Neger Ethiopia Issue 2
Neger Ethiopia Issue 2
Neger Ethiopia Issue 2
You also want an ePaper? Increase the reach of your titles
YUMPU automatically turns print PDFs into web optimized ePapers that Google loves.
1 የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2 ነገረ-ኢትዮጵያ<br />
ነገረ-ኢትዮጵያ<br />
ስለ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊያን እንናገራለን!<br />
ቅፅ 1 ቁጥር 2 አርብ የካቲት 7 2006 ዓ.ም. ዋጋ 8.00<br />
ማርቆስ ሀጎሶች እና<br />
ዳሮ ነጋሾች ዛሬም<br />
ያስፈልጉናል!<br />
‹‹መንግስት›› አሳልፎ<br />
የሰጠው ሉዓላዊነት<br />
12 5<br />
መሬት<br />
ያስቆረሱት<br />
የመለስና<br />
ተከታዮቹ እኩይ<br />
ስምምነቶች<br />
7<br />
ውህደት ወይስ ትብብር?<br />
3<br />
ውህደት በተናጠል በውጠ-ፓርቲ ትግል ፈተና ውስጥ የገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎች መሪዎች ከቀውስ ማምለጫ ወይም አጀንዳ<br />
ማስቀየሻ ሊሆን አይገባም፡፡ በተጨማሪም አንድ ፓርቲ ከገጠመው የገንዘብ እጥረት አሊያም የቢሮ ኪራይ ችግር ለመውጣት<br />
ዘው ብሎ የሚገባበት ጉዳይ መሆን አይኖርበትም፡፡ በሩጫ የሚደረግ ውህደት ውጤቱ ...<br />
ሰማያዊ ፓርቲ ‹የካቲት 12›ን በሰማዕታቱ<br />
ሐውልት በመገኘት ሊዘክር ነው<br />
አዲስ አበባ:- ሰማያዊ ፓርቲ<br />
በዳግም የጣሊያን ወረራ ወቅት<br />
በፋሽስት ግራዚያኒ ትዕዛዝ<br />
በአዲስ አበባ ብቻ ከ30,000 በላይ<br />
ንጹሃን በግፍ የተጨፈጨፉበትን<br />
የየካቲት 12 ሰማዕታት ቀን<br />
በተለያዩ ፕሮግራሞች ሊዘክር<br />
መሆኑን አስታወቀ፡፡<br />
የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት<br />
ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ተክለያሬድ<br />
እንዳስታወቁት፣ ሰማያዊ ፓርቲ<br />
የየካቲት 12 ሰማዕታት ቀንን<br />
ምክንያት በማድረግ በጽ/ቤቱ<br />
የፓናል ውይይት ያካሂዳል፤<br />
በተጨማሪም ስድስት ኪሎ<br />
በሚገኘው የሰማዕታት መታሰቢያ<br />
ሐውልት በዕለቱ በመገኘት<br />
ሰማዕታቱን የመዘከርና የአበባ<br />
ጉንጉን የማስቀመጥ ስነ-ስርዓት<br />
ያከናውናል፡፡<br />
እንደ አቶ ብርሃኑ ገለጻ፣<br />
ፓርቲው ፕሮግራሞችን<br />
ያዘጋጀበት ዋና ዓላማ ሰማዕታቱ<br />
የተሰውት ለሀገር አንድነትና<br />
ሉዓላዊነት ሲሉ ከመሆኑ ጋር<br />
በተገናኘ ሰማዕትነታቸውን<br />
ለትውልድ ለማስተላለፍ ነው፡፡<br />
ቀኑ በአብዛኛው በጥንታዊት<br />
ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች<br />
ብቻ የተወሰነ እየሆነ መምጣቱን<br />
ያወሱት አቶ ብርሃኑ፣<br />
የሰማዕታት ቀን በመላው ህዝብ<br />
ዘንድ የሚታወስ ታላቅ ቀን<br />
ወደ ገፅ 6 ይዞራል<br />
በጎንደር በተካሄደው ሰልፍ የተሳተፉ ወከባ<br />
እየደረሰባቸው መሆኑን አስታወቁ<br />
ሰማያዊ ፓርቲ ጥር 25 ቀን 2006<br />
ዓ.ም ‹የኢትዮጵያ መንግስት መሬት<br />
