካርድ የተባረሩም አሉ። ኢንቨስት ካደረጉ በኋላ<br />

ከማባረር ቀድሞ ነበር እንጂ መደቆስ አትሉም?<br />

መንጌን የሚያስታውሰን ነገር… የጠ/ሚኒስትራችን<br />

ፎቶ በየቢሮው እና በአደባባዩ መሰቀል ከተጀመረ<br />

ከራርሟል አይደለም? አንድ ወዳጄ ይህን ሲያነሳብኝ<br />

‹‹እወደድ ባዩ ሰቀለው እንጂ እሳቸው ይህንን<br />

አልደግፍምም፣ አላየሁም፣ አልሰማሁም፣ ብለዋል<br />

አራት ነጥብ›› ብለው ‹‹በየሚኒስትሮቻችሁ፣<br />

በየኮሚሽነሮቻችሁ ቢሮ ፎቶው ተሰቅሏል። ሰዎቹ<br />

ወይ አይሰሙም፣ ወይ አይታዘዙም ማለት ነው።<br />

የማይታዘዝ ደግሞ ነገ…›› ብሎ ሳይጨርስ እኔም<br />

ቱር ብዬ ጠፋሁ፡፡ የቀረውን አሞራ ትጨርስላችሁ።<br />

በሞቴ ሳልረሳው ልንገራችሁማ ኢቴቪ በሰከንድ<br />

የማስታወቂያውን ክፍያ ጣራ ላይ ሰቀለውኮ<br />

አሃ! ለእኛም ይታሰብልና ማስታወቂያ ባናሰራም<br />

ማስታወቂያ እናያለና! ልክ ነኛ! በማስታወቂያው<br />

ካልተዝናናን ታዲያ በምኑ ልንዝናና ነው…[በርግጥ<br />

ማስታወቂያ ሰሪዎቹ ሁለት ብቻ መስለዋል፡፡ እነሱም<br />

ጣሪያ ወጥተው ሲወርዱ አልቆባቸዋል እያሉ ታች<br />

ሰፈር ያወራሉ] እኛ ሰፈር ቴሌቪዥን ድምፅ ተቀንሶ<br />

ይከፈታል። ማስታወቂያ ሲመጣ ‹‹ከፍ አድርገው<br />

ይባላል›› ሲያልፍ ይቀነሳል እንዲህ ነው ኢቴቪ ጋር<br />

ተስማምተን የምንኖረዋ! ምን ላድርግ ታዲያ ከታች<br />

ሰፈሮች ጋር ሲኖሩ ተስማምቶ ካልሆነ ስለማይቻል<br />

ችያቸዋለሁ።<br />

መቼም የእኔ ነገር አንዱን ጥዬ አንዱን አንጠልጥዬ<br />

ሆነብኝ እንጂ ኢቴቪ ‹‹በኤሌክትሪክ የሚሰራ ባስ<br />

ደብረ ማርቆስ ሊገጣጣም ነው። በቅርቡ ለሙከራ<br />

ከጊዮርጊስ አዲሱ ገበያ ይጀምራል›› ብሎ ካስደሰተን<br />

ይኸው ፀሀይዋ ስንት ጊዜ ገብታ ወጣች መሰላችሁ፡፡<br />

‹‹ከምን ደረሰ ብለው አጣርተዋል?›› አሃ! ከማስደሰት<br />

የገፅታ ግንባታ አንፃር ከሆነማ ይሄ የባቡር ዝርጋታው<br />

ጉዳይስ እንዴት ነው?<br />

ከታች ሰፈር ልጆች ጋር በኮሪያ- ዴጉ ተካሂዶ<br />

የነበረውን የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ፍፃሜ እየተመለከትን<br />

እያለ ምነው አትሌቶቻችን ውጤት ራቃቸው ብል<br />

እየተቀባበሉ ‹‹የሚወራውን አልሰማህም እንዴ?…<br />

‘እያንጓለለ ካልተፈታ’ ብለው አድማ ላይ እኮ<br />

ናቸው›› አሉኝ። ምን ለማለት ፈልገው እንደሆነ ግን<br />

አልገባኝም፡፡ ለማንኛውም ሳምንት በሰላም እንገናኝ<br />

ዘንድ ከስንብቴ በፊት ከተማ ውስጥ የሚወራውን<br />

ሰሞነኛ ምርቃት ቱቱ ብዬ ላድርስዎ። ‹‹በአዲሱ<br />

ዓመት ‘አሸባሪ’ ከመባል ይጠብቅዎ!›› ሰላም!!!<br />

የሚስ አብዮታዊ ዴሞክራሲ ልማታዊ ውበት ምስጢር<br />

አንባብያን ሆይ! የተያያዝነውን የሀገር ገፅታ ግንባታ በማስቀጠሉ ረገድ ጉልህ ሚና እንደሚጫወት የታመነበት ታላቅ ውድድር በቅርቡ መካሄዱ ይታወቃል። በውድድሩም በታሪካችን<br />

ለመጀመሪያ ጊዜ የብሔር ብሔረሰቦችን እኩል ተሳትፎ ባረጋገጠ መልኩ ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጣ የልማታዊ ዳኞች ቡድን፣ የልማታዊ ውበትን እሳቤ የተላበሰች ቆንጆ<br />

መርጦ “ሚስ አብዩታዊት ዴሞክራሲ” ሲል ሰይሟል። ወርቃማው የአሸናፊነት ዘውድ በክብር ከተጫነላት ወጣት ጋር ልማታዊው ጋዜጠኛችን ቀጣዩን አጭር ቆይታ አድርጓል።<br />

ለአድናቂዎችሽ ምን መልዕክት ታስተላልፊያለሽ?<br />

ል.ቆ<br />

ምልክታችሁ እሆን ዘንድ ስለፈቀዳችሁ<br />

አመሰግናለሁ። ይህ ለእኔ የኮንትራት ውል ነው።<br />

ስሜን በተግባር ካላስከበርኩ ህዝቡ ውሉን ያለማደስ<br />

መብቱ ተከብሮለታል። አልፈልግሽም ብሎ ቀይ<br />

ካርድ ሊመዝብኝ ይችላል። ስለዚህ አሁን የምለው<br />

እኔ ለልማት ተግቻለሁ፣ ከጎኔ ቁሙና እጅ ለእጅ<br />

ተያይዘን የአምስት ዓመቱ - አራት ሆነ’ንዴ? -<br />

የእድገት ትራንስሚውቴሽን እቅድ ... ማለቴ እድገትና<br />

ተራንስፊክሴሽን ... ኤጭ! ምን ዕዳ ነው’ቴ ...<br />

የአምስት ዓመቱ የእድገትና ትራንስግሬሽን . . .<br />

ል.ጋ<br />

ትራንስፎርሜሽን<br />

ለ.ቆ<br />

አዎ። እርሱ እንዲሳካ የበኩላችንን እንወጣ።<br />

ል.ጋ<br />

በጣም ጥሩ። በመጨረሻ ከየወረዳ ኃላፊዎች<br />

የሰበሰብኩት ዳታ አለ። ቁጥራቸው እዚህ ግቡ<br />

ማይባልና ግራፉ እንደሚያሳየን ቁልቁል እየወረደ ያለ<br />

ነቃፊዎች አላጣሽም። ምን ትያቸዋለሽ?<br />

ል.ቁ<br />

ወየውላችሁ!<br />

ል.ጋ<br />

አመሰግናለሁ ሚስ አብዮታዊት ዴሞክራሲ። ልማታዊ<br />

ስኬትና አብዮታዊ ደስታ እንዲገጥምሽ እመኛለሁ።<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

9


10<br />

በንፍታሌም<br />

የመፅሐፉ ርዕሥ፡- ፒያሳ (መሐሙድ ጋ ጠብቂኝ)<br />

የመፅሐፉ ደራሲ፡- መሐመድ ሰልማን<br />

የመፅሐፉ አይነት፡- ወግ፣ መጣጠፍ እና የጉዞ<br />

ማስታወሻ<br />

የገፅ ብዛት፡- 181 ገፅ<br />

የመፅሐፉ ዋጋ፡- 29 ብር<br />

ፒያሳን የትውልድ መንደሬ ያህል<br />

አብጠርጥሬ አውቃታለሁ። ለድፍን 15 ዓመታት<br />

በውስጧ ተመላልሼባታሁ። ከእግር እስከ ራሷ ልቅም<br />

አድርጌ አይቻታለሁ ብዬ አምናለሁ። በመሀመድ<br />

ሙዚቃ ቤት ወረድ ብዬ ተረት ሰፈር ውስጥ ወግ<br />

ሰልቄአለሁ። ሸቅብ ተመልሼ በዶሮ ማነቂያ ጉራንጉር<br />

ተሹለክልኬአለሁ። ሰራተኛ ሰፈርን በቀን በለሊትም<br />

ቃኝቻለሁ። ውቤ በረሃን፣ ገዳም ሰፈርን፣ አትክልት<br />

ተራን ወዘተ በየተራ ውዬባቸዋለሁ፤አምሽቼባዋለሁ።<br />

ሁሉንም የፒያሳ ‹‹መዳረሻ››ዎች እስኪበቃኝ ድረስ<br />

አዳርሻቸዋለሁ። እንዲያው በአጭሩ፣ ከአጭሩም<br />

በአጭሩ አውቃቸዋለሁ ባይ ነኝ።<br />

ግን ደግሞ ከእኔ በላይ ፒያሳን የሚያሳየኝ<br />

ሲገኝ ገረመኝ። ምን መገረም ብቻ? ደነቀኝ። ዕለት<br />

በዕለት የምጎበኛትን ፒያሳ እንደ አዲስ በአይነ<br />

ህሊናዬ እየቃኘሁ ሳቅኩ። አንድም በራሴ፣ አንድም<br />

በሁላችንም፣ አንድም በማንነታችን እየሳቅሁ ከራሴ<br />

ጋር ሙግት ገጠምኩ። እየሳቅኩ አዘንኩ። ‹‹እያነቡ<br />

እስክስታ›› እንዲሉ።<br />

እንዲህ ያለ ጥልቅና መንታ ሥሜት<br />

ውስጥ የከተተኝ በቅርቡ ለአንባቢያን የቀረበውና<br />

‹‹ፒያሳ›› የሚል ርዕስ የተሰጠው መፅሐፍ ነው።<br />

‹‹ፒያሳ›› ከሚል ጉልህ ርዕሥ ሥር ‹‹ማሕሙድ<br />

ጋር ጠብቂኝ›› የሚል ንዑስ ርዕሥ በድራቢነት<br />

ተሰጥቶታል። ደራሲው ደግሞ መሐመድ ሰልማን<br />

ይባላል።<br />

ደራሲው መሐመድ ሰልማን ‹‹ፒያሳ››<br />

(መሐሙድ ጋ ጠብቂኝ) የሚል ርዕሥ የሰጠው<br />

ይህ መፅሐፍ ወጎችን፣ መጣጥፎችን እና የጉዞ<br />

ማስታወሻዎችን በአንድነት አጣምሮ ይዟል። በ14<br />

ክፍሎች (ርዕሶች) የተሰደሩት የመሐመድ ሰልማን<br />

በረከቶች በፒያሳ ‹‹ምህዳር›› ብቻ የተከበቡ ይደሉም።<br />

የሀገርን ዳር የሚያካልሉ፣ የሀገርን ሁለንተና ቁልጭ<br />

አድርገው የሚያሳዩ የብዕር ትሩፋቶች ናቸው። በሌላ<br />

አነጋገር የሀገር ዕውነት፣ የሐገር እብደት፣ የሐገር<br />

ንቅዘት፣ የሀገር ዝቅጠት፣ የሀገር እምነት ወዘተ<br />

እንደዘበት የታቀኙባቸው ናቸው። እንደገና በሌላ<br />

አነጋገር የእኛ ማንነት፣ የእኛ ምንነት፣ የእኛ ዕምነት፣<br />

የእኛ ሥነ ምግባር ልኬት ወዘተ በሚጥም ቋንቋ<br />

የተመዘነበት ድንቅ የሥነ ፅሁፍ በረከት ነው።<br />

ለዚህም ይመስለኛል የቀድሞው አዲስ<br />

ነገር ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ መስፍን ነጋሽ ፣ ካለበት<br />

ከሀገረ- ስዊድን የሚከተለውን አስተያየት በመፅሐፉ<br />

መቅድም እንዲህ ሲል ያሰፈረው፡-<br />

‹‹በፀሐፊው እይታ ፖለቲካ/ፖሊሲ፣ ባህል፣<br />

ኢኮኖሚና ጊዜ ተጣምረው የሰሩትን ኢትዮጰያዊ<br />

ህይወት፣ አኗኗር፣ ህልም፣ ብሶት ወዘተ በጋዜጠኛ<br />

አይን ከትቦልናል። ፅሁፎቹ የግለሰቦችንና የቡድኖችን<br />

የቀን ተቀን አኗኗርና ትዝብት የሚያንፀባርቁ<br />

እንደመሆናቸው የዘመኑ ‹ዜና መዋዕል› አካል<br />

ተደርገው ሊታዩ የሚገባቸው ናቸው።…››<br />

ይህ አስተያየት የመፅሐፉን ይዘት ብቻ<br />

ሳይሆን፣ የደራሲውን ላቅ ያለ ችሎታ የሚጠቁም<br />

ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ የሥነ ፅሁፍ አጥኚዎች<br />

(ተመራማሪዎች) አንድ ደራሲ የድርሰቱ ምንጭ<br />

የሆነውን ማህበረሰብ በሚገባ ማወቅ እንዳለበት<br />

ነው ለደራሲነት ክህሎት ቅድሚያ የሚሰጡት።<br />

ደራሲ ማህበረሰቡን የኑሮ ገፅታ፣ የኢኮኖሚውን፣<br />

የፖለቲካውን፣ የማህበራዊ ህይወቱን ሁኔታ፣<br />

ከእነዚህ ጋር ተያያዥ የሆኑ ታሪካዊ ክስተቶችን<br />

ልቅም አድርጎ ማወቅ አለበት ይላሉ። ምክንያቱም<br />

‹‹በሥነ ፅሁፍና በማህበረሰብ መካከል ጥብቅ ትስስር<br />

አለ፤ ትስስሩና የእውኑ ህይወት ገፅታዎች የድርሰቱ<br />

መሠረቶች ናቸውና›› ሲሉ ያሰምሩበታል።<br />

የ‹‹ፒያሳ›› (መሐሙድ ጋ ጠብቂኝ) ደራሲ<br />

መሐመድ ሰልማን፣ ይህንን የማህበረሰብን እና የሥነ-<br />

ፅሁፍን ጥልቅ ትስስር በድንቅ ብቃትና ክህሎት ነው<br />

ያስመሰከረው። ‹‹ዐደይ መቀሌ››፣ ‹‹በኤርትራ ሙዚቃ<br />

የምትደንስ ከተማ››፣ ‹‹የመመረቂያ ፅሁፎች ጥቁር<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

ፒያሳ<br />

በ‹‹ ››<br />

ገበያ››፣ ‹‹ሼ መንደፈር በመርካቶ››፣ ‹‹ከአዲግራት<br />

እስከ ዛል አንበሳ›› ወዘተ በተሰኙ ርዕሶች ያቀረበልን<br />

ታሪኮች ለዚህ አባባል አይነተኛ ማሳያዎች ናቸው።<br />

በነገራችን ላይ በመፅሐፉ ውስጥ<br />

ከተካተቱት ትረካዎች ስምንት ያህሉ በቀድሞዋ<br />

‹‹አዲስ ነገር›› ጋዜጣ ለንባብ የበቁ ናቸው። ቢሆኑስ?<br />

ዛሬም እንደ አዲስ እየተገረምን፣ እየተደመምን፣<br />

በራሳችን እያዘንን እና እየተከዝን እናነባቸዋለን።<br />

ራሳችንን እንፈትሽባቸዋለን። የት እንዳለንና ወዴት<br />

እየሄድን እንደሆነ እናይባቸዋለን። ለማንኛውም ወደ<br />

ዋና ጉዳይ እንመለስ። ወደ ደራሲው።<br />

በ‹‹ፒያሳ›› መፅሐፍ የምናስተውለው<br />

የደራሲውን የላቀ ችሎታ ነው፡፡ ደራሲው መሐመድ<br />

ሰልማን በመማር ብቻ ሳይሆን፣ በተፈጥሮ<br />

የተጎናፀፈው ድንቅ ችሎታ አለው ብንል ማጋነን<br />

አይሆንም። መሐመድ በእርግጥ ይፅፋል። ይፅፋል<br />

ብቻ ሳይሆን በቃላት መሳልን ተክኖበታል። በቃላቶች<br />

ህብረ ነገሮችን አጉልቶ ያሳየናል። አንድን ነገር<br />

በአንባቢያን ልቦናና አዕምሮ ውስጥ ለመቅረፅ ብዙም<br />

አይጨነቅም። በቀላል ቋንቋ፣ በአጭርና በቁጥብ<br />

ዓረፍተ ነገር፣ በተዋበ ስልትና ፍሰት መጥኖ በቀላሉ<br />

ይገልፅልናል።<br />

አገላለፁ ልክ እንደ ልጅነት ልብና አዕምሮ<br />

ንፁህ ነው። ለዚህ አባባል አስረጂ ይሆን ዘንድ<br />

የሚከተለውን መጥቀስ እንችላለን፡-<br />

‹‹ትልቁ የአገራችን የህዝብ ሽንት ቤት<br />

‹ማህሙድ ሙዚቃ ቤት› ማዶ ነው። ግርማዊነታቸው<br />

የፈረንሳይ ህንፃ ባለሙያዎች አስመጥተው ነው<br />

ይህንን የህዝብ ሽንት ቤት ያሰሩት። እውነቴን ነው።<br />

ካላመንክ አቶ ፍቅሩ ኪዳኔ የጻፉትን ‹የፒያሳ ልጅ›<br />

መፅሐፍ አንብብ…›› (ገፅ 7)<br />

መሐመድ ሰልማን አስረጅ ከማቅረቡ<br />

በፊት ‹‹እመነኝ›› ይላል። ‹‹‹ከላማንክ እነ እከሌን<br />

ጠይቅ፣ የእከሌን መፅሐፍ አንብብ›› ይልና ወደ ሌላ<br />

ጉዳይ ያመራል። ህፃን ሆናችሁ ‹‹ካላመንክ እከሌን<br />

እንጠይቅ›› ያላችሁበት የዕውቀት ማስረገጫ እማኝ<br />

የጠራችሁበትን የቅንነት ዘመን አስታወሳችሁ?።<br />

መሐመድ ሰልማን የተከተለው የአተራረክ<br />

አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />

መልካም ዓዲስ ዓመት<br />

p Ç T@<br />

ሽንቁር ሀገር ሲመተር<br />

ስልትና ዘይቤ መራሩን የሚያጣፍጥ፣ ጠፋጩን<br />

የሚያመር ነውና የአንባቢያንን ስሜት ሰቅዞ የመያዝ<br />

ኃይል ደርቧል፡፡<br />

‹‹ፒያሳ ፎቅ አልባ ናት ካልን ‹ገመናዋን<br />

ማን ሸፈነላት?› የሚለው ጥያቄ ይከተላል።<br />

በፒያሳ ወርቅ ወርቁን ስታይ ከጀርባ ምን እንዳለ<br />

ትረሳለህ። በፒያሳ ቆንጆ ኮረዶች ሽው እልም ሲሉ<br />

ስታይ ማሰቢያህ ይሰለባል። ደፈር ብለህ አንዷን<br />

የፒያሳ ቆንጆ ዳሌዋን እያየህ በ‹ብሪቲሽ ካውንስል›<br />

ወይ በ‹አምፒር› ወይ በ‹ሰራተኛ ሠፈር› በኩል ባለ<br />

ቀጭን ቅያስ ውስጥ ትገባለች። መጨረሻዋን ልይ<br />

ብለህ አሁንም ትከተላለህ። እስከ ውስጥ። ድንገት<br />

ትሰለብብሃለች። በዚህ ቅፅበት ምን ሰወራት ብለህ<br />

ለራስህ ስታንሾካሹክ ከጭርንቁስ ቤቷ በመስኮት<br />

ወጥታ ‹ምን አልክ› ልትልህ ትችላለች። ስለዚህ<br />

የፒያሳ ልጅ አትከተል። ከተከተልክም እጇን ይዘህ<br />

ተከተላት፡፡…›› (ገፅ 10)<br />

ይኼኔ ነው የዘይቤን ምንነት ማጠየቅ<br />

የሚገባው። ዘይቤ የአንድን ሀሳብ፣ ድርጊት፣ የአንድን<br />

ነገር ቅርፅ ወይም ሁኔታ፤ እንዲሁም የሰውን ባህርይ<br />

ስሜትና መልክ አጉልቶና አድምቆ ለተመልካችም ሆነ<br />

ለሰሚው ፍስሃ በመስጠት የሚቀርብ የአነጋገር ስልት<br />

መሆኑን ነው የዘርፉ ምሁራን የሚያስረዱት።<br />

ይህ ስልት ግዑዙ ነፍስ እንዲዘራ፣ ደብዛዛው<br />

ብሩህ እንዲሆን፣ ረቂቁ እንዲገዝፍ ከመርዳቱም<br />

በላይ ተገላጩ የስሜት ህዋሳትን ነክቶ ብሩህ ምስል<br />

በመፍጠር በዓይነ ህሊና እንዲታይ፣ በእዝነ ህሊና<br />

እንዲሰማ፣ ጣዕምና ለዛው እንዲታወቅ የማድረግ<br />

ኅይል እንዳለው ነው ምሁራኑ የሚያስረግጡት።<br />

ከዚህ አንፃር መሀመድ ሰልማን በሚያስገርም<br />

ሁኔታ ተሳክቶለታል። ከላይ ለአብነት የጠቀስናትን<br />

የፒያሳ ቆንጆ ታሪክ ልብ በሉ፡፡ የሚከተላትን<br />

ወጣት ሹክሹክታ ብቻ ሰምታ ‹ምን አልክ› ስትል<br />

ትታያችሁ። ያ ቤት በጭቃ ግድግዳ ነው የተሰራው<br />

ወይስ በካርቱን? በካርቱንስ ቢሆን ሹክሹክታን እንዴት<br />

ያሰማል? አይታያችሁም በመሐመድ ብዕር ውስጥ<br />

የዚያች ቆንጆ ልጅ ሰፈር ጉስቁልና? ቤቶች እንዴት<br />

ችምችም ብለው እንደተሰሩ?<br />

ይህ ብቻ አይደለም፤ መለመድ በእያንዳንዱ<br />

ታሪክ ውሰጥ በስላቁ ያስቀናል። እያሳቀን ስቃይና<br />

ሰቆቃን ያሳየናል። እናም ከራሳችን ጋር እንዋቀሳለን።<br />

ከአስተሳሰባችን ንቅዘት ጋር እንብሰለሰላለን። በትካዜና<br />

በቁጭት እንትከነከናለን። የወደፊት ህይወታችንን<br />

በሥጋት እናስተውላለን።<br />

መሀመድ ሰልማን በትረካው ከሚያሳየን<br />

ዕውነታ ውጪ ለማንም ለምንም አይወግንም።<br />

እንዲያም ይበል እንጂ በፍፁም ቅንነትና ጨዋነት<br />

ለኢትዮጵያዊነትና ለመልካም እሴቶቿ ከመወገን<br />

ወደኋለ አይልም። ግን ደግሞ ውግንናው ንፅህናውን<br />

የጠበቀ ነው። ‹‹ሼ መንደፈር በመርካቶ››ን ሊነቅሱ<br />

ይችሏል። እነሆ፡-<br />

‹‹… በየአጋጣሚው የማነባቸው አዳዲስ<br />

መንፈሳዊ መፅሐፍትም ስለፍቅር የሚሰብኩት<br />

ቃላት ጎድለውባቸዋል። ይልቁንም መጪው ዘመን<br />

በኃይማኖቴ ላይ አደጋ የሚያንዣብብበት እንደሚሆን<br />

የሚተነብዩና ነቅቼ እንድጠብቅም የሚያስጠነቅቁ<br />

ናቸው። በተቀራኒው ጎራ የሚፃፉ መፅህፍትም<br />

በተመሳሳይ መልኩ ተናዳፊ ናቸው።… ከቤተ ሙከራው<br />

ሲወጡም ብዙ አማኝን የሚያስቀይም ውጤት ይዘው<br />

እኛን ብቻ ስሙ ሲሉ ይንጎራደዳሉ። ያንኑ በመፅሐፍ፣<br />

በሲዲ፣ በቲ-ሸርት ካልታተመልን ይላሉ። የእኔዋ<br />

የአሁኗ መርካቶ በዚህ ሁሉ ተቃርኖ የተሞላች ናት።<br />

በዚህ ዓመት በጋራ የተጀመሩት የፍልሰታና የረመዳን<br />

ጾሞች ደግሞ ተቃርኖውን አጉልተው እያሳዩኝ ነው።<br />

በመርካቶው ሼ መንደፈር።…›› (ገፅ 146)<br />

መሐመድ ሳልማን ከኃይማኖት ሥነ<br />

ምግባር አልባነት እስከ ትምህርት ጥራት ውድቀት፣<br />

ከፖለቲካ ግራ መጋባት እስከ ማህበራዊ ህይወት<br />

ዝቅጠት፣ ወዘተ ያልዳሰሰው ጉዳይ የለም። በዚህ<br />

ትረካው ስለ ትግራይ ህዝብ ታዝናላችሁ። ስለ<br />

አዲግራት ታዝናላችሁ። ስለ ትግራይ እናቶች<br />

ታለቅሳላችሁ።<br />

‹‹…በአዲግራት የሰማሁት የአፈሣ<br />

ታሪክ አስደንቆልኛል። ለምሳሌ ሰርግ ላይ የነበሩ<br />

ወንድማማቾች ከታደሙበት ሰርግ ድንኳን ታፍሰው<br />

ተወስደዋል። ታላቅ በጦርነቱ ህይወቱ ሲያልፍ፣<br />

ታናሽ ህይወቱ ተርፏል። ይህንን ታሪክ የነገሩኝን<br />

ወዳጆቼን ይህ የሆነው በደርግ ጊዜ ነው? እያልኩ<br />

ሞግቻቸዋለሁ። አይደለም። … መቀሌ ላይ ደግሞ<br />

ዘወትር ማለዳ የቀበሌ ወታደር መልማዮች በየስርቻው<br />

በየመንደሩ ይዞሩ ነበር፡፡ ያገኙትን ኮበሌ ቀብ<br />

አድርገው ስልጠና ያስገቡታል። በየጎዳናው ወጣት<br />

ሲጠፋ ደግሞ ቤት ለቤት አሰሳና አፈሳ ተጀመረ። …<br />

እናቶች ልጆቻቸውን ለመሸሸግ ተገደዱ። ይህ ታሪክ<br />

የደርግ አይደለም። … ‹ደብሪ›ን (ጎተራ) በጦርነቱ ጊዜ<br />

እናቶች ልጆቻቸውን ለመደበቅ ተጠቅመውበታል…››<br />

(ገፅ 167)<br />

መሐመድ ስልማን መራሩን የህይወት<br />

ዕውነታ በቀላል አገላለፅ ቁልጭ አድርገን እንድንጋት<br />

ግድ ይለናል። ያላየነውን የቅንጦት የሚመስል የዘቀጠ<br />

እና መረን የለቀቀን ብልግና እያሳየን እንድንጠየፍ<br />

ያደርገናል። ‹‹የጀሚላ መዳፎች›› (ከገፅ 119-129)<br />

ለዚህ ከበቂ በላይ አስረጅ ናቸው። ውቦቹ የጀሚላ<br />

መዳፎች ፀያፍ ተግባራት የማህበረሰባችንን ብልሹነት<br />

ለመግለፅ በእርግጥም ከበቂ በላይ ናቸው።<br />

በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሶሲዮሎጂ<br />

ዲፓርትመንት ሌክቸረር የሆኑት አቶ ደረሰ ጌታቸው<br />

በመፅሐፉ መግቢያ ‹‹መሿለኪያ›› በሚል ርዕሥ<br />

ባሰፈሩት አስተያየት የሚከተለውን ያሉት ለዚህ<br />

ይመስለኛል።<br />

‹‹አዲስ አበባን ሰንገው የያዙ ችግሮችንም<br />

መሐመድ በሰላ ፅሁፉ ነቅሶ አውጥቷቸዋል።<br />

ሥራ አጥነት፣ የኑሮ ውድነት፣ ሴተኛ አዳሪነትን<br />

የመሳሰሉትን የኑሮ ችግሮች ላይ የራሱን ቁዘማ<br />

(ሪፍሌክሽን) ያስነብበናል። አዲስ አበባን ሲያስስ<br />

የከተማ አውቶብስ አይቀረውም። ከዚያ ወጣ ብሎም<br />

የደረሰባቸውን የሀገሪቱ ክፍሎች በከተሜ ዕይታ<br />

ታዝቧቸዋል። ‹ገጠርን ማዕከል ባደረገ› የልማት<br />

ስትራቴጂና የሰው ኃይል ስብስብ የሚታወቀው<br />

<strong>መንግስት</strong>ና የከተማው ባለስልጣኖች ይህን መፅሐፍ<br />

ቢያነቡት ጥሩ ነው…››<br />

ምን ባሥልጣናት ብቻ? የሀገሪቷ<br />

ህዝብ በሙሉ ቢያነበው ጥሩ ነው እንጂ። መቼም<br />

ባለሥልጣናቱ ያነበንባሉ እንጂ አያነቡም። ህዝቡ ነው<br />

ማንበብ ያለበት። ምክንያቱም ‹‹ፒያሳ›› (መሀሙድ<br />

ጋ ጠብቂኝ) መፅሐፍ ውስጥ የሁሉም ህይወት አለ።<br />

በጥበብና በጥበበኛ ብዕር የተኳለ። ያ ብዕር የመሐመድ<br />

ሠልማን ብዕር ነው። የምናየውን ዕውነት፣ ባላየነው<br />

መንገድና ዕይታ አሳምሮ፣ እንደዋዛ አዋዝቶ ልክ<br />

ልካችንን የሚነግረን ድንቅ ብዕር። አቦ! ‹‹እጅ በነክ››<br />

ብዬ ባሳርግ ነው የሚሻለው። እጅ በነክ!!!


አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />

መልካም ዓዲስ ዓመት<br />

S ´ “ —<br />

‹‹አሰብ የማን ናት?››<br />

መፅሐፍ ለንባብ በቃ<br />

አለም አቀፍ የህግ ባለሙያ የሆኑት እና በኢትዮጵያ ፖለቲካ<br />

ውስጥ ጉልህ ሚና የነበራቸው ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማርያም<br />

አሰብ የማን ናት? በሚል ርዕስ መፅሐፍ ፃፉ፡፡ ዶ/ር ያዕቆብ<br />

የመፅሐፉን ዋና አላማ ሲገልፁም ታሪክን፣ አለም አቀፍ ሕግን፤<br />

የቀይ ባህር አፋሮች አንድነትና መብትን ከግንዛቤ አግብቶ የአሰብ<br />

ወደብ ሕጋዊ ባለቤት ኤርትራ ወይስ ኢትዮጵያ ነች ለሚለው<br />

ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት መሞከር እንደሆነ ነው፡፡ በተለያዩ<br />

ዘመናት አሰብን ለማስመለስ የተደረጉ ትግሎችን፤ ስለ አልጀርሱ<br />

ስምምነት እንዲሁም የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎችን አስተያየት<br />

ከመያዙም በተጨማሪ ወደብ ለአንድ አገር ያለውን ኢኮኖሚያዊ<br />

ፋይዳም አካቶ ይዟል፡፡<br />

መፅሐፉ በ13 ምዕራፎች የተከፋፈለ ሲሆን 260 ገፆች አሉት፡<br />

፡ በመፅሐፉ የተወሰነ ገፅ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ያቀረቡ ሲሆን<br />

ይህንንም በመግቢያቸው አሰብን ወደ ኢትዮጵያ ለማስመለስ<br />

የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ድጋፍ ስለሚያስፈልግ ለእነሱ መጠነኛ<br />

ግንዛቤ ለማስጨበጥ እንደተዘጋጀ ገልፀዋል፡፡<br />

መፅሐፉ በ45 ብር በመሸጥ ላይ ሲሆን ከሽያጩ የሚገኘው<br />

ገቢ ለበጐ አድራጐት ድርጅቶች እንደሚውልና መታሰቢያነቱን<br />

ለዴሞክራሲ፤ ለፍትህና ለአንድነት ሲታገሉ ለወደቁ<br />

ኢትዮጵያዊያን አድርገዋል፡፡<br />

በኳንተም ፊዚክስ ላይ<br />

ውይይት ተካሄደ<br />

በዶክተር አቡሽ አያሌው በተፃፈው ‹‹አልፋና ኦሜጋ››<br />

መፅሀፍና በውስጡ ስለተገለፃው ‹‹ኳንተም ፊዚክስ›› ምንነትና<br />

አጠቃላይ ሀሳብ ላይ ውይይት ተካሄደ። ውይይቱ የተካሄደው<br />

ባለፈው ሳምንት እሁድ ረፋድ ላይ በጥቁር አንበሳ ት/ቤት<br />

የስብሰባ አዳራሽ ውስጥ ሲሆን የእኛና የዩኒቨርስ ማንነት<br />

በኳንተም ፊዚክስ መነጽር ሲታይ ምን ገጽታ እንዳለው፣<br />

ሳይንሱ በህይወታችን ስኬታማነት፣ ሰላምና ፍቅር እንዲሁም<br />

ም ብልፅግና በኩል የሚጫወተውን ሚና እና ተያያዥ ነገሮች<br />

ለህብረተሰቡ ግልፅ ለማድረግ ውይይቱ መካሄድን የመፀሀፉ<br />

ደራሲና አዘጋጅ ዶ/ር አቡሽ አያሌው ገልጿል። የሳይንሱን<br />

ትክክለኛነት በህዝቡ አስተሳሰብ ውስጥ ለማስረፅ ተከታታይ<br />

ውይይቶች እንደሚካሄዱም ነው የተገለፀው።<br />

“የትሮይ ፈረስ” እና ‹‹ገንዘብና<br />

ፍቅር›› ፊልሞች ተመረቁ<br />

በአስቴር ፊልም ፕሮዳክሽን የተዘጋጀውና 1 ሰዓት ከ40 ደቂቃ<br />

የሚፈጀው ‹‹የትሮይ ፈረስ›› ፊልም ባለፈው ሰኞ ነሐሴ 30 ቀን<br />

2003 ዓ.ም በብሔራዊ ቲያትር አዳራሽ በይፋ ተመረቀ።<br />

በቤተሰብ ተፅዕኖ ምክንያት ወንድ ቀርባ የማታውቅ አንዲት<br />

ቆንጆን ለመርታት በሚደረግ ጥረት ላይ የታሪኩን ጨብጥ<br />

የመሠረተው ይህ ፊልም፣ በ1994 ዓ.ም ለህትመት ከበቃው<br />

‹‹የትሮይ ፈረስና ሎሎች አጫጭር ታሪኮች›› ከተሰኘ መፅሐፍ<br />

መነሻ ሀሳቡ የተወሰደ መሆኑ በምርቃት ሥነ ሥርዓቱ ወቅት<br />

ተገልጿል። ይህም የሀገራችንን የአጫጭር ልብ ወለድ ደራሲዎች<br />

ሥራ በማግዘፍ፣ ደራሲዎችን ሊያበረታታ ይችላል ተብሏል።<br />

የፊልሙ ደራሲ አሳምነው ባርጋ ሲሆን፣ ዳይሬክተሩ ደግሞ<br />

አርቲስት ቢንያም ወርቁ ነው።<br />

አርቲስት ሰለሞን ቦጋለ፣ ጌታሁን ሰለሞን፣ ሸዋፈራሁ<br />

ደሳለኝ፣ ይገረም ደጀኔ፣ እፀህይወት አበበና ሎሎች ታዋቂና<br />

አዳዲስ ተዋናዮችም ተሳትፈውበተል። ፊልሙን ሰርቶ<br />

ለማጠናቀቅም 580 ሺህ ብር ወጪ መጠየቁም ታውቋል።<br />

እንዲሁም በኤሊያስ ወርቅነህ ፕሮዲዩስ ተደርጎ በጋላክሲ<br />

ፊልም ፕሮዳክሽን የቀረበው ‹‹ገንዘብና ፍቅር›› ፊልም ሀሙስ<br />

በ8፡00 ሰዓት በሀገር ፍቅር ቲያትር ቤት የኪነ-ጥበብ አፍቃሪያን<br />

ታዋቂ ሰዎችና ጥሪ የተደረገላቸው አንግዶች በተገኙበት<br />

ተመርቋል። አስቂኝ የሆነው ይህ የፍቅር ፊልም 1፡40 ሰዓት<br />

ርዝመት ያለው ሲሆን በርካታ ተዋንያን እንደተሳተፉበትም<br />

ተገልጿል።<br />

‹‹ንቃት›› ፊልም ዛሬ ይመረቃል<br />

በደራሲና አዘጋጅ ዮናስ ጌታቸው ተሰርቶ በሰርድ አይ ፊልም<br />

ፕሮዳክሽን የቀረበው ‹‹ንቃት›› ፊልም ዛሬ በአዲስ አበባ ቴአትርና<br />

ባህል አዳራሽ ይመረቃል። ፊልሙን ሰርቶ ለማጠናቀቅ ከአንድ<br />

ሚሊዮን ብርና ከሁለት አመት በላይ መፍጀቱን አዘጋጆች<br />

ለአውራምባ ታይምስ በላኩት መግለጫ አስታውቀዋል። ልብ<br />

አንጠልጣይ የፍቅር ፊልም እንደሆነ የተነገረው ‹‹ንቃት›› ህዝቡ<br />

ስለ ኤች. አይ. ቪ ግንዛቤ ቢኖረውም ችግሩ ባለመቀረፉ ላይ<br />

እንደሚያጠነጥን እንዲሁም ሙሉ በሙሉ በአሜሪካ አገር<br />

መሠራቱን ጨምረው ገልፀዋል።<br />

ፋንቱ ማንዶዬ 60ኛ የልደትና<br />

44ኛ የሞያ ቆይታውን አከበረ<br />

አንጋፋው የጥበብ ሰው አርቲስት ፋንቱ ማንዶዬ 60ኛ<br />

የልደት በአሉንና 44ኛ የኪነ-ጥበብ ቆይታውን ባለፈው ማክሰኞ<br />

በደማቅ ሁኔታ አከበረ። ጳጉሜ 1 ቀን በአዲስ አበባ ቲያትርና<br />

ባህል አዳራሽ ከቀኑ 8ሰዓት ጀምሮ በተዘጋጀው በዚህ ፕሮግራም<br />

ላይ እጅግ በርካታ የሙያ አጋሮቹ ተገኝተው እንኳን አደሰረህ<br />

ብለውታል። በእለቱ በአርቲስት ተስፋዬ አበበ (ፋዘር) የተፃፈ<br />

‹‹እሱ ማን ነው›› የተሰኘ ህብረ ዝማሬ በተስፋዬ ቲያትር<br />

ማደራጃ አባላት የቀረበ ሲሆን የተለያዩ ስጦታዎችና ሽልማቶች<br />

ለአርቲስት ፋንቱ ተበርክተውለታል። በኪ- ጥበብ ቆይታው<br />

33 የመድረክ ቴአትሮችን፣ 11 የቴሌቪዥን እንዲሁም ሁለት<br />

ተከታታይ የሬዲዮ ድራማዎችን መስራቱ ተገልጿል።<br />

ጥበብ ሀበሻ በልዩ ፕሮግራም<br />

በአሉን ሊያከብር ነው<br />

በሀበሻ ሚዲያና ፕሮሞሽን ሰርቪስ የሚቀርበው ‹‹ጥበብ<br />

ሀበሻ›› የሬዲዮ ፕሮግራም አውድ አመቱን አስመልክቶ ልዩ<br />

የኪነ-ጥበብ ፕሮግራም አዘጋጀ። ዘወትር አርብ ከ9-11 ሰዓት<br />

እና ዘወትር እሁድ ከ6-8 ሰዓት በኪነ-ጥበብ፣ በቤተሰብና በፍቅር<br />

ዙሪያ የመረጃ ፕሮግራሞችን በ96.3 ኤፍ ኤም የሚያቀርበው<br />

ጥበብ ሀበሻ በበዓሉ ዋዜማ ምሽት ከ3-6 ሰዓት የተለያዩ ታዋቂ<br />

ሰዎችን፣ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎችንና አዝማሪዎችን በመጋበዝ<br />

በቀጥታ ሥርጭት እንደሚያስተላልፍ የፕሮግራሙ አዘጋጅ<br />

አብርሀም ግዛው ገልጿል።<br />

እንኳን አደረሰህ ግዛቸው!<br />

እንኳን አብሮ አደረሰን! ሰላም ነው?<br />

በአሉን ለመቀበል ምን ምን ዝግጅቶች እያደረክ ነው?<br />

እርግጥ ብዙ ዝግጅት አላደርግም። ግን ያው<br />

እንደማንኛውም ሰው ማድረግ የሚገባኝን<br />

አደርጋለሁ።<br />

ዘመን መለወጫ ሲመጣ ምን ምን የምታስታውሰው ነገር አለህ?<br />

አዲስ ዓመት ሲመጣ ከሌሎቹ በአላት ለየት<br />

የሚልበት የራሱ ድባብ አለው፡፡ በውስጥሽ<br />

የአዲስነትና የተስፋ ስሜት ያጭራል፡፡ እንደገና<br />

ደግሞ በዓሉ በየትኛውም በሳምንቱ ቀናት ሊሆን<br />

ይችላል። እስከዛሬ ለዋዜማው ስንሰራ ኢቭ እሁድ<br />

ቀን ውሎ አላስታውስም። የዘንድሮው ኢቭ እሁድ<br />

መሆኑ በራሱ ደስ ይላል። አመት በዓል ሲመጣ<br />

ቤት ውስጥ የሚደረገው ሽርጉድ ድባቡ ሁሌም<br />

ይታወሰኛል። ከዛ በተረፈ የተለየ የማስታውሰው<br />

ነገር የለም። በእያንዳንዱ አመት እቅዶች ስላሉኝ<br />

እነሱን አስታውሳለሁ።<br />

በ2003 ምን አቅደህ ምን ተሳካልህ?<br />

የተወሰኑ ነገሮች አቅጀ ነበር። በእቅዴ ያልተካተቱ<br />

በርካታ ነገሮችም ተሳክተውልኛል። ራሴን አንደ<br />

እድለኛ እቆጥራለሁ። ይሄ ነው ያ ነው ከማለት<br />

ተቆጥቤያለሁ። ይህ የእግዚአብሔር ስራ ነውና።<br />

ለበዓል በግ የመግዛት ልማድ አለህ?<br />

አዎ። እገዛለሁ።<br />

ለዚህ በዓል በግ ገዝተህ ቢጠፋ፣ ቢሞት፤ አሊያም በመኪና ቢገጭ<br />

ደግመህ ትገዛለህ ወይስ ለእኔ ባይለው ነው ብለህ ትተወዋለህ?<br />

[በጣም እየሳቀ] ይሄ ከባድ ጥያቅ ነው፡፡ ግን በጉ<br />

ባልሽው መንገድ አደጋ ቢደርስበት ከእኔም ሆነ<br />

ከቤተሰቦቼ ደስታ አይበልጥምና ደግሜ እገዛለሁ<br />

እንጂ አይገርመኝም። ዋናው እኔ ደህና ልሁን<br />

እንጂ ምናባቱ።<br />

ኃብታም ነኝ ለማለት ነው?<br />

እንደዛ ሳይሆን የበጉ መሞት ወይም መጥፋት<br />

ከደስታዬ አይበልጥም ለማለት እንጂ ዋጋው ቀላል<br />

ነው ለማለት አይደለም።<br />

ዶሮ መገነጣጠል ትችላለህ?<br />

እኔ ኧረ አልችልም! እንዴት አይነት ነገር ነው<br />

ባካችሁ?! ምን መሰለሽ፤ በአል ሲሆን ቄጤማው፣<br />

የቡና ስነ-ስርዓቱ፣ ሬዲዩው የሚዘፍነው የበዓል<br />

ዘፈን . . . ሁሉ ነገር ደስ ስለሚለኝ እቤት ዶሮ<br />

ሲሰራ፣ ሲገነጣጠል አያለሁ፤ አብሬም እሆናለሁ፡፡<br />

ግን ዶሮ መገነጣጠልን አስቤው አላውቅም።<br />

በበዓል ብዙ ምግብ በልተህ ታውከህ ታውቃለህ?<br />

የባሠ አታምጣ! [ረዥም ሳቅ] በመጀመሪያ ደረጃ<br />

የምግብ ፍላጎቴ ጥርቅም ብሎ የሚዘጋው በበዓል<br />

ጊዜ ነው። እንኳን ብዙ በልቼ ልታወክ ይቅርና።<br />

በልጅነትህ አበባ ስለህ እየዞርክ ትሰጥ ነበር?<br />

አዎ በጣም! አበባ ስዬ መስጠት ብቻ ሳይሆን<br />

ከየህፃናቱ በ10 ሳንቲም እየገዛሁ እኔ በ15ና<br />

በ25 ሳንቲም የመሸጥ ቢዝነስ ጀምሬ አትራፊ<br />

የነበርኩበትን ጊዜ አስታውሳለሁ። ይሄ እንደውም<br />

ለዚህ በዓል መታሰቢያ ይሁንልኝ፡፡ የሚገርምሽ<br />

አበባ በመሳልም በኩል የሚስተካከለኝ አልነበረም።<br />

ዲዛይነር ነበርኩ ማለት ይቻላል።<br />

የምትስላቸውን ነገሮች ታስታውሳለህ?<br />

አደይ አበባ፣ የሚካኤልን ሥዕል፣ አደይ አበባ ላይ<br />

መስቀል በመሳል መልካም አዲስ ዓመት የሚል<br />

እፅፍና አመተ-ምህረቱን ከጎኑ አድርጌ እስል ነበር።<br />

ቀለም የምገዛው ወይዘሮ ማሚቱ ከሚባሉ የልብስ<br />

ቀለም ከሚሸጡ ሴትዮ ነበር። ቀጨኔ የታወቁ<br />

የልብስ ቀለም ሻጭ ነበሩ። [ቀጨኔ የሽመና ሥራ<br />

የሚካሄድበት አካባቢ መሆኑን ልብ ይሏል።]<br />

ቀለሙን ከገዛሁ በኋላ መጀመሪያ ሸንበቆ እፈልግና<br />

እዛ ላይ ጥጥ እጠመጥማለሁ። ከዛም መቀባት ነው<br />

አልኩሽ።<br />

ስኬች ያደረከው ላይ ማለት ነው?<br />

እንዴ! ተይ እንጂ! ሀበሽኛ አድርጊው እንጂ።<br />

‘ዲዛይን ያደረግከው ላይ’ ለማለት ነው። [‘ዲዛይን’ም<br />

እኮ ግን . . . ???]<br />

1<br />

አፍታ<br />

“እኔ ጋር ሥራ እንጂ ውበት<br />

የሚባል ነገር የለም”<br />

ድምፃዊ ግዛቸው ተሾመ<br />

በባህል ዘፈኖቹ በዙዎች ጎጃም ተወልዶ እንዳደገ ቢገመቱም እሱ ግን የአዲስ አበባ ልጅ መሆኑን ይገልፃል። ከተለያዩ ድምፃውን ጋር በጋራ አልበም በማውጣት ወደሙዚቃው ጠልቆ የገባ ሲሆን<br />

በ2001 ዓ.ም ‹‹ይሁና›› የሚል የራሱን አልበም በመልቀቅ ተደማጭነትን አግኝቷል። ውበቴ ሥራዬ ነው ከሚለው ድምፃዊ ግዛቸው ተሾመ ጋር ናፍቆት ዮሴፍ አዝናኝ ቆይታ አድርጋለች።<br />

