በኢህአዴግ ራዳር ስር የተንበረከከች አገር
በኢህአዴግ ራዳር ስር የተንበረከከች አገር
በኢህአዴግ ራዳር ስር የተንበረከከች አገር
Create successful ePaper yourself
Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.
መንግሥት በዜጎቹ ላይ<br />
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />
ለምን ምቀኛ ይሆናል?<br />
በግርማ ሰይፉ<br />
በ ገፅ 14<br />
4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18 2004 ዋጋ 7፡00 ብር<br />
ከህዝብ ጥቅም ይልቅ<br />
የራስን ፖለቲካዊ ምህዳር<br />
ማስጠበቅ<br />
<strong>በኢህአዴግ</strong> <strong>ራዳር</strong> <strong>ስር</strong> <strong>የተንበረከከች</strong> <strong>አገር</strong><br />
በ ገፅ 4<br />
<strong>ስር</strong> <strong>ራዳር</strong> <strong>በኢህአዴግ</strong><br />
ካሳ ሳይሰጥ እንዳልቀረ ተጠቆመ<br />
በሱራፍኤል ግርማ<br />
የቀድሞዋ ሶማሊያ አካል በነበረችው ፑንትላንድ ውስጥ ሞት ተፈርዶበት<br />
ዕለተ-ሞቱን ሲጠብቅ የነበረውን ኢትዮጵያዊ፤ ድምፃዊ ቴዎድሮስ<br />
ካሳሁን /ቴዲ አፍሮ/ ሳይታደገው እንዳልቀረ ለአርቲስቱ ቅርበት ያላቸው<br />
የአውራምባ ታይምስ ምንጮች ገለፁ።<br />
በውስጥ ገፅ<br />
የአቶ መለስ የአደባባይ ምስክርነት<br />
ከዳኝነት ነፃነት አንፃር<br />
ከምንጮቻችን ባገኘነው መረጃ መሠረት፣ በሰው መግደል<br />
ወንጀል ተከሶ በሞት እንዲቀጣ በጎሳ መሪዎች ውሳኔ የተላለፈበት<br />
ኢትዮጵያዊው አስመሮም ኃይለሥላሴ ላጠፋው ነፍስ ካሳ 700<br />
ሺህ ብር እስከ ትናንት ዓርብ ድረስ መክፈል ከቻለ በነፃ<br />
እንደሚወጣ የሚያመለክት ዜና በሪፖርተር ጋዜጣ ላይ<br />
በ ገፅ 19<br />
በውስጥ ገፅ<br />
ማፊያ<br />
በ ገፅ 3<br />
“ሽብርተኝነት ለኢትዮጵያ ባዕድ የሆነ ነገር ነው<br />
…በዚህ ሰበብ ሽብርተኝነትን እንዳናስተምር እሰጋለሁ”<br />
አቶ መለስ ሲናገሩ አቃቤ ሕጎች፣ ዳኞችና ፖሊሶች ይኼንን<br />
ተከትለው ይሄዳሉ ብለው እንኳን አያስቡም<br />
ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም<br />
‹‹ንቦች አሜሪካ ውስጥ አስቸገሩ››<br />
ሬዲዮ ፋና<br />
‹‹ፋና ሆይ ንቦች ያላስቸገሩበት የት አይታችኋል?››<br />
የታች ሰፈር ልጆች<br />
በዳዊት ከበደ<br />
ቴዲ አፍሮ በሶማሊያ ሞት ለተፈረደበት ኢትዮጵያዊ<br />
ባሕርያቱና ከዴሞክራሲ<br />
እጦት ጋር ያለው ቁርኝት<br />
ሲፒጄ፣ ‘በጋዜጠኞች<br />
ላይ የሽብርተኝነት<br />
ውንጀላው ተጠናክሮ<br />
ቀጥሏል’ ሲል ገለጸ<br />
ባለፈው ሳምንት፣ ጠ/ሚኒስትር<br />
መለስ ዜናዊ በአገሪቱ ውስጥ ያሉትን ጋዜጠኞች<br />
በ“ተላላኪ መልዕክተኝነት” እና “ሽብርተኝነት”<br />
መወንጀላቸውንና አንድ የመንግሥት ጋዜጣ ደግሞ<br />
የነፃው ፕሬስ ኤዲተርን ከሽብርተኞች ጋር ግንኙነት<br />
አለው በማለት የፀጥታ ኃይሎች በጋዜጠኛው ላይ<br />
“እርምጃ እንዲወስዱበት” እንደጠየቀ በማስታወስ፣<br />
በግሉ ፕሬስ ላይ እየተደረገ ያለውን የማሸማቀቅና<br />
የማስፈራራት ዘመቻውን የጋዜጠኞች መብቶች<br />
ተሟጋቹ አውግዟል።<br />
ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ብዙዎቹ<br />
በኢትዮጵያ ያሉ ጋዜጠኞች ከ“ሽብርተኛ”<br />
ቡድኖች ጋር የሚሰሩ “ተላላኪ-መልዕክተኞች”<br />
እንደሆኑና የታሰሩ ጋዜጠኞች ከሽብር ድርጊቶች<br />
ጋር የሚያስተሳስራቸው ቁርኝት እንዳለ የሚያሳይ<br />
ማስረጃ መንግስታቸው ያለው መሆኑን፣ ሌሎች<br />
በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ጋዜጠኞችም ከሽብርተኞች<br />
ጋር ትስ<strong>ስር</strong> እንዳላቸው ባለፈው ሀሙስ በፓርላማ<br />
ባደረጉት ንግግር መጠቆማቸውን ሲፒጄ<br />
ገልጿል።<br />
ከሰኔ ወር ጀምሮ የመንግሥት<br />
ባለሥልጣናት ስድስት የነፃው ፕሬስ ጋዜጠኞችን<br />
በሽብርተኝነት ክስ ወንጅለው ማሰራቸውን<br />
ያወሳው ሲፒጄ፣ የአውራምባ ታይምስ የቀድሞ<br />
ምክትል ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ፣<br />
የፍትህ ጋዜጣ አምደኛ ርዕዮት ዓለሙ፣ ጋዜጠኛ<br />
እስክንድር ነጋ እና ስለሺ ሐጎስ፣ እንዲሁም ጆሃን<br />
ፐርሰንና ማርቲን ሽብዬ የተባሉ ሁለት ስዊድናውያን<br />
ጋዜጠኞች በሽብርተኝነት ተጠርጥረው በእ<strong>ስር</strong> ላይ<br />
እንደሚገኙ አስታውሷል።<br />
የኢትዮጵያ የግል ፕሬሶችን “ጋጠ-<br />
ወጦች” ሲሉ የገለፁት ጠ/ሚኒስትር መለስ<br />
እነዚህን የግል ፕሬሶች ሞያቸውን ያልተረዱ ሲሉ<br />
በውስጥ ገፅ<br />
በ ገፅ 16<br />
በ ገፅ 19<br />
መቆሚያ ያጣው የዋጋ ግሽበት<br />
ገንዘብ ያለገደብ የሚጨመርበት ኢኮኖሚ ለጊዜው ያደገ<br />
እንደሚመስል ፊኛ ነው ‹‹ፊኛ ውስጥ አየር ሲጨመር<br />
የፊኛው መጠን ይተልቃል፤ አየሩ ፊኛው ከሚችለው በላይ<br />
ሲሆን ግን ፊኛው መፈንዳቱ አይቀርም››<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ
2<br />
የካቲት 2000 ዓ.ም<br />
ተመሠረተ<br />
አውራምባ ታይምስ፡- በብሉ<br />
ኤርዝ ጀነራል ቢዝነስ ኃላ/የተ/<br />
የግል/ማህበር <strong>ስር</strong> የሚታተም፤<br />
በፖለቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ<br />
የሚያተኩር፤ በንግድ ሚኒስቴር<br />
በቁጥር 020/2/6572/2001<br />
የተመዘገበ ሳምንታዊ ጋዜጣ ነው፡፡<br />
T’@Í=”Ó ›?Ç=}`<br />
Ç©ƒ ŸuÅ<br />
ª“ ›²ÒÏ<br />
õì
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004 3<br />
ምን ነካቸው?›› ፤ ‹‹ዛሬ<br />
ላይ እንዲህ መቆጣት ለምን<br />
‹‹ሰውዬው<br />
አስፈለገ?››፣ ‹‹ለምንስ እንዲህ<br />
አመረሩ›› እነዚህንና ሌሎች መሰል<br />
አስተያየቶች አቶ መለስ ዜናዊ ባለፈው<br />
ሀሙስ ጥቅምት 9 ቀን 20004 ዓ.ም<br />
በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ተገኝተው<br />
ያቀረቡትን ማስጠንቀቂያ አዘል ንግግር<br />
ተከትሎ በአዲስ አበባ የተለያዩ ስፍራዎች<br />
(ለፖለቲካዊ ጉዳዮች ብዙ ትኩረት<br />
በማይሰጡ ዜጎችም ጭምር) ሲሰነዘሩ<br />
የሰነበቱ የግርምት አስተያየቶች ናቸው፡፡<br />
የ1997ቱን ምርጫ ተከትሎ በአገሪቱ<br />
ፖለቲካዊ ቀውስ በተፈጠረበት ወቅት<br />
አቶ መለስ ከሰነዘሯቸው መሰል<br />
ማስጠንቀቂያዎች ጋር አቆራኝተው<br />
ለማነጻጸር የተገደዱ ወገኖችም አልጠፉም፡<br />
፡ ቀላል የማይባል ቁጥር ያላቸው<br />
ወገኖችም ማስፈራሪያው አነጣጥሮባቸዋል<br />
ያሏቸውን የአውራምባ ታይምስና ፍትህ<br />
ጋዜጣ አዘጋጆችን ሲያፅናኑና አማራጭ<br />
ያሉትን ምክርና የመፍትሄ አስተያየት<br />
ሲሰነዝሩ ተስተውለዋል፡፡<br />
ህገ መንግስቱን ማክበር<br />
ጥፋት ነውን?<br />
ባለፈው ሀሙስ ከአንዱ በስተቀር<br />
የኢህአዴግ አባላት የሆኑ ‹‹ተመራጮች››<br />
ብቻ የተሰባሰቡበት የኢትዮጵያ<br />
ፓርላማ አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ<br />
የሚያቀርቧቸው ጥያቄዎች እጅግ አሰልቺና<br />
ተመሳሳይነት ያላቸው አይነት ነበሩ። ወደ<br />
መጨረሻ አካባቢ ግን ወ/ሮ አታለል መላኩ<br />
(እሳቸውም ገዢውን ግንባር የሚወክሉ<br />
የም/ቤቱ አባል) ያቀረቡት አቤቱታ አዘል<br />
ጥያቄ ግን የጉዳዩ ባለቤቶችን ብቻ ሳይሆን<br />
የብዙዎችን ትኩረት የሚስብ ነበር።<br />
‹‹በሽብር ተጠርጥረው የታሰሩ ሰዎች<br />
ጉዳይ በፍርድ ቤት ተይዞ ሳለ አንዳንድ<br />
የግሉ ፕሬስ ተቋማት የሰዎቹን ነፃ መሆን<br />
እየመሰከሩ ነው፡፡ የጋዜጦቹ ፍላጎትና<br />
የአቶ መለስ የአደባባይ ምስክርነት<br />
ከዳኝነት ነፃነት አንፃር<br />
በዳዊት ከበደ<br />
አላማ ግልፅ ሆኖ ሳለ መንግሥት ክስ<br />
አለመጀመሩ ለዚህ ችግር አስተዋፅዖ<br />
አበርክቷል።›› ነበር ያሉት የፓርላማ<br />
አባሏ፡፡ በእኒህ የተከበሩ የፓርላማ አባል<br />
የተሰነዘረውና ከላይ ሰረዝ የጨመርኩበትን<br />
‹‹አላማችንና ፍላጎታችን›› ምን እንደሆነ<br />
በድምዳሜ የተጠቀሰው ጥንቆላ ቢብራራ<br />
ፍላጎቴ ቢሆንም እሱን ወደ ጎን ትቼ<br />
ተጠርጥሮ በሕግ ጥላ <strong>ስር</strong> የሚገኝ<br />
ሰው ከፍርድ በፊት ‹‹ነፃ ነው›› ወይስ<br />
‹‹ወንጀለኛ›› በሚለው ጉዳይ ላይ ሕገ-<br />
መንግስቱ የሚለውን ላስታውሳችሁ።<br />
በሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 20 ንዑስ ቁጥር<br />
3 ላይ ተከሳሾች ‹‹በፍርድ ሂደት ባሉበት<br />
ጊዜ በተከሰሱበት ወንጀል እንደጥፋተኛ<br />
ያለመቆጠር መብት አላቸው›› ይላል።<br />
ከዚህ አንጻር ይህንን ሕገ-መንግስታዊ<br />
ድንጋጌ አክብሮ ‹‹ነጻ ናቸው›› ብሎ<br />
የሚያምን ግለሰብ ይሁን ተቋም<br />
‹‹ጋጠወጥ›› የሚባልበት ምክንያት<br />
ምንድነው?<br />
ህጉ በተጨባጭ ከእንግሊዝና ከአሜሪካ የተቀዳ ከሆነ፤ ኢትዮጵያ ሲደርስ ለምን የተቃዋሚዎችና የሚዲያዎች ስጋት ሆነ? ለምንድነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ካሜሮን በእንግሊዝ ፓርላማ<br />
ቀርበው በሌቨር ፓርቲ አመራሮች ላይ ሲዝቱ አሊያም ደግሞ የዘ-ጋርዲያን ጋዜጣ አዘጋጆችን ‹‹ጋጠወጥ›› ሲሉ የማንመለከታቸው? ለምንስ ነው ፕሬዚዳንት ኦባማ በኮንግረስ ተገኝተው<br />
የሪፐብሊካን አመራሮችን በሽብርተኝነት የማይወነጅሉት? ለምንስ ነው የኒው ዮርክ ታይምስ ኤዲተሮችን ‹‹የጋዜጠኝነት ሀሁ የማይገባቸው›› ብለው ሲዘልፉ የማንመለከታቸው?<br />
አቶ መለስ ሕገ-መንግስቱን ስለማክበርና<br />
ስለማስከበር ደጋግመው እየነገሩን<br />
ነገር ግን ከላይ የጠቀስነውን ሕገ-<br />
መንግስታዊ ድንጋጌ በመጣስ ተቃራኒውን<br />
እንድንመሰክር ነው እየወተወቱን ያሉት፡<br />
፡ እንኳን እኛ ይቅርና አንድን ጉዳይ<br />
የሚይዙ ዳኞች እንኳን በተቻለ መጠን<br />
የተከሳሽን የንጹህነት መርህ ግምት ውስጥ<br />
በማስገባት ሊያስቀጣ የሚችል ተጨባጭ<br />
ማስረጃ በአቃቤ ህጉ በኩል አሳማኝ በሆነ<br />
መልኩ እንዲቀርብ ነው የሚጫኑት፡፡ ይህ<br />
የሆነበት ምክንያት አንድም አቃቤ ህግ<br />
ግዙፍ መንግስታዊ አካል እንደመሆኑ<br />
ከተከሳሽ (ግለሰብ) ጋር ሲነጻጸር የአቅም<br />
ውስንነት ግምት ውስጥ ስለሚገባ፤<br />
ሁለተኛ ደግሞ ተከሳሹ እስኪፈረድበት<br />
ድረስ ነጻ ነው ተብሎ ስለሚታሰብ ‹‹ነጻ››<br />
የተባለው ግለሰብ ‹‹ወንጀለኛ ነው›› ብሎ<br />
ለመደምደም ከፍ ያለው የቤት ስራ የአቃቤ<br />
ህጉ በመሆኑ ነው፡፡ በተለይ ተከሳሹ<br />
ጥፋተኛ ከተባለ በኋላ የሚወሰንበት<br />
ቅጣት በግለሰቡ ሁለንተናዊ ነጻነት ላይ<br />
ሊያስከትል የሚችለውን ጉዳት ግምት<br />
ውስጥ በማስገባት ተከሳሹ በተጨባጭ<br />
ወንጀሉን መፈጸሙና አለመፈጸሙ<br />
ብዥታ በማይፈጥር መልኩ መረጋገጥ<br />
ስላለበትም ነው፡፡ ታዲያ እነዚህን<br />
ከመሳሰሉ አጠቃላይ ድንጋጌዎችና ስነ<br />
አመክንዮ አንጻር የመንግስትን የመጨረሻ<br />
ስልጣን ከጨበጡት አቶ መለስ አንደበት<br />
‹‹ከበቂ በላይ ማስረጃ አለን፤ ሰዎቹ<br />
ወንጀለኞች ናቸው›› የሚል የአደባባይ<br />
ምስክርነት ሲቀርብ በዳኝነት ሂደቱ ላይ<br />
የጎላ ተጽእኖ የማሳረፍ አቅም የሚኖረው<br />
ማነው? እኛ ወይስ አቶ መለስ? ሕገ-<br />
መንግስቱን የማክበርና የማስከበር ሂሳብ<br />
እናወራርድ ከተባለ ስህተቱ ጨርሶ የእኛ<br />
አይደለም፡፡ ህገ መንግስቱን ካከበርነው<br />
በደንብ እናክብረው እንጂ!<br />
የእኛ ጥፋት<br />
ለመሆኑ ‹‹ተጠርጥረው በህግ ጥላ <strong>ስር</strong><br />
ያሉ ሰዎች “ድብደባ ተፈፅሞብናል”<br />
እያሉ ነው፣ ቤተሰቦቻቸው እንዲጎበኟቸው<br />
አልተፈቀደም›› ይህ ከሕገመንግስቱ ጋር<br />
አብሮ አይሄድም፡፡ ህግን የማስከበር<br />
ኃላፊነት በተጣለባቸው ሰዎች ህገ<br />
መንግስቱ መደፍጠጥ የለበትም›› ብሎ<br />
መጠየቅ “በቅድመ ሁኔታ የተሰጠን<br />
ይቅርታ ሊያሰርዝ የሚችል ወንጀል”<br />
የሚሆነው በምን አይነት የኦሪት ህግ<br />
ነው? በሕግ ጥበቃ <strong>ስር</strong> ያሉ ሰዎች በሕገ-<br />
መግስቱ መሠረት በተፋጠነ ሁኔታ ፍ/<br />
ቤት ይቅረቡ ብሎ መጠየቅስ በ”ጋጠ-<br />
ወጥነት” የሚያስፈረጀው በምን አይነት<br />
ስነ-አመክንዮ ነው? እኛና ሚዲያዎቻችን<br />
እንደሚሉት ሁሉ እናንተም<br />
ወንጀለኛነታቸውን በአደባባይ መስክሩ<br />
አለበለዚያ “የጋዜጠኝነት ሀሁ አታውቁም”<br />
የምንባለውስ ለምንድነው? የጸረ ሽብር<br />
አዋጁ ለሰፊ ትርጓሜ እጅግ የተጋለጠ<br />
በመሆኑ ነው ለዚህ ሁሉ መቅሰፍት<br />
ምክንያት እየሆነ ያለው፤ እናም አዋጁ<br />
በድጋሚ ይሻሻል ብሎ ሀሳብን መግለጽ<br />
‹‹በሽብርተኞች መልእክተኛነት››<br />
የሚያስፈርጀው ብሎም ሽብርተኝነትን<br />
እንደማበረታታትና የሚቆጠረው<br />
ለምንድነው?<br />
‹‹ቃል በቃል ከውጭ<br />
የተቀዳው›› ሕግ<br />
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የፀረ-ሽብርተኝነት<br />
ሕጉ ‹‹እንከን የለሽ›› መሆኑን ለማስረዳት<br />
‹‹ቃል በቃል ከምዕራባዊያን የተቀዳ››<br />
መሆኑን ነግረውናል። የምንኖርበትን<br />
<strong>አገር</strong> ተጨባጭ ሁኔታ ግምት ውስጥ<br />
ሳይገባ አንድ ህግ እንዴት ቃል በቃል<br />
ከውጭ ይኮረጃል፡፡ ሀሳቤን ይበልጽ<br />
ግልጽ ለማድረግ እዚህ ላይ አንድ አብነት<br />
መጥቀሱ ተገቢ ይመስለኛል፡፡ ሰሞኑን<br />
ስለተጨማሪ እሴት ታክስ አሰራር<br />
ለንግዱ ማህበረሰብ ግንዛቤ ለማስጨበጥ<br />
በተጠራ የግንዛቤ ማስጨበጫ ወርክሾፕ<br />
ላይ አንድ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን<br />
ከፍተኛ የሥራ ኃላፊ የተናገሩት ነው፡፡<br />
ሰውዬው እንደገለፁት ኬንያ ተግባራዊ<br />
ያደረገችው የተጨማሪ እሴት ታክስ<br />
ሕግ ቃል-በቃል ከእንግሊዝ የታቀዳ ነው<br />
አሉ። እናም እንግሊዝ የበረዶ ሸርተቴ<br />
የሚያዘወትሩ ዜጎቿን ለማበረታታት<br />
ስትል ‹‹የበረዶ ማንሸራተቻ መሳሪያዎች<br />
ታክስ ሊከፈልባቸው አይገባም›› የሚል<br />
ድንጋጌ በታክስ ሕጓ ላይ አስፍራለች።<br />
በአገሯ ምንም አይነት በረዶ የሌላት<br />
ኬኒያ ሕጉን ቃል-በቃል ከእንግሊዝ<br />
ቀድታ ተግባራዊ ማድረጓን በመጥቀስ<br />
ኃላፊው ተሳታፊውን ፈገግ አሰኙት።<br />
ሰውየው አያይዘውም ኢትዮጵያ<br />
ግን የታክስ ህጉን ከሌሎች አገሮች<br />
ብትኮርጅም ከአገሪቱ ነባራዊ ሁኔታዎች<br />
ጋር በማዛመድ ተግባራዊ አድርጋዋለች<br />
አሉ። ታዲያ የጸረ ሽብር ህጉስ<br />
ከአገራችን ነባራዊ ሁኔታ አንጻር ለምን<br />
አልተቃኘም? እሺ እሱም ይቅር ህጉ<br />
በተጨባጭ ከእንግሊዝና ከአሜሪካ<br />
የተቀዳ ከሆነ፤ ኢትዮጵያ ሲደርስ ለምን<br />
የተቃዋሚዎችና የሚዲያዎች ስጋት<br />
ሆነ? ለምንድነው ጠ/ቅላይ ሚኒስትር<br />
ዴቪድ ካሜሮን በእንግሊዝ ፓርላማ<br />
ቀርበው በሌቨር ፓርቲ አመራሮች ላይ<br />
ሲዝቱ አሊያም ደግሞ የዘ-ጋርዲያን<br />
ጋዜጣ አዘጋጆችን ‹‹ጋጠወጥ››<br />
ሲሉ የማንመለከታቸው? ለምንስ<br />
ነው ፕሬዚዳንት ኦባማ በኮንግረስ<br />
ተገኝተው የሪፐብሊካን አመራሮችን<br />
በሽብርተኝነት የማይወነጅሉት? ለምንስ<br />
ነው የኒው ዮርክ ታይምስ ኤዲተሮችን<br />
‹‹የጋዜጠኝነት ሀሁ የማይገባቸው››<br />
ብለው ሲዘልፉ የማንመለከታቸው?<br />
አዎ! ምክንያቱ በጣም ግልጽ ነው፤<br />
የአሜሪካም ሆነ እንግሊዝ ጠላቶች<br />
ዜጎቻቸውና ተቋሞቻቸው አይደሉም፡፡<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ
4<br />
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />
<strong>በኢህአዴግ</strong> <strong>ራዳር</strong> <strong>ስር</strong> <strong>የተንበረከከች</strong> <strong>አገር</strong><br />
“<br />
. . . ደርግ ሲገለገልበት<br />
የነበረውን የአዲስ አበባ<br />
የሬዲዮ ጣቢያ ለሰፊው<br />
ህዝብ ጥቅም ሲል<br />
ተቆጣጥሮታል። ግንቦት<br />
20/1983 ዓ.ም”። ከፍተኛ<br />
የህይወትና የአካል<br />
መስዋዕትነት የተከፈለበት<br />
እልህ አስጨራሽ የ17<br />
ዓመታት የትግል ምዕራፍ<br />
ተደምድሞ ዴሞክራሲያዊ<br />
<strong>ስር</strong>ዓት መስፈኑን<br />
የሚገልፅ ዲስኩር መሆኑ<br />
ግልጽ ነውና።<br />
በተለያዩ ፖለቲካዊ ተሳትፏቸውና<br />
ጽሑፎቻቸው የሚታወቁት ፕሮፌሰር<br />
መስፍን ወ/ማርያም፣ “ኢትዮጵያ ከዬት<br />
ወዴት?” በሚለው መጽሐፋቸው ላይ<br />
የሚከተለውን ነጥብ አስፍረዋል፡- “ . .<br />
. ሥርዓት ሥርዓትን ይወልዳል። የአፄ<br />
ኃይለሥላሴ ሥርዓት የደርግን ሥርዓት<br />
ወለደ፤ የደርግ ሥርዓት በበኩሉ አሁን<br />
በኤርትራ እና በቀሩት የኢትዮጵያ ክፍሎች<br />
ያሉትን ሥርዓቶች ወለደ። . . . ”<br />
የደርግ መንግሥት በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ<br />
ይፈፅም የነበረው ግፍ እንዲሁም ህዝቡ<br />
ያሰማው የነበረው ብሶት ወደ ትግል<br />
እንዳስገባው በተደጋጋሚ የሚናገረውና<br />
የደርግ ሥርዓት የወለደው ኢህአዴግ፣ ለ17<br />
ዓመታት በደርግ <strong>ራዳር</strong> ውስጥ የነበረችውን<br />
ኢትዮጵያን በገዛ ራዳሩ ውስጥ ካስገባት 20<br />
ዓመታት ተቆጥረዋል።<br />
ኢህአዴግ፣ ግንቦት 20/1983 ሀገሪቱን<br />
‘ሙሉ በሙሉ’ ይቆጣጠር እንጂ፣ ቀስ<br />
በቀስ በተለያዩ ዓመተ-ምህረቶች ጥቂት<br />
የማይባሉ የሀገሪቱ ክፋዮች ከቁጥጥሩ ውጭ<br />
መሆናቸውን መረጃዎች እያመላከቱ ነው።<br />
“ ... ለሰፈው ህዝብ ጥቅም ... ?”<br />
“ ... ለሰፊው ህዝብ ጥቅም ... ” ይህቺ<br />
ሐረግ ለኢትዮጵያ ህዝብ አዲስ አይደለችም።<br />
ከግንቦት 20/1983 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ዛሬ<br />
ድረስ ከአ<strong>ስር</strong> ዲጂት በላይ ለሚሆን ጊዜ<br />
የተደመጠች እና ወደፊትም በአሁኑ ሰዓት<br />
በሥልጣን ላይ የሚገኘው መንግሥት<br />
እስካለ ድረስ የምትደመጥ ሐረግ ነች።<br />
በአባባሏ ላይ ማንም ሰው ቅሬታ<br />
የለውም። ብዙዎችን ከነልዩነታቸው<br />
የሚያስማማው ጉዳይም፣ አንድ<br />
መንግሥት ለሰፊው ህዝብ ጥቅም<br />
መስራት እና መቆም እንዳለበት<br />
ነው። ‹‹ይሁን እንጂ…›› ይላሉ<br />
የኢትዮጵያ መንግስት ሰፊውን<br />
ህዝብ ተጠቃሚ የሚያደርግ<br />
ሥራ እየሰራ አለመሆኑን<br />
የሚያምኑ ወገኖች። ‹‹…<br />
አሁን ባለው ወቅታዊ<br />
ሁኔታ ከሰፊው ህዝብ<br />
ይልቅ ጥቂቶች<br />
እንደ ሮኬት<br />
በመወንጨፍ<br />
ተ ዓ ማ ኒ ነ ት<br />
የጎደለው እድገት<br />
እያሳዩ ነው›› በማለት<br />
የሰፊው ህዝብ ፅንሰ ሀሳብ<br />
ግቡን አለመምታቱን በመጠቆም<br />
ይከራከራሉ።<br />
እስካሁን ድረስ <strong>በኢህአዴግ</strong> ታሪክ፣<br />
የኢትዮጵያ ህዝብ ከጫፍ እስከ<br />
ጫፍ እስከ ልዩነቱ ከመንግሥት ጎን<br />
የቆመው፣ ለሰፊው ህዝብ ከፍተኛ ጥቅም<br />
ይሰጣል ብሎ ባመነበት አንድ ጉዳይ ነው።<br />
እሱም ከደሙና ከታሪኩ ጋር የተሳሰረው<br />
የአባይ ጉዳይ ሆኖበት ነው። እንደውም፣<br />
መንግሥት፣ በሀገሪቱ ውስጥ ሰፊውን<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
ፊ ቸ ር<br />
ከህዝብ ጥቅም ይልቅ የራስን ፖለቲካዊ ምህዳር ማስጠበቅ<br />
<strong>አገር</strong><br />
<strong>የተንበረከከች</strong> <strong>ስር</strong> <strong>ራዳር</strong> <strong>በኢህአዴግ</strong><br />
በታዲዎስ ጌታሁን<br />
ከጥቂት ጊዜያት ወዲህ፣ መንግሥት ሰፋፊ መሬቶችን ለውጭ ባለኃብቶች በወረደ ወይም<br />
አንድ ኪሎ ሙዝ በማይገዛ (በአሁን ሰዓት አንድ ኪሎ ሙዝ 12 ብር ሲሆን አንድ<br />
ሄክታር ድንግል መሬት ደግሞ እስከ አ<strong>ስር</strong> ብር ይሸጣል) ዋጋ መሸጡ እያስገረመ ሳለ፣<br />
ባለኃብቶቹ፣ የሀገራቸውን ሥራ አጦች በአውሮፕላን ጭነው አምጥተው በተረከቡት<br />
መሬት ላይ እንዲሰሩ ማድረጋቸው ብዙዎችን አስቆጥቷል።<br />
ህዝብ የሚያስቆጣ መሠረታዊ ችግሮች<br />
መኖራቸው ስላስፈራው እና የአረብ ሀገራት<br />
አብዮት ወደ ኢትዮጵያ እንደይመጣ<br />
ስለሰጋ ነው አባይን ለመገደብ የተነሳው<br />
ብለው ያምናሉ። ምንም እንኳን ጠቅላይ<br />
ሚኒስትር መለስ ዜናዊ፣ መንግሥታቸውን<br />
ሥጋት ላይ የሚጥል ችግር በኢትዮጵያ<br />
እንደሌለና ሰፊው ህዝብ ከመንግሥት ‹ሰፊ<br />
ጥቅም› በማግኘቱ የ5 ዓመት ኮንትራት<br />
እንደሰጣቸው ተናግረው የነበረ ቢሆንም።<br />
ኑሮ፣ በተዓምር ወይስ በተዓምራዊ ዕድገት?<br />
የሁለተኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሦስተኛ<br />
መደበኛ ስብሰባውን ጥቅምት 9 ቀን<br />
2004 ዓ.ም ያከናወነው የኢፌዴሪ የህዝብ<br />
ተወካዮች ም/ቤት፣ ከወትሮው ለየት ያለ<br />
መንፈስ እና ንግግር ጎብኝቶት ነበር።<br />
የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ<br />
መስከረም 29 ቀን 2004 ዓ.ም ባደረጉት<br />
የምክር ቤት መክፈቻ ንግግር ላይ በሚቀርቡ<br />
የማሻሻያ ሞሽኖች ላይ የመንግሥታቸውን<br />
አቋም ለማስደመጥ በምክር ቤቱ የተገኙት<br />
ጠ/ሚኒስትር መለስ፣ እንደ ከዚህ ቀደሙ<br />
ሁ ሉ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ<br />
ሽቅብ ‘መወንጨፉን’ በ‘ተዓምር’ መስለው<br />
ተናግረዋል።<br />
በምክር ቤቱ ብቸኛው የመድረክ ተወካይ<br />
የሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ፣ “ሀገራችን<br />
ያስመዘገበችው እድገት የትክክለኛ<br />
ፖሊሲዎች ውጤት ነው” የሚለው ዓረፍተ-<br />
ነገር ከኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ጋር<br />
የማይመሳሰል መሆኑን ቢናገሩም፣ በአቶ<br />
መለስ ዜናዊ ተቀባይነት አላገኙም።<br />
ጠ/ሚኒስትሩ፣ የሞተን ሰው ነፍስ ዘርቶ<br />
ከመቃብር የማስነሳት ያህል ‘ተዓምራዊ’<br />
ሲሉ የገለፁትን የኢኮኖሚ ዕድገት የምጣኔ<br />
ኃብት ባለሙያ የሆኑት አቶ ተመስገን<br />
ዘውዴ፣ ከህንፃ ግንባታዎች በስተቀር<br />
በሌሎች ሴክተሮች ላይ የታየ ጉልህ<br />
ለውጥ እንደሌለ በማስረገጥ ተዓምራዊውን<br />
እድገት ዋጋ ያሳጡታል። ቀጠል ያደርጉና<br />
“በእርግጥም የህንፃዎችንና የቪላ ቤቶችን<br />
በብዛት መገንባት ለኢኮኖሚ እድገትና<br />
ለህዝቡ ኑሮ መሻሻል እንደ ማሳያ<br />
ሊያስቀምጡ የሚሞክሩ የኢህአዴግ ወገኖች<br />
አይጠፉም። አነዚህ ወገኖች ግን አዲስ አበባ<br />
ከተማ ውስጥ ያለው የህንፃዎች ግንባታ<br />
በአጠቃላይ አገሪቱ ውስጥ ያለውን የኢኮኖሚ<br />
እንቅስቃሴ ሊወክል ይችላልንን? የሚለውን<br />
ጥያቄ መመለስ የሚችሉ አይመስለኝም”<br />
በማለት የህንፃ ግንባታ አንድ ራሱን የቻለ<br />
ነጠላ ዘርፍ መሆኑን ያስረዳሉ።<br />
የኢፌዴሪ የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ<br />
የባለፈውን ወር የ<strong>አገር</strong> አቀፍ እና የክልሎችን<br />
የሸማቾች ዋጋ መመዘኛ ኢንዴክሶችን<br />
ባወጣበት ሪፖርት ላይ የምግብ ዋጋ<br />
ግሽበት 51.3 በመቶ መድረሱን<br />
ገልጿል። እንዲሁም፣ በመስከረም<br />
ወር 2004 ዓ.ም የተመዘገበው የ12<br />
ወራት ተንከባላይ አማካኝ አገራዊ<br />
አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ካለፈው<br />
ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር<br />
በ26.6 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን<br />
ሪፖርቱ ጨምሮ ገልጿል።<br />
የዋጋ ግሽበት እና የኑሮ<br />
ውድነት ጣራ መንካታቸው<br />
ለአቶ መለስ የሚያስገርም<br />
ጉዳይ አልሆነም። ‹‹የኑሮ<br />
ውድነትም ሆነ የዋጋ<br />
ግሽበት እያለ<br />
ኢኮኖሚ ማደግ ይችላል፤ እነዚህ ሁኔታዎች<br />
ባሉበት ሁኔታ ኢኮኖሚ አያድግም ማለት<br />
የኢኮኖሚን ሀሁ አለመገንዘብ ነው››<br />
በማለት ብዙ ሚሊዮን ህዝብን ግራ እያጋባና<br />
ከዕለት ዕለት ኑሮውን እያመሳቀለ ያለውን<br />
የኑሮ ውድነት ‘ቀላል’ አድርገው ለማየት<br />
ሞክረዋል።<br />
ይህ ዓይነቱ (51.3 በመቶ) የዋጋ ግሽበት<br />
በተከሰተበት ሰዓት ከፍተኛ የኢኮኖሚ<br />
ዕድገት አስመዘግባለሁ ማለት ተጨማሪ<br />
ገንዘብ ወደ ኢኮኖሚው ማፍሰስ መሆኑን<br />
የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ያስረዳሉ።<br />
‹‹ግሽበት ማለት ሌላ ተዓምር አይደለም፤<br />
ጥቂት ምርትና እጅግ በርካታ ገንዘብ<br />
በኢኮኖሚው ውስጥ መኖር ነው›› የሚሉት<br />
አቶ ተመስገን፣ ‹‹ከፍተኛ ዕድገት ቢመጣ<br />
መልካም ነበር ግን መወሰድ ያለባቸውን<br />
እርምጃዎችና መዋጥ ያለባቸውን መራራ<br />
ኪኒኖች ሳይውጡ የማይሆን ነገር<br />
ነው” በማለት የመፍትሄ ሀሳባቸውን<br />
እንደሚከተለው ያካፍላሉ፡- “ግሽበቱን<br />
ለማስተካከልና የታቀደውን ዕቅድ ለማሳካት<br />
መዋጥ ያለባቸው መራራ ኪኒኖች<br />
ፊስካልና ሞኒተሪ መሳሪያዎች ናቸው።<br />
በተለይ በሞኒተሪው በኩል ብሔራዊ ባንክ<br />
ነፃ ወይም ከአስፈፃሚ አካላት ተፅዕኖ<br />
ሊላቀቅ ይገባዋል። ብሔራዊ ባንክ ነፃ<br />
ሆኖ ቢሰራ የወለድ መጠን እንዲጨምር<br />
ያደርጋል። የወለድ መጠን ሲጨምር ሰዎች<br />
ገንዘባቸውን ባንክ ማስቀመጥ ይጀምራሉ።<br />
የዛኔ የኢኮኖሚው ውስጥ የገንዘብ ዝውውር<br />
እየቀነሰ ይመጣል። … ብሔራዊ ባንክ<br />
የንግድ ባንኮች የግዴታ ሊይዙት የሚገባውን<br />
የተቀማጭ ገንዘብ መጠን (ሪዘርቭ<br />
ሪኳየርመንት) እንዲጨምር ማድረግ<br />
ያስፈልጋል። ይህም ገንዘብን ከኢኮኖሚው<br />
ውስጥ ለመቀነስ ይረዳል” በማለት ምሁራዊ<br />
አስተያየታቸውን ያጋራሉ።<br />
የኢኮኖሚን ሀሁ እንደማያውቁ በጠ/<br />
ሚኒስትር መለስ ‘የማረጋገጫ ሰርተፊኬት’<br />
የተሰጣቸው አቶ ግርማ ሰይፉ፣<br />
‹‹እንኳንስና 11.4 በመቶ ሊታደግ ቀርቶ<br />
አምና ከነበረበትም የወረደ ህይወት ነው<br />
የኢትዮጵያ ህዝብ እየመራ ያለው። ሰዉ<br />
በቀን አንዴ መመገብ እንኳን አቅቶት<br />
ባለበት ሁኔታ፣ “ኢኮኖሚው አድጓል ብሎ<br />
ሽንጥን ገትሮ መከራከር እውነታውን መካድ<br />
ነው። እኛኮ 11 በመቶ አድገናል ቢባልም<br />
ሆነ 15 በመቶ፣ በተጨባጭ<br />
ዕድገቱ የዜጎች ህይወት<br />
ላይ ካልተንፀባረቀ ምንም<br />
ለውጥ የለውም” በማለት<br />
ህዝቡ ያለበትን ወቅታዊ<br />
የኑሮ ሁኔታ በቁጭት<br />
ይገመግሙታል።<br />
“ተዓምራዊ እድገት ማለት እኮ<br />
ቀላል ነገር አይደለም። በአሁን ሰዓት<br />
ኢትዮጵያ ውስጥ ‘ተዓምር’ የሚያሰኝ<br />
እድገት ተፈጥሮ ቢሆን ኖሮ የአዲስ ዘመን<br />
ጋዜጣ ኮፒ ወደ 80 ሚሊየን ይጠጋ ነበር።<br />
ምክንያቱም፣ የተዓምራዊው ዕድገት ተቋዳሽ<br />
የሆነው 80 ሚሊየን ህዝብ፣ “ኢኮኖሚው<br />
አላደገም’ ብለው የህዝቡን ብሶት የሚጮሁ<br />
ነፃ ጋዜጦችን ተጠይፎ ከመንግሥት<br />
ጎን ይቆም ነበር” የሚሉ ወገኖች፣ ህዝቡ
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />
በተዓምራዊ ዕድገት ሳይሆን በአንዳች<br />
ተዓምራዊ ኃይል እየኖረ መሆኑን ደግመው<br />
ደጋግመው ያስረግጣሉ።<br />
እነዚሁ ወገኖች ቀጠል በማድረግም፣<br />
“መንግሥት ኢኮኖሚውን ለማስተካከል<br />
ግሽበቱን ከመቆጣጠር ይልቅ የኢኮኖሚ<br />
ባለሙያዎች የሚያቀርቡትን የመፍትሄ<br />
ሀሳብ ተቆጣጥሮ ለማምከን መጣደፉ በጣም<br />
ያስገርማል” በማለት ጭንቅላታቸውን<br />
በሀዘኔታ ይነቀንቃሉ።<br />
ዳቦ ገዢ VS ዳቦ ፈላጊ<br />
ባለፉት የኢህአዴግ 20 ዓመታት ውስጥ፣<br />
ከመንግሥት <strong>ራዳር</strong> ወጥተዋል ተብሎ<br />
የሚነገርላቸውና ለብዛታቸውም የቁጥርና<br />
የፊደል መረጃ የሚጠቀስላቸው ብዙ<br />
ሺህ ‘ስራ አጥ’ ኢትዮጵያውያን አሉ።<br />
የስራ አጦቹ ቁጥር ከሁለቱም መደብ<br />
(ከተመረቀውም ካልተመረቀውም ወይም<br />
ካልተማረው) የተውጣጣ ሲሆን፣ በአሁን<br />
ሰዓት ያሉበት ደረጃ ደግሞ እጅግ አሳሳቢና<br />
አፋጣኝ እርምጃ ከሚሹ ጉዳዮች መካከል<br />
የሚካተት መሆኑ ብዙዎችን ያስማማል።<br />
መንግሥት፣ በአምስት ዓመቱ የዕድገትና<br />
ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ውስጥ አሳካቸዋለሁ<br />
ብሎ በልበ-ሙሉነት ከዘረዘራቸው ጉዳዮች<br />
አንዱ ዩኒቨርስቲዎችን በቁጥር የማሳደግ<br />
ነው። በዚህ ላይ ቅሬታ የሌላቸው ሰዎች<br />
“በቁጥር ካደጉት ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ<br />
ተመርቀው ለሚወጡ ቁጥራቸው የበዛ<br />
ተማሪዎች ምን የተመቻቸ ነገር አለ?<br />
ወይስ የመንግሥት ሥራ ማስመረቅ ብቻ<br />
ነው?” በማለት ሊታሰብበት የሚገባ ወሳኝ<br />
ጥያቄ ይሰነዝራሉ።<br />
የህወሓት መሥራች አባል የነበሩትና<br />
በአሁን ወቅት የአረና ፓርቲ የአመራር<br />
አባል የሆኑት አቶ አስገደ ገ/ሥላሴ፣ “ሙስና<br />
እና ኢንቨስትመንት በትግራይ” በሚለው<br />
መጣጥፋቸው ላይ ያነሱት ጉዳይ አለ፤ “ ...<br />
በሁሉም ዞኖች ያሉ ማኅበራት አብዛኛዎቹ<br />
የከሰሙና የከሰሩ እንዲሁም ለዕለት ጉርስ<br />
እየለቃቀሙ የሚኖሩ ናቸው። ለዚህም<br />
የክልሉ የኢንዱስትሪና የከተማ ልማት<br />
ቢሮ ኃላፊና የህወኃት ማዕከላዊ ኮሚቴ<br />
አባል የሆኑት አቶ በየነ መክሩ በሰማዕታት<br />
ሀውልት እንደተናገሩት፣ አብዛኛዎቹ<br />
የጥቃቅንና አነስተኛ ማኅበራት ገንዘብ<br />
አበደርናቸው፣ ሁሉም ከሰሩ ብለዋል።<br />
“… በትግራይ ክልል የነበረ አናጢ፣ ግንበኛ፣<br />
ለሳኝ በአጠቃላይ ሞያተኞችና የጉልበት<br />
ሰራተኞችን በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ስራ<br />
ፈጥረው ሲያሰሩ የነበሩ የህንፃ ተቋራጮች<br />
(ኮንትራክተሮች) አብዛኛዎቹ በብልሹ<br />
አስተዳደር ምክንያት ከክልሉ ለቀዋል››<br />
በማለት ብልሹ አሰራር ምን ያህል ስራ<br />
አጥ ዜጎችን እየፈጠረ እንደሚገኘም<br />
ያመላክታሉ።<br />
ዳቦ ለመግዛት ወደ ዳቦ ቤት ከሚሄደው<br />
ሰው ይልቅ፣ ዳቦ ፍለጋ ወደ ቫካንሲ<br />
ሰሌዳዎች የሚጎርፈው ሰው በበለጠበት<br />
በዚህ ሰዓት፣ መንግሥት የሥራ ዕድል<br />
ለመፍጠር መትጋት ሲገባው፣ ለብዙ ሥራ-<br />
አጦች በልቶ ማደር ምክንያት የሚሆኑ<br />
ባለኃብቶችን በብልሹ አሰራር ምክንያት<br />
ከቦታ ቦታ ማሳደዱ ያስቆጫቸው አቶ<br />
አስገደ፣ “ ... የትግራይ ባለኃብቶችና<br />
ድርጅቶች የተመቻቸ የኢንቨስትመንት ቦታ<br />
ባለማግኘታቸው እንደ አማራጭ ወደ ሌላ<br />
ቦታ ሄደው ሲበለፅጉ ይታያል” በማለት ብዙ<br />
ሥራ-አጦች እንጀራቸውን ከጉሮሯቸው ላይ<br />
እየተነጠቁ መሆኑን ያስገነዝባሉ።<br />
ከጥቂት ጊዜያት ወዲህ፣ መንግሥት ሰፋፊ<br />
መሬቶችን ለውጭ ባለኃብቶች በወረደ<br />
ወይም አንድ ኪሎ ሙዝ በማይገዛ (በአሁን<br />
ሰዓት አንድ ኪሎ ሙዝ 12 ብር ሲሆን<br />
አንድ ሄክታር ድንግል መሬት ደግሞ እስከ<br />
አ<strong>ስር</strong> ብር ይሸጣል) ዋጋ መሸጡ እያስገረመ<br />
ሳለ፣ ባለኃብቶቹ፣ የሀገራቸውን ሥራ<br />
አጦች በአውሮፕላን ጭነው አምጥተው<br />
በተረከቡት መሬት ላይ እንዲሰሩ<br />
ማድረጋቸው ብዙዎችን አስቆጥቷል።<br />
“ምክንያቱም . . . ” ይላሉ ተቆጪዎቹ፣<br />
“ … ኢትዮጵያውያን ሥራ-አጦች ሊሰሩት<br />
የሚገባውን ሥራ ባህር አቋርጠው የመጡ<br />
ሰዎች መስራታቸው ኢትዮጵያውያን የበይ<br />
ተመልካች እንዲሆኑ አስገድዷቸዋል፤ ይሄ<br />
ደግሞ ከአንድ መንግሥት አይጠበቅም፤<br />
ኢህአዴግ የኢትዮጵያ መንግሥት እንጂ<br />
የህንድና የቻይና (ሥራ-አጦች) መንግሥት<br />
አይደለም” በማለት መንግሥት አቋሙን<br />
እንዲያስተካክል ማሳሰቢያ ይሰጣሉ።<br />
ትግሉ ተቋጨ?<br />
ምንም እንኳን ኢትዮጵያ እንደ ጃፓን<br />
በኒዩክለር ጣጣ፣ እንደ ቱርክ በመሬት<br />
መንቀጥቀጥ፣ … አትመታ እንጂ በሥራ<br />
አጥነት፣ በኑሮ ውድነት፣ በቤት እጦት እና<br />
ኪራይ ችግር … ወዘተ ክፉኛ እየተናወጠችና<br />
እየተመታች እንዲሁም ዜጎቿ ከአቅም<br />
በላይ በሆነ ችግር መኖሪያቸውን ለቀው<br />
እየተሰደዱና በየበረሐው እየሞቱ<br />
መሆናቸውን የተለያዩ አስደንጋጭ<br />
ሪፖርቶች እያመላከቱ ነው።<br />
በአሁን ሰዓት ኢትዮጵያ በከባድ ጎርፍና<br />
ወጀብ አለመመታቷን “ተመስገን” በማለት<br />
የሚገልፁ ወገኖች፣ ሀገሪቱ ቅጥ አምባሩ<br />
በጠፋ የኑሮ ውድነት መሀል አናቷን<br />
መበርቀሷ ግን በየደቂቃው እያባነናቸው<br />
መሆኑን ከመናገር አልተቆጠቡም።<br />
በ2003 ዓ.ም ታህሳስ ወር ላይ፣ ጠቅላይ<br />
ሚኒስትሩን፣ የሚኒስትር ዴኤታዎችን<br />
እና ሌሎች የመንግሥት ባለሥልጣናትን<br />
በአንድ አዳራሽ አሰባስቦ የነበረው የኑሮ<br />
ንረት፣ ዛሬ ከመንግሥት <strong>ራዳር</strong> የወጣበት<br />
ምክንያት ምን እንደሆነ የተገለፀ ነገር<br />
ባይኖርም፣ ኢኮኖሚስቶች ግን ጉዳዩ<br />
(ንረቱ) ከመንግሥት አቅም በላይ መሆኑን<br />
መረጃዎችን በማገላበጥ ያስረዳሉ።<br />
“የነዳጅ ዋጋ መናር በሊቢያና በመሰል<br />
ሀገራት አብዮት ይመካኛል። የሥጋ፣<br />
የበርበሬ፣ የቡና … ዋጋ መናር በማን<br />
ሊሳበብ ነው? ዋጋቸው ስንት እስኪገባስ<br />
ድረስ ነው በዝምታ የሚታዩት?” የሚል<br />
ጥያቄ የሚያቀርቡ ሰዎች ከመንግሥት<br />
የሚሰጣቸው ምላሽ ከሀገሪቱ ወቅታዊ<br />
ሁኔታ ጋር ፍፁም የሚቃረን መሆኑ<br />
ያበሳጫቸዋል።<br />
መንግሥት፣ ይሄ ዕቃ ተወደደ ሲባል<br />
“አድገናል”፤ ኧረ ይሄ ዕቃ ከገበያው ጠፋ<br />
ሲባል “አድገናል አድገናል”፤ ኧረ መፍትሄ<br />
አምጡ በልቶ ማደር አለማደር ልማድ ሆነ<br />
ሲባል፣ “አድገናል አድገናል፣ አድገናል”<br />
የሚለው ህዝብ እንዳይቆጣው አስቀድሞ<br />
ለመቆጣት ነው ይላሉ - የመንግሥትን<br />
አመለ-ቢስነት በቅርበት የሚያውቁ ውስጠ-<br />
አዋቂዎች።<br />
“የኢትዮጵያ ህዝብ ስራ ማጣቱን፣<br />
መራቡን፣ ኑሮ ከአቅሙ በላይ መሆኑን<br />
… ለመግለፅ የግድ እንደ ቱኒዝያዊው<br />
መሐመድ ቡአዚዝ ራሱን አቃጥሎ<br />
መግደል አለበት ወይ?” የምትለውና<br />
የአምስት ልጆች እናት የሆነችው ወ/ሮ<br />
ቅድስት ተክሉ፣ ህዝቡ ክብሪት ጭሮ ራሱን<br />
ባያቃጥልም፣ በመንግሥት ቸልተኝነት እና<br />
በአንዳንድ ራስ-ወዳድ ነጋዴዎች የተጫረው<br />
የኑሮ ንረት ቀስ በቀስ ህዝቡን አቃጥሎ<br />
እየጨረሰው መሆኑን በማስጠንቀቂያ መልክ<br />
ትናገራለች።<br />
የጦር ሠራዊት እና የጦር መሳሪያ<br />
በመሰብሰብ (በመያዝ) ከምስራቅ አፍሪካ<br />