በድብቅ ለሱዳን አሳልፎ ለመስጠት<br />
እየተዘጋጀ መሆኑን› ተከትሎ<br />
የጠራውን ሰላማዊ የተቃውሞ<br />
ሰልፍ ያስተባበሩና በሰልፉ የተሳተፉ<br />
ወጣቶች ከሰልፉ በኋላም በደህንነት<br />
አካላት ወከባ እየደረሰባቸው መሆኑን<br />
ለነገረ-ኢትዮጵያ አስታውቀዋል፡፡<br />
በሰልፉ ወቅት ህዝብ ወደ ሰልፉ<br />
እንዳይቀላቀል ከመከልከል ባለፈ ፎቶ<br />
ግራፍ በማንሳትና ክትትል በማድረግ<br />
ሲያስፈራሩ የዋሉት የደህንነት አባላት<br />
ሰልፉ ከተጠናቀቀ በኋላ የተሳታፊ<br />
ወጣቶችን የቀበሌ መታወቂያ<br />
የቀሟቸው ሲሆን ወጣቶቹ ጥር<br />
26 መታወቂያቸውን ለመቀበል<br />
ወደ ቀበሌ ባቀኑበት ወቅትም<br />
በድጋሚ በመንግስት ላይ የተጠራ<br />
ሰልፍ እንዳይሳተፉ ማስፈራሪያ<br />
እንደደረሰባቸው ገልጸዋል፡፡<br />
በተመሳሳይ በጎንደር ሰልፉን<br />
ወደ ገፅ 6 ይዞራል<br />
መመረጥ በሌላው<br />
ድክመት<br />
ኢህአዴግ ተሸንፏል!<br />
(የጉዞ ማስታወሻ)<br />
13<br />
ሳይሆን በራስ ጥንካሬ<br />
16
ነገረ-ኢትዮጵያ ቅፅ 1 ቁጥር 2 የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. 2<br />
ርዕሰ አንቀጽ<br />
ስለ ሀገርና ወገን የሚታገሉትን ማዋከቡ ይቁም!<br />
ከዚህ በፊት በተለያዩ ጊዜያት ለሀገርና ለወገን<br />
ተቆርቁረው ጥቅማችንን ለማስጠበቅና<br />
ድምጻችንን ለማሰማት በተነሱ ወገኖች ላይ<br />
ከመንግስት የተሰጠው ምላሽ ያልተጠበቀ<br />
እንደነበርና ይህንንም በተለያዬ ጊዜ ብዙዎች<br />
በአገኙት አጋጣሚ ሁሉ መግለጻቸው ይታወቃል፡፡<br />
በእርግጥም በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያገባኛል ብሎ የመሰለውንና<br />
ለሀገር ይጠቅማል ያለውን አቋም በአደባባይ በሚገልጽ<br />
ማንኛውም አካል ላይ የተወሰደው እና እየተወሰደ ያለው<br />
እርምጃ አደናጋሪም አሳፋሪም ነበር፤ ነውም፡፡<br />
ለአብነትም ሰማያዊ ፓርቲ በ2005 ዓ.ም ጣሊያኖች<br />
በወገኖቻችን ላይ ከፍተኛ በደል የፈጸመውን ሮዶልፍ<br />
ግራዚያኒ በትውልድ ከተማው ‹የጀግና› ሐውልት በማቆም<br />
ዕውቅና መስጠታቸውን በመቃወም ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ<br />
በአዲስ አበባ መጥራቱ የሚታወስ ነው፡፡ ሆኖም ግን መንግስት<br />
ከፋሽስቱ ግራዚያኒ ታሪክ ጎን የቆመ በሚያስመስለው መልኩ<br />
ለተቃውሞ ሰልፍ የወጡትን ሰዎች ለቃቅሞ አስሯቸው ነበር፡<br />
፡ ድብደባና እንግልትም አድርሶባቸዋል፡፡<br />
እንዲሁ በሌላ ጊዜ የሳውዲ አረቢያ መንግስት እንጀራ<br />
ፍለጋ ከሀገራቸው የተሰደዱትን ኢትዮጵያዊያን በአስቸኳይ<br />
ሳውዲን ለቀው እንዲወጡ ማድረጉንና ሂደቱም ሰብዓዊነት<br />
በጎደለው ሁኔታ መከናወኑን በመቃወም በዚህ በሀገር ቤት<br />
ስለ ወገኖቻቸው እንግልት ጥብቅና በመቆም ተቃውሞ ባሰሙ<br />
የሰማያዊ ፓርቲ አባላት እና መላ ሀገርና ወገንን ብለው ሰልፍ<br />
የወጡ ዜጎቻችንን በአዲስ አበባ የሳወዲ ኤምባሲ አካባቢ<br />
መንግስት የወሰደባቸው የድብደባና የእንግልት እርምጃ<br />
የሚያሳፍር ሆኖ አልፏል፡፡<br />
ይህም ብቻ ሳይሆን አንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ<br />
(አንድነት) የሚሊዮኖች ድምጽ ለፍትህና ለነጻነት በሚል<br />
