25.07.2013 Views

በኢህአዴግ ራዳር ስር የተንበረከከች አገር

በኢህአዴግ ራዳር ስር የተንበረከከች አገር

በኢህአዴግ ራዳር ስር የተንበረከከች አገር

SHOW MORE
SHOW LESS

Create successful ePaper yourself

Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.

መንግሥት በዜጎቹ ላይ<br />

አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />

ለምን ምቀኛ ይሆናል?<br />

በግርማ ሰይፉ<br />

በ ገፅ 14<br />

4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18 2004 ዋጋ 7፡00 ብር<br />

ከህዝብ ጥቅም ይልቅ<br />

የራስን ፖለቲካዊ ምህዳር<br />

ማስጠበቅ<br />

<strong>በኢህአዴግ</strong> <strong>ራዳር</strong> <strong>ስር</strong> <strong>የተንበረከከች</strong> <strong>አገር</strong><br />

በ ገፅ 4<br />

<strong>ስር</strong> <strong>ራዳር</strong> <strong>በኢህአዴግ</strong><br />

ካሳ ሳይሰጥ እንዳልቀረ ተጠቆመ<br />

በሱራፍኤል ግርማ<br />

የቀድሞዋ ሶማሊያ አካል በነበረችው ፑንትላንድ ውስጥ ሞት ተፈርዶበት<br />

ዕለተ-ሞቱን ሲጠብቅ የነበረውን ኢትዮጵያዊ፤ ድምፃዊ ቴዎድሮስ<br />

ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ ሳይታደገው እንዳልቀረ ለአርቲስቱ ቅርበት ያላቸው<br />

የአውራምባ ታይምስ ምንጮች ገለፁ።<br />

በውስጥ ገፅ<br />

የአቶ መለስ የአደባባይ ምስክርነት<br />

ከዳኝነት ነፃነት አንፃር<br />

ከምንጮቻችን ባገኘነው መረጃ መሠረት፣ በሰው መግደል<br />

ወንጀል ተከሶ በሞት እንዲቀጣ በጎሳ መሪዎች ውሳኔ የተላለፈበት<br />

ኢትዮጵያዊው አስመሮም ኃይለሥላሴ ላጠፋው ነፍስ ካሳ 700<br />

ሺህ ብር እስከ ትናንት ዓርብ ድረስ መክፈል ከቻለ በነፃ<br />

እንደሚወጣ የሚያመለክት ዜና በሪፖርተር ጋዜጣ ላይ<br />

በ ገፅ 19<br />

በውስጥ ገፅ<br />

ማፊያ<br />

በ ገፅ 3<br />

“ሽብርተኝነት ለኢትዮጵያ ባዕድ የሆነ ነገር ነው<br />

…በዚህ ሰበብ ሽብርተኝነትን እንዳናስተምር እሰጋለሁ”<br />

አቶ መለስ ሲናገሩ አቃቤ ሕጎች፣ ዳኞችና ፖሊሶች ይኼንን<br />

ተከትለው ይሄዳሉ ብለው እንኳን አያስቡም<br />

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም<br />

‹‹ንቦች አሜሪካ ውስጥ አስቸገሩ››<br />

ሬዲዮ ፋና<br />

‹‹ፋና ሆይ ንቦች ያላስቸገሩበት የት አይታችኋል?››<br />

የታች ሰፈር ልጆች<br />

በዳዊት ከበደ<br />

ቴዲ አፍሮ በሶማሊያ ሞት ለተፈረደበት ኢትዮጵያዊ<br />

ባሕርያቱና ከዴሞክራሲ<br />

እጦት ጋር ያለው ቁርኝት<br />

ሲፒጄ፣ ‘በጋዜጠኞች<br />

ላይ የሽብርተኝነት<br />

ውንጀላው ተጠናክሮ<br />

ቀጥሏል’ ሲል ገለጸ<br />

ባለፈው ሳምንት፣ ጠ/ሚኒስትር<br />

መለስ ዜናዊ በአገሪቱ ውስጥ ያሉትን ጋዜጠኞች<br />

በ“ተላላኪ መልዕክተኝነት” እና “ሽብርተኝነት”<br />

መወንጀላቸውንና አንድ የመንግሥት ጋዜጣ ደግሞ<br />

የነፃው ፕሬስ ኤዲተርን ከሽብርተኞች ጋር ግንኙነት<br />

አለው በማለት የፀጥታ ኃይሎች በጋዜጠኛው ላይ<br />

“እርምጃ እንዲወስዱበት” እንደጠየቀ በማስታወስ፣<br />

በግሉ ፕሬስ ላይ እየተደረገ ያለውን የማሸማቀቅና<br />

የማስፈራራት ዘመቻውን የጋዜጠኞች መብቶች<br />

ተሟጋቹ አውግዟል።<br />

ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ብዙዎቹ<br />

በኢትዮጵያ ያሉ ጋዜጠኞች ከ“ሽብርተኛ”<br />

ቡድኖች ጋር የሚሰሩ “ተላላኪ-መልዕክተኞች”<br />

እንደሆኑና የታሰሩ ጋዜጠኞች ከሽብር ድርጊቶች<br />

ጋር የሚያስተሳስራቸው ቁርኝት እንዳለ የሚያሳይ<br />

ማስረጃ መንግስታቸው ያለው መሆኑን፣ ሌሎች<br />

በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ጋዜጠኞችም ከሽብርተኞች<br />

ጋር ትስ<strong>ስር</strong> እንዳላቸው ባለፈው ሀሙስ በፓርላማ<br />

ባደረጉት ንግግር መጠቆማቸውን ሲፒጄ<br />

ገልጿል።<br />

ከሰኔ ወር ጀምሮ የመንግሥት<br />

ባለሥልጣናት ስድስት የነፃው ፕሬስ ጋዜጠኞችን<br />

በሽብርተኝነት ክስ ወንጅለው ማሰራቸውን<br />

ያወሳው ሲፒጄ፣ የአውራምባ ታይምስ የቀድሞ<br />

ምክትል ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ፣<br />

የፍትህ ጋዜጣ አምደኛ ርዕዮት ዓለሙ፣ ጋዜጠኛ<br />

እስክንድር ነጋ እና ስለሺ ሐጎስ፣ እንዲሁም ጆሃን<br />

ፐርሰንና ማርቲን ሽብዬ የተባሉ ሁለት ስዊድናውያን<br />

ጋዜጠኞች በሽብርተኝነት ተጠርጥረው በእ<strong>ስር</strong> ላይ<br />

እንደሚገኙ አስታውሷል።<br />

የኢትዮጵያ የግል ፕሬሶችን “ጋጠ-<br />

ወጦች” ሲሉ የገለፁት ጠ/ሚኒስትር መለስ<br />

እነዚህን የግል ፕሬሶች ሞያቸውን ያልተረዱ ሲሉ<br />

በውስጥ ገፅ<br />

በ ገፅ 16<br />

በ ገፅ 19<br />

መቆሚያ ያጣው የዋጋ ግሽበት<br />

ገንዘብ ያለገደብ የሚጨመርበት ኢኮኖሚ ለጊዜው ያደገ<br />

እንደሚመስል ፊኛ ነው ‹‹ፊኛ ውስጥ አየር ሲጨመር<br />

የፊኛው መጠን ይተልቃል፤ አየሩ ፊኛው ከሚችለው በላይ<br />

ሲሆን ግን ፊኛው መፈንዳቱ አይቀርም››<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ


2<br />

የካቲት 2000 ዓ.ም<br />

ተመሠረተ<br />

አውራምባ ታይምስ፡- በብሉ<br />

ኤርዝ ጀነራል ቢዝነስ ኃላ/የተ/<br />

የግል/ማህበር <strong>ስር</strong> የሚታተም፤<br />

በፖለቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ<br />

የሚያተኩር፤ በንግድ ሚኒስቴር<br />

በቁጥር 020/2/6572/2001<br />

የተመዘገበ ሳምንታዊ ጋዜጣ ነው፡፡<br />

T’@Í=”Ó ›?Ç=}`<br />

Ç©ƒ ŸuÅ<br />

ª“ ›²ÒÏ<br />

õì


አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004 3<br />

ምን ነካቸው?›› ፤ ‹‹ዛሬ<br />

ላይ እንዲህ መቆጣት ለምን<br />

‹‹ሰውዬው<br />

አስፈለገ?››፣ ‹‹ለምንስ እንዲህ<br />

አመረሩ›› እነዚህንና ሌሎች መሰል<br />

አስተያየቶች አቶ መለስ ዜናዊ ባለፈው<br />

ሀሙስ ጥቅምት 9 ቀን 20004 ዓ.ም<br />

በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ተገኝተው<br />

ያቀረቡትን ማስጠንቀቂያ አዘል ንግግር<br />

ተከትሎ በአዲስ አበባ የተለያዩ ስፍራዎች<br />

(ለፖለቲካዊ ጉዳዮች ብዙ ትኩረት<br />

በማይሰጡ ዜጎችም ጭምር) ሲሰነዘሩ<br />

የሰነበቱ የግርምት አስተያየቶች ናቸው፡፡<br />

የ1997ቱን ምርጫ ተከትሎ በአገሪቱ<br />

ፖለቲካዊ ቀውስ በተፈጠረበት ወቅት<br />

አቶ መለስ ከሰነዘሯቸው መሰል<br />

ማስጠንቀቂያዎች ጋር አቆራኝተው<br />

ለማነጻጸር የተገደዱ ወገኖችም አልጠፉም፡<br />

፡ ቀላል የማይባል ቁጥር ያላቸው<br />

ወገኖችም ማስፈራሪያው አነጣጥሮባቸዋል<br />

ያሏቸውን የአውራምባ ታይምስና ፍትህ<br />

ጋዜጣ አዘጋጆችን ሲያፅናኑና አማራጭ<br />

ያሉትን ምክርና የመፍትሄ አስተያየት<br />

ሲሰነዝሩ ተስተውለዋል፡፡<br />

ህገ መንግስቱን ማክበር<br />

ጥፋት ነውን?<br />

ባለፈው ሀሙስ ከአንዱ በስተቀር<br />

የኢህአዴግ አባላት የሆኑ ‹‹ተመራጮች››<br />

ብቻ የተሰባሰቡበት የኢትዮጵያ<br />

ፓርላማ አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ<br />

የሚያቀርቧቸው ጥያቄዎች እጅግ አሰልቺና<br />

ተመሳሳይነት ያላቸው አይነት ነበሩ። ወደ<br />

መጨረሻ አካባቢ ግን ወ/ሮ አታለል መላኩ<br />

(እሳቸውም ገዢውን ግንባር የሚወክሉ<br />

የም/ቤቱ አባል) ያቀረቡት አቤቱታ አዘል<br />

ጥያቄ ግን የጉዳዩ ባለቤቶችን ብቻ ሳይሆን<br />

የብዙዎችን ትኩረት የሚስብ ነበር።<br />

‹‹በሽብር ተጠርጥረው የታሰሩ ሰዎች<br />

ጉዳይ በፍርድ ቤት ተይዞ ሳለ አንዳንድ<br />

የግሉ ፕሬስ ተቋማት የሰዎቹን ነፃ መሆን<br />

እየመሰከሩ ነው፡፡ የጋዜጦቹ ፍላጎትና<br />

የአቶ መለስ የአደባባይ ምስክርነት<br />

ከዳኝነት ነፃነት አንፃር<br />

በዳዊት ከበደ<br />

አላማ ግልፅ ሆኖ ሳለ መንግሥት ክስ<br />

አለመጀመሩ ለዚህ ችግር አስተዋፅዖ<br />

አበርክቷል።›› ነበር ያሉት የፓርላማ<br />

አባሏ፡፡ በእኒህ የተከበሩ የፓርላማ አባል<br />

የተሰነዘረውና ከላይ ሰረዝ የጨመርኩበትን<br />

‹‹አላማችንና ፍላጎታችን›› ምን እንደሆነ<br />

በድምዳሜ የተጠቀሰው ጥንቆላ ቢብራራ<br />

ፍላጎቴ ቢሆንም እሱን ወደ ጎን ትቼ<br />

ተጠርጥሮ በሕግ ጥላ <strong>ስር</strong> የሚገኝ<br />

ሰው ከፍርድ በፊት ‹‹ነፃ ነው›› ወይስ<br />

‹‹ወንጀለኛ›› በሚለው ጉዳይ ላይ ሕገ-<br />

መንግስቱ የሚለውን ላስታውሳችሁ።<br />

በሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 20 ንዑስ ቁጥር<br />

3 ላይ ተከሳሾች ‹‹በፍርድ ሂደት ባሉበት<br />

ጊዜ በተከሰሱበት ወንጀል እንደጥፋተኛ<br />

ያለመቆጠር መብት አላቸው›› ይላል።<br />

ከዚህ አንጻር ይህንን ሕገ-መንግስታዊ<br />

ድንጋጌ አክብሮ ‹‹ነጻ ናቸው›› ብሎ<br />

የሚያምን ግለሰብ ይሁን ተቋም<br />

‹‹ጋጠወጥ›› የሚባልበት ምክንያት<br />

ምንድነው?<br />

ህጉ በተጨባጭ ከእንግሊዝና ከአሜሪካ የተቀዳ ከሆነ፤ ኢትዮጵያ ሲደርስ ለምን የተቃዋሚዎችና የሚዲያዎች ስጋት ሆነ? ለምንድነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ካሜሮን በእንግሊዝ ፓርላማ<br />

ቀርበው በሌቨር ፓርቲ አመራሮች ላይ ሲዝቱ አሊያም ደግሞ የዘ-ጋርዲያን ጋዜጣ አዘጋጆችን ‹‹ጋጠወጥ›› ሲሉ የማንመለከታቸው? ለምንስ ነው ፕሬዚዳንት ኦባማ በኮንግረስ ተገኝተው<br />

የሪፐብሊካን አመራሮችን በሽብርተኝነት የማይወነጅሉት? ለምንስ ነው የኒው ዮርክ ታይምስ ኤዲተሮችን ‹‹የጋዜጠኝነት ሀሁ የማይገባቸው›› ብለው ሲዘልፉ የማንመለከታቸው?<br />

አቶ መለስ ሕገ-መንግስቱን ስለማክበርና<br />

ስለማስከበር ደጋግመው እየነገሩን<br />

ነገር ግን ከላይ የጠቀስነውን ሕገ-<br />

መንግስታዊ ድንጋጌ በመጣስ ተቃራኒውን<br />

እንድንመሰክር ነው እየወተወቱን ያሉት፡<br />

፡ እንኳን እኛ ይቅርና አንድን ጉዳይ<br />

የሚይዙ ዳኞች እንኳን በተቻለ መጠን<br />

የተከሳሽን የንጹህነት መርህ ግምት ውስጥ<br />

በማስገባት ሊያስቀጣ የሚችል ተጨባጭ<br />

ማስረጃ በአቃቤ ህጉ በኩል አሳማኝ በሆነ<br />

መልኩ እንዲቀርብ ነው የሚጫኑት፡፡ ይህ<br />

የሆነበት ምክንያት አንድም አቃቤ ህግ<br />

ግዙፍ መንግስታዊ አካል እንደመሆኑ<br />

ከተከሳሽ (ግለሰብ) ጋር ሲነጻጸር የአቅም<br />

ውስንነት ግምት ውስጥ ስለሚገባ፤<br />

ሁለተኛ ደግሞ ተከሳሹ እስኪፈረድበት<br />

ድረስ ነጻ ነው ተብሎ ስለሚታሰብ ‹‹ነጻ››<br />

የተባለው ግለሰብ ‹‹ወንጀለኛ ነው›› ብሎ<br />

ለመደምደም ከፍ ያለው የቤት ስራ የአቃቤ<br />

ህጉ በመሆኑ ነው፡፡ በተለይ ተከሳሹ<br />

ጥፋተኛ ከተባለ በኋላ የሚወሰንበት<br />

ቅጣት በግለሰቡ ሁለንተናዊ ነጻነት ላይ<br />

ሊያስከትል የሚችለውን ጉዳት ግምት<br />

ውስጥ በማስገባት ተከሳሹ በተጨባጭ<br />

ወንጀሉን መፈጸሙና አለመፈጸሙ<br />

ብዥታ በማይፈጥር መልኩ መረጋገጥ<br />

ስላለበትም ነው፡፡ ታዲያ እነዚህን<br />

ከመሳሰሉ አጠቃላይ ድንጋጌዎችና ስነ<br />

አመክንዮ አንጻር የመንግስትን የመጨረሻ<br />

ስልጣን ከጨበጡት አቶ መለስ አንደበት<br />

‹‹ከበቂ በላይ ማስረጃ አለን፤ ሰዎቹ<br />

ወንጀለኞች ናቸው›› የሚል የአደባባይ<br />

ምስክርነት ሲቀርብ በዳኝነት ሂደቱ ላይ<br />

የጎላ ተጽእኖ የማሳረፍ አቅም የሚኖረው<br />

ማነው? እኛ ወይስ አቶ መለስ? ሕገ-<br />

መንግስቱን የማክበርና የማስከበር ሂሳብ<br />

እናወራርድ ከተባለ ስህተቱ ጨርሶ የእኛ<br />

አይደለም፡፡ ህገ መንግስቱን ካከበርነው<br />

በደንብ እናክብረው እንጂ!<br />

የእኛ ጥፋት<br />

ለመሆኑ ‹‹ተጠርጥረው በህግ ጥላ <strong>ስር</strong><br />

ያሉ ሰዎች “ድብደባ ተፈፅሞብናል”<br />

እያሉ ነው፣ ቤተሰቦቻቸው እንዲጎበኟቸው<br />

አልተፈቀደም›› ይህ ከሕገመንግስቱ ጋር<br />

አብሮ አይሄድም፡፡ ህግን የማስከበር<br />

ኃላፊነት በተጣለባቸው ሰዎች ህገ<br />

መንግስቱ መደፍጠጥ የለበትም›› ብሎ<br />

መጠየቅ “በቅድመ ሁኔታ የተሰጠን<br />

ይቅርታ ሊያሰርዝ የሚችል ወንጀል”<br />

የሚሆነው በምን አይነት የኦሪት ህግ<br />

ነው? በሕግ ጥበቃ <strong>ስር</strong> ያሉ ሰዎች በሕገ-<br />

መግስቱ መሠረት በተፋጠነ ሁኔታ ፍ/<br />

ቤት ይቅረቡ ብሎ መጠየቅስ በ”ጋጠ-<br />

ወጥነት” የሚያስፈረጀው በምን አይነት<br />

ስነ-አመክንዮ ነው? እኛና ሚዲያዎቻችን<br />

እንደሚሉት ሁሉ እናንተም<br />

ወንጀለኛነታቸውን በአደባባይ መስክሩ<br />

አለበለዚያ “የጋዜጠኝነት ሀሁ አታውቁም”<br />

የምንባለውስ ለምንድነው? የጸረ ሽብር<br />

አዋጁ ለሰፊ ትርጓሜ እጅግ የተጋለጠ<br />

በመሆኑ ነው ለዚህ ሁሉ መቅሰፍት<br />

ምክንያት እየሆነ ያለው፤ እናም አዋጁ<br />

በድጋሚ ይሻሻል ብሎ ሀሳብን መግለጽ<br />

‹‹በሽብርተኞች መልእክተኛነት››<br />

የሚያስፈርጀው ብሎም ሽብርተኝነትን<br />

እንደማበረታታትና የሚቆጠረው<br />

ለምንድነው?<br />

‹‹ቃል በቃል ከውጭ<br />

የተቀዳው›› ሕግ<br />

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፀረ-ሽብርተኝነት<br />

ሕጉ ‹‹እንከን የለሽ›› መሆኑን ለማስረዳት<br />

‹‹ቃል በቃል ከምዕራባዊያን የተቀዳ››<br />

መሆኑን ነግረውናል። የምንኖርበትን<br />

<strong>አገር</strong> ተጨባጭ ሁኔታ ግምት ውስጥ<br />

ሳይገባ አንድ ህግ እንዴት ቃል በቃል<br />

ከውጭ ይኮረጃል፡፡ ሀሳቤን ይበልጽ<br />

ግልጽ ለማድረግ እዚህ ላይ አንድ አብነት<br />

መጥቀሱ ተገቢ ይመስለኛል፡፡ ሰሞኑን<br />

ስለተጨማሪ እሴት ታክስ አሰራር<br />

ለንግዱ ማህበረሰብ ግንዛቤ ለማስጨበጥ<br />

በተጠራ የግንዛቤ ማስጨበጫ ወርክሾፕ<br />

ላይ አንድ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን<br />

ከፍተኛ የሥራ ኃላፊ የተናገሩት ነው፡፡<br />

ሰውዬው እንደገለፁት ኬንያ ተግባራዊ<br />

ያደረገችው የተጨማሪ እሴት ታክስ<br />

ሕግ ቃል-በቃል ከእንግሊዝ የታቀዳ ነው<br />

አሉ። እናም እንግሊዝ የበረዶ ሸርተቴ<br />

የሚያዘወትሩ ዜጎቿን ለማበረታታት<br />

ስትል ‹‹የበረዶ ማንሸራተቻ መሳሪያዎች<br />

ታክስ ሊከፈልባቸው አይገባም›› የሚል<br />

ድንጋጌ በታክስ ሕጓ ላይ አስፍራለች።<br />

በአገሯ ምንም አይነት በረዶ የሌላት<br />

ኬኒያ ሕጉን ቃል-በቃል ከእንግሊዝ<br />

ቀድታ ተግባራዊ ማድረጓን በመጥቀስ<br />

ኃላፊው ተሳታፊውን ፈገግ አሰኙት።<br />

ሰውየው አያይዘውም ኢትዮጵያ<br />

ግን የታክስ ህጉን ከሌሎች አገሮች<br />

ብትኮርጅም ከአገሪቱ ነባራዊ ሁኔታዎች<br />

ጋር በማዛመድ ተግባራዊ አድርጋዋለች<br />

አሉ። ታዲያ የጸረ ሽብር ህጉስ<br />

ከአገራችን ነባራዊ ሁኔታ አንጻር ለምን<br />

አልተቃኘም? እሺ እሱም ይቅር ህጉ<br />

በተጨባጭ ከእንግሊዝና ከአሜሪካ<br />

የተቀዳ ከሆነ፤ ኢትዮጵያ ሲደርስ ለምን<br />

የተቃዋሚዎችና የሚዲያዎች ስጋት<br />

ሆነ? ለምንድነው ጠ/ቅላይ ሚኒስትር<br />

ዴቪድ ካሜሮን በእንግሊዝ ፓርላማ<br />

ቀርበው በሌቨር ፓርቲ አመራሮች ላይ<br />

ሲዝቱ አሊያም ደግሞ የዘ-ጋርዲያን<br />

ጋዜጣ አዘጋጆችን ‹‹ጋጠወጥ››<br />

ሲሉ የማንመለከታቸው? ለምንስ<br />

ነው ፕሬዚዳንት ኦባማ በኮንግረስ<br />

ተገኝተው የሪፐብሊካን አመራሮችን<br />

በሽብርተኝነት የማይወነጅሉት? ለምንስ<br />

ነው የኒው ዮርክ ታይምስ ኤዲተሮችን<br />

‹‹የጋዜጠኝነት ሀሁ የማይገባቸው››<br />

ብለው ሲዘልፉ የማንመለከታቸው?<br />

አዎ! ምክንያቱ በጣም ግልጽ ነው፤<br />

የአሜሪካም ሆነ እንግሊዝ ጠላቶች<br />

ዜጎቻቸውና ተቋሞቻቸው አይደሉም፡፡<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ


4<br />

አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />

<strong>በኢህአዴግ</strong> <strong>ራዳር</strong> <strong>ስር</strong> <strong>የተንበረከከች</strong> <strong>አገር</strong><br />

“<br />

. . . ደርግ ሲገለገልበት<br />

የነበረውን የአዲስ አበባ<br />

የሬዲዮ ጣቢያ ለሰፊው<br />

ህዝብ ጥቅም ሲል<br />

ተቆጣጥሮታል። ግንቦት<br />

20/1983 ዓ.ም”። ከፍተኛ<br />

የህይወትና የአካል<br />

መስዋዕትነት የተከፈለበት<br />

እልህ አስጨራሽ የ17<br />

ዓመታት የትግል ምዕራፍ<br />

ተደምድሞ ዴሞክራሲያዊ<br />

<strong>ስር</strong>ዓት መስፈኑን<br />

የሚገልፅ ዲስኩር መሆኑ<br />

ግልጽ ነውና።<br />

በተለያዩ ፖለቲካዊ ተሳትፏቸውና<br />

ጽሑፎቻቸው የሚታወቁት ፕሮፌሰር<br />

መስፍን ወ/ማርያም፣ “ኢትዮጵያ ከዬት<br />

ወዴት?” በሚለው መጽሐፋቸው ላይ<br />

የሚከተለውን ነጥብ አስፍረዋል፡- “ . .<br />

. ሥርዓት ሥርዓትን ይወልዳል። የአፄ<br />

ኃይለሥላሴ ሥርዓት የደርግን ሥርዓት<br />

ወለደ፤ የደርግ ሥርዓት በበኩሉ አሁን<br />

በኤርትራ እና በቀሩት የኢትዮጵያ ክፍሎች<br />

ያሉትን ሥርዓቶች ወለደ። . . . ”<br />

የደርግ መንግሥት በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ<br />

ይፈፅም የነበረው ግፍ እንዲሁም ህዝቡ<br />

ያሰማው የነበረው ብሶት ወደ ትግል<br />

እንዳስገባው በተደጋጋሚ የሚናገረውና<br />

የደርግ ሥርዓት የወለደው ኢህአዴግ፣ ለ17<br />

ዓመታት በደርግ <strong>ራዳር</strong> ውስጥ የነበረችውን<br />

ኢትዮጵያን በገዛ ራዳሩ ውስጥ ካስገባት 20<br />

ዓመታት ተቆጥረዋል።<br />

ኢህአዴግ፣ ግንቦት 20/1983 ሀገሪቱን<br />

‘ሙሉ በሙሉ’ ይቆጣጠር እንጂ፣ ቀስ<br />

በቀስ በተለያዩ ዓመተ-ምህረቶች ጥቂት<br />

የማይባሉ የሀገሪቱ ክፋዮች ከቁጥጥሩ ውጭ<br />

መሆናቸውን መረጃዎች እያመላከቱ ነው።<br />

“ ... ለሰፈው ህዝብ ጥቅም ... ?”<br />

“ ... ለሰፊው ህዝብ ጥቅም ... ” ይህቺ<br />

ሐረግ ለኢትዮጵያ ህዝብ አዲስ አይደለችም።<br />

ከግንቦት 20/1983 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ዛሬ<br />

ድረስ ከአ<strong>ስር</strong> ዲጂት በላይ ለሚሆን ጊዜ<br />

የተደመጠች እና ወደፊትም በአሁኑ ሰዓት<br />

በሥልጣን ላይ የሚገኘው መንግሥት<br />

እስካለ ድረስ የምትደመጥ ሐረግ ነች።<br />

በአባባሏ ላይ ማንም ሰው ቅሬታ<br />

የለውም። ብዙዎችን ከነልዩነታቸው<br />

የሚያስማማው ጉዳይም፣ አንድ<br />

መንግሥት ለሰፊው ህዝብ ጥቅም<br />

መስራት እና መቆም እንዳለበት<br />

ነው። ‹‹ይሁን እንጂ…›› ይላሉ<br />

የኢትዮጵያ መንግስት ሰፊውን<br />

ህዝብ ተጠቃሚ የሚያደርግ<br />

ሥራ እየሰራ አለመሆኑን<br />

የሚያምኑ ወገኖች። ‹‹…<br />

አሁን ባለው ወቅታዊ<br />

ሁኔታ ከሰፊው ህዝብ<br />

ይልቅ ጥቂቶች<br />

እንደ ሮኬት<br />

በመወንጨፍ<br />

ተ ዓ ማ ኒ ነ ት<br />

የጎደለው እድገት<br />

እያሳዩ ነው›› በማለት<br />

የሰፊው ህዝብ ፅንሰ ሀሳብ<br />

ግቡን አለመምታቱን በመጠቆም<br />

ይከራከራሉ።<br />

እስካሁን ድረስ <strong>በኢህአዴግ</strong> ታሪክ፣<br />

የኢትዮጵያ ህዝብ ከጫፍ እስከ<br />

ጫፍ እስከ ልዩነቱ ከመንግሥት ጎን<br />

የቆመው፣ ለሰፊው ህዝብ ከፍተኛ ጥቅም<br />

ይሰጣል ብሎ ባመነበት አንድ ጉዳይ ነው።<br />

እሱም ከደሙና ከታሪኩ ጋር የተሳሰረው<br />

የአባይ ጉዳይ ሆኖበት ነው። እንደውም፣<br />

መንግሥት፣ በሀገሪቱ ውስጥ ሰፊውን<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

ፊ ቸ ር<br />

ከህዝብ ጥቅም ይልቅ የራስን ፖለቲካዊ ምህዳር ማስጠበቅ<br />

<strong>አገር</strong><br />

<strong>የተንበረከከች</strong> <strong>ስር</strong> <strong>ራዳር</strong> <strong>በኢህአዴግ</strong><br />