እሺ ‘ዲዛይን’ ያደረከው [የነደፍከው]ላይ? ሂሴን ውጫለሁ<br />

እና እልሻለሁ አበባ ገዝቶ በመሸጥም በመሳልም<br />

አንደኛ ነበርኩ።<br />

የሠርግ ሥራ ሽቀላው እንዴት ይዞሀል?<br />

ኧረ በጣም አሪፍ ነው! በነገራችን ላይ ከሽቀላ አንፃር<br />

ብቻ አትይው፡፡ በተለይ ሰዎች በሠርጋቸው እለት<br />

ሲደሰቱ ማየት ምን ያህል እንደሚያረካ ልነግርሽ<br />

አልችልም። ሽቀላው እንዳለ ሆኖ ማለት ነው። እናም<br />

እኔ ራሱ የሠርግ ካሴት ሰርቼ አጠናቅቄያለሁ።<br />

ከ2004 እቅዴ አንዱ እሱን ማሳካት ነው።<br />

ቢሰራም ባይሰራም በአዲስ አመት ዕቅዶች ይታቀዳሉ። ከካሴቱ ውጭ<br />

ምን ያቀድከው ነገር አለ?<br />

ከላይ የለገፅኩት የሰርጉን ካሴት ለአድማጭ ማድረስ<br />

አንዱ ነው። ሌላው በ2004 ካቀድኩት ውስጥ የራሴን<br />

ባንድ አቋቁሜ በራሴ ባንድ ሰርግ መስራት ነው።<br />

የእግዚአብሔር ፈቃዱ ይሁን።<br />

አንዳንድ ሰዎች መጠጥ የማይወዱ ቢሆኑም እንኳን በአል ሲመጣ<br />

ከተለያዩ መጠጦች ይቀማምሳሉ። ከቢራውም፣ ከጠጁም፣<br />

ከጠላውም፣ ከውስኪውም . . . ። አንተ በበአል ምን መጠጣት<br />

ያስደስትሀል?<br />

እኔ የማልዋሽሽ ነገር፣ እናቴ ቤት ሁሌም በበአል ጠጅ<br />

አለ። ጠጁ ልስልስ ያለና ለተማሪ የሚሰራ አይነት<br />

ነው። ወደ ብርዝ የሚያደላ ማለት ነው። እናቴ ቤት<br />

እሱን ቁጭ ብዬ ስጠጣ ትክክለኛ የአመት በአል<br />

ስሜት ይሰማኛል። በተረፈ ከዚህ በላይ ለመጠጥ ብዙ<br />

ፍላጎት የለኝም።<br />

እንጉርጉሮህን የሰሙ ብዙዎች ግዛቸው ጎጃሜ ነው እንደሚሉ<br />

ታውቃለህ?<br />

በመጀመሪያ እኔ ጎጃሜ ብሆን ደስ ነው የሚለኝ።<br />

ከዛ በላይ ግን ኢትዮጵያዊ ነኝ። ይህ ደግሞ በጣም<br />

ያኮራኛል፡፡ እንደዛም ሆኖ ተወልጄ ያደግኩት<br />

አዲስ አበባ ውስጥ ቀጨኔ መድኃኒያለም<br />

አካባቢ ነው።<br />

ከመልክና ከቁመና ጋር በተያያዘ የግዛቸው ውበቱ<br />

አንገቱ ነው ይባላል፡፡ ትስማማለህ?<br />

የእኔ ውበቴ ወንድነቴ ነው።<br />

ወንድነቴ ስትል?<br />

ወንድ መሆኔ ነዋ!<br />

የአንገትህንስ ነገር ብዙ አትስማማበትም?<br />

እኔ አላውቅውም። እኔ ጋር ውበት<br />

የሚባል ነገር የለም። ሥራ ብቻ ነው።<br />

፡ ግን በጉ ባልሽው መንገድ አደጋ<br />

ቢደርስበት ከእኔም ሆነ ከቤተሰቦቼ ደስታ<br />

አይበልጥምና ደግሜ እገዛለሁ<br />

እንጂ አይገርመኝም።<br />

ዋናው እኔ ደህና<br />

ልሁን እንጂ<br />

ምናባቱ።<br />

በመጀመሪያ ወንድነቴ ነው ውበቴ ያልከኝ ወንድነት ብቻውን<br />

ውበት ነው ማለትህ ነው?<br />

ወዴት ወዴት! እኔ እንደዚህ ወጣኝ? ወንድ<br />

አሁን ቆንጆ ሆነ አልሆነ ለእኔ ግድ የለኝም።<br />

ሴት ልጅ ግን ውበትን በመቀባባትና በተለያዩ<br />

ዘዴዎች ታመጣዋለች። እኔ በግሌ ግን ቆንጆ<br />

ሆንኩ አልሆንኩ ግድ የለኝም። አላስበውምም።<br />

ስራ ላይ ነው ትኩረቴ።<br />

እናስ ቆንጆ ነኝ ብለህ ታምናለህ?<br />

ቆይ በናትሽ . . . ይሄ የሚያስጠላ ጥያቄ<br />

አይመስልሽም? [መመለስ አልፈለገም።]<br />

እስከዛሬ ፊት ለፊት ያላገኘኸው ግን ደግሞ የምታደንቀውና<br />

በዚህ አጋጣሚ እንኳን አደረሰህ ማለት የምትፈልገው ካለ?<br />

እኔ በጣም ደስ የሚሉኝና በጣም የማደንቃቸው<br />

ጠቅላይ ሚኒስትሩን ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር<br />

መለስ ዜናዊን፣ “እንኳን ለ2004 ዓ.ም አዲስ<br />

አመት ከነቤተሰብዎ በሰላም አደረሰዎት! አመቱ<br />

የጤና፣ የሰላምና መልካም የአመራር ጊዜ<br />

እንዲሆንልዎ እመኝልዎታለሁ!” በይልኝ።<br />

ለኢትዮጵያ ህዝብ የትኛውን ዘፈንህን ልጋብዝልህ?<br />

በመጀመሪያ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ እንኳን<br />

ለአዲሱ አመት በሰላም አደረሳችሁ በይልኝ። ከዛም<br />

‹‹አውዳመቱ›› የተሰኘውን ዘፈን ጋብዣቸዋለሁ።<br />

አመሰግናለሁ።<br />

11<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ


12<br />

በኤልያስ ገብሩ<br />

ከተቋቋመ ሦስት ዓመታትን ያስቆጠረው<br />

ጃካራንዳ ኢንተግሬትድ አግሮ ኢንዱስትሪ<br />

አ.ማ በተለያዩ ጊዜያቶች ለሀገር ውስጥ<br />

መገናኛ ብዙሃን የሚያዘጋጃቸውን የመስክ<br />

ጉብኝቶች መሠረት በማድረግ የአውራምባ<br />

ታይምስ ዝግጅት ክፍል እሁድ ነሐሴ<br />

29/2003 ዓ.ም ድርጅቱ ተግባራዊ ሥራውን<br />

እያከናወነ በሚገኝበት በአዋሽ መልካሳ<br />

የግብርና መስክ ላይ ከቀትር ጀምሮ ተገኝቶ<br />

ነበር፡፡ ምንም እንኳን ያለነው በክረምት ወራት<br />

መገባደጃ ላይ ቢሆንም፣ በወቅቱ በአዋሽ<br />

መልካሳ የከረረ ፀሀይ ሳይኖር የሙቀት ወበቁ<br />

ግን ከላይ የተደረበ ልብስን የማስወለቅ አቅም<br />

ነበረው፡፡<br />

አዋሽ መልካሳ ደርሰን ከናዝሬት ወደ አሰላ<br />

በሚወስደው ዋና መንገድ በስተቀኝ በኩል<br />

በሚገኝ ኮረኮንጅ መንገድ ወደ ውስጥ ጥቂት<br />

መቶ ሜትሮች በመኪና ከገባን በኋላ አንድ<br />

አነስተኛ ድልድይ ጋር ደርሰን በመቆም<br />

ከመኪና ወረድን። ቀጥሎም፣ ለመስክ ጉብኝቱ<br />

በስፍራው ለነበርነው ለዚህ ፅሁፍ አቅራቢና<br />

ለአውራምባ ታይምስ ማኔጂንግ ኤዲተር<br />

ዳዊት ከበደ፣ የአክሲዮን ማሕበሩ የቦርድ<br />

ሊቀመንበርና ዋና ሥራ አስኪያጅ የሆኑት<br />

አቶ ደምመላሽ ወጋየሁ ገለፃ ያደርጉልን<br />

ጀመር<br />

ጥናትን መሠረት<br />

ያደረገ የውኃ ጠለፋ<br />

በጠባቧ ድልድይ ሥር 400 ኩንታል<br />

ክብደት ያለው ኮንክሪት ድንጋይ ተቀብሯል፡<br />

- ወደ ወንጂ ስኳር ፋብሪካ የሚሄዱ ከባድ<br />

ተሽከርካሪዎችን መሸከም እንዲችል ታስቦ፡፡<br />

ከድልድዩ በስተቀኝ የተወሰኑ ሜትሮች ራቅ<br />

ብሎ የአዋሽ ወንዝ እንደደፈረሰ በእርጋታ<br />

ተፈጥሯዊ ጉዞውን ሲያደርግ ይታያል፡፡<br />

የውሃ ሥራዎች ዲዛይንና ቁጥጥር ባለስልጣን<br />

መ/ቤት በወንዙ ላይ በቂ ጥናት አድርጎ<br />

ጃካራንዳ ኢንተግሬትድ አግሮ ኢንዱስትሪ<br />

አ.ማ እያካሄደ ለሚገኘው የልማት ሥራ<br />

አገልግሎት እንዲሰጥ ሁለት ኪሎ ሜትር<br />

የውሃ መስመር ጠለፋና የቦይ ግንባታ<br />

መሥራቱን አቶ ደምመላሽ ይናገራሉ፡፡<br />

በሚፈልገው አቅም ውሃ እንዲያመጣ ተደርጎ<br />

በግንብ በተሰራው ቦይ ውስጥ የሚያልፈው<br />

ውሃ በተገቢ የውሃ ፍሰት ቀመር የተስተካከለ<br />

በመሆኑ በአካባቢው የሚገኙትን የሕብረተሰብ<br />

የግብርና ማሳዎች ከጎርፍ ለመከላከል ትልቅ<br />

ድጋፍ ይሰጣል።<br />

በተፈጥሮ የስበት ኃይል አማካኝነት<br />

አንድ ኪሎ ሜትር ያህል የሚጓዘው ይኼ<br />

የተጠለፈው ውሃ ጃካራንዳ በሰራው መጠነኛ<br />

ግድብ ውስጥ ለመጠራጠም ይገደዳል።<br />

[ሌላው አንድ ኪሎ ሜትር በግፊት ኃይል<br />

የሚንቀሳቀስ ነው] በውሃው መሄጃ ግራና<br />

ቀኝ፣ በተለይም በስተግራ በኩል ያሉት<br />

እንደ ዝግባ፣ ግራርና ባህር ዛፍን የመሳሰሉ<br />

ዛፎች፣ ቁጥቋጦዎችና ሳሮች ከሌላው በተለየ<br />

መልኩ ለምልመው ይታያሉ። …‹‹እነዚህ<br />

በፊት ውሃ በአጠገባቸው በማያልፍበት ጊዜ<br />

የመቅላትና የመድረቅ ባህሪ ነበራቸው››<br />

በማለት ስለሁኔታው በንፅፅሮሽ የገለፁት አቶ<br />

ደምመላሽ፣ በጥናት ተመርኩዞ የተካሄደው<br />

የውሃ ጠለፍ ሥራ በአካባቢው ሥነ-ምህዳር<br />

ላይ አዎንታዊ ለውጥ ማምጣቱን በአፅንዎት<br />

ይናገራሉ። በእርግጥም ለዚህ ጥሩ ምስክር<br />

የሚሆን ነገር ወዲያው ተመለከትን፡፡<br />

በግድቡ አጠገብ ቅርንጫፎቻቸው ተንዥርግጎ<br />

አንገታቸውን ወደ መሬት ዳፋ ባደረጉት<br />

የግራር ዛፎች ላይ በሕብረ-ቀለማት ያሸበረቁ<br />

ወፎች ጎጇቸውን ቀልሰው በነፃነት እየዘመሩ<br />

ነበር።<br />

ጥቅመ- ብዙዋ ትንሿ ግድብ<br />

በአጠቃላይ 300 ሜትር ርዝመትና 10<br />

ሜትር የጎን ስፋት ያላት ትንሿ ግድብ ከጥቂት<br />

ወራቶች በኋላ ለመስኖ ልማት፣ ለከብቶችና<br />

ፍየሎች መጠጥ ውሃና ለሌሎች አገልግሎቶች<br />

ጥቅም ለመስጠት ተዘጋጅታለች። በግድቢ<br />

ውስጥም 11 ሺህ አሳዎች በመርባት ላይ<br />

ሲገኙ ከእነዚህም መካከል አንድ ሺህ ያህሉ<br />

ለቻይናዊያኖች ተሽጠዋል፡፡ በቀጣዩ ዓመት<br />

መስከረም ወር ደግሞ የሚረቡት አሳዎች<br />

ቁጥር 40 ሺህ እንደሚደርስ የሚናገሩት<br />

አቶ ደምመላሽ፣ ይህንን በተመለከተ የሰበታ<br />

አሳ ምርምር ድርጅት ተመራማሪዎች ጥናት<br />

ማካሄዳቸውን ይገልፃሉ። ከግድቡም በላይ<br />

ትንሽ ሞልቶ የሚፈስሰው ውሃ ተመሳሳይ<br />

መንገድን ተከትሎ ወደ ሌላኛው የአካባቢ ስፍራ<br />

በአነስተኛ መጠን ሲጓዝ ይታያል፡፡ ሆኖም<br />

ግን፣ እንደ አክስዮን ማህበሩ ኃላፊ ንግግር<br />

ከሆነ ጃካራንዳ ይኼንን የውሃ መስመር 300<br />

ሜትር ያህል አስተካክሎ በማዘጋጀት ሌላ<br />

ተመሳሳይ የአሳ ማርቢያ ግድብ ለመስራት<br />

የአጭር ጊዜ ዕቅድ ነድፏል።<br />

ከግድቡ ጎን ከፍ ብሎ ደግሞ አዲስ<br />

የተሰራ የውሃ መሳቢያ ፓምፕ የሞተር<br />

ክፍል የሚገኝ ሲሆን፣ በኤሌክትሪክ ኃይል<br />

የሚሰራው ይኼ ፓምፕ 90 ኪሎ ዋት<br />

ኃይል ሲኖረው በሰኮንድ 75 ሊትር ውሃ<br />

የመሳብ አቅመ አለው። ይኼም በ45 ሜትር<br />

ርቀት ላይ ተሰርቶ ሙሉ በሙሉ ሊጠናቀቅ<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

ለተቃረበውና ሲያልቅ አምስት ሺህ ኪውቢክ<br />

ሊትር ውሃ የመያዝ አቅም ላለው የውሃ<br />

ማጠራቀሚያ ገንዳ (Reservoir) ውሃን<br />

በፍጥነት ያቀብላል። አንዴ በገንዳው ውስጥ<br />

የሚጠራቀመው ውሃ ለአንድ ሳምንት<br />

ያህል ለካምፓኒው የተለያዩ ስራዎች<br />

አገልግሎት በቂ እንደሆነ የተናገሩት አቶ<br />

ደምመላሽ፣ የውሃ መስመሮች ተዘርግተው<br />

መጠናቀቃቸውንና የኤሌክትሪክ ኃይል<br />

አቅርቦት ለማግኘት ደግሞ ትራንስፎርመር<br />

በጥሩ ሁኔታ መተከሉን ያስረዳሉ፡፡<br />

ሕብረተሰብን ያማከለ ልማት<br />

እስከ ግድቡ ድረስ ባሉት መሬቶች ግራና<br />

ቀኝ ከሚገኙት ቦታዎች መካከል ሁለት<br />

ሁለት ሜትር ብቻ ለጃካራንዳ የሥራና<br />

የመንገድ አገልግሎት በመተው በቁጥቋጦ<br />

በተለይም፣ በቁልቋል የተሸፈኑትን መሬቶች<br />

በመመንጠር በአካባቢው ለሚገኙ 500 ያህል<br />

ወጣቶች ለግብርና ልማት እንዲጠቀሙበት<br />

በዕቅድ ተነድፎ ወደ ሥራ እየተገባ ያለበት<br />

ሁኔታ መኖሩን ኃላፊው ይገልፃሉ። በጉዳዩ<br />

ዙሪያም፣ ከፌዴራል <strong>መንግስት</strong> የኦሮሚያ<br />

ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት ም/ኮሚሽነር<br />

አቶ ሳሙኤል ገዳ ጋር በአካል ተገናኝቶ<br />

በመምከርና አካባቢውን በማስጎብኘት ጥሩ<br />

መግባባት ላይ ተደርሶ ይሁንታ ሊገኝበት<br />

ችሏል። ለወጣቶቹም የተለያዩ የአትክልት<br />

ችግኞችን፣ ዘሮችንና የውሃ አቅርቦትን<br />

የሚሰጣቸው ጃካራንዳ ነው፡፡ ‹‹በአሁን<br />

ወቅት የአካባቢው ሕብረተሰብ ለድርጅታችን<br />

ያለው አመለካከት በጣም መልካም ነው፡<br />

፡ ሕብረተሰብን ያላማከለ ልማት ውጤታማ<br />

አይሆንም፡፡ ከሥራችን ጎን ለጎን ሕብረተሰቡ<br />

ተጠቃሚ እንዲሆን እንፈልጋለን›› ሲሉ<br />

የገለፁልን አቶ ደምመላሽ፣ ከዚህ ቀደም<br />

ተሰርቆባቸው የነበረውን የውሃ መሳቢያ<br />

ፓምፕ ሕብረተሰቡ ተከታትሎ ማስመለሱን<br />

በመልካም አርያነት ያስታውሱታል፡፡<br />

እንደመሬቱ አመቺነት መስራት<br />

የጃካራንዳ ኢንተግሬትድ አግሮ ኢንዱስትሪ<br />

አ.ማ ለሥራ የተሰጠው አብዛኛው መሬት<br />

ለግብርና ልማት በጣም የማያመች መሆኑ<br />

ይገለፃል፡፡ በዓይን አይቶ ምስክርነት<br />

ለመስጠትም ቀላል ነው። አክሲዩን ማሕበሩን<br />

በመጀመሪያዎቹ ወራት ከገጠሙት ችግሮች<br />

መካከል ተፈጥሯዊ የሆኑት ተጠቃሽ ናቸው።<br />

አካባቢው ቀደም ብሎ በቁጥቋጦ ተሸፍኖ<br />

የነበረ ሲሆን የአካባቢው ቀደምት ‹ነዋሪዎች›<br />

የነበሩትን ጅብ፣ ዘንዶ፣ ጊንጥ፣ እና እባብን<br />

ለማባረር ፈታኝ መሆኑ ይታወሳል።<br />

ነገር ግን፣ ቁጥቋጦዎቹ እየተመነጠሩ፣<br />

አካባቢውን የተቆጣጠሩት የእሳት ጎመራ<br />

ውጤት ድንጋዮች ተለቅመው እየተቆሩ<br />

ለግንባታ፣ ለሽያጭና ለቋሚ አትክልትና<br />

ፍራፍሬ ተክሎች ምርት አካባቢው ምቹ<br />

ወደመሆን እየመጣ ነው - ባላሰለሰ የሥራ<br />

ጥረትና ትጋት። ይኼንንም አስመልክቶ<br />

አቶ ደምመላሽ እንዲህ ሲሉ ይገልፃሉ፡<br />

- ‹‹እንደሥራው አመቺነት ሳይሆን እንደ<br />

መሬቱ አመቺነት እየተሰራ ነው።››<br />

አትክልትና ፍራፍሬዎችና<br />

ችግኝ ጣቢያ<br />

ከጃካራንዳ ሳይት አቅራቢያ በኢትዮጵያ<br />

ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የመልካሳ<br />

ግብርና ምርምር ማዕከል ይገኛል። የማዕከሉ<br />

ተመራማሪዎች በሙያ ነክ ጉዳዩች ዙሪያ<br />

የጃካራንዳ አጋሮች ናቸው። ለዚህም ነው<br />

የተሻለ ምርት ሊሰጡ የሚችሉ የቋሚ<br />

አትክልትና ፍራፍሬ ዝርያዎችን ማዕከሉ<br />

ለጃካራንዳ ሰጥቶ በማዳቀል የተወሰኑ<br />

ፍራፍሬዎች በጥሩ ሁኔታ አፍርተው ማየት<br />

የተቻለው።<br />

ቀደም ሲል በ2500 ካሬ ሜትር መሬት<br />

ላይ 250 እግር ማንጎዎች ተተክለው ነበር።<br />

በአሁን ወቅት እነዚህ በግንዶቻቸው ላይ<br />

በርካታ ፍሬዎችን አፍርተዋል። እንዲሁም<br />

ተጨማሪ 750 እግር ያህል ማንጎዎች በቅርቡ<br />

የተተከሉ ሲሆን፣ በአጠቃላይ የሚተከሉት<br />

ማንጎዎች ለአምስት ዓመታት ያህል<br />

በጥራትና በብቃት ተመርተው እንደሚለቀሙ<br />

የአቶ ደምመላሽ ሀሳብ ነው። አቦካዶና ሙዝን<br />

የመሳሰሉ የፍራፍሬ ተክሎችም የጃካራንዳ<br />

ሌሎች የልማቱ ፍሬዎች ናቸው።<br />

በሌላ በኩል ደግሞ፣ 150 ሜትር ርዝመትና<br />

መጠነኛ የጎን ስፋት ባላት አነስተኛ ችግኝ<br />

ጣቢያ (Nursery) ውስጥ ፓፓዬ 200 ሺህ፣<br />

አቦካዶ አንድ ሺህና ማንጎ 400 እግር<br />

ያህል ችግኞች በመፍላት ላይ ይገኛሉ።<br />

የችግኝ ጣቢያው ዋና ዓላማም የከብቶች<br />

ፍግና ተረፈ ምርቶችን (Waste product)<br />

በተፈጥሮ ማዳበሪያነት በመጠቀም ለችግኞቹ<br />

አመቺ ሁኔታን በመፍጠር በቅድሚያ<br />

ለድርጅቱ ልማት፣ ሲተርፍ ደግሞ ለሌሎች<br />

አልሚዎችና ገበሬዎች ችግኞችን መሸጥ<br />

መሆኑን ኃላፊው ይገልፃሉ።<br />

ከብቶች፣ ፍየሎችና ዛፎች<br />

አክስዩን ማሕበሩ ከዚህ ቀደም<br />

እንደሚያደርገው ሁሉ የሚደልቡ ከብቶችን<br />

ከቦረናና ሞያሌ ገዝቶ በማምጣት ሰንጋዎቹ<br />

ተገቢው ክብደት ላይ ሲደርሱ ከነቁማቸው<br />

ወደ ውጭ ሀገራት (ግብፅና አረብ ሀገራት)<br />

ለሽያጭ ይቀርባሉ። በጥር ወር 2003<br />

ዓ.ም ላይ ይኼንን አስመልክቶ አውራምባ<br />

ታይምስ በሰራው ዘገባ ላይ ሰንጋዎቹ ወደ<br />

ማደለቢያው ጣቢያው ሲገቡ ክብደታቸው<br />

ከ270 ኪ.ግ እንደማይበልጥ፣ ለሶስት<br />

አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />

መልካም ዓዲስ ዓመት<br />

እንደ ስሙ በማበብ ላይ ያለው<br />

ጃካራንዳ<br />

ወራት በየቀኑ አስር ሊትር ውሃ እየተቀለቡ<br />

ለሽያጭ ብቁ እንደሚሆኑና ክብደታቸው<br />

እስከ 400 ኪ.ግ እንደሚመዝን፣ እንዲሁም<br />

እነዚህን ለውጭ ገቢያ ብቁ ለማድረግ ሶስት<br />

ወራት እንደሚፈጅ አስፍሯል። በዕለቱ<br />

ያገኘናት የሥራ ተቆጣጣሪም ደልበው<br />

ወደ ውጪ ሃገራት የሚሸጡት ሰንጋዎች<br />

ዋጋቸው ከ6500-8000 ብር ድረስ መሆኑን<br />

ነግራናለች። በመስክ ጉብኝቱ ወቅት በቁጥር<br />

430 ያህል ሰንጋዎችና 213 ያህል ፍየሎች<br />

ነበሩ። የበረቶቹ ቁጥርም ከአራት ወደ ስድስት<br />

ከፍ ብሏል።<br />

በተጨማሪም፣ ድርጅቱ ከአዳማ ወረዳ<br />

ግብርና ፅ/ቤት ጋር በመመካከር የአካባቢውን<br />

የአግሮ-ኢኮሎጂካል ሥነ-ምህዳር ለመጠበቅና<br />

የሙቀቱን መጠን ለመቀነስ በማሰብ<br />

2800 ያህል የጃካራንዳና የድሬዳዋ ዛፎችን<br />

አሰበጣጥሮ በመትከል እየተንከባከቡ<br />

እንደሚገኙ አቶ ደምመላሽ ያስረዳሉ።<br />

ቀጣይ ዕቅዶችና ትግበራዎች<br />

አምስት ሺህ ኪውቢክ ሊትር ውሃ የመያዝ<br />

አቅም ካለው የውሃ ማጠራቀሚያ ገንዳ<br />

በስተቀኝ በኩል አምስት ሄክታር ቦታ ላይ<br />

መሬቱን አመቺ በማድረግ የዶሮ እርባታ<br />

በቀጣይ ወራት ለመጀመር መታቀዱን<br />

የአክስዮን ማሕበሩ የቴክኒክ ክፍል ኃላፊ<br />

የሆነው ወጣት ይስሃቅ ገ/እግዚያብሔር<br />

ገልፀዋል። እንዲሁም ማሕበሩ አሁን ከያዘው<br />

38 ሔክታር መሬት ውጪ ተጨማሪ 15<br />

ሔክታር መሬትን ለመጨመር ተገቢውን<br />

ነገር በማድረግ ከሚመለከተው የ<strong>መንግስት</strong><br />

አካልና የሕብረተሰብ ክፍል ጋር ተነጋግሮ<br />

የግል ይዞታው አድርጓል፡- በመሬቱ ላይ<br />

የተተከሉ አትክልትና ፍራፍሬ እና የተዘሩ<br />

ሰብሎች እስኪነሱ ከመጠበቅ ውጪ። የከብት<br />

ሥጋ እርድና ማቀነባበሪያ ሥራ ግንባታም<br />

የቀጣይ ዕቅዶች አንዱ አካል ነው።<br />

በግማሽ ቀን የነበረንን የመስክ ጉብኝት<br />

አጠናቅቀን በአካባቢው የነበረውን ሁኔታ<br />

በእርጋታ ስንመለከት ጃካራንዳ በእርግጥም<br />

በለውጥ ጎዳና ላይ መሆኑን በቀላሉ መገንዘብ<br />

ችለናል። የአክሲዮን ማሕበሩ የቦርድ<br />

ሊቀመንበርና ዋና ሥራ አስኪያጅ በሆኑት<br />

አቶ ደምመላሽ ላይ የተመለከትነው ጠንካራ<br />

የሥራ ፍላጎትና፣ ተነሳሽነትና የለውጥ ራዕይ<br />

ትልቅ ስሜትን የሚፈጥር ነበር። በመጨረሻም<br />

አቶ ደምመላሽ በአጋጣሚ ፈገግ የሚያደርግ<br />

ንግግርን ተናገሩ። የዚህ ፅሁፍ አቅራቢ<br />

የግብርና ባለሙያ እንደነበረ ሰሙና ትንሽ<br />

ኮስተርና ሳቅ በማለት፣‹‹ በጋዜጠኝነት ሙያ<br />

ወሬ እየፈለክ ወረቀት ከምትቀዳድ ይልቅ<br />

በሙያህ ገበሬ ሆነህ ብትሰራ ይሻልሃል፣<br />

የሚያዋጣው እሱ ነው።›› ሲሉ ተናገሩ።<br />

ቀደም ሲል በ2500 ካሬ ሜትር<br />

መሬት ላይ 250 እግር ማንጎዎች<br />

ተተክለው ነበር። በአሁን ወቅት<br />

እነዚህ በግንዶቻቸው ላይ በርካታ<br />

ፍሬዎችን አፍርተዋል። እንዲሁም<br />

ተጨማሪ 750 እግር ያህል<br />

ማንጎዎች በቅርቡ የተተከሉ ሲሆን፣<br />

በአጠቃላይ የሚተከሉት ማንጎዎች<br />

ለአምስት ዓመታት ያህል በጥራትና<br />

በብቃት ተመርተው እንደሚለቀሙ<br />

የአቶ ደምመላሽ ሀሳብ ነው።


አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />

መልካም ዓዲስ ዓመት<br />

13<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ


14<br />

በዓለም አቀፍ ሕግ በውጭ ሀገራት ለሚገኙ ዜጎች ሚኒስቴር መ/ቤቱ<br />

የሚያደርገው ከለላ ምንድን ነው?<br />

ወደ ዓለም አቀፍ ሕግ ከመሄዳችን በፊት የውጭ<br />

ጉዳይ ሚኒስቴር ካሉት የውጭ ተልዕኮዎች መካከል<br />

አንዱና ዋንኛው በውጭ ያሉ ዜጎችን መጠበቅ ነው።<br />

በውጭ ያሉ ኢትዮጵያውያንን መጠበቅ ሲባል ብዙ<br />

ጉዳዮች አብረው ይነሳሉ። አንደኛ እዛ ያሉ ዜጎች<br />

የሚፈልጓቸውን ሕጋዊ ሰነዶች ማዘጋጀትና ችግር<br />

ሲገጥማቸው ማገዝ ነው።<br />

ወደ ዓለም አቀፍ ሕጉ ስንመጣ፤ እያንዳንዱ ሕግ<br />

ከዓለም አቀፍ ሕግጋት እና ድንጋጌዎች ጋር ተጣጥሞ<br />

ነው መስራት ያለበት። ስለዚህ በዓለም አቀፍ ደረጃ<br />

ለሚንቀሳቀሱ ሰዎች የሚሰጡ ከለላዎች አሉ።<br />

ለምሳሌ ለስደተኞች የሚሰጥ መብት አለ። የተባበሩት<br />

መንግስታት ድርጅት ስለስደተኞች ያፀደቀው ድንጋጌ<br />

አለ። የእኛ ሕግጋትም ከእዛ ጋር የሚጣጣሙ ናቸው።<br />

ስለዚህ ዞሮ ዞሮ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ተልዕኮዎች<br />

ውስጥ አንዱ በውጭ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ከለላ<br />

መስጠት ነው።<br />

ተግባራዊነቱስ ምን ያክል ነው? ምክንያቱም ‹‹ችግር በገጠመን ጊዜ<br />

የሚሰማን የለም›› የሚሉ ቅሬታዎች አረብ ሀገራት ከሚገኙ ዜጎች<br />

ዘንድ በስፋት ይደመጣልና።<br />

እንግዲህ በተቻለ መጠን በውጭ በርካታ ኤምባሲዎችና<br />

ቆንፅላ ጽ/ቤቶች አሉ፡፡ አንዱም የችግሩ ምንጭ<br />

የሚመስለኝ [ከለላ ላለማግኘታቸው] ኤምባሲዎቻችን<br />

በሌሉባቸው ሀገራት ያሉ ዜጎቻችን ጉዳይ ነው።<br />

ይሄ መዋቅራዊ ችግር ነው። አቅም ስንገነባ<br />

ሊቀረፍ የሚችል ነው። ሁለተኛው የችግሩ ምንጭ<br />

ዜጎች ራሳቸው መከተል የሚገባቸውን አካሄዶች<br />

ስለማይከተሉ ነው። ለምሳሌ ኤምባሲዎች ባሉባቸው<br />

ሀገራት ያሉት ኤምባሲ ሄደው አይመዘገቡም።<br />

አድራሻቸውን አለማሳወቅና ችግር ሲከሰት ብቻ ወደ<br />

ኤምባሲ የመሄድ ነገር አለ።<br />

ዜጎችን እየወቀስኩ አይደለም፤ እነሱ ጋር የሚስተዋለው<br />

ችግር የሚመነጨው ምናልባት ከግንዛቤ እጥረት<br />

ይሆናል፤ አሊያም ኤምባሲ ሄዶ የመመዝገብን ጥቅም<br />

አሳንሶ ከማየት የመነጨ ይመስለኛል።<br />

ሶስተኛው አንተም እንዳልከው … እንግዲህ<br />

ኤምባሲዎች ውስጥ የሚሰሩት ሰዎች ናቸውና<br />

ከእነሱም ስህተት አይጠፋም። ከኤምባሲው ፖሊሲ<br />

በተቃራኒ እዛ የሚሠሩ ግለሰቦች ለዜጎች ተገቢውን<br />

ምላሽ ላይሰጡ ይችላሉ።<br />

በጋዳፊ ቤተሰቦች አስከፊ ጥቃት የደረሰባትን የሸዋዬ ጉዳይ <strong>መንግስት</strong><br />

እንዴት አየው?<br />

ይሄ በጣም አሰቃቂ ነው። ማንም <strong>መንግስት</strong><br />

በዜጋው ላይ እንዲህ ዓይነት ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት<br />

አንዲፈፀም አይፈልግም። መረጃው እንደደረሰንም<br />

ፈጥነን የልጅቱን ቤተሰቦች አነጋግረናል። ስለማንነቷ<br />

እና ስለአካሄዷ መረጃዎችን ተቀብለናል። ከዛም<br />

በዚህ ጉዳይ ላይ ተባብረን ልንሰራ የምንችላቸውን<br />

ወገኖች አነጋግረናል። አዲስ አበባ በሚገኘው የሊቢያ<br />

ኤምባሲ ካሉት አምባሳደር ጋርም ተነጋግረናል።<br />

አሁን የደረስንበት ውጤት ልጅቱ የተሻለ ሕክምና<br />

የምታገኝበት ሁኔታ መመቻቸት እንዳለበት ነው።<br />

በዚህ ረገድ የተያዙ አማራጮች አሉ፤ አንደኛው፣<br />

የማልታ <strong>መንግስት</strong> የሕክምና ወጪዋን ችሎ<br />

እንደሚያሳክማት እየገለፀ ነው። ሁለተኛው፣<br />

እንግሊዝና አሜሪካ ለማሳከም ጥያቄ አቅርበዋል።<br />

የትኛውን አማራጭ እንደምትጠቀም ልጅቷ ነች<br />

የምትወስነው። ሌላው የጉዞ ሰነድ በእጇ ስለሌለ<br />

የሚያስፈልጓት ሰነዶች እየተዘጋጁላት ነው።<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

ለሽግግር መንግስቱ ኢትዮጵያ ዕውቅና እንደመስጠቷ መጠን የጋዳፊን<br />

ቤተሰቦች ለመክሰስ <strong>መንግስት</strong> አስቧል?<br />

እንዳልከው ለሽግግር ካውንስሉ ዕውቅና ከሰጡ<br />

የአፍሪካ አገሮች አንዷ ኢትዮጵያ ነች። ጦርነቱ ገና<br />

አልተጠናቀቀም፣ የተረጋጋ ሁኔታም አልተፈጠረም።<br />

እንግዲህ ሁሉም ነገር ሲረጋጋ ነው ይሄን ጉዳይ<br />

ማንሳት የሚቻለው። ጉዳዩ በጣም ትኩረት የሚሰጠው<br />

ነው። ልጅቷ/ቤተሰቦቿ ካሳ የጠየቁበት ሁኔታ አለ ግን<br />

በ<strong>መንግስት</strong> ደረጃ ይሄን ለማድረግ መረጋጋት የግድ<br />

ነው።<br />

እዚህ ካለው የሊቢያ ኤምባሲ ጋር ‹‹ተነጋግረናል›› ብላችኋል …<br />

እነሱ ጉዳዩን እንዴት ነው ያዩት?<br />

በጣም ነው ያዘኑት። ሰውየውና ቤተሰቦቹ [ጋዳፊ]<br />

እንኳንና በሌላ ሀገር ዜጋ ቀርቶ በራሳቸው ዜጎች<br />

ላይም ከእዚህ የበለጠ ግፍ የሚፈፅሙ መሆናቸውን<br />

በመግለፅ አፅናንተውናል።<br />

በሌሎች አረብ ሀገራትም ያሉ ኢትዮጵያውያን ተመሳሳይ ወይም<br />

ከዚህ የባሰ ጥቃት ይፈፀምባቸዋል፤ ለዚህ ምክንያቱ ምንድን ነው?<br />

በተደጋጋሚ የምንናገረው ነገር አለ። አንደኛ፣<br />

ከአካሄዳቸው ጀምሮ ሊታዩ የሚገቡ ጉዳዮች አሉ።<br />

በሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አማካኝነት<br />

ዋስትና ተይዞላቸው የሥራው ሁኔታ ታውቆ፣<br />

ሰብዓዊነት በተከተለና ዓለም አቀፍ ሕግጋትን<br />

በተከተለ ሁኔታ ብዙዎች ሲሄዱ አይስተዋልም።<br />

ለዚህ ነው እንግዲህ በሕገ-ወጥ ደላላ አማካኝነት<br />

ያልሆነ ባዶ ተስፋ ተሞልተው የሚሄዱትና ትልቅ<br />

ችግር የሚያጋጥማቸው። አሰሪዎቹም በሕገ-ወጥ<br />

መንገድ የሚሄዱት ምንም ዋስትና እንደሌላቸው<br />

ስለሚያውቁ እጃቸው ለገባው ኢትዮጵያዊ ደህንነት<br />

አይጨነቁም።<br />

አረብ ሀገራት ያሉ ኢትዮጵያውያን ችግር ደርሶባቸው ለኤምባሲ<br />

በሚያመለክቱበት ጊዜ ‹‹ዞር በል፤ እኛ የመጣነው ኢንቨስተር<br />

ለመሳብ እንጂ ለአሽከር አይደለም›› የሚል መልስ እንደሚሰጣቸው<br />

ይገልፃሉ። በሌላ በኩል ደግሞ የኤምባሲዎች ዋና ዓላማ የኢህአዴግ<br />

ደጋፊ ዳያስፖራዎችን ማሰባሰብ መሆኑን የሚገልጹ አሉ … ዋና<br />

ተልዕኳቸው ምንድን ነው?<br />

በነገራችን ላይ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተሰጠው<br />

ተልዕኮ በውጭ የሚተገበረው በኤምባሲዎች<br />

አማካኝነት ነው። ለመ/ቤቱ ከተሰጠው ተልዕኮ<br />

አንዱ የኢትዮጵያን ልማት፣ ዴሞክራሲ እና ሰላም<br />

ሊደግፉ የሚችሉ ሥራዎችን በውጭ መስራት ነው።<br />

እነዚህም ኢንቨስትመንትን መሳብ፣ የውጭ ገበያ<br />

ማፈላለግና ጎብኚዎችን መሳብ ናቸው፡፡ ነገር ግን<br />

የዜጎችን መብቶች ማስጠበቅም ከዚሁ እኩል ትኩረት<br />

ተሰጥቶት የሚሰራ ነው።<br />

ስለዚህ ‹‹እኔ እዚህ ያለሁት ኢንቨስተር ለመሳብ ብቻ<br />

ነው›› የሚል ዲፕሎማት ካለ ያልገባው ነገር አለ ማለት<br />

ነው። ተልዕኮውን በደንብ አልተረዳም ማለት ነው።<br />

በእርግጥ የሥራችን ዋንኛው ትኩረት ኢኮኖሚያዊ<br />

ዲፕሎማሲ ነው። ሆኖም ኢኮኖሚያዊ ዲፕሎማሲን<br />

በደንብ ለማሳካት ውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን<br />

መብቶች ማስከበር የግድ ነው። ለሚሺነሪዎቻችንም<br />

በየጊዜው ስለተልዕኳቸው ሥልጠናዎች የሚሰጠው<br />

ለዚህ ነው።<br />

እዚህ ጋር አንድ ጥያቄ ላንሳ … አሁን ባለው ሁኔታ በውጭ የሚገኙ<br />

ኢትዮጵያውያን መብቶች አጥጋቢ በሆነ ደረጃ ተከብረዋል?<br />

ቅድም ባነሳናቸው ምክንያቶች ክፍተቶች የግድ<br />

ይኖራሉ። ወደ ኤምባሲ ሄዶ መመዝገብ አነስተኛ<br />

ግምት ስለተሰጠው ዜጎች ሄደው የመመዝገባቸው<br />

ሁኔታ በጣም አነስተኛ ነው። እንዲሁም በአቅም<br />

ውስንነት የተነሳ ኤምባሲ ባልከፈትንባቸው ሀገራት<br />

ያሉ ዜጎችን መብቶች ማስጠበቅ አዳጋች ነው።<br />

አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />

መልካም ዓዲስ ዓመት<br />

‹‹ከተፈፀመ ቆይቷል ግን ሲ.ኤን.ኤን እስኪዘግበው ድረስ<br />

እኛም ቤተሰቦቿም ምንም መረጃ አልነበረንም››<br />

ሸዋዬ ሞላ በተባለች ኢትዮጵያዊት ላይ በጋዳፊ ቤተሰቦች<br />

የተፈጸመው ኢ-ሰብዐዊ ጥቃት አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ ሱራፍኤል ግርማ<br />