መርህ ፀረ-ሽብር ህጉ አፋኝና የማጥቂያ መሳሪያ ነው፣<br />
ስለዚህም መሻሻል አሊያም መሰረዝ ይገባዋል ብሎ የድጋፍ<br />
ፊርማ በሚያሰባስብበት ወቅት በአባላቱ ላይ የተለያዩ<br />
እንግልቶች ሲፈጸምባቸው እንደነበር በተደጋጋሚ ገልጾዋል፡፡<br />
በተጨማሪም የፖለቲካ እና የህሊና እስረኞች ይፈቱ ብለው<br />
በተለያየ መልኩ ህጋዊና ሰላማዊ ጥያቄ ባነሱና ለዚህም<br />
ተግባራዊነት በተንቀሳቀሱ ሀገርና ወገን ወዳዶች ላይ<br />
የሚደርሰው ጫና አሌ የማይባል ነው፡፡<br />
ይህ ሁሉ እንዳለ ሆኖ ደግሞ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ሰማያዊ<br />
ፓርቲ የኢትዮ-ሱዳን የድንበር መሬትን አስመልክቶ ያለው<br />
የመንግስት አካሄድ ግልጽና ተጠያቂነት የሰፈነበት መሆን<br />
እንደሚገባውና ሂደቱንም ዜጎች በየጊዜው እንዲያውቁ<br />
እንዲህም ተብሏል<br />
‹‹መኳንንቶች ሲሻሩ ህዝብ ይሆናሉ፡፡››<br />
አለቃ ዘነብ፣ የዳግማዊ አጼ ቴዎድሮስ ጸሐፊ ትዕዛዝ፤<br />
‹‹ሀገር የጋራ ነው፤ ሀይማኖት የግል ነው፡፡››<br />
ቀዳማዊ አጼ ኃ/ስላሴ፤<br />
መደረግ እንዳለበት በተለያየ መንገድ መጠየቁን ተከትሎ፣<br />
በአባላቱ ላይ ሰፊ የእመቃና የእስር ዘመቻ ተክፍቶባቸው<br />
አይተናል፡፡ ፓርቲው የድንበር መሬቱን ጉዳይ አስመልክቶ<br />
በጎንደር ከተማ ባካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ በተሳተፉ<br />
ሀገር ወዳድ ዜጎችና በፓርቲው አባላት ላይ የተወሰደው<br />
የማሳደድ እርምጃ ዛሬም እንደትናንቱ አሳፋሪነቱ ጎልቶ<br />
ታይቷል፡፡ ገና ሰልፉን በተመለከተ ለከተማዋ ህዝብ የቅስቀሳ<br />
ስራ በወጡ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎቹ ላይ የተጀመረው<br />
ግልጽ የማደናቀፍ ስራ እስከ ሰልፉ ማጠናቀቂያ ቀን ድረስ<br />
የቀጠለ እንደነበር ለመመልከት ችለናል፡፡<br />
ማንም ሰው በቀላሉ ሊረዳው እንደሚችለው በሰላማዊ<br />
የተቃውሞ ሰልፉ ላይ የተነሳው ጉዳይ የሀገር ጉዳይ ነው፡፡<br />
ቢሆን ቢሆን በሀገር ጉዳይ ላይ የፖለቲካ ልዩነታችን ተወግዶ<br />
ወይም ለጊዜው ልዩነቱን ወደ ጎን ገፍተን በአንድነት ብንቆም<br />
እሰየው ነበር፡፡ በዚህም የኢህአዴግ አባላትና ደጋፊዎቻቸው<br />
ሳይቀር በበላይ አለቃዎቻቸው ዘንድ በስውር እየተካሄደ<br />
ነው ስለሚባለው የሀገርን ጥቅም አሳልፎ የመስጠት እኩይ<br />
ተግባር ላይ ግልጽነት እንዲፈጠርና የህዝብ ይሁንታን በተጋፋ<br />
መልኩ እንዳይካሄድ ለመጠየቅ ሰማያዊ ፓርቲ የተጠራውን<br />
የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ በተቀላቀሉ ነበር፡፡<br />
ይህ ካልሆነ ግን ስለሀገር ብለው ድምጻቸውን ከፍ አድርገው<br />
በሚያሰሙ ሰላማዊ ኢትዮጵያዊያን ላይ ያልተገባና ህገ-ወጥ<br />
ተግባር መፈጸምና ከመሬት ቆራሾች ጋር ማበር አሊያም<br />
በዝምታ ማለፍ ነገ በህግ ዛሬ በህሊና ከመጠየቅ እንደማያድን<br />
ልብ ማለት ይገባል፡፡<br />
ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ የማካሄድም ሆነ በተደራጀ<br />
መልኩ የተለያዩ ጥያቄዎችን የማሰማት እንዲሁም ሀሳብን<br />
በነጻነት የማራመድ መብት በህገ-መንግስቱ ተደንግጎ እያለ<br />
በማናለብኝነት ህግን ጥሶ ዜጎችን ማንገላታት ከመንግስት<br />