በታዲዎስ ጌታሁን<br />

ከጥቂት ጊዜያት ወዲህ፣ መንግሥት ሰፋፊ መሬቶችን ለውጭ ባለኃብቶች በወረደ ወይም<br />

አንድ ኪሎ ሙዝ በማይገዛ (በአሁን ሰዓት አንድ ኪሎ ሙዝ 12 ብር ሲሆን አንድ<br />

ሄክታር ድንግል መሬት ደግሞ እስከ አ<strong>ስር</strong> ብር ይሸጣል) ዋጋ መሸጡ እያስገረመ ሳለ፣<br />

ባለኃብቶቹ፣ የሀገራቸውን ሥራ አጦች በአውሮፕላን ጭነው አምጥተው በተረከቡት<br />

መሬት ላይ እንዲሰሩ ማድረጋቸው ብዙዎችን አስቆጥቷል።<br />

ህዝብ የሚያስቆጣ መሠረታዊ ችግሮች<br />

መኖራቸው ስላስፈራው እና የአረብ ሀገራት<br />

አብዮት ወደ ኢትዮጵያ እንደይመጣ<br />

ስለሰጋ ነው አባይን ለመገደብ የተነሳው<br />

ብለው ያምናሉ። ምንም እንኳን ጠቅላይ<br />

ሚኒስትር መለስ ዜናዊ፣ መንግሥታቸውን<br />

ሥጋት ላይ የሚጥል ችግር በኢትዮጵያ<br />

እንደሌለና ሰፊው ህዝብ ከመንግሥት ‹ሰፊ<br />

ጥቅም› በማግኘቱ የ5 ዓመት ኮንትራት<br />

እንደሰጣቸው ተናግረው የነበረ ቢሆንም።<br />

ኑሮ፣ በተዓምር ወይስ በተዓምራዊ ዕድገት?<br />

የሁለተኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሦስተኛ<br />

መደበኛ ስብሰባውን ጥቅምት 9 ቀን<br />

2004 ዓ.ም ያከናወነው የኢፌዴሪ የህዝብ<br />

ተወካዮች ም/ቤት፣ ከወትሮው ለየት ያለ<br />

መንፈስ እና ንግግር ጎብኝቶት ነበር።<br />

የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ<br />

መስከረም 29 ቀን 2004 ዓ.ም ባደረጉት<br />

የምክር ቤት መክፈቻ ንግግር ላይ በሚቀርቡ<br />

የማሻሻያ ሞሽኖች ላይ የመንግሥታቸውን<br />

አቋም ለማስደመጥ በምክር ቤቱ የተገኙት<br />

ጠ/ሚኒስትር መለስ፣ እንደ ከዚህ ቀደሙ<br />

ሁ ሉ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ<br />

ሽቅብ ‘መወንጨፉን’ በ‘ተዓምር’ መስለው<br />

ተናግረዋል።<br />

በምክር ቤቱ ብቸኛው የመድረክ ተወካይ<br />

የሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ፣ “ሀገራችን<br />

ያስመዘገበችው እድገት የትክክለኛ<br />

ፖሊሲዎች ውጤት ነው” የሚለው ዓረፍተ-<br />

ነገር ከኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ጋር<br />

የማይመሳሰል መሆኑን ቢናገሩም፣ በአቶ<br />

መለስ ዜናዊ ተቀባይነት አላገኙም።<br />

ጠ/ሚኒስትሩ፣ የሞተን ሰው ነፍስ ዘርቶ<br />

ከመቃብር የማስነሳት ያህል ‘ተዓምራዊ’<br />

ሲሉ የገለፁትን የኢኮኖሚ ዕድገት የምጣኔ<br />

ኃብት ባለሙያ የሆኑት አቶ ተመስገን<br />

ዘውዴ፣ ከህንፃ ግንባታዎች በስተቀር<br />

በሌሎች ሴክተሮች ላይ የታየ ጉልህ<br />

ለውጥ እንደሌለ በማስረገጥ ተዓምራዊውን<br />

እድገት ዋጋ ያሳጡታል። ቀጠል ያደርጉና<br />

“በእርግጥም የህንፃዎችንና የቪላ ቤቶችን<br />

በብዛት መገንባት ለኢኮኖሚ እድገትና<br />

ለህዝቡ ኑሮ መሻሻል እንደ ማሳያ<br />

ሊያስቀምጡ የሚሞክሩ የኢህአዴግ ወገኖች<br />

አይጠፉም። አነዚህ ወገኖች ግን አዲስ አበባ<br />

ከተማ ውስጥ ያለው የህንፃዎች ግንባታ<br />

በአጠቃላይ አገሪቱ ውስጥ ያለውን የኢኮኖሚ<br />

እንቅስቃሴ ሊወክል ይችላልንን? የሚለውን<br />

ጥያቄ መመለስ የሚችሉ አይመስለኝም”<br />

በማለት የህንፃ ግንባታ አንድ ራሱን የቻለ<br />

ነጠላ ዘርፍ መሆኑን ያስረዳሉ።<br />

የኢፌዴሪ የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ<br />

የባለፈውን ወር የ<strong>አገር</strong> አቀፍ እና የክልሎችን<br />

የሸማቾች ዋጋ መመዘኛ ኢንዴክሶችን<br />

ባወጣበት ሪፖርት ላይ የምግብ ዋጋ<br />

ግሽበት 51.3 በመቶ መድረሱን<br />

ገልጿል። እንዲሁም፣ በመስከረም<br />

ወር 2004 ዓ.ም የተመዘገበው የ12<br />

ወራት ተንከባላይ አማካኝ አገራዊ<br />

አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ካለፈው<br />

ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር<br />

በ26.6 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን<br />

ሪፖርቱ ጨምሮ ገልጿል።<br />

የዋጋ ግሽበት እና የኑሮ<br />

ውድነት ጣራ መንካታቸው<br />

ለአቶ መለስ የሚያስገርም<br />

ጉዳይ አልሆነም። ‹‹የኑሮ<br />

ውድነትም ሆነ የዋጋ<br />

ግሽበት እያለ<br />

ኢኮኖሚ ማደግ ይችላል፤ እነዚህ ሁኔታዎች<br />

ባሉበት ሁኔታ ኢኮኖሚ አያድግም ማለት<br />

የኢኮኖሚን ሀሁ አለመገንዘብ ነው››<br />

በማለት ብዙ ሚሊዮን ህዝብን ግራ እያጋባና<br />

ከዕለት ዕለት ኑሮውን እያመሳቀለ ያለውን<br />

የኑሮ ውድነት ‘ቀላል’ አድርገው ለማየት<br />

ሞክረዋል።<br />

ይህ ዓይነቱ (51.3 በመቶ) የዋጋ ግሽበት<br />

በተከሰተበት ሰዓት ከፍተኛ የኢኮኖሚ<br />

ዕድገት አስመዘግባለሁ ማለት ተጨማሪ<br />

ገንዘብ ወደ ኢኮኖሚው ማፍሰስ መሆኑን<br />

የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ያስረዳሉ።<br />

‹‹ግሽበት ማለት ሌላ ተዓምር አይደለም፤<br />

ጥቂት ምርትና እጅግ በርካታ ገንዘብ<br />

በኢኮኖሚው ውስጥ መኖር ነው›› የሚሉት<br />

አቶ ተመስገን፣ ‹‹ከፍተኛ ዕድገት ቢመጣ<br />

መልካም ነበር ግን መወሰድ ያለባቸውን<br />

እርምጃዎችና መዋጥ ያለባቸውን መራራ<br />

ኪኒኖች ሳይውጡ የማይሆን ነገር<br />

ነው” በማለት የመፍትሄ ሀሳባቸውን<br />

እንደሚከተለው ያካፍላሉ፡- “ግሽበቱን<br />

ለማስተካከልና የታቀደውን ዕቅድ ለማሳካት<br />

መዋጥ ያለባቸው መራራ ኪኒኖች<br />

ፊስካልና ሞኒተሪ መሳሪያዎች ናቸው።<br />

በተለይ በሞኒተሪው በኩል ብሔራዊ ባንክ<br />

ነፃ ወይም ከአስፈፃሚ አካላት ተፅዕኖ<br />

ሊላቀቅ ይገባዋል። ብሔራዊ ባንክ ነፃ<br />

ሆኖ ቢሰራ የወለድ መጠን እንዲጨምር<br />

ያደርጋል። የወለድ መጠን ሲጨምር ሰዎች<br />

ገንዘባቸውን ባንክ ማስቀመጥ ይጀምራሉ።<br />

የዛኔ የኢኮኖሚው ውስጥ የገንዘብ ዝውውር<br />

እየቀነሰ ይመጣል። … ብሔራዊ ባንክ<br />

የንግድ ባንኮች የግዴታ ሊይዙት የሚገባውን<br />

የተቀማጭ ገንዘብ መጠን (ሪዘርቭ<br />

ሪኳየርመንት) እንዲጨምር ማድረግ<br />

ያስፈልጋል። ይህም ገንዘብን ከኢኮኖሚው<br />

ውስጥ ለመቀነስ ይረዳል” በማለት ምሁራዊ<br />

አስተያየታቸውን ያጋራሉ።<br />

የኢኮኖሚን ሀሁ እንደማያውቁ በጠ/<br />

ሚኒስትር መለስ ‘የማረጋገጫ ሰርተፊኬት’<br />

የተሰጣቸው አቶ ግርማ ሰይፉ፣<br />

‹‹እንኳንስና 11.4 በመቶ ሊታደግ ቀርቶ<br />

አምና ከነበረበትም የወረደ ህይወት ነው<br />

የኢትዮጵያ ህዝብ እየመራ ያለው። ሰዉ<br />

በቀን አንዴ መመገብ እንኳን አቅቶት<br />

ባለበት ሁኔታ፣ “ኢኮኖሚው አድጓል ብሎ<br />

ሽንጥን ገትሮ መከራከር እውነታውን መካድ<br />

ነው። እኛኮ 11 በመቶ አድገናል ቢባልም<br />

ሆነ 15 በመቶ፣ በተጨባጭ<br />

ዕድገቱ የዜጎች ህይወት<br />

ላይ ካልተንፀባረቀ ምንም<br />

ለውጥ የለውም” በማለት<br />

ህዝቡ ያለበትን ወቅታዊ<br />

የኑሮ ሁኔታ በቁጭት<br />

ይገመግሙታል።<br />

“ተዓምራዊ እድገት ማለት እኮ<br />

ቀላል ነገር አይደለም። በአሁን ሰዓት<br />

ኢትዮጵያ ውስጥ ‘ተዓምር’ የሚያሰኝ<br />

እድገት ተፈጥሮ ቢሆን ኖሮ የአዲስ ዘመን<br />

ጋዜጣ ኮፒ ወደ 80 ሚሊየን ይጠጋ ነበር።<br />

ምክንያቱም፣ የተዓምራዊው ዕድገት ተቋዳሽ<br />

የሆነው 80 ሚሊየን ህዝብ፣ “ኢኮኖሚው<br />

አላደገም’ ብለው የህዝቡን ብሶት የሚጮሁ<br />

ነፃ ጋዜጦችን ተጠይፎ ከመንግሥት<br />

ጎን ይቆም ነበር” የሚሉ ወገኖች፣ ህዝቡ


አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />

በተዓምራዊ ዕድገት ሳይሆን በአንዳች<br />

ተዓምራዊ ኃይል እየኖረ መሆኑን ደግመው<br />

ደጋግመው ያስረግጣሉ።<br />

እነዚሁ ወገኖች ቀጠል በማድረግም፣<br />

“መንግሥት ኢኮኖሚውን ለማስተካከል<br />

ግሽበቱን ከመቆጣጠር ይልቅ የኢኮኖሚ<br />

ባለሙያዎች የሚያቀርቡትን የመፍትሄ<br />

ሀሳብ ተቆጣጥሮ ለማምከን መጣደፉ በጣም<br />

ያስገርማል” በማለት ጭንቅላታቸውን<br />

በሀዘኔታ ይነቀንቃሉ።<br />

ዳቦ ገዢ VS ዳቦ ፈላጊ<br />

ባለፉት የኢህአዴግ 20 ዓመታት ውስጥ፣<br />

ከመንግሥት <strong>ራዳር</strong> ወጥተዋል ተብሎ<br />

የሚነገርላቸውና ለብዛታቸውም የቁጥርና<br />

የፊደል መረጃ የሚጠቀስላቸው ብዙ<br />

ሺህ ‘ስራ አጥ’ ኢትዮጵያውያን አሉ።<br />

የስራ አጦቹ ቁጥር ከሁለቱም መደብ<br />

(ከተመረቀውም ካልተመረቀውም ወይም<br />

ካልተማረው) የተውጣጣ ሲሆን፣ በአሁን<br />

ሰዓት ያሉበት ደረጃ ደግሞ እጅግ አሳሳቢና<br />

አፋጣኝ እርምጃ ከሚሹ ጉዳዮች መካከል<br />

የሚካተት መሆኑ ብዙዎችን ያስማማል።<br />

መንግሥት፣ በአምስት ዓመቱ የዕድገትና<br />

ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ውስጥ አሳካቸዋለሁ<br />

ብሎ በልበ-ሙሉነት ከዘረዘራቸው ጉዳዮች<br />

አንዱ ዩኒቨርስቲዎችን በቁጥር የማሳደግ<br />

ነው። በዚህ ላይ ቅሬታ የሌላቸው ሰዎች<br />

“በቁጥር ካደጉት ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ<br />

ተመርቀው ለሚወጡ ቁጥራቸው የበዛ<br />

ተማሪዎች ምን የተመቻቸ ነገር አለ?<br />

ወይስ የመንግሥት ሥራ ማስመረቅ ብቻ<br />

ነው?” በማለት ሊታሰብበት የሚገባ ወሳኝ<br />

ጥያቄ ይሰነዝራሉ።<br />

የህወሓት መሥራች አባል የነበሩትና<br />

በአሁን ወቅት የአረና ፓርቲ የአመራር<br />

አባል የሆኑት አቶ አስገደ ገ/ሥላሴ፣ “ሙስና<br />

እና ኢንቨስትመንት በትግራይ” በሚለው<br />

መጣጥፋቸው ላይ ያነሱት ጉዳይ አለ፤ “ ...<br />

በሁሉም ዞኖች ያሉ ማኅበራት አብዛኛዎቹ<br />

የከሰሙና የከሰሩ እንዲሁም ለዕለት ጉርስ<br />

እየለቃቀሙ የሚኖሩ ናቸው። ለዚህም<br />

የክልሉ የኢንዱስትሪና የከተማ ልማት<br />

ቢሮ ኃላፊና የህወኃት ማዕከላዊ ኮሚቴ<br />

አባል የሆኑት አቶ በየነ መክሩ በሰማዕታት<br />

ሀውልት እንደተናገሩት፣ አብዛኛዎቹ<br />

የጥቃቅንና አነስተኛ ማኅበራት ገንዘብ<br />

አበደርናቸው፣ ሁሉም ከሰሩ ብለዋል።<br />

“… በትግራይ ክልል የነበረ አናጢ፣ ግንበኛ፣<br />

ለሳኝ በአጠቃላይ ሞያተኞችና የጉልበት<br />

ሰራተኞችን በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ስራ<br />

ፈጥረው ሲያሰሩ የነበሩ የህንፃ ተቋራጮች<br />

(ኮንትራክተሮች) አብዛኛዎቹ በብልሹ<br />

አስተዳደር ምክንያት ከክልሉ ለቀዋል››<br />

በማለት ብልሹ አሰራር ምን ያህል ስራ<br />

አጥ ዜጎችን እየፈጠረ እንደሚገኘም<br />

ያመላክታሉ።<br />

ዳቦ ለመግዛት ወደ ዳቦ ቤት ከሚሄደው<br />

ሰው ይልቅ፣ ዳቦ ፍለጋ ወደ ቫካንሲ<br />

ሰሌዳዎች የሚጎርፈው ሰው በበለጠበት<br />

በዚህ ሰዓት፣ መንግሥት የሥራ ዕድል<br />

ለመፍጠር መትጋት ሲገባው፣ ለብዙ ሥራ-<br />

አጦች በልቶ ማደር ምክንያት የሚሆኑ<br />

ባለኃብቶችን በብልሹ አሰራር ምክንያት<br />

ከቦታ ቦታ ማሳደዱ ያስቆጫቸው አቶ<br />

አስገደ፣ “ ... የትግራይ ባለኃብቶችና<br />

ድርጅቶች የተመቻቸ የኢንቨስትመንት ቦታ<br />

ባለማግኘታቸው እንደ አማራጭ ወደ ሌላ<br />

ቦታ ሄደው ሲበለፅጉ ይታያል” በማለት ብዙ<br />

ሥራ-አጦች እንጀራቸውን ከጉሮሯቸው ላይ<br />

እየተነጠቁ መሆኑን ያስገነዝባሉ።<br />

ከጥቂት ጊዜያት ወዲህ፣ መንግሥት ሰፋፊ<br />

መሬቶችን ለውጭ ባለኃብቶች በወረደ<br />

ወይም አንድ ኪሎ ሙዝ በማይገዛ (በአሁን<br />

ሰዓት አንድ ኪሎ ሙዝ 12 ብር ሲሆን<br />

አንድ ሄክታር ድንግል መሬት ደግሞ እስከ<br />

አ<strong>ስር</strong> ብር ይሸጣል) ዋጋ መሸጡ እያስገረመ<br />

ሳለ፣ ባለኃብቶቹ፣ የሀገራቸውን ሥራ<br />

አጦች በአውሮፕላን ጭነው አምጥተው<br />

በተረከቡት መሬት ላይ እንዲሰሩ<br />

ማድረጋቸው ብዙዎችን አስቆጥቷል።<br />

“ምክንያቱም . . . ” ይላሉ ተቆጪዎቹ፣<br />

“ … ኢትዮጵያውያን ሥራ-አጦች ሊሰሩት<br />

የሚገባውን ሥራ ባህር አቋርጠው የመጡ<br />

ሰዎች መስራታቸው ኢትዮጵያውያን የበይ<br />

ተመልካች እንዲሆኑ አስገድዷቸዋል፤ ይሄ<br />

ደግሞ ከአንድ መንግሥት አይጠበቅም፤<br />

ኢህአዴግ የኢትዮጵያ መንግሥት እንጂ<br />

የህንድና የቻይና (ሥራ-አጦች) መንግሥት<br />

አይደለም” በማለት መንግሥት አቋሙን<br />

እንዲያስተካክል ማሳሰቢያ ይሰጣሉ።<br />

ትግሉ ተቋጨ?<br />

ምንም እንኳን ኢትዮጵያ እንደ ጃፓን<br />

በኒዩክለር ጣጣ፣ እንደ ቱርክ በመሬት<br />

መንቀጥቀጥ፣ … አትመታ እንጂ በሥራ<br />

አጥነት፣ በኑሮ ውድነት፣ በቤት እጦት እና<br />

ኪራይ ችግር … ወዘተ ክፉኛ እየተናወጠችና<br />

እየተመታች እንዲሁም ዜጎቿ ከአቅም<br />

በላይ በሆነ ችግር መኖሪያቸውን ለቀው<br />

እየተሰደዱና በየበረሐው እየሞቱ<br />

መሆናቸውን የተለያዩ አስደንጋጭ<br />

ሪፖርቶች እያመላከቱ ነው።<br />

በአሁን ሰዓት ኢትዮጵያ በከባድ ጎርፍና<br />

ወጀብ አለመመታቷን “ተመስገን” በማለት<br />

የሚገልፁ ወገኖች፣ ሀገሪቱ ቅጥ አምባሩ<br />

በጠፋ የኑሮ ውድነት መሀል አናቷን<br />

መበርቀሷ ግን በየደቂቃው እያባነናቸው<br />

መሆኑን ከመናገር አልተቆጠቡም።<br />

በ2003 ዓ.ም ታህሳስ ወር ላይ፣ ጠቅላይ<br />

ሚኒስትሩን፣ የሚኒስትር ዴኤታዎችን<br />

እና ሌሎች የመንግሥት ባለሥልጣናትን<br />

በአንድ አዳራሽ አሰባስቦ የነበረው የኑሮ<br />

ንረት፣ ዛሬ ከመንግሥት <strong>ራዳር</strong> የወጣበት<br />

ምክንያት ምን እንደሆነ የተገለፀ ነገር<br />

ባይኖርም፣ ኢኮኖሚስቶች ግን ጉዳዩ<br />

(ንረቱ) ከመንግሥት አቅም በላይ መሆኑን<br />

መረጃዎችን በማገላበጥ ያስረዳሉ።<br />

“የነዳጅ ዋጋ መናር በሊቢያና በመሰል<br />

ሀገራት አብዮት ይመካኛል። የሥጋ፣<br />

የበርበሬ፣ የቡና … ዋጋ መናር በማን<br />

ሊሳበብ ነው? ዋጋቸው ስንት እስኪገባስ<br />

ድረስ ነው በዝምታ የሚታዩት?” የሚል<br />

ጥያቄ የሚያቀርቡ ሰዎች ከመንግሥት<br />

የሚሰጣቸው ምላሽ ከሀገሪቱ ወቅታዊ<br />

ሁኔታ ጋር ፍፁም የሚቃረን መሆኑ<br />

ያበሳጫቸዋል።<br />

መንግሥት፣ ይሄ ዕቃ ተወደደ ሲባል<br />

“አድገናል”፤ ኧረ ይሄ ዕቃ ከገበያው ጠፋ<br />

ሲባል “አድገናል አድገናል”፤ ኧረ መፍትሄ<br />

አምጡ በልቶ ማደር አለማደር ልማድ ሆነ<br />

ሲባል፣ “አድገናል አድገናል፣ አድገናል”<br />

የሚለው ህዝብ እንዳይቆጣው አስቀድሞ<br />

ለመቆጣት ነው ይላሉ - የመንግሥትን<br />

አመለ-ቢስነት በቅርበት የሚያውቁ ውስጠ-<br />

አዋቂዎች።<br />

“የኢትዮጵያ ህዝብ ስራ ማጣቱን፣<br />

መራቡን፣ ኑሮ ከአቅሙ በላይ መሆኑን<br />

… ለመግለፅ የግድ እንደ ቱኒዝያዊው<br />

መሐመድ ቡአዚዝ ራሱን አቃጥሎ<br />

መግደል አለበት ወይ?” የምትለውና<br />

የአምስት ልጆች እናት የሆነችው ወ/ሮ<br />

ቅድስት ተክሉ፣ ህዝቡ ክብሪት ጭሮ ራሱን<br />

ባያቃጥልም፣ በመንግሥት ቸልተኝነት እና<br />

በአንዳንድ ራስ-ወዳድ ነጋዴዎች የተጫረው<br />

የኑሮ ንረት ቀስ በቀስ ህዝቡን አቃጥሎ<br />

እየጨረሰው መሆኑን በማስጠንቀቂያ መልክ<br />

ትናገራለች።<br />

የጦር ሠራዊት እና የጦር መሳሪያ<br />

በመሰብሰብ (በመያዝ) ከምስራቅ አፍሪካ<br />

ሶስተኛ ደረጃ ይዞ የነበረውን የደርግ<br />

መንግሥት በ17 ዓመታት ውስጥ ታግለው<br />

በመጣል ኢትዮጵያን በራዳራቸው ሥር<br />

ያስገቡት ኢህአዴጎች፣ ዛሬ ቤተ-መንግሥት<br />

እና ያማረ ቤት ውስጥ እየኖሩ፣ እንደ<br />

ውሃ በሚፈስ መኪና እየተመላለሱ ህዝቡን<br />

የሚገዳደሩ ችግሮችን ምነው መታገልና<br />

መጣል አቃታቸው? ወይስ ትግሉ ተቋጨ?<br />

የሚል አነጋጋራ ጥያቄዎች እየተነሱበት<br />

ነው - መንግሥት።<br />

ሀና እና መሰሎቿ<br />

ሚያዝያ 22/2000 ዓ.ም የስምንት ዓመት<br />

ልጅ እና የሁለተኛ ክፍል ተማሪ ለነበረችው<br />

ሀና አለማየሁ ጥሩ ቀን አልነበም፡። ቀኑ<br />

እንደመምሸት ሲል ሀና ከወላጆቿ ቤት ወደ<br />

አያቷ ቤት ጉዞ ትጀምራለች። (የወላጆቿ<br />

እና የአያቷ ቤት አንድ ሰፈር ውስጥ ነው<br />

ያለው)<br />

ልጅቷ ቤት ከመድረሷ በፊት እስካሁን<br />

ድረስ ማንነቱና ምንነቱ ያልታወቀ ሰው<br />

ያገኛትና አታሎ ይዟት ይሄዳል። …<br />

አስገድዶ ከደፈራት በኋላ ህይወቷ አለፈ።<br />

ጧት ሀና ሰፈራቸው የሚገኝ ወንዝ ውስጥ<br />

ተጥላ ተገኘች።<br />

የኤልፓንና የቴሌን ህንፃ “ለጥቂት”<br />

ከመጋዬት እና ከመውደም አድኖ<br />

‘ተጠርጣሪ’ ያላቸውን ጋዜጠኞች በቁጥጥር<br />

(በራዳሩ) <strong>ስር</strong> ያዋለ መንግሥት፣ በሀና እና<br />

በመሰሎቿ ላይ ጥቃት ፈፅመው (ያውም<br />

ገድለው) የተሰወሩ ተጠርጣሪዎችን እንዴት<br />

መያዝ አቃተው? የሚል ጥያቄ ይነሳል -<br />

በህብረተሰቡ ዘንድ።<br />

ጥቃት ፈፅመው ከመንግሥት <strong>ራዳር</strong> ውስጥ<br />

የተሰወሩት ተጠርጣሪዎች በመንግሥት<br />

ቸልተኝነት ነው ያልተያዙት? ወይስ<br />

ከመንግሥት አቅም በላይ ሆነው ነው?<br />

ይላሉ የጥቃት ሰለባዎቹ ቤተሰቦች።<br />

መንግሥት፣ ከህዝቡ ጥቅም ይልቅ የራሱ<br />

ጥቅም እንደሚበልጥበት የሚናገሩ ወገኖች፣<br />

የፖለቲካውን ምህዳር ‘ለመጠበቅ’ በሚል<br />

ሰበብ የራሱን የሥልጣን ምህዳር እየጠበቀ<br />

መሆኑኑ በመግለፅ “ጥቃት ፈፅመው<br />

ያልተያዙ ህዝብ አሸባሪዎች አነፍንፎ<br />

ለመያዝ ምነው አፍንጫና እጅ አጠረው?”<br />

ይላሉ።<br />

አንቀጽ<br />

በታዲዎስ ጌታሁን<br />

አራዳሹ ከጥግ እስከ ጥግ በሰው<br />

ጢም ብሏል። ሁሉም ተሰብሳቢ ሰውዬውን<br />

በጉጉት ይጠባበቃል። ሰውዬው በጉጉት<br />

የሚጠበቀው ያለ ምክንያት አይደለም።<br />

የተሰብሳቢዎቹ ችግር የሚቀረፈው<br />

ሰውዬው ለበታቾቹ በሚያስተላልፈው<br />

ትዕዛዝ በመሆኑ ሁሉም ደጅ ደጁን ያያል።<br />

… ወዲያውም የአዳራሹ መግቢያ በር ላይ<br />

ከፍተኛ ግርግር ተፈጠረ።<br />

ደረታቸውንና ጡንቻቸውን<br />

ያሳበጡት የሰውዬው ጠባቂዎች (ጋርዶች)<br />

ነበሩ የግርግሩ መንስዔዎች።<br />

ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ<br />

እንዲሉ ምንም ዓይነት አስጊ ሁኔታ በሌለበት<br />

ሰላማዊ አዳራሸ ውስጥ ወከባ ከፈጠሩ<br />

በኋላ ሰውዬውን የተዘጋጀላቸው ቦታ ላይ<br />

አስቀመጧቸው።<br />

የተሰብሳቢውን ችግር ሰምተው<br />

መፍትሔ ለማምጣት ፊት ለፊት የተሰየሙት<br />

ሰውዬ አንድ በአንድ ጥያቄ ይቀርብላቸው<br />

ጀመር።<br />

‹‹በከተማችን ውስጥ የቤት ችግር<br />

እየተስፋፋ ነው፤ እና ችግሩን ለመቅረፍ ምን<br />

አስባችኋል?›› አለ አንድ ተሰብሳቢ።<br />

ሁለተኛዋ ተሰብሳቢ ደግሞ<br />

የሚከተለውን ጠየቀች፡- ‹‹በድህነት ውስጥ<br />

የምንኖረው እስከ መቼ ነው? ኑሯችን<br />

የሚሻሻለውስ እንዴት ነው?›› እንባዋ ጠብ<br />

ጠብ አያለ ተቀመጠች።<br />

አንድ አሽቃባጭና አጨብጫቢ<br />

ተሰብሳቢ ደግሞ በሦስተኝነት ጥያቄውን<br />

አቀረበ፡- ‹‹በዙሪያችን አሰፍስፈው የቆሙትን<br />

ተቃዋሚዎቻችንን እንዴት ነው መከላከልና<br />

እንቅስቃሴያቸውን ማዳከም ያለብን?›› ሲል<br />

ሰውዬው ፈጠን ብለው፣ ‹‹ጥሩ ጥያቄ ነው!››<br />

አሉ።<br />

ጥሩ ነው ያሉትን ጥያቄ እየፈቱና<br />

እንየበተኑ እንዲሁም ተቃዋሚዎቻቸውን<br />

የማልፈስፈስ ስትራቴጂያቸው ምን<br />

እንደሚመስል በስፋትና በጥራት አወሩ።<br />

አወሩ። አሁንም ደግመው ደጋግመው አወሩ።<br />

…<br />

… ሚያዚያ 25 ቀን 1881 ዓ.ም፤<br />

ንጉስ ምኒልክ ከጣሊያን መንግሥት ጋር፣<br />

ሃያ አንቀጾች የያዘ ውል ለመዋዋል ውጫሌ<br />

ተቀምጠዋል። ምኒልክና ጣሊያን በሌሎቹ<br />

አንቀጾች ይዘት ቢስማሙም፣ መዘዘኛው<br />

አንቀጽ አስራ ሰባት ግን ለከፋ ውዝግብ ወይም<br />

ለአድዋ ጦርነት ዳርጓቸዋል።<br />

‹‹የኢትዮጵያ መንግሥት ከውጭ<br />

<strong>አገር</strong> መንግሥታት ጋራ የሚያደርገውን<br />

ግንኙነት በኢጣሊያ መንግሥት አማካይነት<br />

ማድረግ ይገባዋል›› ይላል የአንቀጽ 17<br />

የጣሊያንኛ ትርጉም።<br />

የአድዋ ጦርነት ያለመደማመጥ<br />

ውጤት ነው። ጣሊያን፣ የልብ ትርታዋንና<br />

ፍላጎቷን እንጂ፣ ኢትዮጵያ በአንቀጽ<br />

17 ላይ ታሰማ የነበረውን የተቃውሞ<br />

ድምፅ አታዳምጥም ነበር። ወይም ደግሞ<br />

ተቃውሞውን ለመቀበል ዝግጁና ፈቃደኛ<br />

አልነበረችም። ለዚህም ነው መሳሪያዋን ጭና<br />

ወደአድዋ ተራሮች መትመም የጀመረችው።<br />

… ‹‹መንግስት ዓይንና ጆሮ<br />

አለው›› ይላል ኢህአዴግ። በእርግጥም ትልቅ<br />

ጆሮ ነው ያለው መንግሥት። ግን አብዛኛውን<br />

ጊዜ ጆሮውን ዘንበል የሚያደርገው ወደ<br />

ህብረተሰቡ ጥያቄ ሳይሆን ወደ ተቃዋሚዎች<br />

መንደር ነው።<br />

‹‹የቤት ችግር አለ፤ ድህነት<br />

ተንሰራፋ፤…›› የሚሉ ህብረተሰብዎች ስፍር<br />

ቁጥር የላቸውም። ጆሮ እንዳለው በፓርላማ<br />

የተናገረው መንግሥት ግን፣ ፈጥኖ ጆሮውን<br />

የሚያዘነብለው ወደ ዶ/ር ነጋሶ፣ ኢንጂነር<br />

ኃይሉ ሻውል፣ ቡርቱካን ሚደቅሳ … ነው።<br />

በተቃዋሚዎች መንደር ምን<br />

እንደተወራ (አንዳንዴ ከተቃዋሚዎቹ አባላት<br />

እንኳን) ቀድሞ የመስማት ‹ችሎታ› አለው።<br />

የህብረተሰቡን የልብ ትርታ እና ፍላጎት<br />

ለመስማት ግን የወራትና የዓመታት እድሜ<br />

ያስቆጥራል።<br />

ይህም የሚያሳው፣ የመንበረ-<br />

ክብሩን ግርማ-ሞገስ ከህብረተሰቡ ፍላጎት<br />

አስበልጦ እና አስቀድሞ እንደሚያፈቅር ነው።<br />

በነገራችን ላይ፣ ይሄ አይነቱ ፀባይ የዚህ<br />

መንግሥት ብቻ አይደለም።<br />

ኃይለሥላሴ፡- የእኚህ ንጉሥ<br />

ሥርዓት እንደማንኛውም መንግሥት ትላልቅ<br />

ጆሮ ነበረው። ችግሩ፣ ሥርዓቱ አስቀድሞ<br />

ይሰማ የነበረው በወቅቱ ህዝቡ ያሰማ<br />

የነበረውን ብሶት አልነበረም።<br />

አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ውስጥ<br />

‹‹ክሮኮዳይልስ›› (አዞዎች) በመባል የሚታወቅ<br />

የተራማጅ ተማሪዎች ቡድን ነበር። ይህ<br />

ተራማጅ ቡድን በ1957 ‹‹መሬት ላራሹ<br />

ይሰጥ›› የሚል መፈክር ተሸክሞ ሰልፍ<br />

ወጣ። መፈክሩ ኢትዮጵያ ውስጥ ከተነሱት<br />

መፈክሮች ሁሉ አደገኛው ነበር። የአፄው<br />

ሥርዓት እንደአብዛኛዎቹ ሥርዓቶች ይሉኝታ<br />

17<br />

በቃልኪዳን ይበልጣል<br />

የሚያጠቃውና የተቃውሞ ድምጾችን የመታገስ<br />

ባህርይ ስላልነበረው ሰልፉ በፖሊስ ተበተነ።<br />

አ<strong>ስር</strong> ኪ. ሜ. መንገድ ለማሰራት<br />

የሚደክመው መንግሥት፣ ሰልፉን ለመበተን<br />

ግን እስከ አ<strong>ስር</strong> ሺህ የሚደርስ ጦር ሠራዊት<br />

ያሰልፋል።<br />

ደርግም፣ ሀገሪቱ ውስጥ ስንትና<br />

ስንት አንገብጋቢ ችግር እያለ፣ እሱ ግን<br />

ተንገብግቦ መላ የሚያበጀው፣ የኢሕአፓን<br />

የፖለቲካ እንቅስቀሴ ወገቡን ለመምታት<br />

ነበር።<br />

የኢህአፓ አባላት ማታ ቡና<br />

እስከስንተኛ ድረስ አንደጠጡ ሳያውቅ<br />

አይቀርም - ደርግ። ምክንያቱም ይቃወሙኛል<br />

ለሥልጣኔ መናጋት ምክንያት ይሆናሉ<br />

ብሎ የሚጠረጥራቸውን ሁሉ እግር በእግር<br />

እየተከተለ እግረ-ሙቅ የሚያጠልቅ ሥርዓት<br />

ነበር። እስራቱንና ጭቆናውን ለማፋፋም፣<br />

በእስራኤሎች የሠለጠነው ‹‹ነበልባል ቡድን››<br />

አዲስ አበባ እንዲመጣ በማድረግ፣ እንደ<br />

ውጫሌው ስምምነት (አንቀጽ አስራ ሰባት)<br />

አቋሙን በግድ ለመጋት ሞክሯል።<br />

ደርግ፣ አቋሙን እንደጣሊያኖች<br />

በአንቀጽ አይክፍለው እንጂ፣ በግልፅ ሲያራምድ<br />

የነበረው ፍላጎቱ፣ ከአንቀጽ አስራ ሰባት ጋር<br />

የጠበቀ መመሳሰል ነበረው።<br />

የአንቀጽ አስራ ሰባት አጭር<br />

ትርጉም፡- ሌሎችን ያለማዳመጥ እና የራስን<br />

ፍላጎት ብቻ መከተል ነው። የደርግም አንደዚያ<br />

ነበር - ሌሎችን ያለመስማት።<br />

አንቀፅ 17 የአድዋን ጦርነት ወለደ።<br />

የደርግ አንቀጽ አስራ ሰባታዊ አቋም (ሌሎችን<br />

ያለመስማት አቋም) የአስራ ሰባት ዓመታታ<br />

ኢህአዴግ የመናገር እንጂ ብዙም የማዳመጥ ልምድና ፍላጎት<br />

የለውም። በተቃራኒው ደግሞ፣ ሌሎች የእሱን ማስጠንቀቂያዎች<br />

የማዳመጥ ፍላጎት እና ልማድ እንዲኖራቸው ይፈልጋል። በዓለም<br />

ላይ ቀላሉ ነገር መናገር ሲሆን ከባዱ ደግሞ ማዳመጥ ነው።<br />

ለመናገር ለመናገርማ ወፈፌም ይናገራል<br />

ጦርነት ወልዶ ደርግን አስወገደ።<br />

ኢትዮጵያ፣ የተቃውሞ ድምጾችንና<br />

ሰልፎችን ፈጥነው የሚያደምጡ፣ የህዝቡን<br />

ችግር ደግሞ ቀ..ስ..ስ ብለው የሚሰሙ<br />

መንግሥታት የተፈራረቁባት ምስኪን <strong>አገር</strong><br />

ነች።<br />

የህዝብ እንባ ምናቸውም አይደል።<br />

‹‹ተቃዋሚዎችን እንዴት እናልፈስፍስ?››<br />

የሚል የአጎብጓቢዎች ጥያቄ ግን ‹‹ጥሩ›› ነው<br />

ለእነሱ። እንዲህ ዓይነቱ ጥያቄ ውሃና የፀሐይ<br />

ብርሃናቸው እንዲሁም ቫይታሚን ኤ፣ ቢ፣<br />

ሲያቸው ነው።<br />

ሥልጣናቸውን የሚያፋፉትና<br />

የሚያጠነክሩት ተቃዋሚዎችን በማቀጨጭ<br />

ነው።<br />

ኢህአዴግ የመናገር እንጂ ብዙም<br />

የማዳመጥ ልምድና ፍላጎት የለውም።<br />

በተቃራኒው ደግሞ፣ ሌሎች የእሱን<br />

ማስጠንቀቂያዎች የማዳመጥ ፍላጎት እና<br />

ልማድ እንዲኖራቸው ይፈልጋል።<br />

በዓለም ላይ ቀላሉ ነገር መናገር<br />

ሲሆን ከባዱ ደግሞ ማዳመጥ ነው። ለመናገር<br />

ለመናገርማ ወፈፌም ይናገራል። አንድ ሰው፣<br />

ሌሎች በአግባቡና በሙሉ ልብ እንዲያዳምጡት<br />

ከፈለገ፣ እሱም ለሌሎች ጆሮውን ወገግ አድርጎ<br />

መክፈት አለበት። የግትርነት አቋም መለኪያና<br />

ማሳያ እንዲሁም የራስ ወዳድነት ምልክት<br />

የሆነው አንቀፅ 17 ለማንም አይጠቅምም -<br />

በተለይ ለመንግሥት።<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

5


6<br />

ፀጥታ እንፈልጋን። እርጋታ<br />

እንፈልጋለን። ስክነት<br />

እንፈልጋለን። በጥቅሉ<br />

ሰላም እንፈልጋለን።<br />

ለመሆኑ አራቱ አጫጭር<br />

አረፍተ ነገሮች ባለቤት<br />

‹‹እኛ›› ማን ነን? እኔና<br />

መሰሎቼ። አረፍተ<br />

ነገሮቹን በዚህ መልኩ ማዋቀሬ ምስጢር<br />

ሲመረመር የሚጠቁመው፡- ሀ) እንደ<br />

በርካታ ቀሺም ፖለቲከኞች የራሴን እምነት<br />

ለማስረፅ ስለ ‹ሰፊው ህዝብ› በሚሏት<br />

ተወዳጅ ሀረግ ለመጠለል መምረጤን<br />

ነው፤ አሊያም ለ) ማንም ያልሰጠኝን<br />

ውክልና ተሸክሜ ለአካባቢዬ ለመቆርቆርና<br />

ለመሟገት ራሴን ማጨቴን ነው።<br />

አንድን ነገር ግን በእርግጠኝነት<br />

መናገር እችላለሁ። እንደ’ኔው በጩኸት<br />

መደንበር ያታከታቸው፣ በየደቂቃው<br />

መበርገግ ያንገሸገሻቸው፣ መዋከብና<br />

መደንገጥ ያማረራቸው፣ ከቤታቸው<br />

ወጥተው እስኪመለሱ በአደንቋሪ ድምጾችና<br />

የጆሮን ታምቡር ሊበጥሱ በሚንደረደሩ<br />

ሁከቶች ተሰንገው የሚሳቀቁ፣ በጥሞና<br />

መጓዝም ሆነ በፀጥታ መተኛት የናፈቃቸው<br />

ብጤዎቼ ጥቂት አይባሉም።<br />

‹‹እዚህ ከተማ ውስጥ የራሱ የሆነ<br />

የነጠረ ስብዕና ያለው ሰው ማግኘት አዳጋች<br />

ነው። አንዱ የአንዱ ፎቶ ኮፒ ለመሆን<br />

ነጋ ጠባ ይታትራል። ይሳካለትማል።<br />

በብልጭልጭ ህንፃ ካበደው ቅንጡ<br />

ሰፈር አንስተህ እስከጨርንቁሱ መንደር<br />

ብታስስ የሚገጥምህ የሰው አይነት ብዙ<br />

አይደለም። ሁሉም የጋራ አካፋዩን እየፈለገ<br />

ተቧድኗል። ድንገት ድንቅ ኃሳብ አፍልቀህ<br />

ተከታይህ ቢበራከት፣ አጀብህ አጀብ<br />

ቢያሰኝ ያጨበጨበልህ ሁሉ ገብተኸው<br />

እንዳይመስልህ። ከምንም በላይ ወረትና<br />

ጊዜያዊ ሆይ-ሆይታ ይማረኩናል። ከፍሬ<br />

ነገሩ በበለጠ አልባሱን ሙጥኝ እንላለን።<br />

ከምስሉ ጋር እንጣበቃለን። በመሆኑም<br />

በተደጋጋሚ በከንቱ እንለፈልፋለን።<br />

እንደናቆራለን።” እንዲህ ያለኝ አንድ<br />

ወዳጄ ነው። ከዓመታት በፊት ጩኸታሟ<br />

ከተማ ያደረሰችብኝን መንፈሳዊ እንግልት<br />

ተናዝዤ ዝምታዋን ብመኝ ግን ምኞቴን<br />

የሚጋሩ ብዙሃን ከተባለው በተለየ<br />

እውነተኛና ከተሞክሯቸው የሚመዘዝ<br />

ነጥብ እንደሚኖራቸው አይታበልም።<br />

ሰው ከጥንተ-ፍጥረት ጀምሮ<br />

ከአከባቢው ጋር ሲታገል ኖሯል።<br />

ተፈጥሮን ድል ነስቶ እንዳሻው ሊያሾራት<br />

ተወተርትሯል። ጢሻውን እየመነጠረ፣<br />

ጋራውን እያስገበረ፣ ጭንጫውን አያለሰለሰ፣<br />

ወንዞች ወደመረጠው ስፍራ እንዲፈሱ<br />

ቦይ እየቀየሰ፣ በተስማማው ቦታ ጎጆውን<br />

እየቀለሰ፣ ተከማችቶ እየሰፈረ፣ ከተሞች<br />

እየቆረቆረ ወደ ሥልጣኔ ተምዘግዝጓል።<br />

ዝርያው በዝቶ ተባዝቶ ምድርን ሲሞላ፣<br />

መፈናፈኛም ሲያጣ ዱርዱሩን እያፀዳ፣<br />

እንስሳቱን እያባረረ ግዛቱን አስፍቷል።<br />

ኑሮው ይቀልለትም ዘንድ መኖሪያውን<br />

ጭስ በሚተፉ ማሽኖች ሞልቷል። ግና<br />

ከማሽኖቹ ጋር የወደቀበት አቅል የሚያስት<br />

ፍቅር ልቡናውን ሰውሮበት በዋይታ<br />

የምታጣጥር መሬትን ዘነጋት። እንባዋ<br />

ጎርፍ፣ ስቅታዋ ናዳ፣ ኡኡታዋ ድርቅ<br />

ሆነው ሲወግሩት አይኑ መገለጥ ያዘ።<br />

እነሆም አረንጓዴው ዘመን ጠባ። ሁሉም<br />

በየአፉ አረንጓዴ ቃላትን ደሰኮረ። ከፋብሪካ<br />

ቡልቅ ቡልቅ እያለ እንደሚወጣ ጥቁር<br />

ጭስ፣ ወንዝ ውስጥ እንደሚጨመር<br />

እጣቢ ወይም ተረፈ-ምርት ሁሉ መኪኖቹ<br />

ማጉያዎቹ የሚያስፈተልኩት ልክ አልባ<br />

ድምፅ ከባቢን በክሎ ጤናን ያቃውሳል<br />

ተባል። የለም ዜጎች በሞላ ‹የምንኖርበት<br />

ቀየ እርጋታና ዝምታ ያሻዋል› እያሉ<br />

መወያየት ብሎም ለተግባር መሰለፍን<br />

ለመዱ። ይሄን ለመሰለው ‹ቅንጦት›<br />

ጊዜ የሌላት አዲስ አበባችን ግን ላንቃዋ<br />

እስኪተረተር መጮህን ልማድ አድርጋ<br />

ኖረች።<br />

በቅርቡ ሬዲዮ ስከታተል<br />

ባለቤቱና ርዕሱ ያመለጠኝ ጥናት ተጠቅሶ<br />

የከተማችን የድምፅ ልቀት መጠን አደኛ<br />

ደረጃ መድረሱን ሰማሁ። የጥናቱን ድጋፍ<br />

ባላገኝም ከሙዚቃ እስከ መዝሙር ቤት፣<br />

ከንግድ ትርኢት እስከ ግንዛቤ ማስጨበጫ<br />

ቅስቀሳ ረባሽ ኬረዳሽ ድለቃቸውን<br />

በየአጋጣሚው ይጋብዙኛልና እውነታውን<br />

አልስተውም። አሁን አሁን አሁን እየተገነቡ<br />

ያሉ የእግረኛ መንገዶች እንደተጠበቁ<br />

ሆነው በአብዛኛው የሸገር ጎዳናዎች<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />

ኮመንትሪ<br />

በጩኸት<br />

ውስጥ መኖር<br />

በቃልኪዳን ይበልጣል<br />

በእግር እየተጓዙ ዘና ማለት አይታሰብም።<br />

የመኪኖቹ ድንፋታ፣ የሸቃጮች የማያባራ<br />

ውትወታ፣ ከየመደብሩ በር ያለከልካይ<br />

የሚለቀቁ ዘፈኖች ዝብርቅርቅታ አናትን<br />

ቢያዞር እንጂ አያጠራም።<br />

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር<br />

ከሀገራችን አዋቂዎች 15% ያህሉ<br />

ለአዕምሮ መታወክ የተጋለጡ መሆናቸውን<br />

መግለፁንም ሰምቻለሁ - ቀደም ባለ ጊዜ።<br />

መቼም የዚህ ቁጥር አስደንጋጭነት<br />

ግልፅ ነው። ባልደረጃ አቅማችን፣ ባልጠና<br />

ጉልበታችን ስንቱን እክል እንችለዋለን?<br />

ይበልጥ የሚያስከፋው ደግሞ ነባራዊው<br />

እውነታችን ቁጥሩን ቁልቁል የሚያወርድ<br />

መላ አለመቋጠሩ ነው። ያለመግቻ ሽቅብ<br />

የሚመነደገው የዋጋ ንረት ለጭንቅላት<br />

የሚያተርፈው ከባድ ጭንቀት ራሱን ችሎ<br />

ህሊናን ቢያቃውስ አይደንቅም። ስራና ተስፋ<br />

ለአንድ ሀገር ውድቀትም<br />

ሆነ ዕድገት ተፅዕኖ<br />

ከሚያሳድሩ ምክንያቶች<br />

ዋና ዋናዎቹ የፖለቲካ፣<br />

የህዝብና የተፈጥሮ<br />

ኩነቶች ናቸው። እነዚህ<br />

ሦስት ጎራዎች በአሉታዊ መንገድ<br />

ሲቃኙ ሀገር ይጎዳል፤ ሀገር ይዳኸያል፣<br />

ይራቆታል። በተቃራኒው መንገድ<br />

ከላይ የጠቀስናቸው ምክንያቶች<br />

ወይም መንስኤዎች በአዎንታዊ<br />

መልኩ ሲጓዙ ሀገር ይለመልማል፣<br />

ይበለፅጋል፣ ያድጋል። ፖለቲካው<br />

ደግሞ ከዚህ ለየት ባለ መልኩ<br />

የተለየ የሰውን ልጅ የእለት ተዕለት<br />

ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ባህላዊ<br />

እንቅስቃሴዎችን በመቆጣጠር ቁልፍ<br />

ሚና ይጫወታል። ታዲያ በዙዎች<br />

የዓለማችን መሪዎች ተራቀውበት፣<br />

እንደ ልብ ተቀኝተውበት፣ ህዝቡንም<br />

ደስታ አጎናፅፈውት አንቱ አስብለው<br />

የሚያስኖሩትን ያክል፣ ብዙዎች<br />

የ3ኛው ዓለም ሀገራት፣ በተለይ<br />

የአፍሪካ መሪዎች፣ ፖለቲካን<br />

ሳያውቋት ምስጢሯን፣ ዓላማዋን፣<br />

ድርጊቷንና ግባቷን ሳይመረምሩት<br />

በግዴለሽነትና በማን-አለብኝነት<br />

እብሪትነት ሲሸልሉበት፣ ሲዘሉበት<br />

ኖረዋል። አሁንም እየኖሩ ያሉ አሉ።<br />

የምዕራቡ ዓለም<br />

ለዕድገታቸው ዋናው ተጠቃሽ<br />

ምክንያት ሁልጊዜም እንደምንለው<br />

መልካም የፖለቲካ አስተዳደር<br />

(Good Governance) ስላላቸው<br />

ነው። ፌዴራሊዝምም ይሁን<br />

ሴንትራሊዝም፣ ፖርሊያመንታሪም<br />

ይሁን ፕሬዝዳንታዊል፣ ኒዮ-<br />

ሊሊበራልም ይከተሉ ሊበራል ብቻ<br />

በየትኛውም በተከሉት የፖለቲካ<br />

ጥርጊያ ለመረጣቸው ህዝብ አሻራ<br />

ለቃል ለማተባቸው ታማኝና አገልጋይ<br />

ወጥ አቋም ነው ያላቸው።<br />

ወደ እኛው አህጉር አፍሪካና<br />

በተለይ ደግሞ በእኛዋ ኢትዮጵያ<br />

‹‹እዚህ ከተማ ውስጥ የራሱ የሆነ የነጠረ ስብዕና ያለው ሰው ማግኘት አዳጋች ነው። አንዱ የአንዱ ፎቶ ኮፒ ለመሆን<br />

ነጋ ጠባ ይታትራል። ይሳካለትማል። በብልጭልጭ ህንፃ ካበደው ቅንጡ ሰፈር አንስተህ እስከጨርንቁሱ መንደር ብታስስ<br />

የሚገጥምህ የሰው አይነት ብዙ አይደለም። ሁሉም የጋራ አካፋዩን እየፈለገ ተቧድኗል። ድንገት ድንቅ ኃሳብ አፍልቀህ<br />

ተከታይህ ቢበራከት፣ አጀብህ አጀብ ቢያሰኝ ያጨበጨበልህ ሁሉ ገብተኸው እንዳይመስልህ<br />

ከሥንታየሁ ዓለማየሁ<br />

[sent_maki@yahoo.com]<br />

ካጡ ወጣቶች አንስቶ እስከተደላደለው<br />

አባወራ ድረስ የሚናውዙበት የጫትና<br />

የሺሳ ሱስ ጠብታዋን የቀውስ ፍንጭ ባህር<br />

እስክታክል ሊያሰፋት ይቻለዋል። እጅግ<br />

አናሳው የጤና ሸፋናችን ደግሞ መውጫ<br />

ቀዳዳ እንዳይታለም ተስፋን ያጨልማል።<br />

አስቡት እስኪ - ከብዙ ህዝቦቿ መካከል<br />

ብዙዎች እርዳታ ያሻቸዋል እየተባለ ያለባት<br />

ሀገር ያዘጋጀችው የአዕምሮ ህመምተኞች<br />

ሆስፒታል አንድ ነው። ለድንጉጥነት፣<br />

ለስሜት ነውጥና ለእንቅልፍ እጦት<br />

በመዳረግ ለአዕምሮ ህመም መንገድ<br />

እንደሚጠርግ የሚታመነው የድምፅ<br />

ብክለትስ?<br />

የወቅቱን የወግ ሞቅታ ተከትሎ<br />

ከማራገብና ከልብ ጠብ የማይሉ ልፍስፍስ<br />

ማስታወቂያዎችን በለሆሳስ ከማስነገር<br />

በዘለለ ጠንካራ እርምጃዎች የሚፈልጉ<br />

የፖለቲካውን እንቅስቃሴ ስንቃኝ<br />

በእውነት መንግሥት ለራሱ ህልውና<br />

እንጂ ለህዝብ ብሎ የሚሰራው ነገር ያለ<br />

አይመስልም። ለዚህ ፅሁፍ መነሻ የሆነኝ<br />

ባላፈው ሳምንት ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ<br />

በፓርላማ ያደረጉት ንግግር ነው።<br />

ጠ/ሚኒስትሩ በተለያዩ<br />

ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ<br />

አጀንዳዎች ላይ ማብራሪያ በሰጡበት<br />

ወቅት በጣም ያሳዘነኝ ነገር ቢኖር<br />

አሉታዊ ሀሳብ የተነሳባቸው አጀንዳዎች<br />

ላይ ምላሽ ሲሰጡ በጋለና በደም<br />

ፍላት ስሜት ሌቦች፣ የቁራ ጩኸት፣<br />

ሀሁ ያልገባቸው የሚሉ ቃላትን<br />

መጠቀማቸው ነው። አንድ መንግስት<br />

በተለይ ደግሞ ዴሞክራሲያዊ ነኝ ለሚል<br />

መንግስት ለህዝብ ስራውን ሊያቀርብ፣<br />

ሊጠየቅና ሊመረመር ይገባዋል እንጂ<br />

እራሱ ሰብስቦ እኔ የምለውን ብቻ<br />

ስሙኝ፣ የእናንተ አስተያየትና ሀሳብ<br />

ከንቱ ነው አይነት እሳቤ፣ ለምን እንዲህ<br />

አልሆነም ሲባል ሀሁ አልገባችሁም፣<br />

እንደ ቁራ አትጩሁ፣ አጭበርባሪ . .<br />

. በማለት በመድብለ ፓርቲ ተሳትፎ<br />

አምናለሁ ከሚል መንግስት አንዱ<br />

ብቻ ሲፈነጭበት፣ ስራውን እራሱ<br />

ይመስለኛል። ‹‹መልሶ ግንባታ››፣<br />

‹‹እድሳት››፣ ‹‹ማስፋፋት››፣ ‹‹አዳዲስ<br />

ግንባታዎች›› እና የመሳሰሉ ከአዲስ አበባ<br />

ጋር ተያይዘው የሚነሱ ቃላትና ሀረጎች<br />

ከተማዋ ያለችበትን ሁኔታ በጨረፍታም<br />

ቢሆን ይጠቁማሉ። በብዙ አቅጣጫዎች<br />

ዘመናዊ ከተማ ለመሆን በደፋ ቀና<br />

ተወጥራለች። የመዘናዊነት መለኪያው<br />

ምንድን ነው ወደሚለው ክርክር ሳንገባ<br />

ለመኖር የምታመች ከተማ ትሆን ዘንድ<br />

ግን እንፈልጋን። ትርጉም አልባና ቅጥ-<br />

የለሽ የድምፅ ልቀት ምቾት ይነሳልና<br />

ደንበኛ ስሬትና ልኬት በጅቶ ፋታ ብናገኝ<br />

አንጠላም።<br />

እውነት እውነት እላችኋለሁ<br />

በጩኸት ውስጥ መኖር እጅጉን<br />

ያስጨንቃል።<br />

መንግሥት እራሱ<br />

ጠ/ሚኒስትሩ በተለያዩ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ አጀንዳዎች<br />

ላይ ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት በጣም ያሳዘነኝ ነገር ቢኖር አሉታዊ ሀሳብ<br />