ለወጣቷ እየተደረገ ስላለው ድጋፍና በአጠቃላይ በአረብ አገራት<br />

ስላሉ ኢትዮጵያዊያን ሁኔታ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ<br />

የሆኑትን አምባሳደር ዲና ሙፍቲን አነጋግሯል፡፡<br />

አምባሳደር ዲና ሙፍቲ<br />

በመሠረቱ ከሆነ አንድ ሥራ መቶ በመቶ ይከናወናል<br />

ብሎ መጠበቅ አዳጋች ነው። የዳያስፖራ ፖሊሲ<br />

ተዘጋጅቶ በውጭ ያሉ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገር<br />

ቤት መጥተው በልማት እንዲሳተፉ አንዳንድ ጥቅማ<br />

ጥቅሞችን በመስጠት ሁሉ እየጣርን ነው።<br />

‹‹ዳያስፖራ›› ሲባል የትኛው ዳያስፖራ ነው?<br />

በሁሉም ሀገራት የሚገኙ የኢትዮጵያ ዳያስፖራዎች<br />

አንድ ዓይነት ሁኔታ ላይ አይደለም ያሉት። ለምሳሌ<br />

ሰሜን አሜሪካና አውሮፓ ያሉ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ<br />

ያሉበትን ሀገር ዜግነት ይወስዳሉ። ስለዚህ እነዚህ<br />

ኢትዮጵያውያን ሳይሆኑ ‹‹ትውልደ ኢትዮጵያውያን››<br />

ነው የሚባሉት። ለእነሱ የሚሰጠው ድጋፍ እንደ<br />

ዜጋ አይደለም። ሌላው በአፍሪካ እና በኢሲያ ያሉ<br />

ዳያስፖራዎች ያሉበትን ሀገር ዜግነት ስለማያገኙ<br />

ኢትዮጵያውያን ናቸው። የሚያገኙት ጥቅምም<br />

እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ነው። ስለዚህ ፖሊሲው<br />

ሁለቱንም የሚመለከት ነው።<br />

የቆንፅላ ጽቤቶች ሥራ ምንድን ነው?<br />

የቆንፅላ ጽ/ቤቶች ከኤምባሲ ዝቅ ያሉ ሲሆን፣ ኤምባሲ<br />

በሌለበት ሀገር ውስጥ ሥራዎችን የሚያከናውኑ<br />

አካላት ናቸው፤ በተለይም ሕጋዊ ሰነዶችን ማዘጋጀትና<br />

ማረጋገጫ መስጠት። በነገራችን ላይ የኤምባሲና<br />

ቆንፅላ ጽ/ቤት አከፋፈት እንደየሀገራት ሁኔታ<br />

ይለያያል። የበለፀጉት ሀገራት በመላው ዓለም በሚገኙ<br />

ሀገራት ኤምባሲዎች ሊኖራቸው ይችላል። በእኛ ደረጃ<br />

ግን ‹‹ወሳኝ›› ተብለው በሚታመኑ ሀገራት ብቻ ነው<br />

ኤምባሲ የሚያስፈልገው። የመን አሁን ኤምባሲ ነው<br />

ያለን። ሳዑዲ አረቢያ ጅዳ ቆንፅላ ጽ/ቤት ነው ያለው።<br />

ዱባይና ቤይሩት ቆንፅላ ነው ያለው።<br />

የሸዋዬ ጉዳይ የማንቂያ ደወል ነውና ከዚህ በኋላ ወደ አረብ ሀገራት<br />

የሚሄዱ ኢትዮጵያውያን ምን ከለላ ይደረግላቸዋል?<br />

‹‹ማንቂያ ደወል›› ያልከው በጣም ትክክለኛ ቃል<br />

ነው። ይሄ ነገር ከተፈፀመ ቆይቷል ግን ሲ.ኤን.ኤን<br />

እስኪዘግበው ድረስ እኛም ቤተሰቦቿም ምንም መረጃ<br />

አልነበረንም። ሌሎች ከዚህ መማር ያለባቸው ነገር<br />

በየሄዱባቸው ሀገራት ሄደው መመዝገብ ያለባቸው<br />

መሆኑን ነው። አካሄደቸውን ሕጋዊ ማድረግ<br />

አለባቸው። የጉዳዩ ትልቁ ባለቤት ተጓዦች ናቸው።<br />

ስለዚህ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው።<br />

ጥሩ . . . ወደ ውጭ የሚሄዱት የጠቀሷቸውን ቅድመ-ሁኔታዎች<br />

ማሟላት አለባቸው። መንግሥትስ ከዚህ በኋላ ለዜጎቹ እንዴት ነው<br />

ከለላ የሚያደርገው?<br />

በየኤምባሲው ያሉ ሰዎች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ<br />

መወጣት አለባቸው። ውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን<br />

ለሚያቀርቧቸው ጥያቄዎች ትክክለኛና ተገቢው ምላሽ<br />

ሊሰጣቸው ይገባል።<br />

በተለያዩ እስር ቤቶች ውስጥም የሚገኙ በርካታ ኢትዮጵያውያን አሉ፤<br />

ለምን አስፈትታችኋቸው ወደ ሀገር ቤት እንዲመጡ አታደርጉም?<br />

የተመዘገቡ ስላልሆኑ የመረጃ ዕጥረት አለ።<br />

የሚደርሱን መረጃዎች የግምት ናቸው። ‹‹የት<br />

እስር ቤት? ብዛታቸውስ?›› የሚለውን ነገር በደንብ<br />

የሚመልስ አይደለም። የሚመጡ ሰዎችም የሚሰጡን<br />

መረጃ አጥጋቢ አይደለም።<br />

የአረቡ ዓለም አብዮት በተቀሰቀሰበት ወቅት ኢትዮጵያውያንን ወደ<br />

ሀገር ቤት የመመለስ ሥራ በ<strong>መንግስት</strong>ና በዓለም አቀፍ ተቋማት በኩል<br />

ይከናወን ነበር። በአንፃሩ ደግሞ ወደዛው የሚሄዱ ሰዎች ነበሩ።<br />

ለምንድን ነው ዝም የሚባለው?<br />

ትክክል። ከየመን ሸሽተው የሚመጡትን ለመቀበል<br />

አየር ማረፊያ ቆመን ወደ የመን የሚሄዱ ሰዎችን<br />

ተመልክተናል። ‹‹ይኸው እነዚህ የሚመለሱት እዛ<br />

ችግር ሆኖ ነው፤ ለምን ትሄዳላችሁ?›› ስንላቸው<br />

ሊሰሙን ፈቃደኞች አልነበሩም። በዚህ ላይ ማንም<br />

ሰው ወደ ፈለገበት ቦታ የመሄድ ሕገ-መንግስታዊ<br />

ነፃነት አለው። ያንን ጥሰን ማስቆም አንችልም።<br />

ግን ከሄዱስ በኋላ ከለላ ማድረግ አይቻልም?<br />

ከሄዱ በኋላ ሌላ ሀገር ነው ያሉት። በሄዱበት ሀገር<br />

ሕግ መሰረት ነው የሚተዳደሩት። <strong>መንግስት</strong> ጣልቃ<br />

መግባት የሚችለው ችግር ሲደርስ ነው። ችግሮች<br />

ሲከሰቱ ከዛ ሀገር <strong>መንግስት</strong> ጋር በመነጋገር ለጉዳዩ<br />

ዕልባት ይሻል እንጂ ለእያንዳንዱ እንቅስቃሴ ከለላ<br />

መስጠት አይችልም።<br />

በርካታ ኢትዮጵያውያን ከሚገኙባት ኳታር ጋር ዲፕሎማሲያዊ<br />

ግንኙነት ተቋርጧል። እዛ ያሉ ኢትዮጵያውያንን ጉዳይ እንዴት ነው<br />

የምትከታተሉት?<br />

እስካሁን ድረስ ያጋጠመ ችግር የለም። ግን እንደ<br />

ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት [IOM] እና በተባበሩት<br />

መንግስታት ድርጅት [UNHCR] ባሉ ዓለም አቀፍ<br />

ተቋማት በኩል መብቶቻቸውን ማስጠበቅ ይቻላል።


አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />

መልካም ዓዲስ ዓመት<br />

15<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ


16<br />

ደርግ ወደ ሥልጣን ሲመጣ እርስዎ የትና በምን<br />

ኃላፊነት ላይ ነበሩ?<br />

ደርግ ወደ ስልጣን ሲመጣ እኔ አሜሪካን<br />

ሀገር ትምህርት ላይ ነበርኩ። ከዚያ<br />

እንማንኛውም በዘመኑ እንደነበሩ ወጣት<br />

ተማሪዎች ለውጡን ደግፌ ተሰለፍኩ።<br />

በነገራችን ላይ ከዚያ በፊት ከውትድርናው<br />

ዓለም ወጥቼ ነበር። የለውጡ እንቅስቃሴ<br />

ሲጀመር ነው እንደገና ወደ ወታደርነት<br />

የተመለስኩት። እናም ለውጡን የበለጠ<br />

ለማንቀሳቀስ ከሌሎች መኮንኖች ጋር<br />

ተባብሬ ተሰለፍኩ፡፡ በደርግ ውስጥ<br />

በሰራሁባቸው ዓመታት ውስጥ የሚቻለንን<br />

ያህል በኢትዮጵያ እውነተኛና መሠረታዊ<br />

ለውጥ ለማምጣት፣ ከድህነት ወደ<br />

ዕድገት፣ ከጦርነት ወደ ሰላም መሸጋገር<br />

የምንችልበትን መንገድ ለመቀየስ<br />

ሞክረናል።<br />

ወደ አሜሪካ ለትምህርት ከመውጣትዎ በፊት የት<br />

ነበር የሚሰሩት?<br />

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ትምህርት ላይ<br />

ነበርኩ። የመጀመሪያ ዲግሪዬን ያገኘሁትም<br />

እዛው ነው። ከዛ በኋላ ወደ አሜሪካ አገር<br />

ወጥቼ ኮሎምቢያ ዩኒቨርስቲ ትምህርት<br />

ጀመርኩ። ኮሎምቢያ ዩኒቨርስቲ ስማር<br />

የሻለቅነት ማዕረግ ማግኘት የምችልበት<br />

ወቅት ነበር። በዚህ የተነሳ ወደ ሀገር<br />

ቤት ስመለስ የሻለቅነት ማዕረግ ሰጡኝ።<br />

ቢሆንም በሻለቅነት ማዕረግ ብዙ ጊዜ<br />

አልሰራሁበትም።<br />

በሐረር ጦር አካዳሚ 2ኛ ኮርስ ሰልጣኝ ነበሩ።<br />

2ኛ ኮርስ መኮንኖች ደግሞ እስከ ጀኔራል ማዕረግ<br />

ደርሰዋል። እርስዎ ታዲያ ለምን እስከ ጄኔራል ማዕረግ<br />

ማግኘት አልቻሉም?<br />

ወደ ወታደርነት ሥራ አልተመለስኩም።<br />

አብዮቱን እንደተቀላቀልኩ በሲቪልነት<br />

ነው ያገለገልኩት።<br />

ከአሜሪካ ወደ አገርዎ የተመለሱት ደርግ ሥልጣን<br />

ከያዘ ከስንት ጊዜ በኋላ ነው?<br />

ንጉሱ መስከረም 2 ቀን ከሥልጣን ወረዱ<br />

ሲባል፣ እኔና ኒውዮርክ አካባቢ የምንገኝ<br />

ሰዎች ወዲያው ነው ጓዛችንን ጠቅልለን<br />

ወደ ሀገር ቤት የገባነው፡፡ በዚያው<br />

በመስከረም ወር ማለት ነው።<br />

መልካም። ለህትመት ባበቁት አንድ መፅሐፍ፣<br />

እርስዎ የሐረር ጦር አካዳሚ፣ ኮ/ል መንግስቱ<br />

ደግሞ የሆለታ ጦር አካዳሚ ሰልጣኝ እንደነበራችሁ፣<br />

ሁለታችሁም በማዕረግ ደረጃ አቻ እንደሆናችሁ<br />

ጠቅሰው፣ ሀገር ቤት እንደገቡ ኮ/ል መንግስቱን<br />

ለማነጋገር ወደ ቤተ<strong>መንግስት</strong> በሄዱ ጊዜ ‹‹አንተ ብዬ<br />

ነው የማነጋግረው›› ብለው ፣ ‹‹ወዲያው ሳላስበው<br />

አንቱ ማለት ጀመርኩ›› ሲሉ የተረኩት ክፍል አለ።<br />

እስቲ ይህ ሊሆን የቻለበትን ሁኔታ መለስ ብለው<br />

ያጫውቱኝ?<br />

ተፈሪ መኮንን ትምህርቴን ከጨረስኩ<br />

በኋላ ወደ ሐረር ጦር አካዳሚ የገባሁት<br />

በግል ፍላጎቴ አይደለም። ተመልምለን ነው<br />

የግድ ወደ ጦር ት/ቤት የተላክነው። እና<br />

የ2ኛ ኮርስ ሰልጣኝ ነኝ። ሐረር ሚሊቴር<br />

አካዳሚ፣ የታወቀ ሚሊተሪ አካዳሚ ነው።<br />

ህንዶች ያቋቋሙት ነው። እዚያ 3 ዓመት<br />

ሰልጥኛለሁ። በእነዚያ ሶስት ዓመታት<br />

በየቀኑ የምንማረው፣ የምንዘጋጀው እና<br />

አዕምሮአችንን የምናሰለጥነው ከራስ<br />

በላይ ሀገርን (ኢትዮጵያን) ማስቀደምን<br />

ነው። ከራስ በፊት ሀገር፣ ከራስ በፊት<br />

ሀገር፣ ከራስ በፊት ሀገር በሚል መርህ<br />

ተኮትኩተን ነው የሰለጠንነው።<br />

ከስልጠና በኋላ አየር ወለድ ገባሁ። የኛ<br />

ኮርስ ሁለተኛው ቡድን ነበር ወደ አየር<br />

ወለድ ሲገባ። ከዚያ ኤርትራ ሄድኩ።<br />

በኤርትራ ለሰራዊቱ የተለያየ ስልጠና<br />

በመስጠት ለብዙ ዓመታት አገለገልኩ።<br />

ከዚያ ደግሞ በአሜሪካን ሀገር (አድቫንስ)<br />

ከፍተኛ የእግረኛ ወታራዊ ትምህርት<br />

ሥልጠና ለ11 ወራት ተማርኩ። እንደገና<br />

ደግሞ ወደ አገር ቤት ተመልሼ ወደ<br />

ምድብ ሥራዬ ኤርትራ አቆናሁ። ውጊያ<br />

ላይ ቆሰልኩ። በመቁሰሌ ምክንያት<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

ከወታደር ቤት ተሰናበትኩና አዲስ አበባ<br />

ዩኒቨርስቲ ገባሁ።<br />

በእነዚህ ወቅቶች ሁሉ እኔ መንግስቱ<br />

ኃ/ማርያምን አላውቀውም። እሱ ግን<br />

ኤርትራ መጥቶ በነበረበት ጊዜ አይቶኛል፤<br />

ያስታውሰኛል። እሱ ከሆለታ ጦር ት/ቤት<br />

ነው የወጣው። የእኔ ሲኒየር ነው። ከአሜሪካ<br />

ለውጡን ደግፈን ወደ ሀገር ቤት ስንመለስ<br />

መንግስቱ የደርግ ምክትል ሊቀመንበር<br />

ነበር። በወቅቱ ማንኛውም መኮንን እንደ<br />

ጓድ “አንተ” ነበር የምንባባለው። እንደ<br />

ጓደኛ ነበር የምንነጋገረው።<br />

እና አሁን አንተ የጠየቅከኝ ፍርሀትና<br />

“አንቱታ” የተፈጠረው በአንድ ጊዜ<br />

ሳይሆን ቀስ በቀስ ነው። መጀመሪያ<br />

“አንቱ” በሉ ተባልን። ማለት ጀመርን።<br />

ከዚያ እጃችሁን ኪሳችሁ ውስጥ አትክተቱ<br />

ተባልን፣ እጃችንን ከኪሳችን ማውጣት<br />

ጀመርን። ከዚያ ቀረብ ብሎ ማነጋገር<br />

ቀረ። በመጨረሻ የምንነጋገረው በ20<br />

ሜትር ርቀት ሆነ። እንዲህ እንዲህ እያለ<br />

ሰውየው የሚያስፈራ ድባብ ፈጠረ። ከዚያ<br />

ትጥቅ ፈትተን እንድንገባ ተደረገ። ያ<br />

ሁኔታ ፍርሃት አሳደረብን። ክብር ሳይሆን<br />

ፍርሀት። እነዚህ ሁኔታዎች ተደምረው<br />

ነው በመፅሐፉ ያልኩት የሆነው።<br />

በነገራችን ላይ ይህንን ሁኔታ የፃፉት ከሀገር ከወጡና<br />

ከደርግ ከተለዩ በኋላ ቢሆንም፣አተራረክ ግን ኮሎኔል<br />

መንግስቱን ያደንቋቸው እንደነበር የሚያሳይ ነው<br />

የሆነብኝ። መፅሐፍዎን ሳነብ እንደተረዳሁት፣ ኮ/ል<br />

መንግስቱን ለማነጋገር ወደ ቤተ <strong>መንግስት</strong> ሲገቡ ተራ<br />

ሰው ጠብቀው በአስተሳሰቡ ላቅ ያለ ሰው እንዳገኙ<br />

አድርገው ነው የገለፁት። ይህ አገላለፅዎ አሁን<br />

ከሚናገሩት ጋር አይጋጭም?<br />

የፍርሃት ስሜት ከየትና እንዴት እንደመጣ<br />

ነው ቀደም ብዬ የነገርኩህ። እንጂ መቼም<br />

ጊዜ ቢሆን ብናገረው የማላፍርበት፣ ከደረግ<br />

ጋር መስራት ከጀመርኩበት ጊዜ አንስቱ<br />

ለተወሰነ ጊዜ ያህል ለኮ/ል መንግስቱ<br />

ታላቅ አክብሮት ነበረኝ።<br />

አብዮቱ ሲጀመር ያየሁበት የኢትዮጵያዊነት<br />

ስሜት ከምጠብቀው በላይ ነው የሆነብኝ።<br />

የመናገር ችሎታው፤ የማዳመጥ<br />

ችሎታው፣ የመምራት ችሎታው በጣም<br />

ነበር ያስደነቀኝ። ትዝ ይለኛል ያኔ እኔ<br />

የዕድገት በህብረት ምክትል አዝማች<br />

ነበርኩ። በእሱ ፊት ዘማች ተማሪዎችን<br />

አሰልፈን ‹‹ቪቫ መንግስቱ›› እያልን<br />

ስናልፍ፣ እኔ ነበርኩ የመጀመሪያው<br />

‹‹ቪቫ መንግስቱ›› ባይ። ከተፈሪ ባንቲ እና<br />

አጥናፉ አባተ እሱን ለይተን ነበር ‹‹ቪቫ››<br />

ስንል የነበረው።<br />

በዚያ ጊዜ የነበረውን ሁኔታ መለስ ብለህ<br />

ከተመለከትከው በኢትዮጵያ ውስጥ ለውጥ<br />

ስንል ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ሳይሆን፣<br />

ህብረተሰባዊ (የህብረተሰብ) ለውጥ ነው።<br />

ፊውዳሊዝምን የማጥፋትና አዲሲቱን<br />

ኢትዮጵያ የመገንባት ህልም ነበርን።<br />

እና የመንግስቱ ኃ/ማርያም ከአናሳ<br />

ብሔረሰብ የመምጣቱ ጉዳይ፣ ከበታች<br />

መኮንንነት የመምጣቱ ጉዳይ፣ ባህርይው፣<br />

ከጀርባውም ሆነ ከፊቱ ያለው ሌላ ሌላ<br />

ነገር ተደማምሮ እንደለውጥ ተምሳሌት<br />

ተወሰደ። በጠቅላላው እሱ የሚያሳው<br />

የለውጥ ምልክት ነበር የኢትዮጵያን<br />

ለውጥ ያሳያል በሚል ደገፍነው፡ ከዚህ<br />

በተጨማሪ በጣም ጎበዝ አርበኛ ነበር።<br />

ሲናገር፣ ሲያሳምን፣ ሲያዳምጥ በጣም<br />

አደንቀው ነበር። በዚያን ጊዜ ያለ ምንም<br />

ማመንታት እሱን ደግፌአለሁ። ለተወሰነ<br />

ጊዜም አመራሩን ተቀብያለሁ።<br />

በደርግ ውስጥ በየትኛው የኃላፊነት ሥልጣን ላይ ነው<br />

የሰሩት?<br />

በመጀመሪያ የዕድገት በህብረት ምክትል<br />

አዝማች ሆኜ ነው የሰራሁት። ዋና<br />

አዝማቹ ኪሮስ አለማየሁ ይባል ነበር።<br />

በኢትዮጵያውያን ዘንድ በስፋት የታቅሁት<br />

ያኔ ነው። ምንም እንኳን ዘመቻውን<br />

<strong>መንግስት</strong> የኋላ ኋላ ለሌላ ነገር<br />

ቢጠቀምበትም በኢትዮጵያ አዲስ ዕይታን፣<br />

አዲስ ዕውቀትን የፈነጠቀ ነበር። ዓላማው<br />

ጥሩ ነበር።<br />

ከዚያ በኋላ የዕርዳታ ማስተባበሪያና<br />

ማቋቋሚያ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር<br />

ነው የሆንኩት። በወቅቱ በኢትዮጵያ<br />

ከፍተኛ ድርቅ ችግር ነበር። ያ ድርቅ<br />

ለደርግ ውድቀት እንደ አንድ ምክንያት<br />

ነው።<br />

የሆነ ሆኖ በረሃብ ለተጎዳው ኢትዮጵያዊ<br />

የተቻለኝን ድጋፍ ለመስጠት ዕድል<br />

ያገኘሁበትም ነው። ከዚያ በኋላ ውጭ<br />

ጉዳይ ሚኒስቴር መ/ቤት ምክትል<br />

ሚኒስትር ሆኜ ተሾምኩ። ኮ/ል ፈለቀ ወ/<br />

ጊዎርጊስ ሚኒስትር፣ እኔ ምክትል ሆኜ<br />

አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />

መልካም ዓዲስ ዓመት<br />

“የ1981 <strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> ለማድረግ<br />

ከሻዕቢያና ከወያኔ ጋር ተስማምተን ነበር”<br />

ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ<br />

ግንቦት 8 ቀን 1981 ዓ.ም በኮሎኔል መንግስቱ ኃ/ማርያም ላይ የተቃጣው መንፈንቅለ <strong>መንግስት</strong> የከሸፈበት ዕለት መሆኑ በኢትዮጵያውያን ዘንድ የሚረሳ አይደለም። የዛሬ 22 ዓመት የተካሄደው ያ የ<strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> ሙከራ ሀገሪቷ በረዥም<br />

ዓመታት ያፈራቻቸውን ምርጥ የጦር ባለሟሎች ያጣችበት ነውና። ኮሎኔል መንግስቱ ወደ ምሥራቅ ጀርመን ለጉብኝት መጓዛቸውን ተከትሎ የተሞከረውና የከሸፈው የግንቦት 8ቱ <strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጪ ሰፊ ዝግጅት<br />

የተደረገበት፣ በዚያ ወቅት የደርግን ሥርዓት ለመጣል የትጥቅ ትግል ሲያካሂዱ ከነበሩት ሻዕቢያና ህወሀት ጋር ሥምምነት የተደረሰበት ነበር ይላሉ፡- ሻለቃ ዳዊት ወ/ጊዎርጊስ። ሻለቃ ዳዊት፣ በሀገር ውስጥ የ<strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> ሙከራ ያደረጉትን<br />

ጄኔራል መኮንኖችንና የደርግ ጦር አዛዦችን፣ እንዲሁም የደርግን ሥርዓት ለመጣል ይፋለሙ የነበሩትን ሻዕቢያና ህወሀትን በማግባባት ወሳኝ ሚና መጫወታቸውን በተመለከተ በይፋ ቃለምልልስ ሰጥተዋል። ሻለቃ ዳዊት ወ/ጊዎርጊስ ሥርዓቱን<br />

ከድተው የወጡ የመጀመሪያው የደርግ ከፍተኛ ባለሥልጣን መሆናቸው ይታወቃል። ከእሳቸው ቀጥሎ ደርግን ከድተው ከሀገር የወጡት ኮ/ል ጎሹ ወልዴ ናቸው። እነዚህ ሁለት ከፍተኛ የደርግ ሹማምንቶች የሐረር ጦር አካዳሚ ምሩቆችም ነበሩ።<br />

ሁለቱም፣ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን የያዙት ከአሜሪካን ሀገር የል ዩኒቨርስቲ እና ኮሎምቢያ ዩኒቨርስቲ ነው። ከድተው ከሀገር የወጡት እነዚህ ሁለት የሥርዓቱ ባለሥልጣናት አገዛዙን ለመጣል ውጭ ሀገር ሆነው ሲታገሉ፣ ሌሎቹ የደርግ ጄኔራሎች ደግሞ<br />

በሀገር ውስጥ <strong>መፈንቅለ</strong> መንግሥት ለማካሄድ ተስማምተው የግንቦት 8ቱ ሙከራን መታቀዱን ሻለቃ ዳዊት ይተርኩልናል። ኮ/ል መንግስቱ ያንን የ<strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> ሙከራ ይሻገሩ እንጂ፣ ከዚያ በኋላ በሥልጣናቸው ላይ የቆዩት ለሁለት ዓመት<br />

ከ5 ቀናት ብቻ ነበር። ይሁን እንጂ ሻለቃ ዳዊት፣ ከግንቦት 8ቱ በኋላም በኮሎኔሉ ላይ <strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> ታቅዶ ነበር ሲሉም አስገራሚ ቃለምልልስ ሰጥተዋል። በአሁኑ ወቅት በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ውስጥ በመስራት ላይ የሚገኙት ሻለቃ<br />

ዳዊት ወ/ጊዎርጊስ፣ ሰሞኑን ወደዋሽንግተን ዲሲ ለሥራ ብቅ ባሉበት ወቅት ለአንጋፋው ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና የሰጡት ቃለ-ምልልስ እስካሁን ያልተሰሙና ተደብቀው የቆዩ ታሪኮችን የያዘ ሆኖ አግኝተነዋል። ስለዚህም ለአንባቢዎቻችን ግንዛቤ ይረዳ<br />

ዘንድ፣ የሻለቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስን ቃለምልልስ እንደሚከተለው አቅርበነዋል።<br />