ማናቸውም አካላት ፈጽሞ የማይጠበቅ ድርጊት መሆኑን<br />
ደጋግመን ማስታወስ እንወዳለን፡፡ አሁን መንግስት የማዋከብና<br />
የማሳደድ እርምጃ እየወሰደባቸው ያሉ አያሌ ኢትዮጵያዊያን<br />
እያነሷቸው ያሉት ጉዳዮች ተራ የፖለቲካ ፍጆታ ከማጋበስ<br />
ጋር የማይገናኙ፣ በአንጻሩ ግን የሀገርና የህዝብ ተቆርቋሪነትን<br />
የሚያሳዩ እንቅስቃሴዎች እንደሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ስለ ሀገርና<br />
ወገን የሚታገሉትን መሸለም እንጂ ማዋከብ የማይገባና<br />
ኢ-ዴሞክራሲያዊነት ነው፡፡<br />
በእርግጥም ከህዝብና ከሀገር ጥቅም ጋር ተጋጭቶ ዜጎችን<br />
ማሳደድ አምባገነንነትና ግዴለሽነት ነው፡፡ ስለሆነም እንዲህ<br />
አይነቱ የመንግስት አካሄድ ሀገር ያለ ተቆርቋሪና ሃይ ባይ<br />
እንድትቀርና ዜጎች በሀገራቸው እና በወገኖቻቸው ላይ<br />
በሚደርስ ማናቸውም አይነት ጥቃት ግዴለሽ እንዲሆኑ<br />
የሚገፋ ኃላፊነት የጎደለው ድርጊት በመሆኑ በአስቸኳይ<br />
ሊቆም ይገባዋል እንላለን፡፡<br />
‹‹ከጠላትህ ጋር ሰላም ለመፍጠር ከፈለክ፣ ከጠላትህ ጋር መስራት ይኖርብሃል፤ ይህንን ጊዜ አጋርህ ይሆናል፡፡››<br />
ኔልሰን ማንዴላ፤<br />
‹‹ከትልቅ ወይም ከትንሽ መወለድ ሙያ አይደለም፤ ራስን ለታላቅ ታሪክ መውለድ ግን ሙያ ነው፡፡››<br />
ዳግማዊ አጤ ምኒልክ (እምዬ)፤<br />
‹‹እኛ ኢትዮጵያዊያን ሁለት ቃል አንወድም፡፡ ለወዳጅነት የፈለጉኝን እፈልጋቸዋለሁ፤ እንዲያቃልሉኝ ግን ፈጽሞ አልፈቅድም፡<br />
፡››<br />
ሻምበል አብዲሳ አጋ፣ ስመጥር አርበኛ፤<br />
አንደኛ ዓመት ቅጽ 1. ቁጥር 2<br />
ነገረ-ኢትዮጵያ ጋዜጣ ጥር 2006 ዓ.ም<br />
ተመሰረተች፡፡ ነገረ-ኢትዮጵያ በሰማያዊ<br />
ፓርቲ አሳታሚነት የምትታተም<br />
ፖለቲካዊ፣ ወቅታዊ፣ ማህበራዊና<br />
ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን የምትዳስስ<br />
በየሳምንቱ አርብ የምትወጣ ጋዜጣ ናት፡፡<br />
ጋዜጣዋ ሚዛናዊና ነጻ ሆና የማገልገል<br />
መርህ አላት፤ ማንኛውም ሀሳብ በነጻነት<br />
የሚስተናገድባትና የሚንሸራሸርባት<br />
እንድትሆን እንፈልጋለን፡፡ ገዥው<br />
ፓርቲም ቢሆን አቋሙንና ፖሊሲውን<br />
ለመግለጽ ቢፈልግ የሰፊ ሚዲያ ባለቤት<br />
ነው ብለን ዕድሉን አንነፍገውም፤ በራችን<br />
ለሁሉም ክፍት ነው፡፡<br />
የአሳታሚ አድራሻ:- የካ ክ/ከተማ ቀበሌ 09/10<br />
ቤት ቁ.460<br />
E-mail:- info@semayawiparty.org<br />
P.O.Box: 180298<br />
ዋና አዘጋጅ<br />
ጌታቸው ሺፈራው<br />
የካ ክ/ከተማ ቀበሌ 01/02<br />
ቤት ቁ. 07/859/14<br />
E-mail:-gecholink@gmail.com<br />
ስልክ ቁጥር:- 09-10-45-99-32<br />
ምክትል ዋና አዘጋጅ<br />
በላይ ማናዬ<br />
የካ ክ/ከተማ ቀበሌ 01/02<br />
ቤት ቁ.099<br />
E-mail:- belaymb@gmail.com<br />
ስልክ ቁጥር:-09-20-19-09-72<br />
አምደኞች<br />
ፕ/ር አለማየሁ ገ/ማርያም<br />
ታዴዎስ ታንቱ<br />
ታምራት ታረቀኝ<br />
አፈወርቅ በደዊ<br />
እያስፔድ ተስፋዬ
3 የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2 ነገረ-ኢትዮጵያ<br />