የተነሳባቸው አጀንዳዎች ላይ ምላሽ ሲሰጡ በጋለና በደም ፍላት ስሜት ሌቦች፣<br />

የቁራ ጩኸት፣ ሀሁ ያልገባቸው የሚሉ ቃላትን መጠቀማቸው ነው<br />

ሰርቶ እራሱ ብቻ የሚያወድስበት፣<br />

ስህተቱን የማያይበት ከሆነ፣ እውነት<br />

ይህ አይነቱ መንግሥት ለራሱ እሱስ<br />

ቢሆን የአስተዳደር ሀሁ ገብቶታል ወይ<br />

ያስብላል።<br />

ጠ/ሚ መለስ በተለያዩ ጉዳዮች<br />

ላይ እንደተነተኑት፣ ንግግራቸውን<br />

ሲጀምሩ፣ ለመንፏቀቅ ያሰበ መንግስት<br />

ተንፏቋልና በመንፏቀቁ ሊመሰገን<br />

አይገባም፤ ይልቁንስ በፍጥነት<br />

ለመራመድ አስቦ የተራመደን<br />

እናመሰግናለን። እኛም በፍጥነት<br />

ለመራመድ አስበን ተራምደናል ነው<br />

አገላለፁ። መንግስት ከአዲስ አበባ እስከ<br />

ጅቡቲ መንገድ ስራ እንደሚያጠናቀቅ፣<br />

ከ8000-10,000 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ<br />

ኃይል እንደሚያመነጭ፣ ከዚህም<br />

5ሺህ 500 አካባቢው ከአባይ ግድብ<br />

እንደሚገኝ ሲገልፁ ባያልቅም ጅምሩ<br />

ተስፋ ሰጪ ይመስላል። በንግዱ ዘርፍ<br />

ደግሞ የጅመላ ንግዱ ዘርፍ ተወዳዳሪ<br />

የሌለበት ስለሆነ የውጭ ኩባንያዎችን<br />

በማስገባት ተዋናዮችን እንፈጥራለን<br />

ብለዋል። እዚሁ ላይ ከአሁን በፊት<br />

ከIMF ጋር በፈጠሩት ያለመግባባት ሳቢያ<br />

ነው የውጭ ኩባንያዎችን ማስገባት


አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />

እና<br />

የማቃለል ዘመን<br />

መጣ! የመቅለል እና<br />

የመቃለል ዘመንም<br />

ተከተለው።›› ይህችን<br />

መሪ መግቢያ<br />

ከወዳጄ ይስማዕከ<br />

‹‹የማቅለል<br />

ወርቁ ሶስተኛ ልብ<br />

ወለድ ወሰድኳት - ዛሬ ስለሶስት ገጽ<br />

መጻፍ መፈለጌን አስረግጥባት ዘንድ።<br />

አምላካችን ካደለን ጸጋ የተነሳ አሁንም<br />

ድረስ በምሕረቱ እና በበጎነቱ እንጠበቃለን።<br />

አሜን!!!<br />

እስትንፋሳችን ነውና ዛሬም እንጽፋለን።<br />

ለመሆኑ ለምንድን ነው የምንጽፈው?<br />

ሕገመንግሥቱ የሰጠን መብት ስለሆነ<br />

እንጽፋለን። ወይም አብጦና ጎርብጦ<br />

አልመቸን ያለ ነግር ሲኖርብን እንጽፍና<br />

እንተነፍሳለን። ወይም መጻፍ ሙያችን፣<br />

እንጀራችን ስለሆነ እንጽፋለን። እውነት<br />

እውነት እላችኋለሁ ከዚህ የተለየ አጀንዳም<br />

የለን። ያላቸው እንኳ ቢኖሩ እንደ ቡርቃ<br />

ዝምታ ደራሲ ስደት የእጃቸው እንደሚሆን<br />

አናጣውምና በሰብዓዊ ፍጡር እቃቃ<br />

ለመጫወት ብርቱም፣ ንቁም አንሆንም።<br />

አንድ ገጽ<br />

ኢትዮጵያ ሀገራችን ከሰለጠኑ ሀገራት<br />

እኩል የሰለጠነች ትሆን ዘንድ ይመኛሉ።<br />

የትምህርት አለመስፋፋት፣ የመሃይምነት<br />

መንገሥ ያስቆጫቸዋል። የፍትሕ<br />

መጓደል፣ የታናሽ መበደል፣ የንጹህ<br />

መገደል ያበሳጫቸዋል።<br />

ወገባቸውን በብርቱ ድግ አደግድገው ደፋ<br />

ቀና ይላሉ። ሀገራችውን ትሰለጥናለች<br />

ብለው ባሰቡበት መንገድ ሁሉ ያታትራሉ።<br />

የዘመን መምጣትና መሄድ፣ አለዚያም<br />

የግለሰብ መውጣትና መውረድ አይደለም<br />

የሚያሳስባቸው። የፍትሕ፣ የዴሞክራሲ፣<br />

የልማት፣ የሥልጣኔ በሀገሪቱ መስፈን<br />

ነው ጮቤ የሚያስረግጣቸው።<br />

ከድሃው ጋር ያለቅሳሉ። ከበላው ጋር<br />

ይስቃሉ። ከጭቁኑ ጋር ይታገላሉ። ነፃ<br />

ከወጣው ጋር ሻማ ይለኩሳሉ። ሁሉን<br />

በልኩ ያውቃሉ። ሁሉንም በየመጠኑ<br />

ይገነዘባሉ።<br />

በደሳለኝ ሥዩም<br />

3ኮመንትሪ<br />

ገጽ<br />

ስለገንዘብ ደንታ የላቸውም። ስለሥልጣን<br />

አይገዳቸውም። ስለኃብት አያሳስባቸውም።<br />

የማሳው በአዝርዕት መሸፈን፣ የሰብሉ አብቦ<br />

ማፍራት፣ የከብቶች ምቾት፣ የሜዳው<br />

መልካም ገጽ፣ የተራሮችን መዓዛ ቁርስ<br />

እና ምሳቸው አድርገው ያስቡታል።<br />

ኢትዮጵያ ተደፈረች ከተባለ ያለማንም<br />

ቀስቃሽ በቀረርቶና በሽለላ ኮራ እንዳሉ<br />

ከፊት ይሰለፋሉ። ጠመንጃ አንግተው<br />

ድንበር ያስከብራሉ። ሰንደቅ አላማዋን<br />

ሲያዩ በእንባ ይታጠባሉ።<br />

እኒህን የመሰሉ ዜጎች ባለፉት ጊዜያትና<br />

መንግሥታት አይተናል። በኖርንበት<br />

ዕድሜም ሁሉ አስተውለናል። ለሀገራቸው<br />

ፋይዳ ካልኖረው የማይማሩ፣ ለወገናቸው<br />

ካልጠቀመ ኃብት የማያከማቹ፣ በሁሉም<br />

ነገራቸው ሀገር እና ወገን ይቅደም ያሉ<br />

ምሁራን፣ ሠራተኞች፣ ነጋዴዎች፣ የኪነ-<br />

ጥበብ ባለሙያዎች፣ ወታደሮች፣ የልዩ<br />

ልዩ ሙያ ባለቤቶችን ይህች ሀገር ባለፉት<br />

ዘመን ሁሉ አፍርታለች። ባለንበትም<br />

ዘመን ሁሉ ታፈራለች።<br />

ሁለት ገጽ<br />

የሚምጉት አየር ደንታ የማይሰጣቸው፤<br />

የቆሙበት ምድር ምንማቸው የሆነ፤<br />

ወጥተው ለሚገቡበት ጎዳና ደንታ ቢስ<br />

የሆኑ እንዴት ናችሁ ለሚላቸው ሕዝብ<br />

ከበሬታ የማይሰጡ።<br />

የዘመናት መለወጥ፣ የመንግሥታት<br />

መገለባበጥ፣ የሰላም መደፍረስ፣ የጦርነት<br />

መቀስቀስ ስሜት የማይሰጣቸው፣<br />

የበሽታ ወረርሽኝ፣ የርሃብና የጎርፍ<br />

አደጋ፤ የድርቅና ድንገተኛ ቀውስ ሁሉ<br />

ትኩረታቸውን የማይስበው።<br />

ያገኙትን በልተው፣ ያሻቸውን ጠጥተው<br />

ካሰኛቸው ጋር አንሶላ ተጋፈው ጨለማው<br />

ነግቶ የነጋው ጨልሞ ለመፈራረቅ ይብቃ<br />

እንጂ ከዚህ በላይ ኑሮ የማይመቻቸው፤<br />

ከዚህ ወዲያ ኑሮ የማይታያቸው<br />

ከንቱዎችን ይህች ሀገር ትናንትም ዛሬም<br />

አፍርታለች።<br />

መኖር አይቆምምና ወደፊትም እነዚህ<br />

ግራ የገባቸው የትውልድ ‹‹ቀዝቃዛዎች››<br />

መፈልፈላቸው አይቀርም። ዜጎች ለሀገራዊ<br />

ዘመቻ ደፋ ቀና ሲሉ ኬሻ ሙሉ ጫት<br />

ዘርግፈው ላባቸውን በመሀረብ እየጠራረጉ<br />

ያመነዥካሉ። ሀገሪቱን ለማሳደግ<br />

ዜጎች በየእውቀታቸው፣ በየሙያቸው፣<br />

በየቦታቸው ሲረባረቡ ጆሮን የሚበጥስ<br />

ሙዚቃ አስከፍተው ለአይን እንዲያሳሱ<br />

ከተኳኳሉ እንስቶች ጋር በሀሽሽ ጥምብዝ<br />

ይላሉ። ከዚህ የዳንኪራ ቤታቸው ውጭ<br />

ያለው ሀገርና ህዝብ ለነሱ ምንም ነው።<br />

ለእያንዳንዱ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣<br />

ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ፖለቲካዊ ጉዳይ<br />

የአስተዳደር ሀሁ አልገባውም<br />

የተፈለገው ወይስ እውነት ገበያውን<br />

ለማረጋጋትና ከህዝቡ ጋር ለመታረቅ?<br />

የሀገርን የኢኮኖሚ ደረጃና የህዝብን ኑሮ<br />

ለማሻሻል ግን እንደ እኔ የራሱን ሀገር<br />

ስራ ፈጣሪና ነጋዴ ማብዛትና መፍጠር<br />

የማያወላውል እርምጃ ይመስለኛል።<br />

ነገር ግን ከአለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር<br />

ለመታረቅ ሲባል እውነተኛውን ገሃድ<br />

የውስጥ ሀቃችንን አጣልተን መሆን<br />

የለበትም ባይ ነኝ።<br />

ክቡር ጠ/ሚኒስትሩ የንግድ<br />

ዘርፎችንና የመሬት አስተዳደርን<br />

ዘመናዊ እናደርጋለን ብለው ወዲህ<br />

ደግሞ ስለ ግብር ክፍያ <strong>ስር</strong>ዓት ሲጠየቁ<br />

ወይም ሲገመገሙ ‹‹አብዛኛው ነጋዴ<br />

እስከዛሬ ድረስ ሲከፍለው የኖረው<br />

መክፈል ከሚገባው በታች ነው። ይሁን<br />

እንጂ አሁን ግን መክፈል የሚባለውን<br />

ክፈል ሲባል አልከፍልም ማለቱ ነገሩ<br />

አወዛጋቢ አድርጎታል። አንዳንዱ ደግሞ<br />

መክፈል ከሚገባው በታች እየከፈለ<br />

በሙስና ኖሯል። በስነ-ምግባር ጉዳይም<br />

ችግር አለ፤ አስከፋዩ እራሱ ሌላ ነው፤<br />

ሌብነት አለ፤ ሌቦች እንደሆኑ እያወቅን<br />

ማስረጃ ስላጣን ግን ዝም ብለናቸው<br />

ኖረናል›› በማለት በራሱ የሚምታታ<br />

ሃሳብ ገልፀዋል። በመጀመሪያ ደረጃ<br />

ማስረጃ ከሌላቸው ሌቦች ለመሆናቸው<br />

ምን ማረጋገጫ አላቸው? ማስረጃ<br />

ይቀድማል ወይስ ማወቅ? ስለኑሮ<br />

ውድነትና ዕድገት ሲወራም በየትኛው<br />

የኢኮኖሚክስ ህግ እንደሆነ እንኳን<br />

ማጣቀሻ ሳይሰጡ ሀገር ሲያድግ የኑሮ<br />

ችግር ሊጠፋ አይችልም›› ብለው ተስፋ<br />

አስቆርጠውናል።<br />

እንደሚባኝ፣ ዘመናዊው የአንድ<br />

ሀገር የዕድገት መለኪያ (development<br />

measurement) እንደ ድሮው በGNP፣<br />

GDP፣ PCI በመሳሰሉት አይደለም።<br />

ይልቁንስ እነዚህ ባህላዊ መለኪያዎች<br />

ከሆኑ ሰነባበቱ። ነገር ግን ዘመናዊው<br />

መለኪያ የህዝቡ የኑሮ ደረጃና ብቃት<br />

ታይቶ ሲሆን፣ ይህም ሲባል በጤና፣<br />

በኢኮኖሚና እንዲሁም በማህበራዊ<br />

እንደ ትምህርት ጥራት የመሳሰሉትን<br />

በመገምገም ትክክለኛውን የህብረተሰቡን<br />

ህይወት በማየት የሚወሰን ነው።<br />

በመግለጫውም ላይ አላደግንም ለሚሉ<br />

አለማወቅ ነው ሲሉ መፍትሄ ብለው<br />

ያስቀሙጠት ደግሞ ይህን አለማወቅ<br />

ማስወገደ ነው የሚለውን ነው።<br />

ታላቁ ሶቅራጠስ፣ ‹‹አለማወቅን<br />

ማወቅ የእውቀት መጀመሪያ ነው››<br />

ብሎ ተናግሮ ነበር። ታዲያ ኢህአዴግ<br />

አሁን አለማወቅን ካለማወቁ ጭምር<br />

ይባስ ብሎ እሱ ያላወቀውን እውቀት<br />

ሳናውቅ እንድናውቅ በግድ ይገፋፋናል።<br />

እንደ’ኔ እምነት፣ በዚህ ጠ/ሚኒስትሩ<br />

ባቀረቡት ሪፖርት ላይ ኢህአዴግ<br />

አመርቂ ውጤት ያስመዘገበው ነገር<br />

ቢኖር የፀረ-ሽብርተኝነት ሕግ በማፅደቅና<br />

ሽብርተኞችን አሳዶ በመያዝ ሲሆን፣<br />

አሁንም በቅርብ ሳምንታት ውስጥ ወደ<br />

‹‹አለማወቅን ማወቅ የእውቀት መጀመሪያ ነው›› ብሎ ተናግሮ ነበር። ታዲያ<br />

ኢህአዴግ አሁን አለማወቅን ካለማወቁ ጭምር ይባስ ብሎ እሱ ያላወቀውን እውቀት<br />

ሳናውቅ እንድናውቅ በግድ ይገፋፋናል። እንደ’ኔ እምነት፣ በዚህ ጠ/ሚኒስትሩ ባቀረቡት<br />

ሪፖርት ላይ ኢህአዴግ አመርቂ ውጤት ያስመዘገበው ነገር ቢኖር የፀረ-ሽብርተኝነት ሕግ<br />

በማፅደቅና ሽብርተኞችን አሳዶ በመያዝ ሲሆን፣ አሁንም በቅርብ ሳምንታት ውስጥ ወደ ቃሊቲ<br />

የሚወረወሩ እንዳሉ ታገሱን ብለው እንድንጠባበቅ ነግረውናል።<br />

የሚቆርጡት ጮማ፣ የሚያንቆረቁሩት ውስኪ፣ የሚያሽከረክሩት መኪናና የሚሽከረከሩበት ወንበር ከእጃቸው<br />

እንዳይወጣ በ‹‹ለምን›› ባዮች ላይ የድንጋይ ናዳ የሚያወርዱ። ይህች ሀገር እኒህን የመሰሉ ዜጎችን ባለፉት<br />

ጊዜያትና መንግሥታት አፍርታ ታይታለች። በኖርንበትና ባለንት ዘመንም ይህ እውነታ ቀጥሏል።<br />

ቃሊቲ የሚወረወሩ እንዳሉ ታገሱን<br />

ብለው እንድንጠባበቅ ነግረውናል።<br />

የጋዜጠኝነት ሀሁ<br />

ያልገባቸው ባሉበት ወቅት<br />

ስለእውነት አፍሪካዊነቴን ጠላሁ።<br />

እነሆ በሰለጠኑት እንደ አሜሪካና<br />

እንግሊዝ ባሉት አይደለም፣ በሀገር<br />

ደረጃ ጠቅላላ ሕግ ይስተካከል ብሎ<br />

ለሚናገር ጋዜጠኛ፣ በግለሰብ ስም<br />

ጠርቶ ለሚሳደብና ለሚያንቋሽሽ<br />

ሰው እንኳን እ<strong>ስር</strong>ና እንግልት<br />

አይደርስበትም። ምክንያቱም ህዝብ<br />

የመሰለውን፣ የሚበጀውን እራሱ<br />

በገሀድ በመሬት ላይ ያለውን ፖለቲካ<br />

ስለሚያውቀው ከአንድ ግለሰብና<br />

ጋዜጠኛ እንዲሁም የፖለቲካ<br />

ፓርቲ ጋር እሰጣ’ገባ አይገባም፣<br />

አያሳድድም። ይልቁንስ ለእነሱ ይህ<br />

ጊዜን ማባከን ነው።<br />

በአጠቃላይ፣ ይህ ሁሉ<br />

እንቅስቃሴ የሚያሳየን መንግስት<br />

እራሱን ከመጠበቅ ባለፈ እውነትን<br />

ከመክደን በዘለለ ትልቅ ስራ<br />

እንደሌለው ነው። ይህም ሲባል<br />

ከሌሎች የሥራ ዘርፎች ይልቅ የፀረ-<br />

ሽብርተኝነት እንቅስቃሴው እራሱን<br />

የቻለ ቦርድ አቋቁሞ ለዛውም ምርጥ<br />

ከተባሉት ከነእንግሊዝ ሕጉን ኮፒ<br />

አድርገው ሲንቀሳቀሱ ሲታይ ምን<br />

ያህል አንገብጋቢ ሥራ እንደነበረበት<br />

ያሳያል። ምናለ እንደው ለሌላው<br />

እውነተኛ የኑሮ ውጥንቅጣችን<br />

እንዲህ ምርጥ ከሚባለው ሀገር<br />

ፖሊሲ ኮፒ ቢያደርጉልን!<br />

አለበለዚያ አንገብጋቢውን ትተው፣<br />

ለፍርሀታቸው የሚሰሩ ከሆነ፣<br />

እኛ ሳንሆን እነርሱ ናቸው ሀሁው<br />

ያልገባቸው።<br />

ሁሉ ግድ የለሽና ባዕድ ናቸው። ምንም<br />

አይሞቃቸው፣ ምንምም አይበርዳቸው።<br />

እነዚሀ ሁለተኛ የዜጎች ገጽታ መሆናቸው<br />

ነው።<br />

ሶስት ገጽ<br />

የሰዎችን ደም በጽዋ እየተቀባበሉ<br />

መጎንጨት የሚዳዳቸው፤ በጎ ነገር ለሀገር፣<br />

ለህዝብ ስለተሰራ ብቻ የሚያማቸው፤<br />

መልካም ሰውን አጋድመው ካልገፈፉ<br />

በስተቀር ሰላም የማይሰማቸው።<br />

የተባረኩት የተከሉትን ችግኝ ከጫፉ<br />

ቀንጥሰው መጣል የእርካታቸው ምንጭ<br />

የሆነ፤ በለመለመ መስክ ላይ ቤንዚን<br />

ማርከፍከፍ ውዴታቸው የሆነ። የተማሩ<br />

ሰዎችን ሲያዩ የሚነስራቸው። የምሁራንን<br />

ሐሳብ ማዳመጥ ውድቀት የሚመስላቸው<br />

ዜጎች።<br />

ክርስቶስ እንዲሰቀል በርባን ግን እንዲፈታ<br />

ከመጮኽ አልፈው ሐሳባችንን ደግፉ፣<br />

አብራችሁ ጩኹ፤ ካልጮኻችሁ<br />

እንገድላችኋለን ብለው አንባጓሮ ሚያነሱ፤<br />

አዎንታዊ ሐሳብ በአእምሯቸው ታስቧቸው<br />

የማያውቅ፤ የራበው ድሃ አስፓልት ዳር<br />

ወድቆ ሲቆራመድ አጥንቱን እየቆጠሩ<br />

ፈገግ የሚሉ።<br />

የሚቆርጡት ጮማ፣ የሚያንቆረቁሩት<br />

ውስኪ፣ የሚያሽከረክሩት መኪናና<br />

የሚሽከረከሩበት ወንበር ከእጃቸው<br />

እንዳይወጣ በ‹‹ለምን›› ባዮች ላይ የድንጋይ<br />

ናዳ የሚያወርዱ።<br />

ይህች ሀገር እኒህን የመሰሉ ዜጎችን<br />

ባለፉት ጊዜያትና መንግሥታት አፍርታ<br />

ታይታለች። በኖርንበትና ባለንት ዘመንም<br />

ይህ እውነታ ቀጥሏል። የሚያብለጨልጭ<br />

ብረት ከሰው ላይ ለመውሰድ ጣትን<br />

ወይም አንገትን ቆርጠው በኪሳቸው<br />

የሚደብቁ፤ ሥልጣኔን መናፈቅ፣<br />

ዴሞክራሲን መስበክ፣ ልማትን ማምጣት<br />

ለምላሳቸው እንጂ ለጭንቅላታቸው ሥራ<br />

ያልሆነላቸው። እኒህ ሶስተኛ ገጽ ዜጎች<br />

መሆናቸው ነው።<br />

ለእነዚህ ማሳያ የሚሆኑት ደግሞ ሁሌም<br />

አዲስ የመከራ ዘመን በሚያበስረው አዲስ<br />

ዘመን ጋዜጣ ላይ የነገሱት ናቸው።<br />

የብዕር አጣጣሉ ሁሌም አንድ ነው።<br />

እገሌ ከ --- (ቦታ) እየተባለ ሥም<br />

ይሰጠው እንጂ ሀሳብን ሳይሆን የፖለቲካ<br />

ትንታኔን፣ የውሳኔ ሀሳብን፣ የመረረ<br />

ጥላቻን የሚያራምድ አንድ መደበኛ<br />

ግለሰብ እንደሚጽፈው ለሚያነቡ ሁሉ<br />

የሚሰወር እውነታ አይደለም።<br />

ብዙ ጊዜ ስድብ ይጻፍበታል። ግለሰቦችና<br />

የግል ሚዲያዎች ይዘለፉበታል - የአዲስ<br />

ዘመኑ ገጽ ሶስት። ካልታሰሩ፣ ካልተዘጉ<br />

ሞቼ እገኛለሁ ይባልበታል። ስለዴሞክራሲ<br />

በሚወራበት ሀገር በአንድ ሰላማዊ<br />

ዜጋ ‹‹ሥም›› እየተጻፈ ግለሰቦች ክፉኛ<br />

ይኮነኑበታል።<br />

አዲስ ዘመን በመሰረቱ ገጽ ሶስትን<br />

እንደተባለው ለተለያዩ ሐሳቦች<br />

ማንሸራሸሪያነት እያዋለው እንዳልሆነ<br />

ይታወቃል። ግን እስኪ የመንግሥትን፣<br />

የፖሊስን፣ የፍርድ ቤትን፣ የይቅርታ<br />

ቦርድን ወዘተ. ኃላፊነትና ሥልጣን ትቶ<br />

ወይም ጣልቃ ገብቶ የሚፈተፍት ጽሑፍ<br />

ማስተናገድ ጋዜጣውን እንደሚያስንቀው<br />

አጥተውት ነው? ሌላው ሁሉ ቀርቶ<br />

ማለቴ ነው።<br />

ይሄኔ የአዲስ ዘመን ቅርጫት ቢፈተሸ<br />

ስለእያንዳንዱ ስድባቸው እንደናቋቸው<br />

የሚገልጹ የብዙ አንባቢዎች የቅሬታና<br />

የቁጣ ደብዳቤ ብዛት ምን ያህል ይሆን?<br />

እስቲ በ’ኔ ሞት የመቀመጫዋን ጉድ<br />

ያላስተዋለች ዝንጀሮ ምሳሌ ከአዲስ ዘመን<br />

ውጭ ለሌላ የሚጠቀስ ምሳሌ መሆን<br />

ነበረበት?<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

7


8<br />

አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />

የአንበሳ አውቶቡስ ጉዞ እና ገጠመኞች<br />

በናፍቆት ዮሴፍ<br />

“ሰፈሬ ሽሮ ሜዳ እንደመሆኑ ከመርካቶ<br />

17 ቁጥር አውቶቡስን ተሳፍሬ<br />

ቅድስት ማሪያም ቤ/ክ ስንደርስ፣ አንድ<br />

አዛውንት ኡኡታ አሰሙ ‹አውቶቡሱ<br />

ሳይከፈት ወደ ፖሊስ ጣቢያ ይሂድልኝ›<br />

ሲሉ ሹፌሩን ተማጠኑ፤ ሶስት ሺህ ብር<br />

ተወስዶብኛል በሚል። ሹፌሩም አራት<br />

ኪሎ አካባቢ (አሁን ፈርሷል) ፖሊስ<br />

ጣቢያ አውቶቡሱን ይዘው ገቡ። ሁሉም<br />

ሰው እንዲወርድ ተደረገ። ምን ዋጋ<br />

አለው ሌባው ቀድሞ ወርዶስ ቢሆንስ<br />

እያልን ወረድን<br />

“የሆነ ሆኖ ሁሉም ሰው ወርዶ እንዲፈተሽ በአንድ<br />

መቶ አለቃ ትዕዛዝ ከተላለፈ ከደቂቃዎች በኋላ<br />

መቶ አለቃው ‹ሌባው ስለተገኘ ፍትሻውን አቁሙ›<br />

ሲል ለባልደረቦቹ ትዕዛዝ አስተላለፈ። እጅግ መልከ<br />

መልካም፣ አራቱም ጣቶቿ ላይ ወርቅ የደረደረች፣<br />

አለባበሷ በእጅጉ የተዋበ ወጣት ላይ የመቶ አለቃው<br />

አይን አረፈ።<br />

“የወሰድሽውን ብር አምጪ” ብሎ ሲያምባርቅባት<br />

የሁላችንም እጢ ዱብ አለ። “የምን ብር!? የሰውን<br />

ማንነት ሳታውቅ አትናገር” ስትል ኮስተር ያለ መልስ<br />

ሰነዘረች ወጣቷ። ይሁን እንጂ መቶ አለቃው፣<br />

“ገብተሽ በጉማሬ አለንጋ ስትሞሸለቂ ታወጪ የለ?”<br />

በማለት እየጎተተ ወሰዳት።<br />

17 ቁጥር አውቶቡስ እና እኛ ተሳፋሪዎች ፖሊስ<br />

ጣቢያው ውስጥ እንደተገተርን ደቂቃዎች፣ ብሎም<br />

ሰዓታት አለፉ። ብዙ እናቶችና አባቶች፣ “ፍፁም<br />

አታደርገውም፤ ለሌላ ጉዳይ ፈልጓት ይሆናል” ሲሉ<br />

አጉተመተሙ። ልጅቷ ጠንከር ያለ አለንጋ ሳትቀምስ<br />

አልቀረችም፣ “እሺ ተወኝ፤ የደበቅሁበትን ላሳይህ”<br />

ስትል መሬት ተሰንጥቃ ብትውጠኝ ደስተኛ ነበርኩ።<br />

በርካታው የአውቶቡሷ ተሳፋሪዎች የሚሆነውን<br />

ለማየት አሰፈሰፍን። ልጅቷም ፖሊሱን እየመራች<br />

የአውቶቡሷ መጨረሻ ወንበር ወደሚገኝበት ሄደች።<br />

ሁሉም ይህን ጉድ ለማየት አሰፈሰፉ። የመጨረሻው<br />

ወንበር ስትደርስ ሶስት ሺህ ብር ሶስት ቦታ በብር<br />

ላስቲክ የታሰረ ስለነበር ከዛን በፊት አይቼው<br />

በማላውቀው አይነት ወፍራም ፕላስተር ከወንበሩ<br />

<strong>ስር</strong> ሶስት ቦታ አጣብቃዋቸለች። እሱን እየፈታች<br />

ለፖሊሱ ስትሰጥ ያልደረሰባት የእርግማን እና የስድብ<br />

አይነት አልነበረም። እኔ አፌ በድንጋጤ ተለጉሟል፤<br />

በኋላ ግን “እንዴት ልታውቃት ቻልክ?” ስል መቶ<br />

አለቃውን በድንገት ብጠይቀው፣ “<strong>አገር</strong> ምድሩን<br />

ያጥለጠለቀው የእሷ ፎቶ ነው። ከዚህ በፊት በርካታ<br />

የ<strong>ስር</strong>ቆት ሪከርድ አለባት። ስንት ጊዜ መሰለህ ታስራ<br />

የተፈታችው?” ሲል ምላሽ ሰጠኝ። እሷም ታሰረች፣<br />

እኛም አውቶቡሳችን ውስጥ ገብተን ወደየምንሄድበት<br />

ጉዟችንን ቀጠልን። የወጣቷም ያለመጠርጠር ጥረት<br />

በዚህ አበቃ።”<br />

ይህ ከላይ ያስነበብናችሁ ገጠመኝ አቶ ጥላሁን<br />

ገዳሙ የተባሉ የ56 ዓመት ጎልማሳ ከ13 ዓመት<br />

በፊት በአውቶቡስ ውስጥ ያጋጠማቸው እውነታ<br />

ነው። አንበሳ የከተማ አውቶቡስ ከ1935 ዓ.ም ጀምሮ<br />

በተለይም ዝቅተኛና መካከለኛ የኑሮ ደረጃ ላላቸው<br />

የህብረተሰብ ክፍሎች የማይረሳ ውለታ ባለቤት ነው።<br />

ምንም እንኳን በአሁኑ ሰዓት የሀብታምና የድሀው<br />

ልዩነት የሰማይና የምድርን ያህል ርቆ መካከለኛ<br />

የኑሮ ደረጃ (Middle class) የሚባለው የህብረተሰብ<br />

ክፍል የለም ብለን ለመናገር በሚያስችለን ደረጃ ላይ<br />

ብንደርስም።<br />

በአንበሳ የከተማ አውቶበስ ውስጥ እጅግ አስገራሚ፣<br />

አሳዛኝ፣ አዝናኝና የተደበላለቀ ስሜትን የሚፈጥሩ<br />

ትዕይንቶች የሚከሰቱበት የመጓጓዣ አውታር መሆኑን<br />

ከማንም በላይ ተጠቃሚዎቹ ጠንቅቀው ያውቁታል።<br />

ለዛሬም የተሳፋሪዎችን፣ የትኬት ቆራጮችን እና<br />

የአንበሳ አውቶቡስ ሹፌሮችን ገጠመኞች እንቃኝ።<br />

ከዚያ በፊት ግን ስለአንበሳ አውቶቡስ አገልግሎት<br />

ጅማሮና የስራ ዘመኑ ጥቂት ማለት አግባብ ነውና<br />

እነሆ።<br />

ወራሪው የፋሺስት ጣሊያን መንግስት ሀገራችን ውስጥ<br />

በነበረበት ጊዜ ይጠቀምባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችንና<br />

የመኪና መለዋወጫ እቃዎችን በማሰባሰብ የስራና<br />

መገናኛ ሚኒስቴር ይባል በነበረው መ/ቤት አማካኝነት<br />

በ1935 ዓ.ም “የህዝብ ማመላለሻ” (ሕ.ማ) በሚል<br />

ስም ነበር የተመሰረተው - አንበሳ የከተማ አውቶበስ<br />

አገልግሎት።<br />

ታህሳስ 2 ቀን 1944 ዓ.ም ህጋዊ ሰውነት በማግኘት<br />

በአክሲዮን ከተቋቋመ በኋላ አረንጓዴና ቢጫ የተቀቡ<br />

10 አውቶቡሶችን ይዞ ሥራ መጀመሩን የድርጅቱ<br />

ማህደር ያመለክታል፤ እነዚህ አውቶቡሶች በከተማዋ<br />

አራት መስመሮች ላይ የተሰማሩ እንደነበር ይነገራል።<br />

ለህብረተሰቡ አገልግሎት ይሰጥ የነበረው የቀድሞው<br />

ህዝብ ማመላለሻ የአሁኑ አንበሳ አውቶቡስ በዚያን<br />

ወቅት የውጭ <strong>አገር</strong> ዜጎችን ጨምሮ 120 ሰራተኞች<br />

ነበሩት።<br />

በ1952 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይሰጥ የነበረው ትራንስፖርት<br />

አገልግሎት መስመሩ ከ4 ወደ 14 እንዲያድግ ሲደረግ<br />

በየመስመሩ ሲመደቡ የነበሩ አውቶብሶች ብዛትም<br />

ከሁለት ወደ ሶስት ከፍ እንዲል ተደረገ። እንዲህ<br />

እንዲህ አያለ በ1986 ዓ.ም በአዋጅ ቁጥር 187/1986<br />

በ14 ሚሊዮን ብር ካፒታል “አንበሳ የከተማ አውቶቡስ<br />

አገልግሎት ድርጅት” ተብሎ በአዲስ መልክ ራሱን<br />

ችሎ ከተቋቋመ በኋላ በየጊዜው ቁጥሩ እየጨመረ<br />

የሚሄደውን የከተማዋን ህዝብ ፍላጎት ለማሟላት<br />

በተለያዩ ጊዜያት በርካታ አውቶቡሶችን በእርዳታና<br />

በግዢ በማስመጣት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።<br />

በአሁን ሰዓት ድርጅቱ አዳዲስ 120 አውቶቡሶችን<br />

ያስገባ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ አስሩ 18 ሜትር<br />

እርዝመት ያላቸው፤ ተቀጣጣይ - አራዶች አኮርዲዮን<br />

ይሏቸዋል - እንደሆኑ ከድርጅቱ የህዝብ ግንኙነት<br />

ኦፊሰር ከአቶ ሸዋረጋ ሳህሌ ለመረዳት ችለናል።<br />

ድርጅቱ በአሁኑ ወቅት በቀን 320 አውቶቡሶችን<br />

ለስራ እንደሚያሰማራ የነገሩን አቶ ሸዋረጋ፣ ከ2740<br />

በላይ ቋሚ ሰራተኞች እንዳሉትም ነግረውናል።<br />

ስለአንበሳ አውቶቡስ አመሰራረት በጥቂቱ ከነገርናችሁ<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

ልዩ ቅኝት<br />

ወደ ዋናው ሃሳባችን እንሆ ተመልሰናል።<br />

የአንበሳ አጋጣሚዎች<br />

አንበሳ አውቶቡስ ውስጥ ብዙ የሚከሰቱ ነገሮች<br />

አንዳሉ ይደመጣል። በተለይ ደግሞ በሚፈጠረው<br />

መተፋፈግና መነካካት የወንዶች ስሜት እንደሚነሳሳ<br />

ይነገራል። የዚህ ሰለባ የሆነ አንድ ወጣት ተከታዩን<br />

አጫውቶኛል፡- “ሁለት ወንዶችና አንድ ወጣት ሴት<br />

ወደተሳፈርኩበት አውቶብስ ሲገቡ ተመለከትኩ።<br />

ሆኖም ሴቷ ወደ እኔ በመጠጋት ትተሻሸኝ ጀመር።<br />

ሁኔታዋ ሁሉ እኔን ወደ ሌላ ስሜት ውስጥ ከተተኝ።<br />

በወቅቱ አውቶቡሱ ውስጥ ካሉት ወንዶች ውስጥ<br />

ይህቺ ቆንጆ እኔን መርጣ በዚያ ሁኔታ ላይ መገኘቷ<br />

ኩራት እንዲሰማኝ አድርጎኛል” ይላል ወጣቱ። ይሁን<br />

እንጂ ወጣቱ በቆንጆዋ ሁኔታ ተማርኮ ስሜቱን<br />

ሲያዳምጥ አብረዋት የነበሩት ሁለት ወንዶች ከኪሱ<br />

1ሺህ አንድ መቶ ብር ሰርቀውት ከወረዱ በኋላ<br />

መባነኑን ያስታውሳል። ቆንጆዋ ማደንዘዣ መሆኗ<br />

ነው።<br />

በአንድ ወቅት ነው አንድ ወጣት 19 ቁጥር አውቶቡስ<br />

ውስጥ ተሳፍሮ ወደ አስኮ እየተጓዘ ነው። አንድ<br />

ትልቅ አዛውንት ካፖርት ለብሰው ቆመዋል። “አባት<br />

ልነሳልዎትና ወንበር ላይ ይቀመጡ አልኳቸው። ግን<br />

ፈቃደኛ አልሆኑም” የሚለው ይህ ወጣት፣ መውረጃው<br />

ሲቀርብ ለመውረድ ከወንበሩ ይነሳል። አዛውንቱ<br />

የያዙትን ብረት ይዞ አውቶቡሱ እስኪቆም ለመጠበቅ<br />

ሲሞክር አውቶቡሱ ይንገጫገጭና ልጁ ሚዛኑን<br />

ይስታል። እናም የሚይዘው ሲያጣ ተንደርድሮ<br />

የአዛውንቱ የካፖርት ኪስ ውስጥ ዘው ይላል።<br />

አዛውንት ሆዬ ካፖርታቸው ኪስ ውስጥ ያለውን እጅ<br />

ይይዙና እሪ ይላሉ። አውቶቡሱ ቆሞ ልጅና አዛውንቱ<br />

ተያይዘው ፖሊስ ይደርሳል። “በህይወቴ አንደዚያ ያለ<br />

ቅሌት ገጥሞኝ አያውቅም። በስንቱ ታቦት ብምል፣<br />

ብገዘት ሰውየው ሊያምኑኝ አልቻሉም። ስለዚህ ጉዳዩ<br />

እስኪጣራ ፖሊስ ጣቢያ አምሽቻለሁ” ሲል ባላሰበበት<br />

መዋሉን ይናገራል።<br />

ራሄል ይስማው ላፉት ስምንት አመታት የአውቶቡስ<br />

ትኬት ቆራጭ ሆና ሰርታለች። በስራዋም ብዙ<br />

ገጠመኞች አሏት። “አንድ ቀን 53 ቁጥር አውቶቡስ<br />

ላይ እየሰራሁ ቲኬት ፈታሽ ይመጣል። አንዱ ትኬቱን<br />

ጥሎት ስለነበር ፈታሹ ሁለት እጥፍ እንዲከፍል<br />

ያስገድደዋል። ልጁ ዘና ብሎ፣ “እሺ እከፍላለሁ”<br />

ብሎ ኪሱ ሲገባ ቦርሳው ተወስዷል” የምትለው<br />

ራሄል፣ በዛን ሰዓት የነበረውን ድንጋጤ አሁንም<br />

እንደምታስታውሰው ትናገራለች። በመጨረሻም<br />

ሁኔታውን ሳይ እኔ ከፈልኩለት። እሱም ሌላ ቀን<br />

እንደሚከፍል ነግሯት ስልኳን ተቀብሎ መውረዱን፣<br />

በዚህም የተነሳ ለረጅም ጊዜ የፍቅር ጓደኛሞች ሆነው<br />

መቆየታቸውን ትናገራለች።<br />

ሞኖ ባንዶች<br />

አውቶቡስ ውስጥ ሲጓዙ ምንም ድምፅ ሳይኖራቸው<br />

የሚዘፍኑ አስቂኝ ማስታወቂያዎችን በመናገር<br />

ከተሳፋሪው የሚቀፍሉ (የሚያባብሉ) [ዘመናዊ<br />

የልመና አይነት ነው] በርካቶች ናቸው። እንደእነዚህ<br />

አይነቶቹን ሰዎች እርሶ በተለይ አውቶቡስ ተጠቃሚ<br />

ከሆኑ በተለያዩ ቁጥር አውቶቡሶች ላይ ያገኟቸዋል።<br />

ራሳቸውን “ሞኖ ባንድ” እያሉ የሚጠሩም ያጋጥማሉ።<br />

“ሞኖ ባንድ እንሰኛለን። እናንተን ለማዝናናት ምንጊዜም<br />

ዝግጁ ነን። ይህን ማይክ የሰጠን እንዲህ አይነት<br />

ሙዚቃ መሳሪያ አስመጪ ድርጅት ነው። የክብር<br />

ስፖንሰራችን ደግሞ አንበሳ የከተማ አውቶቡስ ነው”<br />

እና መሰል ነገሮችን በመደርደር ዘመናዊ ልመናዎች<br />

ይካሄድበታል። አይ አንበሳ አውቶቡስ፤ “በእኔና በባስ<br />

የማይመጣ የለም” ያለው ማን ነበር?<br />

ቀዶ ጥገና<br />

ቀዶ ጥገና ስንል የህክምናውን እንዳይመስልዎ።<br />

በአውቶቡስ ውስጥም የቀዶ ጥገና በርካታ<br />

ስፔሻሊስቶች እንዳሉ ልንጠቁምዎ እንጂ። በአንድ<br />

ወቅት አንድ ጓደኛዬ የገጠመውን እንዲህ አጫዎተኝ።<br />

ሰውየው ከጎጃም በርካታ ማር ጭነው አዲስ አበባ<br />

ለነጋዴ ያስረክባሉ። እናም የዋሁና ገራገሩ የገጠር<br />

ሰው በከረጢት ብራቸውን አንግተው ከኮታቸው <strong>ስር</strong><br />

አንጠልጥለዋል። ከዚያም ወደ ማረፊያቸው ይሄው<br />

ጓደኛዬ ወደተሳፈረበት ስምንት ቁጥር አውቶቡስ<br />

ውስጥ ይሳፈራሉ። አውቶቡሱ ትንሽ እንደተጓዘ<br />

ቀዶ ጠጋኙ የሰውየውን ከረጢት (የሚጋፋ መስሎ)<br />

በመቀስ ይሁን በምላጭ ከስሩ ይሸረክትና ብሩን በ<strong>ስር</strong><br />

በኩል ወስዶ አንዱ ፌርማታ ላይ ዱብ ይላል። ያኔ<br />

አንገታቸው የቀለላቸው የማር ነጋዴ ደረታቸውን<br />

ቢዳብሱ ጊዜ የከረጢታቸው ሆድ መቆዘሩ ቀርቶ ባዶ<br />

ሆኗል።<br />

እናም ሰውየው ኡኡ አሉ እንዲህ እያሉ፡- “እሪ<br />

በል ሸዋ ጎጃም ተበላ እሪ በል ሸዋ ጎጃም ተበላ”።<br />

እንዲህ ያሰኛሉ ቀዶ ጠጋኞች። ይህን የሰማ አንድ<br />

ሌላ ሰው እንዳጫወተኝ ሁለት ጓደኛሞች እቃ ሊገዙ<br />

መርካቶ ይሄዳሉ። አውቶቡስ ፌርማታው ላይ እያሉ<br />

የአንዱ ስልክ ከኪሱ ይጠፋል። ሌላው ጓኛውን፣<br />

“እንዴት ኪስህ ውስጥ ትይዛለህ” በማለት ተቆጣው።<br />

ምክንያቱም እርሱ ሞባይል ስልኩን በማንጠልጠያ<br />

አንገቱ ላይ አንጠልጥሎ ስልኩን ደረት ኪሱ ነው<br />

የሚያስቀምጠው። እናም፣ “አሁን በቃ ተወስዷል።<br />

ለሌላ ጊዜ አንደኔ እንዲህ አድርገህ ያዝ” ብሎ አንገቱ<br />

ላይ ያለውን የስልክ ገመድ ሲስበው ስልኩ ተወስዶ<br />

ገመዱ ብቻ ነው የቀረው። ኪሱን ቀዶ ጠጋኞቹ ቀደው<br />

ስልኩን ወስደዋል። እንዲህ ናቸው ቀዶ ጠጋኞች፤<br />

ከደረት ውስጥ ልብን ለመውሰድ ከአይን ላይ ኩል<br />

ለመንጠቅ ረቀቅ ያለ ሰርጀሪ ይሰራሉ። ከእነርሱ<br />

ይሰውረን ብሎ መፀለይ መልካም ነው።<br />

“አንዴ ነው እቃ ለመግዛት በርከት ያለ ብር ይዤ<br />

አውቶቡስ ውስጥ ነኝ። አንዱ ወጠምሻ አጠገቤ<br />

ቆሟል። ይተሻሸኛል፤ ይገፋኛል። ‘ለምን ራስህን ችለህ<br />

አትቆምም’ ስል ገሰፅኩት። ሆኖም ሊተወኝ አልቻለም”<br />

ትላለች ለገሀር 32 ቁጥርን ስትጠብቅ ያገኘኋት<br />

የትምወርቅ። ግፊያውና ፍትጊያው ሲሰለቻት አምርራ<br />

መቆጣቷን የምትናገረው የትምወርቅ፣ “ቆይ ከእኔ<br />

ምን ፈልገህ ነው እንዲህ የምትሆነው ብለው፣ ‘አንቺ<br />

ገገምሽ አንጂ እኔማ ያጨቅሽውን ብር አይቼ ነው’<br />

አለኝ - አይኑን በጨው አጥቦ፤ እንዴት አወቅክ<br />

ብለው፣ ‘ከፈለግሽ አንኳን ቦርሳሽን ከ<strong>ስር</strong> የለበሽውን<br />

የውስጥ ሱሪ ቀለም እነግርሻለሁ’ በማለት ቀልቤን<br />

በድንጋጤ ገፈፈው” በማለት በጥርጣሬዋ ከሰርጀሪ<br />

መዳኗን ታስታውሳለች። እነዚህ ቀዶ ጠጋኞች ቦርሳን<br />

ብቻ ሳይሆን ውስጥንም ራጅ ማንሳት ይችላሉ እንዴ?<br />

ያስብላል።<br />

የቡድን ሥራ<br />

አውቶቡስ ውስጥ ከሚፈጠሩ አጋጣሚዎች ውስጥ<br />

የረቀቀው የሌቦች የቡድን ስራ ይጠቀሳል። ለዚህም<br />

የተለያዩ ዘዴዎች ይፈበረካሉ። ከላይ እንደጠቀስነው<br />

በሴት ተማርኮ ሲፈዝ ጓደኞቿ የሰረቁት አንድ ሺህ<br />

አንድ መቶ ብር አንዱ የቡድን ስራቸው ውጤት<br />

ነው። ‹‹የተግባረዕድ ተማሪ ሆኜ በአውቶቡስ ነበር<br />

የምመላለሰው። እናም በወቅቱ የወር ክፍያ 48 ብር<br />

ይዣለሁ›› በማለት ገጠመኙን የጀመረው ችሎታው<br />

የተባለ ወጣት በወቅቱ በርከት ያሉ ወጣቶች አውቶቡስ<br />

ውስጥ ገብተው በተንተን ብለው መቆማቸውን<br />

ያስታውሳል። ከመካከላቸው አንዱ እጅግ ተጫዋችና<br />

ሲበዛ ቀልድ አዋቂ ተሳፋሪዎች በሱ ጫወታ ሲፈዙ<br />

ሌሎቹ ወደ ስራቸው ይሰማራሉ። ‹‹እኔንም የገጠመኝ<br />

ይሄው ነው በልጁ ወሬ ተመስጨ ስፈዝ ለካስ ጓደኛው<br />

ኪሴ ገብቶ 48 ብሩን ሊወስድ ይታገላል። በወቅቱ<br />

ጠበብ ያለ ጅንስ ስለለበስኩ እጁ ሲነካኝ ነቃሁ››<br />

በማለት እንዴት እንደተረፈ የሚገልፀው ችሎታው<br />

አሁን ረቀቅ ያሉ ገፋፊዎች ስለተበራከቱ መጠንቀቅ<br />

አንደሚያሻ ይመክራል።<br />

መልካም አጋጣሚዎች<br />

አንድ ነገር መጥፎ ጎን እንዳለው ሁሉ መልካም<br />

ጎኖችም አይጠፉትም። የከተማ አውቶቡሶችም<br />

እንዲሁ። <strong>ስር</strong>ቆቱ ጾታዊ ትንኮሳውና መሰል ጥሩ<br />

ያልሆኑ አጋጣሚዎች የሚፈጠሩ ቢሆንም መልካም<br />

ነገርም ጎን ለጎን ይኖራል። ስማቸውን መናገር<br />

ያልፈለጉ አንድ ጎልማሳ በአንበሳ አውቶቡስ ውስጥ<br />

ለ17 አመታት አገልግለዋል። ድርጊቱ በተፈፀመበት<br />

እለት ጠዋት ተነስተው በስራ ላይ ተገኝተዋል።<br />

ሲያሸከረክሩ ውለው ከቀኑ ወደ 10 ሰዓት አካባቢ<br />

ድንገት ታመው አውቶቡሱን መንዳት ያቅታቸዋል።<br />

መሀል አስፋልት ላይ መኪናው ቀጥ ብሎ ይቆማል።<br />

‹‹ምን እንደነካኝ ሳላውቅ ራሴን እንደመሳት አደረገኝ።<br />

ምን እንደተፈጠረ አላውቅም ነበር›› የሚሉት እኚህ<br />

ግለሰብ ከዚያም አንድ መስፍን የተባለ ወጣት እሳቸውን<br />

አስነስቶ መሪውን በመጨበጥ ህዝቡን የሚፈልግበት<br />

አድርሶ እርሳቸውንም ሀኪም ቤት ወስዶ ማሳከሙን<br />

ያስታውሳሉ።<br />

ሙሉጌታ የ60 ቁጥር አውቶቡስ ደንበኛ ነው።<br />

ሁሌም ከአዲስ አበባ ደብረዘይት ከደብረዘይት አዲስ<br />

አበባ ለመመላለስ ይህቺ አውቶቡስ ባለውለታው ናት።<br />

ምክንያቱም በዛን ወቅት በአየር ኃይል ውስጥ ሬዲዮ<br />

ኦፕሬተር ሆኖ ይሰራ ስለነበር ሁሌም ጠዋትና ማታ<br />

ተመላላሽ ነው። ከሳምንቱ በአንዱ ቀን ከአየር ሀይል<br />

ግቢ ስራውን አጠናቆ 60 ቁጥር ውስጥ ይገባል።<br />

አውቶቡሱ ተጨናንቆ ስለነበር አንዲት ሴት ቦርሳዋን<br />

እንዲይዝላት ትጠይቀዋለች። ይቀበላልም። ‹‹ቦርሳውን<br />

ስትሰጠኝ መልኳን ልብ ብዬ አላየሁትም በኋላ ግን<br />

ወደ አዲስ አበባ እየቀረብን ስንመጣ እንዴት ቦርሳዋን<br />

አትጠይቀኝም እያልኩ አስብ ጀመር። ምክንያቱም ሰው<br />

መንገድ ላይ እየወረደ አውቶቡሱ ቀለል ብሎ ስለነበር”<br />

ይላል። ይሁን እንጂ አውቶቡሱ ለገሀር ደርሶ ሁሉም<br />

ሰው ሲወርድ የቦርሳው ባለቤት የለችም ግራ ገባው።<br />

‹‹ባለቦርሳ ብዬ እንዳልጠራ አንዷ ተነስታ የኔ ነው<br />

ብትለኝስ ብዬ ዝም አልኩ›› ይላል ሙሉጌታ። እናም<br />

በወቅቱ ቦርሳውን ወደቤቱ ይዞ ይሄድና መፈተሽ<br />

ይጀምራል። በውስጡም ፖስፖርት፣ 5 ሺህ ጥሬ<br />

ብር፣ የ19 ሺህ 500 ብር ቼክ፣ ሌሎች ወረቀቶች፣<br />

የቀበሌ መታወቂያና የእጅ ሰዓት በቦርሳው ውስጥ<br />

መኖሩን ማረጋገጡን ያስታውሳል። ‹‹ከራሴ ጋር<br />

ብዙ ተሟገትኩ። መታወቂያው ላይ ባገኘሁት ስልክ<br />

ልደውል አልደውል በሚል። -ደውልላት የሚለው ሀሳቤ<br />

በማመዘኑ ደወልኩላት›› በማለት የነበረበትን የሀሳብ<br />

አጣብቂኝ ይናገራል። ሙሉጌታ ስልኩን በደወለ ጊዜ<br />

ያነሳው ወንድ ነበር። ስለሁኔታው ሲነግረው ‹‹መልሰን<br />

እንደውል ትንሽ ችግር አጋጥሟት አልተረጋጋችም››<br />

ብሎ አንደመለሰለት ከገለፀ በኋላ በዛን ወቅት<br />

ተንቀሳቃሽ ስልክ ስላልነበረው የእናቱን የቤት ስልክ<br />

ቁጥር መስጠቱን ይናገራል። ‹‹ደወለችልኝ ከዚያም<br />

እናቷ በድንገት ታመው አደጋ ውስጥ እንደነበሩ<br />

ስትሰማ ገና ዱከም ስትደርስ ደንግጣ አንደወረደችና<br />

ፈፅሞ ቦርሳውን እንዳላስታወሰች ነገረችኝ›› ይላል<br />

ሙሉጌታ።<br />

ልክ በአራተኛው ቀን ደውላ ደብረዘይት ከመጣ<br />

እንዲያቀብላት መጠየቋን የሚገልፀው ይህ ወጣት<br />

ቦርሳውን ይዞ ደብረ ዘይት ይሄድና በተቀጣጠሩበት<br />

ቦታ ይገናኛሉ። ቤቷ ይዛው ልትሄድ ብትሞክርም<br />

የስራ ሰዓት በመድረሱ ከስራ ሲወጣ እንደሚያገኛት<br />

ቀጠሮ ይዞ ወደ ስራው ያመራል። ሲወጣም በቀጠሮው<br />

መሠረት ቤቷ ይሄዳል። ዝምድናው ከዚህ ይጀምራል።<br />

አሁን ግን የሴትዮዋን ልጅ አግብቶ ሁለት ልጆችን<br />

በመውለድ ባለቦርሳዋን አያት አድርጓታል። መልካም<br />

አጋጣሚ ይሏል ይህ ነው።<br />

‹‹በባስ ውስጥ እየሄድኩ ነው በቁመት ከእኔ እኩል<br />

የሆነ ወጣት ፊት ለፊቴ ቆሟል አንድ ብረትም<br />

ተጋርተን ይዘናል›› ትላለች ረዘምና ጠየም ያለችው<br />

የ29 ዓመት ወጣት አይናለም ዳርሜለህ። ድንገት<br />

ሳይታሰብ አውቶቡሱ ፍሬን ይዞ በመንገጫገጩ እሷና<br />

ከፊት ለፊቷ የቆመው ወጣት ሚዛናቸውን ስተው<br />

ሲወዛወዙ ከንፈራቸው መገጣጠሙን ትናገራለች።<br />

‹‹እነሆ በዚያች በተቀደሰች አጋጠሚ የተነካካው<br />

ከንፈራችን ዛሬም አልተላቀቀም /ተጋብተናል/ በማለት<br />

አስገራሚውን ገጠመኘዋን ትናገራለች።<br />

የስሜት አንበሶች<br />

አንበሳ አውቶቡስ ውስጥ ተሳፍረው እየተጓዙ<br />

ስሜታቸው አንበሳ ሆኖ ጾታዊ ትንኮሳ የሚያስከትሉትስ<br />

ስንቶቹ ናቸው? መቼም እዚህ ጋዜጣ ላይ ለመፃፍ<br />

ባይበቃም በአውቶቡስ ውስጥ የሚያጋጥሙ አፈንጋጭ<br />

የወሲብ ጥቃቶች በርካቶች ናቸው። እንደውም<br />

ገና የሴት ቀሚስ ሲነካቸው ደርሶ ወንድነታቸው<br />

የሚገነፍል፣ በአይን ብቻ ሴትን ለመተኛት ጥረት<br />

የሚያደርጉ ከዚያም አልፈው ተርፈው ‹‹በማንም<br />

አያየኝም›› ድፍረት አስቀያሚ ድርጊት ሲፈፅሙ<br />

በሆነ አጋጣሚ ለሰዎች እይታ ተጋልጠው ውርደት<br />

የሚከናነቡ፣ ይህም ካልሆነ ጣጣቸውን ሰው ላይ<br />

ለጥፈው እስከመሄድ የሚደርሱ ስንቶቹ ናቸው?<br />

እነሆ ገጠመኝ።<br />

‹‹በአንድ ወቅት በ46 ቁጥር ከገርጂ ወደ ካዛንቺስ<br />

እየተጓዝኩ አንዱ ይተሻሸኛል። እናም እሸሻለሁ።<br />

እርሱ እየተጠጋ ስሜቱን ለማርካት ይጣጣራል››<br />

ትላለች ኤፍራታ አዲሱ የተባለች ወጣት። እንደ<br />

ኤፍራታ ገለፃ ሰውየው ፍፁም ስሜት ውስጥ ስለነበር<br />

ምንም ማስተዋል እንደተሳነው ታስታውሳች። ‹‹ነገሩ<br />

ሲብስብኝ ለምን አታርፍም? የሚል ጥያቄ ሳነሳ<br />

‹አርፈሽ ቁሚ ብዬሻለሁ› በማለት አንዴ በጥፊ<br />

ሲያጮለኝ ጮህኩኝ›› የምትለው ኤፍራታ ሰዎች<br />

ምንድነው ብለው መሀል ሲገቡ እሱ ኃፍረተ-<br />

ስጋውን ከሱሪው ውጭ አድርጎት ነበር›› በማለት<br />

በዕለቱ የደረሰባትን ውርደት አስታውሳ ትስቃለች።<br />

በወቅቱ ሰዎች ባይገላግሉሽ ምን እርምጃ ትወስጂ<br />

ነበር የሚል ጥያቄ አንስተንላት ‹‹ባገኘሁች አጋጣሚ<br />

ከስሩ እንደችግኝ ነቅዬ ነበር በእጁ የምሰጠው››<br />

በማለት ስቃ እኛንም አሳቀችን። በነገራችን ላይ በጣም<br />

የሚያሳዝነው አንድ እናት የ7 ዓመት ሴት ልጃቸውን<br />

አውቶቡስ ውስጥ ወንበር ላይ ለተቀመጠ ትልቅ ሰው<br />

አደራ በማለት እናት ይቆማሉ። ከደቂቃዎች በኋላ<br />

ኅጻኗ አውቶቡሱን በእሪታ ታቀልጠዋለች። ሰውየው<br />

ጭናቸው ላይ አስቀምጠው ደፍረዋታል። ይሄውና<br />

ተፈርዶባቸው ዘብጥያ ወርደው ይገኛሉ። እንዲህና<br />

መሰል ሰቅጣጭ ክስተቶች በአንበሳ አውቶቡስ ውስጥ<br />

ይካሄዳሉ።<br />

አዎ በከተማ አውቶቡስ ውስጥ በርካታ ገመጠኞች<br />

አሉ። አዝናኝም አሳዛኝም፣ አስነዋሪም፣ አስገራሚም።<br />

እርሶ የትኛው አጋጣሚ ደርሶዎት ይሆን? ክፉው<br />

ወይስ ደጉ? እንጃ ብቻ ከቀዶ ጠጋኞቹም ከቡድን<br />

ሰራተኞቹም ከቀፋዮቹም ራስን መጠበቅና መጠንቀቁ<br />

አይከፋም። መልካሙን አጋጣሚ መጠቀምም<br />

ብልህነት ነውና አውቶቡስ ተጠቃሚዎች ሆይ ቸር<br />

ይግጠማችሁ እንላለን።


አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />

ማፊያ<br />

በብስራት<br />

ሚና፤ በማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ወይም<br />

በዘመናችን የወንጀል መልክ<br />

እየተለወጠ መጥቷል። ከዚህ<br />

ቀደም ከነበሩ ታላላቅ የተለመዱ<br />

ታዋቂ ማፊያዎች ጎን ለጎን<br />

ሌላ አዲስ የተደራጀ ወንጀል<br />

ብቅ ብሏል። ባለፉት ዓመታት<br />

ጂኦፖለቲካዊ ውጥንቅጥ<br />

ፖለቲካዊ ዘርፎች በተለይ በሕጋዊና ሕገ-ወጥ<br />

ክበብ መሀከል ግልግል ሥራዎችን ለማከናወን<br />

ማፊያዎች ጠቃሚ ሚና ይጫወታሉ። (4)<br />

በክልላዊና ብሔራዊ ደረጃ ከፖለቲካዊ መደብ<br />

(Political Elite) እና ከተቋማት ጋር ያላቸው<br />

ቁርኝት፤ ማፊያ ባለው ትሥሥር ወይም<br />

ግንኙት ምክንያት ወደ አንዳንድ ሕዝብ የኃብት<br />

ምንጮች ወይም ገበያዎች ውስጥ ይገባል።<br />

ውስጥ የተፈጠረውን ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት በዚህም መሰረት በአንዳንድ ሁኔታዎች በሕጋዊ<br />

(Economic Globalization)፣ በዓለም አቀፍ ከለላ በመጠቀም በማኅበረሰቡ ላይ ካለው ተፅዕኖ<br />

የፋይናንስ ዝውውር በመጠቀምና የንግድ አልፎ ለፖለቲካዊ መደቡ ድጋፉን ይለግሳል።<br />

ልውውጥ ውስጥ ራሱን በመሰወር በሰዎች (5) በአንድ ክልል ሥር መሰደድ ወይም ጠንካራ<br />

ከቦታ ቦታ መዘዋወር መፋጠንን በመታገዝ ይዞታ መያዝ፤ አንድ የማፊያ ቡድን በሀገር<br />

እየበለፀገ ይገኛል - የወንጀል ዓለም።<br />

ውስጥና ከሀገር ውጪ በሌሎች አካባቢዎች<br />

እነዚህ አዳዲስ የመጡ ቡድኖች ዕንቅስቃሴ ቢያደርግም ቀድሞ የተመሰረተበትን<br />

ራሳቸውን በፍጥነት በማሳደግና መዋቅራቸውን ቦታ አይለቅም። ሥር ይሰዳል። ለምሳሌ፡-<br />

በመዘርጋት አንዳንዶቹ ቀድሞ በኢጣሊያ፣ ንድራጌታ (Ndrangheta) የተባለ ቡድን በሰሜናዊ<br />

ጃፓን፣ ቻይና፣ ቱርክና በኢጣሎ-አሜሪካን ኢጣሊያ እና በውጭ ሀገራት ዕንቅስቃሴዎችን<br />

በባህላዊ ልማዳቸው፣ በኢኮኖሚ አቅማቸውና ቢያደርግም፣ መጀመሪያ የተቋቋመበትን የካላብር<br />

ከፖለቲካ ጋር ባላቸው ቁርኝት ‹‹ማፊያ›› (Calabre) ክልል ፈጽሞ አልለቀቀም። (6)<br />

የሚለውን መጠሪያ ካገኙት የቀድሞ በድኖች አጠቃላይ የድርጅቱ ኃብት ምንጮች ሕጋዊና<br />

ጋር አቻ የሆነ ሚና በተግባር እስከመጫወት ሕገ-ወጥ ዕንቅስቃሴዎችን አጣምሮ መያዝ፤<br />

ደርሰዋል።<br />

በዓለማችን የማፊያ ቡድንን ወንጀል ከሕግ<br />

በፒራሚዳዊ ቅርጽ በመዋቀር አንጻር ለይተው ያስቀመጡ ሀገራት ከአንዲት<br />

በተፈጠሩበት ሀገር (መጠሪያቸውን የሚያገኙት ሀገር በስተቀር እንደሌሉ ሊሰመርበት ይገባል።<br />

ከዚህ ነው) በደንብ ራሳቸውን አቋቁመው ጣሊያን ካሳለፈችው ታሪካዊ ሁኔታ ይሁን በሌላ<br />

የተወሰኑ የመንግሥት ባለሥልጣናትን በማሞሰን ምክንያት በማፊያ ማኅበር የሚፈፀም ወንጀል<br />

በኢንቨስትመንት ላይ ይሳተፋሉ፤ ኢኮኖማውንም ምን ምን እንደሆነ ከሕግ አንጻር ባግባቡ ለይታ<br />

ይቦጠቡጣሉ። እነዚህ አዳዲስ ቡድኖች የገለፀች ብቸኛ ሀገር ናት።<br />

ዕድሜያቸው አጭር ቢሆንም አደረጃጀታቸው<br />

እነዚህን የማፊያ ማኅብር ዋና<br />

ግን በጣም የቆዩ ያስመስላቸዋል።<br />

ዋና ባህርያት ከተረዳን በኋላ የማፊያ ቡድን<br />

ማፊያ የሚፈጠርበትን ምክንያት ይህ መቼ እንደሚፈጠር እንይ። በአጥኚዎች ገለጻ<br />

ነው ብሎ ለመግለፅ የሚያዳግት ቢሆንም፣ መሠረት ማፊያ የሚፈጠረው ሕዝባዊ ተቋማት<br />

የመንግሥት መዳከም፣ ሥልጣን ርጉዕ በሆነ ፀጥታን ማስከበር ሲሳናቸው ነው። ማፊያ<br />

ፖለቲካዊ ቡድን በምኖፓል ሲያዝ፣ በጎሳ ወይም ከሌሎች ዓይነት የወንጀል ድርጊቶች እና<br />

ጎጠኝነት ላይ የተመሰረተ ማኅበራዊ አደረጃጀት ጥፋቶች ጋር ተጣምሮ ይሄዳል። በመቀጠልም<br />

ወዘተ እንደምክንያት ይጠቀሳሉ።<br />

እንደምንም ኃብት ያካብታል። ማፊያ አመቺ<br />

አንዳንድ የቀድሞ ማፊያ ብዙም ባልሆነ ኢኮኖማያዊ ሁኔታ ውስጥ ሊያቆጠቁጥ<br />

የማያውቃቸው የነበሩ ምዕራባውያን ሀገራት አይችልም። ለምሳሌ በሲሲሊ ውስጥ ኮዛ ኖስትራ<br />

ዛሬ የእነዚህ ዓለም አቀፍ አዳኞች ሰለባ እየሆኑ (Cosa Nostra) የተባ ዕድሜ ጠገብ የማፊያ<br />

ነው። ለምን? የዚህ መነሻው ሁለት ነው። አንድ፡ ቡድን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ ላይ ብቅ<br />

- እነዚህ ቡድኖች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየበዙ ያለው በፓሌርሞ አካባቢ የሚገኙ ሰፋፊ የፍራፍሬ<br />

መምጣታቸው። ሁለት፡- ‹‹ኅቡዕ ካፒታሊዝም›› እርሻዎችን በመታከክ በግብርና ኢኮኖሚ ውስጥ<br />

(Clandestine Capitalism) ኢንተርፐርነር ነው። በመጨሻም ማፊያ ከሕዝባዊ ተቋማት<br />

የሆነው የተደራጀ ወንጀል በአዳዲስ ገበያዎች አካላት ጋር ትሥሥር መፍጠር ግድ ይለዋል።<br />

ውስጥ ቋማ ሥፍራ ለማግኘት ስለሚፈልግ ነው። ይህም ሽርክና የሚፈጠረው ወይ እንደ 19ኛው<br />

ለእነዚህ ገበያዎች ምርቶቹንና አገልግሎቶቹን ክ/ዘመን ሲሲሊ በሀገራዊ ሕገመንግሥት ውስጥ<br />

ያቀርባል። ዕጾችን፣ ሴቶችንና የተለያዩ ወንጀል በሚኖር ክፍተት በመጠቀም አሊያም ደግሞ<br />

ነክ ቴክኖሎጂዎችን ማለትም የማጭበርበሪያ ቅርብ ጊዜ ከ1989 እ.አ.አ በኋላ በቀድሞ ሶቭየት<br />

ወይም ማስመሰያ ደረሰኞችን፣ ጭምብሎችን፣ ኅብረት ሪፑብሊክ እንደተከሰተው የአንድን ሀገር<br />

የባንክ ካርዶችን ኮዶች ለማግኘት የሚረዱ ሚኒ መንኮታኮት ተከትሎ ነው።<br />

ካሜራዎችን ወዘተ።<br />

ማፊያ በሰው ልጆች ታሪክ ውስጥ<br />

እስከቅርብ ጊዜ ድረሰ ለመንግሥታት ከቀድሞም የነበረ ሳይሆን በቅርብ ጊዜ በፖለቲካ<br />

ያለመረጋት ምንጮች ተደርገው ይቆጠሩ መዘመን (Political Moderanity) ጋር የመጣ<br />

የነበሩት ሽብርተኝነትና የኢኮኖሚ ድቀት ብቻ ነው። ዘመናዊ ኢኮኖሚ በተገነባበት ሁኔታ ውስጥ<br />

ነበሩ። ዛሬ ዛሬ ግን በዓለም አቀፍ ትብብርና ዴሞክራሲ ሲከስም ወይም ሲቆረቁዝ ለማፊያ<br />

ሕግጋት ክፍተት በመጠቀም ማፊያ ሌላው አመቺ ሁኔታ ይፈጠራል። የመጀመሪያው<br />

ያልታወቀ ያለመረጋጋት መንስኤ እየሆነ ነው። የማፊያ ማኅበር የተፈጠረው በ19ኛው ከፍለ<br />

ይህ ደግሞ በተለይ በክልላችን ዘመን በሲሲሊ ግዛት ነው።<br />

በምሥራቅ አፍሪካ የራሱ መገለጫ አለው።<br />

የማፊያ ቡድን በአንዳንድ ሀገራት ኖሮ<br />

ያንን በዚህ ጽሑፍ በዝርዝር ለማየት በቂ በሌሎች ደግሞ የማይፈጠረው ለምንድነው?<br />

ጥናትና ምርምር ይጠይቃል። ሆኖም ግን ለዚህ ዋናው ምክንያት የጠንካራ ማዕከላዊ<br />

የማፊያ መለያ ባህርያትና ከዴሞክራሲ ዕጦት መንግሥት መኖር ሲሆን፣ ይህም በአንድ<br />

ጋር ያለውን ቁርኝት ጠቅለል ባለ መልኩ ማየቱ መንግሥት ውስጥ የሌላ ኅቡዕ መንግሥት<br />

ጠቃሚ ነው።<br />

(ልክ እንደማፊያ) ሕገ መንግሥት ወይም ደንብ<br />

ለመሆኑ ማፊያ ከሌሎች የወንጀል እንዳይኖር ስለሚከለክል ነው።<br />

ድርጅቶች የሚለየው በምንድነው? በዘርፉ<br />

አንድ የማፊያ ቡድን ቱባ አለቃዎቹ<br />

አጥኚዎች ማብራሪያ መሠረት ማፊያ ስድስት ሲታሰሩበት ይህን ችግር ተቋቁሞ ለማለፍ<br />

መገለጫ ባህርያት አሉት። እነሱም፡-(1) እንዴት ያደርጋል? የማፊያ ቡድን የራሱ<br />

ድርጅታዊ አወቃቀሩ፤ የማፊያ ቡድን አባላት መዋቅር ያለውና በአንድ አካባቢ ሥር የሚሰድ<br />

የጋራ ግዴታ ወይም ውል እና የተወሰነ ኃይል ነው። ዋና አለቃው ሲገደል በተለምዶ<br />

ውስጠ ደንብ አላቸው። (2) ሁከት ወይም ወዲያው አንድ ግለሰብ በቦታው ይተካል። ሆኖም<br />

የኃየል ድርጊት፤ የማፊያ ቡድን ሁከትን ግን ይህ ዕይታ በአግባቡ መመርመር አለበት<br />

ወይም የኃይል ድርጊትን (Violence) አንዳንድ ይላል አንድ የማፊያን ጉዳይ የሚዳኙ ባለሙያ።<br />

ጊዜ ወደ ባለፀጋነት መሰላል ለመውጣት እና አክለውም፣ “ማፊያ” ሰብዓዊ ክስተት ነው። ልክ<br />

በማስፈራራት ድርጅቱን ለመጠበቅ ወይም ጅማሬ (መነሻ) እንዳለው ሁሉ መጨረሻም<br />

ለመከላከል ይጠቀማል። (3) የማፊያ ማኅበራዊ ይኖረዋል” ይላሉ። ይህ አባባል ያለምክንያት<br />

ባሕርያቱና ከዴሞክራሲ<br />

እጦት ጋር ያለው ቁርኝት<br />

የተሰነዘረ አይደለም። በጥሩ መሰረት ላይ<br />

የቆመ የፀረ-ማፊያ ትግል ከተጠናከረ ማፊያ<br />

የማይወገድበት ምክንያት የለምና።<br />

ለመሆኑ የማፊያ ማኅብራት የተፅዕኖ<br />

ክልላቸውን ለማስፋፋት በሉዓላዊነት /<br />

Globalization/ ይጠቀማሉ? አዎ! ከኢኮኖሚያዊ<br />

ዕይታ አንጻር ካፒታላቸውን ወደ ውጭ ሀገር<br />

ይልካሉ፤ መዋዕለ-ንዋያቸውን ያፈሳሉ። ይህም<br />

በሌላ ሀገር በጀት ሥር አመቺ መጠለያ<br />

እንዲያገኙ ይረዳቸዋል። ከሌላ አንጻር ሲታይ<br />

ደግሞ የኢጣሊያ ማፊያ ከ19ኛው መ/ክ/ዘመን<br />

መጨረሻ ጀምሮ በሌሎች ሀገራት ማለትም<br />

በቱኒዚያ፣ አሜሪካና በአውስትራሊያ እግሩን<br />

ለመትከል ስደት (immigration) እንደ አማራጭ<br />

ተጠቅሟል።<br />

እንደማጠቃለያ፤ እነዚህን ሁኔታዎች<br />

ከሀገራችንና ከአካባቢያችን ሁኔታዎች ጋር<br />

አያይዘን መመርመር ያስፈልጋል። በሀገራችን<br />

የገዢው ፓርቲ መሠረት፣ አያያዝና ባህርይ<br />

እንዲሁም የተቃዋሚ ፓርቲዎች ሁኔታ<br />

እንዴት ነው? ሕዝባዊ ተቋሞቻችንስ ምን<br />

ያህል ፅዱና ጠንካራ ናቸው? የጎረቤታችን<br />

መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ቡድኖችስ<br />

ምን ይመስላሉ? በእኛ ሀገር ተቋማትስ ላይ<br />

ምን ዓይነት ተፅዕኖ ያሳድራሉ?<br />

ከውጭ ሀገር መጥተው መዋዕለ-ንዋያቸውን<br />

የሚያፈሱ ባለኃብቶች ምን ዓይነት ናቸው?<br />

የጀርባ ታሪካቸውን በሚገባ እናውቃለን? ሀገር<br />

ውስጥ ከገቡስ በኋላ ባህሪያቸው እንዴት ነው?<br />

ከሀገራዊ ተቋማት ጋር ያላቸው መስተጋብር<br />

ምን ይመስላል? ሕግ አክባሪ ናቸው? አቋራጭ<br />

መንገድ ይመርጣሉ? ለምን? የእኛስ ዜጎች<br />

ራሳቸው ንብረት ለማፍራት በምን ዓይነት<br />

መንገድ ይሄዳሉ?<br />

በሕጎቻችንና በተለይ<br />

በሕገመንግሥታችን ውስጥ ራሱ ክፍተት አለ<br />

ወይስ የለም? ለምን? ግለሰቦች የሚደርስባቸውን<br />

ችግር ወይም በደል በአግባቡ ለባለሥልጣናት<br />

ወይም ሕግ ፊት ያቀርባሉ? ፍትህስ ያገኛሉ?<br />

ሃሳባቸውን ለመግለጽ በቂ አማራጮች<br />

አሏዋቸው? ለምን ሁነኛ ሀገራዊ ውይይት<br />

ማድረግ ይሳነናል? ለምን በዕርጋታና በሰላም<br />

ግልፅ ውይይት ማድረግ አልቻልንም? ብዙ<br />

ጊዜ የምንለዋወጣቸው ቃላት (በማሕበራዊ<br />

ኑሮ ውስጥ ባልና ሚስት ጎረቤት ለጎረቤት፣<br />

ዐለቃና ምንዝር፣ አግልግሎት ሰጪና ደንበኛ<br />

ወዘተ) በተለይ <strong>በኢህአዴግ</strong> ዘመን ከችግር<br />

የፀዱ ናቸው? ምንስ ያንፀባርቃሉ? እነዚህንና<br />

የመሳሰሉትን ሁኔታዎች በአግባቡ ማጤን ተገቢ<br />

ነው። ይህንንም ስናጤንና የሚያስፈልጉትን<br />

ማስተካከያዎች ስንከውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ<br />

በአንድ ወቅት ያሉትን - ዛሬ ረስተውት እንደሆነ<br />

አይታወቅም - ‹‹የተሻለ ኅብረተሰብ የመገንባት<br />

ጥማት›› እውን ማድረግ እንችላለን። እንደ’ኔ<br />

እመነት ይህ ደግሞ የሚጀምረው ከአለት<br />

መሰረታዊ ተቋማት ነው - ከቤተሰብ፣ ትምህርት<br />

ቤት እና ከዕምነት ተቋማት።<br />

በገበያ ላይ ውሏል<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

9<br />

ሰላም ለኢትዮጵያ፣<br />

ሰላም ለአፍሪካ!