ለ3 ዓመት አገለገልኩ።<br />

ውጭ ጉዳይ ም/ሚኒስትር የሆንኩት<br />

በመጥፎ ጊዜ ነበር። የሱማሌ ወረራ<br />

ነበር በወቅቱ። ያኔ የኢትዮጵያ ድንበር<br />

እንደተደፈረ፣ ህልውናዋ እንደተነካ<br />

በየክፍለ ዓለማቱ እየተዘዋወሩ ለማሳማን<br />

የደከምንበትና ከፍተኛ ትግል የገጠምንበት<br />

ወቅት ነበር።<br />

በዚያ ጊዜ ኢትዮጵያ ማርክስሲት ርዕዮትን<br />

እየተከተለች እንደገና ደግሞ ወደ ምዕራቡ<br />

አገር ሄዳ ዕርዳታና ድጋፍ ለመጠየቅ<br />

የተገደደችበት ወቅት ነበር። በአንድ<br />

በኩል በድርቅ ለተጎዳው ህዝባችን ዕርዳታ<br />

ሰጡን፣ በሌላ በኩል ግሞ ሀገራችን<br />

ስለተወረረች የፖለቲካ ድጋፍ ስጡን<br />

ብሎ ዓለምን መጠየቅና የፈለግነውን ነገር<br />

ማግኘት ቀላል ነገር አልነበረም። ያንን<br />

ሁኔታ አስታርቆና ሚዛን ጠብቆ ተጠቃሚ<br />

መሆን መቻል ፈታኝ ነበር፡፡<br />

ከዚያ በኋላ ደግሞ የኤርትራ ዋና ተጠሪ<br />

ሆኜ ተሾምኩ። ኤርትራን የማስተዳደር<br />

ኃላፊነት የኔ ነበር። በመስክ ያለው ወታደራዊ<br />

ጉዳይ የኔ ኃላፊነት አልነበረም። ህዝቡን<br />

ማስተዳደርን፣ ፀጥታውን ማስጠበቅ፣<br />

የኤርትራ ህዝብ በኢትዮጵያዊነቱ ፀንቶ<br />

እንዲቆይ ማድረግ የእኔ ኃላፊነት ነበር።<br />

ኤርትራ በአስተዳደሪነት 3 ዓመት<br />

ሰርቻለሁ። በጣም ደስተኛ የሆንኩበትን<br />

ፍሬያማ ሥራ አከናውኛለሁ። በወቅቱ<br />

የኤርትራ ህዝብ ሁሉ የሚመሰክረው<br />

ተግባር ተወጥቻለሁ።<br />

እርስዎ በቀይ ኮከብ ዘመቻ ጊዜ የኤርትራ አስተዳዳሪ<br />

ነበሩ?<br />

አዎ! ከ74-76 ዓ.ም ማለት ነው። በዓሉ<br />

ግርማ ኦሮማይን ሲፅፍ ማለት ነው።<br />

አብረን ኤርትራ ነበርን።<br />

ለህትመት ካበቋቸው መፅሐፎች የአንዱን ገቢ<br />

‹‹ለኤርትራና ኢትዮጵያ ህዝቦች ወዳጅነት<br />

ማህበር›› መስጠትዎን አንብቤአለሁ። ከዚህ በኋላ<br />

የኤርትራና የኢትዮጵያ ህዝብ እንደገና አብሮ ይኖራል<br />

የሚል ተስፋ አለዎት ማለት ነው? የመፅሐፍዎን<br />

ሽያጭ የለገሱት ማህበር ዓላማስ ምንድን ነው? ምንስ<br />

እየሰራ ነው?<br />

ምን መሰለህ? አሁን ኤርትራን መገንጠል<br />

የመጀመሪያው አማራጭ ከሆነ፣ ቀጥሎ<br />

መምጣት ያለት አማራጭ የኢትዮጵያ እና<br />

የኤርትራ ህዝብ አንድ መሆን ይገባዋል<br />

የሚል መሆን አለበት። ህዝቡ በጠላትነት<br />

መተያየት የለበትም። ሁለቱ ህዝቦች<br />

ሰላማቸው፣ ኢኮኖሚያቸው፣ አኗኗራቸው<br />

ወዘተ አንድ አይነት ነው። ሁሉም ነገር<br />

የሚያገናኛቸው ናቸው። ኤርትራ ላይ<br />

የመጣ ነገር ኢትዮጵያንም ይነካል።<br />

ኢትዮጰያ ላይ የመጣ ነገር ሁሉ ኤርትራን<br />

ይነካል።<br />

ባለፉት 150 ዓመታት በኢትዮጵያ ወደ<br />

90 ያህል ጦርነቶች ተደርገዋል። ከእነዚህ<br />

ጦርነቶች ውስጥ 95 በመቶ ያህሉ<br />

የመጣው በኤርትራ ባህር በኩል ነው።<br />

አሁንም የእስልምና አክራሪነት ቢከሰት፣<br />

የሶማሌ ጦርነት ቢመጣ፣ የኢኮኖሚ<br />

ችግር ወዘተ ቢፈጠር፣ የሚመጣው<br />

በኤርትራ በኩል ነው። ልክ እንደዚያው<br />

ሁሉ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚፈጠር<br />

ችግር ሁሉ ኤርትራ ውስጥ ይሰማል።<br />

ስለዚህ አብረን መኖር የሚገባን ህዝቦች<br />

ነን። በሁሉም ነገር ተሳስረን ያለን እና<br />

የምንኖር ነን። ይህንን ዕውነታ በፖለቲካ<br />

ማሰር ባይቻልም፣ አብረን በሰላም መኖር<br />

አለብን በሚል መርህ ነው ማህበሩን<br />

የመሰረትነው።ማህበሩ በሁለቱ ሕዝቦች<br />

መሀከል ያለውን የጋራ ትስስርና ታሪክ<br />

የሚያጎላ፣ ህዝቡን የሚያነቃቃ ስለሆነ<br />

ነው የመፅሀፌን ገቢ ያበረከትኩት።<br />

ማህበሩን የመሠረታችሁት ኢትዮጵያውያንና<br />

ኤርትራውያን በጋራ ሆናችሁ ነው?<br />

አዎ! በመሀሉ ግን እኔ የማህበር ሥራ<br />

መስራት አልቻልኩም። አሁን በአሜሪካ<br />

ሳንሆዜ ያሉ ሌሎች ድርጅቶች ናቸው<br />

ዓላማውን የሚያራምዱት።<br />

እርስዎ ግን ኢትዮጵያና ኤርትራ አንድ ቀን<br />

በኮንፌዴሬሽንም ሆነ በሌላ መልክ አብረው መኖር<br />

ይችላሉ ብለው ይገምታሉ?<br />

አዎ ይችላሉ። ግን በመጀመሪያ ደረጃ<br />

መሠረቱ አሁን መጣል አለበት።<br />

መልካም። እርስዎ የእርዳታ ማስተባበሪያ ኮሚሽን<br />

ኮሚሽነር በነበሩበት ጊዜ ስለተከሰተው ረሃብና<br />

ስለሆነው ነገር በጥቂቱ ሊነግሩኝ ይችላሉ?<br />

እ.አ.አ ከ82-85 ዓ.ም ማለት ነው<br />

እኔ በእርዳታ ኮሚሽን ኮሚሽነርንት<br />

ያገለገልኩት። ያኔ ኢትዮጵያ ውስጥ<br />

የተከሰተውን ከባድ የድርቅ ችግር<br />

ለመታደግ ዓለም በሙሉ የተንቀሳቀሰበት<br />

ዘመን ነው።<br />

አሁን በሶማሌ፣ በኢትዮጵያና በኬንያ<br />

የተፈጠረውን የድርቅ ችግር ከዚያ ዘመን<br />

ጋር ይወዳደራል የሚሉ አሉ። ቢሆንም፣<br />

ያኔ የተከሰተው የድርቅ ችግር ግን እጅግ<br />

የከፋ ነበር። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት<br />

ወዲህ መላውን ዓለም ያስተባበረ የድርቅ<br />

ችግር ነበር የተከሰተው።<br />

የአጋጣሚ ነገር ሆኖ፣ ያኔ የደርግ<br />

<strong>መንግስት</strong> የፖለቲካ አሰላለፍ ከምስራቁ<br />

ዓለም ጋር ነበር። ዕርዳታ ለመስጠት<br />

የተዘጋጀው ደግሞ ምዕራቡ ዓለም ነው።<br />

ይህንን ሁለቱን ጉዳይ ማስታረቅ ከባድ<br />

ፈተና ነበር። ከዚህ ሌላ የደርግ <strong>መንግስት</strong><br />

10ኛውን የአብዮት በዓል አከብራለሁ<br />

ብሎ የተነሳበት ነበርና ድርቅ አለ ብሎ<br />

ማመን አልፈለገም። ኢትዮጵያ በሀብት<br />

በለፀገች፣ አደገች፣ በሀብት ተጥለጠለቀች<br />

ተብሎ ፕሮፓጋንዳ የሚነዛበት ወቅት<br />

ነበር። ዕውነታው አፍጥጦ የሚታይ<br />

ነበር። ምዕራቡ ዓለም ዕርዳታ ለመስጠት<br />

ቢዘጋጅም፣ ደርግ መቀበል አልፈለገም።<br />

‹‹ችግር የለም፤ ድርቅ የለም፤ ችግሩን<br />

የፈጠራችሁት እናንተ ናችሁ›› ባይ<br />

ነው። ይህንን ማስታርቆ ህዝቡን ከችግር<br />

መታደግ ለእኔ እጅግ ከባድ ፈተና ነበር።<br />

ያም ሆነ ይህ፣ የዓለም ዕውቅ አርቲስቶች<br />

‹‹We are the World›› የተሰኘ ኮንሰርት<br />

አዘጋጁ። ያንን ዘፈን ሲያዘጋጁ አማክረን<br />

ብለው ወደ አሜሪካ ጠርተውኝ ነበር።<br />

በ ገፅ 18


አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />

መልካም ዓዲስ ዓመት<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

17


18<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

ሴ ት<br />

ሴበመቅደስ<br />

ፍስሐ<br />

tigi.vip@gmail.com<br />

ኪራይ ሰብሳቢዎቹ<br />

በ2002 ዓ.ም ለ2003 መባቻ፣ ‹‹አዲስ›› ብለን ልንቀበለው<br />

የጥቂት ቀናት ልዩነት ሲቀረን፣ በዚሁ ዓምድ<br />

ያቀረብነው አንድ ጽሁፍ ነበር - ኪራይ ሰብሳቢ ሕፃናትን<br />

በማስመልከት።<br />

ለማስታወስ ያህል፡-<br />

ሴቶቹ፣ በአዲስ ዓመት ወቅት የሚጨፍሩበት መንገድና<br />

ወንዶቹ የሚጨፍሩበት መንገድ አንድ እንዳልሆነ ያወዳደርንበት ሁኔታ<br />

ነበር። ባህል እየተበረዘ ነው (ኧረ እንደውም እየጠፋ ነው!) ብለን ነበር።<br />

ልክ ነው። ባህል አጥፊዎቹ ራሳቸው ባህልን ናፋቂዎቹ ሆነው ተቸገርን<br />

እንጂ።<br />

የወንዶቹ ማስጠንቀቂያ አይሉት ‹‹ሆያ-ሆዬ›› አስቂኝም፣<br />

አሳቃቂም ነው። እስቲ በደጅዎ የቆሙ ታዳጊ ሆያ-ሆዬ ጨፋሪ ህፃናት<br />

ሲጨፍሩ እንዳልሰሙአቸው ሆነው ዝም ይበሏቸው፤ ድካማቸው ከንቱ<br />

እንዳይሆን የሰጉት ህፃናት፣ ‹‹ኧረ በቃ በቃ ጉሮሮአችን ነቃ›› ብለው<br />

ሊገስፁዎት ይሞክራሉ። ‹‹እምቢኝ›› ካሉም ወንዶቹ ለእርስዎ የሚሆን<br />

የስድብ ግጥም አያጡም።<br />

አንዳንዴም እነሱ በምን ገንዘብ እንደሚያገኙ ይገባቸዋልና<br />

እንዲገጥምላቸው ብቻ የሚጠቀሙት ንግግርም አጀብ ያሰኛል። የሰማንያ<br />

ዓመቱን ሽማግሌ ‹‹የኔ’ማ አባባ ኢትዮጵያዊው ሩኒ›› ሊሉም ይችላሉ -<br />

ታዲያ ይሄን ምን ይሉታል?<br />

የሴቶቹም ከዚህ በብዙ ይለያል ማለት አይደለም። ነገር ግን<br />

‘የአለማመን’ ዘይቤአቸው ይለያል። የእነሱ እንደወንዶቹ ትዕዛዛዊና<br />

ሽንገላዊ አይደለም። ልምምጥ ነው። ሌላውን ሰው የሚያሳዝን፣<br />

የሚያራራና ሆድ የሚያባባ አይነት ነው። ሴቶቹ እንደወንዶች ‹‹ኧረ<br />

በቃ በቃ ጉሮሮአችን ነቃ›› ላይልዎት ይችላሉ።<br />

የሴቶቹ የጭፈራ ስርዓት ልምምጥንና የሌላውን ሰው<br />

ሩሁሩነት መፈለግ መሆኑን በዚህ ማረጋገጥ እንችላለን፡-<br />

‹‹ . . . እንኳን ቤትና የለኝም አጥር፣<br />

እደጅ አድራለሁ ኮከብ ስቆጥር።<br />

ኮከብ ቆጥሬ ስገባ ቤቴ፣<br />

ትቆጣኛለች የእንጀራ እናቴ።››<br />

በማለት እርስዎ የማያገባዎትን፣ ነገር ግን እነርሱ የእርስዎን ልብ<br />

ያራራል ያሉበትን መንገድ ይጠቀማሉ።<br />

የሴቶቹ ምርቃት ከወንዶቹ ይለያል። ወንዶቹ፡-<br />

‹‹…ክበር በስንዴ ክበር በጤፍ፣<br />

ምቀኛ ይርገፍ፣ እንደቆላ ጤፍ።››<br />

ሊልዎት ይችላሉ። በስንዴና በጤፍ መክበር እንደሚቻል ያገናዘቡ<br />

የሚመስሉት ህፃናቱ፣ ለጭፈራቸው ክፍያ ያበረከቱት ሽልማት በስንዴ<br />

የተጋገረ ዳቦ ቢሆን ይሄ ምርቃት ላይደርስዎም ይችላል።<br />

ሴቶቹ፡- የዛሬ ባለውለታቸውን ለዛሬ ዓመትም እንዲያገኙት<br />

በመመኘት፡-<br />

‹‹ከብረው ይቆዩኝ ከብረው፣<br />

ባ’መት ወንድ ልጅ ወልደው፣<br />

ሰላሳ ጥጆች አስረው።›› ብለው መልካም ምኞትን<br />

ይገለፃሉ።<br />

አንዳንዴ በወንዶች የ‹‹ሆያ-ሆዬ›› በዓል ሴቶች እንደ ወንድ<br />

ሲጨፍሩ ገጥሞዎት ያውቃል? ለምን ይሆን? የሚል ጥያቄ ውስጤ<br />

ያጭራል። እንደ ወንድ መሆን የመመኘት ሀሳቡ የመጣው ከምን<br />

ይሆን? እኔ መልስ የለኝም።<br />

ነጥቡ ከላይ ለትውስታ ያነሳነው ነገር ብቻም አይደለም።<br />

ከዓመት ዓመት ይሄው ጉዳይ እየተቀየረና በሚገርም ሁኔታ ከትክክለኛ<br />

ባህሉ እያፈነገጠ መሆኑ እንጂ። ጠያቂዎቹ ህፃናት እንዳሉ ሆነው<br />

ሰጪዎቹ ምን ነካቸው የሚያስብል ነው።<br />

‹‹ዮንዜና ዮንዜ ሳቢሳ፣ ጠላትህ ይበሳ እንደ አሮጌ ጣሳ።›› .<br />

. . የተባለው አባወራ ምናልባትም ፀበኛ ጎረቤት ካለው የልቡ ደርሷልና<br />

ግጥም አድርጎ ይሸልም ይሆናል። ነገር ግን መሆን ያለበት ያ አልነበረም።<br />

እኛ እንዲህ እያደረግን ተመልሰን ደግሞ ‹‹ወይ ጊዜ!›› ብንል ምን ዋጋ<br />

ይኖረዋል። ባህል ስለመበላሸቱ ተጠያቂው ተረካቢው ትውልድ ሳይሆን<br />

አስረካቢው ትውልድም እንደሆነ ልብ ይሏል። እናስብበት።<br />

ወደአዲስ ዓመት ስንመጣስ? እንዲህ ነው፡- ‹‹አዲስ›› ብለን<br />

አንድ ነገር ስንገዛ ቀድሞ የነበረንን አሮጌ ነገር በአግባቡ ተጠቅመንበት<br />

ሲያልቅ (ተጠቅመንበታል ብለን ስናስብ) ነው። በዚህ ሊያልቅ የቀናት<br />

ልዩነት በቀረው ‹‹አሮጌ›› ዓመት የፈፀምነውን በጎ ተግባር ብቻ በማሰብ<br />

ዓመቱን በጥሩ ሁኔታ ተጠቅመንበታል ብለን የምናስብ ከሆነ ስህተት<br />

ሰርተናል።<br />

ከወንዶቹ በመቀጠል ዓመቱን በመልካም ምኞት ያስጀመሩን<br />

ሴት ህፃናት ለእነሱ የተሳካ ላይሆን ይችላል።<br />

‹ከብረው ይቆዩኝ› ብለው የመረቁዎትና መልካም ምኛታቸውን<br />

የገለፁልዎ ሴት ህፃናት በዓመቱ ያለ እድሜያቸው ወልደው የኃላፊነት<br />

ሸክም ተከምሮባቸው ያገኙዋቸውም ይሆናል። አሊያም ያለአቅማቸው<br />

በተሰጣቸው የስራ ኃላፊነት ላይ ሲዳክሩ፤ አሊያም የትምህርት እድል<br />

ተነፍጓቸው ቤት ውስጥ ቁጭ ብለው … ይህ ሁሉ የሚሆነውና<br />

የሚለወጠው በእርስዎ ነው። ያኔ - ‹‹አዲስ›› አስተሳሰብ ያመጡ ቀን -<br />

ሁሌም ለእርስዎ ዓመቱ አዲስ ይሆናል።<br />

ከብረው ይቆዩኝ!<br />

መልካም አዲስ ዓመት!<br />

የአፍሪካ ዜናዎች<br />

እነ ማይክል ጃክሰን፣ እነ ሊየንል<br />

ሪቼ ወዘተ ሁሉ አግኝቼ<br />

አነጋገርኳቸው። የዘፈኑን ግጥም<br />

ሁሉ አየሁ። ሙዚቃውን ሰሩት።<br />

ብዙ የዕርዳታ ገንዘብ አሰባሰቡ።<br />

ከዛ በኋላ ደግሞ ኢትዮጵያ መጡ።<br />

አክብረን ተቀበልናቸው። ቦብ<br />

ጊልዶፍ ደግሞ ከእንግሊዘ አንዲሁ<br />

ለዕርዳታ ተነሳሳ። ላይቭ ኤይድ<br />

አደረገ። በአሜሪካ ፊያደልፊያ<br />

በተካሄደው ‹‹ባንድ ኤይድ›› ላይ<br />

ብርሃነ ደሬሳ ምክትል ኮሚሽነር<br />

ስለነበር በስፍራው ተገኝቶ ነበር።<br />

እንዲህ እንዲህ ባለ ሁኔታ<br />

በታቻለ መጠን እርዳታ እንዲገባ<br />

አድርገናል።<br />

ነገር ግን ጥረታችንን ከምስራቁ<br />

ዓለም ፖለቲካ ጋር ሊታረቅ<br />

አልቻለም። ‹‹ኮሚኒዝም ተበረዘ፤<br />

በዕርዳታ ሰበብ ምዕራቦች ሰርገው<br />

እየገቡ ነው፤ አብዮቱ ተቀለበሰ››<br />

ተባለ። ያኔ የኢትዮጰያን ገፅታ<br />

በማሳየት ረገድ ፊት ለፊት<br />

የነበርኩት እኔ ስለሆንኩ ክፉኛ<br />

እወቀስ ጀመር።<br />

መወቀስ ማለት? ዕርዳታ ለምን ገባ ነው?<br />

አዎ! ለምን ችግር አለ ብላችሁ<br />

ኢትዮጵያን አጋለጣችሁ ነው<br />

የተባለው። ወቅቱ 10ኛው<br />

አብዮት በአል የሚከበርበት ነው።<br />

መንግስቱ ኃ/ማርያም 6 ሰዓት<br />

ሙሉ ንግግር አደረገ።6 ሰዓት<br />

ሙሉ ንግግር ሲያደርግ የአንጎላው<br />

ፕ/ት ዶ ሳንቶስ፣ የዛምቢያ ፕ/ት<br />

ኬኔት ካውንዳ፣ የዚምባቡዌው<br />

ሙጋቤ፣ የደቡብ የመኑ ፕ/ት እና<br />

ሌሎችም እዚያው አዳራሽ ውስጥ<br />

ነበሩ። በስድስት ሰዓት ንግግሩ<br />

ስለዚያ አስከፊ ድርቅ አንድ<br />

ገፅ አልተናገረም። ብቻ ግን፣<br />

ዕርዳታ እንዲገባ እኔ ምዕራቡን<br />

አለም ስለወተወትኩ ‹‹የሲ.<br />

አይ. ኤ ኤጀንት ነው፤ አብዮቱን<br />

ለማስቀልበስ የተቀጠረ ነው››<br />

ስባል ለህይወቴ ፈራሁ። ያኔ<br />

ጠፋሁ፤ አሜሪካ ገባሁ።<br />

አወጣጥዎ ለሥራ ነበር?<br />

አዎ! ለሥራ ነው የወጣሁት።<br />

ምክንያቱም በግልፅ ነው<br />

የተወገዝኩት። ፖሊት ቢሮ<br />

ተጠርቼ ‹‹የኢትዮጵያን አብዮት<br />

ለመቀልበስ ሞክረሀል፤ በዕርዳታ<br />

ሰበብ የኃይማኖት ሰዎች እየገቡ<br />

አይዲዮሎጂውን እንዲበርዙ<br />

አድርገሀል፤ የምዕራባውያን<br />

ወኪሎች ገብተው በኢትዮጵያ ላይ<br />

ሳቦታጅ እንዲፈፅሙ ተባብረሃል።<br />

ከምሥራቁ ዓለም ጋር እንድንጣላ<br />

አድርገሀል››… ወዘተ ተባልኩ።<br />

ለማንኛውም ዛቻ ሲበዛብኝ ከአገር<br />

እንደወጣሁ ቀረሁ።<br />

በዚያ ረሀብ የተነሳ ምን ያህል ሰው እንደሞተ<br />

ይታወቃል? የተገኘውስ ዕርዳታ ህይወት<br />

በማትረፍ ረገድ ምን ያህል አግዟል?<br />

በእውነቱ መገመት በጣም<br />

አስቸጋሪ ነው። የቁጥር ነገር<br />

አስቸጋሪ ይመስለኛል። በእኔ<br />

ግምት 2 ሚለየን ሕዝብ በረሃብ<br />

ህይወቱን አጥቷል። በወቅቱ<br />

ቤት ይቁጠረው ነው ያልነው።<br />

የውጭው ዓለም ዕርዳታ ባይደርስ<br />

ኖሮ ከዚያም በከፋ መጠን ሕዝብ<br />

ያልቅ ነበር። የእኛ መ/ቤት እና<br />

ሌሎች ምግባረ ሰናይ ድርጅቶች<br />

በመተባበር ነው ዕርዳታ እንዲገኝ<br />

ያደረገው። በእውነቱ እኔ በወቅቱ<br />

ሕዝብን ለመታደግ ብርቱ ጥረት<br />

አድርጌያለሁ። ይህንን ጥረቴ<br />

ደግሞ በዚያ ወቅት የተ.መ.ድ<br />

ባለስልጣን የነበሩ ሰው ለሕትመት<br />

ባበቁት መፅሐፍ ‹‹ዳዊት ወ/<br />

ጊዎርጊስ ብርቱ ጥረት ባያደርግ<br />

ኖሮ ከ1 ሚሊዮን የበለጠ ህዝብን<br />

ህይወት ማትረፍ አይቻልም<br />

ነበር›› ሲሉ ምስክርነታቸውን<br />

ሰጥተውበታል። ማዘር ቴሬዛም<br />

እንዲሁ።<br />

ግን እንደው በሚሊየን የሚቆጠር ሕዝብ<br />

ለዕልቂት ከመዳረጉ በፊት መርዳት<br />

አይቻልም ነበር?<br />

በዚያ ወቅት ደርግ በትግራይ<br />

ከወያኔ፣ በኤርትራ ከሻዕቢያ ጋር<br />

ጦርነት ላይ ነበር። እና የደርግ<br />

<strong>መንግስት</strong> የጦርነቱን ቀጠና ክፍት<br />

አድርጎ ሕዝቡ ይረዳ ማለት<br />

በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ሽምቅ<br />

ተዋጊዎችን መርዳት ነው በሚል<br />

አልተቀበለውም። ሕዝቡን ነጥሎ<br />

መርዳት ደግሞ አይቻልም።<br />

የከፋው ረሀብ ያለው ደግሞ<br />

በጦርነቱ ቀጠና ያለው ሕዝብ<br />

ነው። ይሁን እንጂ የእኛ መ/ቤትና<br />

ሌሎች ምግባረ ሰናይ ድርጅቶች<br />

ከሰብዓዊነት አንፃር ሕዝቡ መረዳት<br />

አለበት የሚል ዕምነት ነበረን።<br />

የደርግ መግስት ጭራሽ ረሃብን<br />

መኖሩንም ለመቀበል ፈቃደኛ<br />

ሊሆን አልቻለም። ረሐብ መኖሩን<br />

ቢያምን ይከበራል እንጂ አይናቅም<br />

ነበር። ባለማመሪ የበለጠ ተናቀ።<br />

ሕዝብን ያስጨረሰ <strong>መንግስት</strong><br />

የሚል ስም አተረፈ።<br />

እናንተ ያለውን ሁኔታ ለ<strong>መንግስት</strong> ማስረዳት<br />

አትችሉም ነበር?<br />

እኛማ ተናገርን። እኔ ራሴ በግሌ<br />

ችግሩን ዘርዝሬ ገልጬ ነበር።<br />

‹‹የለም፤ <strong>መንግስት</strong> በአቅሙ<br />

ይረዳል፤ የውጭው ዓለም<br />

አይስማ›› የሚል ምላሽ ነው<br />

ያገኘሁት። እንዲያም ሆኖ ማይክል<br />

በርግ እና መሀመድ ዓሊ (ጋዜጠኛ)<br />

ኮረም ገብተው ሁኔታውን<br />

በፊልም እንዲቀርፁ አደረግን።<br />

ያ ፊልም በቢ.ቢ.ሲ 24 ደቂቃ፣<br />

በአሜሪካው ቢ.ኤን.ሲ ቴሌቪዥን<br />

ደግሞ 4 ደቂቃ ታየ። ዓለም<br />

በሙሉ ለእርዳታ ተንቀሳቀሰ።<br />

የብዙ ሰዎችንም ህይወት ማትረፍ<br />

ተቻለ።<br />

እርስዎ ህይወትዎን ለማትረፍ ከሀገር<br />

እንደወጡ ቢናገሩም፣ በአሜሪካ የተደላደለ<br />

ህይወት እንደገጠመዎት ነው በወቅቱ<br />

ሲነገር የነበረው። ይህ ሁኔታ ደግሞ የደርግ<br />

<strong>መንግስት</strong> ‹‹ዳዊት የሲ.አይ.ኤ ኤጀንት<br />

ነው›› ሲል ያወጣውን መግለጫ ተዓማኒ<br />

ያደርገዋል የሚሉ አሉ። በዚህ ጉዳይ ላይ<br />

የእርስዎ አስተያየት ምንድነው? ለመሆኑ<br />

አሜሪካ እንደደረሱ ወዴት ሄዱ? ምንስ<br />

አደረጉ?<br />

እንዳልከው ደርግ ‹‹ዘርፎ ከሀገር<br />

ወጣ፤ የሲአይኤ ኤጀንት ነው››<br />

ወዘተ የሚል የሥም ማጥፋት<br />

ዘመቻ አካሂዶብኛል። እኔ ግን<br />

እንደማንኛውም ሰው አሜሪካ<br />

እንደገባሁ የፖለቲካ ጥገኝነት<br />

ነው የጠየቅሁት። በዚያ ወቅት<br />

በዕርዳታ ሰጪ ድርጅቶችና<br />

በውጪ መንግስታት ዘንድ<br />

ዕውቅና ስለነበረኝ ብዙም ችግር<br />

አልገጠመኝም።<br />

አሜሪካ ከገባሁ በኋላ ወዲያውኑ<br />

ለደርግ <strong>መንግስት</strong> ሶስት ደብዳቤ<br />

አከታትዬ ፃፍኩ። እነዚያን<br />

ደብዳቤዎች ደበበ እሸቱ አፈላልጎ<br />

በመፅሐፉ ውስጥ አትሞታል።<br />

ደብዳቤዎቹ በፖለቲካውም ሆነ<br />

በኢኮኖሚው መስክ ደርግ ምን<br />

ማድረግ እንደሚገባው የሚመክሩና<br />

<strong>መንግስት</strong>ን የሚያቃኑ ነበሩ። እኔ<br />

የደርግን <strong>መንግስት</strong> በይፋ መኮነን<br />

እና መውገዝ የጀመርኩት የሥም<br />

ማጥፋት ዘመቻ ከተከፈተብኝ<br />

በኋላ ነው። በዚያው ወደ ፖለቲካ<br />

ትግል ገባሁ። ፖለቲካ ውስጥ<br />

አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />

መልካም ዓዲስ ዓመት<br />

አወዛጋቢው የዙማ ተሿሚ<br />

ስለአስገድዶ መድፈር እንዲሁም በተመሳሳይ ጾታዎች መካከል<br />

ስለሚደረግ ወሲባዊ ግንኙነት ወይም ግብረ-ሰዶማዊነት በተመለከተ<br />

በሚሰነዝሯቸው አነጋጋሪ አስተያየቶች ይታወቃሉ - ሞጎንግ ሞጎንግ።<br />

እኝህን ግለሰብ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ጃኮብ ዙማ ዋና ዳኛ (ቺፍ<br />

ጀስቲስ) አድረገው በቅርቡ መሾማቸው ጠንካራ ትችት እያስሰነዘረባቸው<br />

ይገኛል።<br />

ከሹመቱ አስቀድሞ የሀገሪቱ ቀንደኛ የሚባሉ ጎትጓች<br />

ቡድኖች ጃኮብ ዙማ ዳኛ ሞጎንግን ዋና ዳኛ አድርገው እንዳይሾሟቸው<br />

ቢጎተጉቷቸውም የሚሰማ ጆሮ አላገኙም። ለጉትጎታቸው ዋነኛ ምክንያት<br />

ብለው የሚያነሱት ተሿሚው በአስገድዶ ደፋሪዎች ላይ ያላቸው አቋም<br />

ጠንካራ አይደለም የሚል ነው።<br />

ውንጀላውን በፍጹም የማይቀበሉት ዋና ዳኛ ሞጎንግ፣ ፈጣሪ<br />

ዋና ዳኛ እንዲሆኑ እንደሚፈልግ መግለፃቸውን ባለፈው ሳምንት ቢቢሲ<br />

ዘግቦ ነበር። ከ2009 አንስቶ በሀገሪቱ ሕገመንግሥታዊ ፍርድ ቤት<br />

ያገለገሉት ዳኛ ሞጎንግ፣ ከዚህ ቀደምም በሀገሪቱ ‹‹ኖርዝ ዌስት›› ግዛት<br />

<strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong>...<br />

በሚገኝ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሆነው አገልግለዋል።<br />

ታዋቂ የደቡብ አፍሪካ የሕግ ባለሙያዎች፣ የሰብዓዊ መብት<br />

ተሟጋች ቡድኖች እና የደቡብ አፍሪካ የሰራተኞች ማኅበር፣ ሹመቱን በይፋ<br />

ከተቃወሙ አካላት መካከል ይጠቀሳሉ። ከዚህም በተጨማሪ፣ የኖቤል የሰላም<br />

ሎሬቶችን - የኢራኗ ሽሪን ኢባዲ፣ የአየርላንዷ ሜይሪድ ማጉዌር እና<br />

አሜሪካዊቷ ጆዲ ዊሊያምስ - ያቀፈው ሴት የኖቤል ተሸላሚዎች ቡድን (The<br />

Nobel Women’s Initiative) ዋና ዳኛ ሞጎንግን በመቃወም በደተረገው ዘመቻ<br />

ድጋፋቸውን ለግሰዋል።<br />

‹‹እንደዚህ አይነት ኃለፊት ሲመጣ፣ ሳልፀልይና ኃላፊቱንም<br />

እንድወስድ እግዚአብሔር መፈለጉን ውስጤ ሳያረጋግጥ አልቀበለውም››<br />

ያሉት አዲሱ ተሿሚ ዋና ዳኛ ሞጎንግ ናቸው። ጃኮብ ዙማም በአዲሱ ተሿሚ<br />

ኃላፊነት ሥር የፍትህ ሥርዓቱ በአስተማማኝ መዳፎች ውስጥ እንደሆን<br />

ያላቸውን እምነት ገልፀዋል።<br />

በ2004 ውስጥ ዳኛ ሞጎንግ አንድ የሰባት ዓመት ሴት አስገድዶ<br />

የደፈረ ግለሰብ የተፈረደበትን የዕድሜ ልክ እስራት ወደ 18 ዓመት ዝቅ እንዲል<br />

ከገባህ ደግሞ ጠንካራ ቆዳ<br />

ሊኖርህ ይገባል። እኔም ጠንካራ<br />

ቆዳ ያለኝ ነኝና ከትግል ወደ ኋላ<br />

አላልኩም።<br />

አሜሪካ እንደተራ ስደተኛ ነው የገባሁት<br />

እያሉኝ ነው?<br />

አዎ እንደማንኛውም ተራ ስደተኛ<br />

ነው የገባሁት።<br />

እሺ፤ መቼ ነው የተባበሩት መንግስታት<br />

ድርጅት ውስጥ ሥራ የጀመሩት?<br />

ወያኔ አዲስ አበባ ከገባ በኋላ<br />

ነው።<br />

ከተሰደዱ በኋላ ወደ ፖለቲካው ትግል<br />

የገቡት እንዴት ነው? ምንስ አደረጉ?<br />

እንደነገርኩህ ደርግን በፅሁፍ<br />

በማጋለጥ ነው የፖለቲካ ትግል<br />

የጀመርኩት። ከዚያ በኋላ ደርግን<br />

ከሥልጣን ለመጣል መጠቀም<br />

የሚገባን አማራጭ ጦርነት<br />

ሳይሆን፣ በውስጡ ባሉ ኃይሎች<br />

መፈንቀል ነው በሚል ከጓደኞቼ<br />

ጋር ‹‹ነፃ የወታደሮች ንቅናቄ››ን<br />

አቋቋምን። እናም ተራማጅ በሆኑ፣<br />

ለፍትህ በቆሙና በደርግ ውስጥ<br />

ባሉ ከፍተኛ መኮንንኖች <strong>መፈንቅለ</strong><br />

<strong>መንግስት</strong> ለማድረግ ሞከርን።<br />

የ1981 ዓ.ምን ማለት ነው።በዚያ<br />

<strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> ሙከራ ውስጥ<br />

ከሀገር ውጪ ያለውን ሁኔታ<br />

የምናስተባብረው እኔ እና ጓደኞቼ<br />

ነበርን። ያንን ያደረግነው ደርግን<br />

በ<strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> አስወግዶ፣<br />

በኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ የሽግግር<br />

<strong>መንግስት</strong> ማቋቋም አለብን በሚል<br />

ነው።በዚህ መሰረት ከሻዕቢያ ጋር<br />

ብዙ ከተወያየን በኋላ ሥምምነት<br />

ላይ ደርሰን ተፈራረምን።<br />

ምን የሚል ሥምምነት ላይ ደርሳችሁ<br />

ተፈራረማችሁ?<br />

በ<strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> ደርግ<br />

ከስልጣን ከተወገደ፣ ሻዕቢያ<br />

ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የሽግግር<br />

መንግስቱ አባል ሆኖ፣ ስለኤርትራ<br />

ሁኔታ ይወያያል የሚል ስምምነት<br />

ላይ ደርሰን ነው የተወዳደርነው።<br />

የት ተገናኝታችሁ ነው የተወያያችሁት?<br />

ኤርትራ መሬት። እኔ ራሴ ናቅፋ<br />

ገብቼ ነው የተፈራረምነው።<br />

ፊርማው ከመፈንቅል መንግስቱ ሙከራ<br />

ቀደም ብሎ ነው የተከናወነው?<br />

አዎ። የ<strong>መፈንቅለ</strong> መንግስቱ<br />

ዋነኛ ዓላማ ጦርነቱን ማቆም<br />

ነው። ጦርነት የማይቆም ከሆነ<br />

<strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> ማድረግ<br />

ጥቅም የለውም። በጥቅሉ ጦርነት<br />

እናቆማለን፤ ሠላም እንፈጥራለን፤<br />

ከዚያ ሁሉን አቀፍ የሽግግር<br />

<strong>መንግስት</strong> እንመሰርታለን የሚል<br />

ነው ስምምነቱ። ለዚህ ሁኔታ<br />

መሳካት ደግሞ በቅድሚያ<br />

ከሻዕቢያና ህወሀት፣ ከኢህአፓ፣<br />

ከኦነግ ጋር መስማማት ያስፈልግ<br />

ነበር።<br />

ከህወሀት ጋር የት ተነጋገራችሁ?<br />

ዋሽንተን ውስጥም ተነጋግረናል።<br />

በዋናነት ከህወሀትጋር<br />

የተነጋገርነው ግን በሻዕቢያ በኩል<br />

ነው።<br />

ከሁሉም ተቃዋሚዎች ጋር በእኩልነት<br />

የሽግግር <strong>መንግስት</strong> ለመመስረት ማለት<br />

ነው?<br />

እንደዛ ነበር የተስማማነው።<br />

ከዚያስ?<br />

በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ <strong>መፈንቅለ</strong><br />

<strong>መንግስት</strong> ለማካሄድ በከፍተኛ<br />

መኮንኖችና ባለሥልጣናት<br />

መሀከል ሙሉ ስምምነት ተደርጎ<br />

አያውቅም። ሀገር ውስጥ በሁሉም<br />

ደረጃ ያሉ፣ ሁሉም መኮንኖች<br />

በሃሳቡ ተስማሙ። የፖሊስ፣ የጦር<br />

ሰራዊት፣ የአየር ኃይል፣ የባሕር<br />

ኃይል አዛዦች፣ ምክትል አዛዦች<br />

በሙሉ ጉዳዩን ተስማምተውበት<br />

ነው እዚያ ደረጃ የደረሱት። ችግር<br />

መሆን የነበረበት እዚያ ስምምነት<br />

ላይ መድረስ ነበር። እንጂ <strong>መፈንቅለ</strong><br />

መንግሱትን ማካሄድ ችግር መሆን<br />

አልነበረበትም።<br />

እርስዎ ሁሉም ተስማሙ ቢሉም<br />

ሜ/ጄ/ል ኃብተጊዎርጊስ ሀብተማሪያም<br />

ባለመስማማታቸው እኮ ነው በ<strong>መፈንቅለ</strong><br />

<strong>መንግስት</strong> አድራጊዎቹ እንደተገደሉ<br />

የሚታወቀው። እና…<br />

ሁሉም ተስማሙ ስልህ፣ እዚያ<br />

ጉዳይ ውስጥ መታቀፍ የሌለባቸው<br />

መጀመያውኑም አልተነገራቸውም።<br />

ለደርግ ሙሉ ድጋፍ የነበራቸው<br />

እነ ጄ/ል ኃብተጊዎርጊስ ኃ/ማሪያም<br />

አልተነገራቸውም። ሌሎቹ ግን<br />

ተነግሯቸዋል። ለምሳሌ ጄኔራል<br />

መርዕድን ውሰድ። የታወቁ የጦር<br />

መኮንን ናቸው፤ ኮንጎና ኮርያ<br />

የዘመቱ ትልቅ ዕውቀት የነበራቸው<br />

የጦር ሰው ናቸው። ጄ/ል ደምሴ<br />

ቡልቶ ለኢትዮጵያ ጦር ከፍተኛ<br />

አስተዋጽኦ ያደረጉ ናቸው። የባህር<br />

ኃይል አዛዥ ኮሞደር ተስፋዬም<br />

እንዲሁ። እነዚህ ሁሉ ከፍተኛ<br />

የጦር አዛዦች የተስማሙበት<br />

<strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> ነው<br />

የተካሄደው።<br />

እነዚህ ምርጥ የጦር መኮንኖች በእናንተ<br />

ስምምነት መሰረት የሽግግር <strong>መንግስት</strong><br />

በመመስረቱ ጉዳይ ላይ ተስማምተው ነበር?<br />

<strong>መፈንቅለ</strong> መንግስቱ ቢሳካ እንኳ፣ እነሱ<br />

እርስ በርስ ለሥልጣን ሊሻኮቱ ይችላሉ<br />

የሚል ሥጋት የነበራቸው ብዙ ሰዎች አሉ።<br />

ያ ሁኔታ ላለመከሰቱ ምን ማስተማመኛ<br />

ነበራችሁ?<br />

በዋናነት <strong>መፈንቅለ</strong> መንግስቱ<br />

ከተደረገ በኋላ በ15 ቀን ወይም<br />

3 ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ<br />

የሽግግር መንግሰት ይቋቋማል<br />

የሚል ስምምነት ነው የደረስነው።<br />

ሀገር ቤት የጦሩ ኃላፊነት ያቺን<br />

<strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> ማካሄድ ብቻ<br />

ነበር። ሻዕቢያ፣ ህወሀት፣ ኦነግ፣<br />

ኢህአፓ ወዘተ ወዲያው ሀገር<br />

ቤት ገብተው 15 ቀን ባልሞላ<br />

ጊዜ ውስጥ ሽግግር <strong>መንግስት</strong><br />

ለመመስረት ተስማምተው ነበር።<br />

እዚያ አዲስ አበባ <strong>መፈንቅለ</strong><br />

<strong>መንግስት</strong> ማድረግ የተስማሙት<br />

ሰዎች ሌላ ዓላማ ይኑራቸው<br />

አይኑራቸው አላውቅም። ነገር ግን<br />

ከእኛ ጋር የተደረገው ስምምነትና<br />

ዝግጅት እንደነገርኩህ ነው።<br />

ግን የሽግግር መንግስቱን ለማካሄድ የሆነ<br />

ኮማቴ መኖር አለበት። ኮሚቴ ካለ፣ ያንን<br />

ኮሚቴ ማን እንደሚመራው ይታወቃል?<br />

እኔ በውጭ ሀገር በኩል ያለውን<br />

ሁኔታ ነው የማውቀው። ሀገር<br />

ውስጥ እስከመጨረሻዋ ደረጃ<br />

ድረስ የሆነውን የሰማሁት ልክ<br />

እንደእናንተው ነው። እኛ አርብ<br />

ዕለት ካርቱም ገባን። ስምምነት<br />

ላይ ደረስን። ማክሰኞ <strong>መፈንቅለ</strong><br />

<strong>መንግስት</strong> ይደረጋል አሉን።<br />

ማክሰኞ ዕለት ይሳካል ብለን<br />

ለተባበሩት መንግሰታት አንዳንድ<br />

ነገር ስናደርግ <strong>መፈንቅለ</strong> መንግስቱ<br />

ከሸፈ ተባለ። ሌላውን ነገር እኔ<br />

አላውቅም። የሚያውቁት ሀገር<br />

ውስጥ የነበሩት ናቸው። እኔ<br />

‹‹አሉ››ን ነው የምሰማው።<br />

<strong>መፈንቅለ</strong> መንግስቱ ከከሸፈ በኋላ፣ እናንተ<br />

የመሠረታችሁት ነፃ የወታደሮች ንቅናቄ<br />

ተበተነ ወይስ?<br />

አይ… ሌላ ሁተኛና ሶስተኛ<br />

የ<strong>መፈንቅለ</strong> <strong>መንግስት</strong> ሙከራ<br />

ለማድግ ሞክረናል።<br />

(ሻለቃ ዳዊት ወ/ጊዮርጊስ ለዚህና ለሌሎች<br />

አነጋጋሪ ጥያቄዎች የሰጡትን ምላሽ<br />

በሚቀጥለው ሳምንት ይዘን እንቀርባለን።


አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />

መልካም ዓዲስ ዓመት<br />

አድርገው ነበር። ከዓመት በኋላም የሰባት ዓመት ዕድሜ<br />

ሴትን ለመድፈር ሙከራ ያደረገ ግለሰብ የተፈረደበትን<br />

የአምስት ዓመት እስራት ወደ ሁለት ዓመት ዝቅ አድርገው<br />

ወስነዋል። በሌላ ውሳኔያቸው ደግሞ ለአንድ ባለቤቱን/<br />

ሚስቱን ለደፈረ ባል ይቅረታቸውን አጎናፅፈውታል።<br />

የተዘገበው ምክንያታቸውም በወቅቱ ባለቤቱ የምሽት ልብስ<br />

እና የውስጥ ሱሪ ለብሰው የነበረ መሆኑ ነው።<br />

በባልና በሚስት መሀከል የሚደረግ ወሲባዊ<br />

ግንኙነትን እንደ አስገድዶ ደፈራ እንደማይቆጥሩ<br />

በሶስየትድ ፕሬስ የተዘገበላቸው ዋና ዳኛ ሞጎንግ ግን<br />

ይህ ሁሉ ተቃውሞ ቢሰነዘርባቸውም፣ የደቡብ አፍሪካን<br />

ሕገመንግሥት እንደሚያስፈጽሙ እና በሀገሪቱም ላዕላይ<br />

ሕግ መሰረት እንደሚገዙ በመግለጽ ሹመቱን በጸጋ<br />

ተቀብለዋል።<br />

በዓለም አቀፍ ደረጃ የአስገድዶ ደፈራ ወንጀሎች<br />

በተደጋጋሚ ከሚፈፀሙባቸው ሀገራት መካከል ደቡብ<br />

አፍሪካ ከቀዳሚ ተሰላፊዎች መካከል ግንባር ቀደሟ<br />

ናት። በኢንተርፖል መረጃ መሰረት፣ በደቡብ አፍሪካ<br />

በየ17 ሰከንዶች ውስጥ አንድ የአስገድዶ ደፈራ ወንጀል<br />

ይፈፀማል።<br />

/ምንጭ - ቢ.ቢ.ሲ/<br />

በኤልያስ ገብሩ<br />

ከታህሳስ 1953 ዓ.ም. ጀምሮ የኢትዮጵያ<br />

ሕዝብ የሉዓላዊ ስልጣኑ ባለቤት ለመሆን የጀመረው<br />

ሁሉን አቀፍ ትግል ሳይሳካ ሃምሳ ዓመታት<br />

እንደሞላው በመጥቀስ፣ ‹‹ቀጣዩ ዓመት የጨለማ<br />

ጊዜ ሆኖ መቀጠል የለበትም›› ሲል አንድነት<br />

ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ትናንት<br />

መግለጫ አወጣ።<br />

ቀጣዩ 2004 ዓ.ም. ለሁለንተናዊ ነፃነት<br />

ሁሉን አቀፍ የነፃነት ትግል የሚደረግበት ዓመት<br />

ሊሆን እንደሚገባ የገለፀው አንድነት ‹‹የሚደረገው<br />

የነፃነት ትግልም ለኢትዮጵያውያን ሁሉ ለኢህአዴግ<br />

አባላትም ጭምር ነፃነትን የሚያጎናፅፍ ሊሆን<br />

ይገባዋል። ትግሉ ከዘረኝነት ከበቀልና ከቁርሾ የፀዳ<br />

ሁላችንንም ኢትዮጵያውያንን ከሊቅ -እስከ ደቂቅ<br />

በደቡብ ምስራቃዊ አፍሪካ የምትገኘው ማላዊ መሪ የሆኑት ፕሬዝዳንት ቢንጉ<br />

ዋ ሙታሪካ፣ ባቤታቸውን የመንግሥታቸው የሥራ አስፈፃሚ አካል አባል<br />

ማድረጋቸው፣ እና እንዲሁም ወንድማቸውን በፊት ከነበሩበት መንግሥታዊ<br />

ሥልጣን አንስተው ከፍ ላለ ኃላፊነት መሾማቸው አነጋጋሪ አድርጓቸዋል።<br />

ባለፈው ረቡዕ ነበር ባለቤታቸውን ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ እና የሴቶች ጉዳዮች ሚኒስትር<br />