ሶስተኛ ደረጃ ይዞ የነበረውን የደርግ<br />
መንግሥት በ17 ዓመታት ውስጥ ታግለው<br />
በመጣል ኢትዮጵያን በራዳራቸው ሥር<br />
ያስገቡት ኢህአዴጎች፣ ዛሬ ቤተ-መንግሥት<br />
እና ያማረ ቤት ውስጥ እየኖሩ፣ እንደ<br />
ውሃ በሚፈስ መኪና እየተመላለሱ ህዝቡን<br />
የሚገዳደሩ ችግሮችን ምነው መታገልና<br />
መጣል አቃታቸው? ወይስ ትግሉ ተቋጨ?<br />
የሚል አነጋጋራ ጥያቄዎች እየተነሱበት<br />
ነው - መንግሥት።<br />
ሀና እና መሰሎቿ<br />
ሚያዝያ 22/2000 ዓ.ም የስምንት ዓመት<br />
ልጅ እና የሁለተኛ ክፍል ተማሪ ለነበረችው<br />
ሀና አለማየሁ ጥሩ ቀን አልነበም፡። ቀኑ<br />
እንደመምሸት ሲል ሀና ከወላጆቿ ቤት ወደ<br />
አያቷ ቤት ጉዞ ትጀምራለች። (የወላጆቿ<br />
እና የአያቷ ቤት አንድ ሰፈር ውስጥ ነው<br />
ያለው)<br />
ልጅቷ ቤት ከመድረሷ በፊት እስካሁን<br />
ድረስ ማንነቱና ምንነቱ ያልታወቀ ሰው<br />
ያገኛትና አታሎ ይዟት ይሄዳል። …<br />
አስገድዶ ከደፈራት በኋላ ህይወቷ አለፈ።<br />
ጧት ሀና ሰፈራቸው የሚገኝ ወንዝ ውስጥ<br />
ተጥላ ተገኘች።<br />
የኤልፓንና የቴሌን ህንፃ “ለጥቂት”<br />
ከመጋዬት እና ከመውደም አድኖ<br />
‘ተጠርጣሪ’ ያላቸውን ጋዜጠኞች በቁጥጥር<br />
(በራዳሩ) <strong>ስር</strong> ያዋለ መንግሥት፣ በሀና እና<br />
በመሰሎቿ ላይ ጥቃት ፈፅመው (ያውም<br />
ገድለው) የተሰወሩ ተጠርጣሪዎችን እንዴት<br />
መያዝ አቃተው? የሚል ጥያቄ ይነሳል -<br />
በህብረተሰቡ ዘንድ።<br />
ጥቃት ፈፅመው ከመንግሥት <strong>ራዳር</strong> ውስጥ<br />
የተሰወሩት ተጠርጣሪዎች በመንግሥት<br />
ቸልተኝነት ነው ያልተያዙት? ወይስ<br />
ከመንግሥት አቅም በላይ ሆነው ነው?<br />
ይላሉ የጥቃት ሰለባዎቹ ቤተሰቦች።<br />
መንግሥት፣ ከህዝቡ ጥቅም ይልቅ የራሱ<br />
ጥቅም እንደሚበልጥበት የሚናገሩ ወገኖች፣<br />
የፖለቲካውን ምህዳር ‘ለመጠበቅ’ በሚል<br />
ሰበብ የራሱን የሥልጣን ምህዳር እየጠበቀ<br />
መሆኑኑ በመግለፅ “ጥቃት ፈፅመው<br />
ያልተያዙ ህዝብ አሸባሪዎች አነፍንፎ<br />
ለመያዝ ምነው አፍንጫና እጅ አጠረው?”<br />
ይላሉ።<br />
አንቀጽ<br />
በታዲዎስ ጌታሁን<br />
አራዳሹ ከጥግ እስከ ጥግ በሰው<br />
ጢም ብሏል። ሁሉም ተሰብሳቢ ሰውዬውን<br />
በጉጉት ይጠባበቃል። ሰውዬው በጉጉት<br />
የሚጠበቀው ያለ ምክንያት አይደለም።<br />
የተሰብሳቢዎቹ ችግር የሚቀረፈው<br />
ሰውዬው ለበታቾቹ በሚያስተላልፈው<br />
ትዕዛዝ በመሆኑ ሁሉም ደጅ ደጁን ያያል።<br />
… ወዲያውም የአዳራሹ መግቢያ በር ላይ<br />
ከፍተኛ ግርግር ተፈጠረ።<br />
ደረታቸውንና ጡንቻቸውን<br />
ያሳበጡት የሰውዬው ጠባቂዎች (ጋርዶች)<br />
ነበሩ የግርግሩ መንስዔዎች።<br />
ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ<br />
እንዲሉ ምንም ዓይነት አስጊ ሁኔታ በሌለበት<br />
ሰላማዊ አዳራሸ ውስጥ ወከባ ከፈጠሩ<br />
በኋላ ሰውዬውን የተዘጋጀላቸው ቦታ ላይ<br />
አስቀመጧቸው።<br />
የተሰብሳቢውን ችግር ሰምተው<br />
መፍትሔ ለማምጣት ፊት ለፊት የተሰየሙት<br />
ሰውዬ አንድ በአንድ ጥያቄ ይቀርብላቸው<br />
ጀመር።<br />
‹‹በከተማችን ውስጥ የቤት ችግር<br />
እየተስፋፋ ነው፤ እና ችግሩን ለመቅረፍ ምን<br />
አስባችኋል?›› አለ አንድ ተሰብሳቢ።<br />
ሁለተኛዋ ተሰብሳቢ ደግሞ<br />
የሚከተለውን ጠየቀች፡- ‹‹በድህነት ውስጥ<br />
የምንኖረው እስከ መቼ ነው? ኑሯችን<br />
የሚሻሻለውስ እንዴት ነው?›› እንባዋ ጠብ<br />
ጠብ አያለ ተቀመጠች።<br />
አንድ አሽቃባጭና አጨብጫቢ<br />
ተሰብሳቢ ደግሞ በሦስተኝነት ጥያቄውን<br />
አቀረበ፡- ‹‹በዙሪያችን አሰፍስፈው የቆሙትን<br />
ተቃዋሚዎቻችንን እንዴት ነው መከላከልና<br />
እንቅስቃሴያቸውን ማዳከም ያለብን?›› ሲል<br />
ሰውዬው ፈጠን ብለው፣ ‹‹ጥሩ ጥያቄ ነው!››<br />
አሉ።<br />
ጥሩ ነው ያሉትን ጥያቄ እየፈቱና<br />
እንየበተኑ እንዲሁም ተቃዋሚዎቻቸውን<br />
የማልፈስፈስ ስትራቴጂያቸው ምን<br />
እንደሚመስል በስፋትና በጥራት አወሩ።<br />
አወሩ። አሁንም ደግመው ደጋግመው አወሩ።<br />
…<br />
… ሚያዚያ 25 ቀን 1881 ዓ.ም፤<br />
ንጉስ ምኒልክ ከጣሊያን መንግሥት ጋር፣<br />
ሃያ አንቀጾች የያዘ ውል ለመዋዋል ውጫሌ<br />
ተቀምጠዋል። ምኒልክና ጣሊያን በሌሎቹ<br />
አንቀጾች ይዘት ቢስማሙም፣ መዘዘኛው<br />
አንቀጽ አስራ ሰባት ግን ለከፋ ውዝግብ ወይም<br />
ለአድዋ ጦርነት ዳርጓቸዋል።<br />
‹‹የኢትዮጵያ መንግሥት ከውጭ<br />
<strong>አገር</strong> መንግሥታት ጋራ የሚያደርገውን<br />
ግንኙነት በኢጣሊያ መንግሥት አማካይነት<br />
ማድረግ ይገባዋል›› ይላል የአንቀጽ 17<br />
የጣሊያንኛ ትርጉም።<br />
የአድዋ ጦርነት ያለመደማመጥ<br />
ውጤት ነው። ጣሊያን፣ የልብ ትርታዋንና<br />
ፍላጎቷን እንጂ፣ ኢትዮጵያ በአንቀጽ<br />
17 ላይ ታሰማ የነበረውን የተቃውሞ<br />
ድምፅ አታዳምጥም ነበር። ወይም ደግሞ<br />
ተቃውሞውን ለመቀበል ዝግጁና ፈቃደኛ<br />
አልነበረችም። ለዚህም ነው መሳሪያዋን ጭና<br />
ወደአድዋ ተራሮች መትመም የጀመረችው።<br />
… ‹‹መንግስት ዓይንና ጆሮ<br />
አለው›› ይላል ኢህአዴግ። በእርግጥም ትልቅ<br />
ጆሮ ነው ያለው መንግሥት። ግን አብዛኛውን<br />
ጊዜ ጆሮውን ዘንበል የሚያደርገው ወደ<br />
ህብረተሰቡ ጥያቄ ሳይሆን ወደ ተቃዋሚዎች<br />
መንደር ነው።<br />
‹‹የቤት ችግር አለ፤ ድህነት<br />
ተንሰራፋ፤…›› የሚሉ ህብረተሰብዎች ስፍር<br />
ቁጥር የላቸውም። ጆሮ እንዳለው በፓርላማ<br />
የተናገረው መንግሥት ግን፣ ፈጥኖ ጆሮውን<br />
የሚያዘነብለው ወደ ዶ/ር ነጋሶ፣ ኢንጂነር<br />
ኃይሉ ሻውል፣ ቡርቱካን ሚደቅሳ … ነው።<br />
በተቃዋሚዎች መንደር ምን<br />
እንደተወራ (አንዳንዴ ከተቃዋሚዎቹ አባላት<br />
እንኳን) ቀድሞ የመስማት ‹ችሎታ› አለው።<br />
የህብረተሰቡን የልብ ትርታ እና ፍላጎት<br />
ለመስማት ግን የወራትና የዓመታት እድሜ<br />
ያስቆጥራል።<br />
ይህም የሚያሳው፣ የመንበረ-<br />
ክብሩን ግርማ-ሞገስ ከህብረተሰቡ ፍላጎት<br />
አስበልጦ እና አስቀድሞ እንደሚያፈቅር ነው።<br />
በነገራችን ላይ፣ ይሄ አይነቱ ፀባይ የዚህ<br />
መንግሥት ብቻ አይደለም።<br />
ኃይለሥላሴ፡- የእኚህ ንጉሥ<br />
ሥርዓት እንደማንኛውም መንግሥት ትላልቅ<br />
ጆሮ ነበረው። ችግሩ፣ ሥርዓቱ አስቀድሞ<br />
ይሰማ የነበረው በወቅቱ ህዝቡ ያሰማ<br />
የነበረውን ብሶት አልነበረም።<br />
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ውስጥ<br />
‹‹ክሮኮዳይልስ›› (አዞዎች) በመባል የሚታወቅ<br />
የተራማጅ ተማሪዎች ቡድን ነበር። ይህ<br />
ተራማጅ ቡድን በ1957 ‹‹መሬት ላራሹ<br />
ይሰጥ›› የሚል መፈክር ተሸክሞ ሰልፍ<br />
ወጣ። መፈክሩ ኢትዮጵያ ውስጥ ከተነሱት<br />
መፈክሮች ሁሉ አደገኛው ነበር። የአፄው<br />
ሥርዓት እንደአብዛኛዎቹ ሥርዓቶች ይሉኝታ<br />
17<br />
በቃልኪዳን ይበልጣል<br />
የሚያጠቃውና የተቃውሞ ድምጾችን የመታገስ<br />
ባህርይ ስላልነበረው ሰልፉ በፖሊስ ተበተነ።<br />
አ<strong>ስር</strong> ኪ. ሜ. መንገድ ለማሰራት<br />
የሚደክመው መንግሥት፣ ሰልፉን ለመበተን<br />
ግን እስከ አ<strong>ስር</strong> ሺህ የሚደርስ ጦር ሠራዊት<br />
ያሰልፋል።<br />
ደርግም፣ ሀገሪቱ ውስጥ ስንትና<br />
ስንት አንገብጋቢ ችግር እያለ፣ እሱ ግን<br />
ተንገብግቦ መላ የሚያበጀው፣ የኢሕአፓን<br />
የፖለቲካ እንቅስቀሴ ወገቡን ለመምታት<br />
ነበር።<br />
የኢህአፓ አባላት ማታ ቡና<br />
እስከስንተኛ ድረስ አንደጠጡ ሳያውቅ<br />
አይቀርም - ደርግ። ምክንያቱም ይቃወሙኛል<br />
ለሥልጣኔ መናጋት ምክንያት ይሆናሉ<br />
ብሎ የሚጠረጥራቸውን ሁሉ እግር በእግር<br />
እየተከተለ እግረ-ሙቅ የሚያጠልቅ ሥርዓት<br />
ነበር። እስራቱንና ጭቆናውን ለማፋፋም፣<br />
በእስራኤሎች የሠለጠነው ‹‹ነበልባል ቡድን››<br />
አዲስ አበባ እንዲመጣ በማድረግ፣ እንደ<br />
ውጫሌው ስምምነት (አንቀጽ አስራ ሰባት)<br />
አቋሙን በግድ ለመጋት ሞክሯል።<br />
ደርግ፣ አቋሙን እንደጣሊያኖች<br />
በአንቀጽ አይክፍለው እንጂ፣ በግልፅ ሲያራምድ<br />
የነበረው ፍላጎቱ፣ ከአንቀጽ አስራ ሰባት ጋር<br />
የጠበቀ መመሳሰል ነበረው።<br />
የአንቀጽ አስራ ሰባት አጭር<br />
ትርጉም፡- ሌሎችን ያለማዳመጥ እና የራስን<br />
ፍላጎት ብቻ መከተል ነው። የደርግም አንደዚያ<br />
ነበር - ሌሎችን ያለመስማት።<br />
አንቀፅ 17 የአድዋን ጦርነት ወለደ።<br />
የደርግ አንቀጽ አስራ ሰባታዊ አቋም (ሌሎችን<br />
ያለመስማት አቋም) የአስራ ሰባት ዓመታታ<br />
ኢህአዴግ የመናገር እንጂ ብዙም የማዳመጥ ልምድና ፍላጎት<br />
የለውም። በተቃራኒው ደግሞ፣ ሌሎች የእሱን ማስጠንቀቂያዎች<br />
የማዳመጥ ፍላጎት እና ልማድ እንዲኖራቸው ይፈልጋል። በዓለም<br />
ላይ ቀላሉ ነገር መናገር ሲሆን ከባዱ ደግሞ ማዳመጥ ነው።<br />
ለመናገር ለመናገርማ ወፈፌም ይናገራል<br />
ጦርነት ወልዶ ደርግን አስወገደ።<br />
ኢትዮጵያ፣ የተቃውሞ ድምጾችንና<br />
ሰልፎችን ፈጥነው የሚያደምጡ፣ የህዝቡን<br />
ችግር ደግሞ ቀ..ስ..ስ ብለው የሚሰሙ<br />
መንግሥታት የተፈራረቁባት ምስኪን <strong>አገር</strong><br />
ነች።<br />
የህዝብ እንባ ምናቸውም አይደል።<br />
‹‹ተቃዋሚዎችን እንዴት እናልፈስፍስ?››<br />
የሚል የአጎብጓቢዎች ጥያቄ ግን ‹‹ጥሩ›› ነው<br />
ለእነሱ። እንዲህ ዓይነቱ ጥያቄ ውሃና የፀሐይ<br />
ብርሃናቸው እንዲሁም ቫይታሚን ኤ፣ ቢ፣<br />
ሲያቸው ነው።<br />
ሥልጣናቸውን የሚያፋፉትና<br />
የሚያጠነክሩት ተቃዋሚዎችን በማቀጨጭ<br />
ነው።<br />
ኢህአዴግ የመናገር እንጂ ብዙም<br />
የማዳመጥ ልምድና ፍላጎት የለውም።<br />
በተቃራኒው ደግሞ፣ ሌሎች የእሱን<br />
ማስጠንቀቂያዎች የማዳመጥ ፍላጎት እና<br />
ልማድ እንዲኖራቸው ይፈልጋል።<br />
በዓለም ላይ ቀላሉ ነገር መናገር<br />
ሲሆን ከባዱ ደግሞ ማዳመጥ ነው። ለመናገር<br />
ለመናገርማ ወፈፌም ይናገራል። አንድ ሰው፣<br />
ሌሎች በአግባቡና በሙሉ ልብ እንዲያዳምጡት<br />
ከፈለገ፣ እሱም ለሌሎች ጆሮውን ወገግ አድርጎ<br />
መክፈት አለበት። የግትርነት አቋም መለኪያና<br />
ማሳያ እንዲሁም የራስ ወዳድነት ምልክት<br />
የሆነው አንቀፅ 17 ለማንም አይጠቅምም -<br />
በተለይ ለመንግሥት።<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
5
6<br />
ፀጥታ እንፈልጋን። እርጋታ<br />
እንፈልጋለን። ስክነት<br />
እንፈልጋለን። በጥቅሉ<br />
ሰላም እንፈልጋለን።<br />
ለመሆኑ አራቱ አጫጭር<br />
አረፍተ ነገሮች ባለቤት<br />
‹‹እኛ›› ማን ነን? እኔና<br />
መሰሎቼ። አረፍተ<br />
ነገሮቹን በዚህ መልኩ ማዋቀሬ ምስጢር<br />
ሲመረመር የሚጠቁመው፡- ሀ) እንደ<br />
በርካታ ቀሺም ፖለቲከኞች የራሴን እምነት<br />
ለማስረፅ ስለ ‹ሰፊው ህዝብ› በሚሏት<br />
ተወዳጅ ሀረግ ለመጠለል መምረጤን<br />
ነው፤ አሊያም ለ) ማንም ያልሰጠኝን<br />
ውክልና ተሸክሜ ለአካባቢዬ ለመቆርቆርና<br />
ለመሟገት ራሴን ማጨቴን ነው።<br />
አንድን ነገር ግን በእርግጠኝነት<br />
መናገር እችላለሁ። እንደ’ኔው በጩኸት<br />
መደንበር ያታከታቸው፣ በየደቂቃው<br />
መበርገግ ያንገሸገሻቸው፣ መዋከብና<br />
መደንገጥ ያማረራቸው፣ ከቤታቸው<br />
ወጥተው እስኪመለሱ በአደንቋሪ ድምጾችና<br />
የጆሮን ታምቡር ሊበጥሱ በሚንደረደሩ<br />
ሁከቶች ተሰንገው የሚሳቀቁ፣ በጥሞና<br />
መጓዝም ሆነ በፀጥታ መተኛት የናፈቃቸው<br />
ብጤዎቼ ጥቂት አይባሉም።<br />
‹‹እዚህ ከተማ ውስጥ የራሱ የሆነ<br />
የነጠረ ስብዕና ያለው ሰው ማግኘት አዳጋች<br />
ነው። አንዱ የአንዱ ፎቶ ኮፒ ለመሆን<br />
ነጋ ጠባ ይታትራል። ይሳካለትማል።<br />
በብልጭልጭ ህንፃ ካበደው ቅንጡ<br />
ሰፈር አንስተህ እስከጨርንቁሱ መንደር<br />
ብታስስ የሚገጥምህ የሰው አይነት ብዙ<br />
አይደለም። ሁሉም የጋራ አካፋዩን እየፈለገ<br />
ተቧድኗል። ድንገት ድንቅ ኃሳብ አፍልቀህ<br />
ተከታይህ ቢበራከት፣ አጀብህ አጀብ<br />
ቢያሰኝ ያጨበጨበልህ ሁሉ ገብተኸው<br />
እንዳይመስልህ። ከምንም በላይ ወረትና<br />
ጊዜያዊ ሆይ-ሆይታ ይማረኩናል። ከፍሬ<br />
ነገሩ በበለጠ አልባሱን ሙጥኝ እንላለን።<br />
ከምስሉ ጋር እንጣበቃለን። በመሆኑም<br />
በተደጋጋሚ በከንቱ እንለፈልፋለን።<br />
እንደናቆራለን።” እንዲህ ያለኝ አንድ<br />
ወዳጄ ነው። ከዓመታት በፊት ጩኸታሟ<br />
ከተማ ያደረሰችብኝን መንፈሳዊ እንግልት<br />
ተናዝዤ ዝምታዋን ብመኝ ግን ምኞቴን<br />
የሚጋሩ ብዙሃን ከተባለው በተለየ<br />
እውነተኛና ከተሞክሯቸው የሚመዘዝ<br />
ነጥብ እንደሚኖራቸው አይታበልም።<br />
ሰው ከጥንተ-ፍጥረት ጀምሮ<br />
ከአከባቢው ጋር ሲታገል ኖሯል።<br />
ተፈጥሮን ድል ነስቶ እንዳሻው ሊያሾራት<br />
ተወተርትሯል። ጢሻውን እየመነጠረ፣<br />
ጋራውን እያስገበረ፣ ጭንጫውን አያለሰለሰ፣<br />
ወንዞች ወደመረጠው ስፍራ እንዲፈሱ<br />
ቦይ እየቀየሰ፣ በተስማማው ቦታ ጎጆውን<br />
እየቀለሰ፣ ተከማችቶ እየሰፈረ፣ ከተሞች<br />
እየቆረቆረ ወደ ሥልጣኔ ተምዘግዝጓል።<br />
ዝርያው በዝቶ ተባዝቶ ምድርን ሲሞላ፣<br />
መፈናፈኛም ሲያጣ ዱርዱሩን እያፀዳ፣<br />
እንስሳቱን እያባረረ ግዛቱን አስፍቷል።<br />
ኑሮው ይቀልለትም ዘንድ መኖሪያውን<br />
ጭስ በሚተፉ ማሽኖች ሞልቷል። ግና<br />
ከማሽኖቹ ጋር የወደቀበት አቅል የሚያስት<br />
ፍቅር ልቡናውን ሰውሮበት በዋይታ<br />
የምታጣጥር መሬትን ዘነጋት። እንባዋ<br />
ጎርፍ፣ ስቅታዋ ናዳ፣ ኡኡታዋ ድርቅ<br />
ሆነው ሲወግሩት አይኑ መገለጥ ያዘ።<br />
እነሆም አረንጓዴው ዘመን ጠባ። ሁሉም<br />
በየአፉ አረንጓዴ ቃላትን ደሰኮረ። ከፋብሪካ<br />
ቡልቅ ቡልቅ እያለ እንደሚወጣ ጥቁር<br />
ጭስ፣ ወንዝ ውስጥ እንደሚጨመር<br />
እጣቢ ወይም ተረፈ-ምርት ሁሉ መኪኖቹ<br />
ማጉያዎቹ የሚያስፈተልኩት ልክ አልባ<br />
ድምፅ ከባቢን በክሎ ጤናን ያቃውሳል<br />
ተባል። የለም ዜጎች በሞላ ‹የምንኖርበት<br />
ቀየ እርጋታና ዝምታ ያሻዋል› እያሉ<br />
መወያየት ብሎም ለተግባር መሰለፍን<br />
ለመዱ። ይሄን ለመሰለው ‹ቅንጦት›<br />
ጊዜ የሌላት አዲስ አበባችን ግን ላንቃዋ<br />
እስኪተረተር መጮህን ልማድ አድርጋ<br />
ኖረች።<br />
በቅርቡ ሬዲዮ ስከታተል<br />
ባለቤቱና ርዕሱ ያመለጠኝ ጥናት ተጠቅሶ<br />
የከተማችን የድምፅ ልቀት መጠን አደኛ<br />
ደረጃ መድረሱን ሰማሁ። የጥናቱን ድጋፍ<br />
ባላገኝም ከሙዚቃ እስከ መዝሙር ቤት፣<br />
ከንግድ ትርኢት እስከ ግንዛቤ ማስጨበጫ<br />
ቅስቀሳ ረባሽ ኬረዳሽ ድለቃቸውን<br />
በየአጋጣሚው ይጋብዙኛልና እውነታውን<br />
አልስተውም። አሁን አሁን አሁን እየተገነቡ<br />
ያሉ የእግረኛ መንገዶች እንደተጠበቁ<br />
ሆነው በአብዛኛው የሸገር ጎዳናዎች<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />
ኮመንትሪ<br />
በጩኸት<br />
ውስጥ መኖር<br />
በቃልኪዳን ይበልጣል<br />
በእግር እየተጓዙ ዘና ማለት አይታሰብም።<br />
የመኪኖቹ ድንፋታ፣ የሸቃጮች የማያባራ<br />
ውትወታ፣ ከየመደብሩ በር ያለከልካይ<br />
የሚለቀቁ ዘፈኖች ዝብርቅርቅታ አናትን<br />
ቢያዞር እንጂ አያጠራም።<br />
የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር<br />
ከሀገራችን አዋቂዎች 15% ያህሉ<br />
ለአዕምሮ መታወክ የተጋለጡ መሆናቸውን<br />
መግለፁንም ሰምቻለሁ - ቀደም ባለ ጊዜ።<br />
መቼም የዚህ ቁጥር አስደንጋጭነት<br />
ግልፅ ነው። ባልደረጃ አቅማችን፣ ባልጠና<br />
ጉልበታችን ስንቱን እክል እንችለዋለን?<br />
ይበልጥ የሚያስከፋው ደግሞ ነባራዊው<br />
እውነታችን ቁጥሩን ቁልቁል የሚያወርድ<br />
መላ አለመቋጠሩ ነው። ያለመግቻ ሽቅብ<br />
የሚመነደገው የዋጋ ንረት ለጭንቅላት<br />
የሚያተርፈው ከባድ ጭንቀት ራሱን ችሎ<br />
ህሊናን ቢያቃውስ አይደንቅም። ስራና ተስፋ<br />
ለአንድ ሀገር ውድቀትም<br />
ሆነ ዕድገት ተፅዕኖ<br />
ከሚያሳድሩ ምክንያቶች<br />
ዋና ዋናዎቹ የፖለቲካ፣<br />
የህዝብና የተፈጥሮ<br />
ኩነቶች ናቸው። እነዚህ<br />
ሦስት ጎራዎች በአሉታዊ መንገድ<br />
ሲቃኙ ሀገር ይጎዳል፤ ሀገር ይዳኸያል፣<br />
ይራቆታል። በተቃራኒው መንገድ<br />
ከላይ የጠቀስናቸው ምክንያቶች<br />
ወይም መንስኤዎች በአዎንታዊ<br />
መልኩ ሲጓዙ ሀገር ይለመልማል፣<br />
ይበለፅጋል፣ ያድጋል። ፖለቲካው<br />
ደግሞ ከዚህ ለየት ባለ መልኩ<br />
የተለየ የሰውን ልጅ የእለት ተዕለት<br />
ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ባህላዊ<br />
እንቅስቃሴዎችን በመቆጣጠር ቁልፍ<br />
ሚና ይጫወታል። ታዲያ በዙዎች<br />
የዓለማችን መሪዎች ተራቀውበት፣<br />
እንደ ልብ ተቀኝተውበት፣ ህዝቡንም<br />
ደስታ አጎናፅፈውት አንቱ አስብለው<br />
የሚያስኖሩትን ያክል፣ ብዙዎች<br />
የ3ኛው ዓለም ሀገራት፣ በተለይ<br />
የአፍሪካ መሪዎች፣ ፖለቲካን<br />
ሳያውቋት ምስጢሯን፣ ዓላማዋን፣<br />
ድርጊቷንና ግባቷን ሳይመረምሩት<br />
በግዴለሽነትና በማን-አለብኝነት<br />
እብሪትነት ሲሸልሉበት፣ ሲዘሉበት<br />
ኖረዋል። አሁንም እየኖሩ ያሉ አሉ።<br />
የምዕራቡ ዓለም<br />
ለዕድገታቸው ዋናው ተጠቃሽ<br />
ምክንያት ሁልጊዜም እንደምንለው<br />
መልካም የፖለቲካ አስተዳደር<br />
(Good Governance) ስላላቸው<br />
ነው። ፌዴራሊዝምም ይሁን<br />
ሴንትራሊዝም፣ ፖርሊያመንታሪም<br />
ይሁን ፕሬዝዳንታዊል፣ ኒዮ-<br />
ሊሊበራልም ይከተሉ ሊበራል ብቻ<br />
በየትኛውም በተከሉት የፖለቲካ<br />
ጥርጊያ ለመረጣቸው ህዝብ አሻራ<br />
ለቃል ለማተባቸው ታማኝና አገልጋይ<br />
ወጥ አቋም ነው ያላቸው።<br />
ወደ እኛው አህጉር አፍሪካና<br />
በተለይ ደግሞ በእኛዋ ኢትዮጵያ<br />
‹‹እዚህ ከተማ ውስጥ የራሱ የሆነ የነጠረ ስብዕና ያለው ሰው ማግኘት አዳጋች ነው። አንዱ የአንዱ ፎቶ ኮፒ ለመሆን<br />
ነጋ ጠባ ይታትራል። ይሳካለትማል። በብልጭልጭ ህንፃ ካበደው ቅንጡ ሰፈር አንስተህ እስከጨርንቁሱ መንደር ብታስስ<br />
የሚገጥምህ የሰው አይነት ብዙ አይደለም። ሁሉም የጋራ አካፋዩን እየፈለገ ተቧድኗል። ድንገት ድንቅ ኃሳብ አፍልቀህ<br />
ተከታይህ ቢበራከት፣ አጀብህ አጀብ ቢያሰኝ ያጨበጨበልህ ሁሉ ገብተኸው እንዳይመስልህ<br />
ከሥንታየሁ ዓለማየሁ<br />
[sent_maki@yahoo.com]<br />
ካጡ ወጣቶች አንስቶ እስከተደላደለው<br />
አባወራ ድረስ የሚናውዙበት የጫትና<br />
የሺሳ ሱስ ጠብታዋን የቀውስ ፍንጭ ባህር<br />
እስክታክል ሊያሰፋት ይቻለዋል። እጅግ<br />
አናሳው የጤና ሸፋናችን ደግሞ መውጫ<br />
ቀዳዳ እንዳይታለም ተስፋን ያጨልማል።<br />
አስቡት እስኪ - ከብዙ ህዝቦቿ መካከል<br />
ብዙዎች እርዳታ ያሻቸዋል እየተባለ ያለባት<br />
ሀገር ያዘጋጀችው የአዕምሮ ህመምተኞች<br />
ሆስፒታል አንድ ነው። ለድንጉጥነት፣<br />
ለስሜት ነውጥና ለእንቅልፍ እጦት<br />
በመዳረግ ለአዕምሮ ህመም መንገድ<br />
እንደሚጠርግ የሚታመነው የድምፅ<br />
ብክለትስ?<br />
የወቅቱን የወግ ሞቅታ ተከትሎ<br />
ከማራገብና ከልብ ጠብ የማይሉ ልፍስፍስ<br />
ማስታወቂያዎችን በለሆሳስ ከማስነገር<br />
በዘለለ ጠንካራ እርምጃዎች የሚፈልጉ<br />
የፖለቲካውን እንቅስቃሴ ስንቃኝ<br />
በእውነት መንግሥት ለራሱ ህልውና<br />
እንጂ ለህዝብ ብሎ የሚሰራው ነገር ያለ<br />
አይመስልም። ለዚህ ፅሁፍ መነሻ የሆነኝ<br />
ባላፈው ሳምንት ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ<br />
በፓርላማ ያደረጉት ንግግር ነው።<br />
ጠ/ሚኒስትሩ በተለያዩ<br />
ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ<br />
አጀንዳዎች ላይ ማብራሪያ በሰጡበት<br />
ወቅት በጣም ያሳዘነኝ ነገር ቢኖር<br />
አሉታዊ ሀሳብ የተነሳባቸው አጀንዳዎች<br />
ላይ ምላሽ ሲሰጡ በጋለና በደም<br />
ፍላት ስሜት ሌቦች፣ የቁራ ጩኸት፣<br />
ሀሁ ያልገባቸው የሚሉ ቃላትን<br />
መጠቀማቸው ነው። አንድ መንግስት<br />
በተለይ ደግሞ ዴሞክራሲያዊ ነኝ ለሚል<br />
መንግስት ለህዝብ ስራውን ሊያቀርብ፣<br />
ሊጠየቅና ሊመረመር ይገባዋል እንጂ<br />
እራሱ ሰብስቦ እኔ የምለውን ብቻ<br />
ስሙኝ፣ የእናንተ አስተያየትና ሀሳብ<br />
ከንቱ ነው አይነት እሳቤ፣ ለምን እንዲህ<br />
አልሆነም ሲባል ሀሁ አልገባችሁም፣<br />
እንደ ቁራ አትጩሁ፣ አጭበርባሪ . .<br />
. በማለት በመድብለ ፓርቲ ተሳትፎ<br />
አምናለሁ ከሚል መንግስት አንዱ<br />
ብቻ ሲፈነጭበት፣ ስራውን እራሱ<br />
ይመስለኛል። ‹‹መልሶ ግንባታ››፣<br />
‹‹እድሳት››፣ ‹‹ማስፋፋት››፣ ‹‹አዳዲስ<br />
ግንባታዎች›› እና የመሳሰሉ ከአዲስ አበባ<br />
ጋር ተያይዘው የሚነሱ ቃላትና ሀረጎች<br />
ከተማዋ ያለችበትን ሁኔታ በጨረፍታም<br />
ቢሆን ይጠቁማሉ። በብዙ አቅጣጫዎች<br />
ዘመናዊ ከተማ ለመሆን በደፋ ቀና<br />
ተወጥራለች። የመዘናዊነት መለኪያው<br />
ምንድን ነው ወደሚለው ክርክር ሳንገባ<br />
ለመኖር የምታመች ከተማ ትሆን ዘንድ<br />
ግን እንፈልጋን። ትርጉም አልባና ቅጥ-<br />
የለሽ የድምፅ ልቀት ምቾት ይነሳልና<br />
ደንበኛ ስሬትና ልኬት በጅቶ ፋታ ብናገኝ<br />
አንጠላም።<br />
እውነት እውነት እላችኋለሁ<br />
በጩኸት ውስጥ መኖር እጅጉን<br />
ያስጨንቃል።<br />
መንግሥት እራሱ<br />
ጠ/ሚኒስትሩ በተለያዩ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ አጀንዳዎች<br />
ላይ ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት በጣም ያሳዘነኝ ነገር ቢኖር አሉታዊ ሀሳብ<br />
የተነሳባቸው አጀንዳዎች ላይ ምላሽ ሲሰጡ በጋለና በደም ፍላት ስሜት ሌቦች፣<br />
የቁራ ጩኸት፣ ሀሁ ያልገባቸው የሚሉ ቃላትን መጠቀማቸው ነው<br />
ሰርቶ እራሱ ብቻ የሚያወድስበት፣<br />
ስህተቱን የማያይበት ከሆነ፣ እውነት<br />
ይህ አይነቱ መንግሥት ለራሱ እሱስ<br />
ቢሆን የአስተዳደር ሀሁ ገብቶታል ወይ<br />
ያስብላል።<br />
ጠ/ሚ መለስ በተለያዩ ጉዳዮች<br />
ላይ እንደተነተኑት፣ ንግግራቸውን<br />
ሲጀምሩ፣ ለመንፏቀቅ ያሰበ መንግስት<br />
ተንፏቋልና በመንፏቀቁ ሊመሰገን<br />
አይገባም፤ ይልቁንስ በፍጥነት<br />
ለመራመድ አስቦ የተራመደን<br />
እናመሰግናለን። እኛም በፍጥነት<br />
ለመራመድ አስበን ተራምደናል ነው<br />
አገላለፁ። መንግስት ከአዲስ አበባ እስከ<br />
ጅቡቲ መንገድ ስራ እንደሚያጠናቀቅ፣<br />
ከ8000-10,000 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ<br />
ኃይል እንደሚያመነጭ፣ ከዚህም<br />
5ሺህ 500 አካባቢው ከአባይ ግድብ<br />
እንደሚገኝ ሲገልፁ ባያልቅም ጅምሩ<br />
ተስፋ ሰጪ ይመስላል። በንግዱ ዘርፍ<br />
ደግሞ የጅመላ ንግዱ ዘርፍ ተወዳዳሪ<br />
የሌለበት ስለሆነ የውጭ ኩባንያዎችን<br />
በማስገባት ተዋናዮችን እንፈጥራለን<br />
ብለዋል። እዚሁ ላይ ከአሁን በፊት<br />
ከIMF ጋር በፈጠሩት ያለመግባባት ሳቢያ<br />
ነው የውጭ ኩባንያዎችን ማስገባት
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />
እና<br />
የማቃለል ዘመን<br />
መጣ! የመቅለል እና<br />
የመቃለል ዘመንም<br />
ተከተለው።›› ይህችን<br />
መሪ መግቢያ<br />
ከወዳጄ ይስማዕከ<br />
‹‹የማቅለል<br />
ወርቁ ሶስተኛ ልብ<br />
ወለድ ወሰድኳት - ዛሬ ስለሶስት ገጽ<br />
መጻፍ መፈለጌን አስረግጥባት ዘንድ።<br />
አምላካችን ካደለን ጸጋ የተነሳ አሁንም<br />
ድረስ በምሕረቱ እና በበጎነቱ እንጠበቃለን።<br />
አሜን!!!<br />
እስትንፋሳችን ነውና ዛሬም እንጽፋለን።<br />
ለመሆኑ ለምንድን ነው የምንጽፈው?<br />
ሕገመንግሥቱ የሰጠን መብት ስለሆነ<br />
እንጽፋለን። ወይም አብጦና ጎርብጦ<br />
አልመቸን ያለ ነግር ሲኖርብን እንጽፍና<br />
እንተነፍሳለን። ወይም መጻፍ ሙያችን፣<br />
እንጀራችን ስለሆነ እንጽፋለን። እውነት<br />
እውነት እላችኋለሁ ከዚህ የተለየ አጀንዳም<br />
የለን። ያላቸው እንኳ ቢኖሩ እንደ ቡርቃ<br />
ዝምታ ደራሲ ስደት የእጃቸው እንደሚሆን<br />
አናጣውምና በሰብዓዊ ፍጡር እቃቃ<br />
ለመጫወት ብርቱም፣ ንቁም አንሆንም።<br />
አንድ ገጽ<br />
ኢትዮጵያ ሀገራችን ከሰለጠኑ ሀገራት<br />
እኩል የሰለጠነች ትሆን ዘንድ ይመኛሉ።<br />
የትምህርት አለመስፋፋት፣ የመሃይምነት<br />
መንገሥ ያስቆጫቸዋል። የፍትሕ<br />
መጓደል፣ የታናሽ መበደል፣ የንጹህ<br />
መገደል ያበሳጫቸዋል።<br />
ወገባቸውን በብርቱ ድግ አደግድገው ደፋ<br />
ቀና ይላሉ። ሀገራችውን ትሰለጥናለች<br />
ብለው ባሰቡበት መንገድ ሁሉ ያታትራሉ።<br />
የዘመን መምጣትና መሄድ፣ አለዚያም<br />
የግለሰብ መውጣትና መውረድ አይደለም<br />
የሚያሳስባቸው። የፍትሕ፣ የዴሞክራሲ፣<br />
የልማት፣ የሥልጣኔ በሀገሪቱ መስፈን<br />
ነው ጮቤ የሚያስረግጣቸው።<br />
ከድሃው ጋር ያለቅሳሉ። ከበላው ጋር<br />
ይስቃሉ። ከጭቁኑ ጋር ይታገላሉ። ነፃ<br />
ከወጣው ጋር ሻማ ይለኩሳሉ። ሁሉን<br />
በልኩ ያውቃሉ። ሁሉንም በየመጠኑ<br />
ይገነዘባሉ።<br />
በደሳለኝ ሥዩም<br />
3ኮመንትሪ<br />
ገጽ<br />
ስለገንዘብ ደንታ የላቸውም። ስለሥልጣን<br />
አይገዳቸውም። ስለኃብት አያሳስባቸውም።<br />
የማሳው በአዝርዕት መሸፈን፣ የሰብሉ አብቦ<br />
ማፍራት፣ የከብቶች ምቾት፣ የሜዳው<br />
መልካም ገጽ፣ የተራሮችን መዓዛ ቁርስ<br />
እና ምሳቸው አድርገው ያስቡታል።<br />
ኢትዮጵያ ተደፈረች ከተባለ ያለማንም<br />
ቀስቃሽ በቀረርቶና በሽለላ ኮራ እንዳሉ<br />
ከፊት ይሰለፋሉ። ጠመንጃ አንግተው<br />
ድንበር ያስከብራሉ። ሰንደቅ አላማዋን<br />
ሲያዩ በእንባ ይታጠባሉ።<br />
እኒህን የመሰሉ ዜጎች ባለፉት ጊዜያትና<br />
መንግሥታት አይተናል። በኖርንበት<br />
ዕድሜም ሁሉ አስተውለናል። ለሀገራቸው<br />
ፋይዳ ካልኖረው የማይማሩ፣ ለወገናቸው<br />
ካልጠቀመ ኃብት የማያከማቹ፣ በሁሉም<br />
ነገራቸው ሀገር እና ወገን ይቅደም ያሉ<br />
ምሁራን፣ ሠራተኞች፣ ነጋዴዎች፣ የኪነ-<br />
ጥበብ ባለሙያዎች፣ ወታደሮች፣ የልዩ<br />
ልዩ ሙያ ባለቤቶችን ይህች ሀገር ባለፉት<br />
ዘመን ሁሉ አፍርታለች። ባለንበትም<br />
ዘመን ሁሉ ታፈራለች።<br />
ሁለት ገጽ<br />
የሚምጉት አየር ደንታ የማይሰጣቸው፤<br />
የቆሙበት ምድር ምንማቸው የሆነ፤<br />
ወጥተው ለሚገቡበት ጎዳና ደንታ ቢስ<br />
የሆኑ እንዴት ናችሁ ለሚላቸው ሕዝብ<br />
ከበሬታ የማይሰጡ።<br />
የዘመናት መለወጥ፣ የመንግሥታት<br />
መገለባበጥ፣ የሰላም መደፍረስ፣ የጦርነት<br />
መቀስቀስ ስሜት የማይሰጣቸው፣<br />
የበሽታ ወረርሽኝ፣ የርሃብና የጎርፍ<br />
አደጋ፤ የድርቅና ድንገተኛ ቀውስ ሁሉ<br />
ትኩረታቸውን የማይስበው።<br />
ያገኙትን በልተው፣ ያሻቸውን ጠጥተው<br />
ካሰኛቸው ጋር አንሶላ ተጋፈው ጨለማው<br />
ነግቶ የነጋው ጨልሞ ለመፈራረቅ ይብቃ<br />
እንጂ ከዚህ በላይ ኑሮ የማይመቻቸው፤<br />
ከዚህ ወዲያ ኑሮ የማይታያቸው<br />
ከንቱዎችን ይህች ሀገር ትናንትም ዛሬም<br />
አፍርታለች።<br />
መኖር አይቆምምና ወደፊትም እነዚህ<br />
ግራ የገባቸው የትውልድ ‹‹ቀዝቃዛዎች››<br />
መፈልፈላቸው አይቀርም። ዜጎች ለሀገራዊ<br />
ዘመቻ ደፋ ቀና ሲሉ ኬሻ ሙሉ ጫት<br />
ዘርግፈው ላባቸውን በመሀረብ እየጠራረጉ<br />
ያመነዥካሉ። ሀገሪቱን ለማሳደግ<br />
ዜጎች በየእውቀታቸው፣ በየሙያቸው፣<br />
በየቦታቸው ሲረባረቡ ጆሮን የሚበጥስ<br />
ሙዚቃ አስከፍተው ለአይን እንዲያሳሱ<br />
ከተኳኳሉ እንስቶች ጋር በሀሽሽ ጥምብዝ<br />
ይላሉ። ከዚህ የዳንኪራ ቤታቸው ውጭ<br />
ያለው ሀገርና ህዝብ ለነሱ ምንም ነው።<br />
ለእያንዳንዱ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣<br />
ባህላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ፖለቲካዊ ጉዳይ<br />
የአስተዳደር ሀሁ አልገባውም<br />
የተፈለገው ወይስ እውነት ገበያውን<br />
ለማረጋጋትና ከህዝቡ ጋር ለመታረቅ?<br />
የሀገርን የኢኮኖሚ ደረጃና የህዝብን ኑሮ<br />
ለማሻሻል ግን እንደ እኔ የራሱን ሀገር<br />
ስራ ፈጣሪና ነጋዴ ማብዛትና መፍጠር<br />
የማያወላውል እርምጃ ይመስለኛል።<br />
ነገር ግን ከአለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር<br />
ለመታረቅ ሲባል እውነተኛውን ገሃድ<br />
የውስጥ ሀቃችንን አጣልተን መሆን<br />
የለበትም ባይ ነኝ።<br />
ክቡር ጠ/ሚኒስትሩ የንግድ<br />
ዘርፎችንና የመሬት አስተዳደርን<br />
ዘመናዊ እናደርጋለን ብለው ወዲህ<br />
ደግሞ ስለ ግብር ክፍያ <strong>ስር</strong>ዓት ሲጠየቁ<br />
ወይም ሲገመገሙ ‹‹አብዛኛው ነጋዴ<br />
እስከዛሬ ድረስ ሲከፍለው የኖረው<br />
መክፈል ከሚገባው በታች ነው። ይሁን<br />
እንጂ አሁን ግን መክፈል የሚባለውን<br />
ክፈል ሲባል አልከፍልም ማለቱ ነገሩ<br />
አወዛጋቢ አድርጎታል። አንዳንዱ ደግሞ<br />
መክፈል ከሚገባው በታች እየከፈለ<br />
በሙስና ኖሯል። በስነ-ምግባር ጉዳይም<br />
ችግር አለ፤ አስከፋዩ እራሱ ሌላ ነው፤<br />
ሌብነት አለ፤ ሌቦች እንደሆኑ እያወቅን<br />
ማስረጃ ስላጣን ግን ዝም ብለናቸው<br />
ኖረናል›› በማለት በራሱ የሚምታታ<br />
ሃሳብ ገልፀዋል። በመጀመሪያ ደረጃ<br />
ማስረጃ ከሌላቸው ሌቦች ለመሆናቸው<br />
ምን ማረጋገጫ አላቸው? ማስረጃ<br />
ይቀድማል ወይስ ማወቅ? ስለኑሮ<br />
ውድነትና ዕድገት ሲወራም በየትኛው<br />
የኢኮኖሚክስ ህግ እንደሆነ እንኳን<br />
ማጣቀሻ ሳይሰጡ ሀገር ሲያድግ የኑሮ<br />
ችግር ሊጠፋ አይችልም›› ብለው ተስፋ<br />
አስቆርጠውናል።<br />
እንደሚባኝ፣ ዘመናዊው የአንድ<br />
ሀገር የዕድገት መለኪያ (development<br />
measurement) እንደ ድሮው በGNP፣<br />
GDP፣ PCI በመሳሰሉት አይደለም።<br />
ይልቁንስ እነዚህ ባህላዊ መለኪያዎች<br />
ከሆኑ ሰነባበቱ። ነገር ግን ዘመናዊው<br />
መለኪያ የህዝቡ የኑሮ ደረጃና ብቃት<br />
ታይቶ ሲሆን፣ ይህም ሲባል በጤና፣<br />
በኢኮኖሚና እንዲሁም በማህበራዊ<br />
እንደ ትምህርት ጥራት የመሳሰሉትን<br />
በመገምገም ትክክለኛውን የህብረተሰቡን<br />
ህይወት በማየት የሚወሰን ነው።<br />
በመግለጫውም ላይ አላደግንም ለሚሉ<br />
አለማወቅ ነው ሲሉ መፍትሄ ብለው<br />
ያስቀሙጠት ደግሞ ይህን አለማወቅ<br />
ማስወገደ ነው የሚለውን ነው።<br />
ታላቁ ሶቅራጠስ፣ ‹‹አለማወቅን<br />
ማወቅ የእውቀት መጀመሪያ ነው››<br />
ብሎ ተናግሮ ነበር። ታዲያ ኢህአዴግ<br />
አሁን አለማወቅን ካለማወቁ ጭምር<br />
ይባስ ብሎ እሱ ያላወቀውን እውቀት<br />
ሳናውቅ እንድናውቅ በግድ ይገፋፋናል።<br />
እንደ’ኔ እምነት፣ በዚህ ጠ/ሚኒስትሩ<br />
ባቀረቡት ሪፖርት ላይ ኢህአዴግ<br />
አመርቂ ውጤት ያስመዘገበው ነገር<br />
ቢኖር የፀረ-ሽብርተኝነት ሕግ በማፅደቅና<br />
ሽብርተኞችን አሳዶ በመያዝ ሲሆን፣<br />
አሁንም በቅርብ ሳምንታት ውስጥ ወደ<br />
‹‹አለማወቅን ማወቅ የእውቀት መጀመሪያ ነው›› ብሎ ተናግሮ ነበር። ታዲያ<br />
ኢህአዴግ አሁን አለማወቅን ካለማወቁ ጭምር ይባስ ብሎ እሱ ያላወቀውን እውቀት<br />
ሳናውቅ እንድናውቅ በግድ ይገፋፋናል። እንደ’ኔ እምነት፣ በዚህ ጠ/ሚኒስትሩ ባቀረቡት<br />
ሪፖርት ላይ ኢህአዴግ አመርቂ ውጤት ያስመዘገበው ነገር ቢኖር የፀረ-ሽብርተኝነት ሕግ<br />
በማፅደቅና ሽብርተኞችን አሳዶ በመያዝ ሲሆን፣ አሁንም በቅርብ ሳምንታት ውስጥ ወደ ቃሊቲ<br />
የሚወረወሩ እንዳሉ ታገሱን ብለው እንድንጠባበቅ ነግረውናል።<br />
የሚቆርጡት ጮማ፣ የሚያንቆረቁሩት ውስኪ፣ የሚያሽከረክሩት መኪናና የሚሽከረከሩበት ወንበር ከእጃቸው<br />
እንዳይወጣ በ‹‹ለምን›› ባዮች ላይ የድንጋይ ናዳ የሚያወርዱ። ይህች ሀገር እኒህን የመሰሉ ዜጎችን ባለፉት<br />
ጊዜያትና መንግሥታት አፍርታ ታይታለች። በኖርንበትና ባለንት ዘመንም ይህ እውነታ ቀጥሏል።<br />
ቃሊቲ የሚወረወሩ እንዳሉ ታገሱን<br />
ብለው እንድንጠባበቅ ነግረውናል።<br />
የጋዜጠኝነት ሀሁ<br />
ያልገባቸው ባሉበት ወቅት<br />
ስለእውነት አፍሪካዊነቴን ጠላሁ።<br />
እነሆ በሰለጠኑት እንደ አሜሪካና<br />
እንግሊዝ ባሉት አይደለም፣ በሀገር<br />
ደረጃ ጠቅላላ ሕግ ይስተካከል ብሎ<br />
ለሚናገር ጋዜጠኛ፣ በግለሰብ ስም<br />
ጠርቶ ለሚሳደብና ለሚያንቋሽሽ<br />
ሰው እንኳን እ<strong>ስር</strong>ና እንግልት<br />
አይደርስበትም። ምክንያቱም ህዝብ<br />
የመሰለውን፣ የሚበጀውን እራሱ<br />
በገሀድ በመሬት ላይ ያለውን ፖለቲካ<br />
ስለሚያውቀው ከአንድ ግለሰብና<br />
ጋዜጠኛ እንዲሁም የፖለቲካ<br />
ፓርቲ ጋር እሰጣ’ገባ አይገባም፣<br />
አያሳድድም። ይልቁንስ ለእነሱ ይህ<br />
ጊዜን ማባከን ነው።<br />
በአጠቃላይ፣ ይህ ሁሉ<br />
እንቅስቃሴ የሚያሳየን መንግስት<br />
እራሱን ከመጠበቅ ባለፈ እውነትን<br />
ከመክደን በዘለለ ትልቅ ስራ<br />
እንደሌለው ነው። ይህም ሲባል<br />
ከሌሎች የሥራ ዘርፎች ይልቅ የፀረ-<br />
ሽብርተኝነት እንቅስቃሴው እራሱን<br />
የቻለ ቦርድ አቋቁሞ ለዛውም ምርጥ<br />
ከተባሉት ከነእንግሊዝ ሕጉን ኮፒ<br />
አድርገው ሲንቀሳቀሱ ሲታይ ምን<br />
ያህል አንገብጋቢ ሥራ እንደነበረበት<br />
ያሳያል። ምናለ እንደው ለሌላው<br />
እውነተኛ የኑሮ ውጥንቅጣችን<br />
እንዲህ ምርጥ ከሚባለው ሀገር<br />
ፖሊሲ ኮፒ ቢያደርጉልን!<br />
አለበለዚያ አንገብጋቢውን ትተው፣<br />
ለፍርሀታቸው የሚሰሩ ከሆነ፣<br />
እኛ ሳንሆን እነርሱ ናቸው ሀሁው<br />
ያልገባቸው።<br />
ሁሉ ግድ የለሽና ባዕድ ናቸው። ምንም<br />
አይሞቃቸው፣ ምንምም አይበርዳቸው።<br />
እነዚሀ ሁለተኛ የዜጎች ገጽታ መሆናቸው<br />
ነው።<br />
ሶስት ገጽ<br />
የሰዎችን ደም በጽዋ እየተቀባበሉ<br />
መጎንጨት የሚዳዳቸው፤ በጎ ነገር ለሀገር፣<br />
ለህዝብ ስለተሰራ ብቻ የሚያማቸው፤<br />
መልካም ሰውን አጋድመው ካልገፈፉ<br />
በስተቀር ሰላም የማይሰማቸው።<br />
የተባረኩት የተከሉትን ችግኝ ከጫፉ<br />
ቀንጥሰው መጣል የእርካታቸው ምንጭ<br />
የሆነ፤ በለመለመ መስክ ላይ ቤንዚን<br />
ማርከፍከፍ ውዴታቸው የሆነ። የተማሩ<br />
ሰዎችን ሲያዩ የሚነስራቸው። የምሁራንን<br />
ሐሳብ ማዳመጥ ውድቀት የሚመስላቸው<br />
ዜጎች።<br />
ክርስቶስ እንዲሰቀል በርባን ግን እንዲፈታ<br />
ከመጮኽ አልፈው ሐሳባችንን ደግፉ፣<br />
አብራችሁ ጩኹ፤ ካልጮኻችሁ<br />
እንገድላችኋለን ብለው አንባጓሮ ሚያነሱ፤<br />
አዎንታዊ ሐሳብ በአእምሯቸው ታስቧቸው<br />
የማያውቅ፤ የራበው ድሃ አስፓልት ዳር<br />
ወድቆ ሲቆራመድ አጥንቱን እየቆጠሩ<br />
ፈገግ የሚሉ።<br />
የሚቆርጡት ጮማ፣ የሚያንቆረቁሩት<br />
ውስኪ፣ የሚያሽከረክሩት መኪናና<br />
የሚሽከረከሩበት ወንበር ከእጃቸው<br />
እንዳይወጣ በ‹‹ለምን›› ባዮች ላይ የድንጋይ<br />
ናዳ የሚያወርዱ።<br />
ይህች ሀገር እኒህን የመሰሉ ዜጎችን<br />
ባለፉት ጊዜያትና መንግሥታት አፍርታ<br />