ልብ አድርጉ<br />
ውህደት ወይስ ትብብር?<br />
በላይ ማናዬ<br />
ሀገር አቀፉ ምርጫ 2007 እየደረሰ ነው፤<br />
ምርጫን ተከትሎ የሚስተዋለው የፖለቲካ<br />
ግለትም በትንሹም ቢሆን ከወዲሁ ለብ<br />
ማለት የጀመረ ይመስላል፤ የት መሽገው<br />
እንደከረሙ ጠፍተውብን የነበሩ የፖለቲካ<br />
ፓርቲዎችም አንገታቸውን ብቅ ለማድረግ<br />
እየሞከሩ እንደሆነ መታዘብ ይቻላል፡፡<br />
በሀገራችን በፓርቲዎች የቁጥር ብዛት ረገድ<br />
ችግር የለም ማለት ይቻላል፡፡ ባለፈው<br />
ምርጫ 2002 እንኳ ወደ 90 የሚጠጉ<br />
ፓርቲዎች እንደነበሩ ይታወቃል፡፡<br />
በእርግጥም አሁን ላይ ኢትዮጵያ<br />
ውስጥ በቁጥር በጣም ብዙ የፖለቲካ<br />
ፓርቲዎች ተመዝግበው ይገኛሉ፤<br />
(በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚንቀሳቀሱትን<br />
ህብረ-ብሄር ፓርቲዎችም፣ ጎሳን ወይም<br />
አንድን ብሄረሰብ ማዕከል አድርገው<br />
የሚንቀሳቀሱትንም ማለቴ ነው)፡፡ ለአብነት<br />
በሁለተኛው ረድፍ ላይ ከሚመደቡት እንኳ<br />
ብናይ ለኦሮሞ ህዝብ እንታገላለን የሚሉት<br />
ከ10 በላይ፣ ጉራጌ 5፣ አርጎባ 3፣ ሀረሪ<br />
3 እና ሌሎችም በተመሳሳይ በርካቶች<br />
አሉ፡፡ በዚህም ከአጠቃላይ የፓርቲዎች<br />
ቁጥር አብላጫውን ሀገር አቀፍ ያልሆኑት<br />
ፓርቲዎች ይዘው ይገኛሉ፡፡ (የምዝገባ<br />
ፍቃዱን ወስዶ ዳናው የሚጠፋውም ጥቂት<br />
የሚባል አይደለም፡፡)<br />
ይህ ቁጥሩ የበዛ የፓርቲዎች እንቅስቃሴ<br />
ያለው ደግሞ በተቃውሞው ጎራ በኩል<br />
ነው፡፡ እንዲህ አይነቱ የፓርቲዎች አካሄድ<br />
ማንን እንደሚጠቅም ሳይታለም የተፈታ<br />
ነው፡፡ በምርጫ ወቅት የህዝብን ድምጽ<br />
በመከፋፈል የትኛውም ተቃዋሚ ፓርቲ<br />
አብላጫ ድምጽ በቀላሉ እንዳያገኝ በማድረግ<br />
ለገዥው ፓርቲ በተዘዋዋሪ ይጠቅመዋል፡<br />
፡ ስለሆነም እንዲህ ባለ ወቅት ተቃዋሚ<br />
ፓርቲዎች በሁለት አማራጮች ላይ<br />
ይንጠለጠላሉ፤ አንድም በቁጥር የበዙትን<br />
ፓርቲዎች ወደ አንድ ኃይል ማምጣት<br />
ላይ፣ አሊያም በተናጠልም ቢሆን በሀገር<br />
አቀፍ ደረጃ ጎልቶ ለመውጣት የሚያስችልን<br />
አቅም ፈጥሮ ገዥው ፓርቲንም ሆነ<br />
ሌሎች ተወዳዳሪዎችን ተፎካክሮ ለማሸነፍ<br />
የሚያስችልን እንቅስቃሴ ማድረግ፡፡<br />
በተግባር እንቅስቃሴ ላይ ያሉትን የተለያዩ<br />
ፓርቲዎች ወደ አንድ ኃይል አምጥቶ<br />
ወደ ምርጫ መግባት በባለፉት የምርጫ<br />
ተሞክሮዎቻችን ላይ አይተናል፤ (ቅንጅትን<br />
በ97፣ መድረክን በ2002 መጥቀስ ይቻላል፡፡<br />
) ያለፉት ሂደቶችና ተሞክሮዎች የራሳቸው<br />
ጥንካሬና ድክመት እንደነበረባቸው መካድ<br />
አይቻልም፡፡ ያም ሆነ ይህ ግን አሁን<br />
ሌላ የታሪክ ምዕራፍ ላይ እንገኛለን፡<br />
፡ ቀደም ብዬ እንደጠቀስኩት ምርጫ<br />
2007 እየደረሰ ነው፡፡ ስለሆነም አሁን<br />
ፓርቲዎች የበለጠ ለስራ የሚነሱበት ጊዜ<br />
ነው፤ በተናጠልም፣ በትብብርም፡፡ ከዚህ<br />
ጋር ተያይዞ በዚህ ሰሞን ስለ ፓርቲዎች<br />
ውህደትም የሚያነሱት በዝተዋል፡፡ ይህን<br />
የውህደት ጉዳይ እንደሚከተለው ለማየት<br />
እንሞከራለን፡፡<br />
ውህደት እንዴት?<br />
በአጭሩ ውህደት አንድ መሆን ማለት<br />
ነው፡፡ ከውህደት በፊት ያለው የተናጠል<br />