አድርገው የሾሟቸው። ባለፈው ሀምሌ ወር ውስጥ በመንግሥታቸው ላይ በተካሄደ<br />

የተቃውሞ ሰልፍ በተፈጠረ ግጭት 19 ሰዎች ከሞቱ በኋላ በተከተለው የካቢኒ<br />

ብፕወዛ፣ ከባለቤታቸው ካሊስታ ሹመት በተጨማሪ ወንድማቸው ፒተር ሙታሪካ<br />

በሚኒስትርነት ማዕረግ ወደ ሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ተዘዋውረዋል።<br />

የዚያ የሰው ህይወት የጠፋበት ሰልፍ አደራጆች ለፕሬዝዳንት ሙታሪካ አንድ<br />

ጠንካራና ቆራጥ የተባለ ቀነ-ገደብ አስቀምጠውላቸዋል - እስከ መስከረም 21 ድረስ<br />

መንግሥታዊ ማሻሻያዎችን እንዲወስዱ።<br />

ያም ሆኖ፣ ቀነ-ገደቡ ተከበረም አልተከበረም፣ ሚር. ሙታሪካ የሚመሩትን<br />

መንግሥት የቤተ-ዘመድ መሰብሰቢያ አድርገዋል የሚል ውንጀላ በይፋ ከመሰንዘሩ<br />

በፊት ሚስታቸውንና ወንድማቸውን የካቢኔ አባል ለማድረጋቸው አሳማኝ ምክንያት<br />

ማቅረብ እንደሚጠብቅባቸው ማሳሰቢያ ያስተላፉት የአገሪቱ ተቃዋሚ የፖለቲካ<br />

ድርጅት - የማላዊ ኮንግሬስ ፓርቲ - መሪ ጆን ቴምቦ ናቸው።<br />

እንቅስቃሴዎቹንም በቅርበት ስንከታተል ቆይተናል››<br />

ቢሉም የመድረክ አመራሮች ውድቅ አድርገውታል።<br />

መድረኩ ትናንት በሰጠው ጋዜጣዊ<br />

መግለጫ ላይ ‹‹የደበበ እሸቱን መታሰር መድረክ<br />

በተለይም አንድነት ፓርቲ እንዴት ያየዋል?›› የሚል<br />

ጥያቄ ከአውራምባ ታይምስ ቀርቦ የነበረ ሲሆን፣ ባለው<br />

የፖለቲካ አቋም የተነሳ በኢህአዴግ እንደማይወደድ<br />

ያስታወሱት የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ<br />

ጊዳዳ፣ ‹‹እንደ አንድ የኢትዮጵያ ታጋይ እንዲለቀቅ<br />

አንድነትና መድረክ ይጠይቃሉ›› ብለዋል። የፓርቲው<br />

ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆኑት አቶ አንዷለም አራጌም<br />

ደበበ እሸቱን በደንብ እንደሚያውቁትና ‹‹በሽብር<br />

ተግባር ይሰማራል›› የሚል ዕምነት እንደሌላቸው<br />

ተናግረዋል።<br />

የቀድሞው ቅንጅት የላዕላይ ም/ቤት<br />

አባልና የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ የነበረው አርቲስት<br />

ደበበ፣ ምርጫ 97ን ተከትሎ ከሌሎች የቅንጅት<br />

አመራር አባላት ጋር የዕድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበት<br />

ዜናዎች<br />

ፕሬዝዳንቱ ሚስታቸውን ሾሙ<br />

የአፍሪካ ዜናዎች<br />

እንደተንታኞች እይታ ከሆነ፣ ፕሬዝዳንቱ ወንድማቸውን የሾሙበት ዋነኛ ዓላማ<br />

እየተንገዳገደች ላለችው ሀገር ‹‹አዲስ›› መሪ (ወይም ወራሻቸውን) አስቀድመው ለማዘጋጀት<br />

እና በዚህም መንገድ የዓለማቀፋዊ ግንኙቶች ተሞክሮአቸውን ማዳበር ነው።<br />

በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት መግቢያ አካባቢ የሙታሪካ መንግሥት በሙስና ተጨማልቋል፣<br />

ኢኮኖሚውን አመሳቅሏል በሚሉ ዋነኛ ምክንያቶች ዮናይትድ ኪንግደም ለማላዊ ትሰጥ<br />

የነበረውን እርዳታ ማቋረጧ ይታወሳል።<br />

ይህ የኢኮኖሚ ጉዳይ ባለፈው ወር ለተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ ተጠቃሽ ምክንያት ነበር -<br />

በሀገሪቱ ተቃዋሚዎች። ተቃዋሚዎቹ እንደሚሉት፣ ማላዊ ከእንግሊዝ የ73 ዓመታት የቅኝ<br />

አገዛዝ በኋላ በሀምሌ 6/1964 (እ.አ.አ) ነፃነቷን ከተቀዳጀች በኋላ ካጋጠሟት ኢኮኖሚያዊ<br />

ቀውሶች መካከል ይሄኛው በአስከፊነቱ ቀዳሚው ነው።<br />

ከፍተኛ የነዳጅ፣ የኤሌክትሪክ ኃይል እና የውጭ የመገበያያ ገንዘብ እጥረት በአሁኑ ወቅተ<br />

ሀገሪቱን እያመሷት ይገኛሉ። ባለፈው ወር የፕሬዝዳንት ሙታሪካ መንግሥት የሀገሪቱ<br />

የመገበያያ ገንዘብ (‘ዋቻ’) ከዶላር (የአሜሪካ) ጋር ያለውን የምንዛሬ ተመን/ዋጋ ዋጋ ዝቅ<br />

ለማድረግ ተገዶ ነበር።<br />

ከዓለም እጅግ ደሃ ሀገራት ተርታ የምትሰለፈው ማላዊ፣ 75 በመቶ የሚሆነው ሕዝቧ በቀን<br />

ከአንድ ዶላር ባነሰ ገቢ ነው የሚኖረው፤ መኖር ከተባለ።<br />

/ምንጭ - ቢ.ቢ.ሲ/<br />

ሲፒጄ፣ <strong>መንግስት</strong> በጋዜጠኞች ላይ<br />

ያቀረበው ክስ ፍሬ ቢስ መሆኑን ገለፀ<br />

በሱራፍኤል ግርማ<br />

ማድረጋቸውን ላይወድ ይችላል። ግን ጋዜጠኞቹ ርምጃ ነው›› ያለው ጋዜጠኛ ዳዊት፣ <strong>መንግስት</strong> ጋዜጠኞች በተመሳሳይ ሁኔታ የሽብርተኝነት ክስ<br />

ከሥራቸው ፀባይ አኳያ ሁሉንም ወገኖች ማግኘት ጋዜጠኞችን ‹‹በሽብር ተጠርጥረዋል›› እያለ ማሰሩ ተመስርቶባቸዋል።<br />

ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬና ርዕዮት ዓለሙን ግድ ይላቸዋል›› ሲል የ<strong>መንግስት</strong>ን ‹‹ከአሸባሪዎች የ<strong>መንግስት</strong> ጥገኛ ያልሆኑና ተቺ የሚዲያ ተቋማትን<br />

ብሉምበርግ በድረ ገፁ፣ የ<strong>መንግስት</strong><br />

ጨምሮ በሽብርተኝነት ክስ የቀረበባቸውን የስዊዲን<br />

ጋዜጠኞች <strong>መንግስት</strong> በአፋጣኝ እንዲፈታ የጋዜጠኞች<br />

መብቶች ተሟጋች የሆነው ሲፒጄ ጠየቀ። ባወጣው<br />

መግለጫ የኢትዮጵያ <strong>መንግስት</strong> የፀረ ሽብርተኝነት<br />

ሕጉን ለነፃ ፕሬስ ማፈኛነት እየተጠቀመበት መሆኑን<br />

ያስታወቀ ሲሆን፣ ‹‹<strong>መንግስት</strong> ይሄን ፍሬ ቢስ ክሱን<br />

በመተው ጋዜጠኞቹን ሊፈታ ይገባል›› ብሏል።<br />

የሲፒጄ በአፍሪካ አስተባባሪ የሆነው<br />

ሞሐመድ ኪየታም ‹‹የኢትዮጵያ <strong>መንግስት</strong> ‹ሽብርተኛ›<br />

ብሎ ከፈረጃቸው ወገኖች ጋር ጋዜጠኞቹ ግንኙነት<br />

ጋር ንክኪ አላቸው›› የሚል ክስ ውድቅ አድርጓል።<br />

የአውራምባ ታይምስ ም/ዋና አዘጋጅ<br />

በአሸባሪነት መከስስን አስመልክቶ ለተለያዩ ዓለም<br />

አቀፍ የሚዲያ ተቋማት አስተያየቱን የሰጠው<br />

የአውራምባ ታይምስ ማኔጂንግ ኤዲተር ዳዊት ከበደም<br />

በባልደረባው ላይ የቀረበውን ክስ እንደማይቀበል<br />

አስታውቋል።<br />

ለአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ የእንግሊዘኛ<br />

አገልግሎት ዘጋቢ ፒተር ሄንሌ በስልክ በሰጠው ቃለ<br />

መጠይቅ ‹‹ይህ ክስ ነፃውን ፕሬስ ለማሸማቀቅ የተወሰደ<br />

ለማጥፋት የተቀነባበረ ሴራ መሆኑን ተናግሯል።<br />

የ<strong>መንግስት</strong>ን ፖሊሲዎች መተቸት<br />

በአሸባሪነት እየተተረጎመ መሆኑን ያስገነዘበው<br />

የአውራምባ ታይምስ ማኔጅንግ ኤዲተር፣ ለብሉም<br />

በርግ የዜና አውታርም ‹‹የባልደረባችን በሽብር መከሰስ<br />

ጋዜጣው ላይ ተፅዕኖ የማሳረፊያ አንዱ መንገድ ነው››<br />

ሲል ሁኔታውን አብራርቷል።<br />

በሌላ በኩል ከወራት በፊት ፓርላማ<br />

በአሸባሪነት ከፈረጀው ኦብነግ ታጣቂዎች ጋር<br />

ጂጂጋ ከተማ አካባቢ የተያዙት ስዊዲናያዊያን<br />

ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚኒስትር ዲኤታ አቶ<br />

ሽመልስ ከማል ‹‹ግለሰቦቹ ወደ አገር ውስጥ የገቡት<br />

በሕገ ወጥ መንገድ ነው፡፡ ከጋዜጠኝነት ሥራ ውጪ<br />

የጦር መሳሪያ አጠቃቀም ስልጠና ወስደዋል፤ የጦር<br />

መሳሪያ ይዘው የሚያሳይ የቪዲዮ ቴፕም አቃቤ ሕግ<br />

አለው›› ማለታቸውን አስነብቧል።<br />

ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬና ርዕዮት ዓለሙ<br />

ክስ ከተመሰረተባቸው በኋላ በፖሊስ ምርመራ ላይ<br />

ከነበሩበት ‹‹ማዕከላዊ›› ወደ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት<br />

የተዛወሩ ሲሆን፣ ለጥቅምት ዘጠኝ ቀን 2004ዓ.ም<br />

ተቀጥረዋል።<br />

‹‹የኢትዮጵያ ሕዝብ የተነጠቀው ነፃነቱን ለመቀዳጀት ዛሬውኑ ለትግል ይነሳ››<br />

አንድነት ፓርቲ<br />

የሚያስተባብር አንድነታችንን ከመቼውም ጊዜ በላይ<br />

ጎልቶ የሚወጣበት ሊሆን ይገባዋል።›› ብሏል።<br />

የነፃነት ትግሉም መጀመሪያ ፍርሃትን<br />

ድል መንሳት መሆኑን በመጥቀስም፣ በአሁኑ ወቅት<br />

በአረቡ ዓለም እየተካሄደ ያለው የነፃነት ትግልና<br />

ውጤቱም ተግባራዊ ተሞክሮውን ማጠናከሩን፣<br />

ሕዝቡ ነፃ አውጪዎችን ቁጭ ብሎ የሚጠብቅበት<br />

ጊዜ ማብቃቱንና እያንዳንዱ የኢትዮጵያ ሕዝብም<br />

የነፃነቱ ባለቤት ለመሆን አበክሮ ሊታገል እንደሚገባው<br />

መግለጫው አትቷል።<br />

‹‹የወደፊቷን የበለፀገችና ዴሞክራሲያዊት<br />

ኢትዮጵያን መፍጠር ላለበት ኢትዮጵያዊ ወጣት ግን<br />

አምባገነን አገዛዝን ተሸክሞ መኖር ፈፅሞ አማራጭ<br />

ሊሆን አይችልም። በመሆኑም የነፃነት ህልምን እውን<br />

ለማድረግ በ2004 ዓ.ም. የመጀመሪያው እርምጃ<br />

ፍርሃትን ድል መንሳት ነው›› በማለት ፓርቲው<br />

ለኢትዮጵያዊ ወጣት ጥሪውን አስተላልፏል።<br />

ደበበ እሸቱ እንዲፈታ አንድነት...<br />

እንዲሁም በገዥው ፓርቲ ቡራኬ<br />

የሚተዳደሩና ለገዥው ፓርቲ የጭቆና አገዛዝ<br />

ድጋፋቸውን ቀጥተኛ በሆነና ባልሆነ መንገድ እየሰጡ<br />

የሚገኙ “ተቃዋሚ ፓርቲዎች” ሳይረፍድ ከሕዝብ ጎን<br />

እንዲቆሙ አንድነት ሀሳቡን ሰንዝሯል።<br />

የኢትዮጵያ ዲያስፖራም ትኩረቱ የነፃነት<br />

ጥያቄ ላይ መሆን ስለሚገባው ለጥያቄው ተጠናክኖና<br />

ተደራጅቶ መውጣት እንደሚገባው፣ ዓለም አቀፍ<br />

ማሕበረሰብም የኢትዮጵያ ሕዝብ አሁን ካለበት<br />

የጭቆናና የችጋር አዘቅት ራሱን ነፃ ለማውጣት<br />

ለሚያደርገው ትግል ከመቼውም ጊዜ በላቀ መልኩ<br />

ድጋፍ እንዲሰጥ ፓርቲው ጠይቋል።<br />

በመጨረሻም ለኢህአዴግ ጥሪውን<br />

ያስተላለፈው አንድነት፣ አገዛዙ ለሕዝብ ሰላማዊ<br />

የለውጥ እንቅስቃሴ ሰላማዊ ምላሽ ቢሰጥ ከምንም<br />

በላይ ለራሱ፣ ለሕዝብ፣ ለሀገርና ለትውልድ ጠቃሚና<br />

ክቡር ውጤት ማስመዝገብ ይችላል ብሎ እንደሚያምን<br />

በይቅርታ መፈታቱና ከእስር ከተፈታ በኋላ<br />

በመስራችነት ባቋቋመው አንድነት ለዴሞክራሲና<br />

ለፍትሕ ፓርቲ ውስጥ በተፈጠረው የሀሳብ ልዩነት<br />

የተነሳ ‹‹መርህ ይከበር›› በሚል አቋሙ ከፓርቲው<br />

መሰናበቱ ይታወሳል።<br />

ከፖለቲካዊ እንቅስቃሴው በተጨማሪ<br />

በተለያዩ ኪነ-ጥበባዊና ማህበራዊ ክንዋኔዎች ላይ<br />

ተሳታፊ የነበረው አርቲስት ደበበ፣ በሸገር ኤፍ.ኤም<br />

ላይ የመጽሀፍት ትረካ ሲያቀርብ ቆይቷል።<br />

ከመታሰሩ ጥቂት ሠዓታትን ቀደም ብሎ<br />

ለፍትሕ ጋዜጣ የአዲስ ዓመት መልካም ምኞቱን<br />

የሚገልፅ ፅሁፍ ያስገባው ደበበ እሸቱ፣‹‹አዲሱ ዓመት<br />

ከሰቀቀን ኑሮ ተላቀን እፎይ የምንልበት፣በፍራቻ<br />

ሳይሆን በመምረጥ የምንኖርበት እንዲሆን እመኛለሁ››<br />

ብሎ ነበር።<br />

‹‹ረሐብን ማጋለጥ በሽብርተኝነት<br />

ሊያስወነጅል አይገባም›› በሚል ርዕስ የኢትዮጵያ<br />

ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ በሰጠው<br />

ከመታሰሩ ጥቂት ሠዓታትን ቀደም ብሎ ለፍትሕ ጋዜጣ የአዲስ<br />

ዓመት መልካም ምኞቱን የሚገልፅ ፅሁፍ ያስገባው ደበበ እሸቱ፣‹‹አዲሱ<br />

ዓመት ከሰቀቀን ኑሮ ተላቀን እፎይ የምንልበት፣በፍራቻ ሳይሆን<br />

በመምረጥ የምንኖርበት እንዲሆን እመኛለሁ›› ብሎ ነበር።<br />

19<br />

ገልጿል።<br />

በተያያዘ ዜናም ነሐሴ 29 ቀን 2003<br />

ዓ.ም በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ከዜና እወጃ በኋላ ፕ/ር<br />

በየነ ጴጥሮስ በኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰተውን ድርቅ<br />

ምክንያት በማድረግ ተዘጋጅቶ የነበረውን አንድ<br />

የማስተባበያ ፕሮግራም አንድነት ተችቶታል። በዚህ<br />

ፕሮግራም ላይ ቀርበው ከተናገሩት ሰዎች መካከል<br />

በተለይ ሁለቱ ‹‹የመድረክ አባላት ነን›› በማለት<br />

ያቀረቡት አስተያየት የተሳሳተ መሆኑ በመጥቀስ፣<br />

አንደኛ አቶ አበበ ታምራት ከሀምሌ 13/2003 ዓ.ም<br />

ጀምሮ በሥነ-ምግባር ችግር ምክንያት ከፓርቲው<br />

መታገዳቸውን ተገልጿል። ሁለተኛ አቶ አጥናፉ<br />

የተባለው ግለሰብ ደግሞ በሥነ-ምግባር ብልሹነት<br />

የሚታወቅና የመድረክ አባል አለመሆኑን መድረክ<br />

ትናንት በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።<br />

መግለጫ ዋና ርዕሰ ጉዳይ የነበረው በቅርቡ የታሰሩት<br />

የመድረክ አመራር አባላት ጉዳይ ነበር። ለአቶ በቀለ<br />

ገርባ አና ለአቶ ኦልባና ሌሊሳ መታሰር <strong>መንግስት</strong><br />

‹‹ከኦነግ ጋር ሲያሴሩ ነበር›› የሚል ምክንያት<br />

ቢያቀርብም፣ መድረኩ ይህን ውድቅ አድርጎታል፡፡<br />

በመግለጫው መሠረት ለሁለቱ ግለሰቦች<br />

መታሰር ዋንኛው ምክንያት በኢትዮጵያ ስላለው<br />

አጠቃላይ ሁኔታ ለአምንስቲ ኢንተርናሽናል መረጃ<br />

በመስጠታቸውና የኢህአዴግ <strong>መንግስት</strong> የእርዳታ<br />

እህልን ለፖለቲካ መሳሪያነት እያዋለው መሆኑን<br />

ለዘገቡት የቢቢሲ ጋዜጠኞች ጥቆማ በመስጠታቸው<br />

ነው።<br />

ፖለቲከኞቹ የምር የኦነግ አባላት ቢሆኑ<br />

ኖሮ ከኦነግ የሚፃረር የፖለቲካ ፕሮግራም ባለው<br />

መድረክ ውስጥ አባል ከመሆን ይልቅ መገንጠልን<br />

በሚደግፈው ኢህአዴግ ውስጥ መታቀፍ ይችሉ<br />

እንደነበር አቶ ጥላሁን እንዳሻው የተባሉ የመድረክ<br />

አመራር አስገንዝበዋል።<br />

የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ደሞክራሲያዊ<br />

አንድነት መድረክ ሽብርተኝነትን በምንም መልኩ<br />

እንደማይደግፍ አፅንኦት የሰጡት አቶ ገብሩ አስራት<br />

ደግሞ በበኩላቸው፣ ኢህአዴግ ተቃዋሚዎቹንና<br />

ተቺዎቹን በማሰር አጠቃላይ ሕዝቡን እያሸበረ<br />

መሆኑን ገልፀዋል።<br />

በሽብርተኝነት ክስ ስለተመሰረተባቸው<br />

ስዊዲናዊያን ጋዜጠኞች ጉዳይም በመግለጫው ላይ<br />

ተነስቷል። ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ‹‹ሁለቱ ጋዜጠኞች<br />

በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ በመግባት<br />

ሉዓላዊነታችን መደፈሩን እንዴት ያዩታል?›› የሚል<br />

ጥያቄ ለአቶ አንዷለም አራጌ ቀርቦ የነበረ ሲሆን፣<br />

አቶ አንዷለምም ‹‹ኢህአዴግ ሁለት ሰዎች ድንበር<br />

አቋረጡ ብሎ ሊጨነቅ ይቅርና አገር ገንጥሎ የሚሰጥ<br />

ድርጅት ነው›› የሚል መልስ ሰጥተዋል።<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ


20<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />

መልካም ዓዲስ ዓመት<br />

‹‹በቴሌቪዥን በሚሰሩት ‘ድራማ’<br />

ሀቅ ሊወጣ አይችልም››<br />

ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ<br />

/የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ ሊቀ-መንበር እና የመድረክ ምክትል ሊቀ-መንበር/<br />

በአንድ ወር በፊት ቢቢሲ ኒውስ ናይት በተሰኘው ፕሮግራሙ ላይ የኢትዮጵያ <strong>መንግስት</strong> የሚሰጠውን እርዳታ ለፖለቲካ ፍጆታ እንደሚያውለው፣ የተደበቀ<br />

ረሀብ በኢትዮጵያ እንደሚገኝና ሌሎች ሀሳቦችን የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችን እና ቦታው ድረስ ተገኝቶ ተጎጂ ያላቸውን ዜጎች በማነጋገር ዘገባ<br />

ካቀረበ በኋላ የኢትዮጵያ <strong>መንግስት</strong> በተለያየ መንገድ ዘገባው የተሳሳተ መሆኑን መግለፁ ይታወሳል። ባለፈው እሁድ ምሽት በኢትዮጵያ ፈርስት ድረ-ገጽ<br />

ኤዲተር ቢኒያም ከበደ ተዘጋጅቶ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የቀረበው ‹‹ዶክመንተሪ›› ፊልምም በዋነኛነት ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ላይ ባጠነጠነ መልኩ<br />

ለቢቢሲ የሰጡት አስተያየት እውነትነት እንደሌለው የገለፀ ነበር። በዚህና በመሰል ጉዳዮች ዙሪያ የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ ሊቀ-መንበር፣<br />

የመድረክ ምክትል ሊቀ-መንበርና የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆኑት ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስን አቤል ዓለማየሁ አነጋግሯቸዋል።<br />

ኒውስ ናይት በተሰኘው የቢቢሲ ፕሮግራም ላይ <strong>መንግስት</strong> አገር ውስጥ የሚገባ የእርዳታ እህልን ለፖለቲካ ጥቅም እያዋለው እንደሆነ፣ የሚረዱትም<br />

የኢህአዴግ አባላት (ደጋፊዎች) መሆናቸውን ገልፀዋል። ይህን ሀሳብ የሰነዘሩት ከምን ተነስተው ነው?<br />

ኢህአዴግ አባላቱ በሆኑና ‹‹ተቃዋሚ›› በሚላቸው መሀከል አድሎ እንደሚያደርግ ባለፈው 20 ዓመት ስንናገረው የነበረ<br />

ነው። አሁን እነሱን ለምን እንዲህ እንዳርበተበታቸው እኔ’ንጃ። ጉዳዩ ለንደን ደርሶ በቢቢሲ በኩል ተመልሶ ስለመጣ ነው?<br />

በየቀኑ ለጋዜጠኛ ጋዜጣዊ መግለጫ ስንሰጥ የምንናገረው ነው።<br />

በተራቡት ዜጎች ላይ ሞራል የሚነካ ሥራ እንደሚሠራ በአደባባይ ነጋ ጠባ ስናወራው የነበረ ነው። ፓርላማ ውስጥ<br />

በነበርንበት ጊዜም ስንገልፀው የኖርነው ነው። ስም ዝርዝር ሰብስበን ለእርዳታ ለጋሾች ሰጥተን እናውቃለን። ለኢፒጂ<br />

(Ethiopian Partners Group)፣ ዓለም ባንክና ለሌሎችም ሰጥተናል።<br />

ስም ዝርዝራቸው የተገለፀው ሰዎች ምንድን ናቸው?<br />

በምርጫ ሰሞን ባለ ሽኩቻ ሰዎች ማንን እንደሚደግፉ በሚያደረጉት እንቅስቃሴ ወረዳ አመራሮች ተለይተው ይታወቃሉ።<br />

የተቃዋሚ ደጋፊዎችን ምርጫው እንዳለቀ ከሴፍቲ ኔት ዝርዝር ያስወጧቸዋል። እውነታውን ለመደበቅ የሚጠቀሙበት<br />

ቃል ‹‹እናንተ ጨርሳችኋል›› የሚል ነው። የእነዚህ ሰዎች ስም እና የቦታቸውን ስም ዝርዝር ለጠቀስኳቸው ድርጅቶች<br />

ሰጥተናል።<br />

ይህ ችግር በቀድሞ ጊዜም ሆነ አሁን ድረስ አለ ነው የሚሉት?<br />

ይሄ ችግር ድሮም ሆነ አሁንም ያለ ነው። ኢህአዴግ በበቂ መረጃ ማስተባበል የቻለበትን ሁኔታ እስከዛሬ አልተመለከትኩም።<br />

ይህንን አድበስብሶ ማለፍ አይቻልም። የተራበውን ህዝብ [በተለይ የእኛ ደጋፊውን] ‹‹ይህ የመጣው ለኢህአዴግ አባላት<br />

እና ደጋፊዎች ነው። ለእናንተ በየነ ጴጥሮስ ሲያመጣ ትበላላችሁ›› ይሏቸዋል። ይህ የተለመደ አባባል ነው። ጨዋታው<br />

ያለው እነሱ ካምፕ ነው። ለሁሉም እየሰጡ መሆኑን በተግባር ካየን እኛም ወቀሳችንን እናቆማለን። በቴሌቪዥን<br />

በሚሰሩት ድራማ ሀቅ ሊወጣ አይችልም።<br />

‹‹ኢህአዴግ እርዳታን ለፖለቲካ ጥቅም ያውለዋል›› ሲሉ እውን ፖለቲካ ልዩነትን ከማንፀባረቅ በፀዳ መልኩ ነው?<br />

በምርጫ ሰሞን በከባድ መኪና የእርዳታ እህል ሞልቶ የምግብ እጥረት አለ ወደሚባልበት ቦታ መሄዱ ሲሄዱ ለማን<br />

ድምፅ መስጠት እንዳለባቸውም መመሪያ ይሰጧቸዋል።<br />

ዳቦ በጆንያ ይዘው አድለው ከጨረሱ በኋላ ‹‹አባል ሁኑ›› የሚሉበት ሁኔታ መኖሩን እናውቃለን። ሩቅ ሳትሄድ እዚህ<br />

አዲስ አበባ ለኢህአዴግ ድምፅ ይሰጣል ለተባለ ጎረምሳ ሁሉ ሰላሳ እና ሃምሳ ብር ሲያድሉ ይውሉ አልነበር እንዴ?<br />

አድልዎ ማለት ይሄ ነው፤ በገንዘብ ድምፅ መግዛት።<br />

የትም ቀበሌ ያለ ወጣት ሥራቸውን ይንቃል። ገንዘቧን ግን ‹‹እፈልጋታለሁ›› ብሎ ይወስዳል። ይህን የሚያደርጉት የቀን<br />

የውሎ አበል የሚከፈላቸው ካድሬዎቻቸው ናቸው። በአንድ የምርጫ ክልል ብቻ ሰዎች [የእኛ ደጋፊዎች] ‹‹እህላችን<br />

ሳይደርስ ቀርቶ እርዳታ ብንጠይቅም ተገለልን እናም ተቸግረናል›› ብለው ፅፈው ፈርመው የላኩልን መረጃዎች እጃችን<br />

ላይ አሉ።<br />

ይህ ከሆነ እርዳታ ለጋሾች ሊያውቁ አይችሉም ብለው ያስባሉ?<br />

እርዳታ ሰጪዎች ‹‹እርዳታ የሚገባው ለእነዚህ ነው›› የሚል ሚና የላቸውም። ከወረዳ/ከቀበሌ ተጣርቶ በተላለፈላቸው<br />

ስም ዝርዝር መሰረት ይሰጣሉ። ተመርጠው የመጡት ሰዎች የኢህዴግ ሰዎች ይሁኑ/አይሁኑ የሚያውቁት ነገር<br />

የለም።<br />

መድልዎ እየፈፀመ ያለው ስም ዝርዝር የሚሰጠው አካል ነው። የእኛ አባላት ‹‹በሴፍቲ ኔት አንታቀፍም፣ እርዳታ<br />

ሲመጣ ስም ዝርዝራችን የለም›› ይሉናል። እንደውም መታወቂያ ሁሉ እየታደለ ነው። ለእኛ ሰዎች ግን ያንን መታወቂያ<br />

እሺ ብለው አይሰጡም። እኛ መረጃ ሳይኖረን ዝም ብለን አንናገርም።<br />

ቢቢሲ ዘገባውን ካስተናገደ በኋላ <strong>መንግስት</strong> ላይ ተቺ ሀሳብ የሰነዘራችሁ ተቃዋሚ ፖለቲከኞችን በምርጫ ድምፅ ህዝብ ስለቀጣችሁና ተስፋ ስለቆረጣችሁ<br />