ታይታለች። በኖርንበትና ባለንት ዘመንም<br />
ይህ እውነታ ቀጥሏል። የሚያብለጨልጭ<br />
ብረት ከሰው ላይ ለመውሰድ ጣትን<br />
ወይም አንገትን ቆርጠው በኪሳቸው<br />
የሚደብቁ፤ ሥልጣኔን መናፈቅ፣<br />
ዴሞክራሲን መስበክ፣ ልማትን ማምጣት<br />
ለምላሳቸው እንጂ ለጭንቅላታቸው ሥራ<br />
ያልሆነላቸው። እኒህ ሶስተኛ ገጽ ዜጎች<br />
መሆናቸው ነው።<br />
ለእነዚህ ማሳያ የሚሆኑት ደግሞ ሁሌም<br />
አዲስ የመከራ ዘመን በሚያበስረው አዲስ<br />
ዘመን ጋዜጣ ላይ የነገሱት ናቸው።<br />
የብዕር አጣጣሉ ሁሌም አንድ ነው።<br />
እገሌ ከ --- (ቦታ) እየተባለ ሥም<br />
ይሰጠው እንጂ ሀሳብን ሳይሆን የፖለቲካ<br />
ትንታኔን፣ የውሳኔ ሀሳብን፣ የመረረ<br />
ጥላቻን የሚያራምድ አንድ መደበኛ<br />
ግለሰብ እንደሚጽፈው ለሚያነቡ ሁሉ<br />
የሚሰወር እውነታ አይደለም።<br />
ብዙ ጊዜ ስድብ ይጻፍበታል። ግለሰቦችና<br />
የግል ሚዲያዎች ይዘለፉበታል - የአዲስ<br />
ዘመኑ ገጽ ሶስት። ካልታሰሩ፣ ካልተዘጉ<br />
ሞቼ እገኛለሁ ይባልበታል። ስለዴሞክራሲ<br />
በሚወራበት ሀገር በአንድ ሰላማዊ<br />
ዜጋ ‹‹ሥም›› እየተጻፈ ግለሰቦች ክፉኛ<br />
ይኮነኑበታል።<br />
አዲስ ዘመን በመሰረቱ ገጽ ሶስትን<br />
እንደተባለው ለተለያዩ ሐሳቦች<br />
ማንሸራሸሪያነት እያዋለው እንዳልሆነ<br />
ይታወቃል። ግን እስኪ የመንግሥትን፣<br />
የፖሊስን፣ የፍርድ ቤትን፣ የይቅርታ<br />
ቦርድን ወዘተ. ኃላፊነትና ሥልጣን ትቶ<br />
ወይም ጣልቃ ገብቶ የሚፈተፍት ጽሑፍ<br />
ማስተናገድ ጋዜጣውን እንደሚያስንቀው<br />
አጥተውት ነው? ሌላው ሁሉ ቀርቶ<br />
ማለቴ ነው።<br />
ይሄኔ የአዲስ ዘመን ቅርጫት ቢፈተሸ<br />
ስለእያንዳንዱ ስድባቸው እንደናቋቸው<br />
የሚገልጹ የብዙ አንባቢዎች የቅሬታና<br />
የቁጣ ደብዳቤ ብዛት ምን ያህል ይሆን?<br />
እስቲ በ’ኔ ሞት የመቀመጫዋን ጉድ<br />
ያላስተዋለች ዝንጀሮ ምሳሌ ከአዲስ ዘመን<br />
ውጭ ለሌላ የሚጠቀስ ምሳሌ መሆን<br />
ነበረበት?<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
7
8<br />
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />
የአንበሳ አውቶቡስ ጉዞ እና ገጠመኞች<br />
በናፍቆት ዮሴፍ<br />
“ሰፈሬ ሽሮ ሜዳ እንደመሆኑ ከመርካቶ<br />
17 ቁጥር አውቶቡስን ተሳፍሬ<br />
ቅድስት ማሪያም ቤ/ክ ስንደርስ፣ አንድ<br />
አዛውንት ኡኡታ አሰሙ ‹አውቶቡሱ<br />
ሳይከፈት ወደ ፖሊስ ጣቢያ ይሂድልኝ›<br />
ሲሉ ሹፌሩን ተማጠኑ፤ ሶስት ሺህ ብር<br />
ተወስዶብኛል በሚል። ሹፌሩም አራት<br />
ኪሎ አካባቢ (አሁን ፈርሷል) ፖሊስ<br />
ጣቢያ አውቶቡሱን ይዘው ገቡ። ሁሉም<br />
ሰው እንዲወርድ ተደረገ። ምን ዋጋ<br />
አለው ሌባው ቀድሞ ወርዶስ ቢሆንስ<br />
እያልን ወረድን<br />
“የሆነ ሆኖ ሁሉም ሰው ወርዶ እንዲፈተሽ በአንድ<br />
መቶ አለቃ ትዕዛዝ ከተላለፈ ከደቂቃዎች በኋላ<br />
መቶ አለቃው ‹ሌባው ስለተገኘ ፍትሻውን አቁሙ›<br />
ሲል ለባልደረቦቹ ትዕዛዝ አስተላለፈ። እጅግ መልከ<br />
መልካም፣ አራቱም ጣቶቿ ላይ ወርቅ የደረደረች፣<br />
አለባበሷ በእጅጉ የተዋበ ወጣት ላይ የመቶ አለቃው<br />
አይን አረፈ።<br />
“የወሰድሽውን ብር አምጪ” ብሎ ሲያምባርቅባት<br />
የሁላችንም እጢ ዱብ አለ። “የምን ብር!? የሰውን<br />
ማንነት ሳታውቅ አትናገር” ስትል ኮስተር ያለ መልስ<br />
ሰነዘረች ወጣቷ። ይሁን እንጂ መቶ አለቃው፣<br />
“ገብተሽ በጉማሬ አለንጋ ስትሞሸለቂ ታወጪ የለ?”<br />
በማለት እየጎተተ ወሰዳት።<br />
17 ቁጥር አውቶቡስ እና እኛ ተሳፋሪዎች ፖሊስ<br />
ጣቢያው ውስጥ እንደተገተርን ደቂቃዎች፣ ብሎም<br />
ሰዓታት አለፉ። ብዙ እናቶችና አባቶች፣ “ፍፁም<br />
አታደርገውም፤ ለሌላ ጉዳይ ፈልጓት ይሆናል” ሲሉ<br />
አጉተመተሙ። ልጅቷ ጠንከር ያለ አለንጋ ሳትቀምስ<br />
አልቀረችም፣ “እሺ ተወኝ፤ የደበቅሁበትን ላሳይህ”<br />
ስትል መሬት ተሰንጥቃ ብትውጠኝ ደስተኛ ነበርኩ።<br />
በርካታው የአውቶቡሷ ተሳፋሪዎች የሚሆነውን<br />
ለማየት አሰፈሰፍን። ልጅቷም ፖሊሱን እየመራች<br />
የአውቶቡሷ መጨረሻ ወንበር ወደሚገኝበት ሄደች።<br />
ሁሉም ይህን ጉድ ለማየት አሰፈሰፉ። የመጨረሻው<br />
ወንበር ስትደርስ ሶስት ሺህ ብር ሶስት ቦታ በብር<br />
ላስቲክ የታሰረ ስለነበር ከዛን በፊት አይቼው<br />
በማላውቀው አይነት ወፍራም ፕላስተር ከወንበሩ<br />
<strong>ስር</strong> ሶስት ቦታ አጣብቃዋቸለች። እሱን እየፈታች<br />
ለፖሊሱ ስትሰጥ ያልደረሰባት የእርግማን እና የስድብ<br />
አይነት አልነበረም። እኔ አፌ በድንጋጤ ተለጉሟል፤<br />
በኋላ ግን “እንዴት ልታውቃት ቻልክ?” ስል መቶ<br />
አለቃውን በድንገት ብጠይቀው፣ “<strong>አገር</strong> ምድሩን<br />
ያጥለጠለቀው የእሷ ፎቶ ነው። ከዚህ በፊት በርካታ<br />
የ<strong>ስር</strong>ቆት ሪከርድ አለባት። ስንት ጊዜ መሰለህ ታስራ<br />
የተፈታችው?” ሲል ምላሽ ሰጠኝ። እሷም ታሰረች፣<br />
እኛም አውቶቡሳችን ውስጥ ገብተን ወደየምንሄድበት<br />
ጉዟችንን ቀጠልን። የወጣቷም ያለመጠርጠር ጥረት<br />
በዚህ አበቃ።”<br />
ይህ ከላይ ያስነበብናችሁ ገጠመኝ አቶ ጥላሁን<br />
ገዳሙ የተባሉ የ56 ዓመት ጎልማሳ ከ13 ዓመት<br />
በፊት በአውቶቡስ ውስጥ ያጋጠማቸው እውነታ<br />
ነው። አንበሳ የከተማ አውቶቡስ ከ1935 ዓ.ም ጀምሮ<br />
በተለይም ዝቅተኛና መካከለኛ የኑሮ ደረጃ ላላቸው<br />
የህብረተሰብ ክፍሎች የማይረሳ ውለታ ባለቤት ነው።<br />
ምንም እንኳን በአሁኑ ሰዓት የሀብታምና የድሀው<br />
ልዩነት የሰማይና የምድርን ያህል ርቆ መካከለኛ<br />
የኑሮ ደረጃ (Middle class) የሚባለው የህብረተሰብ<br />
ክፍል የለም ብለን ለመናገር በሚያስችለን ደረጃ ላይ<br />
ብንደርስም።<br />
በአንበሳ የከተማ አውቶበስ ውስጥ እጅግ አስገራሚ፣<br />
አሳዛኝ፣ አዝናኝና የተደበላለቀ ስሜትን የሚፈጥሩ<br />
ትዕይንቶች የሚከሰቱበት የመጓጓዣ አውታር መሆኑን<br />
ከማንም በላይ ተጠቃሚዎቹ ጠንቅቀው ያውቁታል።<br />
ለዛሬም የተሳፋሪዎችን፣ የትኬት ቆራጮችን እና<br />
የአንበሳ አውቶቡስ ሹፌሮችን ገጠመኞች እንቃኝ።<br />
ከዚያ በፊት ግን ስለአንበሳ አውቶቡስ አገልግሎት<br />
ጅማሮና የስራ ዘመኑ ጥቂት ማለት አግባብ ነውና<br />
እነሆ።<br />
ወራሪው የፋሺስት ጣሊያን መንግስት ሀገራችን ውስጥ<br />
በነበረበት ጊዜ ይጠቀምባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችንና<br />
የመኪና መለዋወጫ እቃዎችን በማሰባሰብ የስራና<br />
መገናኛ ሚኒስቴር ይባል በነበረው መ/ቤት አማካኝነት<br />
በ1935 ዓ.ም “የህዝብ ማመላለሻ” (ሕ.ማ) በሚል<br />
ስም ነበር የተመሰረተው - አንበሳ የከተማ አውቶበስ<br />
አገልግሎት።<br />
ታህሳስ 2 ቀን 1944 ዓ.ም ህጋዊ ሰውነት በማግኘት<br />
በአክሲዮን ከተቋቋመ በኋላ አረንጓዴና ቢጫ የተቀቡ<br />
10 አውቶቡሶችን ይዞ ሥራ መጀመሩን የድርጅቱ<br />
ማህደር ያመለክታል፤ እነዚህ አውቶቡሶች በከተማዋ<br />
አራት መስመሮች ላይ የተሰማሩ እንደነበር ይነገራል።<br />
ለህብረተሰቡ አገልግሎት ይሰጥ የነበረው የቀድሞው<br />
ህዝብ ማመላለሻ የአሁኑ አንበሳ አውቶቡስ በዚያን<br />
ወቅት የውጭ <strong>አገር</strong> ዜጎችን ጨምሮ 120 ሰራተኞች<br />
ነበሩት።<br />
በ1952 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይሰጥ የነበረው ትራንስፖርት<br />
አገልግሎት መስመሩ ከ4 ወደ 14 እንዲያድግ ሲደረግ<br />
በየመስመሩ ሲመደቡ የነበሩ አውቶብሶች ብዛትም<br />
ከሁለት ወደ ሶስት ከፍ እንዲል ተደረገ። እንዲህ<br />
እንዲህ አያለ በ1986 ዓ.ም በአዋጅ ቁጥር 187/1986<br />
በ14 ሚሊዮን ብር ካፒታል “አንበሳ የከተማ አውቶቡስ<br />
አገልግሎት ድርጅት” ተብሎ በአዲስ መልክ ራሱን<br />
ችሎ ከተቋቋመ በኋላ በየጊዜው ቁጥሩ እየጨመረ<br />
የሚሄደውን የከተማዋን ህዝብ ፍላጎት ለማሟላት<br />
በተለያዩ ጊዜያት በርካታ አውቶቡሶችን በእርዳታና<br />
በግዢ በማስመጣት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።<br />
በአሁን ሰዓት ድርጅቱ አዳዲስ 120 አውቶቡሶችን<br />
ያስገባ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ አስሩ 18 ሜትር<br />
እርዝመት ያላቸው፤ ተቀጣጣይ - አራዶች አኮርዲዮን<br />
ይሏቸዋል - እንደሆኑ ከድርጅቱ የህዝብ ግንኙነት<br />
ኦፊሰር ከአቶ ሸዋረጋ ሳህሌ ለመረዳት ችለናል።<br />
ድርጅቱ በአሁኑ ወቅት በቀን 320 አውቶቡሶችን<br />
ለስራ እንደሚያሰማራ የነገሩን አቶ ሸዋረጋ፣ ከ2740<br />
በላይ ቋሚ ሰራተኞች እንዳሉትም ነግረውናል።<br />
ስለአንበሳ አውቶቡስ አመሰራረት በጥቂቱ ከነገርናችሁ<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
ልዩ ቅኝት<br />
ወደ ዋናው ሃሳባችን እንሆ ተመልሰናል።<br />
የአንበሳ አጋጣሚዎች<br />
አንበሳ አውቶቡስ ውስጥ ብዙ የሚከሰቱ ነገሮች<br />
አንዳሉ ይደመጣል። በተለይ ደግሞ በሚፈጠረው<br />
መተፋፈግና መነካካት የወንዶች ስሜት እንደሚነሳሳ<br />
ይነገራል። የዚህ ሰለባ የሆነ አንድ ወጣት ተከታዩን<br />
አጫውቶኛል፡- “ሁለት ወንዶችና አንድ ወጣት ሴት<br />
ወደተሳፈርኩበት አውቶብስ ሲገቡ ተመለከትኩ።<br />
ሆኖም ሴቷ ወደ እኔ በመጠጋት ትተሻሸኝ ጀመር።<br />
ሁኔታዋ ሁሉ እኔን ወደ ሌላ ስሜት ውስጥ ከተተኝ።<br />
በወቅቱ አውቶቡሱ ውስጥ ካሉት ወንዶች ውስጥ<br />
ይህቺ ቆንጆ እኔን መርጣ በዚያ ሁኔታ ላይ መገኘቷ<br />
ኩራት እንዲሰማኝ አድርጎኛል” ይላል ወጣቱ። ይሁን<br />
እንጂ ወጣቱ በቆንጆዋ ሁኔታ ተማርኮ ስሜቱን<br />
ሲያዳምጥ አብረዋት የነበሩት ሁለት ወንዶች ከኪሱ<br />
1ሺህ አንድ መቶ ብር ሰርቀውት ከወረዱ በኋላ<br />
መባነኑን ያስታውሳል። ቆንጆዋ ማደንዘዣ መሆኗ<br />
ነው።<br />
በአንድ ወቅት ነው አንድ ወጣት 19 ቁጥር አውቶቡስ<br />
ውስጥ ተሳፍሮ ወደ አስኮ እየተጓዘ ነው። አንድ<br />
ትልቅ አዛውንት ካፖርት ለብሰው ቆመዋል። “አባት<br />
ልነሳልዎትና ወንበር ላይ ይቀመጡ አልኳቸው። ግን<br />
ፈቃደኛ አልሆኑም” የሚለው ይህ ወጣት፣ መውረጃው<br />
ሲቀርብ ለመውረድ ከወንበሩ ይነሳል። አዛውንቱ<br />
የያዙትን ብረት ይዞ አውቶቡሱ እስኪቆም ለመጠበቅ<br />
ሲሞክር አውቶቡሱ ይንገጫገጭና ልጁ ሚዛኑን<br />
ይስታል። እናም የሚይዘው ሲያጣ ተንደርድሮ<br />
የአዛውንቱ የካፖርት ኪስ ውስጥ ዘው ይላል።<br />
አዛውንት ሆዬ ካፖርታቸው ኪስ ውስጥ ያለውን እጅ<br />
ይይዙና እሪ ይላሉ። አውቶቡሱ ቆሞ ልጅና አዛውንቱ<br />
ተያይዘው ፖሊስ ይደርሳል። “በህይወቴ አንደዚያ ያለ<br />
ቅሌት ገጥሞኝ አያውቅም። በስንቱ ታቦት ብምል፣<br />
ብገዘት ሰውየው ሊያምኑኝ አልቻሉም። ስለዚህ ጉዳዩ<br />
እስኪጣራ ፖሊስ ጣቢያ አምሽቻለሁ” ሲል ባላሰበበት<br />
መዋሉን ይናገራል።<br />
ራሄል ይስማው ላፉት ስምንት አመታት የአውቶቡስ<br />
ትኬት ቆራጭ ሆና ሰርታለች። በስራዋም ብዙ<br />
ገጠመኞች አሏት። “አንድ ቀን 53 ቁጥር አውቶቡስ<br />
ላይ እየሰራሁ ቲኬት ፈታሽ ይመጣል። አንዱ ትኬቱን<br />
ጥሎት ስለነበር ፈታሹ ሁለት እጥፍ እንዲከፍል<br />
ያስገድደዋል። ልጁ ዘና ብሎ፣ “እሺ እከፍላለሁ”<br />
ብሎ ኪሱ ሲገባ ቦርሳው ተወስዷል” የምትለው<br />
ራሄል፣ በዛን ሰዓት የነበረውን ድንጋጤ አሁንም<br />
እንደምታስታውሰው ትናገራለች። በመጨረሻም<br />
ሁኔታውን ሳይ እኔ ከፈልኩለት። እሱም ሌላ ቀን<br />
እንደሚከፍል ነግሯት ስልኳን ተቀብሎ መውረዱን፣<br />
በዚህም የተነሳ ለረጅም ጊዜ የፍቅር ጓደኛሞች ሆነው<br />
መቆየታቸውን ትናገራለች።<br />
ሞኖ ባንዶች<br />
አውቶቡስ ውስጥ ሲጓዙ ምንም ድምፅ ሳይኖራቸው<br />
የሚዘፍኑ አስቂኝ ማስታወቂያዎችን በመናገር<br />
ከተሳፋሪው የሚቀፍሉ (የሚያባብሉ) [ዘመናዊ<br />
የልመና አይነት ነው] በርካቶች ናቸው። እንደእነዚህ<br />
አይነቶቹን ሰዎች እርሶ በተለይ አውቶቡስ ተጠቃሚ<br />
ከሆኑ በተለያዩ ቁጥር አውቶቡሶች ላይ ያገኟቸዋል።<br />
ራሳቸውን “ሞኖ ባንድ” እያሉ የሚጠሩም ያጋጥማሉ።<br />
“ሞኖ ባንድ እንሰኛለን። እናንተን ለማዝናናት ምንጊዜም<br />
ዝግጁ ነን። ይህን ማይክ የሰጠን እንዲህ አይነት<br />
ሙዚቃ መሳሪያ አስመጪ ድርጅት ነው። የክብር<br />
ስፖንሰራችን ደግሞ አንበሳ የከተማ አውቶቡስ ነው”<br />
እና መሰል ነገሮችን በመደርደር ዘመናዊ ልመናዎች<br />
ይካሄድበታል። አይ አንበሳ አውቶቡስ፤ “በእኔና በባስ<br />
የማይመጣ የለም” ያለው ማን ነበር?<br />
ቀዶ ጥገና<br />
ቀዶ ጥገና ስንል የህክምናውን እንዳይመስልዎ።<br />
በአውቶቡስ ውስጥም የቀዶ ጥገና በርካታ<br />
ስፔሻሊስቶች እንዳሉ ልንጠቁምዎ እንጂ። በአንድ<br />
ወቅት አንድ ጓደኛዬ የገጠመውን እንዲህ አጫዎተኝ።<br />
ሰውየው ከጎጃም በርካታ ማር ጭነው አዲስ አበባ<br />
ለነጋዴ ያስረክባሉ። እናም የዋሁና ገራገሩ የገጠር<br />
ሰው በከረጢት ብራቸውን አንግተው ከኮታቸው <strong>ስር</strong><br />
አንጠልጥለዋል። ከዚያም ወደ ማረፊያቸው ይሄው<br />
ጓደኛዬ ወደተሳፈረበት ስምንት ቁጥር አውቶቡስ<br />
ውስጥ ይሳፈራሉ። አውቶቡሱ ትንሽ እንደተጓዘ<br />
ቀዶ ጠጋኙ የሰውየውን ከረጢት (የሚጋፋ መስሎ)<br />
በመቀስ ይሁን በምላጭ ከስሩ ይሸረክትና ብሩን በ<strong>ስር</strong><br />
በኩል ወስዶ አንዱ ፌርማታ ላይ ዱብ ይላል። ያኔ<br />
አንገታቸው የቀለላቸው የማር ነጋዴ ደረታቸውን<br />
ቢዳብሱ ጊዜ የከረጢታቸው ሆድ መቆዘሩ ቀርቶ ባዶ<br />
ሆኗል።<br />
እናም ሰውየው ኡኡ አሉ እንዲህ እያሉ፡- “እሪ<br />
በል ሸዋ ጎጃም ተበላ እሪ በል ሸዋ ጎጃም ተበላ”።<br />
እንዲህ ያሰኛሉ ቀዶ ጠጋኞች። ይህን የሰማ አንድ<br />
ሌላ ሰው እንዳጫወተኝ ሁለት ጓደኛሞች እቃ ሊገዙ<br />
መርካቶ ይሄዳሉ። አውቶቡስ ፌርማታው ላይ እያሉ<br />
የአንዱ ስልክ ከኪሱ ይጠፋል። ሌላው ጓኛውን፣<br />
“እንዴት ኪስህ ውስጥ ትይዛለህ” በማለት ተቆጣው።<br />
ምክንያቱም እርሱ ሞባይል ስልኩን በማንጠልጠያ<br />
አንገቱ ላይ አንጠልጥሎ ስልኩን ደረት ኪሱ ነው<br />
የሚያስቀምጠው። እናም፣ “አሁን በቃ ተወስዷል።<br />
ለሌላ ጊዜ አንደኔ እንዲህ አድርገህ ያዝ” ብሎ አንገቱ<br />
ላይ ያለውን የስልክ ገመድ ሲስበው ስልኩ ተወስዶ<br />
ገመዱ ብቻ ነው የቀረው። ኪሱን ቀዶ ጠጋኞቹ ቀደው<br />
ስልኩን ወስደዋል። እንዲህ ናቸው ቀዶ ጠጋኞች፤<br />
ከደረት ውስጥ ልብን ለመውሰድ ከአይን ላይ ኩል<br />
ለመንጠቅ ረቀቅ ያለ ሰርጀሪ ይሰራሉ። ከእነርሱ<br />
ይሰውረን ብሎ መፀለይ መልካም ነው።<br />
“አንዴ ነው እቃ ለመግዛት በርከት ያለ ብር ይዤ<br />
አውቶቡስ ውስጥ ነኝ። አንዱ ወጠምሻ አጠገቤ<br />
ቆሟል። ይተሻሸኛል፤ ይገፋኛል። ‘ለምን ራስህን ችለህ<br />
አትቆምም’ ስል ገሰፅኩት። ሆኖም ሊተወኝ አልቻለም”<br />
ትላለች ለገሀር 32 ቁጥርን ስትጠብቅ ያገኘኋት<br />
የትምወርቅ። ግፊያውና ፍትጊያው ሲሰለቻት አምርራ<br />
መቆጣቷን የምትናገረው የትምወርቅ፣ “ቆይ ከእኔ<br />
ምን ፈልገህ ነው እንዲህ የምትሆነው ብለው፣ ‘አንቺ<br />
ገገምሽ አንጂ እኔማ ያጨቅሽውን ብር አይቼ ነው’<br />
አለኝ - አይኑን በጨው አጥቦ፤ እንዴት አወቅክ<br />
ብለው፣ ‘ከፈለግሽ አንኳን ቦርሳሽን ከ<strong>ስር</strong> የለበሽውን<br />
የውስጥ ሱሪ ቀለም እነግርሻለሁ’ በማለት ቀልቤን<br />
በድንጋጤ ገፈፈው” በማለት በጥርጣሬዋ ከሰርጀሪ<br />
መዳኗን ታስታውሳለች። እነዚህ ቀዶ ጠጋኞች ቦርሳን<br />
ብቻ ሳይሆን ውስጥንም ራጅ ማንሳት ይችላሉ እንዴ?<br />
ያስብላል።<br />
የቡድን ሥራ<br />
አውቶቡስ ውስጥ ከሚፈጠሩ አጋጣሚዎች ውስጥ<br />
የረቀቀው የሌቦች የቡድን ስራ ይጠቀሳል። ለዚህም<br />
የተለያዩ ዘዴዎች ይፈበረካሉ። ከላይ እንደጠቀስነው<br />
በሴት ተማርኮ ሲፈዝ ጓደኞቿ የሰረቁት አንድ ሺህ<br />
አንድ መቶ ብር አንዱ የቡድን ስራቸው ውጤት<br />
ነው። ‹‹የተግባረዕድ ተማሪ ሆኜ በአውቶቡስ ነበር<br />
የምመላለሰው። እናም በወቅቱ የወር ክፍያ 48 ብር<br />
ይዣለሁ›› በማለት ገጠመኙን የጀመረው ችሎታው<br />
የተባለ ወጣት በወቅቱ በርከት ያሉ ወጣቶች አውቶቡስ<br />
ውስጥ ገብተው በተንተን ብለው መቆማቸውን<br />
ያስታውሳል። ከመካከላቸው አንዱ እጅግ ተጫዋችና<br />
ሲበዛ ቀልድ አዋቂ ተሳፋሪዎች በሱ ጫወታ ሲፈዙ<br />
ሌሎቹ ወደ ስራቸው ይሰማራሉ። ‹‹እኔንም የገጠመኝ<br />
ይሄው ነው በልጁ ወሬ ተመስጨ ስፈዝ ለካስ ጓደኛው<br />
ኪሴ ገብቶ 48 ብሩን ሊወስድ ይታገላል። በወቅቱ<br />
ጠበብ ያለ ጅንስ ስለለበስኩ እጁ ሲነካኝ ነቃሁ››<br />
በማለት እንዴት እንደተረፈ የሚገልፀው ችሎታው<br />
አሁን ረቀቅ ያሉ ገፋፊዎች ስለተበራከቱ መጠንቀቅ<br />
አንደሚያሻ ይመክራል።<br />
መልካም አጋጣሚዎች<br />
አንድ ነገር መጥፎ ጎን እንዳለው ሁሉ መልካም<br />
ጎኖችም አይጠፉትም። የከተማ አውቶቡሶችም<br />
እንዲሁ። <strong>ስር</strong>ቆቱ ጾታዊ ትንኮሳውና መሰል ጥሩ<br />
ያልሆኑ አጋጣሚዎች የሚፈጠሩ ቢሆንም መልካም<br />
ነገርም ጎን ለጎን ይኖራል። ስማቸውን መናገር<br />
ያልፈለጉ አንድ ጎልማሳ በአንበሳ አውቶቡስ ውስጥ<br />
ለ17 አመታት አገልግለዋል። ድርጊቱ በተፈፀመበት<br />
እለት ጠዋት ተነስተው በስራ ላይ ተገኝተዋል።<br />
ሲያሸከረክሩ ውለው ከቀኑ ወደ 10 ሰዓት አካባቢ<br />
ድንገት ታመው አውቶቡሱን መንዳት ያቅታቸዋል።<br />
መሀል አስፋልት ላይ መኪናው ቀጥ ብሎ ይቆማል።<br />
‹‹ምን እንደነካኝ ሳላውቅ ራሴን እንደመሳት አደረገኝ።<br />
ምን እንደተፈጠረ አላውቅም ነበር›› የሚሉት እኚህ<br />
ግለሰብ ከዚያም አንድ መስፍን የተባለ ወጣት እሳቸውን<br />
አስነስቶ መሪውን በመጨበጥ ህዝቡን የሚፈልግበት<br />
አድርሶ እርሳቸውንም ሀኪም ቤት ወስዶ ማሳከሙን<br />
ያስታውሳሉ።<br />
ሙሉጌታ የ60 ቁጥር አውቶቡስ ደንበኛ ነው።<br />
ሁሌም ከአዲስ አበባ ደብረዘይት ከደብረዘይት አዲስ<br />
አበባ ለመመላለስ ይህቺ አውቶቡስ ባለውለታው ናት።<br />
ምክንያቱም በዛን ወቅት በአየር ኃይል ውስጥ ሬዲዮ<br />
ኦፕሬተር ሆኖ ይሰራ ስለነበር ሁሌም ጠዋትና ማታ<br />
ተመላላሽ ነው። ከሳምንቱ በአንዱ ቀን ከአየር ሀይል<br />
ግቢ ስራውን አጠናቆ 60 ቁጥር ውስጥ ይገባል።<br />
አውቶቡሱ ተጨናንቆ ስለነበር አንዲት ሴት ቦርሳዋን<br />
እንዲይዝላት ትጠይቀዋለች። ይቀበላልም። ‹‹ቦርሳውን<br />
ስትሰጠኝ መልኳን ልብ ብዬ አላየሁትም በኋላ ግን<br />
ወደ አዲስ አበባ እየቀረብን ስንመጣ እንዴት ቦርሳዋን<br />
አትጠይቀኝም እያልኩ አስብ ጀመር። ምክንያቱም ሰው<br />
መንገድ ላይ እየወረደ አውቶቡሱ ቀለል ብሎ ስለነበር”<br />
ይላል። ይሁን እንጂ አውቶቡሱ ለገሀር ደርሶ ሁሉም<br />
ሰው ሲወርድ የቦርሳው ባለቤት የለችም ግራ ገባው።<br />
‹‹ባለቦርሳ ብዬ እንዳልጠራ አንዷ ተነስታ የኔ ነው<br />
ብትለኝስ ብዬ ዝም አልኩ›› ይላል ሙሉጌታ። እናም<br />
በወቅቱ ቦርሳውን ወደቤቱ ይዞ ይሄድና መፈተሽ<br />
ይጀምራል። በውስጡም ፖስፖርት፣ 5 ሺህ ጥሬ<br />
ብር፣ የ19 ሺህ 500 ብር ቼክ፣ ሌሎች ወረቀቶች፣<br />
የቀበሌ መታወቂያና የእጅ ሰዓት በቦርሳው ውስጥ<br />
መኖሩን ማረጋገጡን ያስታውሳል። ‹‹ከራሴ ጋር<br />
ብዙ ተሟገትኩ። መታወቂያው ላይ ባገኘሁት ስልክ<br />
ልደውል አልደውል በሚል። -ደውልላት የሚለው ሀሳቤ<br />
በማመዘኑ ደወልኩላት›› በማለት የነበረበትን የሀሳብ<br />
አጣብቂኝ ይናገራል። ሙሉጌታ ስልኩን በደወለ ጊዜ<br />
ያነሳው ወንድ ነበር። ስለሁኔታው ሲነግረው ‹‹መልሰን<br />
እንደውል ትንሽ ችግር አጋጥሟት አልተረጋጋችም››<br />
ብሎ አንደመለሰለት ከገለፀ በኋላ በዛን ወቅት<br />
ተንቀሳቃሽ ስልክ ስላልነበረው የእናቱን የቤት ስልክ<br />
ቁጥር መስጠቱን ይናገራል። ‹‹ደወለችልኝ ከዚያም<br />
እናቷ በድንገት ታመው አደጋ ውስጥ እንደነበሩ<br />
ስትሰማ ገና ዱከም ስትደርስ ደንግጣ አንደወረደችና<br />
ፈፅሞ ቦርሳውን እንዳላስታወሰች ነገረችኝ›› ይላል<br />
ሙሉጌታ።<br />
ልክ በአራተኛው ቀን ደውላ ደብረዘይት ከመጣ<br />
እንዲያቀብላት መጠየቋን የሚገልፀው ይህ ወጣት<br />
ቦርሳውን ይዞ ደብረ ዘይት ይሄድና በተቀጣጠሩበት<br />
ቦታ ይገናኛሉ። ቤቷ ይዛው ልትሄድ ብትሞክርም<br />
የስራ ሰዓት በመድረሱ ከስራ ሲወጣ እንደሚያገኛት<br />
ቀጠሮ ይዞ ወደ ስራው ያመራል። ሲወጣም በቀጠሮው<br />
መሠረት ቤቷ ይሄዳል። ዝምድናው ከዚህ ይጀምራል።<br />
አሁን ግን የሴትዮዋን ልጅ አግብቶ ሁለት ልጆችን<br />
በመውለድ ባለቦርሳዋን አያት አድርጓታል። መልካም<br />
አጋጣሚ ይሏል ይህ ነው።<br />
‹‹በባስ ውስጥ እየሄድኩ ነው በቁመት ከእኔ እኩል<br />
የሆነ ወጣት ፊት ለፊቴ ቆሟል አንድ ብረትም<br />
ተጋርተን ይዘናል›› ትላለች ረዘምና ጠየም ያለችው<br />
የ29 ዓመት ወጣት አይናለም ዳርሜለህ። ድንገት<br />
ሳይታሰብ አውቶቡሱ ፍሬን ይዞ በመንገጫገጩ እሷና<br />
ከፊት ለፊቷ የቆመው ወጣት ሚዛናቸውን ስተው<br />
ሲወዛወዙ ከንፈራቸው መገጣጠሙን ትናገራለች።<br />
‹‹እነሆ በዚያች በተቀደሰች አጋጠሚ የተነካካው<br />
ከንፈራችን ዛሬም አልተላቀቀም /ተጋብተናል/ በማለት<br />
አስገራሚውን ገጠመኘዋን ትናገራለች።<br />
የስሜት አንበሶች<br />
አንበሳ አውቶቡስ ውስጥ ተሳፍረው እየተጓዙ<br />
ስሜታቸው አንበሳ ሆኖ ጾታዊ ትንኮሳ የሚያስከትሉትስ<br />
ስንቶቹ ናቸው? መቼም እዚህ ጋዜጣ ላይ ለመፃፍ<br />
ባይበቃም በአውቶቡስ ውስጥ የሚያጋጥሙ አፈንጋጭ<br />
የወሲብ ጥቃቶች በርካቶች ናቸው። እንደውም<br />
ገና የሴት ቀሚስ ሲነካቸው ደርሶ ወንድነታቸው<br />
የሚገነፍል፣ በአይን ብቻ ሴትን ለመተኛት ጥረት<br />
የሚያደርጉ ከዚያም አልፈው ተርፈው ‹‹በማንም<br />
አያየኝም›› ድፍረት አስቀያሚ ድርጊት ሲፈፅሙ<br />
በሆነ አጋጣሚ ለሰዎች እይታ ተጋልጠው ውርደት<br />
የሚከናነቡ፣ ይህም ካልሆነ ጣጣቸውን ሰው ላይ<br />
ለጥፈው እስከመሄድ የሚደርሱ ስንቶቹ ናቸው?<br />
እነሆ ገጠመኝ።<br />
‹‹በአንድ ወቅት በ46 ቁጥር ከገርጂ ወደ ካዛንቺስ<br />
እየተጓዝኩ አንዱ ይተሻሸኛል። እናም እሸሻለሁ።<br />
እርሱ እየተጠጋ ስሜቱን ለማርካት ይጣጣራል››<br />
ትላለች ኤፍራታ አዲሱ የተባለች ወጣት። እንደ<br />
ኤፍራታ ገለፃ ሰውየው ፍፁም ስሜት ውስጥ ስለነበር<br />
ምንም ማስተዋል እንደተሳነው ታስታውሳች። ‹‹ነገሩ<br />
ሲብስብኝ ለምን አታርፍም? የሚል ጥያቄ ሳነሳ<br />
‹አርፈሽ ቁሚ ብዬሻለሁ› በማለት አንዴ በጥፊ<br />
ሲያጮለኝ ጮህኩኝ›› የምትለው ኤፍራታ ሰዎች<br />
ምንድነው ብለው መሀል ሲገቡ እሱ ኃፍረተ-<br />
ስጋውን ከሱሪው ውጭ አድርጎት ነበር›› በማለት<br />
በዕለቱ የደረሰባትን ውርደት አስታውሳ ትስቃለች።<br />
በወቅቱ ሰዎች ባይገላግሉሽ ምን እርምጃ ትወስጂ<br />
ነበር የሚል ጥያቄ አንስተንላት ‹‹ባገኘሁች አጋጣሚ<br />
ከስሩ እንደችግኝ ነቅዬ ነበር በእጁ የምሰጠው››<br />
በማለት ስቃ እኛንም አሳቀችን። በነገራችን ላይ በጣም<br />
የሚያሳዝነው አንድ እናት የ7 ዓመት ሴት ልጃቸውን<br />
አውቶቡስ ውስጥ ወንበር ላይ ለተቀመጠ ትልቅ ሰው<br />
አደራ በማለት እናት ይቆማሉ። ከደቂቃዎች በኋላ<br />
ኅጻኗ አውቶቡሱን በእሪታ ታቀልጠዋለች። ሰውየው<br />
ጭናቸው ላይ አስቀምጠው ደፍረዋታል። ይሄውና<br />
ተፈርዶባቸው ዘብጥያ ወርደው ይገኛሉ። እንዲህና<br />
መሰል ሰቅጣጭ ክስተቶች በአንበሳ አውቶቡስ ውስጥ<br />
ይካሄዳሉ።<br />
አዎ በከተማ አውቶቡስ ውስጥ በርካታ ገመጠኞች<br />
አሉ። አዝናኝም አሳዛኝም፣ አስነዋሪም፣ አስገራሚም።<br />
እርሶ የትኛው አጋጣሚ ደርሶዎት ይሆን? ክፉው<br />
ወይስ ደጉ? እንጃ ብቻ ከቀዶ ጠጋኞቹም ከቡድን<br />
ሰራተኞቹም ከቀፋዮቹም ራስን መጠበቅና መጠንቀቁ<br />
አይከፋም። መልካሙን አጋጣሚ መጠቀምም<br />
ብልህነት ነውና አውቶቡስ ተጠቃሚዎች ሆይ ቸር<br />
ይግጠማችሁ እንላለን።
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />
ማፊያ<br />
በብስራት<br />
ሚና፤ በማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ወይም<br />
በዘመናችን የወንጀል መልክ<br />
እየተለወጠ መጥቷል። ከዚህ<br />
ቀደም ከነበሩ ታላላቅ የተለመዱ<br />
ታዋቂ ማፊያዎች ጎን ለጎን<br />
ሌላ አዲስ የተደራጀ ወንጀል<br />
ብቅ ብሏል። ባለፉት ዓመታት<br />
ጂኦፖለቲካዊ ውጥንቅጥ<br />
ፖለቲካዊ ዘርፎች በተለይ በሕጋዊና ሕገ-ወጥ<br />
ክበብ መሀከል ግልግል ሥራዎችን ለማከናወን<br />
ማፊያዎች ጠቃሚ ሚና ይጫወታሉ። (4)<br />
በክልላዊና ብሔራዊ ደረጃ ከፖለቲካዊ መደብ<br />
(Political Elite) እና ከተቋማት ጋር ያላቸው<br />
ቁርኝት፤ ማፊያ ባለው ትሥሥር ወይም<br />
ግንኙት ምክንያት ወደ አንዳንድ ሕዝብ የኃብት<br />
ምንጮች ወይም ገበያዎች ውስጥ ይገባል።<br />
ውስጥ የተፈጠረውን ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነት በዚህም መሰረት በአንዳንድ ሁኔታዎች በሕጋዊ<br />
(Economic Globalization)፣ በዓለም አቀፍ ከለላ በመጠቀም በማኅበረሰቡ ላይ ካለው ተፅዕኖ<br />
የፋይናንስ ዝውውር በመጠቀምና የንግድ አልፎ ለፖለቲካዊ መደቡ ድጋፉን ይለግሳል።<br />
ልውውጥ ውስጥ ራሱን በመሰወር በሰዎች (5) በአንድ ክልል ሥር መሰደድ ወይም ጠንካራ<br />
ከቦታ ቦታ መዘዋወር መፋጠንን በመታገዝ ይዞታ መያዝ፤ አንድ የማፊያ ቡድን በሀገር<br />
እየበለፀገ ይገኛል - የወንጀል ዓለም።<br />
ውስጥና ከሀገር ውጪ በሌሎች አካባቢዎች<br />
እነዚህ አዳዲስ የመጡ ቡድኖች ዕንቅስቃሴ ቢያደርግም ቀድሞ የተመሰረተበትን<br />
ራሳቸውን በፍጥነት በማሳደግና መዋቅራቸውን ቦታ አይለቅም። ሥር ይሰዳል። ለምሳሌ፡-<br />
በመዘርጋት አንዳንዶቹ ቀድሞ በኢጣሊያ፣ ንድራጌታ (Ndrangheta) የተባለ ቡድን በሰሜናዊ<br />
ጃፓን፣ ቻይና፣ ቱርክና በኢጣሎ-አሜሪካን ኢጣሊያ እና በውጭ ሀገራት ዕንቅስቃሴዎችን<br />
በባህላዊ ልማዳቸው፣ በኢኮኖሚ አቅማቸውና ቢያደርግም፣ መጀመሪያ የተቋቋመበትን የካላብር<br />
ከፖለቲካ ጋር ባላቸው ቁርኝት ‹‹ማፊያ›› (Calabre) ክልል ፈጽሞ አልለቀቀም። (6)<br />
የሚለውን መጠሪያ ካገኙት የቀድሞ በድኖች አጠቃላይ የድርጅቱ ኃብት ምንጮች ሕጋዊና<br />
ጋር አቻ የሆነ ሚና በተግባር እስከመጫወት ሕገ-ወጥ ዕንቅስቃሴዎችን አጣምሮ መያዝ፤<br />
ደርሰዋል።<br />
በዓለማችን የማፊያ ቡድንን ወንጀል ከሕግ<br />
በፒራሚዳዊ ቅርጽ በመዋቀር አንጻር ለይተው ያስቀመጡ ሀገራት ከአንዲት<br />
በተፈጠሩበት ሀገር (መጠሪያቸውን የሚያገኙት ሀገር በስተቀር እንደሌሉ ሊሰመርበት ይገባል።<br />
ከዚህ ነው) በደንብ ራሳቸውን አቋቁመው ጣሊያን ካሳለፈችው ታሪካዊ ሁኔታ ይሁን በሌላ<br />
የተወሰኑ የመንግሥት ባለሥልጣናትን በማሞሰን ምክንያት በማፊያ ማኅበር የሚፈፀም ወንጀል<br />
በኢንቨስትመንት ላይ ይሳተፋሉ፤ ኢኮኖማውንም ምን ምን እንደሆነ ከሕግ አንጻር ባግባቡ ለይታ<br />
ይቦጠቡጣሉ። እነዚህ አዳዲስ ቡድኖች የገለፀች ብቸኛ ሀገር ናት።<br />
ዕድሜያቸው አጭር ቢሆንም አደረጃጀታቸው<br />
እነዚህን የማፊያ ማኅብር ዋና<br />
ግን በጣም የቆዩ ያስመስላቸዋል።<br />
ዋና ባህርያት ከተረዳን በኋላ የማፊያ ቡድን<br />
ማፊያ የሚፈጠርበትን ምክንያት ይህ መቼ እንደሚፈጠር እንይ። በአጥኚዎች ገለጻ<br />
ነው ብሎ ለመግለፅ የሚያዳግት ቢሆንም፣ መሠረት ማፊያ የሚፈጠረው ሕዝባዊ ተቋማት<br />
የመንግሥት መዳከም፣ ሥልጣን ርጉዕ በሆነ ፀጥታን ማስከበር ሲሳናቸው ነው። ማፊያ<br />
ፖለቲካዊ ቡድን በምኖፓል ሲያዝ፣ በጎሳ ወይም ከሌሎች ዓይነት የወንጀል ድርጊቶች እና<br />
ጎጠኝነት ላይ የተመሰረተ ማኅበራዊ አደረጃጀት ጥፋቶች ጋር ተጣምሮ ይሄዳል። በመቀጠልም<br />
ወዘተ እንደምክንያት ይጠቀሳሉ።<br />
እንደምንም ኃብት ያካብታል። ማፊያ አመቺ<br />
አንዳንድ የቀድሞ ማፊያ ብዙም ባልሆነ ኢኮኖማያዊ ሁኔታ ውስጥ ሊያቆጠቁጥ<br />
የማያውቃቸው የነበሩ ምዕራባውያን ሀገራት አይችልም። ለምሳሌ በሲሲሊ ውስጥ ኮዛ ኖስትራ<br />
ዛሬ የእነዚህ ዓለም አቀፍ አዳኞች ሰለባ እየሆኑ (Cosa Nostra) የተባ ዕድሜ ጠገብ የማፊያ<br />
ነው። ለምን? የዚህ መነሻው ሁለት ነው። አንድ፡ ቡድን በ19ኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ ላይ ብቅ<br />
- እነዚህ ቡድኖች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየበዙ ያለው በፓሌርሞ አካባቢ የሚገኙ ሰፋፊ የፍራፍሬ<br />
መምጣታቸው። ሁለት፡- ‹‹ኅቡዕ ካፒታሊዝም›› እርሻዎችን በመታከክ በግብርና ኢኮኖሚ ውስጥ<br />
(Clandestine Capitalism) ኢንተርፐርነር ነው። በመጨሻም ማፊያ ከሕዝባዊ ተቋማት<br />
የሆነው የተደራጀ ወንጀል በአዳዲስ ገበያዎች አካላት ጋር ትሥሥር መፍጠር ግድ ይለዋል።<br />
ውስጥ ቋማ ሥፍራ ለማግኘት ስለሚፈልግ ነው። ይህም ሽርክና የሚፈጠረው ወይ እንደ 19ኛው<br />
ለእነዚህ ገበያዎች ምርቶቹንና አገልግሎቶቹን ክ/ዘመን ሲሲሊ በሀገራዊ ሕገመንግሥት ውስጥ<br />
ያቀርባል። ዕጾችን፣ ሴቶችንና የተለያዩ ወንጀል በሚኖር ክፍተት በመጠቀም አሊያም ደግሞ<br />
ነክ ቴክኖሎጂዎችን ማለትም የማጭበርበሪያ ቅርብ ጊዜ ከ1989 እ.አ.አ በኋላ በቀድሞ ሶቭየት<br />
ወይም ማስመሰያ ደረሰኞችን፣ ጭምብሎችን፣ ኅብረት ሪፑብሊክ እንደተከሰተው የአንድን ሀገር<br />
የባንክ ካርዶችን ኮዶች ለማግኘት የሚረዱ ሚኒ መንኮታኮት ተከትሎ ነው።<br />
ካሜራዎችን ወዘተ።<br />
ማፊያ በሰው ልጆች ታሪክ ውስጥ<br />
እስከቅርብ ጊዜ ድረሰ ለመንግሥታት ከቀድሞም የነበረ ሳይሆን በቅርብ ጊዜ በፖለቲካ<br />
ያለመረጋት ምንጮች ተደርገው ይቆጠሩ መዘመን (Political Moderanity) ጋር የመጣ<br />
የነበሩት ሽብርተኝነትና የኢኮኖሚ ድቀት ብቻ ነው። ዘመናዊ ኢኮኖሚ በተገነባበት ሁኔታ ውስጥ<br />
ነበሩ። ዛሬ ዛሬ ግን በዓለም አቀፍ ትብብርና ዴሞክራሲ ሲከስም ወይም ሲቆረቁዝ ለማፊያ<br />
ሕግጋት ክፍተት በመጠቀም ማፊያ ሌላው አመቺ ሁኔታ ይፈጠራል። የመጀመሪያው<br />
ያልታወቀ ያለመረጋጋት መንስኤ እየሆነ ነው። የማፊያ ማኅበር የተፈጠረው በ19ኛው ከፍለ<br />
ይህ ደግሞ በተለይ በክልላችን ዘመን በሲሲሊ ግዛት ነው።<br />
በምሥራቅ አፍሪካ የራሱ መገለጫ አለው።<br />
የማፊያ ቡድን በአንዳንድ ሀገራት ኖሮ<br />
ያንን በዚህ ጽሑፍ በዝርዝር ለማየት በቂ በሌሎች ደግሞ የማይፈጠረው ለምንድነው?<br />
ጥናትና ምርምር ይጠይቃል። ሆኖም ግን ለዚህ ዋናው ምክንያት የጠንካራ ማዕከላዊ<br />
የማፊያ መለያ ባህርያትና ከዴሞክራሲ ዕጦት መንግሥት መኖር ሲሆን፣ ይህም በአንድ<br />
ጋር ያለውን ቁርኝት ጠቅለል ባለ መልኩ ማየቱ መንግሥት ውስጥ የሌላ ኅቡዕ መንግሥት<br />
ጠቃሚ ነው።<br />
(ልክ እንደማፊያ) ሕገ መንግሥት ወይም ደንብ<br />
ለመሆኑ ማፊያ ከሌሎች የወንጀል እንዳይኖር ስለሚከለክል ነው።<br />
ድርጅቶች የሚለየው በምንድነው? በዘርፉ<br />
አንድ የማፊያ ቡድን ቱባ አለቃዎቹ<br />
አጥኚዎች ማብራሪያ መሠረት ማፊያ ስድስት ሲታሰሩበት ይህን ችግር ተቋቁሞ ለማለፍ<br />
መገለጫ ባህርያት አሉት። እነሱም፡-(1) እንዴት ያደርጋል? የማፊያ ቡድን የራሱ<br />
ድርጅታዊ አወቃቀሩ፤ የማፊያ ቡድን አባላት መዋቅር ያለውና በአንድ አካባቢ ሥር የሚሰድ<br />
የጋራ ግዴታ ወይም ውል እና የተወሰነ ኃይል ነው። ዋና አለቃው ሲገደል በተለምዶ<br />
ውስጠ ደንብ አላቸው። (2) ሁከት ወይም ወዲያው አንድ ግለሰብ በቦታው ይተካል። ሆኖም<br />
የኃየል ድርጊት፤ የማፊያ ቡድን ሁከትን ግን ይህ ዕይታ በአግባቡ መመርመር አለበት<br />
ወይም የኃይል ድርጊትን (Violence) አንዳንድ ይላል አንድ የማፊያን ጉዳይ የሚዳኙ ባለሙያ።<br />
ጊዜ ወደ ባለፀጋነት መሰላል ለመውጣት እና አክለውም፣ “ማፊያ” ሰብዓዊ ክስተት ነው። ልክ<br />
በማስፈራራት ድርጅቱን ለመጠበቅ ወይም ጅማሬ (መነሻ) እንዳለው ሁሉ መጨረሻም<br />
ለመከላከል ይጠቀማል። (3) የማፊያ ማኅበራዊ ይኖረዋል” ይላሉ። ይህ አባባል ያለምክንያት<br />
ባሕርያቱና ከዴሞክራሲ<br />
እጦት ጋር ያለው ቁርኝት<br />
የተሰነዘረ አይደለም። በጥሩ መሰረት ላይ<br />
የቆመ የፀረ-ማፊያ ትግል ከተጠናከረ ማፊያ<br />
የማይወገድበት ምክንያት የለምና።<br />
ለመሆኑ የማፊያ ማኅብራት የተፅዕኖ<br />
ክልላቸውን ለማስፋፋት በሉዓላዊነት /<br />
Globalization/ ይጠቀማሉ? አዎ! ከኢኮኖሚያዊ<br />
ዕይታ አንጻር ካፒታላቸውን ወደ ውጭ ሀገር<br />
ይልካሉ፤ መዋዕለ-ንዋያቸውን ያፈሳሉ። ይህም<br />
በሌላ ሀገር በጀት ሥር አመቺ መጠለያ<br />
እንዲያገኙ ይረዳቸዋል። ከሌላ አንጻር ሲታይ<br />
ደግሞ የኢጣሊያ ማፊያ ከ19ኛው መ/ክ/ዘመን<br />
መጨረሻ ጀምሮ በሌሎች ሀገራት ማለትም<br />
በቱኒዚያ፣ አሜሪካና በአውስትራሊያ እግሩን<br />
ለመትከል ስደት (immigration) እንደ አማራጭ<br />
ተጠቅሟል።<br />
እንደማጠቃለያ፤ እነዚህን ሁኔታዎች<br />
ከሀገራችንና ከአካባቢያችን ሁኔታዎች ጋር<br />
አያይዘን መመርመር ያስፈልጋል። በሀገራችን<br />
የገዢው ፓርቲ መሠረት፣ አያያዝና ባህርይ<br />
እንዲሁም የተቃዋሚ ፓርቲዎች ሁኔታ<br />
እንዴት ነው? ሕዝባዊ ተቋሞቻችንስ ምን<br />
ያህል ፅዱና ጠንካራ ናቸው? የጎረቤታችን<br />
መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ቡድኖችስ<br />
ምን ይመስላሉ? በእኛ ሀገር ተቋማትስ ላይ<br />
ምን ዓይነት ተፅዕኖ ያሳድራሉ?<br />
ከውጭ ሀገር መጥተው መዋዕለ-ንዋያቸውን<br />
የሚያፈሱ ባለኃብቶች ምን ዓይነት ናቸው?<br />
የጀርባ ታሪካቸውን በሚገባ እናውቃለን? ሀገር<br />
ውስጥ ከገቡስ በኋላ ባህሪያቸው እንዴት ነው?<br />
ከሀገራዊ ተቋማት ጋር ያላቸው መስተጋብር<br />
ምን ይመስላል? ሕግ አክባሪ ናቸው? አቋራጭ<br />
መንገድ ይመርጣሉ? ለምን? የእኛስ ዜጎች<br />
ራሳቸው ንብረት ለማፍራት በምን ዓይነት<br />
መንገድ ይሄዳሉ?<br />
በሕጎቻችንና በተለይ<br />
በሕገመንግሥታችን ውስጥ ራሱ ክፍተት አለ<br />
ወይስ የለም? ለምን? ግለሰቦች የሚደርስባቸውን<br />
ችግር ወይም በደል በአግባቡ ለባለሥልጣናት<br />
ወይም ሕግ ፊት ያቀርባሉ? ፍትህስ ያገኛሉ?<br />
ሃሳባቸውን ለመግለጽ በቂ አማራጮች<br />
አሏዋቸው? ለምን ሁነኛ ሀገራዊ ውይይት<br />
ማድረግ ይሳነናል? ለምን በዕርጋታና በሰላም<br />
ግልፅ ውይይት ማድረግ አልቻልንም? ብዙ<br />
ጊዜ የምንለዋወጣቸው ቃላት (በማሕበራዊ<br />
ኑሮ ውስጥ ባልና ሚስት ጎረቤት ለጎረቤት፣<br />
ዐለቃና ምንዝር፣ አግልግሎት ሰጪና ደንበኛ<br />
ወዘተ) በተለይ <strong>በኢህአዴግ</strong> ዘመን ከችግር<br />
የፀዱ ናቸው? ምንስ ያንፀባርቃሉ? እነዚህንና<br />
የመሳሰሉትን ሁኔታዎች በአግባቡ ማጤን ተገቢ<br />
ነው። ይህንንም ስናጤንና የሚያስፈልጉትን<br />
ማስተካከያዎች ስንከውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ<br />
በአንድ ወቅት ያሉትን - ዛሬ ረስተውት እንደሆነ<br />
አይታወቅም - ‹‹የተሻለ ኅብረተሰብ የመገንባት<br />
ጥማት›› እውን ማድረግ እንችላለን። እንደ’ኔ<br />
እመነት ይህ ደግሞ የሚጀምረው ከአለት<br />
መሰረታዊ ተቋማት ነው - ከቤተሰብ፣ ትምህርት<br />
ቤት እና ከዕምነት ተቋማት።<br />
በገበያ ላይ ውሏል<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
9<br />
ሰላም ለኢትዮጵያ፣<br />
ሰላም ለአፍሪካ!