ህጋዊ ህልውና አክትሞ አዲስ ፓርቲ<br />
በአንድ ላይ መመስረት ነው ውህደት፡<br />
፡ አንድ ለመሆን ደግሞ፣ አንድ ለመሆን<br />
የሚያስችሉ ሁኔታዎች መኖር አለባቸው፡<br />
፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለመዋህድ የፖለቲካ<br />
ፕሮግራማቸው መመሳሰልና መቀራረብ<br />
ይኖርበታል፡፡ ከዚህም በላይ ግን ፓርቲዎቹ<br />
ለመዋህድ ፍላጎት ማሳየት የግድ ነው፤<br />
በውህደቱ ሂደትና ከውህደት በኋላ<br />
ስለሚኖረው እንቅስቃሴም የተሻለ መስራት<br />
እንደሚችሉ ሊያምኑበት ይገባል፡፡ በዚህም<br />
ማን ከማን ጋር መዋህድ እንደሚችል<br />
ካላቸው የፖለቲካ ፕሮግራም፣ የውህደት<br />
ፍላጎትና በመዋህዳቸው ሊያመጡት<br />
የሚችሉትን ውጤት ገምግመው፣ ወይ<br />
ወደ ውህደት ይገባሉ አሊያም በራሳቸው<br />
መስመር ጠንክረው ለመስራት ውሳኔ<br />
ያስተላልፋሉ፡፡<br />
ከሰሞኑ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት<br />
ድርጅት (መኢአድ) እና አንድነት<br />
ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት)<br />
በአስቸኳይ ለመዋህድ እየሰሩ እንደሆነ<br />
ገልጸዋል፡፡ ፓርቲዎቹ ጥር 25 ቀን 2006<br />
ዓ.ም መአህድ/መኢአድ የተመሰረተበትን<br />
22ኛ አመት በዓል በጽ/ቤቱ ባከበረበት ወቅት<br />
እንደገለጹት፣ ሁለቱ ፓርቲዎች በፍጥነት<br />
ወደ ውህደት ለመምጣት መወሰናቸውን<br />
በይፋ በመሪዎቻቸው በኩል ግልጽ<br />
አድርገዋል፡፡ የመኢአድ ፓርቲ ፕሬዚዳንት<br />
አቶ አበባው መሐሪ ፓርቲያቸው መኢአድ<br />
ከአንድነት ፓርቲ ጋር መዋሃድ ፍላጎቱ<br />
መሆኑን ተናግረዋል፡፡<br />
በተመሳሳይ በቀድሞ ፓርቲያቸው 22ኛ<br />
አመት ክብረ በዓል ላይ የተገኙት የአንድነት<br />
ፓርቲ ፕሬዚዳንት ኢ/ር ግዛቸው ሺፈራው<br />
በበኩላቸው ፓርቲያቸው ከመኢአድ ጋር<br />
መዋሃድ ፍላጎቱ መሆኑን ገልጸው፣<br />
በ15 ቀናት ውስጥ ውህደቱ እውን ሊሆን<br />
እንደሚችልም ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡<br />
ፓርቲዎቹ ይህን ይበሉ እንጂ (በዕለቱ<br />
በነበረው የመድረክ ሞቅታ እንዳይሆን<br />
እሰጋለሁ) በዚህ ፍጥነት ሊዋሀዱ<br />
የሚችሉበት ሁኔታ ውስጥ እንዳልሆኑ<br />
ጠቋሚ ምልክቶች መኖራቸውን መካድ<br />
አይቻልም፡፡<br />
ውህደት መቼ?<br />
ውህደት ምርጫ ስለቀረበ የሚከናወን<br />
የይድረስ ይድረስ ስራ እንዳልሆነ እሙን<br />
ነው፡፡ በተቃራኒው ግን በሀገራችን የነበሩ፤<br />
ያሉ ፓርቲዎች ውህደት የሚታያቸው<br />
ምርጫ ሲቃረብ መሆኑ አለመታደል ነው፡፡<br />
አንዳንዶቹ ሂደቱን ቀድመው ቢጀምሩትም<br />
ሲያጓትቱ ሲያጓትቱ እስከ ምርጫ መቃረቢያ<br />
ድረስ ያደርሱታል፡፡ የመኢአድና የአንድነት<br />
ውህደት እውን ቢሆን የሚወድ ብዙ ነው፡<br />
፡ ዳሩ ግን ውህደቱ መሆን የነበረበት<br />
(በእውነት ኢ/ር ግዛቸው እንዳሉት በ15<br />
ቀናት ውስጥ የሚከናወን ከሆነ ወይም<br />
ቢሆን ኖሮ) እንዲህ በሩጫ አሁን ላይ<br />
አይደለም፤ (በ15 ቀናት ውስጥ የሚደረግ<br />
ውህደት የፖለቲካ ፓርቲዎች ሳይሆን….)፡<br />
፡ ይህ ውህደት ከምርጫ 2002 ማግስት<br />
ቢሆን በተገባ ነበር፡፡<br />