ባገኛችሁት አጋጣሚ ውሸትን (ጥላቻን) እንደምትሰብኩ በ<strong>መንግስት</strong> መገናኛ ብዙሐን ላይ ስሞታ ቀርቦባችኋል። ይስማማሉ?<br />

ይህ በራሱ በጣም ሰፊ አወያይ ርዕስ ነው። መድረክ ከምርጫው በኋላ ‹‹ኢህአዴግ አዳፍኖት ለማለፍ ያቀደው የአገራችን<br />

የዴሞክራሲ ሂደት ግንባታ በህዝባችን ሰላማዊ ሂደት ይከሽፋል›› የሚል መግለጫ መስጠቱ ይታወሳል። እዚያ ላይ<br />

የነበሩትን ችግሮች ዘርዝረናቸዋል። ‹‹ምርጫው ድራማ እንጂ ፍትሃዊ አልነበረም፣ የምር’ኮ ውጤት ነው›› ብለናል።<br />

እኔ ከማንም በላይ ፓርላማ የቆየሁ ሰው ነኝ፤ ከሽግግሩ ወቅት ጀምሮ። ያኔ ሁሉ የምናቀርበው ክስ ነው። በምርጫ<br />

ባሸነፍኩባቸው ጊዜያት ‹‹በየነ ጴጥሮስን መርጣችሁ ምን አገኛችሁ? እሱ ያመጣውን እርዳታ ብሉ›› እያሉ ይዘባበቱባቸው<br />

ነበር። ይሄ እውነታ እንጂ ከምርጫ መሸነፍና ማሸነፍ ጋር የሚያያዝ አይደለም።<br />

ለምሳሌ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ወደሃድያ አካባቢ፤ ሆሳዕና ድረስ ስንት ጊዜ ሄዱ? ድሮ የትኛው ቦታ ሄደው ያውቁ<br />

ነበር? ጨርሶ ታይተው አይታወቁም። በምርጫ ስለተሸነፉ ግን ተመላለሱ። በተወሰነ መንገድ ተሳክቶላቸዋል። የህዝቡን<br />

ልብ ግን መቼም አያገኙትም። ሰዉ በተወሰነ መልኩ ዲፕሎማት ሆኗል። በቀጥታ መቃወም ትቷል። እኔ ብሄድ ግን<br />

‹‹ሆ›› ብሎ እንደሚቀበለኝ አውቃለሁ። የገለፅኳቸው ነገሮች ሁሉ ያሉና የማምንባቸው ናቸው።<br />

ቢቢሲ ላይ የእናንተ ሀሳብ (ክስ) መስተናገዱን ማጣጣል ላይ መሰረት ያደረገ ‹‹ዶክመንተሪ›› ፊልም ባለፈው እሁድ ምሽት በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን<br />

ቀርቧል። እንደተመለከቱት ነግረውኛልና በዚህ ዙሪያ ምን ይላሉ? አዘጋጁ በእርስዎ የትውልድ መንደር ባደዋቾ ድረስ ሄዶ…<br />

እኔ የተናገርኩት በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው የተደበቀ ረሃብ እንጂ ስለተወለድኩበት አካባቢ የተለየ ሁኔታ<br />

ያነሳሁት ነገር የለም። እንዳለኝ መረጃም ከሆነ የቢቢሲ ዘጋቢዎች እኔ የተወለድኩበት አካባቢም አልሄዱም። እነሱ<br />

በጠቋሚዎቻቸው አማካኝነት ማየት የፈለጉት ኢትዮጵያ ውስጥ የተደበቀ ረሃብ እንዳለ፣ ርዳታ የፖለቲካ አንድምታ<br />

ስላለው በፍትሃዊነት እንደማይዳረስ መረጃ ይዘው ነው የመጡት።<br />

ያወራነው ዋሻ ውስጥ ሳይሆን የሚታወቅ ሆቴል ውስጥ ነው። የአቶ ቢኒያም (የዶክመንተሪው አዘጋጅ እና ኢትዮጵያ<br />

ፈርስት ድረ-ገጽ ኤዲተር) አካሄድ ነገር ፍለጋ እንጂ የሚገናኝም ነገር የለውም፤ ‹‹ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ›› ዓይነት<br />

ነው። እኔ በኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው ነገር እያወራሁ እኔ አካባቢ መሄድ ምን ማለት ነው? የእሱን (የቢኒያምን) ጥበት<br />

ነው የሚያሳየው። የፈለገው እኔን በአካባቢዬ ብቻ ሊገድበኝ ነው። [ሳቅ እያሉ] የእኔ የመረጃ ምንጮች በመላው ኢትዮጵያ<br />

ይገኛሉ። ኃላፊነቴም በዚያው ያህል ነው።<br />

እንደዚህ ዓይነት ነገር ውስጥ የሚገባው ቅጥረኛ ሰው ነው። እውነት እና ሀቅ ፈላጊ ቢሆን ‹‹አንተ የምርጫ ጣቢያ<br />

(የትውልድ አካባቢ) እየሄድኩ ስለሆነ የማናግራቸውን ሰዎች ስጠኝ›› ማለት ነበረበት። ቢቢሲ ቢያናድደውም ስለ ቢቢሲ<br />

የሚታመን የመረጃ አካል መሆንና/አለመሆን እሱ ክሬዲት የመስጠት አቅም ያለው አይመስለኝም። ‹‹የአገራችንን ስም<br />

አጎደፉ›› የሚል ‹‹አርበኛ ነኝ›› ባይ ነው። ምክንያታዊ ሆኖ ‹‹አርበኛ›› ቢሆን እኔ ችግር የለብኝም። ‹‹ጋዜጠኛ (መረጃ<br />

ሰብሳቢ ነኝ)›› ካለ አካሄዱ ጤናማ/ሚዛናዊ አልነበረም። የሄደው ለአንድ ወገን የሚሆን መረጃ ይዞ ለመምጣት ብቻ ነው።<br />

ነገር የማይገባው የዋህ ነው።<br />

ያነጋገራቸው ሰዎች የኢህአዴግ ጥቅም ተካፋዮች ይሆናሉ ብሎ ሳይጠረጥር ቀርቶ ነው? ያነጋገራቸው በአጋጣሚ ደርሶ<br />

ያገኛቸውን ሰዎች ናቸው? [እየሳቁ] አይደለም። የማውቀው የወረዳ ሊቀ-መንበር የቆመበት መሀከል ነው ሲያዋራቸው<br />

የነበረው። እናስ ‹‹ረሃብ፣ ችግር፣ አድሎ አለ›› እንዲሉ ይጠብቃል?<br />

የእርስዎ አጎት ሚስት በግብዓትነት ቀርበው ክስዎ ውሸት መሆኑን ‹‹<strong>መንግስት</strong> ለተቃዋሚ/ለደጋፊ ብሎ ለያይቶ እርዳታ እንደማያከፋፍል ተናግረዋል።<br />