10<br />
እንደመንደርደሪያ<br />
በሶላር ፊልም ፕሮዳክሽን ተዘጋጅቶ<br />
የቀረበ ፊልም ነው። ዘወትር ማክሰኞ<br />
በ8፣ በ10 እና በ12 ሰዓት በሲኒማ<br />
አምፒር በመታየት ላይ ይገኛል።<br />
የዚህ ፅሑፍ ዳሰሳ አቅራቢ ባለፈው ማክሰኞ<br />
ጥቅምት 14 ቀን 2004 ዓ.ም አመሻሽ 12<br />
ሠዓት በቦታው ታድሞ ነበር። ጥቂት ሰዎች<br />
ወደ አዳራሹ ለመግባት ሰልፍ ይዘዋል።<br />
በፈረንጅኛው ‹‹security›› የሚል ቃል<br />
የተፃፈበት ባለ ሎሚ ከለር የለበሰ ጎረምሳ<br />
ወጣት ሴቶችን እየለየ ከሰልፈኛው ቀድመው<br />
እንዲገቡ ያዛል። ይኼኔ ፊልሙ ‹‹ለማየት<br />
ሳይሆን ለመታየት ለወጡ ወጣት ሴቶች ብቻ<br />
ነው እንዴ የተዘጋጀው?›› ስል ራሴን ጠየቅሁ።<br />
እየገረመኝ የመጨረሻው ታዳሚ ሆኜ ገባሁ።<br />
12 ሰዓት ከ10 ደቂቃ ሆኗል። በሲኒማ<br />
አምፒር ታችኛው አዳራሽ በጣት የሚቆጠሩ<br />
ሰዎች አልፎ አልፎ ተቀምጠዋል። 12 ሰዓት<br />
ከ25 ደቂቃ ተጨማሪ ተመልካች አልገባም።<br />
‹‹ሳታማኻኝ ብላ›› የሚለው ሙዚቃ በአዳራሹ<br />
ውስጥ ይናኛል። ነገሩ እየገረመኝ ታችኛው<br />
አዳራሽ ውስጥ ያለውን ሰው መቁጠ ጀመርኩ።<br />
ከእኔ ጋር 45 ሰው ብቻ ታድሟል። ወዲያው<br />
የአዳራሹ መብራት ጨለመ። ፊቴን ወደ ነጩ<br />
መጋረጃ መለስኩ። ላይኛው መመልከቻ ስፍራ<br />
ስንት ሰው ሊኖር እንደሚችል ለመገመት<br />
እየሞከርኩ ‹‹አልሞትም›› የሚል ርዕስ በነጩ<br />
መጋረጃ ላይ ሲነጠፍ አየሁ። እንዴት ነው<br />
ነገሩ? ሲኒማ አምፒር መግቢያ በር ላይ<br />
በረዥሙ የተሰቀለው የፊልሙ ማስታወቂያ<br />
ላይ ያነበብኩት ‹‹ለአንተ ስል አልሞትም››<br />
የሚል ርዕስ ነው። የርዕሱ ርዝማኔ የሰዎችን<br />
የማየት ፍላጐት የሚያነሳሳ አይደለም እያልኩ<br />
ነበር፡- ለራሴ። የፊልሙ ጅማሬ ላይ የተገለፀልኝ<br />
ርዕስ ግን ‹‹አልሞትም›› ብቻ ነው፡፡ ምክንያቱ<br />
ምንድነው? … ቢሆንም ፊልሙን በትኩረት<br />
መከታተል ቀጠልኩ።<br />
የፊልሙ ጭብጥ<br />
ወደ ሲኒማ አምፒር ለሚገቡ ተመልካቾች<br />
በሚበተነው የፊልሙ ማስታወቂያ በራሪ<br />
ወረቀት ላይ የፊልሙ ዋነኛ ጭብጥ ‹‹ልብ<br />
ለሚነካ ህፃን ልጅ የተከፈለ መስዋዕትነት››<br />
መሆኑ ተገልጿል። ይሁን እንጂ የፊልሙ<br />
ዋነኛ ጭብጥ ከላይ የተገለፀው ነው ብሎ<br />
ለመቀበል ይቸግራል። የህፃኑ ልጅ ጉዳይ<br />
በንዑስ ጭብጥነት ሊገለፅ ይችል ይሆናል።<br />
የሆኖ ሆኖ እኔን እንደገባኝ የፊልሙ ዋንኛ<br />
ጭብጥ ወይም ማጠንጠኛ ነገረ ጉዳይ ወንጀል<br />
ነው። የተደራጀ ወንጀል። እንደው ከአጭርም<br />
በአጭሩ ጠቅለል አድርገን እንግለፀው ካልን<br />
‹‹ማፍያ›› ተብለው የሚታወቁት ወንጀለኞች<br />
ታሪክ ነው ብንል ፊልሙን የበለጠ<br />
ይገልፀዋል።<br />
ለዚህ አባባል መጠነኛ አብነት መጥቀስ<br />
ይቻላል። የፊልም ጥበብ ባለሙያዎች<br />
እንደሚሉት፤ የአንድ ፊልም ሁለንተናዊ<br />
ታሪክ ጭብጥ በሶስት ደቂቃ ውስጥ ተመልካች<br />
እንዲረዳው ማድረግ ያስፈልጋል። ከዚህ<br />
አንፃር ‹‹አልሞትም/ለአንተ ስል አልሞትም››<br />
የተዋጣለት መሆኑን አለመመስከር ንፉግነት<br />
ነው።<br />
ምነው ቢሉ ፊልሙ በታሪኩ ጅማሮ በ1994<br />
ዓ.ም ጅማ ላይ የተፈፀመን የተደራጀ<br />
ወንጀል፣ ከጦርነት ባልተናነሰ ቅልጥ ያለ<br />
ተኩስ ያሳየናል። በቅፅበት እዚያው ጅማ<br />
ውስጥ በ2000ዓ.ም የተፈፀመን ወንጀል<br />
ያስቃኘናል። ከዚያም ግንቦት 2 ቀን 1992<br />
ዓ.ም ወደተፈፀመ ድርጊት ይመልሰናል።<br />
ወዘተ… ከ3 ደቂቃ ባለበለጠ ጊዜ በድርጊት<br />
የታጀበ ሁነት በመመስረት ረገድ ብቃት አለው<br />
የምለው ለዚህ ነው። የታሪኩ ዋነኛ ጭብጥም<br />
ይኸው የተደራጀ ወንጀል መሆኑን የተጠቀሰው<br />
ክፍል በቂ ማሳያ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ፊልሙ<br />
በርካታ ግድፈቶችንም ያስተናገደ ነው። ወደ<br />
ግድፈቶቹ ከመሄዳችን በፊት ግን መልካም<br />
ጐኖችን ማበረታታት ያስፈልጋል።<br />
በዚህ ፊልም ውስጥ ሰለሞን ገብሬ፣ አድያም<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
ዓለም፣ ታጠቅ መለሥ፣ ፍሬህይወት<br />
ስዩም፣ ኤደን ሽመልስ፣ ቅዱስ አሰፋ፣<br />
ቢላል እንድሪስ፣ ሰለሞን ነጋሽና ሌሎችም<br />
በተዋንያንነት (Actors) ተሳትፈዋል። ሁሉም<br />
ተዋንያን ማለት ይቻላል፣ በተሰጣቸው ገፀ<br />
ባህሪያት መጠን (የተሰጣቸው ገፀ-ባህሪይ<br />
- ከኢትዮጵያውያን የህይወት ዕውነታ ጋር<br />
የተስማማ ባይሆንም) ኃላፊነታቸውን በሚገባ<br />
ተወጥተዋል። ችሎታቸውንም አሳይተዋል<br />
ማለት ያስደፍራል። በተለይ የህፃኑን ገፀ<br />
ባህሪይ ወርሶ የተጫወተው ታዳጊ ድንቅ ትወና<br />
ማሳየቱን መካድ አይቻልም።<br />
ይህም ብቻ አይደለም። ‹‹ለአንተ ስል<br />
አልሞትም›› ፊልምን የደረሰው ሰለሞን ገብሬ<br />
መሆኑ ከላይ ተጠቅሷል። ነገር ግን ድርሰቱን<br />
ወደ ስክሪፕት ፅሁፍ የለወጡት ብዙአየሁ<br />
እሸቱ እና አንዱዓለም ጌታቸው ናቸው።<br />
ድርሰቱን ወደ ፊልም ፅሁፍነት የቀየሩበት<br />
ስልት ሊደነቅ የሚገባው ነው። ምክንያቱም<br />
ለእያንዳንዱ ገፀ-ባህሪያት በቃለ ተውኔትነት<br />
የተጠቀሙበት አጠርና ቅልብጭ ያለ የቋንቋ<br />
አጠቃቀም ለፊልሙ የተሟላ ህይወት መልካም<br />
ድርሻ ማበርከቱ ይስተዋላል። እንዲያም ሆኖ<br />
ፊልሙ በበርካታ ችግሮች የተዋጠ ነው፡፡<br />
ችግሩ<br />
ፊልሙ ከአገራዊ ፊልም ጥበብ አንፃር<br />
ይመዘን ከተባለ ይህ ነው የሚባል ፋይዳ<br />
ቄሱም ዝም<br />
መጽሀፉም ዝም<br />
ሰውም ዝም<br />
ኑሮውም ዝም<br />
ሁሉም ዝም<br />
ከመዝ …ውአቱ።<br />
ሰላም ለኩልክሙ /ሰላም ለሁላችሁም/ መወድስ<br />
ባናቱ ከነምልዓተ ንባቡ ጋብዣችኋለሁ።<br />
መወድስ<br />
ፀላዕኩ ሰብዐ እምነ-ርዕስየ ዘትርጓሜሁ በቀል<br />
ወዘንባቡ ሀሰት፤<br />
እስመ እምልሳኑ ለሰብዕ አንተ ይበልኦመሬት፤<br />
ለፌትህትና ወለፌ ትዕቢት፤<br />
ይወጽኡ ለስብከት እንዘ በላዕሌሁ ይሔሉ እንተ<br />
ኢይተርፍ ሞት፤<br />
ለዓለም ወለዐለም<br />
ልብየሂ ለዕመጌሠ መንገለ-ሀተታ ገነት፤<br />
ባቲ ዘተጋበዐ ጥበባተ-ሰሎሞን ጽጌያት፤<br />
እሩያነኮኑ በሰምናዊት ሰዐት.<br />
ሰብዕ በዐመፃወእግዚአብሔር በምህረት፤<br />
ትርጉም<br />
ከራሴ ጀምሮ ሰውን ጠላሁ። ከሰው አንደበት<br />
የሚወጣው ነገር<br />
በሙሉ ትርጓሜው በቀል ነው ንባቡም ውሸት<br />
ነው።<br />
በዚህ ውሸት በዛኛው እውነት (ባንድ አፍ ሁለት<br />
ምላስ) ይዘው፣<br />
ለማስተማር ይወጣሉ የማይቀረው ሞት እያለ።<br />
እኔም በተመስጦ የሰለሞን ጥበባት ወደ ተከማቹባት<br />
የገነት ጓሮ ላይ ሆኜ ስመለከት የሰው ልጅና<br />
እግዚብሔር በስምንተኛው ሺህ አንድ ሆኑ<br />
የሰው ልጅ ያጠፋል<br />
እግዚአብሔር ይምራል<br />
(ኤዲያ)<br />
አዱኛው ላይሞላ<br />
ይወደስክ ብላ<br />
በተለምዶ በዘፈኑና በሥነጽሁፉ ባቲ የቆንጆ መዲና<br />
ስትባል እንሰማለን። ስለባቲም ያልተዘፈነ ዘፈን<br />
የለም ብዬ ብናገርም ማጋነን አይሆንብኝም።<br />
ከአራቱ ቅኝቶች መካከልም የባቲ ቅኝት አንዱ<br />
ነው።<br />
1. ትዝታ<br />
2. አምባሰል<br />
3. አንቺ ሆዬ<br />
4. ባቲ<br />
ይህን የምታነቡ በሙሉ ‹‹ባቲ›› ብዬ ስጀመር አገሩን<br />
ነው ወይስ ቅኝቱን? ብላችሁ አስባችሁ ይሆናል።<br />
ያወቃችሁ ደግሞ አውቀችኋል። ባቲ ማለት የግዕዝ<br />
ግስ ሲሆን ትርጉሙም ‘አላት’ ማለት ነው።<br />
ቦ፡- አለ ፤<br />
ቦቱ፡- አለው፤<br />
ባ፡- አላት፤<br />
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />
አለው ማለት አይቻልም። ምነው ቢሉ<br />
የኢትዮጵያውያንን ህይወት፣ የአኗኗር ዘይቤ፣<br />
እምነት፣ አስተሳሰብና ማንነትን የሚያንፀባርቅ<br />
አይደለም። ማንነቱን የማያንፀባርቅ የጥበብ<br />
ስራ ደግሞ የሞተ ነው። ከባህር እንደወጣ አሳ፣<br />
ህይወት አልባ ነው የሚሆነው። የጥበብ ሰው<br />
ደግሞ ያልኖረበትን ዓለም መጠበብ አይችልም።<br />
ባልኖሩበት አለም ልጠበብ ማለት (ጥበበኛ ነኝ)<br />
ማለት ከመቃዠት ተለይቶ አይታይም።<br />
ባቲ፡- አላት፤<br />
የዶሮ እርባታ የማርባቱ አቅም<br />
ባይኖረኝም ባቲ በሚለው የግዕዝ ቃል<br />
እርባታውን አረባላችኋለሁ።<br />
አጽምኡኒ<br />
ስሙኝ<br />
አጽምኡኒ<br />
ስሙኝ<br />
አዱኛው ላይሞላ<br />
እያወደስክ ብላ<br />
ባ…ባተ ለዛቲ ብእሲት እንትን<br />
ለዚያች ሴቲዮ እንትን አላት<br />
አለላት<br />
አለባት<br />
ኖራት ኖረላት ኖረባት<br />
ነበራት ነበረላት ነበረባት<br />
ይኖራታል ይኖርላታል<br />
ይኖርባታል<br />
ይኑራት ይኑርላት ይኑርባት<br />
“ምንድነው ያላት?”<br />
አይ ምንም ነገር የላትም። ዝም ብዬ ግስ<br />
እያረባሁ ነው።<br />
“ሰው ዶሮ ያረባል አንተ ግስ ታረባለህ?<br />
አይደል?”<br />
ተይዟል።<br />
“ምኑ?”<br />
ዶሮው።<br />
“ከብቱስ፣ በጉስ፣ አሳማውስ?”<br />
ዝኒከማሁ (ይህም እንደዚያኛው<br />
ነው) ተይዟል።<br />
p Ç T@<br />
ማፍያዎቹ ፊልመኞች በ‹‹ለአንተ ስል አልሞትም››<br />
የፊልሙ ርዕስ፡- ‹‹ለአንተ ስል አልሞትም››<br />
የፊልሙ ደራሲ፡- ሰለሞን ገብሬ<br />
የፊልሙ ዘውግ፡- አክሽን<br />
የፊልሙ ዳይሬክተር፡- ታጠቅ መለሰ<br />
ፊልሙ የሚፈጀው ጊዜ፡- 1፡40 ሰዓት<br />
በንፍታሌም<br />
በከመ-ይቤ ቅዱስ ኤፍሬም ባለቅኔ<br />
የገዘፈው የፊልሙ ደካማ ጐን<br />
‹‹ለአንተ ስል አልሞትም›› የተሰኘው ይህ<br />
ፊልም ግዙፍ ደካማ ጐን የታሪኩ መዋቅርና<br />
ሁለንተናዊ ይዘት የኢትዮጵያዊያንን ህይወት<br />
የማይወክል መሆኑ ነው ብዬ አምናለሁ።<br />
ምክንያቱም የ‹‹ማፍያ››ዎችን የተደራጀ ወንጀል<br />
ነው የሚያሳየው። በአጠቃላይ የፊልሙ ይዘት<br />
ፊልም ሰሪዎቻችን ‹‹ማፍያዎች›› መሆናቸውን<br />
በገሃድ ያሳዩበት ነው ብል ማጋነን አይሆንም።<br />
አንድ፣ ፊልሙ እንደጣሊያን ሲሲሊያኖች<br />
ማፍያዎች የረቀቀና የተደራጀ ወንጀል መፈፀምና<br />
በዘረፉት ብር ወይም ወርቅ የተነሳ- ግጭት<br />
ውስጥ መግባት ላይ ያጠነጠነ ነው። ፊልሙ<br />
እርስ በእርስ መታኮስ፣ መጠዛጠዝ፣ እርስ በርስ<br />
መሸዋወድ ወዘተ ነው። ፊልሙ በረቀቀ ስልት<br />
ወንጀለኞቹ እርስ በርስ ሲቀጣቀጡና ሲናረቱ..<br />
ወዘተ የሚያሳይ ነው። ከጅማ እስከ አዲስ<br />
አበባ በተዘረጋ የወንጀል መረብ፤ ሰዋራ ቦታ<br />
ላይ፣ ጅምር ህንፃ <strong>ስር</strong>… ወዘተ መቀጣቀጥና<br />
መታኮስ፣ እንደገና መቀጣቀጥና መታኮስ ብቻ<br />
ነው የሚያሳየው፡፡ መርማሪ ፖሊስን ቤቱ ድረስ<br />
ሄዶ አንገቱን መቀንጠስም ያካትታል። ብላ!<br />
ብላ! ብላ!<br />
ሌሎች ሁኔታዎችን እንጥቀስ ካልን የፊልሙን<br />
ሙሉ ታሪክ መነስነስ ሊሆንብን ነውና<br />
ባቲ<br />
ተውነው። የሆኖ ሆኖ ግን ፊልሙ ከውጭ<br />
<strong>አገር</strong> የማፍያ ፊልሞች ሙሉ በሙሉ የተኮረጀ<br />
ወይም የተገለበጠ መሆኑን ለመረዳት ነብይ<br />
መሆን አያስፈልግም።<br />
ችግሩ የፊልሙ ታሪክ ወንጀል ላይ<br />
መመስረቱ አይደለም። እንዲህ አይነቱ<br />
በቡድን የተከፈለና ከጦርነት ያልተናነሰ ተኩስ<br />
የሚተኮስበት ለመንግስትም ፈታኝ የሆነ<br />
የወንጀል ተግባር ላይ አገራችን የደረሰች<br />
አይመስለኝም። አልደረሰችምም፡፡ የፈረንጆቹን<br />
ሴራ (በቋንቋ) ለውጥ ብቻ የእኛ <strong>አገር</strong><br />
ታሪክ አስመስሎ ማቅረብ ደግሞ ይቅር የማ<br />
ይባል ሃጢያት ነው።<br />
ኩረጃ እና ኮራጅ<br />
ኩረጃ በየትኛውም ዘርፍ የሚነቀፍ አይደለም፡<br />
፡ የኮራጅ ተግባር ነው ኩረጃን ፍፁም ወንጀል<br />
የሚያደርገው። ሁሉንም ነገር ከራስ ፀጉሩ እስከ<br />
እግር ጥፍሩ መኮረጅ ጤንነት አይደለም።<br />
በአንድ ወቅት አንድ አባት ያሉኝ ነገር እዚህች<br />
ላይ ትዝ አለችኝ ‹‹መስረቅ ፍፁም ወንጀል<br />
የሚሆነው፣ ሁሉንም ነገር አግበስብሶ ለመውሰድ<br />
ሲሞከር ነው። የዝርፊያ ጥሩ ባይኖረውም<br />
ከማግበስበስ ይልቅ እንጥፍጣፊውን መውሰድ<br />
ነው የሚሻለው›› ነበር ያሉኝ። የእኛ <strong>አገር</strong><br />
የፊልም ጥበብ እንደማፍያዎቹ ሙሉ በሙሉ<br />
የመገልበጥ ያህል መሆኑ ነው የሚያሳዝነው።<br />
ይህም ፊልም ሆኖ፣ ይህም ፊልም ተብሎ፣<br />
ወጣት ሴቶች የፊልም ተመልካቹን ክብር<br />
እየጣሱ ቀድመው ወደ ባዶው አዳራሽ እንዲገቡ<br />
በማድረግ አድልዎ ለመፈፀም መሞከሩ ነው<br />
የሚያሳዝነው፡፡ ሌላው ሌላው ቢዘረዘርማ ችግሩ<br />
የትየለሌ ነው፡፡<br />
(አላት፣ አለላት)<br />
“አይ … ሁሉም ከተያዘ ለምን ሰው<br />
አታረባም?”<br />
የሚረባ ሰው የለም።<br />
“እንዴት?” (መሬት ዐንተ ወትገብዕ<br />
ውስተመሬት)<br />
አፈር ነህና ወደአፈር ትመለሳለህ ስለሚል።<br />
ፍሬ ከርስኪ ነው። ሁሉም ከወሬ የዘለለ ነገር የለውም።<br />
እና … ሁሉም ሰው አይረባም እያልክ ነው?<br />
አዎ ከራሴ ጀምሮ አይረባም።<br />
“አንተስ? ረብተሀል?”<br />
በግሱ ረብቻለሁ፤ በገንዘቡ ግን አረባሁም።<br />
“እስኪ አንድ ነገር ልጠይቅህ፤ አንድ ሰው ይረባል ለማለት<br />
ምን ያስፈልገዋል?”<br />
ያው ገንዘብ ነው። ገንዘብ ካለህ ትረባለህ። ገንዘብ ከሌለህ<br />
ደግሞ አትረባም። አለም ወዳላቸው እንጂ ወደሌላቸው ፊቷን<br />
አታዞርም።<br />
“ገንዘብ ሥትለኝ ያልገባኝ ነገር አለ። ገንዘብ ማለት በእጅ<br />
የሚቆጠረው ወረቀት ማለት ነው?”<br />
እንዴታ! እሱንማ ካልያዝክ ማን እጅ ይነሳሀል? ማንስ<br />
ያከብርሀል? ኧረ ተወኝ ሁሉም ሰው ከቁብም አይቆጥርህ።<br />
“እንዴ ምንድነው የምትለው? የሰው ልጀ ከብር አይበልጥም<br />
እንዴ?”<br />
መብለጥ እንኳን ይበልጣል። የሰው ልጅ ተገዢ ሲሆን ብር<br />
ደግሞ ገዢ ነው። አንድ ብር ላይ ገዢ የሚል ቃል አይተህ<br />
አታውቅም?<br />
“ገዢማ የፈጠረን አምላክ ነው። እንዴት ብር ገዢ<br />
ይሆናል?”<br />
ኤዲያ . . . አምላክንም ገዝቶታል።<br />
“እንዴት አርጎ?”<br />
ለጌታም ጌታ አለው<br />
ገንዘብ ጌታ ሆኖ ጌታን አንገላታው<br />
እና ገንዘብ ይሉሀል ይሄ ነው። ሰላሣ ዲናር ባይኖር አምላክ<br />
ባልተሸጠ፤ ሻጭና ገዢም ባልኖረ። ለዚህ እኮ ነው ባሪያ<br />
ለሁለት ጌቶች መገዛት ይቻለዋልን? ተብሎ ይተፃፈው።<br />
ከር … ከር … ከር ብሎ ሲስቅ፣<br />
ተው አትሳቅ<br />
ለምን?<br />
ሳይኖርህ መሳቅ<br />
ይሆንብሀል መሳቀቅ<br />
አዱኛው ላይሞላ<br />
እያወደስክ ብላ
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />
S ´ “ —<br />
መዝናኛ ዜና<br />
ብሌን ፊልም ነገ<br />
ይመረቃል<br />
በኢዮብ ተስፋዬ ተደርሶ በአንተነህ<br />
ሞትባይኖር የተዘጋጀውና ፕሮዲዩስ የተደረገው<br />
ብሌን ፈልም ነገ እና ከነገ ወዲያ በአዲስ አበባና<br />
በክልል ከተሞች በሚገኙ በርካታ ሲኒማ ቤቶች<br />
ይመረቃል። 1፡40 ሰዓት ርዝማኔ ያለውና የፍቅር<br />
ታሪክ ላይ የሚያጠነጥነው ብሌን ፊልም ተሰርቶ<br />
ለመጠናቀቅ 11 ወራትን ወስዷል። በፊልሙ ላይ<br />
ሰላማዊት ብርሀኑ፣ ኢዮብ ተስፋዬ፣ ትዕግስት<br />
ይልማ፣ አንተነህ ሞት ባይኖር፣ ወይሰው አንተነህ፣<br />
አብነት ዳግምና ሌሎችም ተሳትፈውበታል።<br />
እጃቢ ሙዚቃው በአክሊሉ ተዋበ<br />
የተቀናበረውና አማን ተስፋዬና ዮዲት ወርቁ<br />
በድምፅ የተሳተፉት ብሌን ፊልም በአንዲት ወጣት<br />
ዙሪያ የሚደረግ የፍቅርና የጥቅም መስዋዕትነትን<br />
የሚያሳይ ሲሆን ወጣቷ ቤተሰቦቿንና የአይን<br />
ብርሀኗን በአደጋ በማጣቷ የሚያፈቅራት ወጣት<br />
በአስገራሚ ሁኔታ በሚያደርግላት እንክብካቤና<br />
በአክስቷ ልጅና በፍቅር ጓደኛዋ በሚደርስባት በደል<br />
ላይ የሚያጠነጥን እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።<br />
በሲ.ኤል.ዲ ፊልም ፕሮዳክሽን የቀረበው<br />
ብሌን ፊልም በዋናነት በአዲስ አበባ ስብሰባ ማዕከል<br />
ከቀኑ በ10 ሰዓት በድምቀት እንደሚመረቅም<br />
ለማወቅ ችለናል።<br />
ምራኤል የስኬት<br />
ት/ቤት በአመለካከት<br />
ለውጥና በስኬት ዙሪያ<br />
ውይይት ያካሂዳል<br />
ምራኤል ኢንተርናሽናል የስኬት ት/ቤት<br />
በአመለካከት ለውጥና በስኬት ዙሪያ በ<strong>አገር</strong> አቀፍና<br />
በግለሰብ ደረጃ እንዴት መተግበር እንደሚቻል<br />
የሚያመላክት ውይይት ዛሬ ረፋዱ ላይ በብሔራዊ<br />
ቴአትር ያካሂዳል። እንደ ድርጅቱ መግለጫ ት/<br />
ቤቱ እስካሁን በግለሰብም ሆነ በ<strong>አገር</strong> አቀፍ ደረጃ<br />
ህብረሰቡ የተዛባን አመለካከት በመለወጥ እንዴት<br />
ወደ ስኬት መድረስ እንደሚችል በማሰልጠንና<br />
በርካታ ስልቶችን በማመላከት እየሰራ መሆኑን<br />
ገልጾ፤ በዛሬው ዕለትም በሚያካሂደው ውይይት ላይ<br />
በዘርፉ ውጤት የሚመጣበትን መንገድ ይፈጥራል<br />
ተብሎ ይጠበቃል።<br />
ምራኤል ኢንተርናሽናል በነገው እለት<br />
ከውይይቱ በተጨማሪ እስከዛሬ ያከናወናቸውን<br />
ፍሬያማ ተግባራት መግለፅ፣ በቅርቡ ሚያስገነባውን<br />
የህንፃ ዲዛይን ማስመረቅ፣ በምራኤል ሰልጥነው<br />
ለውጤት የበቁ ምስክሮችን መስማት፣ የማያቋርጥ<br />
ደስታን መፍጠር የሚያስችሉ 10 ሚስጥሮችን<br />
ማሳወቂያ ስልጠና መስጠት፣ በኢትዮጵያ ላይ<br />
በአስተሳሰብ እና በስራ ፈጠራ ላይ ሰፊ ስራ የሰሩ<br />
ግለቦችን መሸለምና የምራኤል ምርጥ ውጤታማ<br />
ተማሪዎችን መሸለም ከፕሮግራሙ ውስጥ<br />
ተካተዋል። በእለቱ ይህን ውይይት ፍላጎት ያላቸው<br />
እንዲካፈሉበት ምራኤል የጋበዘ ሲሆን በእለቱ ታዋቂ<br />
ሰዎች ጋዜጠኞችና ጥሪ የተደገላቸው የመንግስት<br />
ኃላፊዎችና የምራኤል ት/ቤት ማህበረሰብ በውይይቱ<br />
ይታደማሉ ተብሎ ይጠበቃል።<br />
በሬዲዮ ድምፅሽን የሚሰሙ በአካል ሲያገኙሽ<br />
ምን ይሉሻል?<br />
በጣም ነው የሚደነግጡት። ቢሮ<br />
መጥተው እንግዳ መቀበያ ላይ ለተለያየ የስራ<br />
ጉዳይ ስንቀሳቀስ ‹‹ቲጂ የለችም›› ብለው<br />
ይጠይቁኛል። ‹‹እኔ ነኝ›› ስላቸው በፍፁም<br />
አያምኑኝም። የሚያስቡኝ ትልቅ ሴት አድርገው<br />
ነው። እንደምታየኝ ትልቅ ሴት አይደለሁም<br />
አይደል? [ሳቅ] ለሙያው ትንሽ ፈጠን ብያለሁ<br />
መሰለኝ።<br />
አርባ ስንት ዓመትሽ ነው?<br />
[ሳቅ] 27 ዓመቴ ነው።<br />
ህይወትን በስነ-ልቦና አረዳድ እንዴት ታያታለሽ?<br />
እኔ ህይወትን በስነ ልቦና መነፅር<br />
ስመለከታት ይመስለኛል ጥያቄህ…<br />
ትክክል!<br />
ከራሴ እይታ ብናገር ደስ ይለኛል።<br />
እዚህ ህይወት ውስጥ ከገባሁ ጀምሮ የተረዳሁት<br />
ነገር የማትጠብቀውን ነገር ጠብቅ (Expect the<br />
Unexpected) የሚለውን መርህ ነው። በስራ<br />
ላይ እንደ ባህላችሁን ቡና ስንጠጣ ከምንሰማቸው<br />
ወሬዎች በጣም የዘለሉ ጉዳዮች ይመጣሉ። ስለዚህ<br />
ሁሌም ጠዋት ስነሳ የማይጠበቅ፣ ከአቅሜም<br />
በላይ የሆነ ነገር ሊመጣ እንደሚችል ከሙያው<br />
ተረድቻለሁ።<br />
ከአቅምሽ በላይ [በአንቺ የምክር አገልግሎት<br />
ሊያገግሙ የማይችሉ የምትያቸውን] የሆኑ<br />
ችግሮችን ያዘሉ ደንበኞች ሲመጡ ምን<br />
ታደርጊያለሽ?<br />
የስነ-አዕምሮ ሐኪም (ሳይካትሪስት)<br />
የሚያያቸውን ወይም መድኃኒት መጠቀም የደረሱ<br />
ደንበኞችን አንመለከትም። የምንሰራው ከመድኃኒት<br />
ወዲህ ያሉ ሰዎች በቀን ተቀን ኑሯቸው ላይ<br />
የሚያጋጥማቸው ችግሮች ላይ መፍትሄ የማምጣት<br />
ስራ ነው።<br />
ስራው እንዲህ ዘና ብዬ እንደማወራህ<br />
ቀላል አይደለም። በስነ-ልቦና ዓለም የገባኝ ትልቁ<br />
ምስጢር ችግሩ ከባድም ቢሆን ራስን እዚያ ሰው<br />
ጫማ ውስጥ አድርጎ መመልከትን ነው። እኔጋ<br />
ዓለማዊ ወግ<br />
በውሂብ<br />
1<br />
ከያዘ የማይለቅ ሞኝ እና ወረቀት ነው<br />
ይባላል። ከዚሀ በኋላ ግን የኔታም ቢጨመሩበት ደስ<br />
ይለኛል። እና እንዲህ ይባል፡- ከያዘ የማይለቅ የኔታና<br />
ወረቀት ናቸው። አሰለቹኝ። ልንማርበት ከነበረው ዛፍ<br />
ሥር ተነስቸ ወጣሁ።<br />
የግብጽ ጳጳሳትን ሰምተው በዓላትን<br />
ያወጁ ካህናት ትሩፋት የሆኑ ትላልቅ ዛፎች<br />
ቤተክርስቲያኑን ወረውታል። በዓላት ባይኖሩ ኖሮ፣<br />
እንደ ኢትዮጵያውያን ደን የማውደም ፍቅር ይሄኔ<br />
አንድም ዛፍ ባልተገኘ ነበር።<br />
አፍታ<br />
በፋና ኤፍ ኤም 98.1 በሚተላለፉ አዲስ መንገድ እና የእርቅ ማዕድ<br />
በተሰኙ የስነ-ልብዎና ፕሮግራሞች ላይ በምታቀርባቸው ስነ ልቦናዊ<br />
ትንታኔዎች በርካታ አድናቂዎች አሏት። የአስተሳሰብ እና የአዕምሮ<br />
ሂደቶችን ስለሚያጠናው የሳይንስ ዘርፍ (Psychology) እና ስለ ሌሎች<br />
ነጥቦች ‹‹ቲጂ›› አንዳፍታ ቆይታ አድርጋለች፤ ከአቤል ዓለማየሁ ጋር።<br />
‹‹የቤት እንስሳት<br />
ያስባሉ ብዬ አምናለሁ››<br />
ትዕግስት ዋልተ ንጉስ [የስነ-ልቦና ባለሙያ]<br />
በስነ-ልቦና ዓለም የገባኝ ትልቁ<br />
ምስጢር ችግሩ ከባድም ቢሆን ራስን<br />
እዚያ ሰው ጫማ ውስጥ አድርጎ<br />
መመልከትን ነው። እኔጋ የሚመጡ<br />
ሰዎች ‹‹ተበድያለሁ›› ብቻ ሳይሆን<br />
‹‹በድያለሁም›› የሚሉ ናቸው።<br />
ሚስቱን የጎዳ፣ ልጆቹን ያስራበ፣<br />
ወዳጁን በጣም ያስከፋ፣ ገንዘብ<br />
የቀማ ይመጣል።<br />
የሚመጡ ሰዎች ‹‹ተበድያለሁ›› ብቻ ሳይሆን<br />
‹‹በድያለሁም›› የሚሉ ናቸው። ሚስቱን የጎዳ፣<br />
ልጆቹን ያስራበ፣ ወዳጁን በጣም ያስከፋ፣ ገንዘብ<br />
የቀማ ይመጣል። ከውጪ ሆነህ ከተመለከትከው<br />
ርህራሄ የጎደለው ስራ ስለሰራ ሰውዬው ራሱ<br />
ያናድድሀል።<br />
በአዕምሯችን የሚመጡ በጎ እና መጥፎ ሀሳቦች<br />
(Positive & Negative Thoughts) መነሻ ምን<br />
እንደሆነ ልትነግሪኝ ትችያለሽ?<br />
እንደየሰዉ ይለያያል። ይጠቅምህ<br />
እንደሆነ ባላውቅም አንድ መሰረተ ሀሳብ አለ፤<br />
ከቤተክርስቲያኑ ፈንጠር ብሎ ከምጣድ<br />
እንደተፈናጠረ ፈንድሻ ብትንትን ያሉ ጎጆዎች አሉ።<br />
እኒህን ቤቶች ሳይ አንድ ነገር ይታሰበኛል። መቼም<br />
ሀገራችን ብዙ ሥልጣኔዎችን በማምጣት ግንባር<br />
ቀደም እንደሆነች የታወቀ ነው። የዘመናዊ አፓርታማ<br />
እሳቤንም ያመጣችው ሀገራችን ናት። ለዚህም ማሳያው<br />
እኒህ ጎጆዎች እንደሆኑ ይሰማኛል። ብናስጎበኛቸው<br />
ሊያዋጣን ይችላል እያልኩ አስባለሁ።<br />
ሌላ ማረፊያ<br />
ዲያቆን አስማማው ጓደኛዬ ነው። አብረን<br />
እንማራለን። እሱ ግን እየዞሩ ቁራሽ እንደመለመን<br />
ስሜት የሚሰጠው ነገር የለም። ተማር ከሚሉት<br />
ጎጃምን እያካለልክ ቁራሽ ለምን ቢሉት ይዋጣለታል።<br />
በ ገፅ 18<br />
11<br />
ማሰብ፣ ስሜትና ድርጊት የሚል። ‹‹እከሌን<br />
እገለዋለሁ›› የሚል ሰው ነገሩ ሁሉ የሚጀምረው<br />
ከአስተሳሰቡ ነው። ሰባት ቢሊየን የሚሆን የዓለም<br />
ህዝብ ስላለ የዚያን ያህል የተለያየ ስብዕና አለ።<br />
እኔ እና አንተ፣ ቢጫ እና አረንጓዴ የተቀባ ግርግዳ<br />
ብናይ አንተ ቢጫ እኔ ደግሞ አረንጓዴ ሊታየኝ<br />
ይችላል። ነጥቡ የአመለካከት ነው። ተፈጥሯችን<br />
የተለያየ ስለሆነ ነገሮችን የምንተረጉምበት መንገድ<br />
ይለያያል። ዘረ-መል፣ ተፈጥሮ፣ አስተዳደግና<br />
የምትኖርበት ማህበረሰብ በአስተሳሰብህ ላይ ተፅዕኖ<br />
አለው። ጥሩው ነገር ግን ሁሉም መስተካከል<br />
መቻሉ ነው።<br />
ስብሰባ ላይ ተቀምጠን በሚሰጥ አስተያየት<br />
ወይም በዜና ማሰራጫዎች በሰማነው መረጃ ላይ<br />
ተቃርኗዊ አረዳድ/የተለየ አመለካከት ይኖረናል።<br />
ይህ ለምን ይመስልሻል?<br />
ይህ አንተን ብቻ ሳይሆን ሁላችንንም<br />
የሚያስገርም ነገር ነው። በአንድ ወቅት በአንድ<br />
አይነት መንትዮች (Identical Twins) ላይ ጥናት<br />
ተደርጎ ካልተሳሳትኩ 23.8 በመቶ የስብዕና ልዩነት<br />
አላቸው። ስለሆነም ጥያቄውን እኔ ራሴ መመለስ<br />
ያቅተኛል።<br />
እንደማስበው ግን ባህሪ ብቻ ሳይሆን<br />
ተፈጥሮም የምትጫወተው ሚና አላት ብዬ<br />
አስባለሁ። ይዘን የምንወለደው ነገር እንዳለ ሆኖ<br />
አካባቢም ተፅዕኖ አለው። የሰው ልጅ ስብዕና<br />
የሚቀረፀው ከዜሮ እስከ ሰባት ዓመት ነው<br />
ተብሎ ስለሚታመን የአስተሳሰብ ባለሙያዎች<br />
(Behaviorist) ‹‹አንድ የተወለደ ህፃን አምጣልኝ።<br />
ከፈለግክ ሌባ፣ ዶክተር፣ አርክቴክት…<br />
ጎጆው ወስጥ ተኝቷል። ‹‹በሶ ልስጥህ?›› አለ<br />
ከመድረሴ። የበሶ ጭብጦ እየጎመደ ነበር። ትምህርት<br />
ቤት ለምን እንዳልሄደ ስጠይቀው ጭብጦውን በውኃ<br />
አወራረደና፣ ‹‹ለዚች ሀገር ቅስና ሳይሆን ቅድስና<br />
ነው የሚያስፈልጋት›› አለኝ።<br />
በእውነቱ ከሆነ የአስማማውን ፈላስፋነት<br />
ዛሬ ነው ያወቅሁት ማለት ይቻላል።<br />
‹‹ቅስና ትልቀ ነገርማ ቢሆን ኖሮ<br />
የወላጆችህ ትዳር በቄስ ምክንያት ባልደፈረሰ ነበር››<br />
አለ። የምጠላውን የእናቴን ስም እንዳያነሳብኝ ፈራሁ።<br />
ዘነበች . . . ዘነበች . . . አሁን ይህ የሰው ስም<br />
ነው?<br />
‹‹ስለየኔታ የሰማኸው አለ?›› አልኩት።<br />
በ ገፅ 21<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ
12<br />
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />
መቆሚያ ያጣው የዋጋ ግሽበት<br />
በሱራፍኤል ግርማ<br />
ከጊዜ ወደ ጊዜ በመሻሻል ፋንታ<br />
በመባባስ ላይ የሚገኘው የዋጋ<br />
ግሽበት፣ ማዕከላዊ ስታቲስቲክስ<br />
ኤጀንሲ ይፋ ባደረገው መረጃ<br />
መሰረት በመስከረም ወር<br />
2004 ዓ.ም 40.1 በመቶ ሆኖ<br />
ተመዝግቧል። 40.1 በመቶ<br />
የአጠቃላዩ የዋጋ ግሽበት ልኬት<br />
ይሁን እንጂ፣ ለኢትዮጵያውያን<br />
ኑሮን ፈታኝ በማድረግ ቀጣይ<br />
ዕጣ ፈንታቸውን አደጋ ውስጥ<br />
የከተተው የምግብ ዋጋ በተናጥል<br />
የ51.3 ጭማሪ ነው ያሳየው።<br />
በየወሩ በሚያገኙት ቋሚ ገቢ<br />
ብቻ የሚተዳደሩ፣ ጡረተኞች<br />
እንዲሁም በአነስተኛ የዕለት ገቢ<br />
ኑሯቸውን የሚመሩ ላብ አደሮች<br />
በዋጋ ግሽበቱ በተለይም ደግሞ<br />
በምግብ ዋጋ መናር ከፍተኛ ጉዳት<br />
ደርሶባቸዋል፡፡<br />
ምንጩ ምንድን<br />
ነው?<br />
ከ2003 ዓ.ም አጋማሽ አንስቶ<br />
በአስደንጋጭ ሁኔታ ጭማሪ<br />
በማሳየት አሁን ያለበት ደረጃ<br />
ለደረሰው ተከታታይና ባለሁለት<br />
አኃዝ ግሽበት መንግስት የተለያዩ<br />
ምክንያቶችን አስቀምጧል።<br />
<strong>አገር</strong> ውስጥ ለተከሰተው ግሽበት<br />
በዋና ምክንያትነት በመንግስት<br />
የተፈረጀው በዓለም አቀፍ ገበያ<br />
የተከሰተው የዋጋ ግሽበት ነው።<br />
የዓለም ኢኮኖሚ ከማንሰራራት<br />
ይልቅ ይበልጥ የመቃወስ አቅጣጫን<br />
ይዞ እየተጓዘ ባለበት ወቅት፣<br />
በመካከለኛው ምስራቅ የፈነዳው<br />
‹‹የዓረብ አብዮት›› በነዳጅ ዋጋ<br />
ላይ ጭማሪ እንዲመጣ ማድረጉን<br />
የሚገልፀው መንግስት፣ ‹‹ስለዚህ<br />
የነዳጅ ዋጋ መቀጠልን ተከትሎ<br />
የሌሎች ሸቀጦችም ዋጋ ቀጥሏል››<br />
በማለት ለግሽበቱ ዋና ምንጭ ነው<br />
ያለውን ሁኔታ ይገልፃል።<br />
ምንም እንኳን መንግስት በ<strong>አገር</strong><br />
ውስጥ ለሚስተዋለው እጅግ<br />
ከፍተኛ የሆነ የዋጋ ግሽበት<br />
በዋና ምክንያትነት በዓለም አቀፍ<br />
ገበያ የተስተዋለውን የዋጋ ንረት<br />
በመጥቀስ ‹‹እዚህ ያለው ከውጭ<br />
የገባ ግሽበት (imported inflation)<br />
ነው›› ቢልም፣ በዚህ በርካቶች<br />
አይስማሙም።<br />
ፖለቲከኛና የምጣኔ ሐብት<br />
ትምህርት የተከታተሉት አቶ ገብሩ<br />
አስራት አሁን እየተስተዋለ ላለው<br />
የዋጋ ግሽበት ዋና መንስኤው<br />
መንግስት ያለ ገደብ ከብሔራዊ<br />
ባንክ ተበድሮና አሳትሞ ያሰራጨው<br />
የገንዘብ መጠን ከልክ በላይ<br />
መብዛትና የምርት መጠን መቀነስ<br />
መሆኑን በመግለፅ ይሞግታሉ።<br />
ለአጠቃላዩ የዋጋ ግሽበት<br />
መጨመር ከፍተኛውን አስተዋፅዖ<br />
ያበረከተው እዚሁ <strong>አገር</strong> ውስጥ<br />
የሚመረተው ምግብ መሆኑን<br />
በማስታወስ የመንግስትን ‹‹ከውጭ<br />
የገባ ግሽበት›› መከራከሪያ ውድቅ<br />
የሚያደርጉት አቶ ገብሩ፣ ‹‹የምግብ<br />
ዋጋ የናረው <strong>አገር</strong> ውስጥ በቂ<br />
ምርት ስለሌለ ነው›› ይላሉ።<br />
የንግድ አስተዳደር ባለሙያ የሆኑት<br />
አቶ ተመስገን ዘውዴ ከመንግስት<br />
በኩል በተደጋጋሚ የሚደመጠውን<br />
‹‹ከውጭ የገባ ግሽበት›› ዕሳቤ፣<br />
ከጠቅላይ ሚኒስትሩ በተዋረድ<br />
ወደታች እንዲወርዱ የሚደረጉ<br />
ቃላትና ፅንሰ-ሐሳቦች አንድ አካል<br />
አድርገው ይወስዱታል። የነዳጅ<br />
ዋጋ መቀጠል የሚያመጣው የዋጋ<br />
መናር እንዳለ ሆኖ፣ የኢትዮጵያ<br />
ኢኮኖሚ በዓለም አቀፍ ገበያ ካለው<br />
እጅግ አነስተኛ ድርሻ የተነሳ ከውጭ<br />
በሚገባ ግሽበት ማመካኘቱ ወደራስ<br />
ለመመልከት ፈቃደኛ ካለመሆን<br />
እንደሚመነጭ የሚያስገነዝቡት<br />
የንግድ አስተዳደር ባለሙያው፣<br />
ችግሩ የመነጨው ከምርት ዕጥረት<br />
መሆኑን የሚናገሩት አስረግጠው<br />
ነው።<br />
የምግብ ዋጋ ግሽበት የተከሰተው<br />
ከምርት እጥረት የተነሳ መሆኑንና<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
ገንዘብ ያለገደብ የሚጨመርበት ኢኮኖሚ ለጊዜው ያደገ<br />
እንደሚመስል ፊኛ ነው ‹‹ፊኛ ውስጥ አየር ሲጨመር<br />
የፊኛው መጠን ይተልቃል፤ አየሩ ፊኛው ከሚችለው<br />
በላይ ሲሆን ግን ፊኛው መፈንዳቱ አይቀርም››<br />
አቶ ተመስገን ዘውዴ<br />
ይህ ኹነትም የግብርና ምርት<br />
የ11 በመቶ ዕድገት እንዳስመዘገበ<br />
መንግስት የሰጠውን መግለጫ<br />
ጥያቄ ውስጥ እንደሚከተው<br />
ከገለፁት ሁለቱ ባለሙያዎች<br />
በተጨማሪ ሌሎችም ተመሳሳይ<br />
አስተያየት ሰንዝረዋል።<br />
‹‹ግሽበት›› የሚለው ቃል አሁን<br />
የሚስተዋለውን ኹኔታ በሚገባ<br />
እንደማይገልፀውና ከምርት<br />
እጥረት የተነሳ ለተከሰተው የዋጋ<br />
ግሽበት ያለተቆጣጣሪ የሚያድገው<br />
የሕዝብ ቁጥር አስተዋፅኦ<br />
እንዳለው የሚናገሩት በዓለም<br />
ባንክ ውስጥ በኢኮኖሚስትነት<br />
ያገለገሉት አቶ ቡልቻ ደመቅሳ<br />
ናቸው፡፡ በ<strong>አገር</strong> ውስጥ በአነስተኛ<br />
ደረጃ የሚመረተው ምግብ አሁን<br />
ያለውን ሕዝብ መመገብ እንዳልቻለ<br />
የሚያስረዱት አቶ ቡልቻ፣<br />
የ‹‹የሕዝብ ቁጥር እንዳይጨምር<br />
የመከላከል እርምጃ አልወሰደም››<br />
በሚሉት መንግስት ላይ ሙሉ<br />
ተጠያቂነቱን አሳርፈዋል።<br />
የኢትዮጵያ ገበሬዎች ከግማሽ<br />
ሄክታር በምታንስ ኩርማን መሬት<br />
ላይ እያረሱና የዘመናዊ ቴክኖሎጂ<br />
ተጠቃሚ ባልሆኑበት የምርት<br />
ዕድገት ሊኖር እንደማይችል<br />
የገለፁት አቶ ቡልቻ፣ ቁጥሩ<br />
እየጨመረ የሚሄደውን ሕዝብ<br />
ለመመገብና የምግብ እጥረትን<br />
ለማስወገድ የተጠቀሱትን ችግሮች<br />
መፍታት ግድ እንደሚል አፅንዖት<br />
ይሰጡበታል።<br />
መንግስት፣ ከዓለም አቀፍ<br />
ሁኔታዎች በመቀጠል ለግሽበቱ<br />
በመንስዔነት የሚያቀርበው<br />
የንግድ ሥርዓቱ ቅልጥፍና<br />
የጎደለውና ለልዩ ልዩ ኢ-ፍትሐዊ<br />
አሰራሮች የተጋለጠ መሆኑን<br />
ነው። ይህንንም ችግር ለመፍታት<br />
በመሰረታዊ ሸቀጦች ላይ የዋጋ<br />
ተመን ቢያወጣም መልካም<br />
ውጤት ያላገኘ ሲሆን፣ ግሽበቱን<br />
ለማስወገድና የአቅርቦት እጥረትን<br />
ለመቅረፍ ራሱ ሸቀጦችን በማቅረብ<br />
አዲስ የጅምላ ንግድ ሥርዓት<br />
መዘርጋቱም ይታወቃል።<br />
ሆኖም የግሽበቱ ዋና ምንጮች<br />
ሌሎች ጉዳዮች ሆነው ሳለ ችግሩን<br />
በነጋዴዎች ላይ መንግስት<br />
የሚያሳብበው የፖለቲካ ትርፍ<br />
ለማግኘት በማሰብ መሆኑን<br />
የሚገልፁ ወገኖች አልጠፉም።<br />
ኢህአዴግ መራሹ መንግስት ሁሌም<br />
ለችግሮች መፍትሔ የሚሰጠው<br />
ከራሱ የፖለቲካ ትርፍ አኳያ<br />
ብቻ መሆኑን የሚያስገነዝቡት<br />
የሕወሓት/ኢህአዴግ አንዱ<br />
መስራች አቶ ገብሩ አስራት፣<br />
ለአጭር ጊዜ ተግባራዊ ተደርጎ<br />
ፉርሽ የሆነው የዋጋ ተመንም<br />
ለፖለቲካ ትርፍ የታለመ መሆኑን<br />
ይናገራሉ።<br />
‹‹የዋጋ ተመኑ ተግባራዊ<br />
የተደረገው በዋጋ መናር የተነሳ<br />
የተማረረው ሕዝብ ቁጣውን<br />
መንግስት ላይ እንዳይገልፅ<br />
ይልቁኑም ነጋዴውን እንዲጠላ<br />
ለማድረግ ነው›› የሚሉት አቶ<br />
ገብሩ፣ ተመኑ የወጣው ‹‹እሳት<br />
አደጋን›› ለማጥፋት በሚመስል<br />
የጥድፊያ እርምጃ እንጂ ዘላቂ<br />
መፍትሔ ለመስጠት ታስቦ<br />
ባለመሆኑ ብዙም ሳይቆይ መነሳቱ<br />
ላይ ያሰምሩበታል።<br />
ከንግድ ሥርዓቱ ጋር በተያያዘ<br />
‹‹ነጋዴዎች ምርቶችን<br />
አላግባብ ደብቀው በማከማቸት<br />
ዋጋ እያናሩ ነው›› የሚለው<br />
ምክንያትም ለአውራምባ<br />
ታይምስ አስተያየታቸውን<br />
በሰጡ ባለሙያዎች ዘንድ<br />
ተቀባይነት አላገኘም። በአገሪቱ<br />
ያሉት ነጋዴዎች ከፍተኛ ምርት<br />
ደብቀው ሊያከማቹበት የሚችል<br />
ግዙፍ መጋዘኖች እንደሌሉ<br />
የሚያስታውሱት ባለሙያዎች፣<br />
‹‹ይሄ እኮ ግልፅ ነው። የምርት<br />
እጥረት መኖሩን ባለማመን<br />
ሕዝቡንና ነጋዴውን ለማጣላት<br />
የሚደረግ ሴራ ነው›› ባይ<br />
ናቸው።<br />
‹‹ምርት ደብቆ በማከማቸት<br />
እጥረት ተከስቶ ዋጋ ሲንር መሸጥ<br />
የሚፈልግ ነጋዴ እውነት የለም?››<br />
የሚል ጥያቄ ከአውራምባ ታይምስ<br />
ለአስተያየት ሰጪዎቹ ቀርቦ<br />
ነበር። እነሱም ምርት የሚደብቁ<br />
ነጋዴዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ<br />
በማመን፣ ‹‹ሆኖም በገበያው ላይ<br />
ወሳኝ ተፅዕኖ ያላቸው ነጋዴዎች<br />
ኢህአዴግና ደጋፊዎቹ ስለሆኑ<br />
ከእነሱ ውጪ ያሉት ቢደብቁም<br />
ያን ያህል ለውጥ አያመጡም።<br />
ለግሽበቱ የገበያው ሥርዓት<br />
በምክንያትነት የሚቀርብ ከሆነም<br />
ተጠያቂዎቹ ኢህአዴግና ደጋፊዎቹ<br />
ነጋዴዎች ናቸው›› የሚል ምላሽ<br />
ሰጥተዋል።<br />
እስካሁን ከተጠቀሱት ምክንያቶች<br />
ባሻገር ለዋጋ ግሽበት ትልቁ<br />
ምክንያት መንግስት ወጪዎቹን<br />
ለመሸፈን ሲል ከብሔራዊ ባንክ<br />
በመበደርና በማሳተም ወደ<br />
ኢኮኖሚው ያፈሰሰው ገንዘብ<br />
ከመጠን በላይ መሆኑን ብዙዎች<br />
የሚስማሙበት ነው።<br />
የገንዘብ አቅርቦት በኢኮኖሚው<br />
ውስጥ መብዛቱ የተጫወተውን<br />
አሉታዊ ሚና በመገንዘብ<br />
የመንግስትን ወጪ ከብሔራዊ<br />
[በመስከረም ወር<br />
ስለተመዘገበው የዋጋ<br />
ግሽበት አንዳንድ ነጥቦች]<br />
ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ<br />
ወር ጋር ሲነፃፀር አብዛኛዎቹ<br />
የምግብ ክፍሎች ጭማሪ<br />
አሳይተዋል<br />
እህል የ61.9 ከመቶ፣<br />
ጥራጥሬ የ89.4 ከመቶ፣<br />
ዘይትና ቅባቶች<br />
የ69.7ከመቶ፣<br />
ድንችና ሌሎች ስራስሮች<br />
የ41.7ከመቶ፣<br />
ያልተቆላ ቡናና ሻይ ቅጠል<br />
የ88.6ከመቶ፣<br />
ቅመማ ቅመሞች የ62.9<br />
ከመቶ<br />
ጭማሪ አሳይተዋል<br />
ምንጭ፦ የኢፌዴሪ ማዕከላዊ<br />
ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ<br />
ባንክ በሚገኝ ብድር ላለመሸፈን<br />
ከፍተኛ ጥንቃቄ እንደሚያደርግ<br />
(ዘግይቶም ቢሆን) በመግለፅ ላይ<br />
የሚገኘው መንግስት፣ በተያዘው<br />
የበጀት ዓመት ከብሔራዊ ባንክ<br />
ብድር እንደማይወስድ ተናግሯል።<br />
ነገር ግን ይሄንን የመንግስት<br />
ውሳኔ አቶ ገብሩ አስራት<br />
በጥርጣሬ ነው የሚመለከቱት።<br />
መንግስት የጀመራቸውን ግዙፍ<br />
ፕሮጀክቶች ሥራ ለማከናወን<br />
የግድ ከብሔራዊ ባንክ መበደሩ<br />
እንደማይቀር የሚጠቁሙት አቶ<br />
ገብሩ፣ ‹‹አብዛኞቹን ፕሮጀክቶች<br />
ያቀደው ገንዘብ ሳይኖረው ነው።<br />
ስለዚህ እነሱን ለመስራት ሲል<br />
መበደሩ አይቀርም፡፡ ይሄ ደግሞ<br />
ግሽበቱን ያባብሰዋል›› የሚል<br />
መከራከሪያ ያቀርባሉ።<br />
የዋጋ ግሽበት ማለት ሌላ ተዐምር<br />
ሳይሆን በኢኮኖሚው ውስጥ<br />
ጥቂት ምርቶችና በርካታ ገንዘብ<br />
መኖር ማለት መሆኑን ቀለል<br />
ባለ አቀራረብ የሚያስረዱት አቶ<br />
ቡልቻ፣ መንግስት ከብሔራዊ<br />
ባንክ የሚወስደው ብድር<br />
መጠን እንዲታወቅ አለመፈለጉ<br />
ያሳዝናቸዋል። ‹‹መንግስት<br />
ከሚችለው በላይ እየተደበረ<br />
ጥቂት ምርት ባለበት ኢኮኖሚ<br />
ውስጥ ብዙ ገንዘብ አንዲዘዋወር<br />
አድርጓል። በፊት ከብሔራዊ ባንክ<br />
የሚወስደውን የብድር መጠን<br />
የሚወስን ሕግ ነበር። ይሄን<br />
ሕግ ከዓመታት በፊት በፓርላማ<br />
እንዲሻር አድርጓል›› የሚሉት<br />
በዓለም ባንክ በኢኮኖሚስትነት<br />
ያገለገሉት ባለሙያ፣ መንግስት<br />
በፓርላማ የሚሾመውን<br />
ዋና ኦዲተር እንደማያከብር<br />
ይወቅሳሉ።<br />
አቶ ተመስገን ዘውዴም<br />
የመንግስትን አጠቃላይ ዓመታዊ<br />
ሂሳብ መርምሮ ሪፖርቱን ለፓርላማ<br />
በሚያቀርበው ዋና ኦዲተር<br />
መንግስት ደስተኛ እንዳልሆነና<br />
አንዳንዴም ሪፖርቶችን ውድቅ<br />
የሚያደርግበት ሁኔታ መኖሩን<br />
የሚገልፁት በመገረም ነው።<br />
ከጥቂት ዓመታት በፊት የፌደራል<br />