10<br />

እንደመንደርደሪያ<br />

በሶላር ፊልም ፕሮዳክሽን ተዘጋጅቶ<br />

የቀረበ ፊልም ነው። ዘወትር ማክሰኞ<br />

በ8፣ በ10 እና በ12 ሰዓት በሲኒማ<br />

አምፒር በመታየት ላይ ይገኛል።<br />

የዚህ ፅሑፍ ዳሰሳ አቅራቢ ባለፈው ማክሰኞ<br />

ጥቅምት 14 ቀን 2004 ዓ.ም አመሻሽ 12<br />

ሠዓት በቦታው ታድሞ ነበር። ጥቂት ሰዎች<br />

ወደ አዳራሹ ለመግባት ሰልፍ ይዘዋል።<br />

በፈረንጅኛው ‹‹security›› የሚል ቃል<br />

የተፃፈበት ባለ ሎሚ ከለር የለበሰ ጎረምሳ<br />

ወጣት ሴቶችን እየለየ ከሰልፈኛው ቀድመው<br />

እንዲገቡ ያዛል። ይኼኔ ፊልሙ ‹‹ለማየት<br />

ሳይሆን ለመታየት ለወጡ ወጣት ሴቶች ብቻ<br />

ነው እንዴ የተዘጋጀው?›› ስል ራሴን ጠየቅሁ።<br />

እየገረመኝ የመጨረሻው ታዳሚ ሆኜ ገባሁ።<br />

12 ሰዓት ከ10 ደቂቃ ሆኗል። በሲኒማ<br />

አምፒር ታችኛው አዳራሽ በጣት የሚቆጠሩ<br />

ሰዎች አልፎ አልፎ ተቀምጠዋል። 12 ሰዓት<br />

ከ25 ደቂቃ ተጨማሪ ተመልካች አልገባም።<br />

‹‹ሳታማኻኝ ብላ›› የሚለው ሙዚቃ በአዳራሹ<br />

ውስጥ ይናኛል። ነገሩ እየገረመኝ ታችኛው<br />

አዳራሽ ውስጥ ያለውን ሰው መቁጠ ጀመርኩ።<br />

ከእኔ ጋር 45 ሰው ብቻ ታድሟል። ወዲያው<br />

የአዳራሹ መብራት ጨለመ። ፊቴን ወደ ነጩ<br />

መጋረጃ መለስኩ። ላይኛው መመልከቻ ስፍራ<br />

ስንት ሰው ሊኖር እንደሚችል ለመገመት<br />

እየሞከርኩ ‹‹አልሞትም›› የሚል ርዕስ በነጩ<br />

መጋረጃ ላይ ሲነጠፍ አየሁ። እንዴት ነው<br />

ነገሩ? ሲኒማ አምፒር መግቢያ በር ላይ<br />

በረዥሙ የተሰቀለው የፊልሙ ማስታወቂያ<br />

ላይ ያነበብኩት ‹‹ለአንተ ስል አልሞትም››<br />

የሚል ርዕስ ነው። የርዕሱ ርዝማኔ የሰዎችን<br />

የማየት ፍላጐት የሚያነሳሳ አይደለም እያልኩ<br />

ነበር፡- ለራሴ። የፊልሙ ጅማሬ ላይ የተገለፀልኝ<br />

ርዕስ ግን ‹‹አልሞትም›› ብቻ ነው፡፡ ምክንያቱ<br />

ምንድነው? … ቢሆንም ፊልሙን በትኩረት<br />

መከታተል ቀጠልኩ።<br />

የፊልሙ ጭብጥ<br />

ወደ ሲኒማ አምፒር ለሚገቡ ተመልካቾች<br />

በሚበተነው የፊልሙ ማስታወቂያ በራሪ<br />

ወረቀት ላይ የፊልሙ ዋነኛ ጭብጥ ‹‹ልብ<br />

ለሚነካ ህፃን ልጅ የተከፈለ መስዋዕትነት››<br />

መሆኑ ተገልጿል። ይሁን እንጂ የፊልሙ<br />

ዋነኛ ጭብጥ ከላይ የተገለፀው ነው ብሎ<br />

ለመቀበል ይቸግራል። የህፃኑ ልጅ ጉዳይ<br />

በንዑስ ጭብጥነት ሊገለፅ ይችል ይሆናል።<br />

የሆኖ ሆኖ እኔን እንደገባኝ የፊልሙ ዋንኛ<br />

ጭብጥ ወይም ማጠንጠኛ ነገረ ጉዳይ ወንጀል<br />

ነው። የተደራጀ ወንጀል። እንደው ከአጭርም<br />

በአጭሩ ጠቅለል አድርገን እንግለፀው ካልን<br />

‹‹ማፍያ›› ተብለው የሚታወቁት ወንጀለኞች<br />

ታሪክ ነው ብንል ፊልሙን የበለጠ<br />

ይገልፀዋል።<br />

ለዚህ አባባል መጠነኛ አብነት መጥቀስ<br />

ይቻላል። የፊልም ጥበብ ባለሙያዎች<br />

እንደሚሉት፤ የአንድ ፊልም ሁለንተናዊ<br />

ታሪክ ጭብጥ በሶስት ደቂቃ ውስጥ ተመልካች<br />

እንዲረዳው ማድረግ ያስፈልጋል። ከዚህ<br />

አንፃር ‹‹አልሞትም/ለአንተ ስል አልሞትም››<br />

የተዋጣለት መሆኑን አለመመስከር ንፉግነት<br />

ነው።<br />

ምነው ቢሉ ፊልሙ በታሪኩ ጅማሮ በ1994<br />

ዓ.ም ጅማ ላይ የተፈፀመን የተደራጀ<br />

ወንጀል፣ ከጦርነት ባልተናነሰ ቅልጥ ያለ<br />

ተኩስ ያሳየናል። በቅፅበት እዚያው ጅማ<br />

ውስጥ በ2000ዓ.ም የተፈፀመን ወንጀል<br />

ያስቃኘናል። ከዚያም ግንቦት 2 ቀን 1992<br />

ዓ.ም ወደተፈፀመ ድርጊት ይመልሰናል።<br />

ወዘተ… ከ3 ደቂቃ ባለበለጠ ጊዜ በድርጊት<br />

የታጀበ ሁነት በመመስረት ረገድ ብቃት አለው<br />

የምለው ለዚህ ነው። የታሪኩ ዋነኛ ጭብጥም<br />

ይኸው የተደራጀ ወንጀል መሆኑን የተጠቀሰው<br />

ክፍል በቂ ማሳያ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ፊልሙ<br />

በርካታ ግድፈቶችንም ያስተናገደ ነው። ወደ<br />

ግድፈቶቹ ከመሄዳችን በፊት ግን መልካም<br />

ጐኖችን ማበረታታት ያስፈልጋል።<br />

በዚህ ፊልም ውስጥ ሰለሞን ገብሬ፣ አድያም<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

ዓለም፣ ታጠቅ መለሥ፣ ፍሬህይወት<br />

ስዩም፣ ኤደን ሽመልስ፣ ቅዱስ አሰፋ፣<br />

ቢላል እንድሪስ፣ ሰለሞን ነጋሽና ሌሎችም<br />

በተዋንያንነት (Actors) ተሳትፈዋል። ሁሉም<br />

ተዋንያን ማለት ይቻላል፣ በተሰጣቸው ገፀ<br />

ባህሪያት መጠን (የተሰጣቸው ገፀ-ባህሪይ<br />

- ከኢትዮጵያውያን የህይወት ዕውነታ ጋር<br />

የተስማማ ባይሆንም) ኃላፊነታቸውን በሚገባ<br />

ተወጥተዋል። ችሎታቸውንም አሳይተዋል<br />

ማለት ያስደፍራል። በተለይ የህፃኑን ገፀ<br />

ባህሪይ ወርሶ የተጫወተው ታዳጊ ድንቅ ትወና<br />

ማሳየቱን መካድ አይቻልም።<br />

ይህም ብቻ አይደለም። ‹‹ለአንተ ስል<br />

አልሞትም›› ፊልምን የደረሰው ሰለሞን ገብሬ<br />

መሆኑ ከላይ ተጠቅሷል። ነገር ግን ድርሰቱን<br />

ወደ ስክሪፕት ፅሁፍ የለወጡት ብዙአየሁ<br />

እሸቱ እና አንዱዓለም ጌታቸው ናቸው።<br />

ድርሰቱን ወደ ፊልም ፅሁፍነት የቀየሩበት<br />

ስልት ሊደነቅ የሚገባው ነው። ምክንያቱም<br />

ለእያንዳንዱ ገፀ-ባህሪያት በቃለ ተውኔትነት<br />

የተጠቀሙበት አጠርና ቅልብጭ ያለ የቋንቋ<br />

አጠቃቀም ለፊልሙ የተሟላ ህይወት መልካም<br />

ድርሻ ማበርከቱ ይስተዋላል። እንዲያም ሆኖ<br />

ፊልሙ በበርካታ ችግሮች የተዋጠ ነው፡፡<br />

ችግሩ<br />

ፊልሙ ከአገራዊ ፊልም ጥበብ አንፃር<br />

ይመዘን ከተባለ ይህ ነው የሚባል ፋይዳ<br />

ቄሱም ዝም<br />

መጽሀፉም ዝም<br />

ሰውም ዝም<br />

ኑሮውም ዝም<br />

ሁሉም ዝም<br />

ከመዝ …ውአቱ።<br />

ሰላም ለኩልክሙ /ሰላም ለሁላችሁም/ መወድስ<br />

ባናቱ ከነምልዓተ ንባቡ ጋብዣችኋለሁ።<br />

መወድስ<br />

ፀላዕኩ ሰብዐ እምነ-ርዕስየ ዘትርጓሜሁ በቀል<br />

ወዘንባቡ ሀሰት፤<br />

እስመ እምልሳኑ ለሰብዕ አንተ ይበልኦመሬት፤<br />

ለፌትህትና ወለፌ ትዕቢት፤<br />

ይወጽኡ ለስብከት እንዘ በላዕሌሁ ይሔሉ እንተ<br />

ኢይተርፍ ሞት፤<br />

ለዓለም ወለዐለም<br />

ልብየሂ ለዕመጌሠ መንገለ-ሀተታ ገነት፤<br />

ባቲ ዘተጋበዐ ጥበባተ-ሰሎሞን ጽጌያት፤<br />

እሩያነኮኑ በሰምናዊት ሰዐት.<br />

ሰብዕ በዐመፃወእግዚአብሔር በምህረት፤<br />

ትርጉም<br />

ከራሴ ጀምሮ ሰውን ጠላሁ። ከሰው አንደበት<br />

የሚወጣው ነገር<br />

በሙሉ ትርጓሜው በቀል ነው ንባቡም ውሸት<br />

ነው።<br />

በዚህ ውሸት በዛኛው እውነት (ባንድ አፍ ሁለት<br />

ምላስ) ይዘው፣<br />

ለማስተማር ይወጣሉ የማይቀረው ሞት እያለ።<br />

እኔም በተመስጦ የሰለሞን ጥበባት ወደ ተከማቹባት<br />

የገነት ጓሮ ላይ ሆኜ ስመለከት የሰው ልጅና<br />

እግዚብሔር በስምንተኛው ሺህ አንድ ሆኑ<br />

የሰው ልጅ ያጠፋል<br />

እግዚአብሔር ይምራል<br />

(ኤዲያ)<br />

አዱኛው ላይሞላ<br />

ይወደስክ ብላ<br />

በተለምዶ በዘፈኑና በሥነጽሁፉ ባቲ የቆንጆ መዲና<br />

ስትባል እንሰማለን። ስለባቲም ያልተዘፈነ ዘፈን<br />

የለም ብዬ ብናገርም ማጋነን አይሆንብኝም።<br />

ከአራቱ ቅኝቶች መካከልም የባቲ ቅኝት አንዱ<br />

ነው።<br />

1. ትዝታ<br />

2. አምባሰል<br />

3. አንቺ ሆዬ<br />

4. ባቲ<br />

ይህን የምታነቡ በሙሉ ‹‹ባቲ›› ብዬ ስጀመር አገሩን<br />

ነው ወይስ ቅኝቱን? ብላችሁ አስባችሁ ይሆናል።<br />

ያወቃችሁ ደግሞ አውቀችኋል። ባቲ ማለት የግዕዝ<br />

ግስ ሲሆን ትርጉሙም ‘አላት’ ማለት ነው።<br />

ቦ፡- አለ ፤<br />

ቦቱ፡- አለው፤<br />

ባ፡- አላት፤<br />

አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />

አለው ማለት አይቻልም። ምነው ቢሉ<br />

የኢትዮጵያውያንን ህይወት፣ የአኗኗር ዘይቤ፣<br />

እምነት፣ አስተሳሰብና ማንነትን የሚያንፀባርቅ<br />

አይደለም። ማንነቱን የማያንፀባርቅ የጥበብ<br />

ስራ ደግሞ የሞተ ነው። ከባህር እንደወጣ አሳ፣<br />

ህይወት አልባ ነው የሚሆነው። የጥበብ ሰው<br />

ደግሞ ያልኖረበትን ዓለም መጠበብ አይችልም።<br />

ባልኖሩበት አለም ልጠበብ ማለት (ጥበበኛ ነኝ)<br />

ማለት ከመቃዠት ተለይቶ አይታይም።<br />

ባቲ፡- አላት፤<br />

የዶሮ እርባታ የማርባቱ አቅም<br />

ባይኖረኝም ባቲ በሚለው የግዕዝ ቃል<br />

እርባታውን አረባላችኋለሁ።<br />

አጽምኡኒ<br />

ስሙኝ<br />

አጽምኡኒ<br />

ስሙኝ<br />

አዱኛው ላይሞላ<br />

እያወደስክ ብላ<br />

ባ…ባተ ለዛቲ ብእሲት እንትን<br />

ለዚያች ሴቲዮ እንትን አላት<br />

አለላት<br />

አለባት<br />

ኖራት ኖረላት ኖረባት<br />

ነበራት ነበረላት ነበረባት<br />

ይኖራታል ይኖርላታል<br />

ይኖርባታል<br />

ይኑራት ይኑርላት ይኑርባት<br />

“ምንድነው ያላት?”<br />

አይ ምንም ነገር የላትም። ዝም ብዬ ግስ<br />

እያረባሁ ነው።<br />

“ሰው ዶሮ ያረባል አንተ ግስ ታረባለህ?<br />

አይደል?”<br />

ተይዟል።<br />

“ምኑ?”<br />

ዶሮው።<br />

“ከብቱስ፣ በጉስ፣ አሳማውስ?”<br />

ዝኒከማሁ (ይህም እንደዚያኛው<br />

ነው) ተይዟል።<br />

p Ç T@<br />

ማፍያዎቹ ፊልመኞች በ‹‹ለአንተ ስል አልሞትም››<br />

የፊልሙ ርዕስ፡- ‹‹ለአንተ ስል አልሞትም››<br />

የፊልሙ ደራሲ፡- ሰለሞን ገብሬ<br />

የፊልሙ ዘውግ፡- አክሽን<br />

የፊልሙ ዳይሬክተር፡- ታጠቅ መለሰ<br />

ፊልሙ የሚፈጀው ጊዜ፡- 1፡40 ሰዓት<br />

በንፍታሌም<br />

በከመ-ይቤ ቅዱስ ኤፍሬም ባለቅኔ<br />

የገዘፈው የፊልሙ ደካማ ጐን<br />

‹‹ለአንተ ስል አልሞትም›› የተሰኘው ይህ<br />

ፊልም ግዙፍ ደካማ ጐን የታሪኩ መዋቅርና<br />

ሁለንተናዊ ይዘት የኢትዮጵያዊያንን ህይወት<br />

የማይወክል መሆኑ ነው ብዬ አምናለሁ።<br />

ምክንያቱም የ‹‹ማፍያ››ዎችን የተደራጀ ወንጀል<br />

ነው የሚያሳየው። በአጠቃላይ የፊልሙ ይዘት<br />

ፊልም ሰሪዎቻችን ‹‹ማፍያዎች›› መሆናቸውን<br />

በገሃድ ያሳዩበት ነው ብል ማጋነን አይሆንም።<br />

አንድ፣ ፊልሙ እንደጣሊያን ሲሲሊያኖች<br />

ማፍያዎች የረቀቀና የተደራጀ ወንጀል መፈፀምና<br />

በዘረፉት ብር ወይም ወርቅ የተነሳ- ግጭት<br />

ውስጥ መግባት ላይ ያጠነጠነ ነው። ፊልሙ<br />

እርስ በእርስ መታኮስ፣ መጠዛጠዝ፣ እርስ በርስ<br />

መሸዋወድ ወዘተ ነው። ፊልሙ በረቀቀ ስልት<br />

ወንጀለኞቹ እርስ በርስ ሲቀጣቀጡና ሲናረቱ..<br />

ወዘተ የሚያሳይ ነው። ከጅማ እስከ አዲስ<br />

አበባ በተዘረጋ የወንጀል መረብ፤ ሰዋራ ቦታ<br />

ላይ፣ ጅምር ህንፃ <strong>ስር</strong>… ወዘተ መቀጣቀጥና<br />

መታኮስ፣ እንደገና መቀጣቀጥና መታኮስ ብቻ<br />

ነው የሚያሳየው፡፡ መርማሪ ፖሊስን ቤቱ ድረስ<br />

ሄዶ አንገቱን መቀንጠስም ያካትታል። ብላ!<br />

ብላ! ብላ!<br />

ሌሎች ሁኔታዎችን እንጥቀስ ካልን የፊልሙን<br />

ሙሉ ታሪክ መነስነስ ሊሆንብን ነውና<br />

ባቲ<br />

ተውነው። የሆኖ ሆኖ ግን ፊልሙ ከውጭ<br />

<strong>አገር</strong> የማፍያ ፊልሞች ሙሉ በሙሉ የተኮረጀ<br />

ወይም የተገለበጠ መሆኑን ለመረዳት ነብይ<br />

መሆን አያስፈልግም።<br />

ችግሩ የፊልሙ ታሪክ ወንጀል ላይ<br />

መመስረቱ አይደለም። እንዲህ አይነቱ<br />

በቡድን የተከፈለና ከጦርነት ያልተናነሰ ተኩስ<br />

የሚተኮስበት ለመንግስትም ፈታኝ የሆነ<br />

የወንጀል ተግባር ላይ አገራችን የደረሰች<br />

አይመስለኝም። አልደረሰችምም፡፡ የፈረንጆቹን<br />

ሴራ (በቋንቋ) ለውጥ ብቻ የእኛ <strong>አገር</strong><br />

ታሪክ አስመስሎ ማቅረብ ደግሞ ይቅር የማ<br />

ይባል ሃጢያት ነው።<br />

ኩረጃ እና ኮራጅ<br />

ኩረጃ በየትኛውም ዘርፍ የሚነቀፍ አይደለም፡<br />

፡ የኮራጅ ተግባር ነው ኩረጃን ፍፁም ወንጀል<br />

የሚያደርገው። ሁሉንም ነገር ከራስ ፀጉሩ እስከ<br />

እግር ጥፍሩ መኮረጅ ጤንነት አይደለም።<br />

በአንድ ወቅት አንድ አባት ያሉኝ ነገር እዚህች<br />

ላይ ትዝ አለችኝ ‹‹መስረቅ ፍፁም ወንጀል<br />

የሚሆነው፣ ሁሉንም ነገር አግበስብሶ ለመውሰድ<br />

ሲሞከር ነው። የዝርፊያ ጥሩ ባይኖረውም<br />

ከማግበስበስ ይልቅ እንጥፍጣፊውን መውሰድ<br />

ነው የሚሻለው›› ነበር ያሉኝ። የእኛ <strong>አገር</strong><br />

የፊልም ጥበብ እንደማፍያዎቹ ሙሉ በሙሉ<br />

የመገልበጥ ያህል መሆኑ ነው የሚያሳዝነው።<br />

ይህም ፊልም ሆኖ፣ ይህም ፊልም ተብሎ፣<br />

ወጣት ሴቶች የፊልም ተመልካቹን ክብር<br />

እየጣሱ ቀድመው ወደ ባዶው አዳራሽ እንዲገቡ<br />

በማድረግ አድልዎ ለመፈፀም መሞከሩ ነው<br />

የሚያሳዝነው፡፡ ሌላው ሌላው ቢዘረዘርማ ችግሩ<br />

የትየለሌ ነው፡፡<br />

(አላት፣ አለላት)<br />

“አይ … ሁሉም ከተያዘ ለምን ሰው<br />

አታረባም?”<br />

የሚረባ ሰው የለም።<br />

“እንዴት?” (መሬት ዐንተ ወትገብዕ<br />

ውስተመሬት)<br />

አፈር ነህና ወደአፈር ትመለሳለህ ስለሚል።<br />

ፍሬ ከርስኪ ነው። ሁሉም ከወሬ የዘለለ ነገር የለውም።<br />

እና … ሁሉም ሰው አይረባም እያልክ ነው?<br />

አዎ ከራሴ ጀምሮ አይረባም።<br />

“አንተስ? ረብተሀል?”<br />

በግሱ ረብቻለሁ፤ በገንዘቡ ግን አረባሁም።<br />

“እስኪ አንድ ነገር ልጠይቅህ፤ አንድ ሰው ይረባል ለማለት<br />

ምን ያስፈልገዋል?”<br />

ያው ገንዘብ ነው። ገንዘብ ካለህ ትረባለህ። ገንዘብ ከሌለህ<br />

ደግሞ አትረባም። አለም ወዳላቸው እንጂ ወደሌላቸው ፊቷን<br />

አታዞርም።<br />

“ገንዘብ ሥትለኝ ያልገባኝ ነገር አለ። ገንዘብ ማለት በእጅ<br />

የሚቆጠረው ወረቀት ማለት ነው?”<br />

እንዴታ! እሱንማ ካልያዝክ ማን እጅ ይነሳሀል? ማንስ<br />

ያከብርሀል? ኧረ ተወኝ ሁሉም ሰው ከቁብም አይቆጥርህ።<br />

“እንዴ ምንድነው የምትለው? የሰው ልጀ ከብር አይበልጥም<br />

እንዴ?”<br />

መብለጥ እንኳን ይበልጣል። የሰው ልጅ ተገዢ ሲሆን ብር<br />

ደግሞ ገዢ ነው። አንድ ብር ላይ ገዢ የሚል ቃል አይተህ<br />

አታውቅም?<br />

“ገዢማ የፈጠረን አምላክ ነው። እንዴት ብር ገዢ<br />

ይሆናል?”<br />

ኤዲያ . . . አምላክንም ገዝቶታል።<br />

“እንዴት አርጎ?”<br />

ለጌታም ጌታ አለው<br />

ገንዘብ ጌታ ሆኖ ጌታን አንገላታው<br />

እና ገንዘብ ይሉሀል ይሄ ነው። ሰላሣ ዲናር ባይኖር አምላክ<br />

ባልተሸጠ፤ ሻጭና ገዢም ባልኖረ። ለዚህ እኮ ነው ባሪያ<br />

ለሁለት ጌቶች መገዛት ይቻለዋልን? ተብሎ ይተፃፈው።<br />

ከር … ከር … ከር ብሎ ሲስቅ፣<br />

ተው አትሳቅ<br />

ለምን?<br />

ሳይኖርህ መሳቅ<br />

ይሆንብሀል መሳቀቅ<br />

አዱኛው ላይሞላ<br />

እያወደስክ ብላ


አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />

S ´ “ —<br />

መዝናኛ ዜና<br />

ብሌን ፊልም ነገ<br />

ይመረቃል<br />

በኢዮብ ተስፋዬ ተደርሶ በአንተነህ<br />

ሞትባይኖር የተዘጋጀውና ፕሮዲዩስ የተደረገው<br />

ብሌን ፈልም ነገ እና ከነገ ወዲያ በአዲስ አበባና<br />

በክልል ከተሞች በሚገኙ በርካታ ሲኒማ ቤቶች<br />

ይመረቃል። 1፡40 ሰዓት ርዝማኔ ያለውና የፍቅር<br />

ታሪክ ላይ የሚያጠነጥነው ብሌን ፊልም ተሰርቶ<br />

ለመጠናቀቅ 11 ወራትን ወስዷል። በፊልሙ ላይ<br />

ሰላማዊት ብርሀኑ፣ ኢዮብ ተስፋዬ፣ ትዕግስት<br />

ይልማ፣ አንተነህ ሞት ባይኖር፣ ወይሰው አንተነህ፣<br />

አብነት ዳግምና ሌሎችም ተሳትፈውበታል።<br />

እጃቢ ሙዚቃው በአክሊሉ ተዋበ<br />

የተቀናበረውና አማን ተስፋዬና ዮዲት ወርቁ<br />

በድምፅ የተሳተፉት ብሌን ፊልም በአንዲት ወጣት<br />

ዙሪያ የሚደረግ የፍቅርና የጥቅም መስዋዕትነትን<br />

የሚያሳይ ሲሆን ወጣቷ ቤተሰቦቿንና የአይን<br />

ብርሀኗን በአደጋ በማጣቷ የሚያፈቅራት ወጣት<br />

በአስገራሚ ሁኔታ በሚያደርግላት እንክብካቤና<br />

በአክስቷ ልጅና በፍቅር ጓደኛዋ በሚደርስባት በደል<br />

ላይ የሚያጠነጥን እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።<br />

በሲ.ኤል.ዲ ፊልም ፕሮዳክሽን የቀረበው<br />

ብሌን ፊልም በዋናነት በአዲስ አበባ ስብሰባ ማዕከል<br />

ከቀኑ በ10 ሰዓት በድምቀት እንደሚመረቅም<br />

ለማወቅ ችለናል።<br />

ምራኤል የስኬት<br />

ት/ቤት በአመለካከት<br />

ለውጥና በስኬት ዙሪያ<br />

ውይይት ያካሂዳል<br />

ምራኤል ኢንተርናሽናል የስኬት ት/ቤት<br />

በአመለካከት ለውጥና በስኬት ዙሪያ በ<strong>አገር</strong> አቀፍና<br />

በግለሰብ ደረጃ እንዴት መተግበር እንደሚቻል<br />

የሚያመላክት ውይይት ዛሬ ረፋዱ ላይ በብሔራዊ<br />

ቴአትር ያካሂዳል። እንደ ድርጅቱ መግለጫ ት/<br />

ቤቱ እስካሁን በግለሰብም ሆነ በ<strong>አገር</strong> አቀፍ ደረጃ<br />

ህብረሰቡ የተዛባን አመለካከት በመለወጥ እንዴት<br />

ወደ ስኬት መድረስ እንደሚችል በማሰልጠንና<br />

በርካታ ስልቶችን በማመላከት እየሰራ መሆኑን<br />

ገልጾ፤ በዛሬው ዕለትም በሚያካሂደው ውይይት ላይ<br />

በዘርፉ ውጤት የሚመጣበትን መንገድ ይፈጥራል<br />

ተብሎ ይጠበቃል።<br />

ምራኤል ኢንተርናሽናል በነገው እለት<br />

ከውይይቱ በተጨማሪ እስከዛሬ ያከናወናቸውን<br />

ፍሬያማ ተግባራት መግለፅ፣ በቅርቡ ሚያስገነባውን<br />

የህንፃ ዲዛይን ማስመረቅ፣ በምራኤል ሰልጥነው<br />

ለውጤት የበቁ ምስክሮችን መስማት፣ የማያቋርጥ<br />

ደስታን መፍጠር የሚያስችሉ 10 ሚስጥሮችን<br />

ማሳወቂያ ስልጠና መስጠት፣ በኢትዮጵያ ላይ<br />

በአስተሳሰብ እና በስራ ፈጠራ ላይ ሰፊ ስራ የሰሩ<br />

ግለቦችን መሸለምና የምራኤል ምርጥ ውጤታማ<br />

ተማሪዎችን መሸለም ከፕሮግራሙ ውስጥ<br />

ተካተዋል። በእለቱ ይህን ውይይት ፍላጎት ያላቸው<br />

እንዲካፈሉበት ምራኤል የጋበዘ ሲሆን በእለቱ ታዋቂ<br />

ሰዎች ጋዜጠኞችና ጥሪ የተደገላቸው የመንግስት<br />

ኃላፊዎችና የምራኤል ት/ቤት ማህበረሰብ በውይይቱ<br />

ይታደማሉ ተብሎ ይጠበቃል።<br />

በሬዲዮ ድምፅሽን የሚሰሙ በአካል ሲያገኙሽ<br />

ምን ይሉሻል?<br />

በጣም ነው የሚደነግጡት። ቢሮ<br />

መጥተው እንግዳ መቀበያ ላይ ለተለያየ የስራ<br />

ጉዳይ ስንቀሳቀስ ‹‹ቲጂ የለችም›› ብለው<br />

ይጠይቁኛል። ‹‹እኔ ነኝ›› ስላቸው በፍፁም<br />

አያምኑኝም። የሚያስቡኝ ትልቅ ሴት አድርገው<br />

ነው። እንደምታየኝ ትልቅ ሴት አይደለሁም<br />

አይደል? [ሳቅ] ለሙያው ትንሽ ፈጠን ብያለሁ<br />

መሰለኝ።<br />

አርባ ስንት ዓመትሽ ነው?<br />

[ሳቅ] 27 ዓመቴ ነው።<br />

ህይወትን በስነ-ልቦና አረዳድ እንዴት ታያታለሽ?<br />

እኔ ህይወትን በስነ ልቦና መነፅር<br />

ስመለከታት ይመስለኛል ጥያቄህ…<br />

ትክክል!<br />

ከራሴ እይታ ብናገር ደስ ይለኛል።<br />

እዚህ ህይወት ውስጥ ከገባሁ ጀምሮ የተረዳሁት<br />

ነገር የማትጠብቀውን ነገር ጠብቅ (Expect the<br />

Unexpected) የሚለውን መርህ ነው። በስራ<br />

ላይ እንደ ባህላችሁን ቡና ስንጠጣ ከምንሰማቸው<br />

ወሬዎች በጣም የዘለሉ ጉዳዮች ይመጣሉ። ስለዚህ<br />

ሁሌም ጠዋት ስነሳ የማይጠበቅ፣ ከአቅሜም<br />

በላይ የሆነ ነገር ሊመጣ እንደሚችል ከሙያው<br />

ተረድቻለሁ።<br />

ከአቅምሽ በላይ [በአንቺ የምክር አገልግሎት<br />

ሊያገግሙ የማይችሉ የምትያቸውን] የሆኑ<br />

ችግሮችን ያዘሉ ደንበኞች ሲመጡ ምን<br />

ታደርጊያለሽ?<br />

የስነ-አዕምሮ ሐኪም (ሳይካትሪስት)<br />

የሚያያቸውን ወይም መድኃኒት መጠቀም የደረሱ<br />

ደንበኞችን አንመለከትም። የምንሰራው ከመድኃኒት<br />

ወዲህ ያሉ ሰዎች በቀን ተቀን ኑሯቸው ላይ<br />

የሚያጋጥማቸው ችግሮች ላይ መፍትሄ የማምጣት<br />

ስራ ነው።<br />

ስራው እንዲህ ዘና ብዬ እንደማወራህ<br />

ቀላል አይደለም። በስነ-ልቦና ዓለም የገባኝ ትልቁ<br />

ምስጢር ችግሩ ከባድም ቢሆን ራስን እዚያ ሰው<br />

ጫማ ውስጥ አድርጎ መመልከትን ነው። እኔጋ<br />

ዓለማዊ ወግ<br />

በውሂብ<br />

1<br />

ከያዘ የማይለቅ ሞኝ እና ወረቀት ነው<br />

ይባላል። ከዚሀ በኋላ ግን የኔታም ቢጨመሩበት ደስ<br />

ይለኛል። እና እንዲህ ይባል፡- ከያዘ የማይለቅ የኔታና<br />

ወረቀት ናቸው። አሰለቹኝ። ልንማርበት ከነበረው ዛፍ<br />

ሥር ተነስቸ ወጣሁ።<br />

የግብጽ ጳጳሳትን ሰምተው በዓላትን<br />

ያወጁ ካህናት ትሩፋት የሆኑ ትላልቅ ዛፎች<br />

ቤተክርስቲያኑን ወረውታል። በዓላት ባይኖሩ ኖሮ፣<br />

እንደ ኢትዮጵያውያን ደን የማውደም ፍቅር ይሄኔ<br />

አንድም ዛፍ ባልተገኘ ነበር።<br />

አፍታ<br />

በፋና ኤፍ ኤም 98.1 በሚተላለፉ አዲስ መንገድ እና የእርቅ ማዕድ<br />

በተሰኙ የስነ-ልብዎና ፕሮግራሞች ላይ በምታቀርባቸው ስነ ልቦናዊ<br />

ትንታኔዎች በርካታ አድናቂዎች አሏት። የአስተሳሰብ እና የአዕምሮ<br />

ሂደቶችን ስለሚያጠናው የሳይንስ ዘርፍ (Psychology) እና ስለ ሌሎች<br />

ነጥቦች ‹‹ቲጂ›› አንዳፍታ ቆይታ አድርጋለች፤ ከአቤል ዓለማየሁ ጋር።<br />

‹‹የቤት እንስሳት<br />

ያስባሉ ብዬ አምናለሁ››<br />

ትዕግስት ዋልተ ንጉስ [የስነ-ልቦና ባለሙያ]<br />

በስነ-ልቦና ዓለም የገባኝ ትልቁ<br />

ምስጢር ችግሩ ከባድም ቢሆን ራስን<br />

እዚያ ሰው ጫማ ውስጥ አድርጎ<br />

መመልከትን ነው። እኔጋ የሚመጡ<br />

ሰዎች ‹‹ተበድያለሁ›› ብቻ ሳይሆን<br />

‹‹በድያለሁም›› የሚሉ ናቸው።<br />

ሚስቱን የጎዳ፣ ልጆቹን ያስራበ፣<br />

ወዳጁን በጣም ያስከፋ፣ ገንዘብ<br />

የቀማ ይመጣል።<br />

የሚመጡ ሰዎች ‹‹ተበድያለሁ›› ብቻ ሳይሆን<br />

‹‹በድያለሁም›› የሚሉ ናቸው። ሚስቱን የጎዳ፣<br />

ልጆቹን ያስራበ፣ ወዳጁን በጣም ያስከፋ፣ ገንዘብ<br />

የቀማ ይመጣል። ከውጪ ሆነህ ከተመለከትከው<br />

ርህራሄ የጎደለው ስራ ስለሰራ ሰውዬው ራሱ<br />

ያናድድሀል።<br />

በአዕምሯችን የሚመጡ በጎ እና መጥፎ ሀሳቦች<br />

(Positive & Negative Thoughts) መነሻ ምን<br />

እንደሆነ ልትነግሪኝ ትችያለሽ?<br />

እንደየሰዉ ይለያያል። ይጠቅምህ<br />

እንደሆነ ባላውቅም አንድ መሰረተ ሀሳብ አለ፤<br />

ከቤተክርስቲያኑ ፈንጠር ብሎ ከምጣድ<br />

እንደተፈናጠረ ፈንድሻ ብትንትን ያሉ ጎጆዎች አሉ።<br />

እኒህን ቤቶች ሳይ አንድ ነገር ይታሰበኛል። መቼም<br />

ሀገራችን ብዙ ሥልጣኔዎችን በማምጣት ግንባር<br />

ቀደም እንደሆነች የታወቀ ነው። የዘመናዊ አፓርታማ<br />

እሳቤንም ያመጣችው ሀገራችን ናት። ለዚህም ማሳያው<br />

እኒህ ጎጆዎች እንደሆኑ ይሰማኛል። ብናስጎበኛቸው<br />

ሊያዋጣን ይችላል እያልኩ አስባለሁ።<br />

ሌላ ማረፊያ<br />

ዲያቆን አስማማው ጓደኛዬ ነው። አብረን<br />

እንማራለን። እሱ ግን እየዞሩ ቁራሽ እንደመለመን<br />

ስሜት የሚሰጠው ነገር የለም። ተማር ከሚሉት<br />

ጎጃምን እያካለልክ ቁራሽ ለምን ቢሉት ይዋጣለታል።<br />

በ ገፅ 18<br />

11<br />

ማሰብ፣ ስሜትና ድርጊት የሚል። ‹‹እከሌን<br />

እገለዋለሁ›› የሚል ሰው ነገሩ ሁሉ የሚጀምረው<br />

ከአስተሳሰቡ ነው። ሰባት ቢሊየን የሚሆን የዓለም<br />

ህዝብ ስላለ የዚያን ያህል የተለያየ ስብዕና አለ።<br />

እኔ እና አንተ፣ ቢጫ እና አረንጓዴ የተቀባ ግርግዳ<br />

ብናይ አንተ ቢጫ እኔ ደግሞ አረንጓዴ ሊታየኝ<br />

ይችላል። ነጥቡ የአመለካከት ነው። ተፈጥሯችን<br />

የተለያየ ስለሆነ ነገሮችን የምንተረጉምበት መንገድ<br />

ይለያያል። ዘረ-መል፣ ተፈጥሮ፣ አስተዳደግና<br />

የምትኖርበት ማህበረሰብ በአስተሳሰብህ ላይ ተፅዕኖ<br />

አለው። ጥሩው ነገር ግን ሁሉም መስተካከል<br />

መቻሉ ነው።<br />

ስብሰባ ላይ ተቀምጠን በሚሰጥ አስተያየት<br />

ወይም በዜና ማሰራጫዎች በሰማነው መረጃ ላይ<br />

ተቃርኗዊ አረዳድ/የተለየ አመለካከት ይኖረናል።<br />

ይህ ለምን ይመስልሻል?<br />

ይህ አንተን ብቻ ሳይሆን ሁላችንንም<br />

የሚያስገርም ነገር ነው። በአንድ ወቅት በአንድ<br />

አይነት መንትዮች (Identical Twins) ላይ ጥናት<br />

ተደርጎ ካልተሳሳትኩ 23.8 በመቶ የስብዕና ልዩነት<br />

አላቸው። ስለሆነም ጥያቄውን እኔ ራሴ መመለስ<br />

ያቅተኛል።<br />

እንደማስበው ግን ባህሪ ብቻ ሳይሆን<br />

ተፈጥሮም የምትጫወተው ሚና አላት ብዬ<br />

አስባለሁ። ይዘን የምንወለደው ነገር እንዳለ ሆኖ<br />

አካባቢም ተፅዕኖ አለው። የሰው ልጅ ስብዕና<br />

የሚቀረፀው ከዜሮ እስከ ሰባት ዓመት ነው<br />

ተብሎ ስለሚታመን የአስተሳሰብ ባለሙያዎች<br />

(Behaviorist) ‹‹አንድ የተወለደ ህፃን አምጣልኝ።<br />

ከፈለግክ ሌባ፣ ዶክተር፣ አርክቴክት…<br />

ጎጆው ወስጥ ተኝቷል። ‹‹በሶ ልስጥህ?›› አለ<br />

ከመድረሴ። የበሶ ጭብጦ እየጎመደ ነበር። ትምህርት<br />

ቤት ለምን እንዳልሄደ ስጠይቀው ጭብጦውን በውኃ<br />

አወራረደና፣ ‹‹ለዚች ሀገር ቅስና ሳይሆን ቅድስና<br />

ነው የሚያስፈልጋት›› አለኝ።<br />

በእውነቱ ከሆነ የአስማማውን ፈላስፋነት<br />

ዛሬ ነው ያወቅሁት ማለት ይቻላል።<br />

‹‹ቅስና ትልቀ ነገርማ ቢሆን ኖሮ<br />

የወላጆችህ ትዳር በቄስ ምክንያት ባልደፈረሰ ነበር››<br />

አለ። የምጠላውን የእናቴን ስም እንዳያነሳብኝ ፈራሁ።<br />

ዘነበች . . . ዘነበች . . . አሁን ይህ የሰው ስም<br />

ነው?<br />

‹‹ስለየኔታ የሰማኸው አለ?›› አልኩት።<br />

በ ገፅ 21<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ


12<br />

አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />

መቆሚያ ያጣው የዋጋ ግሽበት<br />

በሱራፍኤል ግርማ<br />

ከጊዜ ወደ ጊዜ በመሻሻል ፋንታ<br />

በመባባስ ላይ የሚገኘው የዋጋ<br />

ግሽበት፣ ማዕከላዊ ስታቲስቲክስ<br />

ኤጀንሲ ይፋ ባደረገው መረጃ<br />

መሰረት በመስከረም ወር<br />

2004 ዓ.ም 40.1 በመቶ ሆኖ<br />

ተመዝግቧል። 40.1 በመቶ<br />

የአጠቃላዩ የዋጋ ግሽበት ልኬት<br />

ይሁን እንጂ፣ ለኢትዮጵያውያን<br />

ኑሮን ፈታኝ በማድረግ ቀጣይ<br />

ዕጣ ፈንታቸውን አደጋ ውስጥ<br />

የከተተው የምግብ ዋጋ በተናጥል<br />

የ51.3 ጭማሪ ነው ያሳየው።<br />

በየወሩ በሚያገኙት ቋሚ ገቢ<br />

ብቻ የሚተዳደሩ፣ ጡረተኞች<br />

እንዲሁም በአነስተኛ የዕለት ገቢ<br />

ኑሯቸውን የሚመሩ ላብ አደሮች<br />

በዋጋ ግሽበቱ በተለይም ደግሞ<br />

በምግብ ዋጋ መናር ከፍተኛ ጉዳት<br />

ደርሶባቸዋል፡፡<br />

ምንጩ ምንድን<br />

ነው?<br />

ከ2003 ዓ.ም አጋማሽ አንስቶ<br />

በአስደንጋጭ ሁኔታ ጭማሪ<br />

በማሳየት አሁን ያለበት ደረጃ<br />

ለደረሰው ተከታታይና ባለሁለት<br />

አኃዝ ግሽበት መንግስት የተለያዩ<br />

ምክንያቶችን አስቀምጧል።<br />

<strong>አገር</strong> ውስጥ ለተከሰተው ግሽበት<br />

በዋና ምክንያትነት በመንግስት<br />

የተፈረጀው በዓለም አቀፍ ገበያ<br />

የተከሰተው የዋጋ ግሽበት ነው።<br />

የዓለም ኢኮኖሚ ከማንሰራራት<br />

ይልቅ ይበልጥ የመቃወስ አቅጣጫን<br />

ይዞ እየተጓዘ ባለበት ወቅት፣<br />

በመካከለኛው ምስራቅ የፈነዳው<br />

‹‹የዓረብ አብዮት›› በነዳጅ ዋጋ<br />

ላይ ጭማሪ እንዲመጣ ማድረጉን<br />

የሚገልፀው መንግስት፣ ‹‹ስለዚህ<br />

የነዳጅ ዋጋ መቀጠልን ተከትሎ<br />

የሌሎች ሸቀጦችም ዋጋ ቀጥሏል››<br />

በማለት ለግሽበቱ ዋና ምንጭ ነው<br />

ያለውን ሁኔታ ይገልፃል።<br />

ምንም እንኳን መንግስት በ<strong>አገር</strong><br />

ውስጥ ለሚስተዋለው እጅግ<br />

ከፍተኛ የሆነ የዋጋ ግሽበት<br />

በዋና ምክንያትነት በዓለም አቀፍ<br />

ገበያ የተስተዋለውን የዋጋ ንረት<br />

በመጥቀስ ‹‹እዚህ ያለው ከውጭ<br />

የገባ ግሽበት (imported inflation)<br />

ነው›› ቢልም፣ በዚህ በርካቶች<br />

አይስማሙም።<br />

ፖለቲከኛና የምጣኔ ሐብት<br />

ትምህርት የተከታተሉት አቶ ገብሩ<br />

አስራት አሁን እየተስተዋለ ላለው<br />

የዋጋ ግሽበት ዋና መንስኤው<br />

መንግስት ያለ ገደብ ከብሔራዊ<br />

ባንክ ተበድሮና አሳትሞ ያሰራጨው<br />

የገንዘብ መጠን ከልክ በላይ<br />

መብዛትና የምርት መጠን መቀነስ<br />

መሆኑን በመግለፅ ይሞግታሉ።<br />

ለአጠቃላዩ የዋጋ ግሽበት<br />

መጨመር ከፍተኛውን አስተዋፅዖ<br />

ያበረከተው እዚሁ <strong>አገር</strong> ውስጥ<br />

የሚመረተው ምግብ መሆኑን<br />

በማስታወስ የመንግስትን ‹‹ከውጭ<br />

የገባ ግሽበት›› መከራከሪያ ውድቅ<br />

የሚያደርጉት አቶ ገብሩ፣ ‹‹የምግብ<br />

ዋጋ የናረው <strong>አገር</strong> ውስጥ በቂ<br />

ምርት ስለሌለ ነው›› ይላሉ።<br />

የንግድ አስተዳደር ባለሙያ የሆኑት<br />

አቶ ተመስገን ዘውዴ ከመንግስት<br />

በኩል በተደጋጋሚ የሚደመጠውን<br />

‹‹ከውጭ የገባ ግሽበት›› ዕሳቤ፣<br />

ከጠቅላይ ሚኒስትሩ በተዋረድ<br />

ወደታች እንዲወርዱ የሚደረጉ<br />

ቃላትና ፅንሰ-ሐሳቦች አንድ አካል<br />

አድርገው ይወስዱታል። የነዳጅ<br />

ዋጋ መቀጠል የሚያመጣው የዋጋ<br />

መናር እንዳለ ሆኖ፣ የኢትዮጵያ<br />

ኢኮኖሚ በዓለም አቀፍ ገበያ ካለው<br />

እጅግ አነስተኛ ድርሻ የተነሳ ከውጭ<br />

በሚገባ ግሽበት ማመካኘቱ ወደራስ<br />

ለመመልከት ፈቃደኛ ካለመሆን<br />

እንደሚመነጭ የሚያስገነዝቡት<br />

የንግድ አስተዳደር ባለሙያው፣<br />

ችግሩ የመነጨው ከምርት ዕጥረት<br />

መሆኑን የሚናገሩት አስረግጠው<br />

ነው።<br />

የምግብ ዋጋ ግሽበት የተከሰተው<br />

ከምርት እጥረት የተነሳ መሆኑንና<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

ገንዘብ ያለገደብ የሚጨመርበት ኢኮኖሚ ለጊዜው ያደገ<br />

እንደሚመስል ፊኛ ነው ‹‹ፊኛ ውስጥ አየር ሲጨመር<br />

የፊኛው መጠን ይተልቃል፤ አየሩ ፊኛው ከሚችለው<br />

በላይ ሲሆን ግን ፊኛው መፈንዳቱ አይቀርም››<br />

አቶ ተመስገን ዘውዴ<br />

ይህ ኹነትም የግብርና ምርት<br />

የ11 በመቶ ዕድገት እንዳስመዘገበ<br />

መንግስት የሰጠውን መግለጫ<br />

ጥያቄ ውስጥ እንደሚከተው<br />

ከገለፁት ሁለቱ ባለሙያዎች<br />

በተጨማሪ ሌሎችም ተመሳሳይ<br />

አስተያየት ሰንዝረዋል።<br />

‹‹ግሽበት›› የሚለው ቃል አሁን<br />

የሚስተዋለውን ኹኔታ በሚገባ<br />

እንደማይገልፀውና ከምርት<br />

እጥረት የተነሳ ለተከሰተው የዋጋ<br />

ግሽበት ያለተቆጣጣሪ የሚያድገው<br />

የሕዝብ ቁጥር አስተዋፅኦ<br />

እንዳለው የሚናገሩት በዓለም<br />

ባንክ ውስጥ በኢኮኖሚስትነት<br />

ያገለገሉት አቶ ቡልቻ ደመቅሳ<br />

ናቸው፡፡ በ<strong>አገር</strong> ውስጥ በአነስተኛ<br />

ደረጃ የሚመረተው ምግብ አሁን<br />

ያለውን ሕዝብ መመገብ እንዳልቻለ<br />

የሚያስረዱት አቶ ቡልቻ፣<br />

የ‹‹የሕዝብ ቁጥር እንዳይጨምር<br />

የመከላከል እርምጃ አልወሰደም››<br />

በሚሉት መንግስት ላይ ሙሉ<br />

ተጠያቂነቱን አሳርፈዋል።<br />

የኢትዮጵያ ገበሬዎች ከግማሽ<br />

ሄክታር በምታንስ ኩርማን መሬት<br />

ላይ እያረሱና የዘመናዊ ቴክኖሎጂ<br />

ተጠቃሚ ባልሆኑበት የምርት<br />

ዕድገት ሊኖር እንደማይችል<br />

የገለፁት አቶ ቡልቻ፣ ቁጥሩ<br />

እየጨመረ የሚሄደውን ሕዝብ<br />

ለመመገብና የምግብ እጥረትን<br />

ለማስወገድ የተጠቀሱትን ችግሮች<br />

መፍታት ግድ እንደሚል አፅንዖት<br />

ይሰጡበታል።<br />

መንግስት፣ ከዓለም አቀፍ<br />

ሁኔታዎች በመቀጠል ለግሽበቱ<br />

በመንስዔነት የሚያቀርበው<br />

የንግድ ሥርዓቱ ቅልጥፍና<br />

የጎደለውና ለልዩ ልዩ ኢ-ፍትሐዊ<br />

አሰራሮች የተጋለጠ መሆኑን<br />

ነው። ይህንንም ችግር ለመፍታት<br />

በመሰረታዊ ሸቀጦች ላይ የዋጋ<br />

ተመን ቢያወጣም መልካም<br />

ውጤት ያላገኘ ሲሆን፣ ግሽበቱን<br />

ለማስወገድና የአቅርቦት እጥረትን<br />

ለመቅረፍ ራሱ ሸቀጦችን በማቅረብ<br />

አዲስ የጅምላ ንግድ ሥርዓት<br />

መዘርጋቱም ይታወቃል።<br />

ሆኖም የግሽበቱ ዋና ምንጮች<br />

ሌሎች ጉዳዮች ሆነው ሳለ ችግሩን<br />

በነጋዴዎች ላይ መንግስት<br />

የሚያሳብበው የፖለቲካ ትርፍ<br />

ለማግኘት በማሰብ መሆኑን<br />

የሚገልፁ ወገኖች አልጠፉም።<br />

ኢህአዴግ መራሹ መንግስት ሁሌም<br />

ለችግሮች መፍትሔ የሚሰጠው<br />

ከራሱ የፖለቲካ ትርፍ አኳያ<br />

ብቻ መሆኑን የሚያስገነዝቡት<br />

የሕወሓት/ኢህአዴግ አንዱ<br />

መስራች አቶ ገብሩ አስራት፣<br />

ለአጭር ጊዜ ተግባራዊ ተደርጎ<br />

ፉርሽ የሆነው የዋጋ ተመንም<br />

ለፖለቲካ ትርፍ የታለመ መሆኑን<br />

ይናገራሉ።<br />

‹‹የዋጋ ተመኑ ተግባራዊ<br />

የተደረገው በዋጋ መናር የተነሳ<br />

የተማረረው ሕዝብ ቁጣውን<br />

መንግስት ላይ እንዳይገልፅ<br />

ይልቁኑም ነጋዴውን እንዲጠላ<br />

ለማድረግ ነው›› የሚሉት አቶ<br />

ገብሩ፣ ተመኑ የወጣው ‹‹እሳት<br />

አደጋን›› ለማጥፋት በሚመስል<br />

የጥድፊያ እርምጃ እንጂ ዘላቂ<br />

መፍትሔ ለመስጠት ታስቦ<br />

ባለመሆኑ ብዙም ሳይቆይ መነሳቱ<br />

ላይ ያሰምሩበታል።<br />

ከንግድ ሥርዓቱ ጋር በተያያዘ<br />

‹‹ነጋዴዎች ምርቶችን<br />

አላግባብ ደብቀው በማከማቸት<br />

ዋጋ እያናሩ ነው›› የሚለው<br />

ምክንያትም ለአውራምባ<br />

ታይምስ አስተያየታቸውን<br />

በሰጡ ባለሙያዎች ዘንድ<br />

ተቀባይነት አላገኘም። በአገሪቱ<br />

ያሉት ነጋዴዎች ከፍተኛ ምርት<br />

ደብቀው ሊያከማቹበት የሚችል<br />

ግዙፍ መጋዘኖች እንደሌሉ<br />

የሚያስታውሱት ባለሙያዎች፣<br />

‹‹ይሄ እኮ ግልፅ ነው። የምርት<br />

እጥረት መኖሩን ባለማመን<br />

ሕዝቡንና ነጋዴውን ለማጣላት<br />

የሚደረግ ሴራ ነው›› ባይ<br />

ናቸው።<br />

‹‹ምርት ደብቆ በማከማቸት<br />

እጥረት ተከስቶ ዋጋ ሲንር መሸጥ<br />

የሚፈልግ ነጋዴ እውነት የለም?››<br />

የሚል ጥያቄ ከአውራምባ ታይምስ<br />

ለአስተያየት ሰጪዎቹ ቀርቦ<br />

ነበር። እነሱም ምርት የሚደብቁ<br />

ነጋዴዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ<br />

በማመን፣ ‹‹ሆኖም በገበያው ላይ<br />

ወሳኝ ተፅዕኖ ያላቸው ነጋዴዎች<br />

ኢህአዴግና ደጋፊዎቹ ስለሆኑ<br />

ከእነሱ ውጪ ያሉት ቢደብቁም<br />

ያን ያህል ለውጥ አያመጡም።<br />

ለግሽበቱ የገበያው ሥርዓት<br />

በምክንያትነት የሚቀርብ ከሆነም<br />

ተጠያቂዎቹ ኢህአዴግና ደጋፊዎቹ<br />