ውህደት በተናጠል በውጠ-ፓርቲ ትግል<br />
ፈተና ውስጥ የገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎች<br />
መሪዎች ከቀውስ ማምለጫ ወይም አጀንዳ<br />
ማስቀየሻ ሊሆን አይገባም፡፡ በተጨማሪም<br />
አንድ ፓርቲ ከገጠመው የገንዘብ እጥረት<br />
አሊያም የቢሮ ኪራይ ችግር ለመውጣት<br />
ዘው ብሎ የሚገባበት ጉዳይ መሆን<br />
አይኖርበትም፡፡ በሩጫ የሚደረግ ውህደት<br />
ውጤቱ ምን ሊሆን እንደሚችል ለማንም<br />
የተሰወረ አይሆንም፡፡<br />
እናም ውህደት በቂ ጊዜ ወስዶ መጤን<br />
ያለበት ትልቅ የፖለቲካ ስራ ነው፡፡<br />
እርግጥ ነው ህዝቡ ፓርቲዎቹ እንዲዋህዱ<br />
ይፈልጋል፡፡ ከዚህ በላይ ግን አብዛኛው<br />
ህዝብ ፓርቲዎች ተዋህደው እንዲዘልቁና<br />
ለውጥ እንዲያመጡ እንደሚሻ ግልጽ ነው፡<br />
፡ ለዚህ ደግሞ ከጅምሩ የሰከነ የውህደት<br />
ሂደት መኖሩ ግድ ይላል፡፡<br />
የውህደት ፈተናዎች<br />
የፖለቲካ ፓርቲዎችን ወደ ውህደት<br />
ማምጣት፣ ከውህደት በኋላም ተስማምቶ<br />
መቀጠል ትልቅ ፈተና አለው፡፡ በተለይም<br />
እንዲህ በአጭር ጊዜ ውህደትን እናመጣለን<br />
ብለው ሰርጋቸውን ከሚያፋጥኑ ሰዎች<br />
ወደ ፊት የሚሆነውን በስጋት መመልከት<br />
ግርምትን የሚፈጥር ጉዳይ አይሆንም፡<br />
፡ በተዋሃጆቹም በኩል የእነቶሎ ቶሎ<br />
ቤት…እንዳይሆን መጠንቀቁ የሚበጅ ነው፡<br />
፡ ምርጫ ስለደረሰ ብቻ በፍጥነት ውህደትን<br />
ማከናወን ሊኖረው የሚችለውን ፈተና<br />
ሊያስረሳን አይገባም፡፡ ሰርገኛ መጣ በርበሬ<br />
ቀንጥስ እንዳይሆን መጠንቀቁ የብልሆች<br />
ምርጫ ነው፡፡<br />
በእርግጥም ውህደት የጥቂት ግለሰቦች<br />
ወይም የፖለቲካ ፓርቲዎች መሪዎች<br />
ፍላጎትና ተግባር ብቻ አይደለም፡፡ ከዚያ<br />
ይልቅ የሚዋሃዱት ፓርቲዎች አባላት<br />
(ጠቅላላ ጉባኤ በሚገባ ተወያይቶበት<br />
ውሳኔ ማሳለፍን ይጠይቃል፤) በየደረጃው<br />
ሰፊ ጊዜ ሰጥተው ጉዳዩን ሊወያዩበትና<br />
ሊያጤኑት ግድ ይላል፡፡ ይህን ለማድረግ<br />
የሚያስችላቸው ጊዜም ሊሰጣቸው<br />
እንደሚገባ እሙን ነው፡፡ በሌላ አነጋገር<br />
ውህደቱ ከጅምሩ እሰከ ፍጻሜው አባላትንም<br />
ማዕከል ያደረገ መሆን ይኖርበታል፡፡ ይህ<br />
ሳይሆን ቀርቶ ውህደቱ የጥቂቶች ስራ<br />
ከሆነ፣ አንድም ውህደቱ እውን አይሆንም፣<br />
እውን ከሆነም ዘላቂነቱ አጠራጣሪ ከመሆን<br />
አይድንም፡፡<br />
የውህድ ፓርቲው መሪ<br />
ሌላው ፈተና ውህደቱ ከተፈጸመ በኋላ<br />
የውህድ ፓርቲው (አዲሱ ፓርቲ) መሪ<br />
ማን ይሁን የሚለው ጉዳይ ነው፡፡ የዚህ<br />
ፈተና ምንጭ ውህደቱን ከመሰረቱት<br />
ፓርቲዎች ወገን ሁሉም የቀድሞ ፓርቲው<br />
መሪ፣ የአዲሱ ውህድ ፓርቲ መሪም<br />
ሆኖ እንዲዘልቅለትና ቡድናዊ ጥቅሙን<br />
እንዲያስከብርለት የመፈለጉ ጫና ነው፡፡<br />
በዚህም ሁሉም የየራሱን የቀደመ የትግል<br />
ታሪክና የአደረጃጀት ስፋት እያነሳ ስልጣኑ<br />
እንደሚገባው መሞገቱ ስለማይቀር ነው፡፡<br />
እንዲህ አይነቱ ጉዳይ ደግሞ ማን የተሻለ<br />
መምራት ይችላል ሳይሆን፣ ማን የውህድ<br />
ፓርቲው መሪነት ይገባዋል ወደሚል<br />
ሰንካላ ምክንያት ይገፋናል፡፡<br />
በተመሳሳይ ውህደቱ ከሚከናወንበት<br />
ወቅት አንስቶ፣ ውህደቱ ሊያመጣባቸው<br />