ዋና ኦዲተር ባደረገው ማጣራት<br />
በርካታ ቢሊዮን ብሮች ወደ<br />
ኢኮኖሚው ውስጥ ያላግባብ<br />
ፈሰስ መደረጋቸውን ሪፖርት<br />
ቢያደርግም፣ ጠቅላይ ሚኒስትር<br />
መለስ ዜናዊ ‹‹ተራ የሂሳብ<br />
ሠራተኛ ሊሳሳት የማይችለውን<br />
ስህተት ዋና ኦዲተር ፈፅሟል››<br />
ማለታቸውን ለሚያስታወሱት አቶ<br />
ተመስገን፣ መንግስት ግልፅነት<br />
የጎደለው አካሄድ እየተከተለ<br />
‹‹ግሽበቱን እቆጣጠራለሁ›› ማለቱ<br />
የሚዋጥ አይደለም።<br />
ዕድገት Vs ግሽበት<br />
በአሁኑ ሠዓት የሚስተዋለው<br />
ግሽበት በዕድገት ሂደት<br />
የሚከሰት መሆኑ ከመንግስት<br />
በኩል ይደመጣል። በአንፃሩ<br />
ደግሞ በትክክለኛ ዕድገት ውስጥ<br />
የሚከሰት ግሽበት ከአንድ አሀዝ<br />
እንደማይበልጥ በመግለፅ፣ ‹‹የምር<br />
ግሽበቱ የተከሰተው ከዕድገት ጋር<br />
ተያይዞ ቢሆን ኖሮ ሕዝቡ ለምን<br />
ይቸገራል?›› የሚለው ጥያቄ<br />
የበርካቶች ነው።<br />
ኢኮኖሚ የሚያድገው ብዙ ምርት<br />
ሲኖር እንጂ ከገደብ ባለፈ ገንዘብ<br />
አለመሆኑን የሚያስገነዝቡት<br />
ከአውራምባ ታይምስ ጋር ቆይታ<br />
ያደረጉ ባለሙያ፣ ‹‹11 በመቶ<br />
የኢኮኖሚ እድገት ተመዝግቧል<br />
የሚባለውም ሀሰት ነው፡<br />
፡ በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉት<br />
የምግብ እጥረት፣ የዋጋ መናርና<br />
ሌሎች ችግሮች የአስከፊ ድህነት<br />
መገለጫዎች እንጂ የእድገት<br />
አይደሉም›› በማለት ሞግተዋል።<br />
የኢኮኖሚ ዕድገትንና የዋጋ<br />
ግሽበትን በፊኛና ፊኛው ውስጥ<br />
በሚጨመረው አየር የሚመስሉት<br />
የንግድ አስተዳደር ባለሙያ<br />
የሆኑት አቶ ተመስገን ዘውዴ፣<br />
ኢኮኖሚውን ለማሳደግ በሚል<br />
ምክንያት ገንዘብ ያለ ገደብ ወደ<br />
ኢኮኖሚ ማስገባት ከፍተኛ መዘዝ<br />
እንዳለው ያሳስባሉ። ገንዘብ<br />
ያለገደብ የሚጨመርበት ኢኮኖሚ<br />
ለጊዜው ያደገ እንደሚመስል<br />
‹‹ፊኛ ውስጥ አየር ሲጨመር<br />
የፊኛው መጠን ይተልቃል፤ አየሩ<br />
ፊኛው ከሚችለው በላይ ሲሆን<br />
ግን ፊኛው መፈንዳቱ አይቀርም››<br />
በሚል ምሳሌ ነው ያስረዱት።<br />
‹‹ፊኛው›› ውስጥ የሚጨመረውን<br />
‹‹አየር›› መቀነስ የፊኛውን መጠን<br />
ስለመቀነሱ ከአውራምባ ታይምስ<br />
ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ ‹‹ኢኮኖሚው<br />
ውስጥ የሚረጨው ገንዘብ ይቀንስ<br />
ማለት እኮ መንግስት የልማት<br />
ሥራዎችን ለማከናወን ሙሉ<br />
በሙሉ ገንዘብ አይጠቀም ማለት<br />
አይደለም፤ በሚያስፈልገው ልክ<br />
ብቻ ይጠቀም ማለት እንጂ›› ነበር<br />
ምላሻቸው።<br />
የተወሰነ የግሽበት መጠን ከኢኮኖሚ<br />
እድገት ጋር ተያይዞ በሚፈጠረው<br />
የገንዘብ ዝውውር የተነሳ ሊስተዋል<br />
ቢችልም፣ ኢትዮጵያ ውስጥ<br />
ያለው አደገኛ ግሽበት (hyper<br />
inflation) ግን የእድገት ሳይሆን<br />
የድቀት ማሳያ መሆኑን የሚገልፁ<br />
ባለሙያዎች ደግሞ በበኩላቸው<br />
ችግሩን ‹‹ከልማታዊ መንግስት››<br />
ፅንሰ-ሀሳብ ጋር ያቆራኙታል።<br />
መንግስት ሊሰራቸው ካቀዳቸው<br />
ግዙፍ ፕሮጀክቶች ውስጥ<br />
የግል ባለኃብቶች ሊሰማሩባቸው<br />
የሚገባቸውን ከዕቅዱ ውስጥ<br />
አውጥቶ ወጪውን በመቀነስ<br />
ግሽበቱን መቆጣጠር እንደሚችል<br />
በመግለፅ የመፍትሄ ሀሳብ<br />
ያቀርባሉ።<br />
መፍትሔው ምንድን<br />
ነው?<br />
ለአውራምባ ታይምስ<br />
አስተያታቸውን የሰጡ ባለሙያዎች<br />
ከተራ ግሽበትነት አልፎ አደገኛ<br />
ደረጃ ላይ ለደረሰው የዋጋ ግሽበት<br />
ዋና መፍትሄው መንግስት ወደ<br />
ኢኮኖሚው ያላግባብ የረጨውን<br />
ገንዘብ መሰብሰብ በመሆኑ ላይ<br />
ያሰምሩበታል።<br />
ገንዘብ ከኢኮኖሚው ውስጥ<br />
ለመሰብሰብ ከተጠቆሙት<br />
የመፍትሄ አቅጣጫዎች መካከል<br />
የመጀመሪያው መንግስት<br />
የብሔራዊ ባንክን ነፃነት በማክበር<br />
ከተገቢው በላይ ብድር መውሰዱን<br />
ማቆሙ ሲሆን፣ የባንክ የወለድ<br />
መጠንን በመጨመር ሰዎች<br />
ገንዘብ ባንክ እንዲያስቀምጡ<br />
ማበረታታትና የተለያዩ ዓይነት<br />
ቦንዶችን በመሸጥ ገንዘብ<br />
መሰብሰብም ሌሎች የተጠቆሙ<br />
አማራጭ መፍትሄዎች ናቸው፡፡
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />
ማ ስ ታ ወ ቂ ያ<br />
13<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ
14<br />
መንግሥት በዜጎቹ ላይ<br />
ሬዲዮ የለንም በሬዲዮ መልስ<br />
አይሰጥ ነገር ግራ የገባው ግራ ሆኖብኝ<br />
ነው፡፡ የሬዲዮ ፋና አድማጭ አይደለሁም፡<br />
፡ አብርሃም የሚባል የሬዲዮ ፋና ባልደረባ<br />
ደውሎ በአሸባሪነት አዋጅና በጠቅላይ<br />
ሚኒስትሩ የፓርላማ ውሎ ዙሪያ<br />
የመንግስት ባለስልጣናት የሚገኙበት<br />
የጋራ ውይይት ሰለሚደረግ ፈቃደኝነቴን<br />
ጠየቀኝ፡፡<br />
አኔም ፈቃደኝነቴን ገልጬለት<br />
ቅዳሜ ለሰባት ዕሩብ ጉዳይ ሬዲዮ<br />
ፋና ጣቢያ እንድንገናኛ ቀጠሮ ያዝን፡፡<br />
ጋዜጠኛው ከቀጠሮ ሰዓት ቀደም ብሎ<br />
በአምስት ሰዓት አካባቢ ስልክ ደውሎ<br />
‹‹ሰማኸው አይደል?›› አለኝ። ‹‹ምኑን?››<br />
ስለው ‹‹ማስታወቂያ ለቀናል። ውይይት<br />
እንዳለ አንተም እንደምትገኝ›› አለኝ፤<br />
‹‹ትቀልዳለህ እንዴ? የፋና አድማጭ<br />
አይደለሁም። አሁን ያለሁት ሥራ ላይ<br />
ነው፤ በቀጠሮ ሰዓት ግን እመጣለሁ››<br />
ብዬው በቀልድ ተለያየን።<br />
በእውነትም የሬድዮ ፋና<br />
አድማጭ አይደለሁም። ነገር ግን<br />
እኔ መኪና ውስጥ በአንድ ምክንያት<br />
የተከፈተ ካሴት፣ ሲዲ ወይም ሬዲዮ<br />
ጣቢያ ለሳምንት ምን አልባትም የቴክኒክ<br />
እክል ካልገጠመውና የተሳፋሪ ተቃውሞ<br />
ካልተነሳበት ለወርም ሳይነካ ሊቀጥል<br />
ይችላል። በዚህ ዓይነት ሁኔታ ረቡዕ<br />
በፋና ሬዲዮ ጣቢያ “ተጓዝ ነቃሽ” የተባለ<br />
ፕሮግራም ለመከታተል በቃሁ።<br />
በማግስቱም ዘጠና ደቂቃ<br />
የሚል ፕሮግራም በተመሳሳይ ጉዳይ ላይ<br />
ሲተላለፍ አደመጥኩ። ምቀኝነትን ዜጎች<br />
እርስ በርሳችን በመንግስት ተቋማት<br />
አጋዥነትና በሚዲያ አሟሟቂነት ነብስ<br />
ዘርቶ አገኘሁት፡፡ ዝርዝረሩን ቀጥዬ<br />
አቀርባለሁ።<br />
የፕሮግራሙ ዋና ጭብጥ<br />
በሀገራችን በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ<br />
የመንግስት ቤት ተከራይተው በመንግስት<br />
ቤት አለአግባብ ጥቅም የሚያገኙ፣<br />
ህብረተሰቡን እየበዘበዙ ያሉ ህገወጥ<br />
ሰዎች እንዳሉ፤ እነዚህ ሰዎች ላይም<br />
አስፈላጊው እርምጃ መወሰድ እንዳለበትና<br />
መንግስት እሰከ አሁን ዝም ማለቱ ተገቢ<br />
እንዳልሆነ በተለያየ መንገድ የሚገልፅ<br />
ነው።<br />
ትኩረቱ ቤት ሸንሽነው ለንግድ<br />
ቤትነት የሚያከራዩ ዜጎች ላይ ነው፡፡ ነገሩን<br />
የበለጠ ግልፅ ለማድረግ ከመንግስት ቤት<br />
ተከራይተው ሸንሽነው የሚያከራዩ ሰዎች<br />
ሕገ-ወጥ፣ በዥባዦች፣ ለተፈጠረው<br />
የዋጋ ንረት ተጠያቂዎች ተደርገው የክስ<br />
መዓት ይወርድባቸዋል።<br />
የሚያሳዝነውና እንደመፍትሄ<br />
የቀረበው ደግሞ በሽንሽን ቦታዎች<br />
ላይ ተከራይተው የሚሰሩት ሰዎች<br />
የያዙትን ቦታ ለመውረስና በዝቅተኛ ዋጋ<br />
ተከራይተው እንዲቀጥሉ ያቀረቡት በህግ<br />
ሽፋን የመውረስ ጥያቄ ነው፡፡ ጉዳዩ አቶ<br />
ተፈራ ዋልዋ የአዲስ አበባ መስተዳድር<br />
ከንቲባ እያሉ የነበረውን ዓይነት የተከራይ<br />
አከራይ ድራማ ለመድገም የተጠነሰሰ<br />
ሴራ እንዳለ የሚያመላክት ነገር አለው።<br />
ለማገገም እየሞከረ የነበረውን<br />
በንግድ ማህበረሰብ ውስጥ ያለን ጤናማ<br />
ግንኙነት በድጋሚ እንዲበላሽ የሚያደርግ<br />
ውሳኔ መጠንሰሱን መጠርጠር ደግ<br />
ከመሆኑ በላይ፣ ቤታቸው /የተከራዩትንም<br />
ቢሆን/ ለመወረስ የተዘጋጀ መሆኑን<br />
ሽንሽን ሰርተው በማከራየት ላይ ያሉ<br />
ዜጎች ልብ ሊሉት ይገባል።<br />
በፋና የዋህ አድማጮችና<br />
የሰውን ንብረት ለመውረስ በተዘጋጁ<br />
የሽንሽን ቤት ተከራዮች ከሚቀርቡት<br />
ክሶች ዋነኛ የነበረው “የመንግስትን ቤት<br />
በርካሽ ተከራይተው በውድ እያከራዩ ነው”<br />
የሚለው ነው፡፡ ለመሆኑ የመንግስት<br />
ቤት ማለት ምን ማለት ነው? በመርካቶ<br />
የመንግስት ቤት ማለት የቱ ነው?<br />
መንግስት አንድ ቆርቆሮ ያላለበሰው፣ አንድ<br />
ምስማር ያልመታበት ደርግ የወረሳቸውን<br />
ቤቶች ነው መንግስት “የእኔ ናቸው”<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
በግርማ ሰይፉ<br />
የሚለው፡፡ እንግዲህ ደርግን በመውረሱ<br />
እየኮነነ ደርግ በወረሰው ንብረት ደግሞ<br />
ዜጎችን ለማፈን እየሞከረ ነው።<br />
ሸንሽነው የሚያከራዩ ሰዎች<br />
ግን የሚያከራዩትን ቤት ለገበያ ቦታ<br />
እንዲሆን ገንዘባቸውንና እውቀታቸውን<br />
ገብረውበታል። ከዚያም በላይ <strong>ስር</strong>ዓቱ<br />
የሚጠይቀውን በሽፍንፍን ሙስና፣ በግልፅ<br />
ግን ለግንባታ ማስፈቀጃ ከፍለውበታል።<br />
ጉቦ መክፈላቸው አያስደስተኝም። ከሱ<br />
ጋር የከፈሉት ነፃነታቸው ግን የበለጠ<br />
አንጀቴን ይበላዋል።<br />
ይህን በማድረጋቸው ኢህአዴግን<br />
ሲደግፉ እንደነበረም አውቃለሁ።<br />
የኢህአዴግ ደጋፊ ነጋዴዎች ፎረም<br />
አባል በመሆንም ድጋፍ አድርገዋል።<br />
ኢህአዴግ ግን ዛሬ ከነዚህ ጥቂቶቹ ይልቅ<br />
በሽንሽን ውስጥ ያሉት ብዙኃን የበለጠ<br />
ስለሚያስፈልጉት ነፃነትን ያህል ክብር<br />
የገበሩለት ቢዝነሳቸውን ሊወርስባቸው<br />
ነጋሪት እያስጎሰመ ነው።<br />
ነፃነታችሁን የሸጣችሁ ዕለት<br />
ብዙ ነገር አብሮ እንደተወረሰ ልብ ማለትም<br />
ተገቢ ነበር። አሁን ግን ነፃነታችሁን<br />
የሸጣችሁለት ንብረት ሊወረስ ነው።<br />
የሽንሽን ቤት ወራሾች በናንተ ተራ ገብተው<br />
የናንተን ንብረት ሲወርሱ እነርሱም<br />
በተራቸው ነፃነታቸውን ለማስወረስ<br />
ተዘጋጅተው ብቻ እንዳይመሰላችሁ፤<br />
ለልጆቻቸው ሁሉ የሚነግሩት እውነት<br />
የላቸውም። ዘርፈው እንደሚያወርሷቸው<br />
አይነግሯቸውም።<br />
ሌባ ለልጁ መስረቁን<br />
አይነግርም፤ ልጅ ግን ሁሌም ስለወላጆቹ<br />
የኃብት ምንጭ ያስባል። ልጆቻችንን<br />
ከማሳቀቅ ብንታቀብ ምን ይመስላችኋል?<br />
አንድ ተከራይ ነኝ ያሉ ግለሰብ በብር<br />
ሶስት ሺህ አምስት መቶ እንደተከራዩ<br />
ነገር ግን ስለማያተርፉ ኪራዩን ተበድረው<br />
እንደሚከፍሉ በማሰተዛዘን ገልፀዋል።<br />
ዕውነቱን ለመናገር ኪራይ<br />
በብድር አይከፈልም፤ ዓላማው መንግስት<br />
የዚህን ያህል ኪራይ እንዳያስከፍላቸው፣<br />
ብሎም ከዚህ ጋር ተመጣጣኝ ገቢ መሰረት<br />
አድርጎ የገቢ ግብር እንዳይጠየቁ የዘየዱት<br />
ነው። ከዚህ ባሻገር አከራዩ እንዲከራዩት<br />
አላስገደዳቸውም፤ ምናልባትም ተጫርተው<br />
ነው የተከራዩት፤ እገሌን አስወጣው፤ እኔ<br />
ይህን ያህል እከፍላለሁ ብለው ጭምር<br />
ሊሆን ይችላል።<br />
የኪራይ ቤቶች፣ የሬዲዮ<br />
ጣቢያ አዘጋጆች፣ የተከራዮች ወዘተ …<br />
ምቀኝነት ነብስ ዘርቶ የሚታየው አከራዮቹ<br />
የሚያገኙትን ሂሣብ ሰርተው በምናባቸው<br />
ሲያዩት ነው። ቀደም ሲል እንደገለፅኩት<br />
አንድ ምሰማር ላልመታ መንግስት<br />
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />
ለምን ምቀኛ ይሆናል?<br />
በነገራችን ላይ አንድ የተከራዩትን ቤት ሸንሽነው በውድ እያከራዩ በዘበዙን የምትሉ<br />
ዜጎች እነዚህ ሰዎች ከማከራየት ይልቅ ለብቻቸው ይዘውት እንደአንድ የገበያ ማዕከል<br />
እየሰሩበት ሰራተኛ ቀጥረው ቢሰሩበት ኖሮ ምን ትሉ ይሆን? ከዚህ ይልቅ ግን ሰራተኛ<br />
ቀጥሮ ከማሰተዳደር ሁሉም በነፃነት እንዲሰራ ኃላፊነት እንዲሰማው ማከራየት ይሻላል<br />
ብለው አማራጭ መውሰድ ኃጥያት መደረጉስ ለምንድነው?<br />
የመንግስት ቤት እያሉ የሱ ያልሆነውን<br />
ሲሰጡት፤ የንግድ ሂሣቡን፣ ለተሻለ የገቢ<br />
ምንጭ ብሎ ብዙ ጊዜና ገንዘብ ያወጣውን<br />
ዜጋ ግን በዝባዥ ብለው ያለ ስሙ ስም<br />
ይሰጡታል።<br />
ዜጋ ገንዘብ ሲያገኝ የሚቀና<br />
ምቀኛ ሥርዓትና ይህንን ለማገልገል<br />
የተሰለፉ ሎሌዎች ብዛት ስመለከት<br />
ዕፍረት ይሰማኛል። ጣቢያው በዛው<br />
ዕለት ስለነፃ ኢኮኖሚ ሲሰብክ ብትሰሙት<br />
እንዳይገርማችሁ። ግራ የገባው ግራ<br />
ማለት ይሄኔ ነው። መንግሰት በዘረፋ<br />
የያዘውን ቤትም ቢሆን ዜጎች አከራይተው<br />
ገንዘብ እንደሚያገኙ መረጃ ካለው በንዴት<br />
መብገን ያለበት አይመሰለኝም፤ ተገቢም<br />
አይደለም።።<br />
ዜጎች ባገኙት ገቢ ልክ ግብር<br />
መሰብሰብ ነው ከመንግስት የሚጠበቀው።<br />
የመንግስት ወግ ይህ ነው። ይልቁንም<br />
ተከራዮች በሚከፍሉት ኪራይ ልክ<br />
ግብር እንዳይጠየቁ ኪራይ ተቀንሶ<br />
እንዲነገርላቸው እንደሚማፀኑ ስንቶቻችን<br />
እናውቃለን? እውነቱን ለመነጋገር አከራዩ<br />
ከኪራይ በሚያገኘው ኪራይ ልክ ግብር<br />
አልከፈለም ብለው ሲከሱ የነበሩ ተከራዮች<br />
እስኪ ለኪራይ በከፈሉት ልክ የገቢ ግብር<br />
መክፈላቸውን ይናገሩ። ዓሣ ጎርጓሪ ዘንዶ<br />
ያወጣል ማለት ይህ ይመሰለኛል።<br />
መንግስት ዜጎች ገንዘብ ሲያገኙ<br />
ለምን እንደሚመቀኝ አይገባኝም፡፡ ይህ<br />
ከሶሻሊዝም የወረስነው፤ በአብዮታዊ<br />
ዴሞክራሲ እያዳበርነው ያለነው የመንግስት<br />
ሞግዚትነት አባዜ ውጤት ነው፡፡ ዜጎች<br />
ገንዘብ ሲያገኙ ለተጨማሪ ሥራ ፈጠራ፣<br />
አዳዲስ ቴክኖሎጂ ለማስመጣት፣ ለሀገር<br />
ዕድገት፣ ወዘተ ያውሉታል የሚል ቅን<br />
ልቦናችንን ምን እንደወሰደው መጠየቅ<br />
ያለብን ይመስለኛል።<br />
ሶሻሊዝም በዓለም እንደተወዳዳሪ<br />
ርዕዮት ከተወገደ ከሃያ ዓመት በኋላ<br />
በእኛ ሀገር የሃያና ሃያ አምስት ዓመት<br />
ወጣቶች በዚህ አባዜ ተለክፈው ማየት<br />
ምን እንደሚባል አላውቅም። ከመንግሥት<br />
ይልቅ ግን ዜጎች የሚያገኙትን ገንዘብ<br />
ለተሻለ ሀገራዊ ጥቅም ስለሚያውሉት<br />
መንግሥት ከተወሰኑ መስኮች ውጭ<br />
የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን ለዜጎች መተው<br />
አለበት በሚባልበት ዘመን ላይ ሆነን የእኛ<br />
መንግስት ግን ቤት በማከራየት ሥራ<br />
እንዲሰማራ፣ ሱቅ ሸንሽኖ እንዲያከራየን<br />
እንጠብቃለን።<br />
ዛሬ መንግስት ሱቅ ሸንሸኖ<br />
እንዲያከራየው በሬዲዮ የለመነ ሁሉ<br />
ከዚህ ጋር ተያይዞ መንግስት በነፃነቱ ላይ<br />
የሚያደርሰውን ጫና ለመሸከም ጫንቃውን<br />
ማደንደን ይኖርበታል። መንግስት ከቀበሌ<br />
ቤት እንዳንወጣ፤ ከወጣንም ኮንዶሚኒየም<br />
ውስጥ እንድንገባ የሚፈልገው ስለሚወደን<br />
የሚመሰለው ካለ አይሞኝ። ነፃነታችን<br />
ስለሚያስፈራው ነው። ፋብሪካ ወደ ግል<br />
እንዲዛወር እፈልጋለሁ የሚል መንግስት<br />
ቤት የማከራየት ሥራን ከእጁ ለማውጣት<br />
ወደኋላ የሚለው ለምን ይመሰላችኋል?<br />
አሁንም ቢሆን ከኪራይ ቤቶች<br />
በኪራይ የተያዘን ቤት ሸንሽኖ ማከራየት<br />
ክልክል ከሆነ ይህ በግልፅ ተነግሯቸው<br />
ተከራዮች አማራጭ ሊፈልጉ ይገባል፤<br />
ይህ ሕገ-ወጥ ነው ከተባለም (በእኔ ዕምነት<br />
አይደለም) የንግድ ቦታዎቹን የያዙት ሰዎች<br />
ቦታውን መያዝ ያለባቸው አሁን በያዙት<br />
ዋጋ ሳይሆን በግልፅ ጨረታ በውድድር<br />
አሸንፈው መሆን ይኖርበታል።<br />
የሰው ንብረት ለመውረስ<br />
የቋመጡ የሽንሽን ሱቅ ተከራዮች<br />
ገደባቸውን ሊያልፉ አይገባም። ይህ ውሳኔ<br />
መዘዙ ብዙ ሊሆን እንደሚችል መገመት<br />
አያስቸግርም። የሕይወትና ንብረት<br />
ኪሣራ ሊያስከትል እንደሚችል መንግስት<br />
ተረድቶት ውሣኔውን በጥሞና ሊመረምር<br />
ይገባል።<br />
በነገራችን ላይ አንድ የተከራዩትን<br />
ቤት ሸንሽነው በውድ እያከራዩ በዘበዙን<br />
የምትሉ ዜጎች እነዚህ ሰዎች ከማከራየት<br />
ይልቅ ለብቻቸው ይዘውት እንደአንድ<br />
የገበያ ማዕከል እየሰሩበት ሰራተኛ ቀጥረው<br />
ቢሰሩበት ኖሮ ምን ትሉ ይሆን? ከዚህ<br />
ይልቅ ግን ሰራተኛ ቀጥሮ ከማሰተዳደር<br />
ሁሉም በነፃነት እንዲሰራ ኃላፊነት<br />
እንዲሰማው ማከራየት ይሻላል ብለው<br />
አማራጭ መውሰድ ኃጥያት መደረጉስ<br />
ለምንድነው?<br />
በእኔ ዕምነት የሰው ንብረት<br />
ለመውረስ መንግስትም ካለበት<br />
የተቆጣጣሪነትና በሁሉም ነገር ያገባኛል<br />
ከሚል አባዜ የመጣ ነው የሚል ዕምነት<br />
ነው ያለኝ። ይህ የሰው ንብረት የመውረስ<br />
አባዜ ግን በእኛ ብቻ ሳይሆን ለልጅ<br />
ልጆቻችን የሚተርፍ ጦስ ይዞ ይመጣል።<br />
በጥሞና ልናስብበት ይገባል የሚል ዕምነት<br />
አለኝ። ግለሰብ ከሚበዘብዘኝ፣ መንግስት<br />
ይበዝብዘኝ ነው ምርጫው የሚመሰለው።<br />
የመንግስትን ሚና በቅጡ<br />
ካለመረዳትና ደርግ በቀደደው የመውረስ<br />
መንገድ የተመሰረተ ድርጅት/ኤጀንሲ<br />
ኃላፊ ነን የሚሉ ሰዎችም ወንበራቸው<br />
ጊዜያዊ መሆኑን ተረድተው በማያገባቸው<br />
የሽንሽን ሱቅ የማከራየት ሥራ ባለመግባት<br />
መንግስትን ባያስወቅሱት ደግ ነው።<br />
መንግስት ገቢ ማግኘት አለበት ካሉ<br />
መንግስት ሽንሽን ሱቅ አከራይቶ ሳይሆን<br />
ግብር ሰብሰቦ መሆን ነው ያለበት።<br />
የመንግስት የገቢ ምንጭ መሆን<br />
ያለበት ግብር ነው። በዚህ ፅሁፍ በሽንሽን<br />
ሱቅ ያላችሁ ዜጎች ዛሬ ለጊዜያዊ ጥቅም<br />
የምትወስዱትን አቋም ቆም ብላችሁ<br />
እንድታስቡበት መምከር እወዳለሁ።<br />
ባለፈው ጊዜ መንግስት የፓርኪንግ ሥራ<br />
የጀመሩትን ባለኃብቶች ወርሶ ለፓርኪንግ<br />
ሰጥቶዋል፤ ዛሬ ኪራይ ቤቶች ኤጄንሲ<br />
በተከራይ አከራይ ሰም ሊወርስ ነው፣<br />
ነገ ሌላ ይቀጥላል። እንዲህ እያልን ተራ<br />
በተራ እንወረሳለን ማለት ነው።<br />
/የተከበሩ አቶ ግርማ ሠይፉ<br />
የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል ናቸው/
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />
እንዴት ሰነበታችሁ ሰሞነኛ<br />
ወዳጆቼ? …‹‹አላርፍ ያለች<br />
ጣት ለእጇ ካቴና አታጣም››<br />
ይላሉ እኒያ የማላቃቸው<br />
ሴትዮ። የብዕር ወገብ<br />
በጨበጡ ቁጥር ‹‹ተናገር<br />
ተናገር›› ለሚላቸው ብዕር<br />
ለባሾች በጠቅላይ ሚኒስትራችን በኩል<br />
መልዕክት አስተላልፈናል። መቼም መልዕክቱ<br />
እናንተ ጆሮ ሲደርስ ጣሊያንኛ ይሆናል<br />
ብለን አናስብም። ‹‹መልዕክቱን የተቀበለ እሱ<br />
ይድናል›› ይላሉ ያልተፃፈው መፅሐፍ። ሲፃፍ<br />
ደግሞ ብዙ ይላል ብለን ተስፋ እናደርጋለን።<br />
ወዳጆቼ ለእናንተ የሚሆን ወግ<br />
ፍለጋ ከኳስ ሜዳ እስከ ሽሮ ሜዳ፣ ከቦሌ እስከ<br />
ጉለሌ ስዞር ለወግ ማድመቂያ የሚሆን አንዱ<br />
ሹክ ያለኝን ልንገራችሁማ… ማነህ ወዳጄ<br />
ክሬዲቱ ተይዞልሀል። ነገሩ እንዲህ ነው እድሜ<br />
ለጠሀዩ መንግስታችንና ኑሮ እንደ ሮኬት ላይ<br />
በተስፈነጠረበት በዚህ ጊዜ የሰውዬው የቤት<br />
ሠራተኛው በወጣ በገባ ቁጥር ‹‹እንትን አለቀ<br />
እንትንም የለም›› በማለት ስታሳቅቀው ነበርና<br />
አንድ ቀን መልዕክት ልትነግረው ገና ጋሼ<br />
ስትለው ‹‹904 ደሞ ዛሬ ምን አለቀ?›› አላት<br />
አሉ የጉድ አይደለም? ከጉድ ወዲያንዲያ<br />
እንጂ… [እየበላሽ የማታድጊው ስልኬ ትዝ<br />
አልሽኝ]<br />
ቆይ ሳልረሳውማ የእንትን ሰፈር<br />
ልጆች ቴሌ ሰራተኛ አባሮ እንዴት ሊሰራ<br />
ነው? እያላችሁ ስትንሾካሹኩ አልነበር? ይሄው<br />
የኔትወርኩን ምህዳር ‹‹በማስፋት›› ኩም<br />
አደረገልና! በእርግጥ አዲስ አበባ ከሰው ጋር<br />
በስልክ መነጋገር እንደ ዝቋላ ዳገት አስቸጋሪ<br />
እየሆነ ነው። ‹‹ፖለቲከኞች እና ፖለቲካ<br />
ጋዜጣ ላይ የሚሰሩ ጋዜጠኞች ጋር ስንደውል<br />
ኔትወርክ፣ ሀርድ ዎርክ ይሆንብናል። አሁንማ<br />
ከፍቅር ጓደኛችን ጋር ስናወራም…›› የሚሉ<br />
ወቀሳዎች ኢትዮጵያን ከመጪው ዓለም ጋር<br />
‹‹በማቀራረብ›› ላይ ያለው ቴሌያችን ላይ<br />
እየተሰማ ነው። አንድ አሉባልተኛ ወዳጄማ<br />
‹‹ቴሌ የተለወጠው ስሙ ብቻ ነው›› ብሎኝ<br />
በንዴት የሁለት ወር ጉንፋን ለቆብኛል።<br />
ኢትዮ ቴሌኮምዎች አታሰድቡን እንጂ!<br />
‹‹የደወልንላቸውን ደንበኛ አሁን ማግኘት<br />
ካልቻልን›› በቀጠሮ መቼ እንደምናገኛቸው፣<br />
መቼ እንደሚመቻቸው ጠይቃችሁ ንገሩንማ!<br />
እኔ የምወዳችሁ፣ እናንተ የማትነግሩኝ<br />
ወዳጆቼ ደሞ ለወግ? ነፍ ነበር ምን ዋጋ አለው<br />
የታች ሰፈር ልጆች ጢባራቸው አስቸገረን<br />
ወይኔ ነገር ሲጠመዝዙ … አቦ ተውና!<br />
ሰ ሞ ነ ኛ<br />
አንድ የአማርኛ መዝገበ ቃላት ‹‹ሰሞንኛ›› የሚለውን ቃል፣ ‹‹ከዕሁድ እስከ ዕሁድ የሚያገለግል ሰው›› ሲል<br />
ይተረጉመዋል። እኔም የሰማሁትን ላሰማዎ፣ ያየሁትን ላሳይዎ፣ ትጉ ሰሞነኛ አገልጋይዎ መሆንን ወደድሁ።<br />
‹‹ንቦች አሜሪካ ውስጥ አስቸገሩ››<br />
ሬዲዮ ፋና<br />
‹‹ፋና ሆይ ንቦች ያላስቸገሩበት የት አይታችኋል?›› የታች ሰፈር ልጆች<br />
እኔስ ምኔ ፋራ ‹‹እንቆቅልሽ›› አልኳቸው ‹‹ምን እናውቅልህ?››<br />
ሲሉኝ ‹‹ድርቅ እያለ ረሀብ የሌለባት <strong>አገር</strong>›› ብላቸው እንዴት<br />
ይመልሱት! ማሰቢያ’ኮ የለም፤ ኔፕ ናቸው። ‹‹በቃ ሰፈር ስጡኝ››<br />
ብላቸው ቤተ-መንግስትን አይሰጡኝ መሰልዎ! በስማምዬ! ቤተ-<br />
መንግስት ሆኜ ምን አጥቼ፣ ሁሉ በጄ፣ ሁሉ በደጄ… ስፈልግ<br />
አስሬ፣ ሳልፈልግ ከ<strong>አገር</strong> አባርሬ ምን ነበር ጥያቄው? ጠፋብኝ<br />
መልሱ ግን ኤርትራ ነው።<br />
ብዬ ሃርድ ምናምን ብቦጭቅላቸው ‹‹ሌላስ<br />
የለህም?›› አይሉኝም የሆነ የእንቆቅልሽ ጥያቄ<br />
አስመስለውት። እኔስ ምኔ ፋራ ‹‹እንቆቅልሽ››<br />
አልኳቸው ‹‹ምን እናውቅልህ?›› ሲሉኝ<br />
‹‹ድርቅ እያለ ረሀብ የሌለባት <strong>አገር</strong>›› ብላቸው<br />
እንዴት ይመልሱት! ማሰቢያ’ኮ የለም፤ ኔፕ<br />
ናቸው። ‹‹በቃ ሰፈር ስጡኝ›› ብላቸው ቤተ-<br />
መንግስትን አይሰጡኝ መሰልዎ! በስማምዬ!<br />
ቤተ-መንግስት ሆኜ ምን አጥቼ፣ ሁሉ በጄ፣<br />
ሁሉ በደጄ… ስፈልግ አስሬ፣ ሳልፈልግ ከ<strong>አገር</strong><br />
አባርሬ ምን ነበር ጥያቄው? ጠፋብኝ መልሱ<br />
ግን ኤርትራ ነው። [ምነው ሆዴ ጮኸሳ?<br />
ራበኝ እንዴ? (ይቅርታ ለካ ረሀብ አይባልም)<br />
የምግብ እጥረት አጋጠመኝ እንዴ? ወይስ<br />
ሆዴ ደርቆ ይሆን?]<br />
[ውድ አንባብያን አሁን የዜና<br />
ሰዓታችን ስለ ደረሰ ከዜናው በኋላ ተመልሰን<br />
እናወጋለን]<br />
ጤና ይስጥልኝ ዜና እናሰማለን፤<br />
ምክንያቱም ከማን እናንሳለን።<br />
‹‹የዘንድሮው ዓመት ከቀጣዩ ዓመት<br />
በሁሉም ነገር የተሻለ ይሆናል›› ሲሉ ቃሊቲ<br />
ያሉት ጋሼ ታምሩ ኤክስክሉሲቭ ለታች ሰፈር<br />
ልጆች ተንብየዋል። ልጆቹም ‹‹ከሚመጣው<br />
ይህኛው የተሻለ ከሆነ በዚሁ ዓመት<br />
ይውጣልን›› ማለታቸውን የሰሙ መንገደኛ<br />
‹‹ይውጣልን የሚሉት እ<strong>ስር</strong> ቤትን ኩፍኝ<br />
ማድረጋቸው ነውን?›› ሳይሉ አልቀረም ብሎ<br />
የጠረጠረው ዳተኛው ዘጋቢ ዜናውን ሳይፅፈው<br />
ቀርቷል።<br />
የውጪ ዜና፡- የስድብ አባት የሆኑት<br />
[ይቅርታ የነበሩት] ሙአመር ጋዳፊ ለስድብ<br />
ሳውንድ ትራክ የሚጠቀሙ ብቸኛው መሪ<br />
እንደነበሩ ሰሞኑን አንድ ቀጣፊ ተናግሯል።<br />
ኰሎኔሉም ትንቢተኛ መሆናቸውን ገልጾ<br />
የዚህ ማሳያው ‹‹አይጥ›› እያሉ የተሳደቡት<br />
በአይጥ ጉሬ መሞታቸውን ለመጠቆም ነው<br />
ብሏል። በሚስጥር የተቀበሩበት ምክንያትም<br />
‹‹ሚስጥር ነው ማን ሰውየውን ያምናል።<br />
ሰማይ ቤትም አረንጓዴውን አብዮት ይሰብኩ<br />
ይሆናል›› ይላል ቶክ.com በጀርባ ገጹ።<br />
እኛ ከዜናው ተመልሰናል ጋዳፊ ግን<br />
ጭረዋል። መልካም ጭረት ይባላል እንዴ?<br />
ኧረ ሳቄ ናልኝ አለች የኛ ሰፈሯ… ‹በህመም<br />
ነው የማይቀለደው እንጂ በሞትማ ቀላል<br />
ይቀለዳል እንዴ? በነገራችን ላይ ‹‹በህመም<br />
ነው የማይቀለደው እንጂ በሞት ይቀለዳል››<br />
የሚለው የትኛው ኢንሳይክሎፒዲያ ነው?<br />
የታች ሰፈሩ ላይ ይሆን?<br />
እውነት ግን አዲስ አበባችን እንኳን<br />
ርሃብ ችግር ራሱ በሰረገላ ቁልፍ ሳይቆለፍበት<br />
አልቀረም እውነቴን ነዋ! ቆይ ግን ችግሩ<br />
ሁሉ ተሰብስቦ የተቆለፈበት እኛ ሰፈር ነው<br />
እንዴ? [እርስዎም ይሄንኑ ሳይሉ አይቀርም<br />
ብለን ጠረጠርን] አዲስ አበቤ ምንድን ነው<br />
የምትሉት? ዳውን ታውን ቡጊ ቡጊ ሲል ነው<br />
የሚጨሰዋ! ሰሞኑን አንድ ሚጢጢ ጥገኛ<br />
ባለ ሀብት ይዞኝ ገባ። መጠጡ አናታቸው<br />
ላይ ሲወጣ ከአንደበታቸው ደግሞ ግጥም<br />
15<br />
ሲወጣ አየሁ። የዜማውን ነገር ተውት አሃ!<br />
የዜማው ቅርፅ እንደ አካሄድ በመሰረተ ሀሳቡ<br />
ያስማማኛል። ሬንጁ ጠባብ ሆኖ የሪትሙ<br />
ትራንስፎርሜሽን ልማታዊ አይደለም። ግጥሙ<br />
ግን እንዲህ ይነበባል፡-<br />
እድገት እድገት ይላል ያላየ<br />
ህልመኛ<br />
ዳቦ ዳቦ ይላል የነገ ተስፈኛ<br />
ሰው በራብ መሞቱን ማን አውቆ<br />
ያለኛ!<br />
እውነቴን ነው መታወቂያ በማሳየት<br />
ልይዛቸው አሰብኩና ነገር ግን በዘፈኑ ልክ<br />
እርምጃ ለመውሰድ እንዲመቸኝ ተውኩት።<br />
ልክ ነኛ! ከዘፈኑ በመለስ [ይሄ መለስ ቀለስ<br />
የሚባልበት ቦታ መቼም…] ‹‹ችግር እስካላመጡ<br />
ማንም ‹‹ጋጠወጥ›› አልደግመውም አፉን<br />
መክፈት ይችላል፤ የአፉ አከፋፈት ሌላ ትርጉም<br />
እስካላሰጠ ድረስ›› ስል የታች ሰፈር ልጆች<br />
ተበድረው አይስቁብኝ መሰልዎ… ጥርሳችሁ<br />
ይርገፍ እንዳልል በቦክስ ጨርሰውታል።<br />
አደገኛ ፍንዳታ ሁላ! [በነገራችን ላይ አደገኛ<br />
ፍንዳታ፣ አደገኛ ቦዘኔ ከሚለው አደገኛ፣ አደጋ<br />
ጣይ ቃል የመጣ ነው።]<br />
እኔ የምለው ሰሞኑን ደግሞ ውሃና<br />
ፍሳሾች ከሰው እኩል ሊያደረጉን ነው። ውሃ<br />
ካለበት አካባቢ ወደ ሌለበት ሊያካፍሉን ነው<br />
ወንዳታ! ግንኮ በነካ እጅ ዳቦ ላጣነውም በርገር<br />
በሊታዎች እንዲያካፍሉን ህግ ይውጣልን!<br />
አንዱ ጠብቆ አዳሪ ‹‹መንግስት የከተማ ግብርና<br />
እያደራጀ እንዳለው ሁሉ ለምን እኛንም በከተማ<br />
እርፍና አያደራጀንም?›› ብሎ አረፈው። አዩ<br />
ግን ልዩነት… አንዱ ባደራጀን፣ ሌላው በክፉ<br />
አይኑ ባላየን፣ ሌላው… ሌላው…<br />
ምን ትዝ አለኝ… ‹‹የእጅ መታጠብ<br />
ቀን›› ሰሞኑን ሲከበር ኢቴቪ ላይ ያፈጠጠው<br />
አያቴ ‹‹የሚበላ ሳይኖር እጅ መታጠብ በራሱ<br />
በሽታ ነው›› ሲል የእህቴ ልጅ አቢቲ እየተኮላተፈ<br />
‹‹እንዴ በአምስት ዓመቱ ትራንስፎርሜሽን<br />
‹‹የእጅ መታጠብ ቀን›› የሚበሉት ላላቸው<br />
ተብሎ ይስተካከላል፣ ለሌላቸው ደግሞ ዳቦ<br />
የማይገኝበት ቀን ይከበራል›› ቢላቸው ደማቸው<br />
ባንዴ እንደ ባንዲራ ላይ አይሰቀል መሰልም።<br />
አሁን ግን ለሀዘን ዝቅ እንደሚደረገው ባንዲራ<br />
ትንሽ ዝቅ ብሏል ወላዲቴን! ግን እስቲ አስቡት<br />
‹‹የሚበሉት ባላቸው ዘንድ የሚከበረው የእጅ<br />
መታጠብ ቀን ለዚህ ጊዜ ያህል ተከብሮ ዋለ››<br />
ሲባል።<br />
ሰሞነኛ ወዳጆቼ ሆይ ቆይማ!<br />
ስልኬን መዝጋት አለብኝ እንዴ? አላዋራ<br />
ያለን ቴሌ ተማረሩ ብሎ ሲፈርድብን ነው<br />
መሰለኝ የማስታወቂያ ጋጋታ ያስልክብኛል።<br />
የጠ/ሚኒስትራችንን የበቀደም የፓርላማ ውሎ<br />
ለታሪክ ላኑረው ብዬ ከዩ ቲዩብ ዳውን ሎድ<br />
ላድርግ ብል መከራ ሆነብኝ። ይህን የነገርኩት<br />
ወዳጄ ‹‹ጀምረኸው ናዝሬት፣ ሀዋሳ ዘመድ<br />
ጠይቀህ ብትመለስ ይቀልሀል›› ብሎ ሙድ<br />
ይዞብኛል። ኧረ! ልማታዊ ዳውን ሎድ ስናደርግ<br />
እንኳን ቴሌያችን እንዴት ነው?<br />
ሰሞኑን አሜሪካ ካሊፎርኒያ ውስጥ<br />
ከጭነት መኪና ያመለጡ ንቦች ፖሊሶችን<br />
ሳይቀር እየነደፉ መሆናቸው አስደንጋጭ<br />
እንደሆነ ሬዲዮ ፋና ደጋግሞ እየዘገበ ነው፡<br />
፡ ይህንን የሰሙ የታች ሰፈር ልጆች ‹‹ወይ<br />
ሬዲዮ ፋና እናንተ የሚታያችሁ የፈረንጅ ንቦች<br />
ብቻ ናቸውን?›› ሲሉ አፊዘዋል፡፡ ‹‹የአገራችን<br />
ንቦች ንድፊያ ለምን አልተወራም›› ነው ነገሩ<br />
መሰለኝ። አንዳንድ አሉባልተኞችማ ‹‹ፋና<br />
ሆይ አንተ የንቦችን ማር እንጂ ንድፊያ የት<br />
አውቀኸው?›› እያሉ ያማሉ አሉ። ሌሎች<br />
ደግሞ ‹‹ንቦች ያላስቸገሩበት የት አለ?›› እያሉ<br />
ያንሾካሽካሉ። ለማንኛውም እኔ የለሁበትም<br />
ብሎ መሰናበት ሳይሻል አይቀርም፤ ስንቱን<br />
ገስፀን እንችላለን? በሁለት ሳምንት ውስጥ<br />
አይቀርላችሁም እንደተባለው ‹‹ፀባይ ካላችሁ<br />
ሁለተኛውንም እናሳልፍላችኋለን›› ካሉን<br />
የሳምንት ሰው ይበለን። ሰላም!!!<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ
16<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />
“ሽብርተኝነት ለኢትዮጵያ ባዕድ የሆነ ነገር ነው<br />
…በዚህ ሰበብ ሽብርተኝነትን እንዳናስተምር እሰጋለሁ”<br />
አቶ መለስ ሲናገሩ አቃቤ ሕጎች፣ ዳኞችና ፖሊሶች ይኼንን<br />
ተከትለው ይሄዳሉ ብለው እንኳን አያስቡም<br />
ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም<br />
በኤልያስ ገብሩ<br />
የፀረ-ሽብርተኝነት አዋጁን እንዴት ተመለከቱት?<br />
ለእኔ …የፀረ-ሽብርተኝነት ሕጉ አሜሪካ እንደዚህ አይነት ሕግ ወጥቷል። ይኼም ሕግ ሲወጣ<br />
በአሜሪካ ውጥ ብዙ ጩኸት ነበር። ‹‹የሰብዓዊ መብቶችን ይነካል›› በሚል ብዙ ችግር ነበር።<br />
እኛ ጋር የሚያሳዝነኝ የዛን መገልበጥ፣ እነሱ የሆኑትን መሆን እና እነሱ የሚፈልጉትን<br />
መሆን መሆናችን ነው። በእኛ በራሳችን፣ በታሪካችን፣ በባህላችንና በመንፈሳዊ ህይወታችን<br />
በኩል ተነስተን ብናየው ሽብር። እንደዚህ አይነት ነገር አናውቅም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ገበያ<br />
ላይ ወጥቶ፣ ትምህርትና ሆስፒታል ሄዶ ቦምብ የሚጥል ሕዝብ አይደለም። በታሪካችን<br />
እንደዚህ አይነት ነገር የለም፤ በፍፁም ባዕድ ነው። እና ይኼን የሌለብንን ነገር ‹‹አለባችሁ››<br />
ብሎ ፈረንጆች ስላሉ ብቻ በራሳቸው ችግር… እነሱ ደግሞ ይኼንን እንዴት እንዳገኙት<br />
እናውቀዋለን። ‹‹እኛም ጋር ይሄ ይመጣል›› ብሎ ወይም ‹‹አለ›› ብሎ እንደዚህ ጠ/ሚ/ሩ<br />
በእርግጠኝነት የሚናሩት ከየት እንደመጣ አላውቅም። የተቃዋሚዎችና የስልጣን ተቀናቃኞች<br />
ችግር ይኖራል። ነገር ግን ይኼ ‹‹ሽብርተኛ›› ተብሎ ከሽብርተኛ ጋር የሚያስፈርጅ ምንም<br />
ነገር የለበትም - ለእኔ፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ በዕድሜዬ ያየሁት ድሮ አንድ ጊዜ ሲኒማ<br />
አምፒር፣ ጊዎንና ዋቢ ሸበሌ ሆቴል እና ማዘጋጃ ቤት ቦንብ ፈንድቶ ነበር። እነዚህን እነማን<br />
እንዳደረጉትም እናውቃቸዋለን። ይኼ ‹‹የኢትዮጵያዊ ስሜት አለበት፤ የለበትም›› ብለን<br />
እንደው በሙሉ ልብ ለመናገር እንችላለን። እኔም እንደምገምተው ይመስለኛል። ክርክሩ<br />
‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ የፀረ-ሽብተኝነት ሕግ ‹ትክክል ነው አይደለም?› እኛ ኢትዮጵያውያን<br />
በእውነቱ የሽብር ታሪክና ባህል አለን ወይ?›› ነው። በዙሪያችን የሽብር ባህል ባላቸው ሀገራት<br />
ተከብበናል። ያ ግን እኛን ሽብርተኞች አያደርገንም - በጭራሽ።<br />
ከዚህ ጋር በተያያዘም፣ ጠ/ሚ/ር መለስ ሕጉን ቃል በቃል ከአሜሪካና ከእንግሊዝ መገልበጡን<br />
ተናግረዋል። አንድ ሕግ ወይም አዋጅ ሲወጣ የሀገሪቷን ነባራዊ ሁኔታ ማገናዘብ አይገባውም?<br />
ቃል በቃል ቀድቶ መገልበጥስ ትክክል ነው ይላሉ?<br />
እሱን እኮ ነው የምልህ! ከዚያ ነው የመጣው ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ የሌሎቹን ችግር…<br />
እንደዚሁ ነው የምናደርገው። በደርግ ጊዜም አንዴ ኮሎኔል መንግስቱ ባለበት ስብሰባ<br />
ላይ የተናገርኩት ነገር ነበር። የምናደርገው ችግርን ከመፅሀፈ ውስጥ እንፈልጋለን፡፡<br />
ለምሳሌ፣ ያን ጊዜ ‹‹ብሔረሰብ›› የተባለው ቃል ተፈጥሮ ነበር። ከመፅሀፍ ‹‹ብሔረሰብ››<br />
የሚለውን ቃል አውጥተን፣ የኢትዮጵያ ችግር አድርገን፣ እንደገናም ከመፅሀፉ ውስጥ<br />
መፍትሄ እንፈልግለታለን። የኢትዮጵያ ሕዝብ ችግር ምን እንደሆነ እሱን ራሱን<br />
እየጠየቁ በመረዳትና ለእዛ መፍትሄ ከማግኘት ፈንታ ከዚህ መፅሀፍ አንድ ችግር<br />
አውጥተን ከሌላ መፅሀፍ ደግሞ የዛን ችግር መፍትሄ እያመጣን የኢትዮጵያን<br />
ሁኔታ ለማሻሻል እንፈልጋለን። ይኼ ግን አይቻልም። ከራሳችን መነሳት<br />
አለብን። እኛው ማሰብ አለብን!። ጠ/ሚ/ሩ ከዛ ነው የገለበጥነው የሚሉት<br />
ነገር… ‹‹መገልበጥ›› ማለት ምን ማለት ነው? እኛ እናስብም? የራሳችንን<br />
ችግር መረዳት አንችልም? የራሳችንን ችግር ለይተን ባህላችንንና የሞራል<br />
ችሎታችንን መመርምርና ማወቅ አንችልም? ይኼ ነገር እነሱ ሀገራቸውም<br />
ውስጥ አለ። ለምሳሌ፣ በቅርቡ ኖርዌይ አንድ ሰው 70 ያህል ወጣቶችን<br />
በጥይት አርከፍክፎ በመጨፍጨፍ ገድሏቸው ነበር። እኛ ሀገር ይኼንን<br />
አይነት በሽታ አለ እንዴ?! የለም። በአሜሪካ አላባማ ግዛት እንደዚሁ<br />
ቦንብ አፈንድቶ ብዙ ሰዎችን ገድሏል። ጠበንጃ ይዘው ወጥተው መንገድ<br />
ላይ ያገኙትን ሰዎች በሙሉ ይጨፈጭፋሉ። በዚህ አይነት በሽታ<br />
የምንጠቃ ሕዝቦች አይደለንም። ግን ሌላ በሽታ የለብንም ማለት<br />
አይደለም። የራሳችን በሽታ አለን። ያንን ለማዳን መሞከር ነው<br />
እንጂ የሌለብን በሽታ ለምን ይሰጡናል።<br />
በሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 14፣ 16፣17፣18፣19፣20 እና 29<br />
የዜጎችን ሰብዓዊ መብትና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መደንገጋቸው<br />
ይታወቃል። በዚህም መሠረት ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የመናገር፣<br />
ኃሳብን በነፃ የመግለፅ፣ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ፣ መንግስትን<br />
የመቃወም፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች መ<strong>ስር</strong>ቶ የመንቀሳቀስ፣<br />
የዋስትና፣ የዳኞች ነፃነት መብት፣ ሰዎች ከታሰሩም በኋላ<br />
በወዳጅ ዘመድ የመጎብኘት… ወዘተ መብቶች አሉ፡፡ ሆኖም<br />
እነዚህን ሁሉ ሊሸረሽር የሚችል የፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ<br />
መውጣቱን የሚገልፁ ወገኖች አሉ። ምን ሀሳብ አለዎት?<br />
ከላይ እንደገለፅኩልህ ነው። ይኼ በአሜሪካንም ቢሆን በብዙ<br />
ሰዎች ዘንድ እንደዚሁ አይነት ከሕገ-መንግስቱ ጋር የሰብዓዊ<br />
መብቶችን ‹‹ይቃረናል፤ መብቶችንም አጥብቧል›› የሚል<br />
ክርክር አስነስቷል። በአሜሪካ ክርክሩ አሁንም እየተካሄደ<br />
ነው። በእኛም ሀገር የሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 29 ይመስለኛል<br />
መረጃን እንደፈለክ፣ በፈለከው አይነት ለመቀባበል መብት<br />
ይሰጥሃል። ግን እንደምናየው በኢንተርኔት በምናምን<br />
ያለን የታፈነ ሁኔታ በዚህ ሀገር አለ። ይኼ ስታትስቲክሱን<br />
የሚያሳይ ነው። በአፍሪካ በቅርብ ካሉን ጎረቤት ሀገራት ጋር<br />
ስንወዳደር ለምሳሌ በኬንያ፣ ሞባይል ስልክ ከ1000 ሰዎች<br />
መካከል 500 ያህሉ አላቸው፡፡ በዚህ ሶማሊያና ጅቡቲም<br />
ይበልጡናል። ለምን እንደዚህ ሆነ? ሶማሊያና ጅቡቲ እንዴት<br />
ይበልጡናል? የኢንተርኔት አጠቃቀምንም ከወሰድክ እንደዚሁ ነው፡፡<br />
ያለነው ታች ላይ ነው፡፡ ለምን እንደዚህ ይሆናል፡፡ ይኼ ሁሉ የመታፈን<br />
ሁኔታ እያለ ያንን ሕገ-መንግስቱን ጠቅሶ ‹‹ይኼ ተሻረ… ይኼ ተሻረ››<br />
ማለት እንደው መመፃደቅ ይመስለኛል። ሕገ-መንግስቱ በተለይ በንግግርና<br />
በመፅሀፍ መብት በኩል አንዱ ግልፅ የሆነው ነገር ጠ/ሚ/ሩ ‹‹ማስረጃ<br />
አለን፤ ሰብስበናል›› በማለት ተናግሯል። እንዴ! ያ ማስረጃ ሳይሰበሰብ<br />
ሰዎቹ ለምን ታሰሩ? ሰዎቹን አስሮ ነው ማስረጃ የሚሰበሰበው? ወይስ<br />
መጀመሪያ ማስረጃ ተሰብስቦ ነው ሰዎቹ የሚታሰሩት? ይሄ እኮ በቂ ነው፤<br />
በግልፅ ይታያል። …በእርግጥ ለሽብር የተዘጋጁና ለሽብር የሚዘጋጅ<br />
ሰዎች ካሉ ይኼንን ማን ይፈልጋል? እነዚህን ወንጀለኞች አይያዙ<br />
ብሎ ማን ይከራከራል? ለምን? ..ግን እንደው በጭራሽ [ተግባሩ]<br />
በመንፈሳቸውና በእንደዚህ አይነት ነገር በምንም የማይጠረጠሩ<br />
ሰዎችን ከያዙ በኋላ ‹‹እንመረምራለን፣ ማስረጃ እናሰባስባለን፣
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />
እንዲሁም እንፈልጋለን›› ማለት በሕግ መቀለድ<br />
ነው።<br />
በኢትዮጵያ የፀረ-ሽብርተኝነት ሕግ በትርጓሜ<br />
ደረጃ ሰፊና የተለጠጠ ከመሆኑ ባለፈ እንደወንጀል<br />
የሚቆጥራቸው ከ16-23 የሚሆኑ የሕግ መንግስቱ<br />
አንቀጾችን ጋር የሚጋጭና ‹‹ሽብርተኝነት›› ብሎ<br />
የሚወነጅላቸው ድርጊቶች ግልፅነት የሚጎድላቸው<br />
(vague) መሆናቸው ይገለፃል። እንዲሁም፣<br />
‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ ሕጉ የወጣው ለሀገሪቷ በከፍተኛ<br />
ደረጃ ግልፅና ድርስ ወይም (clear and present<br />