ነጋዴዎች ናቸው›› የሚል ምላሽ<br />

ሰጥተዋል።<br />

እስካሁን ከተጠቀሱት ምክንያቶች<br />

ባሻገር ለዋጋ ግሽበት ትልቁ<br />

ምክንያት መንግስት ወጪዎቹን<br />

ለመሸፈን ሲል ከብሔራዊ ባንክ<br />

በመበደርና በማሳተም ወደ<br />

ኢኮኖሚው ያፈሰሰው ገንዘብ<br />

ከመጠን በላይ መሆኑን ብዙዎች<br />

የሚስማሙበት ነው።<br />

የገንዘብ አቅርቦት በኢኮኖሚው<br />

ውስጥ መብዛቱ የተጫወተውን<br />

አሉታዊ ሚና በመገንዘብ<br />

የመንግስትን ወጪ ከብሔራዊ<br />

[በመስከረም ወር<br />

ስለተመዘገበው የዋጋ<br />

ግሽበት አንዳንድ ነጥቦች]<br />

ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ<br />

ወር ጋር ሲነፃፀር አብዛኛዎቹ<br />

የምግብ ክፍሎች ጭማሪ<br />

አሳይተዋል<br />

እህል የ61.9 ከመቶ፣<br />

ጥራጥሬ የ89.4 ከመቶ፣<br />

ዘይትና ቅባቶች<br />

የ69.7ከመቶ፣<br />

ድንችና ሌሎች ስራስሮች<br />

የ41.7ከመቶ፣<br />

ያልተቆላ ቡናና ሻይ ቅጠል<br />

የ88.6ከመቶ፣<br />

ቅመማ ቅመሞች የ62.9<br />

ከመቶ<br />

ጭማሪ አሳይተዋል<br />

ምንጭ፦ የኢፌዴሪ ማዕከላዊ<br />

ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ<br />

ባንክ በሚገኝ ብድር ላለመሸፈን<br />

ከፍተኛ ጥንቃቄ እንደሚያደርግ<br />

(ዘግይቶም ቢሆን) በመግለፅ ላይ<br />

የሚገኘው መንግስት፣ በተያዘው<br />

የበጀት ዓመት ከብሔራዊ ባንክ<br />

ብድር እንደማይወስድ ተናግሯል።<br />

ነገር ግን ይሄንን የመንግስት<br />

ውሳኔ አቶ ገብሩ አስራት<br />

በጥርጣሬ ነው የሚመለከቱት።<br />

መንግስት የጀመራቸውን ግዙፍ<br />

ፕሮጀክቶች ሥራ ለማከናወን<br />

የግድ ከብሔራዊ ባንክ መበደሩ<br />

እንደማይቀር የሚጠቁሙት አቶ<br />

ገብሩ፣ ‹‹አብዛኞቹን ፕሮጀክቶች<br />

ያቀደው ገንዘብ ሳይኖረው ነው።<br />

ስለዚህ እነሱን ለመስራት ሲል<br />

መበደሩ አይቀርም፡፡ ይሄ ደግሞ<br />

ግሽበቱን ያባብሰዋል›› የሚል<br />

መከራከሪያ ያቀርባሉ።<br />

የዋጋ ግሽበት ማለት ሌላ ተዐምር<br />

ሳይሆን በኢኮኖሚው ውስጥ<br />

ጥቂት ምርቶችና በርካታ ገንዘብ<br />

መኖር ማለት መሆኑን ቀለል<br />

ባለ አቀራረብ የሚያስረዱት አቶ<br />

ቡልቻ፣ መንግስት ከብሔራዊ<br />

ባንክ የሚወስደው ብድር<br />

መጠን እንዲታወቅ አለመፈለጉ<br />

ያሳዝናቸዋል። ‹‹መንግስት<br />

ከሚችለው በላይ እየተደበረ<br />

ጥቂት ምርት ባለበት ኢኮኖሚ<br />

ውስጥ ብዙ ገንዘብ አንዲዘዋወር<br />

አድርጓል። በፊት ከብሔራዊ ባንክ<br />

የሚወስደውን የብድር መጠን<br />

የሚወስን ሕግ ነበር። ይሄን<br />

ሕግ ከዓመታት በፊት በፓርላማ<br />

እንዲሻር አድርጓል›› የሚሉት<br />

በዓለም ባንክ በኢኮኖሚስትነት<br />

ያገለገሉት ባለሙያ፣ መንግስት<br />

በፓርላማ የሚሾመውን<br />

ዋና ኦዲተር እንደማያከብር<br />

ይወቅሳሉ።<br />

አቶ ተመስገን ዘውዴም<br />

የመንግስትን አጠቃላይ ዓመታዊ<br />

ሂሳብ መርምሮ ሪፖርቱን ለፓርላማ<br />

በሚያቀርበው ዋና ኦዲተር<br />

መንግስት ደስተኛ እንዳልሆነና<br />

አንዳንዴም ሪፖርቶችን ውድቅ<br />

የሚያደርግበት ሁኔታ መኖሩን<br />

የሚገልፁት በመገረም ነው።<br />

ከጥቂት ዓመታት በፊት የፌደራል<br />

ዋና ኦዲተር ባደረገው ማጣራት<br />

በርካታ ቢሊዮን ብሮች ወደ<br />

ኢኮኖሚው ውስጥ ያላግባብ<br />

ፈሰስ መደረጋቸውን ሪፖርት<br />

ቢያደርግም፣ ጠቅላይ ሚኒስትር<br />

መለስ ዜናዊ ‹‹ተራ የሂሳብ<br />

ሠራተኛ ሊሳሳት የማይችለውን<br />

ስህተት ዋና ኦዲተር ፈፅሟል››<br />

ማለታቸውን ለሚያስታወሱት አቶ<br />

ተመስገን፣ መንግስት ግልፅነት<br />

የጎደለው አካሄድ እየተከተለ<br />

‹‹ግሽበቱን እቆጣጠራለሁ›› ማለቱ<br />

የሚዋጥ አይደለም።<br />

ዕድገት Vs ግሽበት<br />

በአሁኑ ሠዓት የሚስተዋለው<br />

ግሽበት በዕድገት ሂደት<br />

የሚከሰት መሆኑ ከመንግስት<br />

በኩል ይደመጣል። በአንፃሩ<br />

ደግሞ በትክክለኛ ዕድገት ውስጥ<br />

የሚከሰት ግሽበት ከአንድ አሀዝ<br />

እንደማይበልጥ በመግለፅ፣ ‹‹የምር<br />

ግሽበቱ የተከሰተው ከዕድገት ጋር<br />

ተያይዞ ቢሆን ኖሮ ሕዝቡ ለምን<br />

ይቸገራል?›› የሚለው ጥያቄ<br />

የበርካቶች ነው።<br />

ኢኮኖሚ የሚያድገው ብዙ ምርት<br />

ሲኖር እንጂ ከገደብ ባለፈ ገንዘብ<br />

አለመሆኑን የሚያስገነዝቡት<br />

ከአውራምባ ታይምስ ጋር ቆይታ<br />

ያደረጉ ባለሙያ፣ ‹‹11 በመቶ<br />

የኢኮኖሚ እድገት ተመዝግቧል<br />

የሚባለውም ሀሰት ነው፡<br />

፡ በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉት<br />

የምግብ እጥረት፣ የዋጋ መናርና<br />

ሌሎች ችግሮች የአስከፊ ድህነት<br />

መገለጫዎች እንጂ የእድገት<br />

አይደሉም›› በማለት ሞግተዋል።<br />

የኢኮኖሚ ዕድገትንና የዋጋ<br />

ግሽበትን በፊኛና ፊኛው ውስጥ<br />

በሚጨመረው አየር የሚመስሉት<br />

የንግድ አስተዳደር ባለሙያ<br />

የሆኑት አቶ ተመስገን ዘውዴ፣<br />

ኢኮኖሚውን ለማሳደግ በሚል<br />

ምክንያት ገንዘብ ያለ ገደብ ወደ<br />

ኢኮኖሚ ማስገባት ከፍተኛ መዘዝ<br />

እንዳለው ያሳስባሉ። ገንዘብ<br />

ያለገደብ የሚጨመርበት ኢኮኖሚ<br />

ለጊዜው ያደገ እንደሚመስል<br />

‹‹ፊኛ ውስጥ አየር ሲጨመር<br />

የፊኛው መጠን ይተልቃል፤ አየሩ<br />

ፊኛው ከሚችለው በላይ ሲሆን<br />

ግን ፊኛው መፈንዳቱ አይቀርም››<br />

በሚል ምሳሌ ነው ያስረዱት።<br />

‹‹ፊኛው›› ውስጥ የሚጨመረውን<br />

‹‹አየር›› መቀነስ የፊኛውን መጠን<br />

ስለመቀነሱ ከአውራምባ ታይምስ<br />

ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ ‹‹ኢኮኖሚው<br />

ውስጥ የሚረጨው ገንዘብ ይቀንስ<br />

ማለት እኮ መንግስት የልማት<br />

ሥራዎችን ለማከናወን ሙሉ<br />

በሙሉ ገንዘብ አይጠቀም ማለት<br />

አይደለም፤ በሚያስፈልገው ልክ<br />

ብቻ ይጠቀም ማለት እንጂ›› ነበር<br />

ምላሻቸው።<br />

የተወሰነ የግሽበት መጠን ከኢኮኖሚ<br />

እድገት ጋር ተያይዞ በሚፈጠረው<br />

የገንዘብ ዝውውር የተነሳ ሊስተዋል<br />

ቢችልም፣ ኢትዮጵያ ውስጥ<br />

ያለው አደገኛ ግሽበት (hyper<br />

inflation) ግን የእድገት ሳይሆን<br />

የድቀት ማሳያ መሆኑን የሚገልፁ<br />

ባለሙያዎች ደግሞ በበኩላቸው<br />

ችግሩን ‹‹ከልማታዊ መንግስት››<br />

ፅንሰ-ሀሳብ ጋር ያቆራኙታል።<br />

መንግስት ሊሰራቸው ካቀዳቸው<br />

ግዙፍ ፕሮጀክቶች ውስጥ<br />

የግል ባለኃብቶች ሊሰማሩባቸው<br />

የሚገባቸውን ከዕቅዱ ውስጥ<br />

አውጥቶ ወጪውን በመቀነስ<br />

ግሽበቱን መቆጣጠር እንደሚችል<br />

በመግለፅ የመፍትሄ ሀሳብ<br />

ያቀርባሉ።<br />

መፍትሔው ምንድን<br />

ነው?<br />

ለአውራምባ ታይምስ<br />

አስተያታቸውን የሰጡ ባለሙያዎች<br />

ከተራ ግሽበትነት አልፎ አደገኛ<br />

ደረጃ ላይ ለደረሰው የዋጋ ግሽበት<br />

ዋና መፍትሄው መንግስት ወደ<br />

ኢኮኖሚው ያላግባብ የረጨውን<br />

ገንዘብ መሰብሰብ በመሆኑ ላይ<br />

ያሰምሩበታል።<br />

ገንዘብ ከኢኮኖሚው ውስጥ<br />

ለመሰብሰብ ከተጠቆሙት<br />

የመፍትሄ አቅጣጫዎች መካከል<br />

የመጀመሪያው መንግስት<br />

የብሔራዊ ባንክን ነፃነት በማክበር<br />

ከተገቢው በላይ ብድር መውሰዱን<br />

ማቆሙ ሲሆን፣ የባንክ የወለድ<br />

መጠንን በመጨመር ሰዎች<br />

ገንዘብ ባንክ እንዲያስቀምጡ<br />

ማበረታታትና የተለያዩ ዓይነት<br />

ቦንዶችን በመሸጥ ገንዘብ<br />

መሰብሰብም ሌሎች የተጠቆሙ<br />

አማራጭ መፍትሄዎች ናቸው፡፡


አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />

ማ ስ ታ ወ ቂ ያ<br />

13<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ


14<br />

መንግሥት በዜጎቹ ላይ<br />

ሬዲዮ የለንም በሬዲዮ መልስ<br />

አይሰጥ ነገር ግራ የገባው ግራ ሆኖብኝ<br />

ነው፡፡ የሬዲዮ ፋና አድማጭ አይደለሁም፡<br />

፡ አብርሃም የሚባል የሬዲዮ ፋና ባልደረባ<br />

ደውሎ በአሸባሪነት አዋጅና በጠቅላይ<br />

ሚኒስትሩ የፓርላማ ውሎ ዙሪያ<br />

የመንግስት ባለስልጣናት የሚገኙበት<br />

የጋራ ውይይት ሰለሚደረግ ፈቃደኝነቴን<br />

ጠየቀኝ፡፡<br />

አኔም ፈቃደኝነቴን ገልጬለት<br />

ቅዳሜ ለሰባት ዕሩብ ጉዳይ ሬዲዮ<br />

ፋና ጣቢያ እንድንገናኛ ቀጠሮ ያዝን፡፡<br />

ጋዜጠኛው ከቀጠሮ ሰዓት ቀደም ብሎ<br />

በአምስት ሰዓት አካባቢ ስልክ ደውሎ<br />

‹‹ሰማኸው አይደል?›› አለኝ። ‹‹ምኑን?››<br />

ስለው ‹‹ማስታወቂያ ለቀናል። ውይይት<br />

እንዳለ አንተም እንደምትገኝ›› አለኝ፤<br />

‹‹ትቀልዳለህ እንዴ? የፋና አድማጭ<br />

አይደለሁም። አሁን ያለሁት ሥራ ላይ<br />

ነው፤ በቀጠሮ ሰዓት ግን እመጣለሁ››<br />

ብዬው በቀልድ ተለያየን።<br />

በእውነትም የሬድዮ ፋና<br />

አድማጭ አይደለሁም። ነገር ግን<br />

እኔ መኪና ውስጥ በአንድ ምክንያት<br />

የተከፈተ ካሴት፣ ሲዲ ወይም ሬዲዮ<br />

ጣቢያ ለሳምንት ምን አልባትም የቴክኒክ<br />

እክል ካልገጠመውና የተሳፋሪ ተቃውሞ<br />

ካልተነሳበት ለወርም ሳይነካ ሊቀጥል<br />

ይችላል። በዚህ ዓይነት ሁኔታ ረቡዕ<br />

በፋና ሬዲዮ ጣቢያ “ተጓዝ ነቃሽ” የተባለ<br />

ፕሮግራም ለመከታተል በቃሁ።<br />

በማግስቱም ዘጠና ደቂቃ<br />

የሚል ፕሮግራም በተመሳሳይ ጉዳይ ላይ<br />

ሲተላለፍ አደመጥኩ። ምቀኝነትን ዜጎች<br />

እርስ በርሳችን በመንግስት ተቋማት<br />

አጋዥነትና በሚዲያ አሟሟቂነት ነብስ<br />

ዘርቶ አገኘሁት፡፡ ዝርዝረሩን ቀጥዬ<br />

አቀርባለሁ።<br />

የፕሮግራሙ ዋና ጭብጥ<br />

በሀገራችን በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ<br />

የመንግስት ቤት ተከራይተው በመንግስት<br />

ቤት አለአግባብ ጥቅም የሚያገኙ፣<br />

ህብረተሰቡን እየበዘበዙ ያሉ ህገወጥ<br />

ሰዎች እንዳሉ፤ እነዚህ ሰዎች ላይም<br />

አስፈላጊው እርምጃ መወሰድ እንዳለበትና<br />

መንግስት እሰከ አሁን ዝም ማለቱ ተገቢ<br />

እንዳልሆነ በተለያየ መንገድ የሚገልፅ<br />

ነው።<br />

ትኩረቱ ቤት ሸንሽነው ለንግድ<br />

ቤትነት የሚያከራዩ ዜጎች ላይ ነው፡፡ ነገሩን<br />

የበለጠ ግልፅ ለማድረግ ከመንግስት ቤት<br />

ተከራይተው ሸንሽነው የሚያከራዩ ሰዎች<br />

ሕገ-ወጥ፣ በዥባዦች፣ ለተፈጠረው<br />

የዋጋ ንረት ተጠያቂዎች ተደርገው የክስ<br />

መዓት ይወርድባቸዋል።<br />

የሚያሳዝነውና እንደመፍትሄ<br />

የቀረበው ደግሞ በሽንሽን ቦታዎች<br />

ላይ ተከራይተው የሚሰሩት ሰዎች<br />

የያዙትን ቦታ ለመውረስና በዝቅተኛ ዋጋ<br />

ተከራይተው እንዲቀጥሉ ያቀረቡት በህግ<br />

ሽፋን የመውረስ ጥያቄ ነው፡፡ ጉዳዩ አቶ<br />

ተፈራ ዋልዋ የአዲስ አበባ መስተዳድር<br />

ከንቲባ እያሉ የነበረውን ዓይነት የተከራይ<br />

አከራይ ድራማ ለመድገም የተጠነሰሰ<br />

ሴራ እንዳለ የሚያመላክት ነገር አለው።<br />

ለማገገም እየሞከረ የነበረውን<br />

በንግድ ማህበረሰብ ውስጥ ያለን ጤናማ<br />

ግንኙነት በድጋሚ እንዲበላሽ የሚያደርግ<br />

ውሳኔ መጠንሰሱን መጠርጠር ደግ<br />

ከመሆኑ በላይ፣ ቤታቸው /የተከራዩትንም<br />

ቢሆን/ ለመወረስ የተዘጋጀ መሆኑን<br />

ሽንሽን ሰርተው በማከራየት ላይ ያሉ<br />

ዜጎች ልብ ሊሉት ይገባል።<br />

በፋና የዋህ አድማጮችና<br />

የሰውን ንብረት ለመውረስ በተዘጋጁ<br />

የሽንሽን ቤት ተከራዮች ከሚቀርቡት<br />

ክሶች ዋነኛ የነበረው “የመንግስትን ቤት<br />

በርካሽ ተከራይተው በውድ እያከራዩ ነው”<br />

የሚለው ነው፡፡ ለመሆኑ የመንግስት<br />

ቤት ማለት ምን ማለት ነው? በመርካቶ<br />

የመንግስት ቤት ማለት የቱ ነው?<br />

መንግስት አንድ ቆርቆሮ ያላለበሰው፣ አንድ<br />

ምስማር ያልመታበት ደርግ የወረሳቸውን<br />

ቤቶች ነው መንግስት “የእኔ ናቸው”<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

በግርማ ሰይፉ<br />

የሚለው፡፡ እንግዲህ ደርግን በመውረሱ<br />

እየኮነነ ደርግ በወረሰው ንብረት ደግሞ<br />

ዜጎችን ለማፈን እየሞከረ ነው።<br />

ሸንሽነው የሚያከራዩ ሰዎች<br />

ግን የሚያከራዩትን ቤት ለገበያ ቦታ<br />

እንዲሆን ገንዘባቸውንና እውቀታቸውን<br />

ገብረውበታል። ከዚያም በላይ <strong>ስር</strong>ዓቱ<br />

የሚጠይቀውን በሽፍንፍን ሙስና፣ በግልፅ<br />

ግን ለግንባታ ማስፈቀጃ ከፍለውበታል።<br />

ጉቦ መክፈላቸው አያስደስተኝም። ከሱ<br />

ጋር የከፈሉት ነፃነታቸው ግን የበለጠ<br />

አንጀቴን ይበላዋል።<br />

ይህን በማድረጋቸው ኢህአዴግን<br />

ሲደግፉ እንደነበረም አውቃለሁ።<br />

የኢህአዴግ ደጋፊ ነጋዴዎች ፎረም<br />

አባል በመሆንም ድጋፍ አድርገዋል።<br />

ኢህአዴግ ግን ዛሬ ከነዚህ ጥቂቶቹ ይልቅ<br />

በሽንሽን ውስጥ ያሉት ብዙኃን የበለጠ<br />

ስለሚያስፈልጉት ነፃነትን ያህል ክብር<br />

የገበሩለት ቢዝነሳቸውን ሊወርስባቸው<br />

ነጋሪት እያስጎሰመ ነው።<br />

ነፃነታችሁን የሸጣችሁ ዕለት<br />

ብዙ ነገር አብሮ እንደተወረሰ ልብ ማለትም<br />

ተገቢ ነበር። አሁን ግን ነፃነታችሁን<br />

የሸጣችሁለት ንብረት ሊወረስ ነው።<br />

የሽንሽን ቤት ወራሾች በናንተ ተራ ገብተው<br />

የናንተን ንብረት ሲወርሱ እነርሱም<br />

በተራቸው ነፃነታቸውን ለማስወረስ<br />

ተዘጋጅተው ብቻ እንዳይመሰላችሁ፤<br />

ለልጆቻቸው ሁሉ የሚነግሩት እውነት<br />

የላቸውም። ዘርፈው እንደሚያወርሷቸው<br />

አይነግሯቸውም።<br />

ሌባ ለልጁ መስረቁን<br />

አይነግርም፤ ልጅ ግን ሁሌም ስለወላጆቹ<br />

የኃብት ምንጭ ያስባል። ልጆቻችንን<br />

ከማሳቀቅ ብንታቀብ ምን ይመስላችኋል?<br />

አንድ ተከራይ ነኝ ያሉ ግለሰብ በብር<br />

ሶስት ሺህ አምስት መቶ እንደተከራዩ<br />

ነገር ግን ስለማያተርፉ ኪራዩን ተበድረው<br />

እንደሚከፍሉ በማሰተዛዘን ገልፀዋል።<br />

ዕውነቱን ለመናገር ኪራይ<br />

በብድር አይከፈልም፤ ዓላማው መንግስት<br />

የዚህን ያህል ኪራይ እንዳያስከፍላቸው፣<br />

ብሎም ከዚህ ጋር ተመጣጣኝ ገቢ መሰረት<br />

አድርጎ የገቢ ግብር እንዳይጠየቁ የዘየዱት<br />

ነው። ከዚህ ባሻገር አከራዩ እንዲከራዩት<br />

አላስገደዳቸውም፤ ምናልባትም ተጫርተው<br />

ነው የተከራዩት፤ እገሌን አስወጣው፤ እኔ<br />

ይህን ያህል እከፍላለሁ ብለው ጭምር<br />

ሊሆን ይችላል።<br />

የኪራይ ቤቶች፣ የሬዲዮ<br />

ጣቢያ አዘጋጆች፣ የተከራዮች ወዘተ …<br />

ምቀኝነት ነብስ ዘርቶ የሚታየው አከራዮቹ<br />

የሚያገኙትን ሂሣብ ሰርተው በምናባቸው<br />

ሲያዩት ነው። ቀደም ሲል እንደገለፅኩት<br />

አንድ ምሰማር ላልመታ መንግስት<br />

አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />

ለምን ምቀኛ ይሆናል?<br />

በነገራችን ላይ አንድ የተከራዩትን ቤት ሸንሽነው በውድ እያከራዩ በዘበዙን የምትሉ<br />

ዜጎች እነዚህ ሰዎች ከማከራየት ይልቅ ለብቻቸው ይዘውት እንደአንድ የገበያ ማዕከል<br />

እየሰሩበት ሰራተኛ ቀጥረው ቢሰሩበት ኖሮ ምን ትሉ ይሆን? ከዚህ ይልቅ ግን ሰራተኛ<br />

ቀጥሮ ከማሰተዳደር ሁሉም በነፃነት እንዲሰራ ኃላፊነት እንዲሰማው ማከራየት ይሻላል<br />

ብለው አማራጭ መውሰድ ኃጥያት መደረጉስ ለምንድነው?<br />

የመንግስት ቤት እያሉ የሱ ያልሆነውን<br />

ሲሰጡት፤ የንግድ ሂሣቡን፣ ለተሻለ የገቢ<br />

ምንጭ ብሎ ብዙ ጊዜና ገንዘብ ያወጣውን<br />

ዜጋ ግን በዝባዥ ብለው ያለ ስሙ ስም<br />

ይሰጡታል።<br />

ዜጋ ገንዘብ ሲያገኝ የሚቀና<br />

ምቀኛ ሥርዓትና ይህንን ለማገልገል<br />

የተሰለፉ ሎሌዎች ብዛት ስመለከት<br />

ዕፍረት ይሰማኛል። ጣቢያው በዛው<br />

ዕለት ስለነፃ ኢኮኖሚ ሲሰብክ ብትሰሙት<br />

እንዳይገርማችሁ። ግራ የገባው ግራ<br />

ማለት ይሄኔ ነው። መንግሰት በዘረፋ<br />

የያዘውን ቤትም ቢሆን ዜጎች አከራይተው<br />

ገንዘብ እንደሚያገኙ መረጃ ካለው በንዴት<br />

መብገን ያለበት አይመሰለኝም፤ ተገቢም<br />

አይደለም።።<br />

ዜጎች ባገኙት ገቢ ልክ ግብር<br />

መሰብሰብ ነው ከመንግስት የሚጠበቀው።<br />

የመንግስት ወግ ይህ ነው። ይልቁንም<br />

ተከራዮች በሚከፍሉት ኪራይ ልክ<br />

ግብር እንዳይጠየቁ ኪራይ ተቀንሶ<br />

እንዲነገርላቸው እንደሚማፀኑ ስንቶቻችን<br />

እናውቃለን? እውነቱን ለመነጋገር አከራዩ<br />

ከኪራይ በሚያገኘው ኪራይ ልክ ግብር<br />

አልከፈለም ብለው ሲከሱ የነበሩ ተከራዮች<br />

እስኪ ለኪራይ በከፈሉት ልክ የገቢ ግብር<br />

መክፈላቸውን ይናገሩ። ዓሣ ጎርጓሪ ዘንዶ<br />

ያወጣል ማለት ይህ ይመሰለኛል።<br />

መንግስት ዜጎች ገንዘብ ሲያገኙ<br />

ለምን እንደሚመቀኝ አይገባኝም፡፡ ይህ<br />

ከሶሻሊዝም የወረስነው፤ በአብዮታዊ<br />

ዴሞክራሲ እያዳበርነው ያለነው የመንግስት<br />

ሞግዚትነት አባዜ ውጤት ነው፡፡ ዜጎች<br />

ገንዘብ ሲያገኙ ለተጨማሪ ሥራ ፈጠራ፣<br />

አዳዲስ ቴክኖሎጂ ለማስመጣት፣ ለሀገር<br />

ዕድገት፣ ወዘተ ያውሉታል የሚል ቅን<br />

ልቦናችንን ምን እንደወሰደው መጠየቅ<br />

ያለብን ይመስለኛል።<br />

ሶሻሊዝም በዓለም እንደተወዳዳሪ<br />

ርዕዮት ከተወገደ ከሃያ ዓመት በኋላ<br />

በእኛ ሀገር የሃያና ሃያ አምስት ዓመት<br />

ወጣቶች በዚህ አባዜ ተለክፈው ማየት<br />

ምን እንደሚባል አላውቅም። ከመንግሥት<br />

ይልቅ ግን ዜጎች የሚያገኙትን ገንዘብ<br />

ለተሻለ ሀገራዊ ጥቅም ስለሚያውሉት<br />

መንግሥት ከተወሰኑ መስኮች ውጭ<br />

የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን ለዜጎች መተው<br />

አለበት በሚባልበት ዘመን ላይ ሆነን የእኛ<br />

መንግስት ግን ቤት በማከራየት ሥራ<br />

እንዲሰማራ፣ ሱቅ ሸንሽኖ እንዲያከራየን<br />

እንጠብቃለን።<br />

ዛሬ መንግስት ሱቅ ሸንሸኖ<br />

እንዲያከራየው በሬዲዮ የለመነ ሁሉ<br />

ከዚህ ጋር ተያይዞ መንግስት በነፃነቱ ላይ<br />

የሚያደርሰውን ጫና ለመሸከም ጫንቃውን<br />

ማደንደን ይኖርበታል። መንግስት ከቀበሌ<br />

ቤት እንዳንወጣ፤ ከወጣንም ኮንዶሚኒየም<br />

ውስጥ እንድንገባ የሚፈልገው ስለሚወደን<br />

የሚመሰለው ካለ አይሞኝ። ነፃነታችን<br />

ስለሚያስፈራው ነው። ፋብሪካ ወደ ግል<br />

እንዲዛወር እፈልጋለሁ የሚል መንግስት<br />

ቤት የማከራየት ሥራን ከእጁ ለማውጣት<br />

ወደኋላ የሚለው ለምን ይመሰላችኋል?<br />

አሁንም ቢሆን ከኪራይ ቤቶች<br />

በኪራይ የተያዘን ቤት ሸንሽኖ ማከራየት<br />

ክልክል ከሆነ ይህ በግልፅ ተነግሯቸው<br />

ተከራዮች አማራጭ ሊፈልጉ ይገባል፤<br />

ይህ ሕገ-ወጥ ነው ከተባለም (በእኔ ዕምነት<br />

አይደለም) የንግድ ቦታዎቹን የያዙት ሰዎች<br />

ቦታውን መያዝ ያለባቸው አሁን በያዙት<br />

ዋጋ ሳይሆን በግልፅ ጨረታ በውድድር<br />

አሸንፈው መሆን ይኖርበታል።<br />

የሰው ንብረት ለመውረስ<br />

የቋመጡ የሽንሽን ሱቅ ተከራዮች<br />

ገደባቸውን ሊያልፉ አይገባም። ይህ ውሳኔ<br />

መዘዙ ብዙ ሊሆን እንደሚችል መገመት<br />

አያስቸግርም። የሕይወትና ንብረት<br />

ኪሣራ ሊያስከትል እንደሚችል መንግስት<br />

ተረድቶት ውሣኔውን በጥሞና ሊመረምር<br />

ይገባል።<br />

በነገራችን ላይ አንድ የተከራዩትን<br />

ቤት ሸንሽነው በውድ እያከራዩ በዘበዙን<br />

የምትሉ ዜጎች እነዚህ ሰዎች ከማከራየት<br />

ይልቅ ለብቻቸው ይዘውት እንደአንድ<br />

የገበያ ማዕከል እየሰሩበት ሰራተኛ ቀጥረው<br />

ቢሰሩበት ኖሮ ምን ትሉ ይሆን? ከዚህ<br />

ይልቅ ግን ሰራተኛ ቀጥሮ ከማሰተዳደር<br />

ሁሉም በነፃነት እንዲሰራ ኃላፊነት<br />

እንዲሰማው ማከራየት ይሻላል ብለው<br />

አማራጭ መውሰድ ኃጥያት መደረጉስ<br />

ለምንድነው?<br />

በእኔ ዕምነት የሰው ንብረት<br />

ለመውረስ መንግስትም ካለበት<br />

የተቆጣጣሪነትና በሁሉም ነገር ያገባኛል<br />

ከሚል አባዜ የመጣ ነው የሚል ዕምነት<br />

ነው ያለኝ። ይህ የሰው ንብረት የመውረስ<br />

አባዜ ግን በእኛ ብቻ ሳይሆን ለልጅ<br />

ልጆቻችን የሚተርፍ ጦስ ይዞ ይመጣል።<br />

በጥሞና ልናስብበት ይገባል የሚል ዕምነት<br />

አለኝ። ግለሰብ ከሚበዘብዘኝ፣ መንግስት<br />

ይበዝብዘኝ ነው ምርጫው የሚመሰለው።<br />

የመንግስትን ሚና በቅጡ<br />

ካለመረዳትና ደርግ በቀደደው የመውረስ<br />

መንገድ የተመሰረተ ድርጅት/ኤጀንሲ<br />

ኃላፊ ነን የሚሉ ሰዎችም ወንበራቸው<br />

ጊዜያዊ መሆኑን ተረድተው በማያገባቸው<br />

የሽንሽን ሱቅ የማከራየት ሥራ ባለመግባት<br />

መንግስትን ባያስወቅሱት ደግ ነው።<br />

መንግስት ገቢ ማግኘት አለበት ካሉ<br />

መንግስት ሽንሽን ሱቅ አከራይቶ ሳይሆን<br />

ግብር ሰብሰቦ መሆን ነው ያለበት።<br />

የመንግስት የገቢ ምንጭ መሆን<br />

ያለበት ግብር ነው። በዚህ ፅሁፍ በሽንሽን<br />

ሱቅ ያላችሁ ዜጎች ዛሬ ለጊዜያዊ ጥቅም<br />

የምትወስዱትን አቋም ቆም ብላችሁ<br />

እንድታስቡበት መምከር እወዳለሁ።<br />

ባለፈው ጊዜ መንግስት የፓርኪንግ ሥራ<br />

የጀመሩትን ባለኃብቶች ወርሶ ለፓርኪንግ<br />

ሰጥቶዋል፤ ዛሬ ኪራይ ቤቶች ኤጄንሲ<br />

በተከራይ አከራይ ሰም ሊወርስ ነው፣<br />

ነገ ሌላ ይቀጥላል። እንዲህ እያልን ተራ<br />

በተራ እንወረሳለን ማለት ነው።<br />

/የተከበሩ አቶ ግርማ ሠይፉ<br />

የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል ናቸው/


አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />

እንዴት ሰነበታችሁ ሰሞነኛ<br />

ወዳጆቼ? …‹‹አላርፍ ያለች<br />

ጣት ለእጇ ካቴና አታጣም››<br />

ይላሉ እኒያ የማላቃቸው<br />

ሴትዮ። የብዕር ወገብ<br />

በጨበጡ ቁጥር ‹‹ተናገር<br />

ተናገር›› ለሚላቸው ብዕር<br />

ለባሾች በጠቅላይ ሚኒስትራችን በኩል<br />

መልዕክት አስተላልፈናል። መቼም መልዕክቱ<br />

እናንተ ጆሮ ሲደርስ ጣሊያንኛ ይሆናል<br />

ብለን አናስብም። ‹‹መልዕክቱን የተቀበለ እሱ<br />

ይድናል›› ይላሉ ያልተፃፈው መፅሐፍ። ሲፃፍ<br />

ደግሞ ብዙ ይላል ብለን ተስፋ እናደርጋለን።<br />

ወዳጆቼ ለእናንተ የሚሆን ወግ<br />

ፍለጋ ከኳስ ሜዳ እስከ ሽሮ ሜዳ፣ ከቦሌ እስከ<br />

ጉለሌ ስዞር ለወግ ማድመቂያ የሚሆን አንዱ<br />

ሹክ ያለኝን ልንገራችሁማ… ማነህ ወዳጄ<br />

ክሬዲቱ ተይዞልሀል። ነገሩ እንዲህ ነው እድሜ<br />

ለጠሀዩ መንግስታችንና ኑሮ እንደ ሮኬት ላይ<br />

በተስፈነጠረበት በዚህ ጊዜ የሰውዬው የቤት<br />

ሠራተኛው በወጣ በገባ ቁጥር ‹‹እንትን አለቀ<br />

እንትንም የለም›› በማለት ስታሳቅቀው ነበርና<br />

አንድ ቀን መልዕክት ልትነግረው ገና ጋሼ<br />

ስትለው ‹‹904 ደሞ ዛሬ ምን አለቀ?›› አላት<br />

አሉ የጉድ አይደለም? ከጉድ ወዲያንዲያ<br />

እንጂ… [እየበላሽ የማታድጊው ስልኬ ትዝ<br />

አልሽኝ]<br />

ቆይ ሳልረሳውማ የእንትን ሰፈር<br />

ልጆች ቴሌ ሰራተኛ አባሮ እንዴት ሊሰራ<br />

ነው? እያላችሁ ስትንሾካሹኩ አልነበር? ይሄው<br />

የኔትወርኩን ምህዳር ‹‹በማስፋት›› ኩም<br />

አደረገልና! በእርግጥ አዲስ አበባ ከሰው ጋር<br />

በስልክ መነጋገር እንደ ዝቋላ ዳገት አስቸጋሪ<br />

እየሆነ ነው። ‹‹ፖለቲከኞች እና ፖለቲካ<br />

ጋዜጣ ላይ የሚሰሩ ጋዜጠኞች ጋር ስንደውል<br />

ኔትወርክ፣ ሀርድ ዎርክ ይሆንብናል። አሁንማ<br />

ከፍቅር ጓደኛችን ጋር ስናወራም…›› የሚሉ<br />

ወቀሳዎች ኢትዮጵያን ከመጪው ዓለም ጋር<br />

‹‹በማቀራረብ›› ላይ ያለው ቴሌያችን ላይ<br />

እየተሰማ ነው። አንድ አሉባልተኛ ወዳጄማ<br />

‹‹ቴሌ የተለወጠው ስሙ ብቻ ነው›› ብሎኝ<br />

በንዴት የሁለት ወር ጉንፋን ለቆብኛል።<br />

ኢትዮ ቴሌኮምዎች አታሰድቡን እንጂ!<br />

‹‹የደወልንላቸውን ደንበኛ አሁን ማግኘት<br />

ካልቻልን›› በቀጠሮ መቼ እንደምናገኛቸው፣<br />

መቼ እንደሚመቻቸው ጠይቃችሁ ንገሩንማ!<br />

እኔ የምወዳችሁ፣ እናንተ የማትነግሩኝ<br />

ወዳጆቼ ደሞ ለወግ? ነፍ ነበር ምን ዋጋ አለው<br />

የታች ሰፈር ልጆች ጢባራቸው አስቸገረን<br />

ወይኔ ነገር ሲጠመዝዙ … አቦ ተውና!<br />

ሰ ሞ ነ ኛ<br />

አንድ የአማርኛ መዝገበ ቃላት ‹‹ሰሞንኛ›› የሚለውን ቃል፣ ‹‹ከዕሁድ እስከ ዕሁድ የሚያገለግል ሰው›› ሲል<br />

ይተረጉመዋል። እኔም የሰማሁትን ላሰማዎ፣ ያየሁትን ላሳይዎ፣ ትጉ ሰሞነኛ አገልጋይዎ መሆንን ወደድሁ።<br />

‹‹ንቦች አሜሪካ ውስጥ አስቸገሩ››<br />

ሬዲዮ ፋና<br />

‹‹ፋና ሆይ ንቦች ያላስቸገሩበት የት አይታችኋል?›› የታች ሰፈር ልጆች<br />

እኔስ ምኔ ፋራ ‹‹እንቆቅልሽ›› አልኳቸው ‹‹ምን እናውቅልህ?››<br />

ሲሉኝ ‹‹ድርቅ እያለ ረሀብ የሌለባት <strong>አገር</strong>›› ብላቸው እንዴት<br />

ይመልሱት! ማሰቢያ’ኮ የለም፤ ኔፕ ናቸው። ‹‹በቃ ሰፈር ስጡኝ››<br />

ብላቸው ቤተ-መንግስትን አይሰጡኝ መሰልዎ! በስማምዬ! ቤተ-<br />

መንግስት ሆኜ ምን አጥቼ፣ ሁሉ በጄ፣ ሁሉ በደጄ… ስፈልግ<br />

አስሬ፣ ሳልፈልግ ከ<strong>አገር</strong> አባርሬ ምን ነበር ጥያቄው? ጠፋብኝ<br />

መልሱ ግን ኤርትራ ነው።<br />

ብዬ ሃርድ ምናምን ብቦጭቅላቸው ‹‹ሌላስ<br />

የለህም?›› አይሉኝም የሆነ የእንቆቅልሽ ጥያቄ<br />

አስመስለውት። እኔስ ምኔ ፋራ ‹‹እንቆቅልሽ››<br />

አልኳቸው ‹‹ምን እናውቅልህ?›› ሲሉኝ<br />

‹‹ድርቅ እያለ ረሀብ የሌለባት <strong>አገር</strong>›› ብላቸው<br />

እንዴት ይመልሱት! ማሰቢያ’ኮ የለም፤ ኔፕ<br />

ናቸው። ‹‹በቃ ሰፈር ስጡኝ›› ብላቸው ቤተ-<br />

መንግስትን አይሰጡኝ መሰልዎ! በስማምዬ!<br />

ቤተ-መንግስት ሆኜ ምን አጥቼ፣ ሁሉ በጄ፣<br />

ሁሉ በደጄ… ስፈልግ አስሬ፣ ሳልፈልግ ከ<strong>አገር</strong><br />

አባርሬ ምን ነበር ጥያቄው? ጠፋብኝ መልሱ<br />

ግን ኤርትራ ነው። [ምነው ሆዴ ጮኸሳ?<br />

ራበኝ እንዴ? (ይቅርታ ለካ ረሀብ አይባልም)<br />

የምግብ እጥረት አጋጠመኝ እንዴ? ወይስ<br />

ሆዴ ደርቆ ይሆን?]<br />

[ውድ አንባብያን አሁን የዜና<br />

ሰዓታችን ስለ ደረሰ ከዜናው በኋላ ተመልሰን<br />

እናወጋለን]<br />

ጤና ይስጥልኝ ዜና እናሰማለን፤<br />

ምክንያቱም ከማን እናንሳለን።<br />

‹‹የዘንድሮው ዓመት ከቀጣዩ ዓመት<br />

በሁሉም ነገር የተሻለ ይሆናል›› ሲሉ ቃሊቲ<br />

ያሉት ጋሼ ታምሩ ኤክስክሉሲቭ ለታች ሰፈር<br />

ልጆች ተንብየዋል። ልጆቹም ‹‹ከሚመጣው<br />

ይህኛው የተሻለ ከሆነ በዚሁ ዓመት<br />

ይውጣልን›› ማለታቸውን የሰሙ መንገደኛ<br />

‹‹ይውጣልን የሚሉት እ<strong>ስር</strong> ቤትን ኩፍኝ<br />

ማድረጋቸው ነውን?›› ሳይሉ አልቀረም ብሎ<br />

የጠረጠረው ዳተኛው ዘጋቢ ዜናውን ሳይፅፈው<br />

ቀርቷል።<br />

የውጪ ዜና፡- የስድብ አባት የሆኑት<br />

[ይቅርታ የነበሩት] ሙአመር ጋዳፊ ለስድብ<br />

ሳውንድ ትራክ የሚጠቀሙ ብቸኛው መሪ<br />

እንደነበሩ ሰሞኑን አንድ ቀጣፊ ተናግሯል።<br />

ኰሎኔሉም ትንቢተኛ መሆናቸውን ገልጾ<br />

የዚህ ማሳያው ‹‹አይጥ›› እያሉ የተሳደቡት<br />

በአይጥ ጉሬ መሞታቸውን ለመጠቆም ነው<br />

ብሏል። በሚስጥር የተቀበሩበት ምክንያትም<br />

‹‹ሚስጥር ነው ማን ሰውየውን ያምናል።<br />

ሰማይ ቤትም አረንጓዴውን አብዮት ይሰብኩ<br />

ይሆናል›› ይላል ቶክ.com በጀርባ ገጹ።<br />

እኛ ከዜናው ተመልሰናል ጋዳፊ ግን<br />

ጭረዋል። መልካም ጭረት ይባላል እንዴ?<br />

ኧረ ሳቄ ናልኝ አለች የኛ ሰፈሯ… ‹በህመም<br />

ነው የማይቀለደው እንጂ በሞትማ ቀላል<br />

ይቀለዳል እንዴ? በነገራችን ላይ ‹‹በህመም<br />

ነው የማይቀለደው እንጂ በሞት ይቀለዳል››<br />

የሚለው የትኛው ኢንሳይክሎፒዲያ ነው?<br />

የታች ሰፈሩ ላይ ይሆን?<br />

እውነት ግን አዲስ አበባችን እንኳን<br />

ርሃብ ችግር ራሱ በሰረገላ ቁልፍ ሳይቆለፍበት<br />

አልቀረም እውነቴን ነዋ! ቆይ ግን ችግሩ<br />

ሁሉ ተሰብስቦ የተቆለፈበት እኛ ሰፈር ነው<br />

እንዴ? [እርስዎም ይሄንኑ ሳይሉ አይቀርም<br />

ብለን ጠረጠርን] አዲስ አበቤ ምንድን ነው<br />

የምትሉት? ዳውን ታውን ቡጊ ቡጊ ሲል ነው<br />

የሚጨሰዋ! ሰሞኑን አንድ ሚጢጢ ጥገኛ<br />

ባለ ሀብት ይዞኝ ገባ። መጠጡ አናታቸው<br />

ላይ ሲወጣ ከአንደበታቸው ደግሞ ግጥም<br />

15<br />

ሲወጣ አየሁ። የዜማውን ነገር ተውት አሃ!<br />

የዜማው ቅርፅ እንደ አካሄድ በመሰረተ ሀሳቡ<br />

ያስማማኛል። ሬንጁ ጠባብ ሆኖ የሪትሙ<br />

ትራንስፎርሜሽን ልማታዊ አይደለም። ግጥሙ<br />

ግን እንዲህ ይነበባል፡-<br />

እድገት እድገት ይላል ያላየ<br />

ህልመኛ<br />

ዳቦ ዳቦ ይላል የነገ ተስፈኛ<br />

ሰው በራብ መሞቱን ማን አውቆ<br />

ያለኛ!<br />

እውነቴን ነው መታወቂያ በማሳየት<br />

ልይዛቸው አሰብኩና ነገር ግን በዘፈኑ ልክ<br />

እርምጃ ለመውሰድ እንዲመቸኝ ተውኩት።<br />

ልክ ነኛ! ከዘፈኑ በመለስ [ይሄ መለስ ቀለስ<br />

የሚባልበት ቦታ መቼም…] ‹‹ችግር እስካላመጡ<br />

ማንም ‹‹ጋጠወጥ›› አልደግመውም አፉን<br />

መክፈት ይችላል፤ የአፉ አከፋፈት ሌላ ትርጉም<br />

እስካላሰጠ ድረስ›› ስል የታች ሰፈር ልጆች<br />

ተበድረው አይስቁብኝ መሰልዎ… ጥርሳችሁ<br />

ይርገፍ እንዳልል በቦክስ ጨርሰውታል።<br />

አደገኛ ፍንዳታ ሁላ! [በነገራችን ላይ አደገኛ<br />

ፍንዳታ፣ አደገኛ ቦዘኔ ከሚለው አደገኛ፣ አደጋ<br />

ጣይ ቃል የመጣ ነው።]<br />

እኔ የምለው ሰሞኑን ደግሞ ውሃና<br />

ፍሳሾች ከሰው እኩል ሊያደረጉን ነው። ውሃ<br />

ካለበት አካባቢ ወደ ሌለበት ሊያካፍሉን ነው<br />

ወንዳታ! ግንኮ በነካ እጅ ዳቦ ላጣነውም በርገር<br />

በሊታዎች እንዲያካፍሉን ህግ ይውጣልን!<br />

አንዱ ጠብቆ አዳሪ ‹‹መንግስት የከተማ ግብርና<br />

እያደራጀ እንዳለው ሁሉ ለምን እኛንም በከተማ<br />

እርፍና አያደራጀንም?›› ብሎ አረፈው። አዩ<br />

ግን ልዩነት… አንዱ ባደራጀን፣ ሌላው በክፉ<br />

አይኑ ባላየን፣ ሌላው… ሌላው…<br />

ምን ትዝ አለኝ… ‹‹የእጅ መታጠብ<br />

ቀን›› ሰሞኑን ሲከበር ኢቴቪ ላይ ያፈጠጠው<br />

አያቴ ‹‹የሚበላ ሳይኖር እጅ መታጠብ በራሱ<br />

በሽታ ነው›› ሲል የእህቴ ልጅ አቢቲ እየተኮላተፈ<br />

‹‹እንዴ በአምስት ዓመቱ ትራንስፎርሜሽን<br />

‹‹የእጅ መታጠብ ቀን›› የሚበሉት ላላቸው<br />

ተብሎ ይስተካከላል፣ ለሌላቸው ደግሞ ዳቦ<br />

የማይገኝበት ቀን ይከበራል›› ቢላቸው ደማቸው<br />

ባንዴ እንደ ባንዲራ ላይ አይሰቀል መሰልም።<br />

አሁን ግን ለሀዘን ዝቅ እንደሚደረገው ባንዲራ<br />

ትንሽ ዝቅ ብሏል ወላዲቴን! ግን እስቲ አስቡት<br />

‹‹የሚበሉት ባላቸው ዘንድ የሚከበረው የእጅ<br />

መታጠብ ቀን ለዚህ ጊዜ ያህል ተከብሮ ዋለ››<br />

ሲባል።<br />

ሰሞነኛ ወዳጆቼ ሆይ ቆይማ!<br />

ስልኬን መዝጋት አለብኝ እንዴ? አላዋራ<br />

ያለን ቴሌ ተማረሩ ብሎ ሲፈርድብን ነው<br />

መሰለኝ የማስታወቂያ ጋጋታ ያስልክብኛል።<br />

የጠ/ሚኒስትራችንን የበቀደም የፓርላማ ውሎ<br />

ለታሪክ ላኑረው ብዬ ከዩ ቲዩብ ዳውን ሎድ<br />

ላድርግ ብል መከራ ሆነብኝ። ይህን የነገርኩት<br />

ወዳጄ ‹‹ጀምረኸው ናዝሬት፣ ሀዋሳ ዘመድ<br />

ጠይቀህ ብትመለስ ይቀልሀል›› ብሎ ሙድ<br />

ይዞብኛል። ኧረ! ልማታዊ ዳውን ሎድ ስናደርግ<br />

እንኳን ቴሌያችን እንዴት ነው?<br />

ሰሞኑን አሜሪካ ካሊፎርኒያ ውስጥ<br />

ከጭነት መኪና ያመለጡ ንቦች ፖሊሶችን<br />

ሳይቀር እየነደፉ መሆናቸው አስደንጋጭ<br />

እንደሆነ ሬዲዮ ፋና ደጋግሞ እየዘገበ ነው፡<br />

፡ ይህንን የሰሙ የታች ሰፈር ልጆች ‹‹ወይ<br />

ሬዲዮ ፋና እናንተ የሚታያችሁ የፈረንጅ ንቦች<br />

ብቻ ናቸውን?›› ሲሉ አፊዘዋል፡፡ ‹‹የአገራችን<br />

ንቦች ንድፊያ ለምን አልተወራም›› ነው ነገሩ<br />

መሰለኝ። አንዳንድ አሉባልተኞችማ ‹‹ፋና<br />

ሆይ አንተ የንቦችን ማር እንጂ ንድፊያ የት<br />

አውቀኸው?›› እያሉ ያማሉ አሉ። ሌሎች<br />

ደግሞ ‹‹ንቦች ያላስቸገሩበት የት አለ?›› እያሉ<br />

ያንሾካሽካሉ። ለማንኛውም እኔ የለሁበትም<br />

ብሎ መሰናበት ሳይሻል አይቀርም፤ ስንቱን<br />

ገስፀን እንችላለን? በሁለት ሳምንት ውስጥ<br />

አይቀርላችሁም እንደተባለው ‹‹ፀባይ ካላችሁ<br />

ሁለተኛውንም እናሳልፍላችኋለን›› ካሉን<br />

የሳምንት ሰው ይበለን። ሰላም!!!<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ


16<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />

“ሽብርተኝነት ለኢትዮጵያ ባዕድ የሆነ ነገር ነው<br />

…በዚህ ሰበብ ሽብርተኝነትን እንዳናስተምር እሰጋለሁ”<br />

አቶ መለስ ሲናገሩ አቃቤ ሕጎች፣ ዳኞችና ፖሊሶች ይኼንን<br />

ተከትለው ይሄዳሉ ብለው እንኳን አያስቡም<br />

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም<br />

በኤልያስ ገብሩ<br />

የፀረ-ሽብርተኝነት አዋጁን እንዴት ተመለከቱት?<br />

ለእኔ …የፀረ-ሽብርተኝነት ሕጉ አሜሪካ እንደዚህ አይነት ሕግ ወጥቷል። ይኼም ሕግ ሲወጣ<br />

በአሜሪካ ውጥ ብዙ ጩኸት ነበር። ‹‹የሰብዓዊ መብቶችን ይነካል›› በሚል ብዙ ችግር ነበር።<br />

እኛ ጋር የሚያሳዝነኝ የዛን መገልበጥ፣ እነሱ የሆኑትን መሆን እና እነሱ የሚፈልጉትን<br />

መሆን መሆናችን ነው። በእኛ በራሳችን፣ በታሪካችን፣ በባህላችንና በመንፈሳዊ ህይወታችን<br />

በኩል ተነስተን ብናየው ሽብር። እንደዚህ አይነት ነገር አናውቅም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ገበያ<br />

ላይ ወጥቶ፣ ትምህርትና ሆስፒታል ሄዶ ቦምብ የሚጥል ሕዝብ አይደለም። በታሪካችን<br />

እንደዚህ አይነት ነገር የለም፤ በፍፁም ባዕድ ነው። እና ይኼን የሌለብንን ነገር ‹‹አለባችሁ››<br />

ብሎ ፈረንጆች ስላሉ ብቻ በራሳቸው ችግር… እነሱ ደግሞ ይኼንን እንዴት እንዳገኙት<br />

እናውቀዋለን። ‹‹እኛም ጋር ይሄ ይመጣል›› ብሎ ወይም ‹‹አለ›› ብሎ እንደዚህ ጠ/ሚ/ሩ<br />

በእርግጠኝነት የሚናሩት ከየት እንደመጣ አላውቅም። የተቃዋሚዎችና የስልጣን ተቀናቃኞች<br />

ችግር ይኖራል። ነገር ግን ይኼ ‹‹ሽብርተኛ›› ተብሎ ከሽብርተኛ ጋር የሚያስፈርጅ ምንም<br />

ነገር የለበትም - ለእኔ፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ በዕድሜዬ ያየሁት ድሮ አንድ ጊዜ ሲኒማ<br />