ይህስ ማረጋገጫ መሆን አይችልም?<br />

በ ገፅ 23


አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />

መልካም ዓዲስ ዓመት<br />

በናፍቆት ዮሴፍ<br />

የዘመን መለወጫ<br />

( እ ን ቁ ጣ ጣ ሽ )<br />

በ ሀ ገ ራ ች ን<br />

ከሚከበሩ ሀገራዊና<br />

ሀ ይ ማ ኖ ታ ዊ<br />

በዓላት አንዱ<br />

ከመሆኑም ሌላ<br />

ከሌሎች በዓላት<br />

የሚለይበት በርካታ ገጽታዎች<br />

አሉት።<br />

አሮጌው አልፎ አዲስ ዓመት<br />

ሲተካ ብዙዎች የአዲስነት<br />

ስሜት የሚላበሱበት፤ በአሮጌው<br />

አመት ያላሳኩትን ለመከወን<br />

የሚያቅዱበት፤ ሱሰኞች ከሱስ<br />

ነፃ ለመውጣት፣ ብቸኞች በጋብቻ<br />

ለመጣመር፣ ሌሎች ለመማር<br />

(ከስህተትም ሆነ የቀለም<br />

ትምህርት) የሚያቅዱበት፤<br />

በአጠቃላይ ብሩህ ተስፋ<br />

የሚሰነቅበት በዓል ነው።<br />

በበዓሉ መቃረቢያ ልጃገረዶች<br />

‹‹እንቁጣጣሽ እንኳን መጣሽ››<br />

እያሉ ሲጨፍሩ ልጅነት<br />

የሚታወስበትም ነው - የዘመን<br />

መለወጫ። ከዚያም አልፎ በዓመት<br />

አንድ ጊዜ ብቻ የሚበቅለው ደማቅ<br />

ቢጫ አደይ አበባ የሚታይበትም<br />

ስለሆነ በዓሉ ልዩ ስሜትን<br />

ያላብሳል።<br />

‹‹እንቁጣጣሽ›› ማለት?<br />

በዓሉ ሁለት መጠሪያዎች<br />

እንዳሉት - ‹‹እንቁጣጣሽ›› እና<br />

‹‹ቅዱስ ዮሀንስ››። በዚህ ፅሁፍ<br />

በዓሉ ለምን ቅዱስ ዮሀንስና<br />

እንቁጣጣሽ እንደተባለና ታሪካዊ<br />

ዳራውን ለማስቃኘት ወደናል።<br />

ቅዱስ ዩሀንስ<br />

ሀመር መፅሄት በመስከረም<br />

1996 ዓ.ም እትሙ፣ የአይሁድ<br />

ንጉስ የነበረው ንጉስ ሄሮድስ<br />

የወንድሙ የፊልጶስ ሚስት<br />

የሆነችውንና ‹‹ሄሮዲያደን››<br />

የተባለችውን ሴት ባገባ ጊዜ<br />

መጥምቁ ዮሀንስ ‹‹የወንድምህ<br />

ሚስት ለአንተ እንድትሆን<br />

አልተፈቀደም›› ብሎ በማስተማሩ<br />

ጳጉሜ አንድ ቀን ታስሮ መስከረም<br />

ሁለት ቀን አንገቱ በሰይፍ ተቀልቶ<br />

ሞተ። ይህ ቅዱስ የህግ አዲስ<br />

ካህን፣ ነቢይና ሐዋሪያ በመሆኑ<br />

መታሰቢያው የአዲስ ዘመን<br />

መባቻ ተደርጎ በእስክንድሪያና<br />

በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር<br />

በዓላት የሚከበሩበት፣ እንዲሁም<br />

አፅዋማት የሚገቡበት ተደርጎ<br />

መወሰዱን፣ እናም ቀኑም በስሙ<br />

ቅዱስ ዮሀንስ ተብሎ መሰየሙን<br />

ይገልፃል። ዘመኑም በዚሁ እለት<br />

ይታደሳል፣ ይለወጣል።<br />

መፅሄቱ ሁለት ዮሐንሶች እንዳሉ<br />

ይገልፃል፡- መጥምቀ መለኮት<br />

ቅዱስ ዮሐንስ እና ሐዋሪያውና<br />

ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሀንስ። ዘመኑ<br />

የተሰየመው አራተኛውን ወንጌል<br />

በፃፈው በዮሀንስ ወልደ-ነጎድጓድ<br />

ሲሆን፣ ቃለ-ነቢይ ልዑል ዮሀንስ<br />

መስከረም አንድ ቀን በ1979 ዓ.ም<br />

ለኢትዮጵያ ሬዲዮ የሰጡትን ቃለ-<br />

ምልልስ ጠቅሶ ዘግቧል።<br />

መፅሄቱ፣ ዘመኑ በስሙ<br />

ስለተሰየመለት ቅዱስ ዮሀንስ<br />

ሌላም ተጨማሪ መረጃ<br />

አጣቅሷል።<br />

‹‹ዘመን አልፎ ዘመን ሲተካ<br />

የመሸጋገሪያው ዕለት በየአመቱ<br />

ቅዱስ ዮሀንስ እየተባለ ይጠራል።<br />

ይህም የነቢዩ የዘካሪያስ ልጅ<br />

መጥምቁ ዮሀንስ ነው፡፡ በዘመነ-<br />

ብሉይ መጨረሻና በዘመነ<br />

ሀዲስ መጀመሪያ ላይ ተነስቶ<br />

‹መንግስተ-ሰማያት ቀርባለችና<br />

ንስሀ ግቡ› እያለ ስለክርስቶስ<br />

አዳኝነት ስላስተማረ በየአመቱ<br />

የዘመን መጀመሪያ በእርሱ ሥም<br />

እንዲጠራ ተደርጓል›› ሲሉ ቀሊኃ<br />

ልሳኑ በዛብህ ‹‹ልሳነ-ተዋህዶ ዘ<br />

ኦርቶዶክስ” በተሰኘ፣ በ1987<br />

ዓ.ም በቁጥር ሰባት መፅሀፍ<br />

መፃፋቸውን ያትታል።<br />

ልዩ ቅኝት<br />

እንቁጣጣሽ<br />

Vs<br />

ቅዱስ ዮሐንስ<br />

‹‹እንቁጣጣሽ››<br />

አንዳንዶች ስለ እንቁጣጣሽ በቃል<br />

የተነገረ አንጂ በፅሁፍ የሰፈረ ነገር<br />

አንደሌለ ሲናገሩ፣ ሌሎች ደግሞ<br />

የተጻፈ ታሪካዊ ዳራ እንዳለው<br />

ይከራከራሉ። ሆኖም ከዘመን<br />

ዘመን ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ<br />

ከግዕዝ የተወሰደ ቃል አንደሆነ<br />

መዛግብት ያስረዳሉ። ‹‹እንቁ›<br />

የግዕዝ ቃል ሆኖ ለነጠላ ቁጥር<br />

የሚያገለግል ሲሆን፣ ‹‹አዕናቁ››<br />

የሚለው ለብዙ ቁጥር ያለግላል።<br />

‹‹ጣጣሽ›› የሚለው ‹‹ፃዕፃዕ››<br />

ከሚለው የግዕዝ ቃል የተወረሰ<br />

እንደሆነና የአማርኛ ትርጓሜውም<br />

ጣጣ፣ መባዕ፣ ግብር፣ መፍቀድ፣<br />

ገፀ-በረከት (በረከተ-ገፅ) ማለት<br />

አንደሆነ ከላይ በገለፅነው ዓ.ም<br />

ለንባብ የበቃው ሀመር የተባለው<br />

መንፈሳዊ መፅሄት መረጃዎችን<br />

ጠቅሶ አስፍሯል። በአጠቃላይ<br />

እንቁጣጣሽ ማለት የእንቁጣጣሽ<br />

ግብር፣ የእንቁጣጣሽ ገፀ-በረከት<br />

ማለት እንደሆነ የታሪክ ድርሳናት<br />

ያስረዳሉ። በመፅሀፍ ብሉያትም<br />

ቢሆን ለመባዕ የሚገባውን ግብር<br />

‹‹ፃዕፃዕ›› ይሉት እንደነበር ነው<br />

መረጃዎች የሚጠቁሙት።<br />

መነን መፅሄት በ1965 ዓ.ም<br />

‹‹እንቁጣጣሽ ምንድን ነው›› በሚል<br />

ርዕስ እንዳስነበበው፣ በሀገራችን<br />

ለመጀመሪያ ጊዜ እንቁጣጣሽ (ገፀ-<br />

በረከት) የተበረከተው ለቀዳማዊ<br />

ምኒልክ እናት ለንግስት ማክዳ<br />

እንደነበርና ንግስቲቱ ምኒልክን<br />

በወለደች ጊዜ ህዝቡ ንጉስ<br />

ተወለደ ብሎ እልል በማለት<br />

የአበባ እንቁጣጣሽ ለንግስት ማክዳ<br />

አበረከተ።<br />

ታዲያ እንቁጣጣሽ የተባለው<br />

በመጀመሪያ ለንግስቲቱ ስለተበረከተ<br />

እንጂ ለንጉሱ ተበርክቶ ቢሆን<br />

ኖሮ ‹‹ዕንቁ ፃፃሁ›› ይባል ነበር።<br />

ከዚህም በተጨማሪ ንጉስ ሰለሞን<br />

ከደስታው ብዛት ለንግስቲቱ<br />

ለጣትሽ መታሰቢያ ይሁንሽ ሲል<br />

የዕንቁ ቀለበት ሰጥቷት እንደነበር<br />

ሊቃውንት ያስረዳሉ።<br />

በ1951 ዓ.ም ብርሀንና ሰላም<br />

ጋዜጣ ላይ በዓሉን አስመልክቶ<br />

‹‹ርዕሰ አውደ ዓመት›› በሚል ርዕስ<br />

የሰፈረው ጽሁፍ ንግስት አዜብ<br />

ለንጉስ ሰለሞን ‹‹ተንካራ›› የተሰኘ<br />

እንቁ ወስዳ ገፀ-በረከት በሰጠችው<br />

ጊዜ ‹‹እንቁጣጣሽ ይሁን›› ብሏት<br />

እንደነበር ያስረዳል።<br />

ጋዜጣው ጨምሮ እንደገለፀው፣<br />

በኢትዮጵያ ስለ ሕግ የተሰበከው<br />

በንግስት አዜብ በምኒልክ እናት<br />

በመሆኑ ሲታሰብ እንደሚኖር፣<br />

በዚህም ቀን የቅድስ ዮሀንስ<br />

መጥምቅ በዓል እንደሚከበር ነው፡፡<br />

ታዲያ የኢትዮጵያ ሴቶች ለምለም<br />

ሳርና አበባ በእጃቸው ይዘው<br />

በዓሉን የሚያከብሩት ለምለም<br />

ሳርና አበባው በኖህ ጊዜ ‹‹ማየ<br />

አይህ›› (የጥፋት ውሀ) መጉደሉን<br />

ለማብሰር እርግብ በአፏ ቅጠል<br />

ይዛ ታይታ ስለነበር ነው። ምንም<br />

እንኳን ‹‹ማየ አይህ›› የጥፋት<br />

ቢሆንም፣ ክረምት አለፈ የሚለውን<br />

ሀሳብ እንደሚወክል ብርሀንና<br />

ሰላም ጋዜጣ ከላይ በገለፅነው ዓ.ም<br />

እትሙ አስፍሮታል።<br />

በሌላ በኩል ስለ ዘመን መለወጫ<br />

(እንቁጣጣሽ በዓል) አለቃ አያሌው<br />

ታምሩ በ1953 ዓ.ም ባሳተሙት<br />

‹‹የኢትዮጵያ እምነት በሶስቱ<br />

ህግጋት›› በተሰኘው መፅሀፋቸው<br />

የዘመን መለወጫ በሶስት መንገድ<br />

መታወቁን አስፍረዋል። አንደኛ፣<br />

እስራኤላውያን በብሉይ ኪዳን<br />

ያከብሩት የነበረው ሚያዚያ 1<br />

ቀን፤ ሁለተኛ፣ የአለም ክርስቲያን<br />

የክርስቶስን ልደት ተቀዳሚ<br />

በማድረግ የሚያከብሩት ጥር 1<br />

ቀን፤ ሶስተኛ፣ ኢትዮጵያ ከጥንት<br />

መሠረት አውቃ የምታከብረው<br />

መስከረም 1 ቀን ናቸው።<br />

እስራኤላውያን የዘመን መለወጫ<br />

በአልን ሚያዚያ 1 ቀን ማድረጋቸው<br />

በዚሁ ወር ከግብፅ ባርነት ነፃ<br />

በመውጣተቸው፣ እንዲሁም<br />

እግዚአብሔር ይህንን የነፃነት በአል<br />

በየአመቱ እዲያከብሩ ስላዘዛቸውና<br />

የአለም ክርስቲያን ጥር 1 ቀን<br />

ማክበራቸው የክርስቶስን ልደት<br />

ምክንያት በማድረግ መሆኑ ግልፅ<br />

ነው፡፡ የኢትዮጵያ መስከረም 1 ቀን<br />

አውድ አመት (ዘመን መለወጫ)<br />

ስላደረገችበት ጥቂት እንበል።<br />

ኢትዮጵያ ይህንን በዓል<br />

የተቀበለችው ከ‹‹ካም›› ነው፡<br />

፡ የተጀመረበትም ካም እና ልጁ<br />

ኩሣ ወደ ኢትዮጵያ የገቡበትና<br />

አኩስም (አክሱም) በኩሳ ስም<br />

የተመሰረተችበት ጊዜ ነው።<br />

ዘመኑም በኢትዮጵያ ከ4900<br />

ዓመት በላይ ሲሆን፣ ጊዜውም<br />

ከጥፋት ውሀ በኋላ መሆኑን<br />

የአለቃ አያሌው መጽሀፍ ያስረዳል፡<br />

፡<br />

ስለ ዘመን መለወጫ ስያሜዎች<br />

ማለትም ስለ ቅዱስ ዮሀንስና<br />

እንቁጣጣሽ አለቃ አያሌው<br />

ታምሩ በ2001 ዓ.ም ባሳተሙት<br />

‹‹ትምህርተ-ሀይማኖት›› በተሰኘ<br />

መጽሐፋቸው ‹‹እንቁጣጣሽ››<br />

የሚለው ቃል ከግብር፣ ከመባዕ፣<br />

ከገፀ-በረከት ጋር የተቆራኘ ትርጓሜ<br />

በየዘመኑ የመጡ ምሁራን<br />

ያመጡት እንጂ እውነታው ወዲህ<br />

ነው ይላሉ። ይሁን እንጂ ‹‹ቅዱስ<br />

ዮሀንስ›› ስለተባለው የዘመን<br />

መለወጫ ስያሜ እላይ ከሰፈረው<br />

ጋር ብዙ የሚያመሳስለው ነገር<br />

አለ።<br />

‹‹ቅዱስ ዮሀንስ› አለቃ<br />

አያሌው እንደገለፁት<br />

አለቃ አያሌው ታምሩ ዘመኑ<br />

በአራቱ ወንጌላውያን የተሰየመ<br />

ነው ይላሉ። የዘመን መለወጫው<br />

‹‹ቅዱስ ዮሐንስ›› የሚባልበትንም<br />

ምክንያት ሲያስረዱ፣ ወንጌልን<br />

የሚቀበሉ ሁሉ በአራቱ<br />

ወንጌላዊያን (በዩሀንስ፣ በማቲዎስ፣<br />

በማርቆስና በሉቃስ) የዘመን ቁጥር<br />

መስመራቸውን እንደሚያሳርፉ<br />

ገልጸው፣ ኢትዮጵያ ዘመን<br />

መለወጫን ‹‹ቅዱስ ዮሃንስ››<br />

የምትልበት ሁለት ዋና ዋና<br />

ምክንያቶች አንዳሏት ያብራራሉ፡<br />

፡ አንደኛ፣ ቅዱስ ዮሀንስ ወንጌላዊ<br />

ወንጌሉን የጀመረው በዜና<br />

ፍጥረት መሆኑን እንደሚከተለው<br />

ገልጾታል፡-<br />

‹‹ቃል ቀዳማዊ፣ ቃል<br />

በእግዚአብሔር ዘንድ ነበር።<br />

እግዚአብሔር ቃል ነበር፣ እርሱ<br />

በእግዚአብሔር ዘንድ ነበር። ሁሉ<br />

በእርሱ ሆነ›› ብሎ ሙሴ ‹‹ቀዳማዊ<br />

ገብረእግዛብሔር ሰማየ ወምድረ<br />

(እግዚአብሔር መጀመሪያ ሰማይና<br />

ምድርን ፈጠረ ሲል በቀዳማዊ<br />

ቃሉ በኢየሱስ ክርስቶስ አለሙን<br />

መፍጠሩን ያስረዳ በመሆኑና<br />

ቅዱስ ዮሀንስም የወንጌልን<br />

ትምህርት ከሙሴ ስብከት ጋር፣<br />

የወንጌልን ፅህፈት ከሙሴ አፃፃፍ<br />

ጋር እንዲሁም የወንጌልን ጥንት<br />

ከሙሴ አነሳስ ጋር በማስተባበር<br />

(ቃል ቀዳማዊ ነው) ሁሉ በእርሱ<br />

ሆነ) በማለት ስላጠናቀቀው፣<br />

ቤተክርስቲያንም በቅዱስ ዮሀንስ<br />

ወንጌል መሠረት እለቱን ‹‹ቅዱስ<br />

ዮሀንስ›› ብላ ትጠራለች” ካሉ<br />

በኋላ በተጨማሪም በቁጥር<br />

ስርአት አንድ ጊዜ ወደ ፊት<br />

አንድ ጊዜ ወደኋላ ነው ብለን<br />

ካመንን ዘንድ ወደኋላ ተመልሰን<br />

አሁን ባለው በአራቱ ወንጌላውያን<br />

መስፈሪያ ያለውን ዘመን ስንለካ<br />

ስነ-ፍጥረት ጥንተ-ፍጥረት በዘመነ<br />

ዮሀንስ ሆኖ ይገኛል። እናም ከቃሉ<br />

አፃፃፍ ጋር ተስማምቶ ስላገኘችው<br />

ቤተ-ክርስቲያን ቅዱስ ዮሀንስ ብላ<br />

ትጠራለች።<br />

ሁለተኛው ደግሞ ‹‹ወንጌላውያን<br />

ሁሉ የተባበሩት በቅዱስ ዮሀንስ<br />

መጥምቅ ዜና ነው። ወንጌላውያን<br />

ሁሉ ወንጌልን የጀመሩት በቅዱስ<br />

ዮሀንስ ስብከት ነው፡፡ ይህም<br />

ማቴዎስ ምዕራፍ 3፣ ማርቆስ<br />

መዕራፍ1፣ ሉቃስ ምዕራፍ 3፣<br />

ቅዱስ ዮሀንስ በምዕራፍ 1 ሁሉም<br />

ለወንጌል ትምህርት መሠረት<br />

መግቢያ ያደረጉት የቅዱስ ዮሀንስን<br />

መጥምቅ ትምህርት ነው›› ሲሉ<br />

አስፍረዋል።<br />

አለቃ አያሌው በመፅሀፋቸው<br />

‹‹ከዚህም ጋር ቅዱስ ዮሀንስ<br />

በንጉስ ሄሮድስ ትዕዛዝ ጳጉሜ<br />

1 ቀን ታስሮ መስከረም 2 ቀን<br />

በሰማዕትነት ሞቷል›› ሲሉ<br />

አስፍረዋል።<br />

እንቁጣጣሽ በአለቃ አያሌው ገለፃ<br />

አለቃ አያሌው የእንቁጣጣሽን<br />

ትርጉሜ በተመለከተ እዳሰፈሩት<br />

የቃሉ ትርጓሜና ታሪኩ ከምድርና<br />

ከኢትዮጵያ አመሰራረት ጋር<br />

የተያያዘ እንደሆነ ገልፀው<br />

‹‹እግዚአብሄር ፍጥረትን መፍጠር<br />

በጀመረ በሶስተኛው ቀን ‹ምድር<br />

ሳርም ቡቃያም ታውጣ›› ብሎ<br />

ሲናገር ሰማዩን በከዋክብት<br />

ከማስጌጡ አስቀድሞ ምድርን<br />

በአበባ አስጊጧል›› ሲሉ በመፅሀፉ<br />

ያሰፈሩት ሲሆን በዚህም ምክንያት<br />

“ምድር ተንቆጠቆጠች ማለት<br />

እንቁጣጣሽ መሰለች፣ አበበች፣<br />

ለመለመች አጌጠች ለማለት<br />

ነው። እንቁጣጣሽ የሚባለው<br />

በአሁኑ ጊዜ በየአመቱ መጀመሪያ<br />

ላይ ከሌሎች አበቦች አስቀድሞ<br />

የሚታየው በአማርኛ ቋንቋ ‹‹አደይ<br />

አበባ›› የተባለው ቢጫ አበባ ነው።<br />

ይሄ ነው እንቁጣጣሽ ያሰኘው”<br />

ሲሉ በትምህርተ-ሃይማኖት<br />

መጽሃፋቸው ላይ አስፍረውታል።<br />

አለቃ አያሌው እንደፃፉት፣<br />

ስለእንቁጣጣሽ ተራኪዎች የተለያየ<br />

ቋንቋ እንደሰጡት ጠቁመው<br />

በተለይም ‹‹የሠለሞንን ዘር<br />

መመኪያ እናደርጋለን የሚሉ<br />

ተራኪዎች›› ያሏቸው ንጉስ<br />

ሰለሞን ከንግስት ሳባ ጋር በተገናኘ<br />

ጊዜ ስለክብሯ አንቁጣጣሽ ብሎ<br />

የዕንቁ ቀለበት ሰጥቷት ነበር።<br />

ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ነው እንቁጣጣሽ<br />

የተባለው” ብለው ይተርካሉ። ግን<br />

“ትክክለኛ ታሪክ አይደለም›› ሲሉ<br />

ያጣጥሉታል፡፡<br />

የሆነ ሆኖ እንደ ግዕዙ ቃል<br />

እንቁጣጣሽ ‹‹ጣጣ›› ከሚለው ቃል<br />

መጥቶ ግብር፣ ገፀ-በረከት፣ ጣጣ<br />

የሚለውን ትርጉሜ አግኝቶም<br />

ከሆነ በአሉ በርካታ ግብርን<br />

(ወጪን) የሚጠይቅ በመሆኑ<br />

ጥንቃቄ ማድረግ ይጠበቅብናል፡፡<br />

› እንደአለቃ አያሌው ገለፃ ምድር<br />

ለመለመች፣ አጌጠች፣ አበበች<br />

ማለትም ከሆነ ለሀገራችን አሜን<br />

ያድርግለን፡፡ ስለዘመን መለወጫ<br />

ካነሳን አይቀር በዚሁ አጋጣሚ ስለ<br />

ጳጉሜም ትንሽ እንበል።<br />

ይህቺ የሀገራችን 13ኛ ወር<br />

(ጳጉሜ) ትርጓሜዋ ‹‹ጭማሪ››<br />

ማለት ነው፡፡ በመሆኑም ጭማሪ<br />

ወጪም ትሆናለችና ልብ ልንላት<br />

ይገባል፤ ዘንድሮ ደግሞ ስድስት<br />

ቀን ሆና ትውላለችና።<br />

መልካም ቅዱስ ዮሀንስ! መልካም<br />

የእንቁጣጣሽ በዓል!<br />

21<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ


22<br />

በኤልያስ ገብሩ<br />

በአዲስ<br />

elias.gebru32@gmail.com<br />

ዓመት አዲስ መንፈስ<br />

ኢትዮጵያኖች የፊታችን<br />

ሰኞ አዲስ ዓመትን<br />

የ ም ን ጀ ም ር በ ት<br />

ዕለት ነው። አዲስ<br />

ዓመት ብዙዎቻችን<br />

አዲስ እንዲሆንልን<br />

እ ና ስ ባ ለ ን ፣<br />

እንመኛለን። በአዲስ ዓመት ለውጥ<br />

ለማየትና ስኬትን ለመቀዳጀት ዕቅድ<br />

ነድፈውና ለራሳቸው ቃል ገብተው በአዲስ<br />

የመንፈስ ሀይል ለመንቀሳቀስ የሚሹና<br />

እንዳሰቡትም የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦችና<br />

አካሎች መኖራቸው እሙን ነው። በአንፃሩ<br />

ደግሞ፣ አዲስ ዓመት ስለመጣ ብቻ አዲስ<br />

ነገር ማድረግ እንዳለባቸው በማሰብ<br />

ስሜታዊ ሃሳብ ላይ በመመርኮዝ እርጋታ<br />

የጎደለው ስሜታዊ ዕቅድን ይነድፋሉ።<br />

እነዚህም በአዲሱ ዓመት ብዙም<br />

ሳይጓዙ ከእቅዳቸው ውጪ እንደሚሆኑ<br />

አያጠራጥርም። ለማንኛውም…… አዲስ<br />

ዓመት እንዴት ነው የምናከብረው?<br />

እንዲሁ በቀላሉ እቤት ውስጥ በመቀመጥ<br />

እና ዓመቱን አቅልሎ በመመልከት? ብዙ<br />

ሕዝብ በዓሉን ለማክበር በተሰበሰበበት<br />

ቦታ በመገኘት ወይስ ወዳልለመድነው ቦታ<br />

በመጓዝ? የበዓሉስ አከባበር የጠበቅነውን<br />

ያህል ይሆንልን ይሆን?<br />

ጠቃሚ ነገሮች ላይ<br />

የፀባይ ውሳኔዎች ላይ ነው። በሕይወት<br />

ውስጥ የሚገኙ የፀባይ ውሳኔዎች የሰዎችን<br />

ስኬት ይወስኑታል። የሚፈልጉትን<br />

ወይም ማድረግ የሚሹትን ለማሟላት<br />

ሰዎች ለራሳቸው ሕይወት ተጠያቂዎች<br />

መሆናቸው ይገለፃል።<br />

የተለየ ነገር ምን<br />

እናድርግ?<br />

የቢዝነስ ባለቤቶች፣ የድርጅት ማናጀሮች<br />

ወይም አስፈፃሚዎች የራሳቸውን የሥራ<br />

ዕቅድ የማስፈፀም ኃላፊነት እንዳለባቸው<br />

ሁሉ ሠራተኞቻቸውም የሚጠበቅባቸውን<br />

ነገሮች ማሳካት እንዲችሉ የመደገፍ<br />

ኃላፊነት ሊኖራቸው ይገባል፡፡<br />

በአሜሪካ ሀገር በአዲስ ዓመት መግቢያ<br />

ሰሞን በአንድ ትምህርት ቤት መግቢያ<br />

በር ላይ እንዲህ የሚል መርህ ቃል<br />

ተፅፎ በትልቁ ተለጥፏል፡- ‹‹High<br />

Expectation = High Achievement››<br />

(ከፍተኛ ግምት = ከፍተኛ ውጤት)፡፡<br />

በዚህም በአካባቢው ለሚገኙ መምህራን<br />

እንዲደርስ ታስቦ መዘጋጀቱን የሚገልፀው<br />

መረጃው፣ መምህራኖች ከተማሪዎቻቸው<br />

ከፍተኛ ውጤት የሚጠብቁ ከሆነ እነሱም<br />

ከራሳቸው የሚጠብቁት ነገር ከፍ ያለ<br />

ይሆናል። መምህራኖች ከራሳቸው የላቀ<br />

ነገር እንደሚጠበቅ ሲያስቡ ደግሞ<br />

ተማሪዎቻቸውን በዕውቀትና በሥነ-ምግባር<br />

ሊያሳድግ የሚችል ጥራት ያለው ትምህርት<br />

ለመስጠት ያስችላቸዋል፡፡ ይኼንንም<br />

ተከትሎ ተማሪዎች የሚጠበቅባቸው<br />

ደረጃ ላይ ይገኛሉ። ‹‹የቢዝነስ ባለቤቶች፣<br />

የድርጅት ማናጀሮች ወይም አስፈፃሚዎች<br />

ራሳቸውን እንደአስተማሪ፣ ሰራተኞቻቸውን<br />

ደግሞ እንደተማሪ ሊያስቧቸው ይገባል።››<br />

በማለት በአሜሪካን ሀገር የወጣ አንድ<br />

መረጃ ዘግቧል፡፡<br />

አዲስ ዓመት በመጣ ቁጥር አዲስ<br />

የባህሪ ውሳኔ ለማድረግ ከፍተኛ እድልን<br />

ይፈጥራል። ሽግግሩ ሥነ-አዕምሯዊ<br />

ለውጥን ለማድረግ በጣም ቀላል<br />

የሚያደርግ ሲሆን፣ ሰብኮንሺየስ የሆነው<br />

የሠው የአንጎል ክፍል አዲሱን ውሳኔ<br />

በቀላሉ ይቀበላል። ምን አይነት አዲስ<br />

የፀባይ ለውጥ ውሳኔ ማድረግ አለብን?<br />

በዋነኝነት እርስ በእርስ በመተባበር ትስስር<br />

እና ቁርኝትን መፍጠር ነው። ለምሳሌ፣<br />

በቢዝነስ ሥራ ውስጥ የሚጠበቀውን<br />

ውስጣዊና ውጫዊ ስኬቶችን ለመጎናፀፍ<br />

አዲስ የፀባይ ለውጥ ውሳኔ ለማድረግ<br />

ሚናው የጎላ ነው። እንዲሁም አንድ<br />

ሰው በውስጡና ከእሱ ውጪ እንዲሆኑ<br />

የሚጠብቃቸው ነገሮች እንዲለወጡ ድጋፍ<br />

ይሰጣል። በቢዝነስ ዓለምም አንድ ድርጅት<br />

በአዲስ ዓመት ከእሱ ውጭ ካሉ ሸሪኮች<br />

ጋር ለውጤት የሚያበቃ ስትራቴጂን<br />

በመንደፍ ሕብረት መፍጠር አለበት፡<br />

፡ ቅድሚያ ግን፣ ለካምፓኒው/ ለድርጅቱ<br />

ስኬት አጋር መሆን የሚችሉ ሸሪኮችን<br />

መምረጥ ተገቢ ነው።<br />

የድርጅቱን ምርጥ<br />

ታሪክ መምረጥ<br />

በካምፓኒው ወይንም በድርጅቱ ውስጥ<br />

ስላለው መልካም ነገር ሰራተኞች አዎንታዊ<br />

አመለካከትን ይዘው የባለቤትነት ስሜት<br />

እንዲሰማቸው አዲስ ስትራቴጂን መንደፍ<br />

ወሳኝነት እንዳለው መረጃዎች ያስረዳሉ።<br />

የድርጅት ባለቤቶች ወይንም የተቋም<br />

ኃላፊዎች ደግሞ ለሥራቸው እድገት<br />

ዕውቀትና ጥበብን ያማከለ ኃላፊነትንና<br />

የተጠና ሪስክን ሊወስዱ ይገባቸዋል።<br />

ሰራተኞች ከድርጅቱ ራዕይ ጋር ራሳቸውን<br />

ማስማማት እንዲችሉ የድርጅቱን ያለፈ<br />

ታሪክ እንዲያውቁ ማድረግ ብልህነት<br />

ነው፡፡ በድርጅቱ ታሪክ ውስጥም ጥሩ<br />

የሚባለውን መርጦ በመለየት በሰራተኞቹ<br />

እንዲደገም ደጋግሞ መናገር የባለቤቶች<br />

ወይም የኃላፊዎች ድርሻ ሲሆን<br />

ሰራተኞችም በዚህ ተገቢውን የፀባይ ለውጥ<br />

ውሳኔ እንዲያመጡ ማድረግ ያስፈልጋል።<br />

ትኩረት ማድረግ<br />

በአዲስ ዓመት ከግዢ ጋር ለተገናኙ<br />

የተለያዩ ነገሮች ይበልጥ ትኩረት ሰጥቶ<br />

ከማክበር ይልቅ በአዲስ ዓመት ለራስና<br />

ከራስ ውጪ ትልቅ ለውጥ ሊያመጡ<br />

በሚችሉ ቅድመ-ዕቅዶች ላይ የላቀ ትኩረት<br />

የኢትዮጵያዊያን ሰቆቃ...<br />

መስጠቱ በጣም ጠቀሜታ እንዳለው<br />

መረጃዎች ያስረዳሉ። ለምሳሌ በብዙ<br />

የአዲስ ዓመት ወቅቶች ላይ፣ ሁሌም<br />

ለማለት በሚያስችል መልኩ በርካታ<br />

ሕፃናት ልጆች፣ ታዳጊዎችና ወጣቶች<br />

ከቤተሰቦቻቸው አዳዲስ አልባሳትና<br />

ጫማዎች ተገዝተው እንዲበረከትላቸው<br />

ይፈልጋሉ፣ ይጠብቃሉም። ብዙዎች<br />

እንዳሰቡት ሆኖ ሊያገኙት ይችላሉ። ነገር<br />

ግን፣ በአጋጣሚም ይሁን በሌላ [ቤተሰብ<br />

በብር እጥረት ምክንያት መግዛት ካልቻለ]<br />

በየዓመቱ ለልጆች ያስለመዳቸውን ነገር<br />

በሚያስቀርበት ጊዜ አዳዲስ አልባሳትና<br />

ጫማዎችን ይጠብቁ የነበሩ ሕፃናት፣<br />

ታዳጊና ወጣት ልጆች ራሳቸውን<br />

ከጓደኞቻቸው/ ከጎረቤት ልጆች ጋር<br />

በማነፃፀር መከፋታቸውና መበሳጨታቸው<br />

አይቀሩ ነው፡- የቤተሰብን ችግር በበቂ<br />

ምክንያት ካለተረዱት በስተቀር።<br />

አለበለዚያ ያ የአዲስ ዓመት ትውስታ<br />

ሁሌም በአዕምሯቸው ውስጥ ተቀምጦ<br />

ይረብሻቸዋል። በአሉታዊ መንገድ<br />

የተቀረፀው ትዝታ ልጆቹን ማንቀሳቀስ<br />

ካልቻለ ደግሞ ትዝታው አሁንም ድረስ<br />

በውስጣቸው መኖሩን ጠቋሚ ምልክት ነው።<br />

ይኼ ከላይ ልጆችን መሠረት በማድረግ<br />

የተጠቀሰው ምሳሌ በአዋቂ ሰዎች፣<br />

በድርጅቶች፣ በአካባቢዎችና በዝግጅቶች<br />

ላይ የሚሰራ መሆኑ ይገለፃል። በአዲስ<br />

ዓመት የሆነ ነገር እንደሚደረግላቸው<br />

የሚጠብቁ ሰዎችም ሆኑ ድርጅቶች<br />

የሚጠብቁት ነገር ካልተደረገላቸው በቀላሉ<br />

ስሜታቸው ሊነካ፣ የመስራት አቅማቸው<br />

ሊቀንስ፣ ብሎም ለውድቀት ሊዳረጉ<br />

እንደሚችሉ በጉዳዩ ላይ ጥናት ያደረጉ<br />

ምሁራን ያስረዳሉ። የሚጠበቀው ነገር<br />

አንዳንዴ እውነት ላይሆን እንደሚችልም<br />

ጠቁመዋል። በአጠቃላይ ሕፃናት፣<br />

አዋቂዎች፣ ድርጅቶች…አዲስ ዓመት<br />

በመጣ ቁጥር የሆነ ጥቅም ነክ-ነገር ከሰዎች<br />

ወይም ከሌላ አካል እንዲደረግላቸው<br />

አብዝቶ ከመፈለግ ይልቅ በሕይወታቸው<br />

ላይ በመሰረታዊ ሁኔታ ትልቅ ሊያመጡ<br />

በሚችሉ እውነተኛ ዕቅዶች ላይ ትኩረት<br />

ማድረግ እንደሚገባቸው አፅንዎት<br />

ሰጥተውታል፡- የዘርፉ ተመራማሪዎች።<br />

ያልተሟላ የፍላጎት ስሜታችንን<br />

ወደ ውስጣችን እንዲገባ ከፈቀድንለት<br />

ሕይወታችንን ውስብስብ የማድረግ አቅም<br />

አለው። ፍላጎታችን ካልሟላ ሕይወት<br />

ይበልጥ አስቸጋሪ ትሆናለች። ከእኛነታችን<br />

ውጪ የምንጠብቀው ነገር በተለያየ<br />

መልኩ ይመጣል። በገንዘብና በቢዝነስ፣<br />

በሥራ፣ በትምህርት፣ በፍቅርና በትዳር<br />

ሕይወት፣ በመንፈሳዊ ሕይወት …<br />

እነዚህን ነገሮች ለማግኘት የቁጥጥር ስራ<br />

ወሳኝ ነው። ይኼንን መስራት ካልተቻለ<br />

ደግሞ ብዙ ኃይልን ውጤት በማያመጣ<br />

ነገር ላይ ማዋሉ ተገቢ አለመሆኑን<br />

በዘርፉ የምርምር ጥናት ያደረጉ ምሁራን<br />

ይናገራሉ። ቁጥጥሩ የሚደረገው በሰዎች<br />

የሥራ ጫና መቋቋም አቅቷቸው የሸሹ ኢትዮጵያውያን በድብቅ እንዳነጋገሩት<br />

የሚያስታውሰው ነቢዩ፤ በሊባኖስ፣ በባሕሬን፣ በዱባይና አቡዳቢ ዜጎች በተመሳሳይ<br />

ሁኔታ ለችግር ቢዳረጉም በ<strong>መንግስት</strong> ተወካዮች ምንም ዓይነት የመብት ጥበቃ<br />

እንዳልተደረገላቸው አረጋግጧል።<br />

በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ሰቆቃ የተለያዩ መገናኛ ዘዴዎችን<br />

በመጠቀም ይፋ በማድረጉ ‹‹<strong>መንግስት</strong> ሊሰራ ይገባ የነበረውን ሥራ እየከወነ ነው››<br />

ተብሎ የሚሞካሸው ይህ ጋዜጠኛ በአካባቢው ያሉ ዲፕሎማቶች የኢትዮጵያውያንን<br />

ጩኸት ሰምቶ ምላሽ ለመስጠት ለምን እንደከበዳቸው ጥያቄ ማቅረቡ አልቀረም።<br />

ቀደም ሲል የጅዳ ቆንፅላ ጽ/ቤት ኃላፊ የነበሩት አምባሳደር ተክለአብ ከበደና<br />

ሌሎች ሠራተኞች ሲሰጡት የቆየው መልስ ‹‹የበጀትና የሰው ኃየል ዕጥረት አለብን››<br />

የሚል ነበር፡፡ ሆኖም ፕሬዝደንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ ጅዳ በሄዱ ጊዜ ተመሳሳዩን<br />

ጥያቄ አቅርቦላቸው ‹‹የበጀትና የሰው ኃይል እጥረት ስለመኖሩ ጥያቄ አልቀረበልንም፡<br />

፡ ሲቀርብልን ምላሽ እንሰጥበታለን›› ማለታቸው ችግሩ የቅንጅትና የበሰለ አመራር<br />

እጥረት እንደሆነ መመስከሩን ያስታውሳል።<br />

‹‹አለ›› የተባለውን የገንዘብና የሰው ኃይል ዕጥረት ለመቅረፍ ከልብ ስላልታሰበበት<br />

እንጂ የጅዳው ቆንፅላ ጽ/ቤት በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን ፓስፖርት በማደስና<br />

የውክልና ወረቀት በመስጠት በሚያስገባው ከፍተኛ ገቢ ችግሩን ማቃለል<br />

እንደሚቻልም መረጃዎች ይጠቁማሉ። በውጭ አገራት በተለይም በአረብ አገራት<br />

የሚገኙ ዲፕሎማሲያዊ ሚሲዮኖች በስፍራው የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ችግር<br />

ከመፍታት ይልቅ የኢህአዴግ ደጋፊ ዲያስፖራዎችን በማሰባሰቡ ላይ እንደሚያተኩሩ<br />

የሚያስገነዝቡ ወቀሳዎች ሲቀርቡ ይስተዋላል።<br />

ካለፈው አራት ዓመት ወዲህ በጅዳና አካባቢው ያሉ ኢትዮጵያውያንን እንዲያገለግሉ<br />

ተመድበው በነበሩት አቶ ሙክታር መሐመድ ላይም ተመሳሳይ ትችት ተሰንዝሯል።<br />

ምንም እንኳን የዲፕሎማቱ ዋና ተልዕኮ ለኢትዮጵያውያን አንገብጋቢ ጥያቄዎች<br />

ምላሽ መስጠት ቢሆንም እሳቸው ግን ብሔር ተኮር ‹‹የልማት ማህበሮችን››<br />

በማደራጀት ላይ ተጠምደው የሥራ ጊዜያቸውን እንዳገባደዱ ምንጮች ለአውራምባ<br />

ታይምስ ገልፀዋል።<br />

በየዕለቱ በርካታ ኢትዮጵያውያን በሚጎርፉባት የመን ያሉ ኢትዮጰያውያንም እዚያ<br />

ያለው ኤምባሲ ጩኸታቸውን ለመስማት ፈቃደኛ አለመሆኑን ሲገልጹ ቆይተዋል።<br />

በተለይም የዘመናት ብሶት የወለደው የዓረብ አብዮት በየመንም መቀጣጠሉን ተከትሎ<br />

ኢትዮጵያውያን ከፍተኛ ስጋት ውስጥ እንደነበሩ በአንድ ወቅት ግሩም ተ/ኃይማኖት<br />

የተባሉ ስደተኛ አውራምባ ታይምስ ላይ ባሰፈሩት ፅሁፍ መግለፃቸው አይዘነጋም።<br />

ምንም እንኳን የኢትዮጵያ <strong>መንግስት</strong> /የመን የሚገኘው ኤምባሲ/ ከ IOM ጋር<br />

በመተባበር በየመን ሊቀሰቀስ በሚችለው ጦርነት ዜጎች እንዳይጎዱ ኢትዮጵያውያንን<br />

ወደ ኢትዮጵያ ሲመልስ የነበረ ቢሆንም፣ ‹‹የመን ባለው ኤምባሲ አንተማመንም››<br />

ያሉት ኢትዮጵያውያን በርካታ ናቸው።<br />

ግፍ ተፈፅሞባቸው ወደ ኤምባሲው በመሄድ ጥያቄ የሚያቀርቡ ወገኖችን<br />

‹‹እኛ ለገረድ አልመጣንም›› በሚል ዲፕሎማቶቹ ሲገፏቸው እንደነበር አቶ<br />

ግሩም በፅሁፋቸው ከማስታወሳቸው ባሻገር፣ በ<strong>መንግስት</strong>ና በIOM አማካኝነት ወደ<br />

ሐገራቸው የተመለሱትም ለአውራምባ ታይምስ ይህንኑ ተናግረዋል። በወቅቱ<br />

ተመላሾቹ በሰው ሀገር ከደረሰባቸው ግፍና መከራ የተነሳ እንባ እየተናነቃቸው<br />

‹‹ኤምባሲው ከሰውም አይቆጥረንም። እንደምንም ገንዘብ አግኝተን ስልክ ስንደውል<br />

‹ጠግበህ ነው የመጣኸው፤ ይበልህ የራስህ ጉዳይ ነው› ይሉናል›› ሲሉ ነበር በአረብ<br />

አገራት የሚገኙ ኤምባሲዎች ከኢትዮጵያውያን ጋር ሆድና ጀርባ መሆናቸውን<br />

ያመለከቱት።<br />

ከአውራምባ ታይምስ ጋር ቆይታ ያደረጉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ<br />

አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፣ ‹‹መቼም ኤምባሲዎች ውስጥ የሚሠሩት ሰዎች ናቸውና<br />

ከኤምባሲዎች ፖሊሲ በተጻራሪ ስህተት መሥራታቸው አይቀርም›› በማለት<br />

አቤቱታውን በከፊል ቢጋሩትም <strong>መንግስት</strong> በውጭ አገራት ለሚገኙ ዜጎች ከለላ<br />

በማድረግ ላይ መሆኑን በመግለጽ በፅኑ ሞግተዋል፡፡<br />

‹‹ልጆቻችን እና እህቶቻችን ላይ የሚደርስ ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት አገራችንንም ሆነ<br />

የሚመሩትን ሰዎች የሚያስከብር ካለመሆኑም በላይ የዲፕሎማቲክ እንቅስቃሴ<br />

ውድቀት ማሳያ ነው›› የሚሉት ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ‹‹ኤምባሲው ከመኖር<br />

መዝለል አለበት›› ሲሉ ይወቅሳሉ።<br />

ዲና ሙፍቲ በአቅም ውስንነት የተነሳ ኤምባሲ ባልተከፈተባቸው አገራት ያሉ<br />

ዜጎች መብት ማስጠበቅ አዳጋች ነው ቢሉም በየነ በዚህ አይስማሙም። ‹‹ሁሉ አገር<br />

ኤምባሲና ቆንስላ አይኖርም። በሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና በሌሎች አገሮች<br />

በኩል የቅርብ የጎንዮሽ ክትትል ያደርጋሉ›› ሲሉ የኤምባሲ እና ቆንስላ አለመኖር<br />

ሁሌ እንደ ችግር መታየት እንደሌለበት ጠቁመዋል።<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

ጤ ና<br />

አዲስ ዓመት በመጣ ቁጥር አዲስ የባህሪ ውሳኔ ለማድረግ ከፍተኛ እድልን ይፈጥራል። ሽግግሩ ሥነ-አዕምሯዊ ለውጥን<br />

ለማድረግ በጣም ቀላል የሚያደርግ ሲሆን፣ ሰብኮንሺየስ የሆነው የሠው የአንጎል ክፍል አዲሱን ውሳኔ በቀላሉ ይቀበላል<br />

አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />

መልካም ዓዲስ ዓመት<br />

አንድን ድርጅት ስኬታማ ወደሆነ የሥራ<br />

ባህል መውሰድ ጊዜ ስለሚጠይቅ በተቻለ<br />

መጠን ትግስተኛ መሆን ይመከራል፡፡<br />

ለዚህ ምን ማድረግ ያስፈልጋል?<br />

ከአሮጌው ዓመት ራስን መነጠል<br />

አንድ ድርጅት በአዲስ ዓመት ስኬታማ<br />

ለመሆን የተሻሉ ሰራተኞችን መምረጥ<br />

መቻል ወሳኝና ቁልፍ ተግባሩ ማድረግ<br />

አለበት፡፡ አንድ የሥራ ኃላፊ ከራሱ<br />

ጋር በውስጡ የሚነጋገረው ነገር በፀባይ<br />

ለውጥ ውሳኔዎች ላይ ጫና የመፍጠር<br />

አቅም አለው። ከእሱ በሚጠበቀው ነገር<br />

ላይ ውጤታማ ለመሆን ኃላፊው ግለሰባዊ<br />

ባህሪውን በመጀመሪያ መቆጣጠር አለበት።<br />

በአካላዊ ሰውነቱ ላይ የኬሚካል ወይንም<br />

የሆርሞኖች አለመመጣጠት ካልኖረ<br />

በስተቀር ፀባዩን መቆጣጠር ይችላል።<br />

ግለሰቡ የሥነ-አዕምሮ ችግር ካለ ደግሞ<br />

የሕክምና ባለሙያ ጋር በመሄድ ሕክምና<br />

መውሰድ እና ስላለበት ችግር በዙሪያው<br />

ላሉት ሰዎችና የሥራ ባልደረቦቹ ማሳወቁ<br />

መልካም መሆኑን መረጃዎች ያስረዳሉ።<br />

በዚህ ወቅት ሰራተኞች ለኃላፊው በጣም<br />

ቅን ሊያስቡለት፣ በቀላሉ ሊረዱትና እና<br />

ትዕግስተኛ ሊሆኑለት የሚችሉበት ዕድል<br />

ከፍተኛ ነው፡፡ … የሆነ ሆኖ፣ በተቻለ<br />

መጠን ስላለፈው አሮጌ ዓመት ከማሰብ<br />

መታቀብ ብልህነት መሆኑ ይገለፃል።<br />

ስለዚህ ሰዎች ለስኬታማ ሥራቸውና<br />

ሕይወታቸው ያላቸውን ሙሉ ኃይል<br />

እና አቅም በአዲሱ ዓመት ላይ ማድረግ<br />

እንደሚገባቸው በዘርፉ ጥናት ያደረጉ<br />

ባለሙያዎች ይመክራሉ፡፡ ይኼም ማለት<br />

ብዙ ጊዜን ለእውነተኛ ዕቅድ በመስጠት<br />

ስኬት ላይ ማነጣጠር ሲሆን ባለፈ ጊዜ<br />

ውድቀት እና ስኬት አልባነት ላይ እያሰቡ<br />

ጊዜ ማባከኑ ዋጋ የለውም።<br />

መልካም አዲስና የጤና ዓመት<br />

ይሁንላችሁ!<br />

ተስፋ እና ስጋት<br />

ከወራት በፊት ም/ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ኃ/ማርያም<br />

ደሳለኝ ሳዑዲ አረቢያን ከጎበኙ በኋላ፣ ሳዑዲ አረቢያ ወደ 30 ሺህ የሚጠጉ ኢትዮጵያዊ<br />

የኮንትራት ሠራተኞችን እንደምትፈልግ ይፋ ማድረጋቸውን ተከትሎ ከ15 ሺህ በላይ<br />

የሚገመቱ ዜጎች ወደ ሳዑዲ መግባታቸውን መረጃዎች ይጠቁማሉ።<br />

30 ሺህ ሠራተኞች በሳዑዲ አረቢያ መፈለጋቸው አገር ውስጥ በሥራ አጥነትና<br />

በድህነት ለሚማቅቀው ወጣት አስደሳች ዜና ቢሆንም ስጋቶችም አብረው መከሰታቸው<br />

አልቀረም። ለዚህ ሐተታዊ ፅሁፍ ሰፊና በማስረጃ የተደገፉ ማብራሪያዎችን በመስጠት<br />

ተባባሪ የሆነው ጋዜጠኛ ነቢዩ ሲራክ፣ ስጋቱ የሚመነጨው በሁለቱ ሀገራት መካከል<br />

ስለተደረገው ስምምነት የተፈረመ ሰነድ ይፋ ካለመደረጉ መሆኑን ያስገነዝባል።<br />

በኮንትራት ስለሚሄዱ ሠራተኞች ደመወዝ፣ የሥራ ሠዓት ህክምናና ተዛማጅ<br />

መብቶችን በሚመለከት የሚነሱ ጥያቄዎችን መመለስ የሚችል ሰነድ ይፋ አለመሆኑ<br />

ኢትዮጵያውያንን ለብዝበዛ ሊዳርግ እንደሚችል በመግለፅ ትዝብቱን አካፍሏል።<br />

በአዲሱ የሥራ ዕድል ‹‹ተጠቃሚ›› ሆነው ሳዑዲ አረቢያ ከገቡ ኢትዮጵያውያን<br />

መካከል አንዳንዶች ተቀባይ አጥተው ሲንገላቱ መመልከቱን ለአውራምባ ታይምስ<br />

የገለፀው የመካከኛው ምስራቅ የጀርመን ሬዲዮ ዘጋቢ፣ አሠሪዎቻቸውን አግኝተው<br />

ወደ ሥራ የተሰማሩትም በምግብ እጦትና በሥራ ብዛት ለከፋ ችግር መዳረጋቸውን<br />

አልሸሸገም።<br />

ይህንንም ችግር ለመቅረፍ ያሉት አማራጮች ለሠራተኛና አሠሪ አገናኝ ኤጀንሲዎች<br />

ፍቃድ በሚሰጠው የሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴርና በየሀገሩ በሚገኙት<br />

ዲፕሎማቲክ መሥሪያ ቤቶች መካከል ያለውን የመረጃ ክፍተት ማጥበብና ዜጎችን<br />

ወደ ባዕድ አገር ከላኩ በኋላ ችግር ሲደርስ ዝም የሚሉ ሥራ አገናኝ ኤጀንሲዎች ላይ<br />

ጥብቅ ቁጥጥር የማያደርግ መሆኑን የሚያስገነዝቡ አሉ። ‹‹ውል ገብተው እስከላኩ<br />

ድረስ ሠራተኞችን በሚመለከት ማናቸውም ጉዳይ ከኃላፊነትና ከተጠያቂነት ማምለጥ<br />

እንደማይችሉ <strong>መንግስት</strong> እርምጃ በመውሰድ ትምህርት ሊሰጥ ይገባል›› በማለት<br />

ሀሳቡን ያጠናክራል፤ ነብዩ።<br />

ሸዋዬ - የማንቂያ ደወል?<br />

‹‹ዘመናዊ ባርነትን ለማስፋፋት የሚሯሯጡትን ጥጋጥግ ላይ ያሉትን ሕገ-ወጥ<br />

ደላሎች ተከታትሎ መቆጣጠር <strong>መንግስት</strong> አቅቶት ነውን?›› ሲሉ የሚጠይቁት<br />

ፕሮፌሰር በየነ መረጃው ጠፍቶት ሳይሆን ኃላፊነት ያለመስማት ችግር ነው ካሉ<br />

በኋላ ይህን ችግር መቅረፍ የችግሩን ግማሽ ያህል መቅረፍ መሆኑን ይስማማሉ።<br />

‹‹ሸዋዬ ሞላ ለደረሰባት ጉዳቶች፣ ሕመምና ስቃይ ካሳ ይገባታል›› የሚል አመለካከት<br />

አለኝ›› የሚሉት ዶ/ር ሼክስፒር ፈይሳ ‹‹የደረሱባት ከባድ ጉዳቶች በቀጥታ ከጋዳፊ<br />

ቤተሰብ እርምጃዎች የመነጩ ናቸውና ጋዳፊንና ቀንደኛ ጋሻግሬዎቻውን በፍትሐ<br />

ብሔርም ብቻ ሳይሆን በወንጀል ሕግም ተጠያቂ ሊያደርጋቸው ስለሚችል ካሳ<br />

ለማስከፈል የኢትዮጵያ <strong>መንግስት</strong>ን ትጋት ይሻል›› ይላሉ።<br />

በሸዋዬ ሞላ ላይ የተፈፀመው ድርጊት እጅግ አስከፊና በኢትዮጰያዊነት ብሔራዊ ኩራት<br />

ላይ የተቃጣ ቢሆንም፣ የተገለፁትን ችግሮች ለመቅረፍ እንደማንቂያ ደወል ሊወሰድ<br />

እንደሚገባ እየተገለፀ ነው። ወጣቷ የተሻለ ኑሮ ፍለጋን ሲንከራተቱ በየበረኻውና<br />

በየባሕሩ ድምፃቸው ዳግም ላይሰማ ጠፍቶ የቀረ እንዲሁም በአሠሪዎቻቸው ግፍ<br />

ለሚፈፀምባቸው ሌሎች የአገሯ ልጆች ሁሉ ማሳያ ተደርጋ እየተወሰደች ነው። የወጣቷ<br />

ጉዳይ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሰፊ ሽፋን ተሰጥቶት በመዘገቡ የተነሳ የእርዳታ እጆች<br />

እንዲዘረጉ የተማፅኖ ጥሪዎች እየቀረቡ ሲሆን፣ በተመሳሳይ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ<br />

ኢትዮጵያውያን ዕልፍ አዕላፍ መሆናቸውን በመግለፅ ‹‹እነሱንም እንታደጋቸው››<br />

የሚሉ ድምጾች ሊበረክቱ እንደሚገባ የሚወተውቱ ወገኖች መደመጥ ጀምረዋል።<br />

ሌሎች ደግሞ ይህ ወቅት የኢትዮጵያ <strong>መንግስት</strong> መፈተኛው መሆኑን<br />

በመግለፅ ላይ ናቸው። ‹‹<strong>መንግስት</strong> የድርጊቱን ፈፃሚዎች በዓለም አቀፍ ፍ/<br />

ቤት በመክሰስ ተመጣጣኙን ቅጣት ሊያስወስንባቸው ይገባል›› የሚሉት እነዚህ<br />

ወገኖች፣ ኢትዮጵያውያን በርክተው ከሚገኙባቸው የአረብ አገራት መንግስታት ጋር<br />

የዜጎቹን ሁኔታ አስመልክቶ ከእስካሁኑ ‹‹ኮስተር›› ባለ መልኩ ሊነጋገር እንደሚገባ<br />

አስገንዝበዋል።<br />

‹‹‘የማንቂያ ደወል’ የሚለው አገላለፅ ትክክለኛ ነው›› የሚሉት አምባሳደር ዲና<br />

ሙፍቲ ደግሞ በበኩላቸው፣ ከዚህ በኋላ ወደ አረብ ሐገራት ለመጓዝ የሚያስቡ<br />

አካሄዳቸውን ሕጋዊ በማድረግና በአቅራቢያቸው ወዳለ ኤምባሲ አሊያም ቆንጽላ<br />

ጽ/ቤት ሄደው በመመዝገብ ለራሳቸው ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚኖርባቸው<br />

አስገንዝበዋል፡፡<br />

ዞሮ ዞሮ በአረብ ሐገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን መብት ስለማስከበር ሲነሳ<br />

ዓይኖች ወደ ኤምባሲዎች ማነጣጠራቸው አይቀርምና ወደ አካባቢው የሚላኩት<br />

ዲፕሎማቶች ከፖለቲካ ታማኝነታቸው ባለፈ በሰብዓዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸው በቂ<br />

የሥራ ልምድና ፍላጎት ግምት ውስጥ ሊገባ እንደሚገባ የበርካቶች መስማሚያ ነጥብ<br />

ነው።


አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 184 ቅዳሜ ጳጉሜ 5/ 2003<br />

መልካም ዓዲስ ዓመት<br />

}SdeK¨< Ÿ}c\ ð×” ¾h¨` ¨

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!