danger) የሆነ የሚያሰጋ የሽብርተኝነት ተግባር<br />
በሌለበት ሁኔታ ነው›› እየተባለ ነው። ይኼንን<br />
ከዜጎችን ሰብዓዊ መብቶችና ከፖለቲካ ምህዳር<br />
ማጥበብ አንጻር እንዴት ያዩታል?<br />
እኔ ይኼንን ከዚያ በላይ ነው የማየው። ‹‹ሰብዓዊ<br />
መብቶች›› የሚባሉ ነገሮችን ለብዙ ዓመታት በዚህ<br />
ሀገር አይቻለሁ። ይኼን ያህል የሚነሳ አይደለም።<br />
እኔን በጣም የሚያሰጋኝ ‹‹ሽብርተኛ›› እና ‹‹ሽብር››<br />
የሚባለው ነገር እንዲህ.. እንዲህ እየተባለ ሲነገርና<br />
እያሰፋነው ስንሄድ ሕዝቡን ነገሩን እንዳናስተምረው<br />
ነው። በፀረ-ሽብርተኝነት ሕግና ሰበብ ሽብርተኝነትን<br />
እያስተማርን ነው ወይ? ይኼ ነገር ያሳዝነኛል::<br />
ለወደፊትም ያሰጋኛል፡፡<br />
መንግስት እያንዳንዱን ጥቃቅን ድርጊት ሁሉ<br />
‹‹ሽብርተኝነት›› ብሎ ከተረጎመው በዚህ ሁኔታ<br />
በአሁን ወቅት በኢትዮጵያ ውስጥ ምን አይነት<br />
የፖለቲካ እንቅስቃሴ ማድረግ ይቻላል? ሲሉ<br />
በጭንቀት የሚጠይቁ ወገኖች አሉ፡፡ በዚህ ላይ ምን<br />
ይላሉ?<br />
የፖለቲካ ትግሉ የተለያየ ፈርጅ ነው። በእርግጥ አንድ<br />
ነገር ማለት እፈልጋለሁ፡፡ አንዳንዴ ጊዜ የሚታዩ<br />
ነገሮች ስላሉ የፖለቲካ ድርጅቶችና ተቀናቃኝ ቡድኖች<br />
ግልፅ ማድረግ አለባቸው፡፡ ‹‹ትግላችን በሠላም<br />
የሆነ እንደሆነ “መልካም”፣ በሠላም ካልሆነ ደግሞ<br />
“እንዴ!? ምናምን” የሚባል ነገር አለ። ሌላ መንገድ<br />
የለም። ለፖለቲካ ትግል ከሠላም ውጪ ሌላ መንገድ<br />
የለም። በዚህም ‹‹በሰላማዊ ትግል ሄደን እናሸንፋለን።<br />
እየገደሉን እንታገላለን። እየደበደቡን እንታገላለን።<br />
እያሰሩን እንታገላለን›› የሚሉ የፖለቲካ ቡድኖች<br />
መነሳትና በግልፅ ይኼንን መናገር አለባቸው።<br />
…‹‹ይኼ የአመራሩ አገዛዝ ልክ አይደለም፤<br />
እንቃወመዋለን። የምንቃመው በሰላማዊ መንገድ<br />
እንጂ ሌላ መንገድ የለንም። ሊገድለን ሲዘጋጅና<br />
ሲገድለንም እንሞትለታለን።›› መባል አለበት፡<br />
፡ ይኼንን በአረቡ ዓለም እያየን አይደለም እንዴ?<br />
ለመሞት መዘጋጀት የሚያቅተው ሰው መግደልን ማን<br />
ያስተምረዋል? መታሰርም ያው ነው። ግን ጥፋቱ<br />
ቆይቶ በማንም ላይ ይደርሳል ነው፡፡ ዛሬ [ቃለምልልሱ<br />
የተደረገው ከትናንት በስትያ ነበር] በአርጀንቲና 12<br />
የጦር ኃይሉ መኮንኖች የዛሬ 30 ዓመት በፈፀሙት<br />
ወንጀል ዕድሜ ልክ ተርዶባቸዋል፡፡ በግብፅ ሁለት<br />
ፖሊሶች ባለፈው ጊዜ አንድ ወጣት ገድለው<br />
ተፈርዶባቸው ነበር። ማምለጥ አይቻልም። በአሁኑ<br />
ጊዜ የዓለም ማሕበረሰብና ዓለም አቀፋዊ ህሊና፤<br />
እንዲሁም ሰዎች መሸሽና ማምለጥ የማይችሉበት<br />
ሁኔታ እየተፈጠረ ነው። ስለዚህ ልናድግና ልንሻሻል<br />
የምንችለው በወንጀል፣ በጠብና በዱላ አይደለም<br />
- በክርክር እንጂ። እንከራከር በቃላትም እንዋጋ<br />
የፖለቲካ ትግል ማለት ያ ነው። ያንን እንልመደው፡፡<br />
‹‹የፖለቲካ ፓርቲዎች ሳያወላውሉ የፖለቲካ ትግልን<br />
መስመር ለመያዝ መታገል አለባቸው›› እላለሁ።<br />
በአንፃሩ በአገዛዙ በኩል ጡንቻና ጉልበት አላቸው።<br />
‹‹በዚህ በጉልበታችን እየተጠቀምን እንገድላለን፣<br />
እናስራለን፣ እንደበድባለን፣ እናስፈራራለን›› ቢሉ<br />
ሽብር ይኼ ነው። ‹‹ያንን ሽብር ደግሞ እኛም<br />
ሳንፈራ እንቀበላለን›› ብሎ ቆርጦ በመንፈሳዊ ኃይል<br />
ለመዋጋት መዘጋጀት ያስፈልጋል።<br />
በአዋጁ መሠረት ፖሊስ ያለምንም የፍ/ቤት ትዕዛዝ<br />
ተጠርጣሪዎችን ማ<strong>ስር</strong> የሚችልበት ሁኔታ አለ፡<br />
፡ ካሰረም በኋላ መረጃ ለመሰብሰብ እስከ አራት<br />
ወር ጊዜ ድረስ መጠቀም እንደሚችል ሰፊ መብት<br />
ተሰጥቶታል። በሕገ-መንግስቱ መሠረት ደግሞ<br />
አንድ ሰው በ48 ሰዓታት ውስጥ ፍ/ቤት መቅረብ<br />
አለበት ይላል። ከዚህ አንጻር አንደኛው ህግ መሻሻል<br />
የለበትም ይላሉ፤ወይም ህገመንግስቱ? ወይም<br />
የጸረሽብር ህጉ?<br />
ሕገ-መንግስቱ እነሱ ሲፈልጉ የሚጠቅሱት ነገርና<br />
ሲፈልጉም አንተን ለማጥቂያ የሚጠቀሙበት<br />
መሳሪያ እንጂ ለዜጎች መከላከያና ከለላ እንዲሆን<br />
ማድረግ አልቻሉም። ከላይ እንደተናገርኩት፣ አሁን<br />
ባለንበት ጊዜ አንድን ሰው ይዘኸው መረጃና ማስረጃ<br />
መሰብሰብ ልክ አይደለም። ይኼ እንኳን ኢትዮጵያ<br />
ውስጥ ቀርቶ በዚህ የሽብረተኝነት ጉዳይ በአሜሪካም<br />
እየተደረገ ነው፡፡ ለእነሱ የአሜሪካ ማድረጉ ትልቅ<br />
መስክርነት ነው። …መነሻው ‹‹እኛ ከእነሱ ልንሻል<br />
አንችልም›› ነው። ለምን ልንችል አንችልም?<br />
[እየሳቁ] እነሱ ከተሳሳቱ እኛም መሳሳት አለብን? -<br />
ያውም በታሪክና በባህላችን፤ በማናውቀውና በፍፁም<br />
በሌለብን በሽታ። አሁን መሸሸጊያና መከራከሪያችን<br />
ሕገ-መንግስቱ ብቻ አይደለም፡- የታሪክ፣ የባህላችንና<br />
መንፈሳዊ መሠረታችን ጭምር እንጂ።<br />
የፀረ-ሽብርተኝነት ሕግን በርካታ አገሮች አውጥተዋል።<br />
ለምሳሌ፣ በአፍሪካ ኬኒያንና ናይጄሪያን ብንወስድ ሕጉ<br />
በሰላማዊ መንገድ በሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች<br />
ላይ ተፅዕኖ ሲፈጥር አይታይም። በኢትዮጵያ ግን<br />
ተፅዕኖ እየፈጠረ እንደሚገኝ በተደጋጋሚ ይገለፃል።<br />
የእኛን አዋጅ ከሌሎቹ ጋር እንዴት ያነፃፅሩታል?<br />
በአፍሪካ ብዙ ሀገሮች …ሩቅም ሳንሄድ እዚሁ<br />
ጎረቤታችን ያሉትን እንመልከት፡፡ ለምሳሌ፣ ኬንያ<br />
ከእኛ የበለጠ በሽብርተኞች ተጠቅተዋል፡፡ አሁንም<br />
እየተጠቁ ነው። ነገር ግን፣ በተቻላቸው መጠን<br />
ወጣና ጥልቅ ብለው ሳይገቡበትም ከአሜካኖችና<br />
ምዕራባውያን ጋር በአጠቃላይ ያላቸው ግንኙነት<br />
እንደኛ አይደለም። እኛ ጥልቅ ብለን ነው የገባንበት<br />
-ለምሳሌ በሶማሊያ ስንገባ፡፡ ከዛም በኋላ አሁን<br />
እንደምትለው በሕጉ ላይ የምናሳየው ጠንካራነትና<br />
ኃይለኛነት፡፡ …ሁለት የስዊድናውያን ጋዜጠኞችን<br />
ያለፍቃድ ወደ ሀገር ውስጥ ገብተዋል ተብሎ ይህ<br />
ሁሉ ነገር…እኔ እንደዛ ናቸው ብዬ ለመገመት<br />
ያስቸግረኛል። ምዕራባዊያኖቹ ቀደም ሲል<br />
ለህወሃትም ሲያዝኑ ነበር። ለሻዕቢያም ሲያዝኑና<br />
ሲረዱ ነበር። አሁን እንደዚህ አይነት ነገር እያደረጉ<br />
ይሆናል። ይተዋወቃሉ። ይኼ ይመስለኛል። ነገር<br />
ግን፣ እኛ ከአፍሪካኖች፣ ከአሜሪካኖች፣ ከእንግሊዞች<br />
ጋር የተለያየን ነን። በሽብር በፍፁም ከእነሱ ጋር<br />
አንወዳደርም - ታሪካችንን እንዲህ በትንሹ ያየው<br />
ሰው እንደዚህ አይነት ነገር የለብንም። ይኼ የእኛ<br />
በሽታ አይደለም። ‹‹የኢትዮጵያ ሕዝብ ነኩኝ፤<br />
መብቴን ነጠቁኝ›› ብሎ ከዛ ካጠቃው ባለጋራው<br />
ጋራ ይጣላል። ነገር ግን፣ ለምሳሌ በሌላ ወንጀልም<br />
ቢሆን የሴቶችን አይን ማውጣትና በአሲድ<br />
ማቃጠል የመሳሰሉ አዲስ በሽታ ሆነው እዚህ ሀገር<br />
መጥተዋል። እንደዚህ አይነት ነገር ነው ሕዝቡን<br />
የምናስተምረው፡፡<br />
‹‹የፀረ ሽብርተኝነት አዋጁ አያስፈልግም፤ ለመሰል<br />
ወንጀለኞች የኢትዮጵያ የወንጀልኛ መቅጫ ሕግ<br />
በቂ ነበር›› የሚሉ ፖለቲከኞች አሉ። በእርስዎ<br />
እምነት የአዋጁ መውጣት ተገቢ ነው?<br />
ለእኔ ሕግ ሲወጣ ችግሩ መጀመሪያ መኖር አለበት።<br />
ያ ሕግ ያስፈልገበት ምክንያት መኖር አለበት።<br />
እኛ ሀገር ‹‹ሽብር›› ከምን ተነስተን ነው? ከላይ<br />
የገለፅኳቸው አንዳንድ የዛሬ ስንት ዓመት አንድ..<br />
ሦስት.. አራት ቦታ የተጣሉ ቦምቦችን ይዘን ነው<br />
ኢትዮጵያ ውስጥ ሽብር አለ ብለን የምንነሳው? ወይስ<br />
ምን ችግር አለ ብለን? እዚህ ስንት ችግር ያለበት<br />
ነው። ለምሳሌ፣ ለችጋርና ችጋርን ለማስወገድ ለምን<br />
እውነተኛና ደንበኛ ሕግ አይወጣም? ሽብርተኝነት<br />
የለብንም በሽታችን አይደለም። በሽታችን ካልሆነ<br />
ለምን ሕግ እናወጣለታለን? አስፈላጊ አይደለም።<br />
‹‹በኢትዮጵያ ውስጥ ሽብር ሳይኖር እንዳለ አድርገን<br />
የምንናገር ከሆነ እውነተኛ ሽብርተኝነት ሊፈጠር<br />
ይችላል›› እያሉኝ ነው?<br />
አዎን፤ አዎን! ‹‹እንዲህ ነው.. እንዲህ ማድረግ…<br />
እንዲህ ማድረግ›› እያልክ በተናገርክ ቁጥር<br />
ማስተማር እኮ ነው።<br />
በዓለም ላይ መንግስታዊ ሽብርተኝነት መኖሩ<br />
ይነገራል። ህወሓትም በትጥቅ ትግሉ ወቅት<br />
የሽብር ድርጊት ይፈፅም እንደነበረ ተገልጾ በዓለም<br />
የሽብርተኝነት ዝርዝር ውስጥ መካተቱን መረጃዎች<br />
ያስረዳሉ። ይኼ አሁን መንግስት ከያዘው አቋም<br />
ጋር አይጣረስም?<br />
ህወሓት ጫካ በነበረበት ጊዜ ያለ ምንም ጥርጥር<br />
ሽብርተኝነትን ፈፅሟል። ጠ/ሚ/ሩ እኮ በአደባባይ<br />
በቴሌቭዥን ባንክ እንደዘረፉ እኮ ነግረውናል። ይኼ<br />
ሽብርተኝነት አይደለም? [እየሳቁ] ይኼ ሽብርተኝነት<br />
ከሚባሉ ነገሮች ውስጥ አንዱ ነው። ግን ከዛ በኋላ<br />
መንግስት ሆነዋል። መልካም! መንግስት ከሆኑ<br />
በኋላ ሌሎች ድርጅቶች ድሮ እነሱ በነበሩበት በትጥቅ<br />
ትግል ‹‹እንታገላለን፤ ስልጣን እንይዛለን›› የሚሉ<br />
ድርጅቶችን ለመቋቋም እነሱ በትጥቅ ትግል በኩል<br />
ስላለፉ ምን ምን እንደሚያስፈልግና ሽብርተኝነትም<br />
እንደሚያስፈልግ ያውቃሉ። ስለዚህ በእነዛ በትጥቅ<br />
ትግል በተዘጋጁት ድርጅቶች ላይ ‹‹እነዚህን ድሮ<br />
ስናደርግ እንደነበረው ያደርጋሉና እናግዳቸው፣<br />
እናፍናቸው፣ እኛም ያደረግነውን እንዳያደርጉ<br />
እናድርጋቸው›› የሚል ስሜት ሊያደርባቸው<br />
ይችላል። ነገር ግን፣ ‹‹በፖለቲካ ትግል ሕጋዊ በሆነ<br />
መንገድ እንታገላለን›› የሚሉትን የፖለቲካ ቡድኖች<br />
እዚህ ውስጥ ማስገባት ተገቢ አይደለም። እንግዲህ<br />
ልዩነቱ ይኼ ነው። በትጥቅ ትግል የሚሄዱትንና<br />
እንሄዳለን የሚሉትን በዚሁ በሽብርተኝነት መክሰስና<br />
መወንጀል ምናልባት ያስኬድ ይሆናል። ግን ‹‹እነዛም<br />
ተቀናቃኝ የፖለቲካ ቡድኖች ናቸው›› ብሎ በትጥቅ<br />
ትግል ያሉትን የፖለቲካ ቡድኖች በሰላማዊ ትግል<br />
ውስጥ ካሉት የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር አንድ<br />
አድርጎ ማየትና መወንጀል በፍፁም የሚያስኬድ<br />
አይደለም። የፖለቲካ ፓርቲዎቹም ‹‹በፖለቲካ<br />
ትግል ነው የምንሄደው፤ በሕጋዊ <strong>ስር</strong>ዓት ነው<br />
የምንታገለው›› ብለው የቆዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች<br />
ይኼንን ግልፅ አድርገው ማሳየት አለባቸው።<br />
ነገር ግን፣ በወላዋይነት አንድ እግራቸውን እዚህ<br />
አንደኛውን ደግሞ እዚያ አንፈራጥጠው የሚሄዱ<br />
ከሆነ ያም አያስኬድም፤ ልክ አይደሉም።<br />
መንግስት ‹‹ሽብርተኛ›› ብሎ የፈጃቸውን የፖለቲካ<br />
ቡድኖች ከኤርትራ መንግስት ጋር ተባብረው<br />
እንደሚሰሩ በተደጋጋሚ ውንጀላውን ያቀርባል፡<br />
፡ የኤርትራን መንግስት ግን ‹‹ሽብርተኛ›› ብሎ<br />
አልፈረጀም። የዚህ አንደምታው ምንድን ነው?<br />
ወንጅሏል እንጂ! ኤርትራን ‹‹የአሸባሪዎች ረዳት<br />
ነች›› ብሏል። በተጨማሪም፣ በአሜሪካና በተባበሩት<br />
መንግስታትም ይኸው ፍዳቸውን እያሳያቸው<br />
ነው። ለእኔም ሆነ ለማንም ሰው ግልፅ የሆነው<br />
አንድም ቦታ ኤርትራ በአሻባሪነት የሚፈርጅበት<br />
ሁኔታ አይታየኝም። የኢትዮጵያ አገዛዝ የኤርትራ<br />
መንግስት ተቀናቃኞችን ይረዳል፤ ያግዛል።<br />
እዚህ እየመጡ ስብሰባ ያደርጉ የለም እንዴ?!<br />
ኤርትራ ደግሞ የኢትዮጵያ መንግስት ተቀናቃኝ<br />
ቡድኖችን ይረዳል። ይኼ አንዱ አንዱን ለመጥለፍ<br />
የሚያደርገው ጥረት እንዴት አድርጎ ‹‹ሽብርተኛ››<br />
እንደሚሆን አላውቅም - ለእኔ።<br />
በኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔን መ<strong>ስር</strong>ተው<br />
በአመራርነት ለረዥም ዓመታት መስራትዎ<br />
ይታወቃል። የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ<br />
እንዴት ያዩታል?<br />
ኢሰመጉ አሁን የለም፤ ጠፍቷል፡፡ ከስሟል<br />
እንዲከስምም አድርገውታል። ስለዚህ የኢትዮጵያ<br />
እሳቸው ሲናገሩ አቃቤ ሕጎች፣ ዳኞችና<br />
ፖሊሶች ይኼንን ተከትለው ሌላ ነገር<br />
ያደርጋሉ ብለው እንኳን አያስቡም። …<br />
ለምሳሌ፣ ከዚህ በፊት እኛ በ1998 ዓ.ም<br />
ልንታሰር ስንል ጥፋታችንን ከነፍርዱ ነበር<br />
የሚናገሩት። ‹‹እንደዚህ አድርገዋል፣<br />
እንደዚህ አጥፍተዋል፣ ይኼንን ያህል<br />
ይፈረድባቸው። እስከ ዕድሜ ልክ<br />
ሊፈረድባቸው ይችላል›› ብለው ነበር።<br />
ዕድሜ ልክም ፈረዱብን።<br />
ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የሚባለው ተቋቁሟል። እሱ<br />
ደግሞ ስለ ሰብዓዊ መብቶች ሲናገር አንሰማም። ይኼ<br />
ነው ያለንበት ሁኔታ።<br />
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽንን ለማቋቋም<br />
ለምን የተፈለገ ይመስልዎታል?<br />
ደህና… የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በሌሎች ሀገሮች<br />
አለ። መጥፎው ነገር እሱ መቋቋሙ ሳይሆን የሲቪል<br />
ማሕበረሰቡን እና በግል በራሳቸው የሚያቋቁሙትን<br />
የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶችን ማጥፋቱ ነው።<br />
የራሳቸውን ማቋቋማቸው መጥፎ አይደለም።<br />
በቅርቡ የኮሚሽኑን ኮሚሽነር አምባሳደር ጥሩነህ<br />
ዜናን አነጋግረናቸው ነበር። ኮሚሽነሩ በሽብርተኝነትን<br />
ተጠርጥረው በመጀመሪያ የታሰሩ ጋዜጠኞችን<br />
መኖራቸውን ለሶስት ወራት ያህል አያውቁም ነበር።<br />
ይኼ ተገቢ ነው?<br />
[እየሳቁ] …ይኼንን እንዲከታተሉ አይደለም እኮ<br />
የተቋቋሙት፤ ለምን ይወቁት¡ [ከልባቸው እየሳቁ]<br />
የኢትዮጵያ ሕዝብስ በትክክል ሰብዓዊ መብቱን<br />
ያውቃል? አውቆስ መብቱን ለማስከበር ምን ያህል<br />
ዝግጁ ነው?<br />
መብቱን በደንብ ያውቃል። የኢትዮጵያ ሕዝብ<br />
በሕግ በኩል ምንም የሚጎድለው አይደለም። ድሮ<br />
የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያውቁትን የአንተ ትውልድ<br />
ያልደረሱበትን ነገር አለ። ሕዝቡ ስለ ሕግና ፍትሕ<br />
በደንብ ያውቃል። ማንም መንገደኛ ሰው ዳኛ ነው፡<br />
፡ ምስክር ነው፡፡ ፓሊስ ነው። አንድ ሰው ሲጠቃ<br />
ዝም ብሎ አይሄድም። ቆሞ በነገሩ ውስጥ ገብቶ፣<br />
የሚያዘውን ይዞ ዳኛ ጋር ወስዶ ይሄዳል። አስፈላጊም<br />
ሲሆን የተጣሉትን ሰዎች ኩታና ኩታቸውን ቋጥሮና<br />
አስፈፅሞ ምንም ሳታደርጉ ዳኛ ጋር እንድትሄዱ<br />
ብሎ ዳኛ ጋር ይልካቸዋል። ሰዎቹም በቀጥታ እዛ<br />
ዳኛ ጋር ይሄዳሉ። እንደዚህ አይነት ሕጋዊ <strong>ስር</strong>ዓት<br />
ያለው ሕዝቡ የትም የለም፡፡ ዛሬ ሰው ቢደባደብና<br />
ቢጋደል ማንም ዞር ብሎ የሚያይ የለም፡፡ ቆሞ ግን<br />
ይመለከታል። የኢትዮጵያ ሕዝብ እንደዚህ አይደለም፡፡<br />
ጥቃት ሲፈፀም ዝም ብሎ አያይም። በጦርነትም ጊዜ<br />
ወታደሩ እሱ ነው። ተነስ ሲባል ተነስቶ ይዘምታል<br />
- በራሱ መሳሪያ፡፡ ስለዚህ መብቱን እንዳይጠቀም<br />
ያደረገው <strong>ስር</strong>ዓቱ ነው?<br />
በአሁን ወቅት የተቃዋሚ ፓርቲዎች መዳከማቸው<br />
ይታያል። በእርስ በርሱ ሽኩቻ ህልውናቸው አደጋ<br />
ላይ የወደቁም አሉ። በዚህ ሂደት ኢህአዴግ ለረዥም<br />
ዓመት ኢትዮጵያን ከመምራት ምን ያግደዋል?<br />
አዎን። ችግር አለ፤ ግልፅ ነው። ቢፈራርሱም እኔ<br />
ለራሴ አላለቅስም። በራሳቸው ችግር ነው። ከአሁን<br />
ወዲያ እውነተኛና ደንበኛ የፖለቲካ ፓርቲዎች<br />
ቢቋቋሙ ከሕዝቡ የሚነሱ ለስልጣን የቋመጡ<br />
ጥቂት ሰዎችን ስብስበው ወይም የፓርላማ ደመወዝ<br />
እየበሉ ለመኖር የሚፈልጉ ሰዎች የሚያቋቁሙት<br />
ፓርቲ ሳይሆን እውነተኛ ትግል ውስጥ መግባት<br />
የሚፈልጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ከሕዝብ ጋር ሆነው<br />
የሕዝቡን ብሶት/ ሮሮ/ ችግሮች የሚያንፀባርቁ ሰዎች<br />
የሚኖሩበትና የሚመሩት ፓርቲ መምጣት አለበት።<br />
እርግጠኛ ነኝ ይመጣል›› ነገም ከነገ ወዲያም ቀስ<br />
ብሎ እንደዚህ አይነት ፓርቲ ይፈጠራል።<br />
ባሳለፍነው ሳምንት ጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ በፓርላማ<br />
ከሽብርተኝነት ጋር በተገናኘ ቁጣ አዘልና ማስጠንቀቂያ<br />
የተቀላቀለበት ንግግሮችን ለተቃዋሚዎችና<br />
ለጋዜጠኞች መናገራቸው ይታወሳል። ይኼንን<br />
እንዴት ተመለከቱት?<br />
አቶ መለስ ማስፈራራታቸው አዲስ ነገር ነው እንዴ?<br />
ሁልጊዜ ይሳደባሉ፣ ያስፈራራሉ፣ እንደልባቸው<br />
ይናገራሉ፡፡ ሌላው ቀርቶ እሳቸው ሲናገሩ አቃቤ<br />
ሕጎች፣ ዳኞችና ፖሊሶች ይኼንን ተከትለው ሌላ ነገር<br />
ያደርጋሉ ብለው እንኳን አያስቡም። …ለምሳሌ፣<br />
ከዚህ በፊት እኛ በ1998 ዓ.ም ልንታሰር ስንል<br />
ጥፋታችንን ከነፍርዱ ነበር የሚናገሩት። ‹‹እንደዚህ<br />
አድርገዋል፣ እንደዚህ አጥፍተዋል፣ ይኼንን ያህል<br />
ይፈረድባቸው። እስከ ዕድሜ ልክ ሊፈረድባቸው<br />
ይችላል›› ብለው ነበር። ዕድሜ ልክም ፈረዱብን።<br />
ይኼ የሚያደርጉት ነው። ‹‹ማስረጃ አለን፤<br />
እየሰበሰብን ነው›› ማለት ምን ማለት ነው? ሕጋዊ<br />
ለሆነ ሰውና ሕጋዊ <strong>ስር</strong>ዓትን ለሚመራ ሰው ይኼ<br />
በፍፁም የሚያስኬድ አባባል አይደለም። ምርመራው<br />
ተደርጎ፣ መረጃዎች ተሰብስበው፣ ማስረጃ ሁሉ<br />
ተዘጋጅቶ ነው ክስ የሚመሰረተው። ንፁውን ሰውዬ<br />
ይዞና አስሮ ብዙ መረጃ ለመሰብሰብ መሯሯጥ<br />
ተገቢ አይደለም። ታስረው ያሉ የሚሰቃዩ ሰዎች፣<br />
ጋዜጠኛችና አንዳንዶቹም የእኛ ጓደኞች በደንብ<br />
የማውቃቸው ሰዎች አሉ። ደበበ እሸቱ በምንም በኩል<br />
በደንብ አውቀዋለሁ። ቃሊቲም አብረን ነበርን። ከዛም<br />
በኋላ እንነጋገራለን፤ እንወያያለን። እንደዚህ አይነት<br />
ነገር በጭራሽ መንፈስ የለም፡፡ ይች ርዕዮትም<br />
የምትባል ልጅ ጥሩ ፀሀፊና ጥሩ ችሎታ ያላት ነች።<br />
ግን እንዴት አድርገው እዚህ ውስጥ እንዳስገቧትና<br />
እንደገባች እኔ አላውቀውም። እስክንድር ነጋም ፊት<br />
ለፊት የሚናገር ሰው ነው። ኃይለኛ ፀሀፊ ነው።<br />
እንደዚሁ እ<strong>ስር</strong> ቤት ሲገባና ሲወጣ 20 ዓመቱ ነው።<br />
ስለዚህ መቻቻል አለብን። ሽብርን በምንም አይነት<br />
መንገድ ልንጠራውና ልንለምደው የሚገባን ነገር<br />
አይደለም። ይኼ ሁሉ ጎረምሳ እዚህ ሀገር ጦሙን<br />
እያደረ በሰላም ይሄዳል። አጠገባችንና ጎረቤታችን<br />
ያሉት ሀገራት እኮ እንደዚህ አይደሉም። ይኼንን<br />
መንፈሳዊ መሠረታችንን ይዘነው ብንቆይ? በተለይ<br />
ወጣቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይኼንን ነገር እንዳይማር<br />
ብናደርግ የተሻለ ይመስለኛል።<br />
አቶ መለስ በተደጋጋሚ ‹‹ይኼ የመጨረሻ የስልጣን<br />
ዘመኔ ነው›› ብለዋል። እንዳሉት ቃላቸውን ጠብቀው<br />
ከስልጣን ቢወርዱ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሁኔታ<br />
ሊለወጥ ይችላል ብለው በሚገምቱ ወገኖች አሉ፡<br />
፡ ይስማማሉ?<br />
በመጀመሪያ እስኪ እሳቸው በምርጫ ተሸንፈውም<br />
ይሁን ከውስጣቸው ለአንዱ የተሻለ ሰው አግኝተው<br />
ስልጣን አስረክበው መደማመጥ የሚቻልበት ሁኔታ<br />
ከተፈጠረ ጥሩ ነው። ላለፉት 20 ዓመታት እኮ<br />
መደማመጥ የለም። አንድ አቅጣጫ ብቻ ነው።<br />
አቶ መለስ ይናገራሉ፤ ከላይ እንካችሁ ይላሉ።<br />
ከእኛ በኩል፣ ከሌላው ከሕዝቡ፣ ከጋዜጣውና ከሌላ<br />
የሚመጣውን ነገር ሰምቶ፣ አዳምጦና አብላልቶ<br />
ለዚያ ተገቢ መልስ የሚሰጥበት ሁኔታ የለም። ‹‹እኔ<br />
ልንገራችሁ እናንተ ስሙኝ። እኔ ትዕዛዝ ልስጣችሁ<br />
እናንተ ፈፅሙ ነው›› ያለው።<br />
በአሁኑ ወቅት ኑሮ በከፍተኛ ሁኔታ እየተወደደ<br />
መጥቷል። የምግብ ዋጋ ግሽበቱም 51.3 በመቶ<br />
ደርሷል። መንግስት ደግሞ ይኼንን የዕድገት አንዱ<br />
ምልክት ነው ይለዋል። በከተማ ውስጥ ሰው በረሃብ<br />
እየሞተ ባለበት ሁኔታ ግሽበት እንዴት የዕድገት<br />
ምልክት ሊሆን ይችላል? ብለው የሚጠይቁ ወገኖች<br />
ተበራክተዋል፡፡ ምን አስተያየት አለዎት?<br />
ስለዚህ በመንግስትም በሌላም ያሉ ኢኮኖሚስቶች<br />
ይናገሩ። …ድሮ ገና በአፄ ኃይለስላሴ ጊዜ በአዋሽ<br />
ተፋሰስ ላይ ባለስልጣን በሚቋቋምበት ጊዜ እድገትን<br />
አስመልክቶ አንድ ፅሁፍ ፅፌ ነበር። በአዋሽ ተፋሰስ<br />
ላይ የወንጂ ስኳር ፋብሪካን ለማቋቋም በእዛ ያሉትን<br />
ከብት አርቢዎችና ዘላኖች ወደ ደረቁ ቦታ ገፍተዋቸው<br />
ለሙን መሬት በሙሉ ለወንጂ ስኳር ፋብሪካ ሸንኮራ<br />
አገዳ ማምረቻ ሰጧቸው። ያን ጊዜ የፃፍኩት ነገር<br />
‹‹ምንድን ነው ዕድገት?›› የሚል ነበር። ለእነዚህ<br />
ለተገፉት ሰዎች ለአፋሮችና ለጂሌ ኦሮሞዎች ዕድገት<br />
ምን ማለት ነው? ሌሎች ሰዎች መጥተው ቤት<br />
ሰርተው፣ ሸንኮራ አገዳ ተክለውና ፋብሪካ አቋቁመው<br />
ሀብታሞች ሲሆኑ ማየትና መመልከት ነው ለእነዚህ<br />
ሰዎች እድገት? ያ ዕድገት እነሱን ይጨምራል ወይ?<br />
እየገፏቸው እንዴት ይጨምራቸዋል? ወደ ውጪና<br />
ወዳልተሻለ ቦታና መሬት እየመሯቸው እንዴት<br />
ያሻሽላቸዋል? ብዬ የዛሬ 45 ወይም 50 ዓመት ፅፌ<br />
ነበር፡፡ አሁንም የማየው እንደዛ ነው። ትልልቅ ፎቅ<br />
ቤቶች ተሰርተዋል። መንገዶች ተሰርተዋል። ግን<br />
ራሳችንን እንጠይቅ አንድ ትልቅ ፎቅ ቤት ሲሰራ<br />
ስንት ቤተሰብ መንገድ ላይ ተጥሏል? አንድ ኪሎ<br />
ሜትር መንገድ ሲሰራ ስንት ቤተሰብ መንገድ ላይ<br />
ተጥሏል? ለእነዛ ሰዎች ልማትና ዕድገት ይኼ<br />
ነው? ለአንዳንዶቹ ግን ነው። እዛ ላይ ደግሞ ብዙ<br />
የማናስበው ነገር አለ። ለጊዜው የምናየው ፎቅ ቤት<br />
መሰራቱን ብቻ ነው። ሰሞኑን በቱርክ በመሬት<br />
መንቀጥቀጥ በጣም በርካታ ቤቶች ድራሻቸው ነው<br />
የጠፋው። በድንገት ዝም ብለው የተሰሩ ትልልቅ<br />
ፎቆች ናቸው። አዋቂዎች ግና የዛሬ 50 ዓመት እዚህ<br />
ሀገር ከአምስት ፎቅ በላይ እንዳይሰራ ተናግረዋል።<br />
ያም መሠረቱ በደንብ ከተሰራ ነው፡፡ ዛሬ ዝም<br />
ብለን ለጠፍ ለጠፍ አድርገን ቤቶች ዝም ተብለው<br />
ይሰራሉ። እነዚህ የሀገር ሀብት ናቸው። እንዲቆዩልን<br />
እንፈልጋለን። ጉዳትም እንዲያመጡም አንፈልግም።<br />
ዕድገት ለሚባለው ነገር እነዚህ ሁሉ ነገሮች አብረው<br />
መታየት አለባቸው፡፡<br />
ኢትዮጵያ በድህነት ውስጥ ትገኛለች። ከእርስዎ<br />
የረዥም ጊዜ የሕይወት ልምድ አኳያ ኢትዮጵያ<br />
በአሁኑ ወቅት ምን ያስፈልጋታል ብለው ያስባሉ።<br />
ለመንግስት፣ ለተቃዋሚዎችና ለሕዝቡ ምን<br />
ይመክራሉ?<br />
በእኛ ሀገር አንድ የጎደለው ትልቁ ነገር መነጋገር<br />
አለመቻላችን ነው። ያለነው ተኳርፈን ነው።<br />
የመንግስት ስልጣን ይዘናል የሚሉት፣ በተለይም<br />
ስለሕዝቡ እናውቃለን፣ የህዝቡን ብሶትና ሮሮ<br />
እንናገር የሚሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ጋዜጠኞችም<br />
ሆኑ በግል ያሉ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች<br />
መንግስት ከሚባሉት ባለስልጣናት ጋር በቅን መንፈስ<br />
ለመነጋገርና ለመወያየት አልቻሉም። ‹‹ልንገርህ/ሽ››<br />
ሳይሆን ‹‹እንነጋገር ወይም እንደማመጥ›› የሚባለው<br />
ነገር ኢትዮጵያ ውስጥ ጎድሏል፡፡<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
17
18<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
ሴ ት<br />
ሴበመቅደስ<br />
ፍስሐ<br />
Mekdi745@gmail.com<br />
እኩልም ነሽ፤<br />
እኩልም አይደለሽም<br />
እኩልነት ማለት አለመበላለጥ ነው። በእኩልነት<br />
ስንቶችን እናምናለን? “ሴቶች ከወንዶች እኩል ነን” እንላለን።<br />
አንዳንዴ ይሄንኑ አባባላችንን ራሳችን አባባል ሆኖ እንዲቀር<br />
እናደርገዋለን። አንዳንዶች፣ “ሴቶች ከወንድ ‘እኩል ነን’ ብለው<br />
ካሰቡ እኩል መሆናቸውን ማንሳት በራሱ ምን አስፈለገ?”<br />
(ለምን ያስታውሱናል አይነት ነገር) ሲሉ አንዳንዶች ደግሞ፣<br />
“አይሆንም፤ ሴቶች የራሳቸው ጥንካሬ እንዳላቸው ሁሉ<br />
ከወንዶች የሚያንሱበት መንገድም አለ” ይላሉ። እናንተ በምን<br />
ትስማሙ ይሆን? እርግጥ አንዳንዴ እኩል የማያደርጉን ሰው<br />
ሰራሽና ተፈጥሮአዊ ነገሮች አሉ። ሰው ሰራሹ ራሳችን ሴቶቹ<br />
የፈጠርናቸው ሲሆኑ፣ የተፈጥሮው ደግሞ በተፈጥሮ ደረጃ<br />
በሴቶች ሊሰሩ የማይሞከሩ አንዳንድ ነገሮችን ማለቴ ነው።<br />
አሁን ስለእኩልነት ልሰብክ አይደለም - ብዙ ተብሏልና።<br />
ከዚህ ወጣ እንበልና፤ ወንዶች ከእኛ በምን ይበልጣሉ? እኛስ<br />
በምን እንበልጣቸዋለን? የሚለውን ነገር አስበን እናውቅ ይሆን?<br />
እንዲህ ነው፡- እነሱ በቀላል መንገድ የተቋቋሙት፣<br />
እንደ ተራራ የገዘፈ ነገር ሊኖር ይችላል። እናም፣ ያን የገዘፈ<br />
ሁነት በቀላሉ ተቋቁመውታልና ይበልጡናል። እኛ ሴቶች<br />
ያለፍነው፣ ነገር ግን ወንዶች ከባድ አድርገው የሚወስዱት ነገር፣<br />
ለእኛ “ኢምንት” ሆኖ እናገኘዋለን፣ ወይም ለእነሱ ተራራ ሊሆን<br />
ይችላል። ስለዚህ እዚህ ጋር ልዩነት ሲመጣ እኩል የመሆን ነገሩ<br />
ያከትማል ማለት ነው።<br />
ወንዱ በሴት የሚከወነውን ስራ ሙሉ ቀን ቁጭ<br />
ብለህ ስራ ከምትሉት ሞቱን ይመርጣል። አልወጣውም ብሎ<br />
ስለሚያስብ ብቻም ላይሆን ይችላል። እርግጥ ነው አይወጣውም።<br />
ቢወጣው እንኳ እሷ በተወጣችበት መንገድ ላይሆን ይችላል።<br />
አንድን ሴት ከወንድ እኩል ሙሉውን ጊዜ የጉልበት<br />
ሥራ ስሪ ብንላት የአቅሟ ሁኔታ የሚያስተማምን አይሆንም።<br />
እሷም አትቀበለውም። “ኧረ እኔ ሴት ነኝ! እንዴት እችለዋለሁ?”<br />
የሚል ጥያቄ ልታቀርብ ትችላለች። አይፈረድባትም።<br />
አንዳንዴ ወንዶች ሀዘንን በመቋቋም (ባለማክረር)<br />
ይበልጡናል ብዬ አስባለሁ። “ይሄማ አይሆንም። እነሱ እንደውም<br />
አይቋቋሙም” ያሉኝ ሴቶችም አሉ።<br />
እንደ’ኔ ግን ወንዶች ከእኛ በተሻለ ሁኔታ<br />
ይቋቋሙታል ባይ ነኝ። አንድ ሰው ከእኛ በሞት ሲለይ ማሰብ<br />
ባለብን መጠን ልናስበው ግድ ቢልም፣ ወንዶቹ ለለቅሶው ተብሎ<br />
ከሚባክኑ ወጪዎች አንስቶ “ፍራሽ ዘርግቶ” በመቀመጥ ነገሩን<br />
እየቆሰቆሱ ከማባባስ የፀዱ ናቸው።<br />
በዚህ የማይስማሙ አንዳንዶች፣ “እንበልና ሴቷ<br />
በባሏ ሞት ምክንያት ብቻዋን ብትቀር ሌላ ባል የማግባቷ ጉዳይ<br />
ምናልባትም እዚያ ላይ ሊያበቃ ይችላል፤ ካላበቃ እንኳን ሌላ<br />
የመተካቱ ነገር ይረዝማል። እንዲህ እንዲሆን ያደረገው ደግሞ<br />
ሃዘንን መቋቋም መቻሏ ነው” ይላሉ።<br />
ወንዱስ? ብቸኝነቱንና ሐዘኑን መቋቋም ወዲያው<br />
ይከብደዋል። እሱ፣ ከእሷ በተቃራኒ፣ እሷን የሚያስታውሱትን<br />
ነገሮች ከአጠገቡ አያርቅም። እሱ ግን እሷን ለመርሳት በሌላ<br />
ሊተካት ይፈልጋል - ይተካታልም። ያ ማለት ሃዘኑ ጎድቶታል፣<br />
ጎድቶትም እንዲቀጥል አይፈልግም ይላሉ።<br />
ሌላው የማነሳው ደግሞ ቸኩሎ ውሳኔ በመስጠት<br />
በኩል ሴቶች ረጋ ይላሉ ብል ማድላት አይሆንብኝም። አንድን<br />
ነገር ከመወሰን ይልቅ ከውሳኔ በኋላ ሊኖር የሚችለውን ውጤት<br />
(consequence) በማሰብ በኩል አንደኛ ይመስሉኛል - ሴቶች።<br />
እንዲህ ያለ አስተሳሰብ ያላቸው ወንዶች እንዳሉ አውቃለሁ፤<br />
ብዛታቸው የሴቶችን ያህል አይሆኑም ብዬ በማሰብ እንጂ።<br />
ለዚያም ነው ከውሳኔያቸው በኋላ ሴቶቹን ለመመለስ ለወንዶች<br />
ከባድ የሚሆነው።<br />
ምናልባትም የእሷ ውሳኔ ከዚያ በኋላ ግራ ያጋባህ<br />
ይሆናል። የማታውቃት መስሎ ሊሰማህም ይችላል። ነገር ግን<br />
በእርግጠኝነት የምነገረህ ወደዚህ ውሳኔ ከመምጣቷ በፊት<br />
ደጋግማ አስጠንቅቃሃለች። በዚህ ላይ አንባቢ የራሱን ግምት<br />
ይውሰድ።<br />
ሦስተኛውና የመጨረሻው ነጥቤስ?<br />
አንድን ነገር እየቻልን በራስ መተማመናችን ባዶ<br />
በመሆኑ ምክንያት ብቻ አንድን ኃላፊነት አሳልፈን ለወንድ<br />
የምንሰጥም አለን። ይሄ የእኛ የሴቶች ድክመታችን ነው። ይሄ<br />
የእኛ ልዩነታችን ነው።<br />
የሚገርመው አንድ ሴት ያላትን ጥንካሬ<br />
ተጠቅማ ለውጤት ብትበቃ “ወንድ ነሽ/ናት” የሚል አግባብነት<br />
የሌለው ሙገሳን እንቸራታለን። ራሷን እንደ ወንድ እንድታይ<br />
እናደርጋታለን።<br />
እኔ እንድጽፍ የተሰጠኝ ቦታ አልቆ ተገደብኩ።<br />
ነገር ግን አንቺስ? “እኔን ከወንድ እኩል የማያደርገኝ ተፈጥሮና<br />
ራሴ የፈጠርኩት (ሰው ሰራሽ) ምክንያቶች አሉ” ብለሽ አታምኚ<br />
ይሆን? አዎን። የምትበልጭበትም የምታንሽበትም፣ እንዲሁም<br />
እኩል የሚያደርጉሽም ነጥቦች አሉ ብዬ አስባለሁ። እኩልም ነሽ<br />
እኩልም አይደለሽም።<br />
ከምንም ነገር በላይ ደግሞ በራስ የመተማመን<br />
መንፈሳችን ዝቅተኛ መሆኑ አንዱ ከወንድ እኩል እንዳንሆን<br />
የሚያደርገን መሆኑን ልናጤነው ግድ ይለናል። በቅድሚያ<br />
ለራሳችን ያለን ግንዛቤ ከፍ ሊል ይገባል ባይ ነኝ።<br />
ምክር ቤቱ<br />
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />
‹‹የቤት እንስሳት ያስባሉ. . .<br />
አደርገዋለሁ›› ይላሉ። እኔ ግን እነሱ ትንሽ<br />
አበዙት እላለሁ።<br />
ከሰው ልጅ የማይጠበቅ ስህተት/ድርጊት<br />
[በተለምዶ እንስሳዊ የምንለው አይነት]<br />
ፈፅመው የሚገኙን ‹‹ከእንስሳት ታዲያ<br />
በምን ተለየህ? በማሰብህ አልነበረም<br />
እንዴ?›› እንላለን። እንስሳት እንደማያስቡ<br />
ርግጠኛ መሆን ይቻላል? [በርግጥ አንቺ<br />
የሰው ልጅ እንጂ የእንስሳ አዕምሮ ባለሙያ<br />
አይደለሽም]<br />
የሚያስቡ ይመስለኛል። ውሻን<br />
ልትወስድ ትችላለህ። [የውሻ አድናቂ እና<br />
አፍቃሪ ነኝ፤ ቀረቤታውም አለኝ] የሰው<br />
ልጆች ከሚያደርጉት በላይ ያደርጋል።<br />
በርግጥ አመክንዮ አያውቅም። አጥንቱን<br />
ቁጭ አድርጎ ስታልፍ ሊነክስህ ይችላል።<br />
‹‹አጥንቴን ሊወስድብኝ ነው›› ብሎ ስላሰበ<br />
ነው። ምናልባት ‹‹እኔ የነካሁትን አጥንት<br />
የሰው ልጅ አይበላም›› ብሎ ቢያስብ ኖሮ<br />
አይነክስህም ነበር። በተለይ የቤት እንስሳት<br />
በደንብ ያስባሉ ብዬ አምናለሁ። እንደ ሰው<br />
የተወሳሰቡ ነገሮችን ላያስቡ ይችላሉ። [በጣም<br />
እየሳቀች] በርግጥ እስካሁን ያለሁት ሰው ላይ<br />
ነው። ወደፊት ስለ እንስሳት አጠና ይሆናል።<br />
[በቅርቡ አሜሪካ ውስጥ 911 ደውሎ ህመም<br />
ውስጥ የነበረ ጌታውን ውሻው ታድጓል]<br />
ስለ አዕምሮ…<br />
የሰው ልጅ አዕምሮን ለሁለት<br />
ከፍለን ማየት እንችላለን። የግራው<br />
ምክንያታዊ፣ ቀኙ ደግሞ ስሜታዊ ክፍል<br />
ነው። የህፃናት እስከ ሁለት ዓመታቸው ድረስ<br />
75 በመቶ የሚሰራው ቀኙ (ስሜታዊው)<br />
ክፍል ነው። ለዚያ ነው ሲርባቸው፣ ሲናደዱ<br />
ወይም በሌላ ምክንያት የሚያለቅሱት።<br />
የተነሳሽነት፣ የማቀድና ማስፈፀም ስንፈት<br />
ከስነ-ልቦና ችግር ጋር ይያያዛል?<br />
በጣም እንጂ። እኔ ጋር የሚመጡ<br />
የፍቅር፣ የባልና ሚስት ችግሮች ብቻ<br />
አይደሉም። ብር ኖሯቸው ምን መስራት<br />
እንዳለባቸው የማያውቁ እና የሚፈሩም<br />
ይመጣሉ። እንደዚህ አይነት ችግሮች<br />
ሲመጡ የኋላ ታሪካቸውን እናጠናለን።<br />
እንደማምነው 90 በመቶ ያህል የስነ-ልቦና<br />
ችግር የሚመጣው ከልጅነት ችግራችን<br />
ነው። ጉንፋን የያዘው ሰው ያስላል። ሳሉ<br />
ግን ጉንፋን ብቻ ነው ማለት አይቻልም።<br />
ውስጡ መታከም አለበት።<br />
ብዙ ነገሮች ማድረግ እየቻሉ ‹‹እኔ<br />
ብቁ አይደለሁም›› ብለው የሚያስቡ ሰዎች<br />
አሉ። አንዳንድ ሰዎች ማጌጥ የሚፈልጉት<br />
‹‹ይመጥነኛል›› በሚሉት ነገር ነው። አንተ<br />
እጅ ላይ ወርቅ አለ። ያደረግከው ይመጥነኛል<br />
ብለህ ነው። ለአንዳንድ ሰዎች ግን ወርቅ<br />
ብትሰጣቸው ‹‹ሰዎች ወርቁን ሲያዩ እኔ<br />
አንሼ እታያቸዋለሁ›› (ከወርቁ አንሳለሁ)<br />
ብለው ስለሚያስቡ አያደርጉትም። እንዲህ<br />
አይነት ሰዎች ብዙ ጊዜ ‹‹አትችልም››<br />
ተብለው ያደጉ ናቸው።<br />
አዲስ መንገድ እና የእርቅ ማዕድ የተሰኙ<br />
የስነ ልብዎና የሬዳዮ ፕሮግራም አላችሁ።<br />
ማህበረሰቡ ጋር ምን ያህል እንደደረሳችሁ<br />
ዳታው ባይኖረኝም በግላዊ ምልከታዬ<br />
ፍቅረኞች፣ ባለ ትዳሮች፣ ቤተሰብ፣ የፍቅር<br />
ግንኙነታቸው ማደስ የሚፈልጉ እና በኑሮ<br />
ሂደት የትዳር ወይም ቤተሰባዊ ግንኙነታው<br />
የደፈረሰ ለእርቅ እንዲሰናዱ ሊያዳምጧቸው<br />
የሚገቡ ሁለት ፕሮግራሞች ናቸው። ምን<br />
አይነት ግብረ መልስ ታገኛላችሁ?<br />
እኛ በግላችን ስለ ፕሮግራማችን<br />
የሰራነው ጥናት የለንም። ፋና የ<strong>ስር</strong>ጭት<br />
ማዕከል ከሚሰራው ጥናት ተነስቶ ጥሩ እና<br />
ተደማጭ ፕሮግራም እንደሆነ ይነግረናል።<br />
አነቃቂ ስልጠና (Motivational Training)<br />
ለመስጠት በተለያዩ ቦታዎች ስገኝ<br />
የሚቀበሉኝ በደስታ ነው። ‹‹ወይኔ ታድዬ<br />
ቲጂን አወቅኳት›› እስከ ማለት የሚደርሱ<br />
ያጋጥሙኛል። በሚወዱህ መሀከል መስራት<br />
አስደሳች ነው። ይሄ ለእኛ ትልቁ ሽልማት<br />
ነው።<br />
እግዚአብሔር ይመስገን እጅግ<br />
በጣም ቆንጆ ምላሽ አለን። የስልጠና እና<br />
የማማከር ስራውን ስንጀምር በ400 ብር<br />
ቢሮ ተከራይተን ሲሆን ጠረጴዛ እንኳን<br />
አልነበረንም። እኔም ሆንኩ የድርጅታችን<br />
ሌላው ባለድርሻ (እንዳልካቸው አሰፋ)<br />
ስራ ከቀደመ፣ ገንዘብ እንደሚከተለን<br />
እናውቀዋለን። [ድርጅታቸው በርካታ<br />
ጥንዶችን አስታርቋል።]<br />
ፕሮግራማችሁን ስከታተል ብዙዎች<br />
እንደሚወዱሽ እና እንደሚያደንቁሽ<br />
[ሁለቱም ፆታዎች] ይናገራሉ። በድምፅሽ<br />
እና በአወራር ዘዬሽ የሚሳቡ ያሉ<br />
ይመስለኛል። የፍቅር ጥያቄዎችም<br />
እንደሚቀርብልሽ ሰምቻለሁ።<br />
እንዲህ ወጣ ያለ ጥያቄ ደስ<br />
ይላል። በህይወት ውስጥ የሚያጋጥም ነገር<br />
ነው። ደንበኞቼን በር ከፍቼ ‹‹እንኳን ደህና<br />
መጣችሁ›› ብዬ እቀበላቸዋለሁ። የምክር<br />
አገልግሎት እየሰጠኋቸው ቢያለቅሱ፣<br />
ቢያዝኑ በእጄ እንዲህ (በአመልካች ጣቷ<br />
እየጠቆመች) አልነካቸውም። በጣም ካለቀሱ<br />
ናብኪን አውጥቼ ሰጣቸዋለሁ። ከደንበኞች<br />
ጋር (ወንድም ሆነ ሴት) መገባበዝ<br />
አይፈቀድም። ስጦታ መቀበል ስለማይቻል<br />
መጥቶልኝ መልሼ አውቃለሁ። ይህን<br />
የማደርገው ለእኔም ለደንበኞቼም ደህንነት<br />
ሲባል ነው።<br />
በቀደም ሱሰኝነትን ስለማስወገድ<br />
በሬዲዮ እያወራን ‹‹በድምፅሽ ሱሰኛ ሆኛለሁ››<br />
የሚሉ የፅሁፍ መልዕክቶች ደርሰውኛል።<br />
[እየሳቀች] ሱሰኛ ስላለመሆን እያወራሁ<br />
‹‹ሱስ ሆኖብኛል›› ማለት ጥሩ አይደለም።<br />
ምንም አይነት ነገር ቢመጣ የሙያው<br />
ስነ-ምግባር ገትሮ ይይዝልኛል። እውነት<br />
ለመናገር ስለ ድምፄ አንተ እንዳልከው ያሉኝ<br />
አሉ። ስቱዲዮ ውስጥ በጣም ነፃ ሆኜ፣ ራሴን<br />
ሆኜ ነው የማወራው።<br />
አዎ! ከደንበኞች አንስቶ የፍቅር<br />
ጥያቄ ይገጥመኛል። የፍቅር ጓደኛ አለኝ።<br />
በፕሮግራማችሁ ላይ የምታወሪውን<br />
ትኖሪዋለሽ?<br />
ቆንጆ ጥያቄ ነው።<br />
የማደርጋቸውም፣ የማላደርጋቸውም አሉ።<br />
በግል ህይወቴ ያደረግኳቸው ዋነኛ ለውጦች<br />
አሉ። በጣም ፈሪ፣ ዝምተኛ እና አይናፋር<br />
ነበርኩ። ‹‹ድድ ማስጫ›› ላይ ለሚቀመጡ<br />
ጎረምሶች ‹‹የመጨረሻ ሙድ መያዣ››<br />
ነበርኩ። እናቴ ሬዲዮ ላይ ስትሰማኝ<br />
‹‹የምታወራው እውነት የእኔ ልጅ ናት?››<br />
ብላ ትገረማለች።<br />
አሁን የምሰራው ሰዎች ከእንደዚህ<br />
ያሉ ፍርሃቶች እንዲወጡ ነው። በነፃነት<br />
አልደራደርም፤ እኔ እንደነበርኩበት የሰው<br />
ልጅ በጭንቀት ባርነት ውስጥ እንዲኖር<br />
አልፈልግም።<br />
በብዛት የማወራውን ባደርግም<br />
በጣም በተቀናጀ አካሄድ እና በፕሮግራም<br />
የምመራ አይነት ሰው ግን አይደለሁም።<br />
ማስተካከል ግን ፈልጋለሁ።<br />
ከአንድ ጫፍ ወደ ሌላ ጫፍ<br />
የመጣሁት በራሴ ቢሆንም ዮሐንስ አፈወርቅ<br />
የተባለ ጓደኛዬ እና የስራ ባልደረባዬ እንዳልክ<br />
ብዙ ነገር አደፋፍረውኛል።<br />
አንቺስ አማካሪ እና ቴራፒስት አለሽ?<br />
ሰው እንደመሆኔ መጠን እኔም<br />
ችግር ስላለብኝ መደበኛ አማካሪ አለኝ።<br />
ሲጨንቅሽ ምን ማድረግ ያስደስትሻል?<br />
በጣም ሲጨንቀኝ ልደታ ቤተ<br />
ክርስቲያን ሄዳለሁ። ዛፎቹ <strong>ስር</strong> መቀመጥ<br />
ደስ ይለኛል። ከጎኔ ካለ ሰው ጋር ማውራት<br />
ደስ ይለኛል። ነገር ስለማያከብድ ከፍቅር<br />
ጓደኛዬ ጋር ማውራትም ያስደስተኛል።<br />
አንዳንዴ ግን ሰዎች አይረዱኝም።<br />
ስንት ኪሎ ነሽ?<br />
52፡፡ ቁመቴ ደግሞ አንድ<br />
ሜትር ከሰባ ነው፤ ረዥም ነኝ። ቅጥነቴን<br />
እወደዋለሁ።<br />
ሁለት ሰከንድ ነው የምሰጥሽ የአዲስ አበባ<br />
ከንቲባ ስም ማን እንደሚባል ንገሪኝ።<br />
‘Oh My God’… [በቁጭት<br />
አንገቷን የተቀመጠችበት ወንበር መደገፊያ<br />
ላይ አኑራ ወደ ጣሪያ እያየች ከትከት ብላ<br />
ሳቀች] በጣም አዝናለሁ አላውቅም። [አንድ<br />
የስነ-ልብዎና ባለሙያ የከተማዋን ከንቲባ<br />
ስም አታውቅም ቢባል ማን ያምናል? አቶ<br />
ኩማ ደመቅሳ መሆናቸውን ነግሬያት እንኳን<br />
ተጠራጥራለች። በሳቅ እየተፍለቀለቀች<br />
‹‹ከፖለቲካ ጉዳዮች ሩቅ ነኝ›› ብላለች።<br />
ይህን ለመመለስ ፖለቲካ የግድ ማወቅ<br />
ያስፈልጋል?]