አምፒር፣ ጊዎንና ዋቢ ሸበሌ ሆቴል እና ማዘጋጃ ቤት ቦንብ ፈንድቶ ነበር። እነዚህን እነማን<br />

እንዳደረጉትም እናውቃቸዋለን። ይኼ ‹‹የኢትዮጵያዊ ስሜት አለበት፤ የለበትም›› ብለን<br />

እንደው በሙሉ ልብ ለመናገር እንችላለን። እኔም እንደምገምተው ይመስለኛል። ክርክሩ<br />

‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ የፀረ-ሽብተኝነት ሕግ ‹ትክክል ነው አይደለም?› እኛ ኢትዮጵያውያን<br />

በእውነቱ የሽብር ታሪክና ባህል አለን ወይ?›› ነው። በዙሪያችን የሽብር ባህል ባላቸው ሀገራት<br />

ተከብበናል። ያ ግን እኛን ሽብርተኞች አያደርገንም - በጭራሽ።<br />

ከዚህ ጋር በተያያዘም፣ ጠ/ሚ/ር መለስ ሕጉን ቃል በቃል ከአሜሪካና ከእንግሊዝ መገልበጡን<br />

ተናግረዋል። አንድ ሕግ ወይም አዋጅ ሲወጣ የሀገሪቷን ነባራዊ ሁኔታ ማገናዘብ አይገባውም?<br />

ቃል በቃል ቀድቶ መገልበጥስ ትክክል ነው ይላሉ?<br />

እሱን እኮ ነው የምልህ! ከዚያ ነው የመጣው ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ የሌሎቹን ችግር…<br />

እንደዚሁ ነው የምናደርገው። በደርግ ጊዜም አንዴ ኮሎኔል መንግስቱ ባለበት ስብሰባ<br />

ላይ የተናገርኩት ነገር ነበር። የምናደርገው ችግርን ከመፅሀፈ ውስጥ እንፈልጋለን፡፡<br />

ለምሳሌ፣ ያን ጊዜ ‹‹ብሔረሰብ›› የተባለው ቃል ተፈጥሮ ነበር። ከመፅሀፍ ‹‹ብሔረሰብ››<br />

የሚለውን ቃል አውጥተን፣ የኢትዮጵያ ችግር አድርገን፣ እንደገናም ከመፅሀፉ ውስጥ<br />

መፍትሄ እንፈልግለታለን። የኢትዮጵያ ሕዝብ ችግር ምን እንደሆነ እሱን ራሱን<br />

እየጠየቁ በመረዳትና ለእዛ መፍትሄ ከማግኘት ፈንታ ከዚህ መፅሀፍ አንድ ችግር<br />

አውጥተን ከሌላ መፅሀፍ ደግሞ የዛን ችግር መፍትሄ እያመጣን የኢትዮጵያን<br />

ሁኔታ ለማሻሻል እንፈልጋለን። ይኼ ግን አይቻልም። ከራሳችን መነሳት<br />

አለብን። እኛው ማሰብ አለብን!። ጠ/ሚ/ሩ ከዛ ነው የገለበጥነው የሚሉት<br />

ነገር… ‹‹መገልበጥ›› ማለት ምን ማለት ነው? እኛ እናስብም? የራሳችንን<br />

ችግር መረዳት አንችልም? የራሳችንን ችግር ለይተን ባህላችንንና የሞራል<br />

ችሎታችንን መመርምርና ማወቅ አንችልም? ይኼ ነገር እነሱ ሀገራቸውም<br />

ውስጥ አለ። ለምሳሌ፣ በቅርቡ ኖርዌይ አንድ ሰው 70 ያህል ወጣቶችን<br />

በጥይት አርከፍክፎ በመጨፍጨፍ ገድሏቸው ነበር። እኛ ሀገር ይኼንን<br />

አይነት በሽታ አለ እንዴ?! የለም። በአሜሪካ አላባማ ግዛት እንደዚሁ<br />

ቦንብ አፈንድቶ ብዙ ሰዎችን ገድሏል። ጠበንጃ ይዘው ወጥተው መንገድ<br />

ላይ ያገኙትን ሰዎች በሙሉ ይጨፈጭፋሉ። በዚህ አይነት በሽታ<br />

የምንጠቃ ሕዝቦች አይደለንም። ግን ሌላ በሽታ የለብንም ማለት<br />

አይደለም። የራሳችን በሽታ አለን። ያንን ለማዳን መሞከር ነው<br />

እንጂ የሌለብን በሽታ ለምን ይሰጡናል።<br />

በሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 14፣ 16፣17፣18፣19፣20 እና 29<br />

የዜጎችን ሰብዓዊ መብትና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መደንገጋቸው<br />

ይታወቃል። በዚህም መሠረት ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የመናገር፣<br />

ኃሳብን በነፃ የመግለፅ፣ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ፣ መንግስትን<br />

የመቃወም፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች መ<strong>ስር</strong>ቶ የመንቀሳቀስ፣<br />

የዋስትና፣ የዳኞች ነፃነት መብት፣ ሰዎች ከታሰሩም በኋላ<br />

በወዳጅ ዘመድ የመጎብኘት… ወዘተ መብቶች አሉ፡፡ ሆኖም<br />

እነዚህን ሁሉ ሊሸረሽር የሚችል የፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ<br />

መውጣቱን የሚገልፁ ወገኖች አሉ። ምን ሀሳብ አለዎት?<br />

ከላይ እንደገለፅኩልህ ነው። ይኼ በአሜሪካንም ቢሆን በብዙ<br />

ሰዎች ዘንድ እንደዚሁ አይነት ከሕገ-መንግስቱ ጋር የሰብዓዊ<br />

መብቶችን ‹‹ይቃረናል፤ መብቶችንም አጥብቧል›› የሚል<br />

ክርክር አስነስቷል። በአሜሪካ ክርክሩ አሁንም እየተካሄደ<br />

ነው። በእኛም ሀገር የሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 29 ይመስለኛል<br />

መረጃን እንደፈለክ፣ በፈለከው አይነት ለመቀባበል መብት<br />

ይሰጥሃል። ግን እንደምናየው በኢንተርኔት በምናምን<br />

ያለን የታፈነ ሁኔታ በዚህ ሀገር አለ። ይኼ ስታትስቲክሱን<br />

የሚያሳይ ነው። በአፍሪካ በቅርብ ካሉን ጎረቤት ሀገራት ጋር<br />

ስንወዳደር ለምሳሌ በኬንያ፣ ሞባይል ስልክ ከ1000 ሰዎች<br />

መካከል 500 ያህሉ አላቸው፡፡ በዚህ ሶማሊያና ጅቡቲም<br />

ይበልጡናል። ለምን እንደዚህ ሆነ? ሶማሊያና ጅቡቲ እንዴት<br />

ይበልጡናል? የኢንተርኔት አጠቃቀምንም ከወሰድክ እንደዚሁ ነው፡፡<br />

ያለነው ታች ላይ ነው፡፡ ለምን እንደዚህ ይሆናል፡፡ ይኼ ሁሉ የመታፈን<br />

ሁኔታ እያለ ያንን ሕገ-መንግስቱን ጠቅሶ ‹‹ይኼ ተሻረ… ይኼ ተሻረ››<br />

ማለት እንደው መመፃደቅ ይመስለኛል። ሕገ-መንግስቱ በተለይ በንግግርና<br />

በመፅሀፍ መብት በኩል አንዱ ግልፅ የሆነው ነገር ጠ/ሚ/ሩ ‹‹ማስረጃ<br />

አለን፤ ሰብስበናል›› በማለት ተናግሯል። እንዴ! ያ ማስረጃ ሳይሰበሰብ<br />

ሰዎቹ ለምን ታሰሩ? ሰዎቹን አስሮ ነው ማስረጃ የሚሰበሰበው? ወይስ<br />

መጀመሪያ ማስረጃ ተሰብስቦ ነው ሰዎቹ የሚታሰሩት? ይሄ እኮ በቂ ነው፤<br />

በግልፅ ይታያል። …በእርግጥ ለሽብር የተዘጋጁና ለሽብር የሚዘጋጅ<br />

ሰዎች ካሉ ይኼንን ማን ይፈልጋል? እነዚህን ወንጀለኞች አይያዙ<br />

ብሎ ማን ይከራከራል? ለምን? ..ግን እንደው በጭራሽ [ተግባሩ]<br />

በመንፈሳቸውና በእንደዚህ አይነት ነገር በምንም የማይጠረጠሩ<br />

ሰዎችን ከያዙ በኋላ ‹‹እንመረምራለን፣ ማስረጃ እናሰባስባለን፣


አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />

እንዲሁም እንፈልጋለን›› ማለት በሕግ መቀለድ<br />

ነው።<br />

በኢትዮጵያ የፀረ-ሽብርተኝነት ሕግ በትርጓሜ<br />

ደረጃ ሰፊና የተለጠጠ ከመሆኑ ባለፈ እንደወንጀል<br />

የሚቆጥራቸው ከ16-23 የሚሆኑ የሕግ መንግስቱ<br />

አንቀጾችን ጋር የሚጋጭና ‹‹ሽብርተኝነት›› ብሎ<br />

የሚወነጅላቸው ድርጊቶች ግልፅነት የሚጎድላቸው<br />

(vague) መሆናቸው ይገለፃል። እንዲሁም፣<br />

‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ ሕጉ የወጣው ለሀገሪቷ በከፍተኛ<br />

ደረጃ ግልፅና ድርስ ወይም (clear and present<br />

danger) የሆነ የሚያሰጋ የሽብርተኝነት ተግባር<br />

በሌለበት ሁኔታ ነው›› እየተባለ ነው። ይኼንን<br />

ከዜጎችን ሰብዓዊ መብቶችና ከፖለቲካ ምህዳር<br />

ማጥበብ አንጻር እንዴት ያዩታል?<br />

እኔ ይኼንን ከዚያ በላይ ነው የማየው። ‹‹ሰብዓዊ<br />

መብቶች›› የሚባሉ ነገሮችን ለብዙ ዓመታት በዚህ<br />

ሀገር አይቻለሁ። ይኼን ያህል የሚነሳ አይደለም።<br />

እኔን በጣም የሚያሰጋኝ ‹‹ሽብርተኛ›› እና ‹‹ሽብር››<br />

የሚባለው ነገር እንዲህ.. እንዲህ እየተባለ ሲነገርና<br />

እያሰፋነው ስንሄድ ሕዝቡን ነገሩን እንዳናስተምረው<br />

ነው። በፀረ-ሽብርተኝነት ሕግና ሰበብ ሽብርተኝነትን<br />

እያስተማርን ነው ወይ? ይኼ ነገር ያሳዝነኛል::<br />

ለወደፊትም ያሰጋኛል፡፡<br />

መንግስት እያንዳንዱን ጥቃቅን ድርጊት ሁሉ<br />

‹‹ሽብርተኝነት›› ብሎ ከተረጎመው በዚህ ሁኔታ<br />

በአሁን ወቅት በኢትዮጵያ ውስጥ ምን አይነት<br />

የፖለቲካ እንቅስቃሴ ማድረግ ይቻላል? ሲሉ<br />

በጭንቀት የሚጠይቁ ወገኖች አሉ፡፡ በዚህ ላይ ምን<br />

ይላሉ?<br />

የፖለቲካ ትግሉ የተለያየ ፈርጅ ነው። በእርግጥ አንድ<br />

ነገር ማለት እፈልጋለሁ፡፡ አንዳንዴ ጊዜ የሚታዩ<br />

ነገሮች ስላሉ የፖለቲካ ድርጅቶችና ተቀናቃኝ ቡድኖች<br />

ግልፅ ማድረግ አለባቸው፡፡ ‹‹ትግላችን በሠላም<br />

የሆነ እንደሆነ “መልካም”፣ በሠላም ካልሆነ ደግሞ<br />

“እንዴ!? ምናምን” የሚባል ነገር አለ። ሌላ መንገድ<br />

የለም። ለፖለቲካ ትግል ከሠላም ውጪ ሌላ መንገድ<br />

የለም። በዚህም ‹‹በሰላማዊ ትግል ሄደን እናሸንፋለን።<br />

እየገደሉን እንታገላለን። እየደበደቡን እንታገላለን።<br />

እያሰሩን እንታገላለን›› የሚሉ የፖለቲካ ቡድኖች<br />

መነሳትና በግልፅ ይኼንን መናገር አለባቸው።<br />

…‹‹ይኼ የአመራሩ አገዛዝ ልክ አይደለም፤<br />

እንቃወመዋለን። የምንቃመው በሰላማዊ መንገድ<br />

እንጂ ሌላ መንገድ የለንም። ሊገድለን ሲዘጋጅና<br />

ሲገድለንም እንሞትለታለን።›› መባል አለበት፡<br />

፡ ይኼንን በአረቡ ዓለም እያየን አይደለም እንዴ?<br />

ለመሞት መዘጋጀት የሚያቅተው ሰው መግደልን ማን<br />

ያስተምረዋል? መታሰርም ያው ነው። ግን ጥፋቱ<br />

ቆይቶ በማንም ላይ ይደርሳል ነው፡፡ ዛሬ [ቃለምልልሱ<br />

የተደረገው ከትናንት በስትያ ነበር] በአርጀንቲና 12<br />

የጦር ኃይሉ መኮንኖች የዛሬ 30 ዓመት በፈፀሙት<br />

ወንጀል ዕድሜ ልክ ተርዶባቸዋል፡፡ በግብፅ ሁለት<br />

ፖሊሶች ባለፈው ጊዜ አንድ ወጣት ገድለው<br />

ተፈርዶባቸው ነበር። ማምለጥ አይቻልም። በአሁኑ<br />

ጊዜ የዓለም ማሕበረሰብና ዓለም አቀፋዊ ህሊና፤<br />

እንዲሁም ሰዎች መሸሽና ማምለጥ የማይችሉበት<br />

ሁኔታ እየተፈጠረ ነው። ስለዚህ ልናድግና ልንሻሻል<br />

የምንችለው በወንጀል፣ በጠብና በዱላ አይደለም<br />

- በክርክር እንጂ። እንከራከር በቃላትም እንዋጋ<br />

የፖለቲካ ትግል ማለት ያ ነው። ያንን እንልመደው፡፡<br />

‹‹የፖለቲካ ፓርቲዎች ሳያወላውሉ የፖለቲካ ትግልን<br />

መስመር ለመያዝ መታገል አለባቸው›› እላለሁ።<br />

በአንፃሩ በአገዛዙ በኩል ጡንቻና ጉልበት አላቸው።<br />

‹‹በዚህ በጉልበታችን እየተጠቀምን እንገድላለን፣<br />

እናስራለን፣ እንደበድባለን፣ እናስፈራራለን›› ቢሉ<br />

ሽብር ይኼ ነው። ‹‹ያንን ሽብር ደግሞ እኛም<br />

ሳንፈራ እንቀበላለን›› ብሎ ቆርጦ በመንፈሳዊ ኃይል<br />

ለመዋጋት መዘጋጀት ያስፈልጋል።<br />

በአዋጁ መሠረት ፖሊስ ያለምንም የፍ/ቤት ትዕዛዝ<br />

ተጠርጣሪዎችን ማ<strong>ስር</strong> የሚችልበት ሁኔታ አለ፡<br />

፡ ካሰረም በኋላ መረጃ ለመሰብሰብ እስከ አራት<br />

ወር ጊዜ ድረስ መጠቀም እንደሚችል ሰፊ መብት<br />

ተሰጥቶታል። በሕገ-መንግስቱ መሠረት ደግሞ<br />

አንድ ሰው በ48 ሰዓታት ውስጥ ፍ/ቤት መቅረብ<br />

አለበት ይላል። ከዚህ አንጻር አንደኛው ህግ መሻሻል<br />

የለበትም ይላሉ፤ወይም ህገመንግስቱ? ወይም<br />

የጸረሽብር ህጉ?<br />

ሕገ-መንግስቱ እነሱ ሲፈልጉ የሚጠቅሱት ነገርና<br />

ሲፈልጉም አንተን ለማጥቂያ የሚጠቀሙበት<br />

መሳሪያ እንጂ ለዜጎች መከላከያና ከለላ እንዲሆን<br />

ማድረግ አልቻሉም። ከላይ እንደተናገርኩት፣ አሁን<br />

ባለንበት ጊዜ አንድን ሰው ይዘኸው መረጃና ማስረጃ<br />

መሰብሰብ ልክ አይደለም። ይኼ እንኳን ኢትዮጵያ<br />

ውስጥ ቀርቶ በዚህ የሽብረተኝነት ጉዳይ በአሜሪካም<br />

እየተደረገ ነው፡፡ ለእነሱ የአሜሪካ ማድረጉ ትልቅ<br />

መስክርነት ነው። …መነሻው ‹‹እኛ ከእነሱ ልንሻል<br />

አንችልም›› ነው። ለምን ልንችል አንችልም?<br />

[እየሳቁ] እነሱ ከተሳሳቱ እኛም መሳሳት አለብን? -<br />

ያውም በታሪክና በባህላችን፤ በማናውቀውና በፍፁም<br />

በሌለብን በሽታ። አሁን መሸሸጊያና መከራከሪያችን<br />

ሕገ-መንግስቱ ብቻ አይደለም፡- የታሪክ፣ የባህላችንና<br />

መንፈሳዊ መሠረታችን ጭምር እንጂ።<br />

የፀረ-ሽብርተኝነት ሕግን በርካታ አገሮች አውጥተዋል።<br />

ለምሳሌ፣ በአፍሪካ ኬኒያንና ናይጄሪያን ብንወስድ ሕጉ<br />

በሰላማዊ መንገድ በሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች<br />

ላይ ተፅዕኖ ሲፈጥር አይታይም። በኢትዮጵያ ግን<br />

ተፅዕኖ እየፈጠረ እንደሚገኝ በተደጋጋሚ ይገለፃል።<br />

የእኛን አዋጅ ከሌሎቹ ጋር እንዴት ያነፃፅሩታል?<br />

በአፍሪካ ብዙ ሀገሮች …ሩቅም ሳንሄድ እዚሁ<br />

ጎረቤታችን ያሉትን እንመልከት፡፡ ለምሳሌ፣ ኬንያ<br />

ከእኛ የበለጠ በሽብርተኞች ተጠቅተዋል፡፡ አሁንም<br />

እየተጠቁ ነው። ነገር ግን፣ በተቻላቸው መጠን<br />

ወጣና ጥልቅ ብለው ሳይገቡበትም ከአሜካኖችና<br />

ምዕራባውያን ጋር በአጠቃላይ ያላቸው ግንኙነት<br />

እንደኛ አይደለም። እኛ ጥልቅ ብለን ነው የገባንበት<br />

-ለምሳሌ በሶማሊያ ስንገባ፡፡ ከዛም በኋላ አሁን<br />

እንደምትለው በሕጉ ላይ የምናሳየው ጠንካራነትና<br />

ኃይለኛነት፡፡ …ሁለት የስዊድናውያን ጋዜጠኞችን<br />

ያለፍቃድ ወደ ሀገር ውስጥ ገብተዋል ተብሎ ይህ<br />

ሁሉ ነገር…እኔ እንደዛ ናቸው ብዬ ለመገመት<br />

ያስቸግረኛል። ምዕራባዊያኖቹ ቀደም ሲል<br />

ለህወሃትም ሲያዝኑ ነበር። ለሻዕቢያም ሲያዝኑና<br />

ሲረዱ ነበር። አሁን እንደዚህ አይነት ነገር እያደረጉ<br />

ይሆናል። ይተዋወቃሉ። ይኼ ይመስለኛል። ነገር<br />

ግን፣ እኛ ከአፍሪካኖች፣ ከአሜሪካኖች፣ ከእንግሊዞች<br />

ጋር የተለያየን ነን። በሽብር በፍፁም ከእነሱ ጋር<br />

አንወዳደርም - ታሪካችንን እንዲህ በትንሹ ያየው<br />

ሰው እንደዚህ አይነት ነገር የለብንም። ይኼ የእኛ<br />

በሽታ አይደለም። ‹‹የኢትዮጵያ ሕዝብ ነኩኝ፤<br />

መብቴን ነጠቁኝ›› ብሎ ከዛ ካጠቃው ባለጋራው<br />

ጋራ ይጣላል። ነገር ግን፣ ለምሳሌ በሌላ ወንጀልም<br />

ቢሆን የሴቶችን አይን ማውጣትና በአሲድ<br />

ማቃጠል የመሳሰሉ አዲስ በሽታ ሆነው እዚህ ሀገር<br />

መጥተዋል። እንደዚህ አይነት ነገር ነው ሕዝቡን<br />

የምናስተምረው፡፡<br />

‹‹የፀረ ሽብርተኝነት አዋጁ አያስፈልግም፤ ለመሰል<br />

ወንጀለኞች የኢትዮጵያ የወንጀልኛ መቅጫ ሕግ<br />

በቂ ነበር›› የሚሉ ፖለቲከኞች አሉ። በእርስዎ<br />

እምነት የአዋጁ መውጣት ተገቢ ነው?<br />

ለእኔ ሕግ ሲወጣ ችግሩ መጀመሪያ መኖር አለበት።<br />

ያ ሕግ ያስፈልገበት ምክንያት መኖር አለበት።<br />

እኛ ሀገር ‹‹ሽብር›› ከምን ተነስተን ነው? ከላይ<br />

የገለፅኳቸው አንዳንድ የዛሬ ስንት ዓመት አንድ..<br />

ሦስት.. አራት ቦታ የተጣሉ ቦምቦችን ይዘን ነው<br />

ኢትዮጵያ ውስጥ ሽብር አለ ብለን የምንነሳው? ወይስ<br />

ምን ችግር አለ ብለን? እዚህ ስንት ችግር ያለበት<br />

ነው። ለምሳሌ፣ ለችጋርና ችጋርን ለማስወገድ ለምን<br />

እውነተኛና ደንበኛ ሕግ አይወጣም? ሽብርተኝነት<br />

የለብንም በሽታችን አይደለም። በሽታችን ካልሆነ<br />

ለምን ሕግ እናወጣለታለን? አስፈላጊ አይደለም።<br />

‹‹በኢትዮጵያ ውስጥ ሽብር ሳይኖር እንዳለ አድርገን<br />

የምንናገር ከሆነ እውነተኛ ሽብርተኝነት ሊፈጠር<br />

ይችላል›› እያሉኝ ነው?<br />

አዎን፤ አዎን! ‹‹እንዲህ ነው.. እንዲህ ማድረግ…<br />

እንዲህ ማድረግ›› እያልክ በተናገርክ ቁጥር<br />

ማስተማር እኮ ነው።<br />

በዓለም ላይ መንግስታዊ ሽብርተኝነት መኖሩ<br />

ይነገራል። ህወሓትም በትጥቅ ትግሉ ወቅት<br />

የሽብር ድርጊት ይፈፅም እንደነበረ ተገልጾ በዓለም<br />

የሽብርተኝነት ዝርዝር ውስጥ መካተቱን መረጃዎች<br />

ያስረዳሉ። ይኼ አሁን መንግስት ከያዘው አቋም<br />

ጋር አይጣረስም?<br />

ህወሓት ጫካ በነበረበት ጊዜ ያለ ምንም ጥርጥር<br />

ሽብርተኝነትን ፈፅሟል። ጠ/ሚ/ሩ እኮ በአደባባይ<br />

በቴሌቭዥን ባንክ እንደዘረፉ እኮ ነግረውናል። ይኼ<br />

ሽብርተኝነት አይደለም? [እየሳቁ] ይኼ ሽብርተኝነት<br />

ከሚባሉ ነገሮች ውስጥ አንዱ ነው። ግን ከዛ በኋላ<br />

መንግስት ሆነዋል። መልካም! መንግስት ከሆኑ<br />

በኋላ ሌሎች ድርጅቶች ድሮ እነሱ በነበሩበት በትጥቅ<br />

ትግል ‹‹እንታገላለን፤ ስልጣን እንይዛለን›› የሚሉ<br />

ድርጅቶችን ለመቋቋም እነሱ በትጥቅ ትግል በኩል<br />

ስላለፉ ምን ምን እንደሚያስፈልግና ሽብርተኝነትም<br />

እንደሚያስፈልግ ያውቃሉ። ስለዚህ በእነዛ በትጥቅ<br />

ትግል በተዘጋጁት ድርጅቶች ላይ ‹‹እነዚህን ድሮ<br />

ስናደርግ እንደነበረው ያደርጋሉና እናግዳቸው፣<br />

እናፍናቸው፣ እኛም ያደረግነውን እንዳያደርጉ<br />

እናድርጋቸው›› የሚል ስሜት ሊያደርባቸው<br />

ይችላል። ነገር ግን፣ ‹‹በፖለቲካ ትግል ሕጋዊ በሆነ<br />

መንገድ እንታገላለን›› የሚሉትን የፖለቲካ ቡድኖች<br />

እዚህ ውስጥ ማስገባት ተገቢ አይደለም። እንግዲህ<br />

ልዩነቱ ይኼ ነው። በትጥቅ ትግል የሚሄዱትንና<br />

እንሄዳለን የሚሉትን በዚሁ በሽብርተኝነት መክሰስና<br />

መወንጀል ምናልባት ያስኬድ ይሆናል። ግን ‹‹እነዛም<br />

ተቀናቃኝ የፖለቲካ ቡድኖች ናቸው›› ብሎ በትጥቅ<br />

ትግል ያሉትን የፖለቲካ ቡድኖች በሰላማዊ ትግል<br />

ውስጥ ካሉት የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር አንድ<br />

አድርጎ ማየትና መወንጀል በፍፁም የሚያስኬድ<br />

አይደለም። የፖለቲካ ፓርቲዎቹም ‹‹በፖለቲካ<br />

ትግል ነው የምንሄደው፤ በሕጋዊ <strong>ስር</strong>ዓት ነው<br />

የምንታገለው›› ብለው የቆዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች<br />

ይኼንን ግልፅ አድርገው ማሳየት አለባቸው።<br />

ነገር ግን፣ በወላዋይነት አንድ እግራቸውን እዚህ<br />

አንደኛውን ደግሞ እዚያ አንፈራጥጠው የሚሄዱ<br />

ከሆነ ያም አያስኬድም፤ ልክ አይደሉም።<br />

መንግስት ‹‹ሽብርተኛ›› ብሎ የፈጃቸውን የፖለቲካ<br />

ቡድኖች ከኤርትራ መንግስት ጋር ተባብረው<br />

እንደሚሰሩ በተደጋጋሚ ውንጀላውን ያቀርባል፡<br />

፡ የኤርትራን መንግስት ግን ‹‹ሽብርተኛ›› ብሎ<br />

አልፈረጀም። የዚህ አንደምታው ምንድን ነው?<br />

ወንጅሏል እንጂ! ኤርትራን ‹‹የአሸባሪዎች ረዳት<br />

ነች›› ብሏል። በተጨማሪም፣ በአሜሪካና በተባበሩት<br />

መንግስታትም ይኸው ፍዳቸውን እያሳያቸው<br />

ነው። ለእኔም ሆነ ለማንም ሰው ግልፅ የሆነው<br />

አንድም ቦታ ኤርትራ በአሻባሪነት የሚፈርጅበት<br />

ሁኔታ አይታየኝም። የኢትዮጵያ አገዛዝ የኤርትራ<br />

መንግስት ተቀናቃኞችን ይረዳል፤ ያግዛል።<br />

እዚህ እየመጡ ስብሰባ ያደርጉ የለም እንዴ?!<br />

ኤርትራ ደግሞ የኢትዮጵያ መንግስት ተቀናቃኝ<br />

ቡድኖችን ይረዳል። ይኼ አንዱ አንዱን ለመጥለፍ<br />

የሚያደርገው ጥረት እንዴት አድርጎ ‹‹ሽብርተኛ››<br />

እንደሚሆን አላውቅም - ለእኔ።<br />

በኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔን መ<strong>ስር</strong>ተው<br />