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />
ዜናዎች<br />
“በሻዕቢያ ነጭ ለባሽነት ሀገር የሚያውቃቸው<br />
የኢህአዴግ መሪዎች ናቸው”<br />
መድረክ<br />
በሱራፍኤል ግርማ<br />
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ<br />
አንድነት መድረክ፣ በሻዕቢያ ነጭ ለባሽነት<br />
የሚጠረጠሩትና ሀገር የሚያውቃቸው የኢህአዴግ<br />
መሪዎች ሆነው ሳለ፣ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችን<br />
መንግሥት በዚህ መወንጀሉ ግራ የሚያጋባ መሆኑን<br />
አስታወቀ።<br />
ፓርቲው ትናንት ባወጣው መግለጫ፣<br />
“ኢህአዴግ ከሻዕቢያ ጋር ለመታረቅ እየተማፀነ ባለበት<br />
በአሁኑ ጊዜ እንኳን ሳይቀር መድረክ የኢትዮጵያን<br />
ጥቅም በማስጠበቅ ረገድ የአልጀርሱ ስምምነት መሰረዝ<br />
እንዳለበትና የአሰብ ወደብ ባለቤትነት ጉዳይ ድርድርና<br />
ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ሊደረግበት እንደሚገባ የፖለቲካ<br />
በናፍቆት ዮሴፍ<br />
በደቡብ ብሄሮች ብሄረሰቦችና<br />
ህዝቦች ክልላዊ መንግስት በዳውሮ<br />
ዞን ዋካ ከተማ “ወረዳችን ከቀርጫ<br />
ተነስቶ አማካኝ ቦታ ላይ ይሁንልን”<br />
በሚል ህብረተሰቡ ባነሳው ጥያቄ፣<br />
ህዝቡ እንዲያምፅ የድጋፍ ፊርማ<br />
አሰባስበዋል በሚል ከ30 በላይ ሰዎች መታሰራቸውን<br />
የአካባቢው ነዋሪዎች ለአውራምባ ታይምስ ገለፁ።<br />
እንደነዋሪዎቹ ገለፃ፣ ከዚህ ቀደም የአካባቢው<br />
ወረዳ “ማረቃ” እንደነበር እና ለጊዜያዊነት ወደ ቀርጫ<br />
የተዛወረ መሆኑን ገልፀው፣ ምንም እንኳን በጊዜያዊነት<br />
የተዛወረ ቢሆንም አሁን ግን ቋሚ በመደረጉ ህዝቡ<br />
አቋም የያዘ ፓርቲ ነው” ብሏል።<br />
የሻዕቢያ ተላላኪ ሊሆን ቀርቶ ከሻዕቢያ ጋር<br />
ሊያስማማው የሚችል ባህሪና አቋም እንደሌለው የገለፀው<br />
መድረክ፣ በጋዜጠኞችና በተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ላይ<br />
እየተፈፀመ ያለውን ወከባ አውግዟል። ፕሬዝዳንት<br />
ግርማ ወ/ጊዮርጊስ ለፓርላማ መክፈቻ ንግግር ሲያደርጉ<br />
በአባላቱና በሌሎች ጠንካራ ተቃዋሚዎች ላይ ኢህአዴግ<br />
መራሹ መንግስት የሚወስዳቸውን የኃይል እርምጃዎች<br />
ባለመጥቀስ “አንዳንድ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች<br />
በሽብር ተግባር ላይ ተሰማርተዋል” ማለታቸውን<br />
መድረኩ በፅኑ ኮንኗል።<br />
ከተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተጨማሪ፣<br />
ነፃ ጋዜጠኞችን መንግስት እያሳደደ መሆኑን የገለፀው<br />
መድረክ፣ “ለዚህ ሁሉ መነሻው ኢህአዴግ ሙስናን<br />
ለእንግልት እየተዳረገ መሆኑን አስታውቀዋል።<br />
በዞኑ ከ37 በላይ የቀበሌ ማህበር ነዋሪዎች<br />
መኖራቸውን የገለፁት የአውራምባ ታይምስ ምንጮች፣<br />
ወረዳው ከማረቃ ወደ ቀርጫ ከተዘዋወረ ወዲህ ለፍርድ<br />
ቤት ጉዳይ፣ ለህክምና እና ለመሰል ማህበራዊ ጉዳዮች<br />
ቀርጫ ድረስ መመላለሱ ህዝቡን እያንገላታው በመሆኑና<br />
ጥያቄውንም የዞኑ መስተዳድር ባለመመለሱ፣ እስከ<br />
ክልል አቤት በማለት መፍትሄ ባለማግኘታቸው ህዝቡ<br />
ተሰብስቦ ሰልፍ በመውጣቱ ህዝቡ ለአመፅ እንዲነሳሳ<br />
አስተባብራችኋል በሚል ነበር ከትላንት ወዲያ ለእ<strong>ስር</strong><br />
የተዳረጉት።<br />
በትላንትናው ዕለት በአካባቢው ያሉ ትምህርት<br />
ቤቶች በሙሉ ተዘግተው መዋላቸውንና አስተማሪዎችም<br />
ከቀኑ ስምንት ሰዓት ላይ ለአስቸኳይ ስብሰባ<br />
መዋጋት፣ መልካም አስተዳደርን ማስፈን፣ ሰብዓዊና<br />
ዴሞክራሲያዊ መብቶችን ማስከበር፣ እንዲሁም የሕግ<br />
የበላይነትን ማስጠበቅ ስላቃተው ነው” የሚል ምክንያት<br />
አስቀምጧል።<br />
ኢህአዴግ ኢትዮጵያ ውስጥ ፍትሕን<br />
ማረጋገጥና የዜጎችን ክብር ማስጠበቅ እንዳቃተው<br />
በመግለፅም የገዢው ፓርቲ ሥርዓተ-መንግስት<br />
በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ሳይውል ሳያድር መተካት<br />
እንዳለበትም አሳስቧል።<br />
በሀገሪቱ ሥር እየሰደደ ላለው ችግር<br />
ተጠያቂው ኢህአዴግ እንጂ ተቃዋሚ ፓርቲዎች<br />
አለመሆናቸውን ያስገነዘበው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ<br />
አንድነት መድረክ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ<br />
በፓርላማ ተገኝተው ባቀረቡት ንግግር ላይም ትችት<br />
በዳውሮ ዞን ዋካ ከተማ ከ30 በላይ ሰዎች ታሰሩ<br />
»<br />
አጣጥለዋቸዋል። አቶ መለስ በዚህ ወር መጀመሪያ<br />
ከኖርዌዩ አፍተንፖስተን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ-<br />
ምልልስ እነዚህ ስዊድናውያን ጋዜጠኞች “የሽብርተኞች<br />
ግብረ-አበሮች” እና “ጋዜጠኛ ያልሆኑ” መሆናቸውን<br />
ገልፀዋል።<br />
ይህ የአቶ መለስ የፓርላማ አስተያየት<br />
በመንግስት የሚመራው ዕለታዊ ጋዜጣ አዲስ ዘመን<br />
ተዘግቦ የተመለከተው ቴዲ አፍሮ፣ ኢትዮጵያዊውን ነፃ<br />
ለማውጣት አስፈላጊውን ገንዘብ እንደከፈለ ተገምቷል።<br />
እንደ “ሪፖርተር” ዘገባ ከሆነ፣ አስመሮም<br />
ሞት የተፈረደበት ሆን ብሎና አስቦ ሰው ገድሎ ሳይሆን፣<br />
በመኖሪያ ቤቱ ውስጥ እያለ ባለቤቱን ለመድፈር የመጡ<br />
ግለሰቦችን ለመከላከል በወሰደው እርምጃ ነው።<br />
መረጃው ትክክል ሆኖ ድምፃዊው በጎሳ<br />
መሪዎቹ የተጠየቀውን የ700 ሺህ ብር የነፍስ ካሳ<br />
ሙሉ በሙሉ በመክፈል ኢትዮጵያዊውን ወጣት<br />
ከሞት የሚያተርፈው ከሆነ፣ መንግስት ልጃቸውን<br />
እንዲያድንላቸው በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል<br />
ተደጋጋሚ ተማፅኖ ሲያቀርቡ ቆይተው በቂ ምላሽ<br />
ላላገኙት ቤተሰቦቹ እፎይታ እንደሚሆን ተገምቷል።<br />
በጉዳዩ ላይ አስተያየታቸውን ለአውራምባ<br />
ታይምስ የሰጡት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል-አቀባይ<br />
ትናንትና የአካባቢው በርካታ ት/ቤቶች ተዘግተው ውለዋል<br />
ሲፒጄ፣ ‘በጋዜጠኞች . . .<br />
ቴዲ አፍሮ በሶማሊያ ሞት ...<br />
በነፃው ሳምንታዊ ጋዜጣ አውራምባ ታይምስ ላይ እጅግ<br />
የሰላ ትችት ባተመ በማግስቱ የተሰነዘረ ሲሆን፤ ይህም<br />
በጋዜጣው ላይና በማኔጂንግ ኤዲተሩ ዳዊት ከበደ ላይ<br />
ከተቀጣጠለ የተራዘመ የስም-ማጥፋት ዘመቻ አንዱ<br />
ነው። በሲፒጄ አማካኝነት ከአማርኛ ወደ እንግሊዝኛ<br />
በተተረጎመው ጽሁፉ አዲስ ዘመን፣ “አመጽ ናፋቂዎችን<br />
መታገስ እስከመቼ?” ሲል ያተመው የአስተያየት ዘገባ<br />
መጠራታቸውን የገለፁት ምንጮች፤ ከተዘጉት ት/ቤቶች<br />
ውስጥ ዋካ መሰናዶ ት/ቤት፣ ኮጀብ መምህራን ኮሌጅ፣<br />
ዋካ አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት፣ ሞዴል<br />
አንደኛ ደረጃ ት/ቤት እና ሌሎችም ተዘግተው ውለዋል።<br />
እንደምንጮቻችን ገለጻ በአካባቢው ያሉ ጋዜጠኞች<br />
የተፈጠረውን ችግር እንዳይዘግቡ ተከልክለዋል።<br />
“ወደ ዋካ ከተማ ከክልል ፖሊሶች ቢመጡም<br />
የዞኑ አስተዳዳሪዎች ግን ጥያቄያችንን የሁለትና የሦስት<br />
ግለሰቦች ጥያቄ እንደሆነ በመግለፅ መፍትሔ እንዳናገኝ<br />
ተከልክለናል” ሲሉ ገልፀዋል። “የዞኑና የወረዳው<br />
አስተዳዳሪዎች በቀርጫ መኖሪያ ቤታቸውን ስለሰሩ<br />
እኛ ወደ ቀድሞ ወረዳችን ማረቃ አሊያም አማካይ ቦታ<br />
ይሁንልን ስንል ‹የመንገድና የወረዳ ጥያቄ የሚያነሳ ገደል<br />
ይግባ› ሲሉ ተሳልቀውብናል›› ያሉት የአካባቢው ሰዎች<br />
አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ደግሞ በበኩላቸው መንግስት<br />
ኢትዮጵያዊውን ለማትረፍ ጥረት ሲያደረግ መቆየቱን<br />
ተናግረዋል።<br />
አስመሮም ኃይለሥላሴ ነፍስ ካጠፋና በጎሳ<br />
መሪዎች ውሳኔው ከተላለፈበት አንድ ዓመት እንደሆነው<br />
ያስታወሱት አምባሳደር ዲና፣ “ልጁ እስካሁን ሳይገደል<br />
የቆየው ፑንት ላንድ ያለው ቆንፅላ ጽ/ቤታችን ባደረገው<br />
ጥረት ነው” ብለዋል።<br />
ቤተሰቦቹ ልጃቸውን ለማስለቀቅ<br />
የሚያስፈልገውን ያህል ገንዘብ በዕርዳታ ማግኘታቸውን<br />
የገለፁትን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ፣<br />
ቤተሰቦቹ ገንዘቡን ባያገኙ ኖሮ መንግስት ከፍሎ<br />
ያስለቅቀው እንደነበር ጠይቀናቸው፣ “‘ቢሆን ኖሮ’ ብዬ<br />
መልስ ለመስጠት አልችልም” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።<br />
ስለ ጉዳዩ ድምጻዊ ቴዲ አፍሮን ለመጠየቅ<br />
ወደ ተንቀሳቃሽ ስልኩ ተደጋጋሚ የስልክ ጥሪ<br />
ብናደርግም ስልኩ ዝግ በመሆኑ አስተያየቱን ለማካተት<br />
አልቻልንም።<br />
19<br />
ሰንዝሯል።<br />
“ጠቅላይ ሚኒስትሩና ፓርቲያቸው ኢህአዴግ<br />
በሀገራችን ያለው የፖለቲካ ምህዳር ችግር እንደሌለበትና<br />
የጨዋታ ሕግን ተከትሎ መሄድ ለፈለገ ሁሉ ምቹ<br />
እንደሆነ ለማስረዳት ሞክረዋል፤ ሆኖም በተጨባጭ<br />
የሚታየው ሁኔታ የተገላቢጦሽ ነው” ይላል - የፓርቲው<br />
መግለጫ።<br />
መግለጫው በማከልም፣ ከምርጫ 97<br />
በኋላ ኢህአዴግ ካደረበት ድንጋጤ የተነሳ የሲቪል<br />
ማሕበረሰቡን፣ የግል ጋዜጦችንና የተቃዋሚ ፓርቲዎችን<br />
እንቅስቃሴ የሚገድቡ አዋጆች እንዲፀድቁ ማድረጉን<br />
አስታውሷል።<br />
መንግስት ጉዳዩን ተመልክቶ እልባት ይሰጣቸው ዘንድ<br />
ጥያቄ አቅርበዋል።<br />
ዝግጅት ክፍላችንም የዞኑ የድርጅት ጉዳይ<br />
ኃላፊ ለሆኑት ለአቶ ለማ መሰለ፣ ለዳውሮ ዞን ዋና<br />
አስተዳዳሪ ለአቶ እስራኤል አካሉና በዞኑ የፀጥታ መምሪያ<br />
ኃላፊ ለሆኑት አቶ ተነሣ ብሩ ደውለን ስልካቸውን ያላነሱ<br />
በመሆኑ ምላሻቸውን አያላካተትን ቢሆንም፣ በወረዳው<br />
የህብረት ሥራና ግብይት ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ<br />
እስክንድር ተፈራ ችግሩ መፈጠሩን አምነው ወረዳ<br />
ይቀየር በሚል ህዝቡ አድማ እንዲያደርግ የድጋፍ ፊርማ<br />
አሰባስበዋል ተብለው የተጠረጠሩ ሰዎች መታሰራቸውን<br />
ገልፀው፣ ጉዳዩን ፍርድ ቤት እያየው እንደሚገኝ<br />
ለአውራምባ ታይምስ ገልፀዋል።<br />
የፀጥታ ኃይሎች በአቶ ዳዊት ላይ “እርምጃ እንዲወስዱ”<br />
ወትውቷል-ብሏል ሲፒጄ<br />
ጋዜጣው የሲፒጄ ዓለም አቀፍ የፕሬስ ነፃነት<br />
ሽልማት አሸናፊው ዳዊት ከበደን ከ“ሽብርተኛ ቡድኖች”<br />
ጋር በመስራት ከመወንጀሉም በላይ፣ መንግስት<br />
የ1997ቱን ምርጫ ተከትሎ በግል ሚዲያው ላይ<br />
በወሰደው እርምጃ ከ21 ወራቶች እ<strong>ስር</strong> በኋላ በቅድመ-<br />
ሁኔታዊ ይቅርታ የተፈታውን ይህን ጋዜጠኛ ይቅርታውን<br />
በመሻር ዳግመኛ እንዲያስረው ጠይቋል።<br />
እነዚህ የአዲስ ዘመን የቅርብ አስተያየቶች<br />
በአውራምባ ታይምስ ላይ እየተሰነዘሩ ካሉ ተከታታይ<br />
ጽሁፎች መካከል የቅርቦቹ ናቸው። በሀምሌ ወር አቶ<br />
ዳዊት ከበደ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ አቶ<br />
አንተነህ ኃይሉ እና በአታሚው የኢትዮጵያ ፕሬስ<br />
ድርጅት ላይ የስም ማጥፋት ክስ መ<strong>ስር</strong>ተው እንደነበር<br />
ሲታወስ፣ ክሱም በዳኛው ሙሉቀን ተሻለ ውድቅ<br />
እንደተደረገ የሲፒጄ የጥናት ቡድን አረጋግጧል።<br />
የሲፒጄ የምስራቅ አፍሪካ አማካሪ ቶም<br />
ሮዴስ እንዳብራሩት፣ “ይህ በቅርቡ የተሰማው የጠ/<br />
ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የቁጣ ናዳ በኢትዮጵያ ያሉ ነፃና<br />
ገለልተኛ ጋዜጠኞችን ሽብርተኝነት በሚሉ ውንጀላዎች<br />
ከስራቸው ለመንቀል እየተደረገ ያለው ስልታዊ ዘመቻ<br />
አካል ነው። በመንግስት ሚዲያዎች የሚሰራጨው ስም<br />
የማጥፋት ዘመቻ በአገሪቱ ውስጥ ያለውን የፍርሃት<br />
ድባብ በማባባስ የበኩሉን ሚና ይወጣል። በግል ፕሬሱ<br />
ላይ በተፋፋሙ የማስፈራሪያ እርምጃዎችም ኢትዮጵያ<br />
እንደ ዴሞክራሲያዊ መንግስት ያላትን ተቀባይነት<br />
እየሰዋች ነው።” ብሏል፡፡<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ
20<br />
በኤልያስ ገብሩ<br />
elias.gebru32@gmail.com<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
ጤና<br />
ኢትዮጵያ በታህሳስ ወር ለምታዘጋጀው 16ኛው ዓለም አቀፍ የኤድስና አባላዘር በሽታዎች የአፍሪካ ኮንፈረንስ እየተደረገ<br />
ያለው ዝግጅት ምን ደረጃ ላይ ይገኛል?<br />
ዝግጅቱ ሁለት ዘርፍ አለው። አንዱ የፕሮግራም ዝግጅት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የሎጀስቲክ<br />
ነው። ፕሮግራሞቹ ሳይንሳዊ፣ ሕብረተሰባዊና አመራርን የተመለከቱ ናቸው። በሳይንሳዊው<br />
ዙሪያ በርካታ ሥራዎች ተሰርተዋል። ወደ ሦስት ሺህ የሚጠጉ የጥናት ፅሁፎች ቀርበው፣<br />
ከእነዚህም ውስጥ አንድ ሺህዎቹ በዓለም አቀፍ ደረጃ ባሉ ሳይንቲስቶች ተመርጠው በቃልና<br />
በፖስተር ኤግዚብሽን ሊቀርቡ ዝግጁ ሆነዋል። እነዚህን በተመለከተ ጠቅለል ያለ መረጃ<br />
የሚሰጥ መጽሐፍ ተዘጋጅቷል። በአመራር ዘርፍ በርካታ ዝግጅቶች ተደርገዋል። የፖለቲካና<br />
የኃይማኖት መሪዎች፣ የቢዝነስ ዘርፉ፣ ዓለም አቀፍ የልማት አጋሮች፣ የኤች.አይ.ቪ/ኤ.<br />
አይ.ዲ.ኤስ ቫይረስ በደማቸው ውስጥ ያለባቸው ሰዎች የግንኙነት መረቦች /ቡድኖች/፣<br />
የማሕበራት መሪዎችን የመሳሰሉት የሚሳተፉባቸው በርካታ ፕሮግራሞች አሉ። የቀድሞ<br />
የሀገር መሪዎች፣ ሚኒስትሮች፣ ቀዳማዊ እመቤቶችና የተባበሩት መንግስታት ዳይሬክተሮች<br />
የሚሳተፉበት ፕሮግራምም አለ።<br />
በሕብረተሰብ በኩል የሕብረተሰብ መሪዎች የሚናገሩባቸው በርካታ ዝግጅቶች ተዘጋጅተዋል።<br />
ሕብረተሰቡም ሊሳተፍበት የሚችል “Community Village” የሚባል ፕሮግራም አለ። እዛ<br />
ውስጥ የተለያዩ የወጣቶች፣ የሴቶችና የሕብረተሰብ ክፍሎች ኤግዚብሽንና ውይይቶች<br />
የሚያደርጉባቸው ፕሮግራሞችና ትርዒቶች ይገኛሉ። ሎጀስቲክን በተመለከተ፤ የሆቴል<br />
መስተንግዶ፣ የትራንስፖርት አገልግሎት፣ የተለያዩ የመሰብሰቢያ አዳራሾች፣ የቪዛ፣ የደህንነት<br />
ጉዳይና ፕሮቶኮልን የተመለከቱ ዝግጅቶችች እየተከናወኑ ነው። የተለያዩ ኢንፎርሜሽን<br />
ቴክኖሎጂ መሳሪያዎችም ያሉ ሲሆን እነሱን ወደመቋጫ ላይ ነን። ብዙ ነገሮች በጥሩ ሁኔታ<br />
ላይ ነው ያሉት።<br />
ኢትዮጵያ ኮንፈረንሱን ማዘጋጀቷ ፋይዳው ምንድን ነው?<br />
በመጀመሪያ ደረጃ በኤች.አይ.ቪ/ኤ.አይ.ዲ.ኤስ እና በተዛማጅ ችግሮች ዙሪያ አዘጋጁ ሀገር<br />
ጉባዔውን በማዘጋጀቱ ዓለም አቀፍ ግዴታውን መወጣቱን ያስመሰክራል። በአፍሪካም ሆነ<br />
በዓለም አቀፍ ደረጃ ኤች.አይ.ቪ/ኤ.አይ.ዲ.ኤስን ከመከላከል እና ከመቆጣጠር አኳያ ሀገሪቱ<br />
ዓለም አቀፋዊ ድርሻዋን በትልቁ እንደተወጣች ያስቆጥራል። ሁለተኛ፣ ሀገሪቱ ከዚህ በፊት<br />
በኤ.አይ.ዲ.ኤስ፣ በቲቢ እና ወባን በመሳሰሉት ከፍተኛ ችግሮች ዙሪያ ስትሰራቸው የነበሩትንና<br />
ውጤት ያገኘችባቸውን ሥራዎች የምታሳይበት ነው። ከዚህም ሌላ በቱሪዝም መስክ ከፍተኛ<br />
ቦታ እያገኘ ላለው የኮንፈረንስ ቱሪዝም ጥቅም አለው። በዚህ ከፍተኛ ጥቅም እያገኙ የሚገኙ<br />
የታወቁ ሀገሮች አሉ። በዚህ ከፍተኛ የሥራ መስክም የሚፈጠርበት ሲሆን እየተሰራ ያለው<br />
ከዚህ ቀደም እንደተለመደው የቱሪዝም አይነት ብቻ አይደለም። ከዚህ አንፃር ኢትዮጵያ<br />
በዘርፉ የምትወዳደርበት ይሆናል። ይኼንን ኮንፈረንስ ሀገሪቱ በብቃት ከተወጣች ወደፊት<br />
ተመሳሳይ የሆኑ ኮንፈረንሶች ለማዘጋጀት ያላትን ብቃት ታስመሰክራለች ማለት ነው።<br />
በማስተዋወቅ ደረጃም የተለያዩ ሴክተሮች በዚህ ስብሰባ ይጠቀማሉ - ቀጥተኛ በሆነ የገንዘብ<br />
ጥቅም፣ ከሰዎች ጋር ግንኙነት በማድረግ፣ በቢዝነስና በምርምር ሥራ መረጃ በመለዋወጥ።<br />
ኮንፈረንሱ የሀገሪቱን በጎ ገፅታ ከመገንባት አንፃርም ትልቅ ሚና አለው። እንዲሁም፣ ከፍተኛ<br />
የሆነ የሚዲያ ፍሰት የሚመጣበት ሁኔታም አለ።<br />
በኮንፈረንሱ ላይ ይበልጥ የሚቀርቡት ሳይንሳዊ የምርምር ጥናታዊ ፅሁፎች ናቸው። በተለይ ከሰሃራ በታች በሚገኙት<br />
የአፍሪካ ሀገራት ባለው የበሽታው <strong>ስር</strong>ጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ወደ ተግባር ሥራ የሚያስገቡ ጉዳዮች ላይ<br />
ኮንፈረንሱ ምን ውጤት ይሰጣል?<br />
የጉባዔው የመጨረሻ ውጤት ምንድን ነው ስንል በመጀመሪያ በኤች.አይ.ቪ/ኤ.አይ.ዲ.ኤስ<br />
መከላከል እና መቆጣጠር ዙሪያ ከፍተኛ የሕብረተሰብ እንቅስቃሴ ላይ ያሉ ባለድርሻ አካላትን<br />
የማንቀሳቀስ እና ለጉዳዩ ምላሽ ከፍተኛ ቁርጠኝነት እና ድጋፍ እንዲሰጡ<br />
የማድረግ ነው። እነዚህ ባለድርሻ አካላት የሀገርና የተለያዩ ተቋማት<br />
መሪዎች፣ የዓለም አቀፍ የልማት አጋሮች፣ ሕብረተሰቡ፣<br />
የቢዝነሱ ዘርፍ፣ ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ ያሉ የሕብረሰብ<br />
ክፍሎች ናቸው። የኮንፈረንሱ መሪ ቃልም “Own, Scale<br />
up & Sustain” (ባለቤትነት፣ ማስፋትና ቀጣይነት)<br />
የሚል በመሆኑ ባለድርሻ አካላትን በከፍተኛ ደረጃ<br />
የሚያንቀሳቅስ ነው። በሁለተኛ ደረጃ በርካታ ሳይንሳዊ<br />
ፅሁፎች ከመቅረባቸው ባሻገር ሌሎች የተቀመሩ ጥሩ<br />
መልካም ልምዶችም በተለያየ መልኩ ይቀርባሉ።<br />
ይኼም የሚጠቅመው ለኤች.አይ.ቪ/ኤ.አይ.ዲ.ኤስ<br />
ምላሽ በሳይንስ እና በመረጃ ላይ እንዲሆን ለማድረግ<br />
ነው። ስለዚህ ከብዙ የአፍሪካ ሀገራት የመነጩ<br />
ጥናታዊ ፅሁፎችና በጎ ልምዶች፤ ከአፍሪካም ውጪ<br />
ተመሳሳይ ሁኔታ ባለባቸው ደሃ ሀገራት በሽታውን<br />
ከመከላከልና ከመቆጣጠር አንፃር በሕብረተሰብ፣<br />
በመንግሥት ወይም በኃይማኖት ደረጃ የተሰሩ<br />
ሥራዎች ይቀርባል።<br />
ሌላ ከውጤት አንፃር ከኮንፈረንሱ የምንጠብቀው፣<br />
ኤች.አይ.ቪ/ኤ.አይ.ዲ.ኤስን ከመዋጋት አንፃር በመሪዎችና<br />
በአጋሮች ደረጃ ቃልኪዳን ተገብተው የተፈፀመውና<br />
ያልተፈፀሙ የተለያዩ ነገሮች አሉ። እና<br />
እነዚህ የተለያዩ አካላት “ግዴታቸውን<br />
ተወጥተዋል ወይስ<br />
አልተወጡም” ተብለው<br />
የ ሚ ጠ የ ቁ በ ት ና<br />
ው ይ ይ ት<br />
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />
“በኢትዮጵያ የኤች.አይ.ቪ ቫይረስ<br />
ሥርጭት መቀነሱ ሊያዘናጋን አይገባም”<br />
ዶ/ር ይገረሙ አበበ<br />
/የ16ኛው የአይካሳ ኮንፍረንስ ሰብሳቢ/<br />
ዶ/ር ይገረሙ አበበ ኢትዮጵያ በቀጣይ ታህሳስ ወር ላይ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የምታዘጋጀው 16ኛው ዓለም አቀፍ<br />
የኤድስና አባላዘር በሽታዎች የአፍሪካ ኮንፈረንስ (ICASA) ሰብሳቢ ናቸው። ለአራት ቀናት በሚቆየው ዓለም አቀፍ<br />
ጉባዔ ዙሪያ ዶ/ር ይገረሙን የጤና አምድ አዘጋጅ እንዲህ አነጋግሯዋል።<br />
“<br />
“<br />
ትክክለኛውን ቁጥር አሁን መጥቀስ<br />
ባልችልም፣ በኢትዮጵያ የበሽታው ወረርሽኝ<br />
በብዛት ያለው በከተማ ነው። ነገር ግን፣<br />
የቫይረሱ <strong>ስር</strong>ጭት በከፍተኛ ደረጃ እየቀነሰ<br />
ነው። ይህንን መገንዘብ የምንችለውና<br />
በነፍሰ-ጡሮች ላይ የሚደረገው ክትትል<br />
እንደሚያሳየው፣ በአዲስ አበባ እና በሌሎች<br />
የክልል ከተሞች በአንድ ወቅት ላይ<br />
<strong>ስር</strong>ጭቱ ከ16-17 በመቶ ደርሶ ነበር።<br />
አሁን ግን <strong>ስር</strong>ጭቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ<br />
ከ2-3 በመቶ፣ እንዲሁም በገጠር 0.9<br />
በመቶ የደረሰበት ሁኔታ አለ።<br />
ተደርጎባቸው መልስ የሚገኘበት ነው። በተጨማሪም ሌላ ውጤታማ የሆኑ የተለያዩ<br />
ስትራቴጂዎች፣ ፖሊሲዎችና ፕሮግራሞች ውይይት ላይ ቀርበው ውሳኔ የሚሰጥባቸው<br />
ናቸው። ኃብትን ከማሰባሰብም አንፃር አሁን ብዙ አገልግሎት የሚያገኙ የሕብረተሰብ<br />
ክፍሎች አሉ። በእርግጥ ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ ያሉ በርካታ በሶስተኛው ዓለም የሚገኙ<br />
የሕብረተሰቡ ክፍሎች ሕክምና እያገኙ ቢሆንም ያላገኙት ይበልጣሉ። ነገር ግን፣ በሽታውን<br />
ስለ መከላከል መረጃ የሚያገኙት ወጣቶች ቁጥር እየጨመረ መጥቷል። ብዙ የሚቀርም አለ።<br />
ለዚህ ደግሞ መዋዕለ-ንዋይ ያስፈልጋል። ስለዚህ በዚህ ስብሰባ ላይ ከፍተኛ ድጋፍ ሲሰጡ<br />
የኖሩ አካላት ድጋፋቸውን እንዲጨምሩ፤ ድጋፋቸውን ያቆሙ ኃብታም ሀገራትም ድጋፋቸውን<br />
ዳግም እንዲጀምሩ ያደርጋል። በሌላ በኩል እንደ ቻይና፣ ሕንድና ብራዚልን የመሳሰሉ በጣም<br />
በፍጥነት እያደጉ ያሉ ሀገራት ለግሎባል ፈንድ ገንዘብ ማዋጣት ጀምረዋል።<br />
እነዚህ የበለጠ ገንዘብ ማዋጣት እንዳለባቸው ቅስቀሳ የሚደረግበትና ባለፉት ጊዜያት የተዋጡ<br />
መዋዕለ-ንዋዮች በአግባቡ ሥራ ላይ መዋል አለመዋላቸው በኮንፈረንሱ ላይ ውይይት<br />
የሚደረግበት ነው። ጉባዔውም ለአራት ቀናት በመሆኑ በርካታ ጥቅሞች አሉት። ብዙ<br />
መልዕክቶችም ይተላለፋሉ። በአጠቃላይ በአይካሳ ላይ የሚወሰኑት ውሳኔዎች ኢትዮጵያን ብቻ<br />
ብሎ ሳይሆን አጠቃላይ አፍሪካን ጭምር ነው። በተለይም ችግሩ በስፋት ባለበት ከሰሃራ በታች<br />
በሚገኙ ሀገራት ነው። ስለዚህ ኢትዮጵያ ከዚህ ለራሷ የምትወስደው ነገር ሊኖር ይችላል።<br />
ውጤት ሲባል አጠቃላይ የአፍሪካ ወጤት ነው። በኮንፈረንሱ ላይ የሚተላለፉት ውሳኔዎች<br />
ሁሉንም የሚመለከቱ ሆነው ሀገራት የየራሳቸውን ድርሻ ይወስዳሉ።<br />
በአሁኑ ወቅት በዓለም ላይ ያለው የበሽታው <strong>ስር</strong>ጭት ምን ይመስላል?<br />
በአጠቃላይ በዓለም ላይ ከ30 ሚሊዮን በላይ የሚቆጠሩ ሰዎች ከቫይረሱ ጋር ይኖራሉ።<br />
ከዚህም ሌላ በአዲስ መልክ ቫይረሱ የሚተላለፍበት ሁኔታ አለ። በእርግጥ ይሄ እየቀነሰ<br />
መጥቷል። የሞት ቁጥሩም መድኃኒቱ ተመጣጣኝ በሆነ ዋጋ በስፋት እየተሰራጨ በመሆኑ<br />
እየቀነሰ ነው። አሁንም ግን በአፍሪካ በተለይም ከሰሃራ በታች በስተደቡብ ባሉ ሀገራት፣<br />
ከሌሎች ጋር ሲወዳደር፣ በበሽታው በከፍተኛ ደረጃ እየተጎዱ ናቸው። … ለውጦች ቢኖሩም<br />
ገና ብዙ ለውጥ ያስፈልጋል። በአብዛኛው ከ70 በመቶ በላይ የሚሆኑት ቫይረሱ በደማቸው<br />
ያለባቸው ሰዎች የሚኖሩት ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ ነው። በአዲስ መልክ<br />
ሕፃናት እና ወጣቶች በቫይረሱ የሚያዙት እና የሚሞቱት በዚሁ አካባቢ ነው። ግን ከላይ<br />
እንደገለፅሁት፣ ገና ቢቀርም፣ የሞት እና የቫይረሱ መተላለፊያዎች ቀንሰዋል።<br />
የበሽታውን <strong>ስር</strong>ጭት ከአፍሪካ ውጪ በዓለም አቀፍ ደረጃ ስናየው አዳዲስ ወረርሽኞች<br />
በአንዳንድ አካባቢዎች በተለያዩ ምክንያቶች እየተከሰቱ ናቸው። ለምሳሌ፣ በምስራቅ አውሮፓ<br />
ራሺያን ጨምሮ በአንዳንድ የቻይና ክፍሎች በመርፌ በሚሰጥ አደንዛዥ ዕፅ (Injected Drugs)<br />
አማካኝነት <strong>ስር</strong>ጭቱ እየጨመረ ይገኛል። “ከቫይረሱ ነፃ ናቸው” ተብለው ለረዥም ጊዜያት<br />
የተገመቱት የሰሜን አፍሪካና የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ውስጥ፣ አሁንም በመርፌ<br />
በሚሰጥ አደንዛዥ ዕፅና በግብረ-ሰዶማዊነት አማካኝነት <strong>ስር</strong>ጭቱ እየጨመረ ነው። በአጠቃላይ<br />
የበሽታው <strong>ስር</strong>ጭት በዓለም አቀፍ ደረጃ እየቀነሰ ነው። በአፍሪካ ቢቀንስም ችግሩ ሰፊ በመሆኑ<br />
በሌላ አዳዲስ ምክንያቶች እንደወረርሽኝ የሚከሰትባቸው አካባቢዎች አሉ።<br />
ለ<strong>ስር</strong>ጭቱ መቀነስ ምን ምን ምክንያቶች ይጠቀሳሉ?<br />
ኤች.አይ.ቪ/ኤ.አይ.ዲ.ኤስን ለመቆጣጠር እና ለመከላከል ብዙ ስትራቴጂዎች አሉ። አንዳንዶቹ<br />
አዳዲሶች ናቸው። አንዳንዶቹ ደግሞ ቀድሞ የነበሩ ናቸው። ሁሉም የየራሳቸው ድርሻ አላቸው።<br />
የባህሪ ለውጥ ለማምጣት የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ኮንዶም፣ የአባላዘር በሽታዎችን ጉዳይና<br />
ከእናት ወደ ልጅ ቫይረሱ እንዳይተላለፍ የሚደረገው እንቅስቃሴ በከፍተኛ ደረጃ የየራሳቸው<br />
ድርሻ አላቸው። አዳዲሶቹ ደግሞ <strong>ስር</strong>ጭታቸውን በሕክምና አማካኝነት በመከላከልና ይህም<br />
መንገድ በሕብረተሰቡ ውስጥ በሚስፋፋበት ጊዜ የቫይረሱ <strong>ስር</strong>ጭት የመቀነስ ዕድሉ ሰፊ ነው።<br />
ይኼ በግለሰብ ደረጃ አይደለም። ምክንያቱም መድኃኒቱን የጀመሩ ሰዎች የሚመከሩት ደህንነቱ<br />
የተጠበቀ ግንኙነት እንዲፈፀሙ ነው። ያንን ካላደረጉ አሁንም ቫይረሱ የመተላለፍ ዕድል<br />
አለው። ስለዚህ “መድኃኒት የቫይረሱ መተላለፈያን ይቀንሳል” ሲባል በሕብረተሰብ ደረጃ እንጂ<br />
ግለሰቡ፣ “መድኃኒት ጀምሬያለሁና እንደፈለኩ ያለጥንቃቄ ወሲብ እፈፅማለሁ” ቢል ቫይረሱን<br />
ለሌላው ያስተላልፋል። ለራሱም ቢሆን ቫይረሱን የለመዱ መድኃኒቶች ሊያገኙት ይችላሉ።<br />
ስለዚህ ዘዴው በማሕበረሰብ ደረጃ አንዱ የመከላከያ መንገድ ነው። በስፋት መድኃኒቱን<br />
መጠቀም ለሚያስፈልጋቸውና መድኃኒቱን ለሚወስዱት ሰዎች በጥንቃቄ በሀኪም ትዕዛዝ<br />
መሰረት መውሰዱ የቫይረሱን <strong>ስር</strong>ጭት በሕብረተሰቡ ውስጥ እንዲቀንስ ያደርጋል። በተጨማሪም<br />
ሌሎች አዳዲስ የመከላከል ዘዴዎች እየታዩ ነው።<br />
ወደ ሀገራችን እንምጣና፣ የበሽታውን <strong>ስር</strong>ጭት እንዴት ይገልፁታል?<br />
ትክክለኛውን ቁጥር አሁን መጥቀስ ባልችልም፣ በኢትዮጵያ የበሽታው ወረርሽኝ በብዛት ያለው<br />
በከተማ ነው። ነገር ግን፣ የቫይረሱ <strong>ስር</strong>ጭት በከፍተኛ ደረጃ እየቀነሰ ነው። ይህንን መገንዘብ<br />
የምንችለውና በነፍሰ-ጡሮች ላይ የሚደረገው ክትትል እንደሚያሳየው፣ በአዲስ አበባ እና<br />
በሌሎች የክልል ከተሞች በአንድ ወቅት ላይ <strong>ስር</strong>ጭቱ ከ16-17 በመቶ ደርሶ ነበር። አሁን ግን<br />
<strong>ስር</strong>ጭቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ2-3 በመቶ፣ እንዲሁም በገጠር 0.9 በመቶ የደረሰበት ሁኔታ<br />
አለ። ይሄ አጠቃላይ ሁኔታ እንዳለ ሆኖ፣ ቫይረሱ እጅግ በጣም የተሰራጨባቸው የምንላቸው<br />
አንዳንድ ቦታዎች አሉ። በእነዚህና በአንዳንድ የሕብረተሰብ ክፍሎች አካባቢ <strong>ስር</strong>ጭቱ ከፍተኛ<br />
እንደሆነና በዚህም ዙሪያ ብዙ ሥራ መሠራት እንዳለበት ነው የሚያሳየው። በመሆኑም<br />
የሥርጭቱ የመቀነስ ሁኔታ ብዙ ሊያዘናጋን አይገባም።<br />
ለኮንፈረንሱ ከኢትዮጵያ ብዙ ጥናታዊ ፅሁፎች ቀርበዋል?<br />
አዎን። ደስ የሚለው ጥናታዊ ጽሁፍ በማቅረብ ኢትዮጵያ ከናይጄሪያ ቀጥላ ሁለተኛ ነች።<br />
ይኼ የሚያስመሰግን ነው። ምክንያቱም አንደኛ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ሳይንሳዊ ሕብረተሰብ<br />
ብዙ ስራ እየሰራ እንዳለ የሚያሳይ ሲሆን፣ ሁለተኛ ደግሞ በሀገሩ እንደዚህ አይነት ጉባዔ<br />
ሲደረግ በከፍተኛ ደረጃ ለመሳተፍ ዝግጁ መሆኑን ያሳያል።<br />
ጽሑፎች ከመቅረባቸው ባሻገር ተቀባይነት ያገኙና ያላገኙ ጥናቶች አሉ። አብዛኛዎቹ ግን<br />
ተቀባይነት አላገኙም።<br />
ከላይ እንደገለፁልኝ፣ የኮንፈረንሱ አንዱ ትርፍ የኢትዮጵያን በጎ ገጽታ ማሳየት ነው። ነገር ግን፣ በከተሞች በተለይም<br />
በመዲናችን አዲስ አበባ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተበራከተ የመጣው የሴተኛ አዳሪዎችና የመንገድ ላይ የወሲብ ንግድ<br />
የተባለውን በጎ ገፅታ አያሳይም። በዚህ ላይ ምን ታስቧል?<br />
መጀመሪያ ያልከው ነገር “ጨምሯል” ሲባል በደንብ በጥናት<br />
መታወቅ አለበት። ሌላው ነገር ይሄ ማሕበራዊ ችግር<br />
በሁሉም የአፍሪካ ሀገራት ያለ ችግር በመሆኑ የተለየ<br />
ነገር ተደርጎ አይወሰድም። በመሆኑም፣ ስብሰባው<br />
ሲካሄድ የሚደረግ ምንም የተለየ እርምጃ ሊኖር<br />
አይችልም። የተባሉትን ሰዎች ማግለልን የመሳሰሉ<br />
ነገሮች አይደረግም። ምክንያቱም፣ ከዚህም<br />
የባሰ ሁኔታ ላይ የሚገኙ አሉ። በሂደት ሀገሪቱ<br />
እያደገችና ከድህነት እየወጣች በምትሄድበት ጊዜ<br />
ይሄ ሁኔታ እየከሰመ ይሄዳል። ሀገሪቷ እስክታድግ<br />
ድረስ የማይጠበቁና የተባሉትን ሴቶች የሚመለከቱ<br />
ስራዎች እየተሰሩ ነው። በመንግስትና በምግባረ-<br />
ሰናይ ድርጅቶች አማካኝነት የአጭርና የረዥም ጊዜ<br />
ዕቅዶችም አሉ። ሆኖም እነዚህን ሰዎች በኃይል<br />
አስገድዶ ወደ አንድ ቦታ ማስቀመጥ ትክክለኛ አሰራር<br />
አይሆንም። ኮንፈረንሱም ይኼንን አያደርግም።
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />
በታዳሽ የኃይል ምንጮች<br />
የሚከንፉ ዘመናዊ ኦቶሞቢሎች<br />
በአብዱ መሐመድ<br />
ከስኳር ዝቃጭ ኢታኖል<br />
የተባለውን ነዳጅ በማምረትና በኢታኖል<br />
የሚሽከረከሩ ኦቶሞቢሎችን በመፈብረክ<br />
ቴክኖሎጂውን በበላይነት የምትመራው፣<br />
ዓለም በተለይ በእግር ኳሷ የሚያውቃት<br />
ብራዚል ነች።<br />
ኢታኖል፣ ስኳር በማምረት<br />
ሂደት የሚመጣውን ዝቃጭ<br />
‹‹ፈርመንቴሽን›› በተባለው ኬሚካላዊ<br />
ሂደት ‹‹ይስት›› በተባለ በውስጡ ኢንዛይም<br />
በያዘ ባክቴሪያ በማብላላት ለኃይል ፍጆታ<br />
የሚውል ነዳጅ ነው።<br />
ይህንን ነዳጅ እ.አ.አ ከ1982<br />
ጀምሮ እስከ 5.7 ሜጋ ሜትር ኪዩብ<br />
በየዓመቱ በማምረት የኃይል ፍላጎቷን<br />
ማሟላት በጀመረችው ብራዚል እ.አ.አ<br />
ከ2000 ጀምሮ 75 በመቶ የኃይል ፍላጎቷን<br />
የምታሟላውና በጎዳናው ላይ የሚተራመሱ<br />
ኦቶሞቢሎች የሚተራመሱት በኢታኖል<br />
ነው።<br />
የኢነርጂ ጥናት ባለሙያዎች<br />
የብራዚልን ተሞኩሮ መነሻ በማድረግ<br />
ባቀረቡት ጥናት መረጃ በአንድ ሄክታር<br />
በአማካይ 50 ቶን ሸንኮራ አገዳ ማምረት<br />
ይቻላል። ይህንን የሸንኮራ አገዳ ወደ ስኳር<br />
በመለወጥ ሂደት ከስኳር ኢንዱስትሪ<br />
ከሚወጣው ዝቃጭ ከአንድ ቶን ሸንኮራ<br />
በአማካይ 70 ሊትር፤ በአንድ ሄክታር ላይ<br />
ከሚመረት የሸንኮራ አገዳ፣ 3500 ሊትር<br />
ኢታኖል ይወጣል።<br />
ኢታኖልን በሀገራችን<br />
እንደሚሰራበት ከተፈጥሮ ነዳጅ ጋር<br />
ከመቀየጥ ባለፈ በኦቶሞቢል ግንባታ<br />
ከአለማችን ቀዳሚ የሆኑ እንደ ቮልስዋገን፣<br />
ፎርድ፣ ፊያትና ጀነራል ሞተርስ<br />
በብራዚል በሚገኙ ቅርንጫፍ መስሪያ<br />
ቤቶች የሚያመርቷቸው ኦቶሞቢሎች<br />
እንደባለቤቱ ፍላጎት ሲያስፈልግ በተፈጥሮ<br />
ነዳጅ አሊያም በኢታኖል የሚንቀሳቀሱ<br />
ናቸው። ከነዚህ ኦቶሞቢሎች ‘ፍሌክስ’<br />
የተባለው ኦቶሞቢል ከብራዚል አልፎ<br />
በሰለጠነችው አሜሪካ የፈላጊው ቁጥር<br />
ከ20 በመቶ የበለጠ ዕድገት ማስመዝገብ<br />
የጀመረው እ.አ.አ ከ2003 ጀምሮ ነው።<br />
ብራዚል በኢታኖል የኃይል<br />
ፍላጎቷን አሟልታ ከአንድ ሚሊየን<br />
ለሚበልጥ ዜጋዋ የሥራ ዕድል<br />
ከመፍጠሯም በተጨማሪ፣ ቴክኖሎጂውን<br />
በመሸጥ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማግኘት<br />
በከፍተኛ ርቀት ዓለምን እየመራች ነው።<br />
አሁን በየጊዜው እየነጠፈና ጣራ እየነካ<br />
የመጣውን የነዳጅ ውዝግብ ለመፍታት<br />
እንዲሁም የአካባቢ ብክለትን ለመቀነስ<br />
እተለወጠ በመጣው የቴክኖሎጂ ሽግግር<br />
ከብክለት የፀዱ የኃይል ምንጮች<br />
የሚንቀሳቀሱ ኦቶሞቢሎች እየተፈበረኩና<br />
ወደጎን እየወጡ መሆናቸውን በየጊዜው<br />
የሚደመጥ ዜና ሆኗል።<br />
በየጊዜው እየተመረቱ የሚወጡ<br />
ከብክለት የፀዱ ቴክኖሎጂ የሚጠቀሙ<br />
ኦቶሞቢሎችን በሚያስተዋውቀው<br />
‹‹ካር መጋዚን›› በተባለ መፅሄትና<br />
በየዓመቱ በየዘርፉ ለውድድር ቀዳሚ<br />
ለሆኑት እውቅና በሚሰጠው የጊነስ ቡክ<br />
በተቀመጠው መረጃ አሁን ከፍተኛ ቦታ<br />
የተሰጣቸው የሀይብሪድና የኤሌክትሪክ<br />
ኦቶሞቢሎች ናቸው።<br />
‹‹ሀይብሪድ ካር›› ውሃ<br />
ከተሰራባቸው የኬሚካል ቅንጣቶች<br />
ከሀይድሮጅንና ከኦክሲጅን ሀይድሮጅንን<br />
‹‹ኤሌክትሮሊስስ›› በተባለው የኬሚስትሪ<br />
ዘዴ እየለየ ለኦቶሞቢል ኢንጂን በመቀለብና<br />
ውሀን በተረፈ ምርት በማስወገድ<br />
የሚንቀሳቀሱ ኦቶሞቢሎች ናቸው።<br />
በዚህ ቴክኖሎጂ እንዲንቀሳቀሱና<br />
ከተፈበረኩ ኦቶሞቢሎች በሚያወጣው<br />
ጉልበትና ፍጥነት የአለምን ሪከርድ ሰብሮ<br />
ባለፈው ሳምንት በጊነስ ቡክ የሰፈረው<br />
በእንግሊዝ ሳንታ ሮድ ከተማ በተዘጋጀ<br />
የሀይብሪድ ካር ውድድር አሸናፊ ለመሆን<br />
የቻለው ‹‹ኢንፊኒቲ ኤም 35 ኤች›› የተባለ<br />
ሥያሜ የተሰጠው ኦቶሞቢል ነው።<br />
ዘመናዊ ከሆኑት ከቢኤም<br />
ደብሊው 5 ሲፊየስና ከጃጓር ኤክስ ኤፍ<br />
ዲዛይን ጋር ተመሳስሎ የቀረበው ‹M35H›<br />
3.5 ሊትር ሀይድሮጅን ወደኤሌክትሪክ<br />
በሚቀይሩ በድምሩ 302 የፈረስ ጉልበት<br />
በሚያመነጭ v-6 በተባለ ኢንጂን በሰዓት<br />
105.95 ኪሎ ሜትር በመክነፍ ውድድሩን<br />
ምንም ብክለት በሌላቸው ‹‹ዜሮ ኢሚሽን›› የተባሉ<br />
ከባትሪ የሚያገኙትን ኃይል ወደ ኤሌክትሪክ እየለወጡና<br />
የኤሌክትሪክ ሀይል እየተሞሉ ከሚጓዙ ኦቶሞቢሎች<br />
ሪከርዱን በስማቸው ያስመዘገቡት ለመኪና ውድድር ስፖርት<br />
የተዘጋጀው ‹‹አክሲራይድ›› እና ለሰው መጓጓዣ የተዘጋጀው<br />
‹‹ብላክ ከረንት›› የተባለው ኦቶሞቢል ነው።<br />
ያጠናቀቀው በአማካይ እያንዳንዱን አንድ<br />
አራተኛ ማይል (402.3 ሜትር) በ13.9<br />
ሰከንድ በመክነፍ ነው።<br />
በኢታኖል ከሚከንፉ<br />
ኦቶሞቢሎች ቀዳሚ የሆነው የብራዚሉ<br />
ሥሪት ፍሊክስ ሙሉ በሙሉ ከብክለት<br />
የፀዳ ባለመሆኑ ከብክለት ከፀዱት ጋር<br />
ለውደድር ባይቀርብም የአምሳዮቹን<br />
ሪከርድ የሰበረው በሰዓት 364.6 ኪሎ<br />
ሜትር በተመዘገበ ፍጥነት እንደሆነ የጊነስ<br />
መረጃ ይጠቁማል።<br />
ምንም ብክለት በሌላቸው<br />
‹‹ዜሮ ኢሚሽን›› የተባሉ ከባትሪ<br />
የሚያገኙትን ኃይል ወደ ኤሌክትሪክ<br />
እየለወጡና የኤሌክትሪክ ሀይል እየተሞሉ<br />
ከሚጓዙ ኦቶሞቢሎች ሪከርዱን በስማቸው<br />
ያስመዘገቡት ለመኪና ውድድር ስፖርት<br />
የተዘጋጀው ‹‹አክሲራይድ›› እና ለሰው<br />
መጓጓዣ የተዘጋጀው ‹‹ብላክ ከረንት››<br />
የተባለው ኦቶሞቢል ነው።<br />
በእንግሊዛዊ ወንድማማቾች<br />
በኦሊ እና ሳም ያንግ ለሰው መጓጓዣ<br />
የፈበረኳት ‹‹ብላክ ከረንት›› ጠቅላላ<br />
የውጭና የውስጥ ዲዛይኗ የተወሰደው<br />
እ.አ.አ በ1965 ለመጀመሪያ ጊዜ ጎዳና<br />
ከወጣችው ከቮልስ ዋገን ነው። ይህን<br />
ዲዛይን ተላብሳ በሰኔ 16/2011 በእንግሊዝ<br />
ኖርዝ ሀምብተን በተካሄደ የኤሌክትሪክ<br />
መኪናዎች ውድድር አዲስ ሪከርድ<br />
ያስመዘገበችው ከቆመችበት ተነስታ በሰዓት<br />
96.5 ኪሎ ሜትር እየከነፈች ውድድሩን<br />
በቀዳሚነት ያጠናቀቀችው እያንዳንዳቸው<br />
12 ቮልት የሚያመነጩ 60 የሞተር<br />
ሳይክል ባትሪዎች የተገጠሙላት በመሆኗ<br />
ነው።<br />
ለመኪና ውድድር ስፖርት<br />
ከተዘጋጁ ባትሪን ወደ ኤሌክትሪክ<br />
ኃይል ከሚለውጡ መኪናዎች ወደጃፓን<br />
የማቱሺታ ኤሌክትሪክ ኢንዱስትሪያል<br />
ካምፓና የበኦሳካ ሳንጊዩ ዩኒቨርስቲ<br />
ለውጤት ያበቃችው ‘ኦክስራይድ’ ከባትሪ<br />
ከምታገኘው ኃይል የአምሳያዎቿን<br />
የፍጥነት ወሳን የሰበረችው በሰዓት<br />
105.95 ኪ.ሜ. የመክነፍ ብቃት ተላብሳ<br />
ወደጎንና በመውጣቷ ነው።<br />
በቀጥታ ከኤሌክትሪክ ሀይል<br />
ማመንጫ የኤሌክትሪክ ሀይል የሚሞሉና<br />
ይህን ሀይል አምቀው ከሚያስቀምጡ<br />
ካፓሲተሮች ኃይል እየተመገቡ ከሚከንፉ<br />
መኪናዎች የአለም ክብረወሰን ባለቤት<br />
‹‹ፎርሙሊክ EFOL›› የተባለችው<br />
ኦቶሞቢል ነች።<br />
ፓሪስ በሚገኘው ፎርሙሊክ<br />
ካምፓኒና ከፍተኛ አድናቆትና ውደሳ<br />
የተላበሰችው ፎርሙሊክ ከብክለት<br />
የፀዳች ከመሆኗ በተጨማሪ ኃይልን<br />
በመቆጠብና በፍጥነት በመክነፍ ያላትን<br />
ብቃት በሚተነትነው መረጃ በሰዓት<br />
እስከ 260 ኪ.ሜ. ፍጥነት እያቀያየረች<br />
መጓዝ ትችላለች። ይህ ፍጥነቷ ፎርሙላ<br />
3 ከተባሉ ለመኪና ውድድር ስፖርት<br />
ከተዘጋጁ በተፈጥሮ ነዳጅ ከሚከንፉ<br />
መኪናዎች የሚቀራረብ ከመሆኑ<br />
በተጨማሪ ቀጥ ባሉ ጎዳናዎች ከበካዩቹ<br />
ኦቶሞቢሎች ጋር ለውድድር መቅረብ<br />
የምትችል ናት። አንድ ጊዜ በተሞላቸው<br />
የኤሌክትሪክ ሀይል በምትጓዝበት ጎዳና<br />
ጠመዝማዛነት ወጣ-ገባነት ላይ የተመረኮዘ<br />
ቢሆንም፣ እንደገና የኤሌክትሪክ ቻርጅ<br />
የምትሞላው ያለማቋረጥ ከተጓዘች ከአንድ<br />
እስከ አንድ ሰዓት ተኩል በሚረዝም የጊዜ<br />
ልዩነት ነው።<br />
በዓለማችን የኦቶሞቢል<br />
አምራች ድርጅቶች እየተጠናከረ በመጣው<br />
ከብክለት የፀዱ ኦቶሞቢሎች ግንባታ ገበያ<br />
የሚቀርቡ ኦቶሞቢሎች የሚመዘኑት<br />
በዋጋቸውና ኃይልን በመቆጠብ ብቃታቸው<br />
ነው።<br />
እንደዛሬው ነዳጅ በበርሜል<br />
ከ100 ዶላር በላይ ጣሪያ ነክቶ ባለሀብቶች<br />
ከተራው ሰው ጋር በአውቶቡስና በባቡር<br />
ለመሄድ ከመገደዳቸው በፊት የኦቶሞቢል<br />
ካምፓኒዎች ትኩረት ባለሀብቶችን<br />
ከተራው ሰው ለይተው በጎዳና ላይ<br />
የሚያንደላቅቁ የኦቶሞቢል ዲዛይኖችን<br />
ለገበያ ማቅረብ ነበር። ይህንን መመዘኛ<br />
በመንተራስ ከ1950ዎቹ ወዲህ ከተፈበረኩ<br />
ኦቶሞቢሎች ጣራ በነካ ዋጋ በመሸጥ<br />
እስካሁን ሪከርዱን ይዞ የዘለቀው እ.አ.አ<br />
በ1963 ቼሪስ ኢቫንስ የተባለው እንግሊዛዊ<br />
ባለሀብት በ17,275,00 ዶላር በአሁኑ<br />
የገዛት ፌራሪ 250GT የተባለች ኦቶሞቢል<br />
ናት።<br />
በተመረተ በአንድ ዓመት<br />
ውስጥ ከፍተኛ ሀብት ባስመዘገበ ከፍተኛ<br />
ሽያጭ የዓለማችን ባለሀብቶች በብዛት<br />
ቀዳሚ ሆነው የሸመቱት እ.አ.አ በ1997<br />
እያንዳንዱ በ1,547,620 ዶላር ለገበያ<br />
የቀረበው ‹‹ሜርሴዲስ ቤንዝ CLK/LM<br />
የተባለው ኦቶሞቢል ነው።<br />
ፅሁፋችንን የምንቋጨው<br />
በአብዛኛው የዓለም ህዝብ ጆሮ ያልደረሰውን<br />
ባለፈው ሳምንት ጥቅምት 20/2011 በጊነስ<br />
ቡክ አዲስ የዋጋ ሪከርድ ያስመዘገበውን<br />
ተንቀሳቃሽ የቤት ኦቶሞቢል (Luxury<br />
motorhomes) በማስተዋወቅ ነው።<br />
ባለፈው ሳምንት በኦስትሪያ<br />
ተዘጋጅቶ በከተማዋ ጎዳና በመንፈላሰስ<br />
ለዕይታ የበቃው ‹‹The eleMMent››<br />
ውድ ተንቀሳቃሽ የቤት ኦቶሞቢል<br />
ባለአምስት ኮከብ ሆቴሎች ውስጥ የሚገኙ<br />
መጠጥ ቤቶች የሚሰጡትን አገልግሎትና<br />
ውበት የተላበሰ ተንቀሳቃሽ መኪና ነው።<br />
የተደራረቡ ሁለት ጥንድ መኪናዎች<br />
የሚመስል ገፅታ በተላበሰው በላይኛው<br />
ክፍል አሥራ-ሁለት ሜትር ርዝመት ወደ<br />
ጎን ተዘረጋግቶ የሚጋጠም 30 ስኩየር<br />
ሜትር ስፋት ያለው መኖሪያ ይገኛል።<br />
ከታች ያለው መኪና ከላይ<br />
የተሸከመውን መኖሪያ ይዞና እስከ 20 ቶን<br />
ክብደት ተሸክሞ በሰአት 150 ኪሎ ሜትር<br />
የሚከንፈው 510 የፈረስ ጉልበት ባለው<br />
ሞተር ነው።<br />
ከላይ ወዳለው መኖሪያ<br />
ስትዘልቁ በዋናው መኝታ ቤት በቁሳቁስ<br />
የተሞላ የተንጣለለ አልጋና 40 ኢንች<br />
ስፋት ያለው የሳተላይት ቴሌቭዥን፣<br />
የኢንተርኔት ሞባይልና የቪዲዮ ማሳያ<br />
ዴኮችን ትመለከታላችሁ። መኝታ ቤቱን<br />
በማለፍ ወደ ውስጥ ስትዘልቁ ዘመናዊ<br />
የመታጠቢያ ገንዳ ያለው ክፍልና የመፀዳጃ<br />
ክፍሎችን ታገኛላችሁ። በታችኛው ሹፌሩ<br />
በሚቀመጥበት ክፍል የሹፌሩ ማረፊያ<br />
አልጋ የተዘረጋበት ክፍልና የእንግዳ<br />
መቀመጫ ሳሎን የያዘ ነው። ይህ ዘመናዊ<br />
ኦቶሞቢል እና ተንቀሳቃሽ መኖሪያ ግንባሩ<br />
ላይ በተለጠፈው የፀሐይ ብርሀን ወደ<br />
ኤሌክትሪክ ሀይል ከሚለውጥ መስታወት<br />
በሚያገኘው ሀይልና ነዳጅን በ20 በመቶ<br />
በሚቆጥብ ኢንጂን ነው።<br />
ይህ ብቃት ተላብሶ ለውጤት<br />
የበቃውን ኦቶሞቢል ተንቀሳቃሽ መኖሪያ<br />
ከተሸከሙ ኦቶሞቢሎች በዋጋ ውድነቱ<br />
የጊነስን ሪከርድ የሰበረው ኦቶሞቢሉን<br />
የፈበረከው ማርቺ ሞባይልስ የተባለው<br />
የኦስትሪያ ካምፓኒ የመሸጫ ዋጋው<br />
2.96 ሚሊየን ዶላር ወይም 49 ሚሊየን<br />
ሶስት መቶ ሺህ ብር መሆኑን። ወዳጁ<br />
ባለሀብቶች፣ ይወቁልኝ ማለቱን ተከትሎ<br />
ነው።<br />
ዓለማዊ ወግ...<br />
‹‹የለም፤ ስለየኔታ ሳይሆን ስላንተ<br />
ከየኔታ የሰማሁት ነገር አለ›› አለኝ።<br />
‹‹ምን?››<br />
‹‹አብዷል ብለው ስላንተ<br />
ማበድ ነገሩኝ››<br />
‹‹እኔ! እኔ አብጄ?›› ባጣም<br />
ተደናግጬ ነበር የጠየቅሁት።<br />
‹‹ኋላ እኔ ነኝ ያበድኩት!››<br />
በማለት ሲያሾፍብኝ የኔታ ታላቅ ደባ<br />
እንደሰሩብኝ አወቅሁ። ቅድም ወደ<br />
ትምህርት ስሄድና ስደርስ የተገጠመውን<br />
ግጥም አሰብኩ።<br />
ለምንት አንገለጉ አሕዛብ<br />
ወሕዝብኒ ነበቡ ከንቶ<br />
መቸ በከንቱ ነው ልባቸው<br />
ተነክቶ<br />
የኔታ አበሳጩኝ። እኔ<br />
ወደ ትምህርት ሳልደርስ በፊት እኔን<br />
ሲያሙኝ እንደነበረ ገባኝ። ተማሪዎች<br />
ደግሞ ተታለውላቸዋል። እንዴት<br />
አንድ የቅስና መምህር በቂም በቀል<br />
ተማሪውን ያማል? አስማማውን<br />
አከበርኩት። እውነትም ከቅስና በፊት<br />
ቅድስና መብለጥ አለበት።<br />
‹‹ሌላስ የነገሯችሁ ነገር<br />
አለ?›› አልኩት። ‹‹የለም፤ ሌላ እንኳ<br />
አልሰማሁም።››<br />
ደስ አለኝ። ማን ተማን<br />
ያንሳል። እኔን እንዳሙኝ እኔም<br />
ጉዳቸውን አወጣዋለሁ።<br />
ስለየኔታና ‘ኔ ሁሉንም ነገር<br />
ለአስማማው ነገርኩትና “ታዲያ ምን<br />
እንዳደርግ ትመክረኛለህ?›› አልኩት።<br />
ፈላስፋው ብዙ ጊዜ ወስዶ ሲያስብ ቆየ፤<br />
‹‹እኔ አንተን ብሆን?›› አለና አጓጓኝ።<br />
ምርጥ ሀሳብ እንዳሰበ ስለገመትኩ<br />
በትዕግስት መጠባበቅን መረጥኩ።<br />
‹‹አንድ ነገር ልንገርህ<br />
እንዳለው? ጥፋ!!! እኔም ወደዚያው ነኝ<br />
. . . እዚህ ተምረን ምን ልንፈጥር<br />
ነው? መቸም ስምንተኛው ሺህ ደርሶ<br />
ነው እንጂ መሪጌቶች ሁሉ እንዲህ<br />
ሁነው የተበለሻሹ የጤና አይመስለኝም<br />
‘ና ጥፋ!!!››<br />
‹‹ጠፍቸስ የት እሄዳለሁ?››<br />
‹‹አዲስ አበባ ሂድ፤ እኔም<br />
ወደዚያው ነኝ!››<br />
‹‹እዚያ ሄደህ በምን<br />
ትተዳደራለህ? እኔስ በምን እንድተዳደር<br />
ትመክረኛለህ?››<br />
‹‹ፈራህ እንዴ? እኔ አንዲት<br />
በምስጢር የማዘጋጃት ጉዳይ ስላለችኝ<br />
ነው እንጂ አብረን እንሄድ ነበር። ጥፋ’ና<br />
አንድ ቀን እንገናኛለን፡፡››<br />
. . .<br />
አዲስ አበባ ቁራሽ የሚለምን<br />
ሰው ‘ለማኝ’ ነው እንጂ የቆሎ ተማሪ<br />
አይደለም። እኔ ደግሞ በስደት አዲስ አበባ<br />
ገብቸ ግራ ገብቶኛል። የምሰራውም፣<br />
የምበላውም እያጣሁ እግሬ እስኪያጥር<br />
ድረስ ስዞር እውላለሁ። ከሀገሬ እያለሁ<br />
ስለ አዲስ አበባ ብዙ ሲወራ እሰማ ነበር።<br />
“የአዲስ አበባ ውኃ ምግብ ነው” ያሉትን<br />
ሰምቸ እንደመጣሁ ብዙ ውኃ ጠጣሁ።<br />
የተረፈኝ ነገር ቢኖር ግን በየደቂቃው<br />
ሽንቴን በየአጥሩ ጥግ መሽናት ነበር።<br />
መቸም የኔ መጥፊያ ሽንት<br />
ነው። ከሀገሬ የተሰደድኩት በሽንት<br />
የተነሳ ከየኔታ ጋር ተቀያይሜ ነው።<br />
አዲስ አበባ ደግሞ አንድ አጥር<br />
ጥግ እግሬን አንቧትሬ ስሸና አንድ<br />
ወጠምሻ እንደ ድመት ጋማዬን ይዞ<br />
አንጠለጠለኝ።<br />
ሁለት ወይም ሶስት ጊዜ<br />
የካልቾ ድምጽ መስማቴ ትዝ ይለኛል።<br />
ከዚያ ወዲያ እንዴት እንደመታኝ፤<br />
መቸ እንደመታኝ ሳይታወቀኝ ሰውነቴ<br />
ቆሳስሎና ደክሞ ተገኘሁ። አጥሩን<br />
ተደግፌ ለሰባት ትውልድ የሚበቃ እንባ<br />
አፈሰስኩ። አሁን እኔ ሰው ነኝ? ወይስ<br />
የካራቴ መለማመጃ ከረጢት? ማልቀሱ<br />
ሲደክመኝ ማልቀሴን ትቸ በእግሬ<br />
መጓዝ ጀመርኩ።<br />
ብዙ መንገድ በእግሬ<br />
ተጉዤ ቀና ስል የባህል ህክምና የሚል<br />
ማስታወቂያ አየሁ፡፡ በተላላኪነት እንኳ<br />
ቢቀጥሩኝ ብየ ወደዚያው አመራሁ።<br />
እንደውም ሳስበው<br />
21<br />
አስማማው በምስጢር የማዘጋጃት ጉዳይ<br />
ስላለችኝ ነው ያለው ስራ-<strong>ስር</strong> ሊለቅምና<br />
እዚህ መጥቶ አዋቂ ነኝ ሊል እንደሆነ<br />
ገምቸ ነበር። አዲስ አበባ እንደሆነች<br />
ትንሽ ግዕዝና የገጠር አማርኛ የሚችል<br />
ሁሉ የባህል መድኃኒት እና የድግምት<br />
አዋቂ የሆነባት ከተማ ናት።<br />
የባሕል ሐኪሙ ዘንድ<br />
ደንበኛ የሆኑ ብዙ ሰዎችን አገኘሁ።<br />
ከእነዚህም መካከል ዘፋኞች፣ አትሌቶች፣<br />
አርቲስቶች፣ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣<br />
የፓርላማ ተወካዮች፣ የተለያዩ<br />
ሃይማኖቶች መሪዎች፣ የጥቃቅንና<br />
አነስተኛ ንግድ ባለቤቶች ወዘተ ይገኙበት<br />
ነበር። ሌሎችን የተመለከቱ መረጃዎችን<br />
ሳምንት እንደምነግራችሁ ቃል በመግባት<br />
አሁን ግን ከአንዱ ዘፋኝ ጋር ያደረኩትን<br />
ንግግር ሳልደብቅ ላጫውታችሁ።<br />
አቋሙ ከሲታ ነው። እንደ<br />
እውነቱ ከሆነ ከዚህ ግለሰብ የሚወጣው<br />
ድምጽ ሕዝብን ያዝናናል ከማለት<br />
ይልቅ ያሳቅቃል ብሎ መገመት ያሸልም<br />
ይሆናል። ጉሮሮው ላይ ያለውን ክርክር<br />
የተመለከተ ያዝንለታል እንጂ ዘፍኖ<br />
ያዝናናኛል ብሎ ተስፋ አይጥልበትም።<br />
‹‹ምነው ‘ጓዴ! ምን እግር<br />
ጥሎህ መጣህ?›› ይህ የእኔ ጥያቄ<br />
ነበር።<br />
ሰውየው የዋዛ አልነበረም።<br />
እንደሚከተለው አማረረ፡-<br />
‹‹አንድ አይሉ ሁለት ካሴቶችን<br />
ሰርቻለሁ ግን ከአንድ ቀበሌ ገበሬ ማኅበር<br />
ሰላሳ ሰው እንኳ አልሰማኝም። ድምጤ<br />
እግዚአብሔር ይመስገነው ደህና ነው!<br />
ያለመደመጤ መንስኤ ምን እንደሆነ<br />
ስላላወቅሁት የሆነ መተት ሰርተውም<br />
ቢሆን አኒህ ቅዱስ አባታችን በቢል-<br />
ቦርድ ላይ ቁጥር አንድ እንዲያደርጉኝ<br />
ለመለመን ነው የመጣሁት። እንዴት<br />
ነው፤ የሚሳካልኝ ይመስልሃል?››<br />
በእውነቱ ይህንን ሲጠይቀኝ<br />
የምመልሰውን አጥቼ ነበር። ይሁንና<br />
ስለያሬዳዊ ዜማ ከሚያወቁት ወገን ነኝና<br />
‹‹ስለ ኢትዮጵያ ቅኝቶች፣ ማለቴ የዜማ<br />
ዓይነቶች ምን ታውቃለህ?›› አልሁት።<br />
ተረጋግቶ እየመለሰልኝ<br />
ነበር፤ ‹‹ስለዜማ ዓይነቶች በማወቅ<br />
እና በመመራመር የሚያህለኝ የለም።<br />
ከፈለግህ የተመኘኸውን ጠይቀኝ›› በማት<br />
በኩራት መለሰ።<br />
‹‹እንግዲያው እየጠየቅሁህ<br />
አይደለምን፤ ስንት የዘፈን፣ ማለቴ የዜማ<br />
አይነቶች አሉ?››<br />
‹‹አራት ናቸው›› ብሎ ሲመልስ<br />
አከበርሁት። ‹‹እስቲ ዘርዝራቸው››<br />
ይህንን የጠየቅሁት ስለ አንባሰል፣<br />
አንች ሆዬ፣ ባቲ እና ትዝታ እውቀት<br />
ስላለኝ ነበር። እርሱ መመለስ ጀመረ፡-<br />
“የኢትዮጵያ ዘፈኖች በአራት ይከፈላሉ።<br />
እነሱም የሀዘን፣ የጦርነት፣ የሥራ እና<br />
የሠርግ ተብለው ነው›› አለ፡፡ ኩም<br />
አልኩ፡፡ /ይቅርታ አሁን ስለተበሳጨሁ<br />
ሌሎችን እንዴት እንዳናገርኋቸው?<br />
መናገር አልችልም፤ ሳምንት ጠብቁኝ።/<br />
የሄድኩበት የባህል ሀኪም<br />
ዓነተ--ብዙ የሆኑ ጥያቄዎችን እየጠየቀ<br />
ሲያውጣጣኝ ቆየ። እኔ ምኔ ሞኝ? አሻፈረኝ<br />
አልሁ! የማውቀው መድኃኒት ቢኖር<br />
እንዴት እንደሚቀመም ሊያውጣጣኝ<br />
አይደል? ምንም ስላልነገርኩት ተበሳጭቶ<br />
የታሰረ ውሻ ፈትቶ ለቀቀብኝ። ሮጬ<br />
አመለጥሁ። ወዲያው ሊታከም ይመጣ<br />
ከነበረ አንድ ወጣት ጋር ግቢው ፊት<br />
ለፊት ተገናኘን።<br />
‹‹የሃኪሙ ቤት እዚህ ነው?››<br />
አለኝ ወጣቱ<br />
‹‹አዎ! ምን ፈልገህ ነው?››<br />
ወጣቱ ገልመጥመጥ ብሎ አካባቢውን<br />
ተመለከተና፣ ‹‹ፍቅር ይዞኝ . . .<br />
መስተፋቅር . . . ››<br />
‹‹ስንት ትከፍላለህ?›› አልኩት<br />
እንዲህ አይነት ትልቅ ሲሳይ ተገኝቶ<br />
ማለፍ ሞኝነት መሰለኝ።<br />
‹‹የተጠየቅሁትን እከፍላለሁ››<br />
አለ ወጣቱ ባለማመን። ‹‹እሺ አንድ ቦታ<br />
ተቀምጠን እናውራ፤ የደረሰብህን ፍቅር<br />
በደንብ አብራተህ ልትነግረኝ ይገባል።››<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ
22<br />
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሁለት ዓመት<br />
የስራ ጉዞን እንዴት ይቃኙታል?<br />
ይህ ፌዴሬሽን ብዙ ችግሮች በነበሩበት ጊዜ<br />
የመጣ ስለ ነበር ነገሮችን <strong>ስር</strong>ዓት ለማስያዝ ብዙ ስራ<br />
ሰርቷል። እግር ኳሳችን በውጤት ደረጃ ደካማ በመሆኑ<br />
የህዝቡን ፍላጎት ማሟላት አልቻለም። በዘርፉ ያሉን<br />
ባለሙያዎች በቂ አይደሉም። ባለን አቅም ስራዎችን<br />
ተከፋፍለን ለመስራት ሞክረናል።<br />
በወንዶችም ሆነ በሴቶች በዓለም አቀፍ<br />
ውድድሮች ላይ ተካፋይ ነበርን። የእውነት ነው<br />
የምልህ ሴቶቹ ላይ የቻልነውን ያህል በጣም ብዙ ስራ<br />
ሰርተናል። ያው እንደምታውቀው የሴቶች ኦሎምፒክ<br />
ቡድናችን የለንደን ኦሎምፒክን በር አንኳኩቶ<br />
በመጨረሻው ጨዋታ በደቡብ አፍሪካ በመሸነፉ ሳይገባ<br />
ተመልሷል።<br />
ሴቶች እግር ኳስ ተጨዋቾቹን ፌዴሬሽኑ ሰርቶባቸው<br />
የተገኙ ናቸው ማለት እንችላለን?<br />
ፌዴሬሽኑ ከታች ሰርቶባቸው የመጡ<br />
ባይሆኑም ከመጡ በኋላ ቀባብተን (በአግባቡ በመያዝ)<br />
እንደቀድሞው ጊዜ በሴቶች ለዓለም አቀፍ ውድድር<br />
በራችንን ሳንዘጋ ሰርተንባቸዋል። ረዥም ጊዜ አብረው<br />
እንዲቆዩ በማድረግ፣ የኪስ ገንዘብ፣ ሽልማትና<br />
የሚፈልጉትን ነገር በማሟላት ጥሩ የሚባል ውጤት<br />
ላይ ደርሰዋል። ብዙ ብር ስላፈሰስንባቸው አንፀፀትም።<br />
ምክንያቱም ልጆቹን ክለቦች እየያዟቸው ነው።<br />
በ2004 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተሳታፊ<br />
ቡድኖች የሴት ቡድን መያዝ የግድ እንዳለባቸው<br />
ስትገልፁ ቆይታችሁ ሀሳባችሁን በመቀየር ወደ 2005<br />
ዓ.ም. አምጥታችሁታል። ምክንያታችሁ ምንድን<br />
ነው?<br />
ወደ 2005 ዓ.ም. የተገፋው አንዳንድ<br />
ቡድኖች የመዘጋጃ ጊዜ እንዲኖራቸው ተብሎ ነው።<br />
በዚህ ዓመት በሁለተኛ ወር፣ በአራተኛ ወር ወይም<br />
በአንዱ ወር ቡድን ሊያቋቁሙ ይችላሉ። ይህን<br />
የሚቆጣጠር አካል አለ። በአፍሪካ ሻምፒዮንስ ሊግ<br />
እና ኮንፌዴሬሽን ካፕ ላይ የሚካፈሉ ሁለት ክለቦች<br />
የሴት እና የታዳጊ ቡድን ከሌላቸው በጭራሽ መወዳደር<br />
አይችሉም ተብሏል፤ በካፍ።<br />
እውን ይህ አስገዳጅ ህግ ነው?<br />
በአዲስ አበባ በተካሄደው በ‘Win in Africa<br />
with Africa’ የክለብ አመራሮች ስልጠና ላይ ክለቦች<br />
በ2004 የሴት ቡድን ለማቋቋም ውሳኔ ላይ ደርሰው<br />
ነበር።<br />
ክለቦች ‹‹በዚህ ዓ.ም. የሴት ቡድን ይኖረኛል›› ብለው<br />
ቃል ሊገቡ ይችላሉ። የእኔ ጥያቄ ህጉ አስገዳጅ<br />
ነወይ ነው? እንደዚያ ከሆነ የእንግሊዙ ታላቅ ክለብ<br />
ማን.ዩናይትድን ጨምሮ ያሉ የሴት ቡድን የሌላቸው<br />
ክለቦች ሊታገዱ ነው ማለት ነው?<br />
ማን.ዩናይትድ የሴት ቡድን እንደሌለው<br />
እርግጠኛ ነህ?<br />
በጣም፤ የለውም።<br />
እኔ መረጃው የለኝም። እንዲኖራችሁ ስለተባለ<br />
የተወሰኑ ክለቦች የሴት ቡድን አቋቁመዋል። የተወሰኑ<br />
ክለቦች ደግሞ ‹‹ለከርሞ እንጂ ለዘንድሮ አናዘጋጅም››<br />
ብለዋል። እንደዚህ እየተባለ ከተሄደ በሚቀጥለው<br />
ዓመትም ዋስትና አይሰጥም። በተለየ ይህን ሁኔታ<br />
የሚከታተለው የሊግ ኮሚቴ ነው። እነሱን ብትጠይቅ<br />
የተሻለ መልስ ይሰጡሀል።<br />
2005 ዓ.ም. መጨረሻ የስራ ጊዜያችሁ ስለሚያበቃ<br />
‹‹የሴት ቡድን አቋቁመው ወጡ›› መባልን<br />
ስለምትፈልጉ ገደብ ያላችሁትን እንዳዘዋወራችሁት<br />
የሚናገሩ አሉ። ይስማማሉ?<br />
አንድ ስራ ስትሰራ ግላዊ ሳይሆን ተቋማዊ<br />
በሆነ መልኩ ሊሆን ይገባል። እኔ የጀመርኩትን<br />
ሁሉ ጨርሼ ሄዳለሁ ማለት አይደለም። ሳንሰራው<br />
ለሌላው አስተላልፈን ለመሄድ ብቻም አንሰራም። ብዙ<br />
የሰራናቸው፣ ብዙ የቀሩ ነገሮች አሉ። የቻልነውን<br />
ያህል እንሰራለን።<br />
የአፍሪካ ሴቶች ሻምፒዮና ቅድመ ማጣሪያ በጥር ወር<br />
የመጀመሪያ ሳምንት ይደረጋል። ኢትዮጵያ ከግብፅ<br />
መመደቧ ይታወቃል። ዝግጅት መቼ ለመጀመር<br />
አሰባችሁ? [ወ/ሮ ጥሩወርቅ የብ/ቡድኑ የቡድን መሪ<br />
ናቸው።]<br />
የጠቅላላ ጉባዔ ስብሰባ በተደረገበት ወቅት<br />
ትኩረት ተሰጥቶት የተወያየነው በብሔራዊ ቡድን<br />
ላይ ነው። በግልፅ መስተካከል ያለባቸው ነገሮች<br />
ተቀምጠዋል። ‹‹የብሔራዊ ቡድን መተዳደሪያ<br />
መመሪያ›› ወጥቷል። ይህ ከፀደቀ በኋላ ብ/ቡድን ለስንት<br />
ቀን ልምምድ መስራት እንዳለበት ስለሚገልፅ በዚያ<br />
መሰረት እንወስናለን። እርግጠኛ ባልሆንም ታህሳስ<br />
ውስጥ ልጆቹ ተሰባስበው ልምምድ ይጀምራሉ ብዬ<br />
ገምታለሁ። ከዚያ በፊት ውድድሮች ይኖራቸዋል።<br />
የሴቶች ውድድር በእርግጠኝነት የሚጀመርበት ቀን<br />
ይታወቃል?<br />
ይህን የሚወስነው ሊግ ኮሚቴው ነው። ልጆቹ<br />
በአሁን ሰዓት በየክለባቸው ልምምድ ላይ ናቸው።<br />
[የኢትዮጵያ እና ግብፅ አሸናፊ በሰኔ ወር መጀመሪያ<br />
ከናሚቢያ እና ታንዛኒያ አሸናፊ ጋር የመጀመሪያ ዙር<br />
የማጣሪያ ጨዋታ ታደርጋለች።]<br />
ከቀድሞው ፌዴሬሽን በተለየ የሰራችሁት ነገር እንደሌለ<br />
ለመረጃ ቅርብ ይሁኑ<br />
ስ ፖ ር ት<br />
አቤል ዓለማየሁ<br />
የሚገልፁ አሉ። በሁለት ዓመት የስራ ጊዜያችሁ<br />
በዋናነት ‹‹ሰርተነዋል›› የምትሉት ተጨባጭ ነገር<br />
ምንድን ነው?<br />
የእግር ኳስ ችግራችንን በአንድ የስራ ዘመን<br />
(term) እንፈታዋለን ማለት አይቻልም። ቢያንስ<br />
የቢሮውን አደረጃጀት መለወጥ አለብን። እኛ ስንመጣ<br />
በጣም ጥቂት የነበረው የፅ/ቤት ሠራተኞች ቁጥር<br />
ከማደጉም በላይ ቢሮው በብቃት እየተደራጀ ነው።<br />
ራሱን የቻለ ቢሮ ያለው የዳኞች ኮሚቴ አልነበረንም፤<br />
አሁን ኖሮናል። ፊፋ ይህን አይቶ ‹‹በብዙ አፍሪካ<br />
አገሮች የሌለ ነው›› በማለት መሻሻላችንን አድንቋል።<br />
የቴክኒክ ዳይሬክተር ባይኖረንም በቴክኒክ<br />
ክፍል ውስጥ ብቁ ባለሙያዎችን ቀጥረናል። ስራዎችን<br />
በየዘርፉ በመስጠታችን ለክተን እንደሰጠነው፣ ለክተን<br />
መቀበል እንችላለን። ጉድለቶች ቢኖሩም እነዚህን<br />
እንደ ትልቅ እድገት አያቸዋለሁ።<br />
የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው በእግር ኳሱ ላይ<br />
በታሪክ የሚታወስ ስራ አከናውኖ የሚያልፍ<br />
ይመስልዎታል?<br />
ይህንን ካላደረግንማ መምጣትም<br />
አልነበረብንም። ወደ ፌዴሬሽኑ ስመጣ ብዙ ነገር<br />
ፈታለሁ ብዬ ሳይሆን ቢያንስ የተሻለ ነገር ከውናለሁ<br />
በሚል ነው። ይህ ክፍል [ቆይታ ያደረግንበት<br />
የፌዴሬሽኑ የዳኞች ኮሚቴ ቢሮ] በመኖሩ የዳኞችን<br />
የፋይል አደረጃጀት ችግር ፈትቼ አልፋለሁ። ‹‹ዳኛው<br />
ማን ነው? ምን ሰርቷል?›› የሚለውን መረጃ<br />
ከሰበሰብን ማንም መጥቶ ስለ ዳኛው በቂ ነገር ማግኘት<br />
ይችላል።<br />
የዳኞችን ሙሉ መረጃ የሚይዝ ፋይል<br />
ማደራጀታችሁ ጥሩ ስራ ቢሆንም በዳኞች ላይ ስራ<br />
ለመሰራቱ ዋና ማሳያ ይሆናል ብዬ አላምንም።<br />
መለኪያው የዳኞቹ ብቃት እንዲዳብር ምን ተሰራ<br />
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />
‹‹ፌዴሬሽኑ ውስጥ የምሰራው<br />
ተመችቶኝ አይደለም››<br />
ወ/ሮ ጥሩወርቅ ብርሃኑ<br />
[የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን - የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል]<br />
ስለ ፌዴሬሽኑ ሁለት የስራ ዓመታት፣ በዳኝነት ዙሪያ ስለሚታዩ ችግሮችና በሴቶች እግር ኳስ ዙሪያ የሚነሱ ጉዳዮችን<br />
አስመልክቶ አቤል ዓለማየሁ ላቀረበላቸው ጥያቄዎች የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል<br />
እና የዳኞች ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት ወ/ሮ ጥሩወርቅ ብርሃኑ ግልፅነት የተሞላው ምላሽ ሰጥተዋል።<br />
አንድ ስራ ስትሰራ ግላዊ ሳይሆን ተቋማዊ በሆነ መልኩ ሊሆን<br />
ይገባል። እኔ የጀመርኩትን ሁሉ ጨርሼ ሄዳለሁ ማለት አይደለም።<br />
ሳንሰራው ለሌላው አስተላልፈን ለመሄድ ብቻም አንሰራም። ብዙ<br />
የሰራናቸው፣ ብዙ የቀሩ ነገሮች አሉ።<br />
የሚለው ነው።<br />
ለምሳሌ ኢንተርናሽናል አርቢትር ባምላክ<br />
ተሰማ ጥሩ ዳኛችን ነው እንበል። ዛሬ ሲያጫውት<br />
ምንም ገላጭ ሰነድ ከሌለው በቀጣይ በአመራርነት<br />
የሚመጣ ሰው ስለ እሱ በ<strong>አገር</strong>ም ሆነ በውጪ <strong>አገር</strong><br />
ስላጫወታቸው ጨዋታዎችና ሌሎች መረጃዎች<br />
ሊኖሩት አይችሉም። ታዲያ እንዴት የፋይል<br />
አደረጃጀት ዘዴ አያስፈልግም?<br />
ፋይል መደራጀቱንማ አከብራለሁ። ልል<br />
የፈለግኩት የተሻለ ለመሰራቱ ማሳያው የባምላክ<br />
የዳኝነት ብቃት መጎልበት እንጂ የፋይሉ መደራጀት<br />
አይደለም ለማለት ነው።<br />
ያነሳሁልህ እንደ ምሳሌ ነው። እንደ ተቋም<br />
መስራት ያለብን ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ ነገሮች<br />
ላይ ነው። ጨዋታን መሸከም የሚችል ብቃት<br />
ያለው ዳኛ በቁጥርም፣ በጥራትም ሳናወጣ በዘርፉ<br />
ለመስራታችን ማሳያ እንደማይሆን እናውቀዋለን።<br />
የፋይል አደረጃጀቱ ግን ስራ ለመሰራቱ አንዱ ማሳያ<br />
ሊሆን ይገባል።<br />
መስከረም 26 እና 27/ 2004 ዓ.ም. በግዮን<br />
ሆቴል በተደረገው የፌዴሬሽኑ የጠቅላላ ጉባዔ<br />
ስብሰባ ላይ ከእርስዎ በ2012 ኢንተርናሽናል ዳኞች<br />
እንደማይኖሩን ሲገለፅ ምናልባት ከንግግር ስህተት<br />
ይሁን ከእኛ የአረዳድ ችግር ባላውቅም በተለያዩ<br />
መገናኛ ብዙሐን ላይ ይሄው መረጃ ተላለፈ።<br />
[ሳምንት እኔም ከጉባዔው በላይ ማንን ልመን ብዬ<br />
ይሄንኑ መረጃ ገልጬ ነበር] ትንሽ የተዛባ ነገር<br />
ያለ መሰለኝ። የሚታወቅበት ጊዜ ገና በመሆኑ<br />
ኢንተርናሽናል ዳኛ ሆነው የሚቀጥሉ እንደሚኖሩ<br />
እየሰማሁ ነው።<br />
አንዳንድ ጊዜ ነገሮች ብድግ ይሉና በጣም<br />
ተጋነው ቀርበው፣ ሰዎችን ወደ ስህተት ይመራሉ።<br />
ካሉን 18 ኢንተርናሽናል ዳኞች ውስጥ [12 ወንድ<br />
እና 6 ሴት] አንዷ ሴት ረዳት ዳኛ እና ሦስት ወንድ<br />
ዋና ዳኞች በአካል ብቃት ፈተና ወድቀዋል። የወደቁት<br />
ማላዊ ለድጋሚ ፈተና ከኪሳቸው ገንዘብ አውጥተው<br />
ሄደው በድጋሚ ወድቀው መጡ። ይህ ማለት ካሉን<br />
ኢንተርናሽናል ዳኞች ውስጥ ቁጥራቸው ያንሳል<br />
እንጂ ምንም ኢንተርናሽናል ዳኛ የለንም ማለት<br />
ከእውነት መራቅ ነው። ካፍ ይቀበለው/አይቀበለው<br />
ባናውቅም 13 ኢንተርናሽናል ዳኖች [4 ዋና እና 9<br />
ረዳት] በ2012ም ሊኖረን ይችላል። በወጡት ቦታም<br />
ሌሎችን እንዲቀበሏቸው ጠይቀናል።<br />
ኢንተርናሽናል ባጅ ያገኙት ዳኞችም ቢሆኑ የውጪ<br />
ጨዋታዎች እንዲያጫውቱ ያን ያህል ሲጠሩ<br />
አይታይም። ትክክል ነው?<br />
በእኛ 2001 ዓ.ም. አንድ ወይም ሁለት<br />
ጨዋታ ብቻ ነው የተጠሩት፣ 2002 ላይ ትንሽ<br />
የተሻለ ነበር። 2003 በጣም የተሻለ ነበር፤ ከሴካፋ<br />
እስከ አፍሪካ ታላላቅ ውድድሮች አጫውተዋል።<br />
አንዳንድ ዳኞች ደግሞ ባጁን ይዘው አንድ ጨዋታ<br />
ሳይዳኙ የሚወርዱ አሉ።<br />
ባጁ የተሰጣቸው ብቁ ናቸው ተብለው ነውና ባጁን<br />
ከማግኘት ባለፈ ተመድበው እንዲሰሩ ከካፍ ጋር<br />
ግንኙነት ታደርጋላችሁ?<br />
በዚህ ረገድ የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ<br />
ሳህሉ ገ/ወልድ እንቅስቃሴ በጣም ብዙ ነው። በካፍ<br />
ስብሰባዎች ላይ ሲገኝ እና ኮሚሽነር ሆኖ በሄደበት<br />
ሁሉ የካፍ ሰዎችን ሲያገኝ የእኛ ዳኞች እንዲመደቡ<br />
ጥያቄዎችን ያቀርባል። እንደሚመደቡ ቃል እየገቡልን<br />
ነው። እንዲበረቱ እና የአካል ብቃታቸውን እንዲያሻሽሉ<br />
ይነግሩናል። ሊዲያ እና ትርሃስ በቅርቡ የመላው አፍሪካ<br />
ጨዋታዎችን ላይ መርተው መጥተዋል። በቅርቡም<br />
አራት ሴት ዳኞች ተመድበዋል። ወንዶቹም በቅርቡ<br />
ወጥተው እንዲያጫውቱ ጥሪ መጥቶላቸዋል።<br />
ሜዳ ላይ በግልፅ ብዙ ዳኞች ተሯሩጦ ማጫወት<br />
የሚያስችል የአካል ብቃት ችግር እንዳለባቸው<br />
እየታየ ነው። የፊሽካ ድምጾች በርቀት እየተሰሙ<br />
ነው። ችግሮቹን ለመቅረፍ ምን እያሰባችሁ ነው?<br />
ችግሩ መኖሩንስ ታምናላችሁ?<br />
እሱማ ታየ። ዳኞች ተፈትነው ሲወድቁብህ<br />
ችግሩ መኖሩን ትረዳለህ። ችግሩን ለመፍታት<br />
እንደ ዳኞች ኮሚቴ ማድረግ ያለብን የአካል ብቃት<br />
አሰልጣኞችን መጨመር ነው። በካፍ ሁለት<br />
አሰልጣኞች (ቸርነት አሰፋ እና ኃይለመላክ ተሰማ)<br />
ሰልጥነው መጥተዋል።<br />
ክልል ላይ ተፈትነው የሚመጡ ዳኞች ፈተና<br />
ምናልባት አጥጋቢ ላይሆን ስለሚችል ወደ ውድድር<br />
ከማስገባታችን በፊት እንፈትናቸዋለን። ይህን ፈተና<br />
ማለፍ ካልቻለ አይዳኝም። በዓመት በፊት አንድ የአካል<br />
ብቃት ፈተና ያለፈ ዳኛ ዓመቱን ሙሉ ይዳኝ ነበር።<br />
አሁን ግን ፈተናውን በዓመት አራት ጊዜ እያደረግን
አውራምባ ታይምስ 4ኛ ዓመት ቁጥር 191 ቅዳሜ ጥቅምት 18/ 2004<br />
}SdeK¨< Ÿ}c\ ð×” ¾h¨` ¨