በአመራርነት ለረዥም ዓመታት መስራትዎ<br />

ይታወቃል። የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ<br />

እንዴት ያዩታል?<br />

ኢሰመጉ አሁን የለም፤ ጠፍቷል፡፡ ከስሟል<br />

እንዲከስምም አድርገውታል። ስለዚህ የኢትዮጵያ<br />

እሳቸው ሲናገሩ አቃቤ ሕጎች፣ ዳኞችና<br />

ፖሊሶች ይኼንን ተከትለው ሌላ ነገር<br />

ያደርጋሉ ብለው እንኳን አያስቡም። …<br />

ለምሳሌ፣ ከዚህ በፊት እኛ በ1998 ዓ.ም<br />

ልንታሰር ስንል ጥፋታችንን ከነፍርዱ ነበር<br />

የሚናገሩት። ‹‹እንደዚህ አድርገዋል፣<br />

እንደዚህ አጥፍተዋል፣ ይኼንን ያህል<br />

ይፈረድባቸው። እስከ ዕድሜ ልክ<br />

ሊፈረድባቸው ይችላል›› ብለው ነበር።<br />

ዕድሜ ልክም ፈረዱብን።<br />

ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የሚባለው ተቋቁሟል። እሱ<br />

ደግሞ ስለ ሰብዓዊ መብቶች ሲናገር አንሰማም። ይኼ<br />

ነው ያለንበት ሁኔታ።<br />

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽንን ለማቋቋም<br />

ለምን የተፈለገ ይመስልዎታል?<br />

ደህና… የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በሌሎች ሀገሮች<br />

አለ። መጥፎው ነገር እሱ መቋቋሙ ሳይሆን የሲቪል<br />

ማሕበረሰቡን እና በግል በራሳቸው የሚያቋቁሙትን<br />

የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶችን ማጥፋቱ ነው።<br />

የራሳቸውን ማቋቋማቸው መጥፎ አይደለም።<br />

በቅርቡ የኮሚሽኑን ኮሚሽነር አምባሳደር ጥሩነህ<br />

ዜናን አነጋግረናቸው ነበር። ኮሚሽነሩ በሽብርተኝነትን<br />

ተጠርጥረው በመጀመሪያ የታሰሩ ጋዜጠኞችን<br />

መኖራቸውን ለሶስት ወራት ያህል አያውቁም ነበር።<br />

ይኼ ተገቢ ነው?<br />

[እየሳቁ] …ይኼንን እንዲከታተሉ አይደለም እኮ<br />

የተቋቋሙት፤ ለምን ይወቁት¡ [ከልባቸው እየሳቁ]<br />

የኢትዮጵያ ሕዝብስ በትክክል ሰብዓዊ መብቱን<br />

ያውቃል? አውቆስ መብቱን ለማስከበር ምን ያህል<br />

ዝግጁ ነው?<br />

መብቱን በደንብ ያውቃል። የኢትዮጵያ ሕዝብ<br />

በሕግ በኩል ምንም የሚጎድለው አይደለም። ድሮ<br />

የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያውቁትን የአንተ ትውልድ<br />

ያልደረሱበትን ነገር አለ። ሕዝቡ ስለ ሕግና ፍትሕ<br />

በደንብ ያውቃል። ማንም መንገደኛ ሰው ዳኛ ነው፡<br />

፡ ምስክር ነው፡፡ ፓሊስ ነው። አንድ ሰው ሲጠቃ<br />

ዝም ብሎ አይሄድም። ቆሞ በነገሩ ውስጥ ገብቶ፣<br />

የሚያዘውን ይዞ ዳኛ ጋር ወስዶ ይሄዳል። አስፈላጊም<br />

ሲሆን የተጣሉትን ሰዎች ኩታና ኩታቸውን ቋጥሮና<br />

አስፈፅሞ ምንም ሳታደርጉ ዳኛ ጋር እንድትሄዱ<br />

ብሎ ዳኛ ጋር ይልካቸዋል። ሰዎቹም በቀጥታ እዛ<br />

ዳኛ ጋር ይሄዳሉ። እንደዚህ አይነት ሕጋዊ <strong>ስር</strong>ዓት<br />

ያለው ሕዝቡ የትም የለም፡፡ ዛሬ ሰው ቢደባደብና<br />

ቢጋደል ማንም ዞር ብሎ የሚያይ የለም፡፡ ቆሞ ግን<br />

ይመለከታል። የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደዚህ አይደለም፡፡<br />

ጥቃት ሲፈፀም ዝም ብሎ አያይም። በጦርነትም ጊዜ<br />

ወታደሩ እሱ ነው። ተነስ ሲባል ተነስቶ ይዘምታል<br />

- በራሱ መሳሪያ፡፡ ስለዚህ መብቱን እንዳይጠቀም<br />

ያደረገው <strong>ስር</strong>ዓቱ ነው?<br />

በአሁን ወቅት የተቃዋሚ ፓርቲዎች መዳከማቸው<br />

ይታያል። በእርስ በርሱ ሽኩቻ ህልውናቸው አደጋ<br />

ላይ የወደቁም አሉ። በዚህ ሂደት ኢህአዴግ ለረዥም<br />

ዓመት ኢትዮጵያን ከመምራት ምን ያግደዋል?<br />

አዎን። ችግር አለ፤ ግልፅ ነው። ቢፈራርሱም እኔ<br />

ለራሴ አላለቅስም። በራሳቸው ችግር ነው። ከአሁን<br />

ወዲያ እውነተኛና ደንበኛ የፖለቲካ ፓርቲዎች<br />

ቢቋቋሙ ከሕዝቡ የሚነሱ ለስልጣን የቋመጡ<br />

ጥቂት ሰዎችን ስብስበው ወይም የፓርላማ ደመወዝ<br />

እየበሉ ለመኖር የሚፈልጉ ሰዎች የሚያቋቁሙት<br />

ፓርቲ ሳይሆን እውነተኛ ትግል ውስጥ መግባት<br />

የሚፈልጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ከሕዝብ ጋር ሆነው<br />

የሕዝቡን ብሶት/ ሮሮ/ ችግሮች የሚያንፀባርቁ ሰዎች<br />

የሚኖሩበትና የሚመሩት ፓርቲ መምጣት አለበት።<br />

እርግጠኛ ነኝ ይመጣል›› ነገም ከነገ ወዲያም ቀስ<br />

ብሎ እንደዚህ አይነት ፓርቲ ይፈጠራል።<br />

ባሳለፍነው ሳምንት ጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ በፓርላማ<br />

ከሽብርተኝነት ጋር በተገናኘ ቁጣ አዘልና ማስጠንቀቂያ<br />

የተቀላቀለበት ንግግሮችን ለተቃዋሚዎችና<br />

ለጋዜጠኞች መናገራቸው ይታወሳል። ይኼንን<br />

እንዴት ተመለከቱት?<br />

አቶ መለስ ማስፈራራታቸው አዲስ ነገር ነው እንዴ?<br />

ሁልጊዜ ይሳደባሉ፣ ያስፈራራሉ፣ እንደልባቸው<br />

ይናገራሉ፡፡ ሌላው ቀርቶ እሳቸው ሲናገሩ አቃቤ<br />

ሕጎች፣ ዳኞችና ፖሊሶች ይኼንን ተከትለው ሌላ ነገር<br />

ያደርጋሉ ብለው እንኳን አያስቡም። …ለምሳሌ፣<br />

ከዚህ በፊት እኛ በ1998 ዓ.ም ልንታሰር ስንል<br />

ጥፋታችንን ከነፍርዱ ነበር የሚናገሩት። ‹‹እንደዚህ<br />

አድርገዋል፣ እንደዚህ አጥፍተዋል፣ ይኼንን ያህል<br />

ይፈረድባቸው። እስከ ዕድሜ ልክ ሊፈረድባቸው<br />

ይችላል›› ብለው ነበር። ዕድሜ ልክም ፈረዱብን።<br />

ይኼ የሚያደርጉት ነው። ‹‹ማስረጃ አለን፤<br />

እየሰበሰብን ነው›› ማለት ምን ማለት ነው? ሕጋዊ<br />

ለሆነ ሰውና ሕጋዊ <strong>ስር</strong>ዓትን ለሚመራ ሰው ይኼ<br />

በፍፁም የሚያስኬድ አባባል አይደለም። ምርመራው<br />

ተደርጎ፣ መረጃዎች ተሰብስበው፣ ማስረጃ ሁሉ<br />

ተዘጋጅቶ ነው ክስ የሚመሰረተው። ንፁውን ሰውዬ<br />

ይዞና አስሮ ብዙ መረጃ ለመሰብሰብ መሯሯጥ<br />

ተገቢ አይደለም። ታስረው ያሉ የሚሰቃዩ ሰዎች፣<br />

ጋዜጠኛችና አንዳንዶቹም የእኛ ጓደኞች በደንብ<br />

የማውቃቸው ሰዎች አሉ። ደበበ እሸቱ በምንም በኩል<br />

በደንብ አውቀዋለሁ። ቃሊቲም አብረን ነበርን። ከዛም<br />

በኋላ እንነጋገራለን፤ እንወያያለን። እንደዚህ አይነት<br />

ነገር በጭራሽ መንፈስ የለም፡፡ ይች ርዕዮትም<br />

የምትባል ልጅ ጥሩ ፀሀፊና ጥሩ ችሎታ ያላት ነች።<br />

ግን እንዴት አድርገው እዚህ ውስጥ እንዳስገቧትና<br />

እንደገባች እኔ አላውቀውም። እስክንድር ነጋም ፊት<br />

ለፊት የሚናገር ሰው ነው። ኃይለኛ ፀሀፊ ነው።<br />

እንደዚሁ እ<strong>ስር</strong> ቤት ሲገባና ሲወጣ 20 ዓመቱ ነው።<br />

ስለዚህ መቻቻል አለብን። ሽብርን በምንም አይነት<br />

መንገድ ልንጠራውና ልንለምደው የሚገባን ነገር<br />

አይደለም። ይኼ ሁሉ ጎረምሳ እዚህ ሀገር ጦሙን<br />

እያደረ በሰላም ይሄዳል። አጠገባችንና ጎረቤታችን<br />

ያሉት ሀገራት እኮ እንደዚህ አይደሉም። ይኼንን<br />

መንፈሳዊ መሠረታችንን ይዘነው ብንቆይ? በተለይ<br />

ወጣቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይኼንን ነገር እንዳይማር<br />

ብናደርግ የተሻለ ይመስለኛል።<br />

አቶ መለስ በተደጋጋሚ ‹‹ይኼ የመጨረሻ የስልጣን<br />

ዘመኔ ነው›› ብለዋል። እንዳሉት ቃላቸውን ጠብቀው<br />

ከስልጣን ቢወርዱ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሁኔታ<br />

ሊለወጥ ይችላል ብለው በሚገምቱ ወገኖች አሉ፡<br />

፡ ይስማማሉ?<br />

በመጀመሪያ እስኪ እሳቸው በምርጫ ተሸንፈውም<br />

ይሁን ከውስጣቸው ለአንዱ የተሻለ ሰው አግኝተው<br />

ስልጣን አስረክበው መደማመጥ የሚቻልበት ሁኔታ<br />

ከተፈጠረ ጥሩ ነው። ላለፉት 20 ዓመታት እኮ<br />

መደማመጥ የለም። አንድ አቅጣጫ ብቻ ነው።<br />

አቶ መለስ ይናገራሉ፤ ከላይ እንካችሁ ይላሉ።<br />

ከእኛ በኩል፣ ከሌላው ከሕዝቡ፣ ከጋዜጣውና ከሌላ<br />

የሚመጣውን ነገር ሰምቶ፣ አዳምጦና አብላልቶ<br />

ለዚያ ተገቢ መልስ የሚሰጥበት ሁኔታ የለም። ‹‹እኔ<br />

ልንገራችሁ እናንተ ስሙኝ። እኔ ትዕዛዝ ልስጣችሁ<br />

እናንተ ፈፅሙ ነው›› ያለው።<br />

በአሁኑ ወቅት ኑሮ በከፍተኛ ሁኔታ እየተወደደ<br />

መጥቷል። የምግብ ዋጋ ግሽበቱም 51.3 በመቶ<br />

ደርሷል። መንግስት ደግሞ ይኼንን የዕድገት አንዱ<br />

ምልክት ነው ይለዋል። በከተማ ውስጥ ሰው በረሃብ<br />

እየሞተ ባለበት ሁኔታ ግሽበት እንዴት የዕድገት<br />

ምልክት ሊሆን ይችላል? ብለው የሚጠይቁ ወገኖች<br />

ተበራክተዋል፡፡ ምን አስተያየት አለዎት?<br />

ስለዚህ በመንግስትም በሌላም ያሉ ኢኮኖሚስቶች<br />

ይናገሩ። …ድሮ ገና በአፄ ኃይለስላሴ ጊዜ በአዋሽ<br />

ተፋሰስ ላይ ባለስልጣን በሚቋቋምበት ጊዜ እድገትን<br />

አስመልክቶ አንድ ፅሁፍ ፅፌ ነበር። በአዋሽ ተፋሰስ<br />

ላይ የወንጂ ስኳር ፋብሪካን ለማቋቋም በእዛ ያሉትን<br />

ከብት አርቢዎችና ዘላኖች ወደ ደረቁ ቦታ ገፍተዋቸው<br />

ለሙን መሬት በሙሉ ለወንጂ ስኳር ፋብሪካ ሸንኮራ<br />

አገዳ ማምረቻ ሰጧቸው። ያን ጊዜ የፃፍኩት ነገር<br />

‹‹ምንድን ነው ዕድገት?›› የሚል ነበር። ለእነዚህ<br />

ለተገፉት ሰዎች ለአፋሮችና ለጂሌ ኦሮሞዎች ዕድገት<br />

ምን ማለት ነው? ሌሎች ሰዎች መጥተው ቤት<br />

ሰርተው፣ ሸንኮራ አገዳ ተክለውና ፋብሪካ አቋቁመው<br />

ሀብታሞች ሲሆኑ ማየትና መመልከት ነው ለእነዚህ<br />

ሰዎች እድገት? ያ ዕድገት እነሱን ይጨምራል ወይ?<br />

እየገፏቸው እንዴት ይጨምራቸዋል? ወደ ውጪና<br />

ወዳልተሻለ ቦታና መሬት እየመሯቸው እንዴት<br />

ያሻሽላቸዋል? ብዬ የዛሬ 45 ወይም 50 ዓመት ፅፌ<br />

ነበር፡፡ አሁንም የማየው እንደዛ ነው። ትልልቅ ፎቅ<br />

ቤቶች ተሰርተዋል። መንገዶች ተሰርተዋል። ግን<br />

ራሳችንን እንጠይቅ አንድ ትልቅ ፎቅ ቤት ሲሰራ<br />

ስንት ቤተሰብ መንገድ ላይ ተጥሏል? አንድ ኪሎ<br />

ሜትር መንገድ ሲሰራ ስንት ቤተሰብ መንገድ ላይ<br />

ተጥሏል? ለእነዛ ሰዎች ልማትና ዕድገት ይኼ<br />

ነው? ለአንዳንዶቹ ግን ነው። እዛ ላይ ደግሞ ብዙ<br />

የማናስበው ነገር አለ። ለጊዜው የምናየው ፎቅ ቤት<br />

መሰራቱን ብቻ ነው። ሰሞኑን በቱርክ በመሬት<br />

መንቀጥቀጥ በጣም በርካታ ቤቶች ድራሻቸው ነው<br />

የጠፋው። በድንገት ዝም ብለው የተሰሩ ትልልቅ<br />

ፎቆች ናቸው። አዋቂዎች ግና የዛሬ 50 ዓመት እዚህ<br />

ሀገር ከአምስት ፎቅ በላይ እንዳይሰራ ተናግረዋል።<br />

ያም መሠረቱ በደንብ ከተሰራ ነው፡፡ ዛሬ ዝም<br />

ብለን ለጠፍ ለጠፍ አድርገን ቤቶች ዝም ተብለው<br />

ይሰራሉ። እነዚህ የሀገር ሀብት ናቸው። እንዲቆዩልን<br />

እንፈልጋለን። ጉዳትም እንዲያመጡም አንፈልግም።<br />

ዕድገት ለሚባለው ነገር እነዚህ ሁሉ ነገሮች አብረው<br />

መታየት አለባቸው፡፡<br />

ኢትዮጵያ በድህነት ውስጥ ትገኛለች። ከእርስዎ<br />

የረዥም ጊዜ የሕይወት ልምድ አኳያ ኢትዮጵያ<br />

በአሁኑ ወቅት ምን ያስፈልጋታል ብለው ያስባሉ።<br />

ለመንግስት፣ ለተቃዋሚዎችና ለሕዝቡ ምን<br />

ይመክራሉ?<br />

በእኛ ሀገር አንድ የጎደለው ትልቁ ነገር መነጋገር<br />

አለመቻላችን ነው። ያለነው ተኳርፈን ነው።<br />

የመንግስት ስልጣን ይዘናል የሚሉት፣ በተለይም<br />

ስለሕዝቡ እናውቃለን፣ የህዝቡን ብሶትና ሮሮ<br />

እንናገር የሚሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ጋዜጠኞችም<br />

ሆኑ በግል ያሉ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች<br />

መንግስት ከሚባሉት ባለስልጣናት ጋር በቅን መንፈስ<br />

ለመነጋገርና ለመወያየት አልቻሉም። ‹‹ልንገርህ/ሽ››<br />

ሳይሆን ‹‹እንነጋገር ወይም እንደማመጥ›› የሚባለው<br />

ነገር ኢትዮጵያ ውስጥ ጎድሏል፡፡<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

17


18<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

ሴ ት<br />

ሴበመቅደስ<br />

ፍስሐ<br />

Mekdi745@gmail.com<br />

እኩልም ነሽ፤<br />

እኩልም አይደለሽም<br />

እኩልነት ማለት አለመበላለጥ ነው። በእኩልነት<br />

ስንቶችን እናምናለን? “ሴቶች ከወንዶች እኩል ነን” እንላለን።<br />

አንዳንዴ ይሄንኑ አባባላችንን ራሳችን አባባል ሆኖ እንዲቀር<br />

እናደርገዋለን። አንዳንዶች፣ “ሴቶች ከወንድ ‘እኩል ነን’ ብለው<br />

ካሰቡ እኩል መሆናቸውን ማንሳት በራሱ ምን አስፈለገ?”<br />

(ለምን ያስታውሱናል አይነት ነገር) ሲሉ አንዳንዶች ደግሞ፣<br />

“አይሆንም፤ ሴቶች የራሳቸው ጥንካሬ እንዳላቸው ሁሉ<br />

ከወንዶች የሚያንሱበት መንገድም አለ” ይላሉ። እናንተ በምን<br />

ትስማሙ ይሆን? እርግጥ አንዳንዴ እኩል የማያደርጉን ሰው<br />

ሰራሽና ተፈጥሮአዊ ነገሮች አሉ። ሰው ሰራሹ ራሳችን ሴቶቹ<br />

የፈጠርናቸው ሲሆኑ፣ የተፈጥሮው ደግሞ በተፈጥሮ ደረጃ<br />

በሴቶች ሊሰሩ የማይሞከሩ አንዳንድ ነገሮችን ማለቴ ነው።<br />

አሁን ስለእኩልነት ልሰብክ አይደለም - ብዙ ተብሏልና።<br />

ከዚህ ወጣ እንበልና፤ ወንዶች ከእኛ በምን ይበልጣሉ? እኛስ<br />

በምን እንበልጣቸዋለን? የሚለውን ነገር አስበን እናውቅ ይሆን?<br />

እንዲህ ነው፡- እነሱ በቀላል መንገድ የተቋቋሙት፣<br />

እንደ ተራራ የገዘፈ ነገር ሊኖር ይችላል። እናም፣ ያን የገዘፈ<br />

ሁነት በቀላሉ ተቋቁመውታልና ይበልጡናል። እኛ ሴቶች<br />

ያለፍነው፣ ነገር ግን ወንዶች ከባድ አድርገው የሚወስዱት ነገር፣<br />

ለእኛ “ኢምንት” ሆኖ እናገኘዋለን፣ ወይም ለእነሱ ተራራ ሊሆን<br />

ይችላል። ስለዚህ እዚህ ጋር ልዩነት ሲመጣ እኩል የመሆን ነገሩ<br />

ያከትማል ማለት ነው።<br />

ወንዱ በሴት የሚከወነውን ስራ ሙሉ ቀን ቁጭ<br />

ብለህ ስራ ከምትሉት ሞቱን ይመርጣል። አልወጣውም ብሎ<br />

ስለሚያስብ ብቻም ላይሆን ይችላል። እርግጥ ነው አይወጣውም።<br />

ቢወጣው እንኳ እሷ በተወጣችበት መንገድ ላይሆን ይችላል።<br />

አንድን ሴት ከወንድ እኩል ሙሉውን ጊዜ የጉልበት<br />

ሥራ ስሪ ብንላት የአቅሟ ሁኔታ የሚያስተማምን አይሆንም።<br />

እሷም አትቀበለውም። “ኧረ እኔ ሴት ነኝ! እንዴት እችለዋለሁ?”<br />

የሚል ጥያቄ ልታቀርብ ትችላለች። አይፈረድባትም።<br />

አንዳንዴ ወንዶች ሀዘንን በመቋቋም (ባለማክረር)<br />

ይበልጡናል ብዬ አስባለሁ። “ይሄማ አይሆንም። እነሱ እንደውም<br />

አይቋቋሙም” ያሉኝ ሴቶችም አሉ።<br />

እንደ’ኔ ግን ወንዶች ከእኛ በተሻለ ሁኔታ<br />

ይቋቋሙታል ባይ ነኝ። አንድ ሰው ከእኛ በሞት ሲለይ ማሰብ<br />

ባለብን መጠን ልናስበው ግድ ቢልም፣ ወንዶቹ ለለቅሶው ተብሎ<br />

ከሚባክኑ ወጪዎች አንስቶ “ፍራሽ ዘርግቶ” በመቀመጥ ነገሩን<br />

እየቆሰቆሱ ከማባባስ የፀዱ ናቸው።<br />

በዚህ የማይስማሙ አንዳንዶች፣ “እንበልና ሴቷ<br />

በባሏ ሞት ምክንያት ብቻዋን ብትቀር ሌላ ባል የማግባቷ ጉዳይ<br />

ምናልባትም እዚያ ላይ ሊያበቃ ይችላል፤ ካላበቃ እንኳን ሌላ<br />

የመተካቱ ነገር ይረዝማል። እንዲህ እንዲሆን ያደረገው ደግሞ<br />

ሃዘንን መቋቋም መቻሏ ነው” ይላሉ።<br />

ወንዱስ? ብቸኝነቱንና ሐዘኑን መቋቋም ወዲያው<br />

ይከብደዋል። እሱ፣ ከእሷ በተቃራኒ፣ እሷን የሚያስታውሱትን<br />

ነገሮች ከአጠገቡ አያርቅም። እሱ ግን እሷን ለመርሳት በሌላ<br />

ሊተካት ይፈልጋል - ይተካታልም። ያ ማለት ሃዘኑ ጎድቶታል፣<br />

ጎድቶትም እንዲቀጥል አይፈልግም ይላሉ።<br />

ሌላው የማነሳው ደግሞ ቸኩሎ ውሳኔ በመስጠት<br />

በኩል ሴቶች ረጋ ይላሉ ብል ማድላት አይሆንብኝም። አንድን<br />

ነገር ከመወሰን ይልቅ ከውሳኔ በኋላ ሊኖር የሚችለውን ውጤት<br />

(consequence) በማሰብ በኩል አንደኛ ይመስሉኛል - ሴቶች።<br />

እንዲህ ያለ አስተሳሰብ ያላቸው ወንዶች እንዳሉ አውቃለሁ፤<br />

ብዛታቸው የሴቶችን ያህል አይሆኑም ብዬ በማሰብ እንጂ።<br />

ለዚያም ነው ከውሳኔያቸው በኋላ ሴቶቹን ለመመለስ ለወንዶች<br />

ከባድ የሚሆነው።<br />

ምናልባትም የእሷ ውሳኔ ከዚያ በኋላ ግራ ያጋባህ<br />

ይሆናል። የማታውቃት መስሎ ሊሰማህም ይችላል። ነገር ግን<br />

በእርግጠኝነት የምነገረህ ወደዚህ ውሳኔ ከመምጣቷ በፊት<br />

ደጋግማ አስጠንቅቃሃለች። በዚህ ላይ አንባቢ የራሱን ግምት<br />

ይውሰድ።<br />

ሦስተኛውና የመጨረሻው ነጥቤስ?<br />

አንድን ነገር እየቻልን በራስ መተማመናችን ባዶ<br />

በመሆኑ ምክንያት ብቻ አንድን ኃላፊነት አሳልፈን ለወንድ<br />

የምንሰጥም አለን። ይሄ የእኛ የሴቶች ድክመታችን ነው። ይሄ<br />

የእኛ ልዩነታችን ነው።<br />

የሚገርመው አንድ ሴት ያላትን ጥንካሬ<br />

ተጠቅማ ለውጤት ብትበቃ “ወንድ ነሽ/ናት” የሚል አግባብነት<br />

የሌለው ሙገሳን እንቸራታለን። ራሷን እንደ ወንድ እንድታይ<br />

እናደርጋታለን።<br />

እኔ እንድጽፍ የተሰጠኝ ቦታ አልቆ ተገደብኩ።<br />

ነገር ግን አንቺስ? “እኔን ከወንድ እኩል የማያደርገኝ ተፈጥሮና<br />

ራሴ የፈጠርኩት (ሰው ሰራሽ) ምክንያቶች አሉ” ብለሽ አታምኚ<br />

ይሆን? አዎን። የምትበልጭበትም የምታንሽበትም፣ እንዲሁም<br />

እኩል የሚያደርጉሽም ነጥቦች አሉ ብዬ አስባለሁ። እኩልም ነሽ<br />

እኩልም አይደለሽም።<br />

ከምንም ነገር በላይ ደግሞ በራስ የመተማመን<br />

መንፈሳችን ዝቅተኛ መሆኑ አንዱ ከወንድ እኩል እንዳንሆን<br />

የሚያደርገን መሆኑን ልናጤነው ግድ ይለናል። በቅድሚያ<br />

ለራሳችን ያለን ግንዛቤ ከፍ ሊል ይገባል ባይ ነኝ።<br />

ምክር ቤቱ<br />

አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />

‹‹የቤት እንስሳት ያስባሉ. . .<br />

አደርገዋለሁ›› ይላሉ። እኔ ግን እነሱ ትንሽ<br />

አበዙት እላለሁ።<br />

ከሰው ልጅ የማይጠበቅ ስህተት/ድርጊት<br />

[በተለምዶ እንስሳዊ የምንለው አይነት]<br />

ፈፅመው የሚገኙን ‹‹ከእንስሳት ታዲያ<br />

በምን ተለየህ? በማሰብህ አልነበረም<br />

እንዴ?›› እንላለን። እንስሳት እንደማያስቡ<br />

ርግጠኛ መሆን ይቻላል? [በርግጥ አንቺ<br />

የሰው ልጅ እንጂ የእንስሳ አዕምሮ ባለሙያ<br />

አይደለሽም]<br />

የሚያስቡ ይመስለኛል። ውሻን<br />

ልትወስድ ትችላለህ። [የውሻ አድናቂ እና<br />

አፍቃሪ ነኝ፤ ቀረቤታውም አለኝ] የሰው<br />

ልጆች ከሚያደርጉት በላይ ያደርጋል።<br />

በርግጥ አመክንዮ አያውቅም። አጥንቱን<br />

ቁጭ አድርጎ ስታልፍ ሊነክስህ ይችላል።<br />

‹‹አጥንቴን ሊወስድብኝ ነው›› ብሎ ስላሰበ<br />

ነው። ምናልባት ‹‹እኔ የነካሁትን አጥንት<br />

የሰው ልጅ አይበላም›› ብሎ ቢያስብ ኖሮ<br />

አይነክስህም ነበር። በተለይ የቤት እንስሳት<br />

በደንብ ያስባሉ ብዬ አምናለሁ። እንደ ሰው<br />

የተወሳሰቡ ነገሮችን ላያስቡ ይችላሉ። [በጣም<br />

እየሳቀች] በርግጥ እስካሁን ያለሁት ሰው ላይ<br />

ነው። ወደፊት ስለ እንስሳት አጠና ይሆናል።<br />

[በቅርቡ አሜሪካ ውስጥ 911 ደውሎ ህመም<br />

ውስጥ የነበረ ጌታውን ውሻው ታድጓል]<br />

ስለ አዕምሮ…<br />

የሰው ልጅ አዕምሮን ለሁለት<br />

ከፍለን ማየት እንችላለን። የግራው<br />

ምክንያታዊ፣ ቀኙ ደግሞ ስሜታዊ ክፍል<br />

ነው። የህፃናት እስከ ሁለት ዓመታቸው ድረስ<br />

75 በመቶ የሚሰራው ቀኙ (ስሜታዊው)<br />

ክፍል ነው። ለዚያ ነው ሲርባቸው፣ ሲናደዱ<br />

ወይም በሌላ ምክንያት የሚያለቅሱት።<br />

የተነሳሽነት፣ የማቀድና ማስፈፀም ስንፈት<br />

ከስነ-ልቦና ችግር ጋር ይያያዛል?<br />

በጣም እንጂ። እኔ ጋር የሚመጡ<br />

የፍቅር፣ የባልና ሚስት ችግሮች ብቻ<br />

አይደሉም። ብር ኖሯቸው ምን መስራት<br />

እንዳለባቸው የማያውቁ እና የሚፈሩም<br />

ይመጣሉ። እንደዚህ አይነት ችግሮች<br />

ሲመጡ የኋላ ታሪካቸውን እናጠናለን።<br />

እንደማምነው 90 በመቶ ያህል የስነ-ልቦና<br />

ችግር የሚመጣው ከልጅነት ችግራችን<br />

ነው። ጉንፋን የያዘው ሰው ያስላል። ሳሉ<br />

ግን ጉንፋን ብቻ ነው ማለት አይቻልም።<br />

ውስጡ መታከም አለበት።<br />

ብዙ ነገሮች ማድረግ እየቻሉ ‹‹እኔ<br />

ብቁ አይደለሁም›› ብለው የሚያስቡ ሰዎች<br />

አሉ። አንዳንድ ሰዎች ማጌጥ የሚፈልጉት<br />

‹‹ይመጥነኛል›› በሚሉት ነገር ነው። አንተ<br />

እጅ ላይ ወርቅ አለ። ያደረግከው ይመጥነኛል<br />

ብለህ ነው። ለአንዳንድ ሰዎች ግን ወርቅ<br />

ብትሰጣቸው ‹‹ሰዎች ወርቁን ሲያዩ እኔ<br />

አንሼ እታያቸዋለሁ›› (ከወርቁ አንሳለሁ)<br />

ብለው ስለሚያስቡ አያደርጉትም። እንዲህ<br />

አይነት ሰዎች ብዙ ጊዜ ‹‹አትችልም››<br />

ተብለው ያደጉ ናቸው።<br />

አዲስ መንገድ እና የእርቅ ማዕድ የተሰኙ<br />

የስነ ልብዎና የሬዳዮ ፕሮግራም አላችሁ።<br />

ማህበረሰቡ ጋር ምን ያህል እንደደረሳችሁ<br />

ዳታው ባይኖረኝም በግላዊ ምልከታዬ<br />

ፍቅረኞች፣ ባለ ትዳሮች፣ ቤተሰብ፣ የፍቅር<br />

ግንኙነታቸው ማደስ የሚፈልጉ እና በኑሮ<br />

ሂደት የትዳር ወይም ቤተሰባዊ ግንኙነታው<br />

የደፈረሰ ለእርቅ እንዲሰናዱ ሊያዳምጧቸው<br />

የሚገቡ ሁለት ፕሮግራሞች ናቸው። ምን<br />

አይነት ግብረ መልስ ታገኛላችሁ?<br />

እኛ በግላችን ስለ ፕሮግራማችን<br />

የሰራነው ጥናት የለንም። ፋና የ<strong>ስር</strong>ጭት<br />

ማዕከል ከሚሰራው ጥናት ተነስቶ ጥሩ እና<br />

ተደማጭ ፕሮግራም እንደሆነ ይነግረናል።<br />

አነቃቂ ስልጠና (Motivational Training)<br />

ለመስጠት በተለያዩ ቦታዎች ስገኝ<br />

የሚቀበሉኝ በደስታ ነው። ‹‹ወይኔ ታድዬ<br />

ቲጂን አወቅኳት›› እስከ ማለት የሚደርሱ<br />

ያጋጥሙኛል። በሚወዱህ መሀከል መስራት<br />

አስደሳች ነው። ይሄ ለእኛ ትልቁ ሽልማት<br />

ነው።<br />

እግዚአብሔር ይመስገን እጅግ<br />

በጣም ቆንጆ ምላሽ አለን። የስልጠና እና<br />

የማማከር ስራውን ስንጀምር በ400 ብር<br />

ቢሮ ተከራይተን ሲሆን ጠረጴዛ እንኳን<br />

አልነበረንም። እኔም ሆንኩ የድርጅታችን<br />

ሌላው ባለድርሻ (እንዳልካቸው አሰፋ)<br />

ስራ ከቀደመ፣ ገንዘብ እንደሚከተለን<br />

እናውቀዋለን። [ድርጅታቸው በርካታ<br />

ጥንዶችን አስታርቋል።]<br />

ፕሮግራማችሁን ስከታተል ብዙዎች<br />

እንደሚወዱሽ እና እንደሚያደንቁሽ<br />

[ሁለቱም ፆታዎች] ይናገራሉ። በድምፅሽ<br />

እና በአወራር ዘዬሽ የሚሳቡ ያሉ<br />

ይመስለኛል። የፍቅር ጥያቄዎችም<br />

እንደሚቀርብልሽ ሰምቻለሁ።<br />

እንዲህ ወጣ ያለ ጥያቄ ደስ<br />

ይላል። በህይወት ውስጥ የሚያጋጥም ነገር<br />

ነው። ደንበኞቼን በር ከፍቼ ‹‹እንኳን ደህና<br />

መጣችሁ›› ብዬ እቀበላቸዋለሁ። የምክር<br />

አገልግሎት እየሰጠኋቸው ቢያለቅሱ፣<br />

ቢያዝኑ በእጄ እንዲህ (በአመልካች ጣቷ<br />

እየጠቆመች) አልነካቸውም። በጣም ካለቀሱ<br />

ናብኪን አውጥቼ ሰጣቸዋለሁ። ከደንበኞች<br />

ጋር (ወንድም ሆነ ሴት) መገባበዝ<br />

አይፈቀድም። ስጦታ መቀበል ስለማይቻል<br />

መጥቶልኝ መልሼ አውቃለሁ። ይህን<br />

የማደርገው ለእኔም ለደንበኞቼም ደህንነት<br />

ሲባል ነው።<br />

በቀደም ሱሰኝነትን ስለማስወገድ<br />

በሬዲዮ እያወራን ‹‹በድምፅሽ ሱሰኛ ሆኛለሁ››<br />

የሚሉ የፅሁፍ መልዕክቶች ደርሰውኛል።<br />

[እየሳቀች] ሱሰኛ ስላለመሆን እያወራሁ<br />

‹‹ሱስ ሆኖብኛል›› ማለት ጥሩ አይደለም።<br />

ምንም አይነት ነገር ቢመጣ የሙያው<br />

ስነ-ምግባር ገትሮ ይይዝልኛል። እውነት<br />

ለመናገር ስለ ድምፄ አንተ እንዳልከው ያሉኝ<br />

አሉ። ስቱዲዮ ውስጥ በጣም ነፃ ሆኜ፣ ራሴን<br />

ሆኜ ነው የማወራው።<br />

አዎ! ከደንበኞች አንስቶ የፍቅር<br />

ጥያቄ ይገጥመኛል። የፍቅር ጓደኛ አለኝ።<br />

በፕሮግራማችሁ ላይ የምታወሪውን<br />

ትኖሪዋለሽ?<br />

ቆንጆ ጥያቄ ነው።<br />

የማደርጋቸውም፣ የማላደርጋቸውም አሉ።<br />

በግል ህይወቴ ያደረግኳቸው ዋነኛ ለውጦች<br />

አሉ። በጣም ፈሪ፣ ዝምተኛ እና አይናፋር<br />

ነበርኩ። ‹‹ድድ ማስጫ›› ላይ ለሚቀመጡ<br />

ጎረምሶች ‹‹የመጨረሻ ሙድ መያዣ››<br />

ነበርኩ። እናቴ ሬዲዮ ላይ ስትሰማኝ<br />

‹‹የምታወራው እውነት የእኔ ልጅ ናት?››<br />

ብላ ትገረማለች።<br />

አሁን የምሰራው ሰዎች ከእንደዚህ<br />

ያሉ ፍርሃቶች እንዲወጡ ነው። በነፃነት<br />

አልደራደርም፤ እኔ እንደነበርኩበት የሰው<br />

ልጅ በጭንቀት ባርነት ውስጥ እንዲኖር<br />

አልፈልግም።<br />

በብዛት የማወራውን ባደርግም<br />

በጣም በተቀናጀ አካሄድ እና በፕሮግራም<br />

የምመራ አይነት ሰው ግን አይደለሁም።<br />

ማስተካከል ግን ፈልጋለሁ።<br />

ከአንድ ጫፍ ወደ ሌላ ጫፍ<br />

የመጣሁት በራሴ ቢሆንም ዮሐንስ አፈወርቅ<br />

የተባለ ጓደኛዬ እና የስራ ባልደረባዬ እንዳልክ<br />

ብዙ ነገር አደፋፍረውኛል።<br />

አንቺስ አማካሪ እና ቴራፒስት አለሽ?<br />

ሰው እንደመሆኔ መጠን እኔም<br />

ችግር ስላለብኝ መደበኛ አማካሪ አለኝ።<br />

ሲጨንቅሽ ምን ማድረግ ያስደስትሻል?<br />

በጣም ሲጨንቀኝ ልደታ ቤተ<br />

ክርስቲያን ሄዳለሁ። ዛፎቹ <strong>ስር</strong> መቀመጥ<br />

ደስ ይለኛል። ከጎኔ ካለ ሰው ጋር ማውራት<br />

ደስ ይለኛል። ነገር ስለማያከብድ ከፍቅር<br />

ጓደኛዬ ጋር ማውራትም ያስደስተኛል።<br />

አንዳንዴ ግን ሰዎች አይረዱኝም።<br />

ስንት ኪሎ ነሽ?<br />

52፡፡ ቁመቴ ደግሞ አንድ<br />

ሜትር ከሰባ ነው፤ ረዥም ነኝ። ቅጥነቴን<br />

እወደዋለሁ።<br />

ሁለት ሰከንድ ነው የምሰጥሽ የአዲስ አበባ<br />

ከንቲባ ስም ማን እንደሚባል ንገሪኝ።<br />

‘Oh My God’… [በቁጭት<br />

አንገቷን የተቀመጠችበት ወንበር መደገፊያ<br />

ላይ አኑራ ወደ ጣሪያ እያየች ከትከት ብላ<br />

ሳቀች] በጣም አዝናለሁ አላውቅም። [አንድ<br />

የስነ-ልብዎና ባለሙያ የከተማዋን ከንቲባ<br />

ስም አታውቅም ቢባል ማን ያምናል? አቶ<br />

ኩማ ደመቅሳ መሆናቸውን ነግሬያት እንኳን<br />

ተጠራጥራለች። በሳቅ እየተፍለቀለቀች<br />

‹‹ከፖለቲካ ጉዳዮች ሩቅ ነኝ›› ብላለች።<br />

ይህን ለመመለስ ፖለቲካ የግድ ማወቅ<br />

ያስፈልጋል?]


አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />

ዜናዎች<br />

“በሻዕቢያ ነጭ ለባሽነት ሀገር የሚያውቃቸው<br />

የኢህአዴግ መሪዎች ናቸው”<br />

መድረክ<br />

በሱራፍኤል ግርማ<br />

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ<br />

አንድነት መድረክ፣ በሻዕቢያ ነጭ ለባሽነት<br />

የሚጠረጠሩትና ሀገር የሚያውቃቸው የኢህአዴግ<br />

መሪዎች ሆነው ሳለ፣ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችን<br />

መንግሥት በዚህ መወንጀሉ ግራ የሚያጋባ መሆኑን<br />

አስታወቀ።<br />

ፓርቲው ትናንት ባወጣው መግለጫ፣<br />

“ኢህአዴግ ከሻዕቢያ ጋር ለመታረቅ እየተማፀነ ባለበት<br />

በአሁኑ ጊዜ እንኳን ሳይቀር መድረክ የኢትዮጵያን<br />

ጥቅም በማስጠበቅ ረገድ የአልጀርሱ ስምምነት መሰረዝ<br />

እንዳለበትና የአሰብ ወደብ ባለቤትነት ጉዳይ ድርድርና<br />

ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ሊደረግበት እንደሚገባ የፖለቲካ<br />

በናፍቆት ዮሴፍ<br />

በደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና<br />

ህዝቦች ክልላዊ መንግስት በዳውሮ<br />

ዞን ዋካ ከተማ “ወረዳችን ከቀርጫ<br />

ተነስቶ አማካኝ ቦታ ላይ ይሁንልን”<br />

በሚል ህብረተሰቡ ባነሳው ጥያቄ፣<br />

ህዝቡ እንዲያምፅ የድጋፍ ፊርማ<br />

አሰባስበዋል በሚል ከ30 በላይ ሰዎች መታሰራቸውን<br />

የአካባቢው ነዋሪዎች ለአውራምባ ታይምስ ገለፁ።<br />

እንደነዋሪዎቹ ገለፃ፣ ከዚህ ቀደም የአካባቢው<br />

ወረዳ “ማረቃ” እንደነበር እና ለጊዜያዊነት ወደ ቀርጫ<br />

የተዛወረ መሆኑን ገልፀው፣ ምንም እንኳን በጊዜያዊነት<br />

የተዛወረ ቢሆንም አሁን ግን ቋሚ በመደረጉ ህዝቡ<br />

አቋም የያዘ ፓርቲ ነው” ብሏል።<br />

የሻዕቢያ ተላላኪ ሊሆን ቀርቶ ከሻዕቢያ ጋር<br />

ሊያስማማው የሚችል ባህሪና አቋም እንደሌለው የገለፀው<br />

መድረክ፣ በጋዜጠኞችና በተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ላይ<br />

እየተፈፀመ ያለውን ወከባ አውግዟል። ፕሬዝዳንት<br />

ግርማ ወ/ጊዮርጊስ ለፓርላማ መክፈቻ ንግግር ሲያደርጉ<br />

በአባላቱና በሌሎች ጠንካራ ተቃዋሚዎች ላይ ኢህአዴግ<br />

መራሹ መንግስት የሚወስዳቸውን የኃይል እርምጃዎች<br />

ባለመጥቀስ “አንዳንድ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች<br />

በሽብር ተግባር ላይ ተሰማርተዋል” ማለታቸውን<br />

መድረኩ በፅኑ ኮንኗል።<br />

ከተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተጨማሪ፣<br />

ነፃ ጋዜጠኞችን መንግስት እያሳደደ መሆኑን የገለፀው<br />

መድረክ፣ “ለዚህ ሁሉ መነሻው ኢህአዴግ ሙስናን<br />

ለእንግልት እየተዳረገ መሆኑን አስታውቀዋል።<br />

በዞኑ ከ37 በላይ የቀበሌ ማህበር ነዋሪዎች<br />

መኖራቸውን የገለፁት የአውራምባ ታይምስ ምንጮች፣<br />

ወረዳው ከማረቃ ወደ ቀርጫ ከተዘዋወረ ወዲህ ለፍርድ<br />

ቤት ጉዳይ፣ ለህክምና እና ለመሰል ማህበራዊ ጉዳዮች<br />

ቀርጫ ድረስ መመላለሱ ህዝቡን እያንገላታው በመሆኑና<br />

ጥያቄውንም የዞኑ መስተዳድር ባለመመለሱ፣ እስከ<br />

ክልል አቤት በማለት መፍትሄ ባለማግኘታቸው ህዝቡ<br />

ተሰብስቦ ሰልፍ በመውጣቱ ህዝቡ ለአመፅ እንዲነሳሳ<br />

አስተባብራችኋል በሚል ነበር ከትላንት ወዲያ ለእ<strong>ስር</strong><br />

የተዳረጉት።<br />

በትላንትናው ዕለት በአካባቢው ያሉ ትምህርት<br />

ቤቶች በሙሉ ተዘግተው መዋላቸውንና አስተማሪዎችም<br />

ከቀኑ ስምንት ሰዓት ላይ ለአስቸኳይ ስብሰባ<br />

መዋጋት፣ መልካም አስተዳደርን ማስፈን፣ ሰብዓዊና<br />

ዴሞክራሲያዊ መብቶችን ማስከበር፣ እንዲሁም የሕግ<br />

የበላይነትን ማስጠበቅ ስላቃተው ነው” የሚል ምክንያት<br />

አስቀምጧል።<br />

ኢህአዴግ ኢትዮጵያ ውስጥ ፍትሕን<br />

ማረጋገጥና የዜጎችን ክብር ማስጠበቅ እንዳቃተው<br />

በመግለፅም የገዢው ፓርቲ ሥርዓተ-መንግስት<br />

በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ሳይውል ሳያድር መተካት<br />

እንዳለበትም አሳስቧል።<br />

በሀገሪቱ ሥር እየሰደደ ላለው ችግር<br />

ተጠያቂው ኢህአዴግ እንጂ ተቃዋሚ ፓርቲዎች<br />

አለመሆናቸውን ያስገነዘበው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ<br />

አንድነት መድረክ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ<br />

በፓርላማ ተገኝተው ባቀረቡት ንግግር ላይም ትችት<br />

በዳውሮ ዞን ዋካ ከተማ ከ30 በላይ ሰዎች ታሰሩ<br />

»<br />

አጣጥለዋቸዋል። አቶ መለስ በዚህ ወር መጀመሪያ<br />

ከኖርዌዩ አፍተንፖስተን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ-<br />

ምልልስ እነዚህ ስዊድናውያን ጋዜጠኞች “የሽብርተኞች<br />

ግብረ-አበሮች” እና “ጋዜጠኛ ያልሆኑ” መሆናቸውን<br />

ገልፀዋል።<br />

ይህ የአቶ መለስ የፓርላማ አስተያየት<br />

በመንግስት የሚመራው ዕለታዊ ጋዜጣ አዲስ ዘመን<br />

ተዘግቦ የተመለከተው ቴዲ አፍሮ፣ ኢትዮጵያዊውን ነፃ<br />

ለማውጣት አስፈላጊውን ገንዘብ እንደከፈለ ተገምቷል።<br />

እንደ “ሪፖርተር” ዘገባ ከሆነ፣ አስመሮም<br />

ሞት የተፈረደበት ሆን ብሎና አስቦ ሰው ገድሎ ሳይሆን፣<br />

በመኖሪያ ቤቱ ውስጥ እያለ ባለቤቱን ለመድፈር የመጡ<br />

ግለሰቦችን ለመከላከል በወሰደው እርምጃ ነው።<br />

መረጃው ትክክል ሆኖ ድምፃዊው በጎሳ<br />

መሪዎቹ የተጠየቀውን የ700 ሺህ ብር የነፍስ ካሳ<br />

ሙሉ በሙሉ በመክፈል ኢትዮጵያዊውን ወጣት<br />

ከሞት የሚያተርፈው ከሆነ፣ መንግስት ልጃቸውን<br />

እንዲያድንላቸው በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል<br />

ተደጋጋሚ ተማፅኖ ሲያቀርቡ ቆይተው በቂ ምላሽ<br />

ላላገኙት ቤተሰቦቹ እፎይታ እንደሚሆን ተገምቷል።<br />

በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን ለአውራምባ<br />

ታይምስ የሰጡት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል-አቀባይ<br />

ትናንትና የአካባቢው በርካታ ት/ቤቶች ተዘግተው ውለዋል<br />

ሲፒጄ፣ ‘በጋዜጠኞች . . .<br />

ቴዲ አፍሮ በሶማሊያ ሞት ...<br />

በነፃው ሳምንታዊ ጋዜጣ አውራምባ ታይምስ ላይ እጅግ<br />

የሰላ ትችት ባተመ በማግስቱ የተሰነዘረ ሲሆን፤ ይህም<br />

በጋዜጣው ላይና በማኔጂንግ ኤዲተሩ ዳዊት ከበደ ላይ<br />

ከተቀጣጠለ የተራዘመ የስም-ማጥፋት ዘመቻ አንዱ<br />

ነው። በሲፒጄ አማካኝነት ከአማርኛ ወደ እንግሊዝኛ<br />

በተተረጎመው ጽሁፉ አዲስ ዘመን፣ “አመጽ ናፋቂዎችን<br />

መታገስ እስከመቼ?” ሲል ያተመው የአስተያየት ዘገባ<br />

መጠራታቸውን የገለፁት ምንጮች፤ ከተዘጉት ት/ቤቶች<br />

ውስጥ ዋካ መሰናዶ ት/ቤት፣ ኮጀብ መምህራን ኮሌጅ፣<br />

ዋካ አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት፣ ሞዴል<br />

አንደኛ ደረጃ ት/ቤት እና ሌሎችም ተዘግተው ውለዋል።<br />

እንደምንጮቻችን ገለጻ በአካባቢው ያሉ ጋዜጠኞች<br />

የተፈጠረውን ችግር እንዳይዘግቡ ተከልክለዋል።<br />

“ወደ ዋካ ከተማ ከክልል ፖሊሶች ቢመጡም<br />

የዞኑ አስተዳዳሪዎች ግን ጥያቄያችንን የሁለትና የሦስት<br />

ግለሰቦች ጥያቄ እንደሆነ በመግለፅ መፍትሔ እንዳናገኝ<br />

ተከልክለናል” ሲሉ ገልፀዋል። “የዞኑና የወረዳው<br />

አስተዳዳሪዎች በቀርጫ መኖሪያ ቤታቸውን ስለሰሩ<br />

እኛ ወደ ቀድሞ ወረዳችን ማረቃ አሊያም አማካይ ቦታ<br />

ይሁንልን ስንል ‹የመንገድና የወረዳ ጥያቄ የሚያነሳ ገደል<br />

ይግባ› ሲሉ ተሳልቀውብናል›› ያሉት የአካባቢው ሰዎች<br />

አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ደግሞ በበኩላቸው መንግስት<br />

ኢትዮጵያዊውን ለማትረፍ ጥረት ሲያደረግ መቆየቱን<br />

ተናግረዋል።<br />

አስመሮም ኃይለሥላሴ ነፍስ ካጠፋና በጎሳ<br />

መሪዎች ውሳኔው ከተላለፈበት አንድ ዓመት እንደሆነው<br />

ያስታወሱት አምባሳደር ዲና፣ “ልጁ እስካሁን ሳይገደል<br />

የቆየው ፑንት ላንድ ያለው ቆንፅላ ጽ/ቤታችን ባደረገው<br />

ጥረት ነው” ብለዋል።<br />

ቤተሰቦቹ ልጃቸውን ለማስለቀቅ<br />

የሚያስፈልገውን ያህል ገንዘብ በዕርዳታ ማግኘታቸውን<br />

የገለፁትን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ፣<br />

ቤተሰቦቹ ገንዘቡን ባያገኙ ኖሮ መንግስት ከፍሎ<br />

ያስለቅቀው እንደነበር ጠይቀናቸው፣ “‘ቢሆን ኖሮ’ ብዬ<br />

መልስ ለመስጠት አልችልም” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።<br />

ስለ ጉዳዩ ድምጻዊ ቴዲ አፍሮን ለመጠየቅ<br />

ወደ ተንቀሳቃሽ ስልኩ ተደጋጋሚ የስልክ ጥሪ<br />

ብናደርግም ስልኩ ዝግ በመሆኑ አስተያየቱን ለማካተት<br />

አልቻልንም።<br />

19<br />

ሰንዝሯል።<br />

“ጠቅላይ ሚኒስትሩና ፓርቲያቸው ኢህአዴግ<br />

በሀገራችን ያለው የፖለቲካ ምህዳር ችግር እንደሌለበትና<br />

የጨዋታ ሕግን ተከትሎ መሄድ ለፈለገ ሁሉ ምቹ<br />

እንደሆነ ለማስረዳት ሞክረዋል፤ ሆኖም በተጨባጭ<br />

የሚታየው ሁኔታ የተገላቢጦሽ ነው” ይላል - የፓርቲው<br />

መግለጫ።<br />

መግለጫው በማከልም፣ ከምርጫ 97<br />

በኋላ ኢህአዴግ ካደረበት ድንጋጤ የተነሳ የሲቪል<br />

ማሕበረሰቡን፣ የግል ጋዜጦችንና የተቃዋሚ ፓርቲዎችን<br />

እንቅስቃሴ የሚገድቡ አዋጆች እንዲፀድቁ ማድረጉን<br />

አስታውሷል።<br />

መንግስት ጉዳዩን ተመልክቶ እልባት ይሰጣቸው ዘንድ<br />

ጥያቄ አቅርበዋል።<br />

ዝግጅት ክፍላችንም የዞኑ የድርጅት ጉዳይ<br />

ኃላፊ ለሆኑት ለአቶ ለማ መሰለ፣ ለዳውሮ ዞን ዋና<br />

አስተዳዳሪ ለአቶ እስራኤል አካሉና በዞኑ የፀጥታ መምሪያ<br />

ኃላፊ ለሆኑት አቶ ተነሣ ብሩ ደውለን ስልካቸውን ያላነሱ<br />

በመሆኑ ምላሻቸውን አያላካተትን ቢሆንም፣ በወረዳው<br />

የህብረት ሥራና ግብይት ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ<br />

እስክንድር ተፈራ ችግሩ መፈጠሩን አምነው ወረዳ<br />

ይቀየር በሚል ህዝቡ አድማ እንዲያደርግ የድጋፍ ፊርማ<br />

አሰባስበዋል ተብለው የተጠረጠሩ ሰዎች መታሰራቸውን<br />

ገልፀው፣ ጉዳዩን ፍርድ ቤት እያየው እንደሚገኝ<br />

ለአውራምባ ታይምስ ገልፀዋል።<br />

የፀጥታ ኃይሎች በአቶ ዳዊት ላይ “እርምጃ እንዲወስዱ”<br />

ወትውቷል-ብሏል ሲፒጄ<br />

ጋዜጣው የሲፒጄ ዓለም አቀፍ የፕሬስ ነፃነት<br />

ሽልማት አሸናፊው ዳዊት ከበደን ከ“ሽብርተኛ ቡድኖች”<br />

ጋር በመስራት ከመወንጀሉም በላይ፣ መንግስት<br />

የ1997ቱን ምርጫ ተከትሎ በግል ሚዲያው ላይ<br />

በወሰደው እርምጃ ከ21 ወራቶች እ<strong>ስር</strong> በኋላ በቅድመ-<br />

ሁኔታዊ ይቅርታ የተፈታውን ይህን ጋዜጠኛ ይቅርታውን<br />

በመሻር ዳግመኛ እንዲያስረው ጠይቋል።<br />

እነዚህ የአዲስ ዘመን የቅርብ አስተያየቶች<br />

በአውራምባ ታይምስ ላይ እየተሰነዘሩ ካሉ ተከታታይ<br />

ጽሁፎች መካከል የቅርቦቹ ናቸው። በሀምሌ ወር አቶ<br />

ዳዊት ከበደ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ አቶ<br />

አንተነህ ኃይሉ እና በአታሚው የኢትዮጵያ ፕሬስ<br />

ድርጅት ላይ የስም ማጥፋት ክስ መ<strong>ስር</strong>ተው እንደነበር<br />

ሲታወስ፣ ክሱም በዳኛው ሙሉቀን ተሻለ ውድቅ<br />

እንደተደረገ የሲፒጄ የጥናት ቡድን አረጋግጧል።<br />

የሲፒጄ የምስራቅ አፍሪካ አማካሪ ቶም<br />

ሮዴስ እንዳብራሩት፣ “ይህ በቅርቡ የተሰማው የጠ/<br />

ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የቁጣ ናዳ በኢትዮጵያ ያሉ ነፃና<br />

ገለልተኛ ጋዜጠኞችን ሽብርተኝነት በሚሉ ውንጀላዎች<br />

ከስራቸው ለመንቀል እየተደረገ ያለው ስልታዊ ዘመቻ<br />

አካል ነው። በመንግስት ሚዲያዎች የሚሰራጨው ስም<br />

የማጥፋት ዘመቻ በአገሪቱ ውስጥ ያለውን የፍርሃት<br />

ድባብ በማባባስ የበኩሉን ሚና ይወጣል። በግል ፕሬሱ<br />

ላይ በተፋፋሙ የማስፈራሪያ እርምጃዎችም ኢትዮጵያ<br />

እንደ ዴሞክራሲያዊ መንግስት ያላትን ተቀባይነት<br />

እየሰዋች ነው።” ብሏል፡፡<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ


20<br />

በኤልያስ ገብሩ<br />

elias.gebru32@gmail.com<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

ጤና<br />

ኢትዮጵያ በታህሳስ ወር ለምታዘጋጀው 16ኛው ዓለም አቀፍ የኤድስና አባላዘር በሽታዎች የአፍሪካ ኮንፈረንስ እየተደረገ<br />

ያለው ዝግጅት ምን ደረጃ ላይ ይገኛል?<br />

ዝግጅቱ ሁለት ዘርፍ አለው። አንዱ የፕሮግራም ዝግጅት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የሎጀስቲክ<br />

ነው። ፕሮግራሞቹ ሳይንሳዊ፣ ሕብረተሰባዊና አመራርን የተመለከቱ ናቸው። በሳይንሳዊው<br />

ዙሪያ በርካታ ሥራዎች ተሰርተዋል። ወደ ሦስት ሺህ የሚጠጉ የጥናት ፅሁፎች ቀርበው፣<br />

ከእነዚህም ውስጥ አንድ ሺህዎቹ በዓለም አቀፍ ደረጃ ባሉ ሳይንቲስቶች ተመርጠው በቃልና<br />

በፖስተር ኤግዚብሽን ሊቀርቡ ዝግጁ ሆነዋል። እነዚህን በተመለከተ ጠቅለል ያለ መረጃ<br />

የሚሰጥ መጽሐፍ ተዘጋጅቷል። በአመራር ዘርፍ በርካታ ዝግጅቶች ተደርገዋል። የፖለቲካና<br />

የኃይማኖት መሪዎች፣ የቢዝነስ ዘርፉ፣ ዓለም አቀፍ የልማት አጋሮች፣ የኤች.አይ.ቪ/ኤ.<br />

አይ.ዲ.ኤስ ቫይረስ በደማቸው ውስጥ ያለባቸው ሰዎች የግንኙነት መረቦች /ቡድኖች/፣<br />

የማሕበራት መሪዎችን የመሳሰሉት የሚሳተፉባቸው በርካታ ፕሮግራሞች አሉ። የቀድሞ<br />

የሀገር መሪዎች፣ ሚኒስትሮች፣ ቀዳማዊ እመቤቶችና የተባበሩት መንግስታት ዳይሬክተሮች<br />

የሚሳተፉበት ፕሮግራምም አለ።<br />

በሕብረተሰብ በኩል የሕብረተሰብ መሪዎች የሚናገሩባቸው በርካታ ዝግጅቶች ተዘጋጅተዋል።<br />

ሕብረተሰቡም ሊሳተፍበት የሚችል “Community Village” የሚባል ፕሮግራም አለ። እዛ<br />

ውስጥ የተለያዩ የወጣቶች፣ የሴቶችና የሕብረተሰብ ክፍሎች ኤግዚብሽንና ውይይቶች<br />

የሚያደርጉባቸው ፕሮግራሞችና ትርዒቶች ይገኛሉ። ሎጀስቲክን በተመለከተ፤ የሆቴል<br />

መስተንግዶ፣ የትራንስፖርት አገልግሎት፣ የተለያዩ የመሰብሰቢያ አዳራሾች፣ የቪዛ፣ የደህንነት<br />

ጉዳይና ፕሮቶኮልን የተመለከቱ ዝግጅቶችች እየተከናወኑ ነው። የተለያዩ ኢንፎርሜሽን<br />

ቴክኖሎጂ መሳሪያዎችም ያሉ ሲሆን እነሱን ወደመቋጫ ላይ ነን። ብዙ ነገሮች በጥሩ ሁኔታ<br />

ላይ ነው ያሉት።<br />

ኢትዮጵያ ኮንፈረንሱን ማዘጋጀቷ ፋይዳው ምንድን ነው?<br />

በመጀመሪያ ደረጃ በኤች.አይ.ቪ/ኤ.አይ.ዲ.ኤስ እና በተዛማጅ ችግሮች ዙሪያ አዘጋጁ ሀገር<br />

ጉባዔውን በማዘጋጀቱ ዓለም አቀፍ ግዴታውን መወጣቱን ያስመሰክራል። በአፍሪካም ሆነ<br />

በዓለም አቀፍ ደረጃ ኤች.አይ.ቪ/ኤ.አይ.ዲ.ኤስን ከመከላከል እና ከመቆጣጠር አኳያ ሀገሪቱ<br />

ዓለም አቀፋዊ ድርሻዋን በትልቁ እንደተወጣች ያስቆጥራል። ሁለተኛ፣ ሀገሪቱ ከዚህ በፊት<br />

በኤ.አይ.ዲ.ኤስ፣ በቲቢ እና ወባን በመሳሰሉት ከፍተኛ ችግሮች ዙሪያ ስትሰራቸው የነበሩትንና<br />

ውጤት ያገኘችባቸውን ሥራዎች የምታሳይበት ነው። ከዚህም ሌላ በቱሪዝም መስክ ከፍተኛ<br />

ቦታ እያገኘ ላለው የኮንፈረንስ ቱሪዝም ጥቅም አለው። በዚህ ከፍተኛ ጥቅም እያገኙ የሚገኙ<br />

የታወቁ ሀገሮች አሉ። በዚህ ከፍተኛ የሥራ መስክም የሚፈጠርበት ሲሆን እየተሰራ ያለው<br />

ከዚህ ቀደም እንደተለመደው የቱሪዝም አይነት ብቻ አይደለም። ከዚህ አንፃር ኢትዮጵያ<br />

በዘርፉ የምትወዳደርበት ይሆናል። ይኼንን ኮንፈረንስ ሀገሪቱ በብቃት ከተወጣች ወደፊት<br />

ተመሳሳይ የሆኑ ኮንፈረንሶች ለማዘጋጀት ያላትን ብቃት ታስመሰክራለች ማለት ነው።<br />

በማስተዋወቅ ደረጃም የተለያዩ ሴክተሮች በዚህ ስብሰባ ይጠቀማሉ - ቀጥተኛ በሆነ የገንዘብ<br />

ጥቅም፣ ከሰዎች ጋር ግንኙነት በማድረግ፣ በቢዝነስና በምርምር ሥራ መረጃ በመለዋወጥ።<br />

ኮንፈረንሱ የሀገሪቱን በጎ ገፅታ ከመገንባት አንፃርም ትልቅ ሚና አለው። እንዲሁም፣ ከፍተኛ<br />

የሆነ የሚዲያ ፍሰት የሚመጣበት ሁኔታም አለ።<br />

በኮንፈረንሱ ላይ ይበልጥ የሚቀርቡት ሳይንሳዊ የምርምር ጥናታዊ ፅሁፎች ናቸው። በተለይ ከሰሃራ በታች በሚገኙት<br />

የአፍሪካ ሀገራት ባለው የበሽታው <strong>ስር</strong>ጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ወደ ተግባር ሥራ የሚያስገቡ ጉዳዮች ላይ<br />

ኮንፈረንሱ ምን ውጤት ይሰጣል?<br />

የጉባዔው የመጨረሻ ውጤት ምንድን ነው ስንል በመጀመሪያ በኤች.አይ.ቪ/ኤ.አይ.ዲ.ኤስ<br />

መከላከል እና መቆጣጠር ዙሪያ ከፍተኛ የሕብረተሰብ እንቅስቃሴ ላይ ያሉ ባለድርሻ አካላትን<br />

የማንቀሳቀስ እና ለጉዳዩ ምላሽ ከፍተኛ ቁርጠኝነት እና ድጋፍ እንዲሰጡ<br />

የማድረግ ነው። እነዚህ ባለድርሻ አካላት የሀገርና የተለያዩ ተቋማት<br />

መሪዎች፣ የዓለም አቀፍ የልማት አጋሮች፣ ሕብረተሰቡ፣<br />

የቢዝነሱ ዘርፍ፣ ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ ያሉ የሕብረሰብ<br />

ክፍሎች ናቸው። የኮንፈረንሱ መሪ ቃልም “Own, Scale<br />

up & Sustain” (ባለቤትነት፣ ማስፋትና ቀጣይነት)<br />

የሚል በመሆኑ ባለድርሻ አካላትን በከፍተኛ ደረጃ<br />

የሚያንቀሳቅስ ነው። በሁለተኛ ደረጃ በርካታ ሳይንሳዊ<br />

ፅሁፎች ከመቅረባቸው ባሻገር ሌሎች የተቀመሩ ጥሩ<br />

መልካም ልምዶችም በተለያየ መልኩ ይቀርባሉ።<br />

ይኼም የሚጠቅመው ለኤች.አይ.ቪ/ኤ.አይ.ዲ.ኤስ<br />

ምላሽ በሳይንስ እና በመረጃ ላይ እንዲሆን ለማድረግ<br />

ነው። ስለዚህ ከብዙ የአፍሪካ ሀገራት የመነጩ<br />

ጥናታዊ ፅሁፎችና በጎ ልምዶች፤ ከአፍሪካም ውጪ<br />

ተመሳሳይ ሁኔታ ባለባቸው ደሃ ሀገራት በሽታውን<br />

ከመከላከልና ከመቆጣጠር አንፃር በሕብረተሰብ፣<br />

በመንግሥት ወይም በኃይማኖት ደረጃ የተሰሩ<br />

ሥራዎች ይቀርባል።<br />

ሌላ ከውጤት አንፃር ከኮንፈረንሱ የምንጠብቀው፣<br />

ኤች.አይ.ቪ/ኤ.አይ.ዲ.ኤስን ከመዋጋት አንፃር በመሪዎችና<br />

በአጋሮች ደረጃ ቃልኪዳን ተገብተው የተፈፀመውና<br />

ያልተፈፀሙ የተለያዩ ነገሮች አሉ። እና<br />

እነዚህ የተለያዩ አካላት “ግዴታቸውን<br />

ተወጥተዋል ወይስ<br />

አልተወጡም” ተብለው<br />

የ ሚ ጠ የ ቁ በ ት ና<br />

ው ይ ይ ት<br />

አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />

“በኢትዮጵያ የኤች.አይ.ቪ ቫይረስ<br />

ሥርጭት መቀነሱ ሊያዘናጋን አይገባም”<br />

ዶ/ር ይገረሙ አበበ<br />

/የ16ኛው የአይካሳ ኮንፍረንስ ሰብሳቢ/<br />

ዶ/ር ይገረሙ አበበ ኢትዮጵያ በቀጣይ ታህሳስ ወር ላይ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የምታዘጋጀው 16ኛው ዓለም አቀፍ<br />

የኤድስና አባላዘር በሽታዎች የአፍሪካ ኮንፈረንስ (ICASA) ሰብሳቢ ናቸው። ለአራት ቀናት በሚቆየው ዓለም አቀፍ<br />

ጉባዔ ዙሪያ ዶ/ር ይገረሙን የጤና አምድ አዘጋጅ እንዲህ አነጋግሯዋል።<br />

“<br />

“<br />

ትክክለኛውን ቁጥር አሁን መጥቀስ<br />

ባልችልም፣ በኢትዮጵያ የበሽታው ወረርሽኝ<br />

በብዛት ያለው በከተማ ነው። ነገር ግን፣<br />

የቫይረሱ <strong>ስር</strong>ጭት በከፍተኛ ደረጃ እየቀነሰ<br />

ነው። ይህንን መገንዘብ የምንችለውና<br />

በነፍሰ-ጡሮች ላይ የሚደረገው ክትትል<br />

እንደሚያሳየው፣ በአዲስ አበባ እና በሌሎች<br />

የክልል ከተሞች በአንድ ወቅት ላይ<br />

<strong>ስር</strong>ጭቱ ከ16-17 በመቶ ደርሶ ነበር።<br />

አሁን ግን <strong>ስር</strong>ጭቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ<br />

ከ2-3 በመቶ፣ እንዲሁም በገጠር 0.9<br />

በመቶ የደረሰበት ሁኔታ አለ።<br />

ተደርጎባቸው መልስ የሚገኘበት ነው። በተጨማሪም ሌላ ውጤታማ የሆኑ የተለያዩ<br />

ስትራቴጂዎች፣ ፖሊሲዎችና ፕሮግራሞች ውይይት ላይ ቀርበው ውሳኔ የሚሰጥባቸው<br />

ናቸው። ኃብትን ከማሰባሰብም አንፃር አሁን ብዙ አገልግሎት የሚያገኙ የሕብረተሰብ<br />

ክፍሎች አሉ። በእርግጥ ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ ያሉ በርካታ በሶስተኛው ዓለም የሚገኙ<br />

የሕብረተሰቡ ክፍሎች ሕክምና እያገኙ ቢሆንም ያላገኙት ይበልጣሉ። ነገር ግን፣ በሽታውን<br />

ስለ መከላከል መረጃ የሚያገኙት ወጣቶች ቁጥር እየጨመረ መጥቷል። ብዙ የሚቀርም አለ።<br />

ለዚህ ደግሞ መዋዕለ-ንዋይ ያስፈልጋል። ስለዚህ በዚህ ስብሰባ ላይ ከፍተኛ ድጋፍ ሲሰጡ<br />

የኖሩ አካላት ድጋፋቸውን እንዲጨምሩ፤ ድጋፋቸውን ያቆሙ ኃብታም ሀገራትም ድጋፋቸውን<br />

ዳግም እንዲጀምሩ ያደርጋል። በሌላ በኩል እንደ ቻይና፣ ሕንድና ብራዚልን የመሳሰሉ በጣም<br />

በፍጥነት እያደጉ ያሉ ሀገራት ለግሎባል ፈንድ ገንዘብ ማዋጣት ጀምረዋል።<br />

እነዚህ የበለጠ ገንዘብ ማዋጣት እንዳለባቸው ቅስቀሳ የሚደረግበትና ባለፉት ጊዜያት የተዋጡ<br />

መዋዕለ-ንዋዮች በአግባቡ ሥራ ላይ መዋል አለመዋላቸው በኮንፈረንሱ ላይ ውይይት<br />

የሚደረግበት ነው። ጉባዔውም ለአራት ቀናት በመሆኑ በርካታ ጥቅሞች አሉት። ብዙ<br />

መልዕክቶችም ይተላለፋሉ። በአጠቃላይ በአይካሳ ላይ የሚወሰኑት ውሳኔዎች ኢትዮጵያን ብቻ<br />

ብሎ ሳይሆን አጠቃላይ አፍሪካን ጭምር ነው። በተለይም ችግሩ በስፋት ባለበት ከሰሃራ በታች<br />

በሚገኙ ሀገራት ነው። ስለዚህ ኢትዮጵያ ከዚህ ለራሷ የምትወስደው ነገር ሊኖር ይችላል።<br />

ውጤት ሲባል አጠቃላይ የአፍሪካ ወጤት ነው። በኮንፈረንሱ ላይ የሚተላለፉት ውሳኔዎች<br />

ሁሉንም የሚመለከቱ ሆነው ሀገራት የየራሳቸውን ድርሻ ይወስዳሉ።<br />

በአሁኑ ወቅት በዓለም ላይ ያለው የበሽታው <strong>ስር</strong>ጭት ምን ይመስላል?<br />

በአጠቃላይ በዓለም ላይ ከ30 ሚሊዮን በላይ የሚቆጠሩ ሰዎች ከቫይረሱ ጋር ይኖራሉ።<br />

ከዚህም ሌላ በአዲስ መልክ ቫይረሱ የሚተላለፍበት ሁኔታ አለ። በእርግጥ ይሄ እየቀነሰ<br />

መጥቷል። የሞት ቁጥሩም መድኃኒቱ ተመጣጣኝ በሆነ ዋጋ በስፋት እየተሰራጨ በመሆኑ<br />

እየቀነሰ ነው። አሁንም ግን በአፍሪካ በተለይም ከሰሃራ በታች በስተደቡብ ባሉ ሀገራት፣<br />

ከሌሎች ጋር ሲወዳደር፣ በበሽታው በከፍተኛ ደረጃ እየተጎዱ ናቸው። … ለውጦች ቢኖሩም<br />

ገና ብዙ ለውጥ ያስፈልጋል። በአብዛኛው ከ70 በመቶ በላይ የሚሆኑት ቫይረሱ በደማቸው<br />

ያለባቸው ሰዎች የሚኖሩት ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ ነው። በአዲስ መልክ<br />

ሕፃናት እና ወጣቶች በቫይረሱ የሚያዙት እና የሚሞቱት በዚሁ አካባቢ ነው። ግን ከላይ<br />

እንደገለፅሁት፣ ገና ቢቀርም፣ የሞት እና የቫይረሱ መተላለፊያዎች ቀንሰዋል።<br />

የበሽታውን <strong>ስር</strong>ጭት ከአፍሪካ ውጪ በዓለም አቀፍ ደረጃ ስናየው አዳዲስ ወረርሽኞች<br />

በአንዳንድ አካባቢዎች በተለያዩ ምክንያቶች እየተከሰቱ ናቸው። ለምሳሌ፣ በምስራቅ አውሮፓ<br />

ራሺያን ጨምሮ በአንዳንድ የቻይና ክፍሎች በመርፌ በሚሰጥ አደንዛዥ ዕፅ (Injected Drugs)<br />

አማካኝነት <strong>ስር</strong>ጭቱ እየጨመረ ይገኛል። “ከቫይረሱ ነፃ ናቸው” ተብለው ለረዥም ጊዜያት<br />

የተገመቱት የሰሜን አፍሪካና የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ውስጥ፣ አሁንም በመርፌ<br />

በሚሰጥ አደንዛዥ ዕፅና በግብረ-ሰዶማዊነት አማካኝነት <strong>ስር</strong>ጭቱ እየጨመረ ነው። በአጠቃላይ<br />

የበሽታው <strong>ስር</strong>ጭት በዓለም አቀፍ ደረጃ እየቀነሰ ነው። በአፍሪካ ቢቀንስም ችግሩ ሰፊ በመሆኑ<br />

በሌላ አዳዲስ ምክንያቶች እንደወረርሽኝ የሚከሰትባቸው አካባቢዎች አሉ።<br />

ለ<strong>ስር</strong>ጭቱ መቀነስ ምን ምን ምክንያቶች ይጠቀሳሉ?<br />

ኤች.አይ.ቪ/ኤ.አይ.ዲ.ኤስን ለመቆጣጠር እና ለመከላከል ብዙ ስትራቴጂዎች አሉ። አንዳንዶቹ<br />

አዳዲሶች ናቸው። አንዳንዶቹ ደግሞ ቀድሞ የነበሩ ናቸው። ሁሉም የየራሳቸው ድርሻ አላቸው።<br />

የባህሪ ለውጥ ለማምጣት የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ኮንዶም፣ የአባላዘር በሽታዎችን ጉዳይና<br />

ከእናት ወደ ልጅ ቫይረሱ እንዳይተላለፍ የሚደረገው እንቅስቃሴ በከፍተኛ ደረጃ የየራሳቸው<br />

ድርሻ አላቸው። አዳዲሶቹ ደግሞ <strong>ስር</strong>ጭታቸውን በሕክምና አማካኝነት በመከላከልና ይህም<br />

መንገድ በሕብረተሰቡ ውስጥ በሚስፋፋበት ጊዜ የቫይረሱ <strong>ስር</strong>ጭት የመቀነስ ዕድሉ ሰፊ ነው።<br />

ይኼ በግለሰብ ደረጃ አይደለም። ምክንያቱም መድኃኒቱን የጀመሩ ሰዎች የሚመከሩት ደህንነቱ<br />

የተጠበቀ ግንኙነት እንዲፈፀሙ ነው። ያንን ካላደረጉ አሁንም ቫይረሱ የመተላለፍ ዕድል<br />

አለው። ስለዚህ “መድኃኒት የቫይረሱ መተላለፈያን ይቀንሳል” ሲባል በሕብረተሰብ ደረጃ እንጂ<br />

ግለሰቡ፣ “መድኃኒት ጀምሬያለሁና እንደፈለኩ ያለጥንቃቄ ወሲብ እፈፅማለሁ” ቢል ቫይረሱን<br />

ለሌላው ያስተላልፋል። ለራሱም ቢሆን ቫይረሱን የለመዱ መድኃኒቶች ሊያገኙት ይችላሉ።<br />

ስለዚህ ዘዴው በማሕበረሰብ ደረጃ አንዱ የመከላከያ መንገድ ነው። በስፋት መድኃኒቱን<br />

መጠቀም ለሚያስፈልጋቸውና መድኃኒቱን ለሚወስዱት ሰዎች በጥንቃቄ በሀኪም ትዕዛዝ<br />

መሰረት መውሰዱ የቫይረሱን <strong>ስር</strong>ጭት በሕብረተሰቡ ውስጥ እንዲቀንስ ያደርጋል። በተጨማሪም<br />

ሌሎች አዳዲስ የመከላከል ዘዴዎች እየታዩ ነው።<br />

ወደ ሀገራችን እንምጣና፣ የበሽታውን <strong>ስር</strong>ጭት እንዴት ይገልፁታል?<br />

ትክክለኛውን ቁጥር አሁን መጥቀስ ባልችልም፣ በኢትዮጵያ የበሽታው ወረርሽኝ በብዛት ያለው<br />

በከተማ ነው። ነገር ግን፣ የቫይረሱ <strong>ስር</strong>ጭት በከፍተኛ ደረጃ እየቀነሰ ነው። ይህንን መገንዘብ<br />

የምንችለውና በነፍሰ-ጡሮች ላይ የሚደረገው ክትትል እንደሚያሳየው፣ በአዲስ አበባ እና<br />

በሌሎች የክልል ከተሞች በአንድ ወቅት ላይ <strong>ስር</strong>ጭቱ ከ16-17 በመቶ ደርሶ ነበር። አሁን ግን<br />

<strong>ስር</strong>ጭቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ2-3 በመቶ፣ እንዲሁም በገጠር 0.9 በመቶ የደረሰበት ሁኔታ<br />

አለ። ይሄ አጠቃላይ ሁኔታ እንዳለ ሆኖ፣ ቫይረሱ እጅግ በጣም የተሰራጨባቸው የምንላቸው<br />

አንዳንድ ቦታዎች አሉ። በእነዚህና በአንዳንድ የሕብረተሰብ ክፍሎች አካባቢ <strong>ስር</strong>ጭቱ ከፍተኛ<br />

እንደሆነና በዚህም ዙሪያ ብዙ ሥራ መሠራት እንዳለበት ነው የሚያሳየው። በመሆኑም<br />

የሥርጭቱ የመቀነስ ሁኔታ ብዙ ሊያዘናጋን አይገባም።<br />

ለኮንፈረንሱ ከኢትዮጵያ ብዙ ጥናታዊ ፅሁፎች ቀርበዋል?<br />

አዎን። ደስ የሚለው ጥናታዊ ጽሁፍ በማቅረብ ኢትዮጵያ ከናይጄሪያ ቀጥላ ሁለተኛ ነች።<br />

ይኼ የሚያስመሰግን ነው። ምክንያቱም አንደኛ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ሳይንሳዊ ሕብረተሰብ<br />

ብዙ ስራ እየሰራ እንዳለ የሚያሳይ ሲሆን፣ ሁለተኛ ደግሞ በሀገሩ እንደዚህ አይነት ጉባዔ<br />

ሲደረግ በከፍተኛ ደረጃ ለመሳተፍ ዝግጁ መሆኑን ያሳያል።<br />

ጽሑፎች ከመቅረባቸው ባሻገር ተቀባይነት ያገኙና ያላገኙ ጥናቶች አሉ። አብዛኛዎቹ ግን<br />

ተቀባይነት አላገኙም።<br />

ከላይ እንደገለፁልኝ፣ የኮንፈረንሱ አንዱ ትርፍ የኢትዮጵያን በጎ ገጽታ ማሳየት ነው። ነገር ግን፣ በከተሞች በተለይም<br />

በመዲናችን አዲስ አበባ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተበራከተ የመጣው የሴተኛ አዳሪዎችና የመንገድ ላይ የወሲብ ንግድ<br />

የተባለውን በጎ ገፅታ አያሳይም። በዚህ ላይ ምን ታስቧል?<br />

መጀመሪያ ያልከው ነገር “ጨምሯል” ሲባል በደንብ በጥናት<br />

መታወቅ አለበት። ሌላው ነገር ይሄ ማሕበራዊ ችግር<br />

በሁሉም የአፍሪካ ሀገራት ያለ ችግር በመሆኑ የተለየ<br />

ነገር ተደርጎ አይወሰድም። በመሆኑም፣ ስብሰባው<br />

ሲካሄድ የሚደረግ ምንም የተለየ እርምጃ ሊኖር<br />

አይችልም። የተባሉትን ሰዎች ማግለልን የመሳሰሉ<br />

ነገሮች አይደረግም። ምክንያቱም፣ ከዚህም<br />

የባሰ ሁኔታ ላይ የሚገኙ አሉ። በሂደት ሀገሪቱ<br />

እያደገችና ከድህነት እየወጣች በምትሄድበት ጊዜ<br />

ይሄ ሁኔታ እየከሰመ ይሄዳል። ሀገሪቷ እስክታድግ<br />

ድረስ የማይጠበቁና የተባሉትን ሴቶች የሚመለከቱ<br />

ስራዎች እየተሰሩ ነው። በመንግስትና በምግባረ-<br />

ሰናይ ድርጅቶች አማካኝነት የአጭርና የረዥም ጊዜ<br />

ዕቅዶችም አሉ። ሆኖም እነዚህን ሰዎች በኃይል<br />

አስገድዶ ወደ አንድ ቦታ ማስቀመጥ ትክክለኛ አሰራር<br />

አይሆንም። ኮንፈረንሱም ይኼንን አያደርግም።


አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />

በታዳሽ የኃይል ምንጮች<br />

የሚከንፉ ዘመናዊ ኦቶሞቢሎች<br />

በአብዱ መሐመድ<br />

ከስኳር ዝቃጭ ኢታኖል<br />

የተባለውን ነዳጅ በማምረትና በኢታኖል<br />

የሚሽከረከሩ ኦቶሞቢሎችን በመፈብረክ<br />

ቴክኖሎጂውን በበላይነት የምትመራው፣<br />

ዓለም በተለይ በእግር ኳሷ የሚያውቃት<br />

ብራዚል ነች።<br />

ኢታኖል፣ ስኳር በማምረት<br />

ሂደት የሚመጣውን ዝቃጭ<br />

‹‹ፈርመንቴሽን›› በተባለው ኬሚካላዊ<br />

ሂደት ‹‹ይስት›› በተባለ በውስጡ ኢንዛይም<br />

በያዘ ባክቴሪያ በማብላላት ለኃይል ፍጆታ<br />

የሚውል ነዳጅ ነው።<br />

ይህንን ነዳጅ እ.አ.አ ከ1982<br />

ጀምሮ እስከ 5.7 ሜጋ ሜትር ኪዩብ<br />

በየዓመቱ በማምረት የኃይል ፍላጎቷን<br />

ማሟላት በጀመረችው ብራዚል እ.አ.አ<br />

ከ2000 ጀምሮ 75 በመቶ የኃይል ፍላጎቷን<br />

የምታሟላውና በጎዳናው ላይ የሚተራመሱ<br />

ኦቶሞቢሎች የሚተራመሱት በኢታኖል<br />

ነው።<br />

የኢነርጂ ጥናት ባለሙያዎች<br />

የብራዚልን ተሞኩሮ መነሻ በማድረግ<br />

ባቀረቡት ጥናት መረጃ በአንድ ሄክታር<br />

በአማካይ 50 ቶን ሸንኮራ አገዳ ማምረት<br />

ይቻላል። ይህንን የሸንኮራ አገዳ ወደ ስኳር<br />

በመለወጥ ሂደት ከስኳር ኢንዱስትሪ<br />

ከሚወጣው ዝቃጭ ከአንድ ቶን ሸንኮራ<br />

በአማካይ 70 ሊትር፤ በአንድ ሄክታር ላይ<br />

ከሚመረት የሸንኮራ አገዳ፣ 3500 ሊትር<br />

ኢታኖል ይወጣል።<br />

ኢታኖልን በሀገራችን<br />

እንደሚሰራበት ከተፈጥሮ ነዳጅ ጋር<br />

ከመቀየጥ ባለፈ በኦቶሞቢል ግንባታ<br />

ከአለማችን ቀዳሚ የሆኑ እንደ ቮልስዋገን፣<br />

ፎርድ፣ ፊያትና ጀነራል ሞተርስ<br />

በብራዚል በሚገኙ ቅርንጫፍ መስሪያ<br />

ቤቶች የሚያመርቷቸው ኦቶሞቢሎች<br />

እንደባለቤቱ ፍላጎት ሲያስፈልግ በተፈጥሮ<br />

ነዳጅ አሊያም በኢታኖል የሚንቀሳቀሱ<br />

ናቸው። ከነዚህ ኦቶሞቢሎች ‘ፍሌክስ’<br />

የተባለው ኦቶሞቢል ከብራዚል አልፎ<br />

በሰለጠነችው አሜሪካ የፈላጊው ቁጥር<br />

ከ20 በመቶ የበለጠ ዕድገት ማስመዝገብ<br />

የጀመረው እ.አ.አ ከ2003 ጀምሮ ነው።<br />

ብራዚል በኢታኖል የኃይል<br />

ፍላጎቷን አሟልታ ከአንድ ሚሊየን<br />

ለሚበልጥ ዜጋዋ የሥራ ዕድል<br />

ከመፍጠሯም በተጨማሪ፣ ቴክኖሎጂውን<br />

በመሸጥ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማግኘት<br />

በከፍተኛ ርቀት ዓለምን እየመራች ነው።<br />

አሁን በየጊዜው እየነጠፈና ጣራ እየነካ<br />

የመጣውን የነዳጅ ውዝግብ ለመፍታት<br />

እንዲሁም የአካባቢ ብክለትን ለመቀነስ<br />

እተለወጠ በመጣው የቴክኖሎጂ ሽግግር<br />

ከብክለት የፀዱ የኃይል ምንጮች<br />

የሚንቀሳቀሱ ኦቶሞቢሎች እየተፈበረኩና<br />

ወደጎን እየወጡ መሆናቸውን በየጊዜው<br />

የሚደመጥ ዜና ሆኗል።<br />

በየጊዜው እየተመረቱ የሚወጡ<br />

ከብክለት የፀዱ ቴክኖሎጂ የሚጠቀሙ<br />

ኦቶሞቢሎችን በሚያስተዋውቀው<br />

‹‹ካር መጋዚን›› በተባለ መፅሄትና<br />

በየዓመቱ በየዘርፉ ለውድድር ቀዳሚ<br />

ለሆኑት እውቅና በሚሰጠው የጊነስ ቡክ<br />

በተቀመጠው መረጃ አሁን ከፍተኛ ቦታ<br />

የተሰጣቸው የሀይብሪድና የኤሌክትሪክ<br />

ኦቶሞቢሎች ናቸው።<br />

‹‹ሀይብሪድ ካር›› ውሃ<br />

ከተሰራባቸው የኬሚካል ቅንጣቶች<br />

ከሀይድሮጅንና ከኦክሲጅን ሀይድሮጅንን<br />

‹‹ኤሌክትሮሊስስ›› በተባለው የኬሚስትሪ<br />

ዘዴ እየለየ ለኦቶሞቢል ኢንጂን በመቀለብና<br />

ውሀን በተረፈ ምርት በማስወገድ<br />

የሚንቀሳቀሱ ኦቶሞቢሎች ናቸው።<br />

በዚህ ቴክኖሎጂ እንዲንቀሳቀሱና<br />

ከተፈበረኩ ኦቶሞቢሎች በሚያወጣው<br />

ጉልበትና ፍጥነት የአለምን ሪከርድ ሰብሮ<br />

ባለፈው ሳምንት በጊነስ ቡክ የሰፈረው<br />

በእንግሊዝ ሳንታ ሮድ ከተማ በተዘጋጀ<br />

የሀይብሪድ ካር ውድድር አሸናፊ ለመሆን<br />

የቻለው ‹‹ኢንፊኒቲ ኤም 35 ኤች›› የተባለ<br />

ሥያሜ የተሰጠው ኦቶሞቢል ነው።<br />

ዘመናዊ ከሆኑት ከቢኤም<br />

ደብሊው 5 ሲፊየስና ከጃጓር ኤክስ ኤፍ<br />

ዲዛይን ጋር ተመሳስሎ የቀረበው ‹M35H›<br />

3.5 ሊትር ሀይድሮጅን ወደኤሌክትሪክ<br />

በሚቀይሩ በድምሩ 302 የፈረስ ጉልበት<br />

በሚያመነጭ v-6 በተባለ ኢንጂን በሰዓት<br />

105.95 ኪሎ ሜትር በመክነፍ ውድድሩን<br />

ምንም ብክለት በሌላቸው ‹‹ዜሮ ኢሚሽን›› የተባሉ<br />

ከባትሪ የሚያገኙትን ኃይል ወደ ኤሌክትሪክ እየለወጡና<br />

የኤሌክትሪክ ሀይል እየተሞሉ ከሚጓዙ ኦቶሞቢሎች<br />

ሪከርዱን በስማቸው ያስመዘገቡት ለመኪና ውድድር ስፖርት<br />

የተዘጋጀው ‹‹አክሲራይድ›› እና ለሰው መጓጓዣ የተዘጋጀው<br />

‹‹ብላክ ከረንት›› የተባለው ኦቶሞቢል ነው።<br />

ያጠናቀቀው በአማካይ እያንዳንዱን አንድ<br />

አራተኛ ማይል (402.3 ሜትር) በ13.9<br />

ሰከንድ በመክነፍ ነው።<br />

በኢታኖል ከሚከንፉ<br />

ኦቶሞቢሎች ቀዳሚ የሆነው የብራዚሉ<br />

ሥሪት ፍሊክስ ሙሉ በሙሉ ከብክለት<br />

የፀዳ ባለመሆኑ ከብክለት ከፀዱት ጋር<br />

ለውደድር ባይቀርብም የአምሳዮቹን<br />

ሪከርድ የሰበረው በሰዓት 364.6 ኪሎ<br />

ሜትር በተመዘገበ ፍጥነት እንደሆነ የጊነስ<br />

መረጃ ይጠቁማል።<br />

ምንም ብክለት በሌላቸው<br />

‹‹ዜሮ ኢሚሽን›› የተባሉ ከባትሪ<br />

የሚያገኙትን ኃይል ወደ ኤሌክትሪክ<br />

እየለወጡና የኤሌክትሪክ ሀይል እየተሞሉ<br />

ከሚጓዙ ኦቶሞቢሎች ሪከርዱን በስማቸው<br />

ያስመዘገቡት ለመኪና ውድድር ስፖርት<br />

የተዘጋጀው ‹‹አክሲራይድ›› እና ለሰው<br />

መጓጓዣ የተዘጋጀው ‹‹ብላክ ከረንት››<br />

የተባለው ኦቶሞቢል ነው።<br />

በእንግሊዛዊ ወንድማማቾች<br />

በኦሊ እና ሳም ያንግ ለሰው መጓጓዣ<br />

የፈበረኳት ‹‹ብላክ ከረንት›› ጠቅላላ<br />

የውጭና የውስጥ ዲዛይኗ የተወሰደው<br />

እ.አ.አ በ1965 ለመጀመሪያ ጊዜ ጎዳና<br />

ከወጣችው ከቮልስ ዋገን ነው። ይህን<br />

ዲዛይን ተላብሳ በሰኔ 16/2011 በእንግሊዝ<br />

ኖርዝ ሀምብተን በተካሄደ የኤሌክትሪክ<br />

መኪናዎች ውድድር አዲስ ሪከርድ<br />

ያስመዘገበችው ከቆመችበት ተነስታ በሰዓት<br />

96.5 ኪሎ ሜትር እየከነፈች ውድድሩን<br />

በቀዳሚነት ያጠናቀቀችው እያንዳንዳቸው<br />

12 ቮልት የሚያመነጩ 60 የሞተር<br />

ሳይክል ባትሪዎች የተገጠሙላት በመሆኗ<br />

ነው።<br />

ለመኪና ውድድር ስፖርት<br />

ከተዘጋጁ ባትሪን ወደ ኤሌክትሪክ<br />

ኃይል ከሚለውጡ መኪናዎች ወደጃፓን<br />

የማቱሺታ ኤሌክትሪክ ኢንዱስትሪያል<br />

ካምፓና የበኦሳካ ሳንጊዩ ዩኒቨርስቲ<br />

ለውጤት ያበቃችው ‘ኦክስራይድ’ ከባትሪ<br />

ከምታገኘው ኃይል የአምሳያዎቿን<br />

የፍጥነት ወሳን የሰበረችው በሰዓት<br />

105.95 ኪ.ሜ. የመክነፍ ብቃት ተላብሳ<br />

ወደጎንና በመውጣቷ ነው።<br />

በቀጥታ ከኤሌክትሪክ ሀይል<br />

ማመንጫ የኤሌክትሪክ ሀይል የሚሞሉና<br />

ይህን ሀይል አምቀው ከሚያስቀምጡ<br />

ካፓሲተሮች ኃይል እየተመገቡ ከሚከንፉ<br />

መኪናዎች የአለም ክብረወሰን ባለቤት<br />

‹‹ፎርሙሊክ EFOL›› የተባለችው<br />

ኦቶሞቢል ነች።<br />

ፓሪስ በሚገኘው ፎርሙሊክ<br />

ካምፓኒና ከፍተኛ አድናቆትና ውደሳ<br />

የተላበሰችው ፎርሙሊክ ከብክለት<br />

የፀዳች ከመሆኗ በተጨማሪ ኃይልን<br />

በመቆጠብና በፍጥነት በመክነፍ ያላትን<br />

ብቃት በሚተነትነው መረጃ በሰዓት<br />

እስከ 260 ኪ.ሜ. ፍጥነት እያቀያየረች<br />

መጓዝ ትችላለች። ይህ ፍጥነቷ ፎርሙላ<br />

3 ከተባሉ ለመኪና ውድድር ስፖርት<br />

ከተዘጋጁ በተፈጥሮ ነዳጅ ከሚከንፉ<br />

መኪናዎች የሚቀራረብ ከመሆኑ<br />

በተጨማሪ ቀጥ ባሉ ጎዳናዎች ከበካዩቹ<br />

ኦቶሞቢሎች ጋር ለውድድር መቅረብ<br />

የምትችል ናት። አንድ ጊዜ በተሞላቸው<br />

የኤሌክትሪክ ሀይል በምትጓዝበት ጎዳና<br />

ጠመዝማዛነት ወጣ-ገባነት ላይ የተመረኮዘ<br />

ቢሆንም፣ እንደገና የኤሌክትሪክ ቻርጅ<br />

የምትሞላው ያለማቋረጥ ከተጓዘች ከአንድ<br />

እስከ አንድ ሰዓት ተኩል በሚረዝም የጊዜ<br />

ልዩነት ነው።<br />

በዓለማችን የኦቶሞቢል<br />

አምራች ድርጅቶች እየተጠናከረ በመጣው<br />

ከብክለት የፀዱ ኦቶሞቢሎች ግንባታ ገበያ<br />

የሚቀርቡ ኦቶሞቢሎች የሚመዘኑት<br />

በዋጋቸውና ኃይልን በመቆጠብ ብቃታቸው<br />

ነው።<br />

እንደዛሬው ነዳጅ በበርሜል<br />

ከ100 ዶላር በላይ ጣሪያ ነክቶ ባለሀብቶች<br />

ከተራው ሰው ጋር በአውቶቡስና በባቡር<br />

ለመሄድ ከመገደዳቸው በፊት የኦቶሞቢል<br />

ካምፓኒዎች ትኩረት ባለሀብቶችን<br />

ከተራው ሰው ለይተው በጎዳና ላይ<br />

የሚያንደላቅቁ የኦቶሞቢል ዲዛይኖችን<br />

ለገበያ ማቅረብ ነበር። ይህንን መመዘኛ<br />

በመንተራስ ከ1950ዎቹ ወዲህ ከተፈበረኩ<br />

ኦቶሞቢሎች ጣራ በነካ ዋጋ በመሸጥ<br />

እስካሁን ሪከርዱን ይዞ የዘለቀው እ.አ.አ<br />

በ1963 ቼሪስ ኢቫንስ የተባለው እንግሊዛዊ<br />

ባለሀብት በ17,275,00 ዶላር በአሁኑ<br />

የገዛት ፌራሪ 250GT የተባለች ኦቶሞቢል<br />

ናት።<br />

በተመረተ በአንድ ዓመት<br />

ውስጥ ከፍተኛ ሀብት ባስመዘገበ ከፍተኛ<br />

ሽያጭ የዓለማችን ባለሀብቶች በብዛት<br />

ቀዳሚ ሆነው የሸመቱት እ.አ.አ በ1997<br />

እያንዳንዱ በ1,547,620 ዶላር ለገበያ<br />

የቀረበው ‹‹ሜርሴዲስ ቤንዝ CLK/LM<br />

የተባለው ኦቶሞቢል ነው።<br />

ፅሁፋችንን የምንቋጨው<br />

በአብዛኛው የዓለም ህዝብ ጆሮ ያልደረሰውን<br />

ባለፈው ሳምንት ጥቅምት 20/2011 በጊነስ<br />

ቡክ አዲስ የዋጋ ሪከርድ ያስመዘገበውን<br />

ተንቀሳቃሽ የቤት ኦቶሞቢል (Luxury<br />

motorhomes) በማስተዋወቅ ነው።<br />

ባለፈው ሳምንት በኦስትሪያ<br />

ተዘጋጅቶ በከተማዋ ጎዳና በመንፈላሰስ<br />

ለዕይታ የበቃው ‹‹The eleMMent››<br />

ውድ ተንቀሳቃሽ የቤት ኦቶሞቢል<br />

ባለአምስት ኮከብ ሆቴሎች ውስጥ የሚገኙ<br />

መጠጥ ቤቶች የሚሰጡትን አገልግሎትና<br />

ውበት የተላበሰ ተንቀሳቃሽ መኪና ነው።<br />

የተደራረቡ ሁለት ጥንድ መኪናዎች<br />

የሚመስል ገፅታ በተላበሰው በላይኛው<br />

ክፍል አሥራ-ሁለት ሜትር ርዝመት ወደ<br />

ጎን ተዘረጋግቶ የሚጋጠም 30 ስኩየር<br />

ሜትር ስፋት ያለው መኖሪያ ይገኛል።<br />

ከታች ያለው መኪና ከላይ<br />

የተሸከመውን መኖሪያ ይዞና እስከ 20 ቶን<br />

ክብደት ተሸክሞ በሰአት 150 ኪሎ ሜትር<br />

የሚከንፈው 510 የፈረስ ጉልበት ባለው<br />

ሞተር ነው።<br />

ከላይ ወዳለው መኖሪያ<br />

ስትዘልቁ በዋናው መኝታ ቤት በቁሳቁስ<br />

የተሞላ የተንጣለለ አልጋና 40 ኢንች<br />

ስፋት ያለው የሳተላይት ቴሌቭዥን፣<br />

የኢንተርኔት ሞባይልና የቪዲዮ ማሳያ<br />

ዴኮችን ትመለከታላችሁ። መኝታ ቤቱን<br />

በማለፍ ወደ ውስጥ ስትዘልቁ ዘመናዊ<br />

የመታጠቢያ ገንዳ ያለው ክፍልና የመፀዳጃ<br />

ክፍሎችን ታገኛላችሁ። በታችኛው ሹፌሩ<br />

በሚቀመጥበት ክፍል የሹፌሩ ማረፊያ<br />

አልጋ የተዘረጋበት ክፍልና የእንግዳ<br />

መቀመጫ ሳሎን የያዘ ነው። ይህ ዘመናዊ<br />

ኦቶሞቢል እና ተንቀሳቃሽ መኖሪያ ግንባሩ<br />

ላይ በተለጠፈው የፀሐይ ብርሀን ወደ<br />

ኤሌክትሪክ ሀይል ከሚለውጥ መስታወት<br />

በሚያገኘው ሀይልና ነዳጅን በ20 በመቶ<br />

በሚቆጥብ ኢንጂን ነው።<br />

ይህ ብቃት ተላብሶ ለውጤት<br />

የበቃውን ኦቶሞቢል ተንቀሳቃሽ መኖሪያ<br />

ከተሸከሙ ኦቶሞቢሎች በዋጋ ውድነቱ<br />

የጊነስን ሪከርድ የሰበረው ኦቶሞቢሉን<br />

የፈበረከው ማርቺ ሞባይልስ የተባለው<br />

የኦስትሪያ ካምፓኒ የመሸጫ ዋጋው<br />

2.96 ሚሊየን ዶላር ወይም 49 ሚሊየን<br />

ሶስት መቶ ሺህ ብር መሆኑን። ወዳጁ<br />

ባለሀብቶች፣ ይወቁልኝ ማለቱን ተከትሎ<br />

ነው።<br />

ዓለማዊ ወግ...<br />

‹‹የለም፤ ስለየኔታ ሳይሆን ስላንተ<br />

ከየኔታ የሰማሁት ነገር አለ›› አለኝ።<br />

‹‹ምን?››<br />

‹‹አብዷል ብለው ስላንተ<br />

ማበድ ነገሩኝ››<br />

‹‹እኔ! እኔ አብጄ?›› ባጣም<br />

ተደናግጬ ነበር የጠየቅሁት።<br />

‹‹ኋላ እኔ ነኝ ያበድኩት!››<br />

በማለት ሲያሾፍብኝ የኔታ ታላቅ ደባ<br />

እንደሰሩብኝ አወቅሁ። ቅድም ወደ<br />

ትምህርት ስሄድና ስደርስ የተገጠመውን<br />

ግጥም አሰብኩ።<br />

ለምንት አንገለጉ አሕዛብ<br />

ወሕዝብኒ ነበቡ ከንቶ<br />

መቸ በከንቱ ነው ልባቸው<br />

ተነክቶ<br />

የኔታ አበሳጩኝ። እኔ<br />

ወደ ትምህርት ሳልደርስ በፊት እኔን<br />

ሲያሙኝ እንደነበረ ገባኝ። ተማሪዎች<br />

ደግሞ ተታለውላቸዋል። እንዴት<br />

አንድ የቅስና መምህር በቂም በቀል<br />

ተማሪውን ያማል? አስማማውን<br />

አከበርኩት። እውነትም ከቅስና በፊት<br />

ቅድስና መብለጥ አለበት።<br />

‹‹ሌላስ የነገሯችሁ ነገር<br />

አለ?›› አልኩት። ‹‹የለም፤ ሌላ እንኳ<br />

አልሰማሁም።››<br />

ደስ አለኝ። ማን ተማን<br />

ያንሳል። እኔን እንዳሙኝ እኔም<br />

ጉዳቸውን አወጣዋለሁ።<br />

ስለየኔታና ‘ኔ ሁሉንም ነገር<br />

ለአስማማው ነገርኩትና “ታዲያ ምን<br />

እንዳደርግ ትመክረኛለህ?›› አልኩት።<br />

ፈላስፋው ብዙ ጊዜ ወስዶ ሲያስብ ቆየ፤<br />

‹‹እኔ አንተን ብሆን?›› አለና አጓጓኝ።<br />

ምርጥ ሀሳብ እንዳሰበ ስለገመትኩ<br />

በትዕግስት መጠባበቅን መረጥኩ።<br />

‹‹አንድ ነገር ልንገርህ<br />

እንዳለው? ጥፋ!!! እኔም ወደዚያው ነኝ<br />

. . . እዚህ ተምረን ምን ልንፈጥር<br />

ነው? መቸም ስምንተኛው ሺህ ደርሶ<br />

ነው እንጂ መሪጌቶች ሁሉ እንዲህ<br />

ሁነው የተበለሻሹ የጤና አይመስለኝም<br />

‘ና ጥፋ!!!››<br />

‹‹ጠፍቸስ የት እሄዳለሁ?››<br />

‹‹አዲስ አበባ ሂድ፤ እኔም<br />

ወደዚያው ነኝ!››<br />

‹‹እዚያ ሄደህ በምን<br />

ትተዳደራለህ? እኔስ በምን እንድተዳደር<br />

ትመክረኛለህ?››<br />

‹‹ፈራህ እንዴ? እኔ አንዲት<br />

በምስጢር የማዘጋጃት ጉዳይ ስላለችኝ<br />

ነው እንጂ አብረን እንሄድ ነበር። ጥፋ’ና<br />

አንድ ቀን እንገናኛለን፡፡››<br />

. . .<br />

አዲስ አበባ ቁራሽ የሚለምን<br />

ሰው ‘ለማኝ’ ነው እንጂ የቆሎ ተማሪ<br />

አይደለም። እኔ ደግሞ በስደት አዲስ አበባ<br />

ገብቸ ግራ ገብቶኛል። የምሰራውም፣<br />

የምበላውም እያጣሁ እግሬ እስኪያጥር<br />

ድረስ ስዞር እውላለሁ። ከሀገሬ እያለሁ<br />

ስለ አዲስ አበባ ብዙ ሲወራ እሰማ ነበር።<br />

“የአዲስ አበባ ውኃ ምግብ ነው” ያሉትን<br />

ሰምቸ እንደመጣሁ ብዙ ውኃ ጠጣሁ።<br />

የተረፈኝ ነገር ቢኖር ግን በየደቂቃው<br />

ሽንቴን በየአጥሩ ጥግ መሽናት ነበር።<br />

መቸም የኔ መጥፊያ ሽንት<br />

ነው። ከሀገሬ የተሰደድኩት በሽንት<br />

የተነሳ ከየኔታ ጋር ተቀያይሜ ነው።<br />

አዲስ አበባ ደግሞ አንድ አጥር<br />

ጥግ እግሬን አንቧትሬ ስሸና አንድ<br />

ወጠምሻ እንደ ድመት ጋማዬን ይዞ<br />

አንጠለጠለኝ።<br />

ሁለት ወይም ሶስት ጊዜ<br />

የካልቾ ድምጽ መስማቴ ትዝ ይለኛል።<br />

ከዚያ ወዲያ እንዴት እንደመታኝ፤<br />

መቸ እንደመታኝ ሳይታወቀኝ ሰውነቴ<br />

ቆሳስሎና ደክሞ ተገኘሁ። አጥሩን<br />

ተደግፌ ለሰባት ትውልድ የሚበቃ እንባ<br />

አፈሰስኩ። አሁን እኔ ሰው ነኝ? ወይስ<br />

የካራቴ መለማመጃ ከረጢት? ማልቀሱ<br />

ሲደክመኝ ማልቀሴን ትቸ በእግሬ<br />

መጓዝ ጀመርኩ።<br />

ብዙ መንገድ በእግሬ<br />

ተጉዤ ቀና ስል የባህል ህክምና የሚል<br />

ማስታወቂያ አየሁ፡፡ በተላላኪነት እንኳ<br />

ቢቀጥሩኝ ብየ ወደዚያው አመራሁ።<br />

እንደውም ሳስበው<br />

21<br />

አስማማው በምስጢር የማዘጋጃት ጉዳይ<br />

ስላለችኝ ነው ያለው ስራ-<strong>ስር</strong> ሊለቅምና<br />

እዚህ መጥቶ አዋቂ ነኝ ሊል እንደሆነ<br />

ገምቸ ነበር። አዲስ አበባ እንደሆነች<br />

ትንሽ ግዕዝና የገጠር አማርኛ የሚችል<br />

ሁሉ የባህል መድኃኒት እና የድግምት<br />

አዋቂ የሆነባት ከተማ ናት።<br />

የባሕል ሐኪሙ ዘንድ<br />

ደንበኛ የሆኑ ብዙ ሰዎችን አገኘሁ።<br />

ከእነዚህም መካከል ዘፋኞች፣ አትሌቶች፣<br />

አርቲስቶች፣ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣<br />

የፓርላማ ተወካዮች፣ የተለያዩ<br />

ሃይማኖቶች መሪዎች፣ የጥቃቅንና<br />

አነስተኛ ንግድ ባለቤቶች ወዘተ ይገኙበት<br />

ነበር። ሌሎችን የተመለከቱ መረጃዎችን<br />

ሳምንት እንደምነግራችሁ ቃል በመግባት<br />

አሁን ግን ከአንዱ ዘፋኝ ጋር ያደረኩትን<br />

ንግግር ሳልደብቅ ላጫውታችሁ።<br />

አቋሙ ከሲታ ነው። እንደ<br />

እውነቱ ከሆነ ከዚህ ግለሰብ የሚወጣው<br />

ድምጽ ሕዝብን ያዝናናል ከማለት<br />

ይልቅ ያሳቅቃል ብሎ መገመት ያሸልም<br />

ይሆናል። ጉሮሮው ላይ ያለውን ክርክር<br />

የተመለከተ ያዝንለታል እንጂ ዘፍኖ<br />

ያዝናናኛል ብሎ ተስፋ አይጥልበትም።<br />

‹‹ምነው ‘ጓዴ! ምን እግር<br />

ጥሎህ መጣህ?›› ይህ የእኔ ጥያቄ<br />

ነበር።<br />

ሰውየው የዋዛ አልነበረም።<br />

እንደሚከተለው አማረረ፡-<br />

‹‹አንድ አይሉ ሁለት ካሴቶችን<br />

ሰርቻለሁ ግን ከአንድ ቀበሌ ገበሬ ማኅበር<br />

ሰላሳ ሰው እንኳ አልሰማኝም። ድምጤ<br />

እግዚአብሔር ይመስገነው ደህና ነው!<br />

ያለመደመጤ መንስኤ ምን እንደሆነ<br />

ስላላወቅሁት የሆነ መተት ሰርተውም<br />

ቢሆን አኒህ ቅዱስ አባታችን በቢል-<br />

ቦርድ ላይ ቁጥር አንድ እንዲያደርጉኝ<br />

ለመለመን ነው የመጣሁት። እንዴት<br />

ነው፤ የሚሳካልኝ ይመስልሃል?››<br />

በእውነቱ ይህንን ሲጠይቀኝ<br />

የምመልሰውን አጥቼ ነበር። ይሁንና<br />

ስለያሬዳዊ ዜማ ከሚያወቁት ወገን ነኝና<br />

‹‹ስለ ኢትዮጵያ ቅኝቶች፣ ማለቴ የዜማ<br />

ዓይነቶች ምን ታውቃለህ?›› አልሁት።<br />

ተረጋግቶ እየመለሰልኝ<br />

ነበር፤ ‹‹ስለዜማ ዓይነቶች በማወቅ<br />

እና በመመራመር የሚያህለኝ የለም።<br />

ከፈለግህ የተመኘኸውን ጠይቀኝ›› በማት<br />

በኩራት መለሰ።<br />

‹‹እንግዲያው እየጠየቅሁህ<br />

አይደለምን፤ ስንት የዘፈን፣ ማለቴ የዜማ<br />

አይነቶች አሉ?››<br />

‹‹አራት ናቸው›› ብሎ ሲመልስ<br />

አከበርሁት። ‹‹እስቲ ዘርዝራቸው››<br />

ይህንን የጠየቅሁት ስለ አንባሰል፣<br />

አንች ሆዬ፣ ባቲ እና ትዝታ እውቀት<br />

ስላለኝ ነበር። እርሱ መመለስ ጀመረ፡-<br />

“የኢትዮጵያ ዘፈኖች በአራት ይከፈላሉ።<br />

እነሱም የሀዘን፣ የጦርነት፣ የሥራ እና<br />

የሠርግ ተብለው ነው›› አለ፡፡ ኩም<br />

አልኩ፡፡ /ይቅርታ አሁን ስለተበሳጨሁ<br />

ሌሎችን እንዴት እንዳናገርኋቸው?<br />

መናገር አልችልም፤ ሳምንት ጠብቁኝ።/<br />

የሄድኩበት የባህል ሀኪም<br />

ዓነተ--ብዙ የሆኑ ጥያቄዎችን እየጠየቀ<br />

ሲያውጣጣኝ ቆየ። እኔ ምኔ ሞኝ? አሻፈረኝ<br />

አልሁ! የማውቀው መድኃኒት ቢኖር<br />

እንዴት እንደሚቀመም ሊያውጣጣኝ<br />

አይደል? ምንም ስላልነገርኩት ተበሳጭቶ<br />

የታሰረ ውሻ ፈትቶ ለቀቀብኝ። ሮጬ<br />

አመለጥሁ። ወዲያው ሊታከም ይመጣ<br />

ከነበረ አንድ ወጣት ጋር ግቢው ፊት<br />

ለፊት ተገናኘን።<br />

‹‹የሃኪሙ ቤት እዚህ ነው?››<br />

አለኝ ወጣቱ<br />

‹‹አዎ! ምን ፈልገህ ነው?››<br />

ወጣቱ ገልመጥመጥ ብሎ አካባቢውን<br />

ተመለከተና፣ ‹‹ፍቅር ይዞኝ . . .<br />

መስተፋቅር . . . ››<br />

‹‹ስንት ትከፍላለህ?›› አልኩት<br />

እንዲህ አይነት ትልቅ ሲሳይ ተገኝቶ<br />

ማለፍ ሞኝነት መሰለኝ።<br />

‹‹የተጠየቅሁትን እከፍላለሁ››<br />

አለ ወጣቱ ባለማመን። ‹‹እሺ አንድ ቦታ<br />

ተቀምጠን እናውራ፤ የደረሰብህን ፍቅር<br />

በደንብ አብራተህ ልትነግረኝ ይገባል።››<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ


22<br />

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሁለት ዓመት<br />

የስራ ጉዞን እንዴት ይቃኙታል?<br />

ይህ ፌዴሬሽን ብዙ ችግሮች በነበሩበት ጊዜ<br />

የመጣ ስለ ነበር ነገሮችን <strong>ስር</strong>ዓት ለማስያዝ ብዙ ስራ<br />

ሰርቷል። እግር ኳሳችን በውጤት ደረጃ ደካማ በመሆኑ<br />

የህዝቡን ፍላጎት ማሟላት አልቻለም። በዘርፉ ያሉን<br />

ባለሙያዎች በቂ አይደሉም። ባለን አቅም ስራዎችን<br />

ተከፋፍለን ለመስራት ሞክረናል።<br />

በወንዶችም ሆነ በሴቶች በዓለም አቀፍ<br />

ውድድሮች ላይ ተካፋይ ነበርን። የእውነት ነው<br />

የምልህ ሴቶቹ ላይ የቻልነውን ያህል በጣም ብዙ ስራ<br />

ሰርተናል። ያው እንደምታውቀው የሴቶች ኦሎምፒክ<br />

ቡድናችን የለንደን ኦሎምፒክን በር አንኳኩቶ<br />

በመጨረሻው ጨዋታ በደቡብ አፍሪካ በመሸነፉ ሳይገባ<br />

ተመልሷል።<br />

ሴቶች እግር ኳስ ተጨዋቾቹን ፌዴሬሽኑ ሰርቶባቸው<br />

የተገኙ ናቸው ማለት እንችላለን?<br />

ፌዴሬሽኑ ከታች ሰርቶባቸው የመጡ<br />

ባይሆኑም ከመጡ በኋላ ቀባብተን (በአግባቡ በመያዝ)<br />

እንደቀድሞው ጊዜ በሴቶች ለዓለም አቀፍ ውድድር<br />

በራችንን ሳንዘጋ ሰርተንባቸዋል። ረዥም ጊዜ አብረው<br />

እንዲቆዩ በማድረግ፣ የኪስ ገንዘብ፣ ሽልማትና<br />

የሚፈልጉትን ነገር በማሟላት ጥሩ የሚባል ውጤት<br />

ላይ ደርሰዋል። ብዙ ብር ስላፈሰስንባቸው አንፀፀትም።<br />

ምክንያቱም ልጆቹን ክለቦች እየያዟቸው ነው።<br />

በ2004 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተሳታፊ<br />

ቡድኖች የሴት ቡድን መያዝ የግድ እንዳለባቸው<br />

ስትገልፁ ቆይታችሁ ሀሳባችሁን በመቀየር ወደ 2005<br />

ዓ.ም. አምጥታችሁታል። ምክንያታችሁ ምንድን<br />

ነው?<br />

ወደ 2005 ዓ.ም. የተገፋው አንዳንድ<br />

ቡድኖች የመዘጋጃ ጊዜ እንዲኖራቸው ተብሎ ነው።<br />

በዚህ ዓመት በሁለተኛ ወር፣ በአራተኛ ወር ወይም<br />

በአንዱ ወር ቡድን ሊያቋቁሙ ይችላሉ። ይህን<br />

የሚቆጣጠር አካል አለ። በአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ<br />

እና ኮንፌዴሬሽን ካፕ ላይ የሚካፈሉ ሁለት ክለቦች<br />

የሴት እና የታዳጊ ቡድን ከሌላቸው በጭራሽ መወዳደር<br />

አይችሉም ተብሏል፤ በካፍ።<br />

እውን ይህ አስገዳጅ ህግ ነው?<br />

በአዲስ አበባ በተካሄደው በ‘Win in Africa<br />

with Africa’ የክለብ አመራሮች ስልጠና ላይ ክለቦች<br />

በ2004 የሴት ቡድን ለማቋቋም ውሳኔ ላይ ደርሰው<br />

ነበር።<br />

ክለቦች ‹‹በዚህ ዓ.ም. የሴት ቡድን ይኖረኛል›› ብለው<br />

ቃል ሊገቡ ይችላሉ። የእኔ ጥያቄ ህጉ አስገዳጅ<br />

ነወይ ነው? እንደዚያ ከሆነ የእንግሊዙ ታላቅ ክለብ<br />

ማን.ዩናይትድን ጨምሮ ያሉ የሴት ቡድን የሌላቸው<br />

ክለቦች ሊታገዱ ነው ማለት ነው?<br />

ማን.ዩናይትድ የሴት ቡድን እንደሌለው<br />

እርግጠኛ ነህ?<br />

በጣም፤ የለውም።<br />

እኔ መረጃው የለኝም። እንዲኖራችሁ ስለተባለ<br />

የተወሰኑ ክለቦች የሴት ቡድን አቋቁመዋል። የተወሰኑ<br />

ክለቦች ደግሞ ‹‹ለከርሞ እንጂ ለዘንድሮ አናዘጋጅም››<br />

ብለዋል። እንደዚህ እየተባለ ከተሄደ በሚቀጥለው<br />

ዓመትም ዋስትና አይሰጥም። በተለየ ይህን ሁኔታ<br />

የሚከታተለው የሊግ ኮሚቴ ነው። እነሱን ብትጠይቅ<br />

የተሻለ መልስ ይሰጡሀል።<br />

2005 ዓ.ም. መጨረሻ የስራ ጊዜያችሁ ስለሚያበቃ<br />

‹‹የሴት ቡድን አቋቁመው ወጡ›› መባልን<br />

ስለምትፈልጉ ገደብ ያላችሁትን እንዳዘዋወራችሁት<br />

የሚናገሩ አሉ። ይስማማሉ?<br />

አንድ ስራ ስትሰራ ግላዊ ሳይሆን ተቋማዊ<br />

በሆነ መልኩ ሊሆን ይገባል። እኔ የጀመርኩትን<br />

ሁሉ ጨርሼ ሄዳለሁ ማለት አይደለም። ሳንሰራው<br />

ለሌላው አስተላልፈን ለመሄድ ብቻም አንሰራም። ብዙ<br />

የሰራናቸው፣ ብዙ የቀሩ ነገሮች አሉ። የቻልነውን<br />

ያህል እንሰራለን።<br />

የአፍሪካ ሴቶች ሻምፒዮና ቅድመ ማጣሪያ በጥር ወር<br />

የመጀመሪያ ሳምንት ይደረጋል። ኢትዮጵያ ከግብፅ<br />

መመደቧ ይታወቃል። ዝግጅት መቼ ለመጀመር<br />

አሰባችሁ? [ወ/ሮ ጥሩወርቅ የብ/ቡድኑ የቡድን መሪ<br />

ናቸው።]<br />

የጠቅላላ ጉባዔ ስብሰባ በተደረገበት ወቅት<br />

ትኩረት ተሰጥቶት የተወያየነው በብሔራዊ ቡድን<br />

ላይ ነው። በግልፅ መስተካከል ያለባቸው ነገሮች<br />

ተቀምጠዋል። ‹‹የብሔራዊ ቡድን መተዳደሪያ<br />

መመሪያ›› ወጥቷል። ይህ ከፀደቀ በኋላ ብ/ቡድን ለስንት<br />

ቀን ልምምድ መስራት እንዳለበት ስለሚገልፅ በዚያ<br />

መሰረት እንወስናለን። እርግጠኛ ባልሆንም ታህሳስ<br />

ውስጥ ልጆቹ ተሰባስበው ልምምድ ይጀምራሉ ብዬ<br />

ገምታለሁ። ከዚያ በፊት ውድድሮች ይኖራቸዋል።<br />

የሴቶች ውድድር በእርግጠኝነት የሚጀመርበት ቀን<br />

ይታወቃል?<br />

ይህን የሚወስነው ሊግ ኮሚቴው ነው። ልጆቹ<br />

በአሁን ሰዓት በየክለባቸው ልምምድ ላይ ናቸው።<br />

[የኢትዮጵያ እና ግብፅ አሸናፊ በሰኔ ወር መጀመሪያ<br />

ከናሚቢያ እና ታንዛኒያ አሸናፊ ጋር የመጀመሪያ ዙር<br />

የማጣሪያ ጨዋታ ታደርጋለች።]<br />

ከቀድሞው ፌዴሬሽን በተለየ የሰራችሁት ነገር እንደሌለ<br />

ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />

ስ ፖ ር ት<br />

አቤል ዓለማየሁ<br />

የሚገልፁ አሉ። በሁለት ዓመት የስራ ጊዜያችሁ<br />

በዋናነት ‹‹ሰርተነዋል›› የምትሉት ተጨባጭ ነገር<br />

ምንድን ነው?<br />

የእግር ኳስ ችግራችንን በአንድ የስራ ዘመን<br />

(term) እንፈታዋለን ማለት አይቻልም። ቢያንስ<br />

የቢሮውን አደረጃጀት መለወጥ አለብን። እኛ ስንመጣ<br />

በጣም ጥቂት የነበረው የፅ/ቤት ሠራተኞች ቁጥር<br />

ከማደጉም በላይ ቢሮው በብቃት እየተደራጀ ነው።<br />

ራሱን የቻለ ቢሮ ያለው የዳኞች ኮሚቴ አልነበረንም፤<br />

አሁን ኖሮናል። ፊፋ ይህን አይቶ ‹‹በብዙ አፍሪካ<br />

አገሮች የሌለ ነው›› በማለት መሻሻላችንን አድንቋል።<br />

የቴክኒክ ዳይሬክተር ባይኖረንም በቴክኒክ<br />

ክፍል ውስጥ ብቁ ባለሙያዎችን ቀጥረናል። ስራዎችን<br />

በየዘርፉ በመስጠታችን ለክተን እንደሰጠነው፣ ለክተን<br />

መቀበል እንችላለን። ጉድለቶች ቢኖሩም እነዚህን<br />

እንደ ትልቅ እድገት አያቸዋለሁ።<br />

የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው በእግር ኳሱ ላይ<br />

በታሪክ የሚታወስ ስራ አከናውኖ የሚያልፍ<br />

ይመስልዎታል?<br />

ይህንን ካላደረግንማ መምጣትም<br />

አልነበረብንም። ወደ ፌዴሬሽኑ ስመጣ ብዙ ነገር<br />

ፈታለሁ ብዬ ሳይሆን ቢያንስ የተሻለ ነገር ከውናለሁ<br />

በሚል ነው። ይህ ክፍል [ቆይታ ያደረግንበት<br />

የፌዴሬሽኑ የዳኞች ኮሚቴ ቢሮ] በመኖሩ የዳኞችን<br />

የፋይል አደረጃጀት ችግር ፈትቼ አልፋለሁ። ‹‹ዳኛው<br />

ማን ነው? ምን ሰርቷል?›› የሚለውን መረጃ<br />

ከሰበሰብን ማንም መጥቶ ስለ ዳኛው በቂ ነገር ማግኘት<br />

ይችላል።<br />

የዳኞችን ሙሉ መረጃ የሚይዝ ፋይል<br />

ማደራጀታችሁ ጥሩ ስራ ቢሆንም በዳኞች ላይ ስራ<br />

ለመሰራቱ ዋና ማሳያ ይሆናል ብዬ አላምንም።<br />

መለኪያው የዳኞቹ ብቃት እንዲዳብር ምን ተሰራ<br />

አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />

‹‹ፌዴሬሽኑ ውስጥ የምሰራው<br />

ተመችቶኝ አይደለም››<br />

ወ/ሮ ጥሩወርቅ ብርሃኑ<br />

[የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን - የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል]<br />

ስለ ፌዴሬሽኑ ሁለት የስራ ዓመታት፣ በዳኝነት ዙሪያ ስለሚታዩ ችግሮችና በሴቶች እግር ኳስ ዙሪያ የሚነሱ ጉዳዮችን<br />

አስመልክቶ አቤል ዓለማየሁ ላቀረበላቸው ጥያቄዎች የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል<br />

እና የዳኞች ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት ወ/ሮ ጥሩወርቅ ብርሃኑ ግልፅነት የተሞላው ምላሽ ሰጥተዋል።<br />

አንድ ስራ ስትሰራ ግላዊ ሳይሆን ተቋማዊ በሆነ መልኩ ሊሆን<br />

ይገባል። እኔ የጀመርኩትን ሁሉ ጨርሼ ሄዳለሁ ማለት አይደለም።<br />

ሳንሰራው ለሌላው አስተላልፈን ለመሄድ ብቻም አንሰራም። ብዙ<br />

የሰራናቸው፣ ብዙ የቀሩ ነገሮች አሉ።<br />

የሚለው ነው።<br />

ለምሳሌ ኢንተርናሽናል አርቢትር ባምላክ<br />

ተሰማ ጥሩ ዳኛችን ነው እንበል። ዛሬ ሲያጫውት<br />

ምንም ገላጭ ሰነድ ከሌለው በቀጣይ በአመራርነት<br />

የሚመጣ ሰው ስለ እሱ በ<strong>አገር</strong>ም ሆነ በውጪ <strong>አገር</strong><br />

ስላጫወታቸው ጨዋታዎችና ሌሎች መረጃዎች<br />

ሊኖሩት አይችሉም። ታዲያ እንዴት የፋይል<br />

አደረጃጀት ዘዴ አያስፈልግም?<br />

ፋይል መደራጀቱንማ አከብራለሁ። ልል<br />

የፈለግኩት የተሻለ ለመሰራቱ ማሳያው የባምላክ<br />

የዳኝነት ብቃት መጎልበት እንጂ የፋይሉ መደራጀት<br />

አይደለም ለማለት ነው።<br />

ያነሳሁልህ እንደ ምሳሌ ነው። እንደ ተቋም<br />

መስራት ያለብን ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ ነገሮች<br />

ላይ ነው። ጨዋታን መሸከም የሚችል ብቃት<br />

ያለው ዳኛ በቁጥርም፣ በጥራትም ሳናወጣ በዘርፉ<br />

ለመስራታችን ማሳያ እንደማይሆን እናውቀዋለን።<br />

የፋይል አደረጃጀቱ ግን ስራ ለመሰራቱ አንዱ ማሳያ<br />

ሊሆን ይገባል።<br />

መስከረም 26 እና 27/ 2004 ዓ.ም. በግዮን<br />

ሆቴል በተደረገው የፌዴሬሽኑ የጠቅላላ ጉባዔ<br />

ስብሰባ ላይ ከእርስዎ በ2012 ኢንተርናሽናል ዳኞች<br />

እንደማይኖሩን ሲገለፅ ምናልባት ከንግግር ስህተት<br />

ይሁን ከእኛ የአረዳድ ችግር ባላውቅም በተለያዩ<br />

መገናኛ ብዙሐን ላይ ይሄው መረጃ ተላለፈ።<br />

[ሳምንት እኔም ከጉባዔው በላይ ማንን ልመን ብዬ<br />

ይሄንኑ መረጃ ገልጬ ነበር] ትንሽ የተዛባ ነገር<br />

ያለ መሰለኝ። የሚታወቅበት ጊዜ ገና በመሆኑ<br />

ኢንተርናሽናል ዳኛ ሆነው የሚቀጥሉ እንደሚኖሩ<br />

እየሰማሁ ነው።<br />

አንዳንድ ጊዜ ነገሮች ብድግ ይሉና በጣም<br />

ተጋነው ቀርበው፣ ሰዎችን ወደ ስህተት ይመራሉ።<br />

ካሉን 18 ኢንተርናሽናል ዳኞች ውስጥ [12 ወንድ<br />

እና 6 ሴት] አንዷ ሴት ረዳት ዳኛ እና ሦስት ወንድ<br />

ዋና ዳኞች በአካል ብቃት ፈተና ወድቀዋል። የወደቁት<br />

ማላዊ ለድጋሚ ፈተና ከኪሳቸው ገንዘብ አውጥተው<br />

ሄደው በድጋሚ ወድቀው መጡ። ይህ ማለት ካሉን<br />

ኢንተርናሽናል ዳኞች ውስጥ ቁጥራቸው ያንሳል<br />

እንጂ ምንም ኢንተርናሽናል ዳኛ የለንም ማለት<br />

ከእውነት መራቅ ነው። ካፍ ይቀበለው/አይቀበለው<br />

ባናውቅም 13 ኢንተርናሽናል ዳኖች [4 ዋና እና 9<br />

ረዳት] በ2012ም ሊኖረን ይችላል። በወጡት ቦታም<br />

ሌሎችን እንዲቀበሏቸው ጠይቀናል።<br />

ኢንተርናሽናል ባጅ ያገኙት ዳኞችም ቢሆኑ የውጪ<br />

ጨዋታዎች እንዲያጫውቱ ያን ያህል ሲጠሩ<br />

አይታይም። ትክክል ነው?<br />

በእኛ 2001 ዓ.ም. አንድ ወይም ሁለት<br />

ጨዋታ ብቻ ነው የተጠሩት፣ 2002 ላይ ትንሽ<br />

የተሻለ ነበር። 2003 በጣም የተሻለ ነበር፤ ከሴካፋ<br />

እስከ አፍሪካ ታላላቅ ውድድሮች አጫውተዋል።<br />

አንዳንድ ዳኞች ደግሞ ባጁን ይዘው አንድ ጨዋታ<br />

ሳይዳኙ የሚወርዱ አሉ።<br />

ባጁ የተሰጣቸው ብቁ ናቸው ተብለው ነውና ባጁን<br />

ከማግኘት ባለፈ ተመድበው እንዲሰሩ ከካፍ ጋር<br />

ግንኙነት ታደርጋላችሁ?<br />

በዚህ ረገድ የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ<br />

ሳህሉ ገ/ወልድ እንቅስቃሴ በጣም ብዙ ነው። በካፍ<br />

ስብሰባዎች ላይ ሲገኝ እና ኮሚሽነር ሆኖ በሄደበት<br />

ሁሉ የካፍ ሰዎችን ሲያገኝ የእኛ ዳኞች እንዲመደቡ<br />

ጥያቄዎችን ያቀርባል። እንደሚመደቡ ቃል እየገቡልን<br />

ነው። እንዲበረቱ እና የአካል ብቃታቸውን እንዲያሻሽሉ<br />

ይነግሩናል። ሊዲያ እና ትርሃስ በቅርቡ የመላው አፍሪካ<br />

ጨዋታዎችን ላይ መርተው መጥተዋል። በቅርቡም<br />

አራት ሴት ዳኞች ተመድበዋል። ወንዶቹም በቅርቡ<br />

ወጥተው እንዲያጫውቱ ጥሪ መጥቶላቸዋል።<br />

ሜዳ ላይ በግልፅ ብዙ ዳኞች ተሯሩጦ ማጫወት<br />

የሚያስችል የአካል ብቃት ችግር እንዳለባቸው<br />

እየታየ ነው። የፊሽካ ድምጾች በርቀት እየተሰሙ<br />

ነው። ችግሮቹን ለመቅረፍ ምን እያሰባችሁ ነው?<br />

ችግሩ መኖሩንስ ታምናላችሁ?<br />

እሱማ ታየ። ዳኞች ተፈትነው ሲወድቁብህ<br />

ችግሩ መኖሩን ትረዳለህ። ችግሩን ለመፍታት<br />

እንደ ዳኞች ኮሚቴ ማድረግ ያለብን የአካል ብቃት<br />

አሰልጣኞችን መጨመር ነው። በካፍ ሁለት<br />

አሰልጣኞች (ቸርነት አሰፋ እና ኃይለመላክ ተሰማ)<br />

ሰልጥነው መጥተዋል።<br />

ክልል ላይ ተፈትነው የሚመጡ ዳኞች ፈተና<br />

ምናልባት አጥጋቢ ላይሆን ስለሚችል ወደ ውድድር<br />

ከማስገባታችን በፊት እንፈትናቸዋለን። ይህን ፈተና<br />

ማለፍ ካልቻለ አይዳኝም። በዓመት በፊት አንድ የአካል<br />

ብቃት ፈተና ያለፈ ዳኛ ዓመቱን ሙሉ ይዳኝ ነበር።<br />

አሁን ግን ፈተናውን በዓመት አራት ጊዜ እያደረግን


አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />

}SdeK¨< Ÿ}c\ ð×” ¾h¨` ¨

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!