የሚችለውን ከጥቅማ ጥቅምና ስልጣን<br />
ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን ማጣት በማጤን<br />
ቅሬታ የሚሰማቸው ግለሰቦችም ሌላኛዎቹ<br />
ፈተናዎች መሆናቸው የማይቀር ነው፡<br />
፡ ከሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ<br />
ፓርቲዎች ወደ አንድ ሲመጡ፣ ቀድሞ<br />
በተናጠል የነበረውን የስራ አስፈጻሚ ያህል<br />
ቁጥር ሊያካትት አይችልም፡፡ በዚህ ጊዜ<br />
ተቀናሾች መኖራቸው ግድ ነው፤ እዚህ<br />
ጋር የሚነሳው ጉዳይ የመቀነሻ መስፈርቶቹ<br />
ናቸው፡፡ ያም ሆነ ይህ በአዲሱ ፓርቲ<br />
የሚደረገው የስልጣን ሽግሽግ በውህደት<br />
ወቅትና ከውህደት በኋላ ከሚገጥሙ<br />
ፈተናዎች መካከል መሆኑ የማይቀር ነው፡፡<br />
በሌላ በኩል ደግሞ ከውህደት በኋላም፣<br />
ከግል የስልጣን ጥማቸው ጋር በተገናኘ<br />
በስልጣን ተዋረድ ውስጥ ሁለተኛ ሰው<br />
ሆነው ለመስራት የማይፈልጉና ሁሌም ከኔ<br />
በላይ ላሳር ባዮች አይጠፉም፡፡ በዚህም፣<br />
እንዲህ አይነት ግለሰቦች አንዴ ከፖለቲካ<br />
ሲርቁ፣ ሌላ ጊዜ ያችኑ የመሪነት ቦታ<br />
ሲሰጣቸው ወደ መድረኩ ብቅ የሚሉ<br />
ናቸው፡፡ የእነዚህ ግለሰቦች የስልጣን ጥም<br />
የመሪነት ቦታ የነፈጋቸውን ፓርቲ ለቅቀው<br />
ወደ ሌላ ፓርቲ እስከመሄድ የሚያደርሳቸው<br />
ነው፡፡ ስለሆነም እነዚህን መሰል ግለሰቦች<br />
ዛሬ ስለውህደት አብዝተው ቢሰብኩም<br />
ያችኑ የመሪነት ቦታ የሚያሳጣቸው ጉዳይ<br />
ሲመጣ ሲያቀነቅኑት የነበረውን ዓላማ<br />
ረስተው የውህደቱ እንቅፋት ከመሆን<br />
ላይመለሱ ይችላሉ፡፡<br />
ደካማ የቀደመ የፖለቲካ ፓርቲዎች ውህደት<br />
ተሞክሮ ያለን ከመሆኑ ጋር ተያይዞ<br />
(በቅንጅቱ መፍረስ የተፈጠረ መንፈስን<br />
ማስታወስ ይበቃል፤) በህዝቡ ዘንድ ያለው<br />
ተስፋ የመቁረጥ ስሜትም እንደ አንድ ሌላ<br />
ፈተና ሊወሰድ የሚችል ነው፡፡ ፈጥኖ ወደ<br />
ውህደት የመግባትን ያህል ከውህደት በኋላ<br />
ተስማምቶ የመቀጠሉ ፈተናም ከባድ ነው፡<br />
፡ ስለሆነም መዋሃዱ መልካም ሆኖ፣ ነገር<br />
ግን አሁንም ከውህደት በፊት መሰራት<br />
ያለባቸው የቤት ስራዎች በጊዜ ከተከናወኑ<br />
በኋላ ቢሆን የተሻለ ውጤት ይኖረዋል፡፡<br />
አሁን ላይ ውህደት ወይስ ትብብር?<br />
ቀደም ብሎ እንደተጠቀሰው ውህደትን<br />
ለማከናወን የተዋሃጅ ፓርቲዎች ፕሮግራም<br />
ተመሳሳይ ወይም ተቀራራቢ መሆን<br />
ይኖርበታል፡፡ በዚህም አንድ ፓርቲ ከሌላው<br />
ጋር ለመዋሃድ መሰሉን ወይም ቢጤውን<br />
መፈለግ ግድ ይለዋል፤ ይህም የሚሆነው<br />
የሌላኛው ፓርቲ ፍላጎት ሲጨመርበት<br />
ነው፡፡ እናም ውህደት አግላይ ጎንም<br />
እንዳለው መገንዘብ ይቻላል፡፡ ለአብነትም<br />
የመኢአድ ሊቀመንበር አቶ አበባው መሐሪ<br />
የፓርቲያቸውን አቋም በሚከተለው መልኩ<br />
ገልጸውታል፡፡<br />
‹‹መኢአድ በኢትዮጵያ አንድነት ላይ<br />
ከማያምኑ የብሄር (የጎሳ) የፖለቲካ<br />
ድርጅቶች፣ በኢትዮጵያ አንድነት ላይ<br />
አልደራደርም በማለት፣ በውህደት ደረጃ<br />
አብሮ ለመስራት እቸገራለሁ የሚለው በቂ<br />
ምክንያት ስላለው ነው፡፡›› (አንድነት ከአረና<br />
ትግራይ ጋር ለመዋሀድ ንግግር መጀመሩ<br />
የሚታወቅ ነው፡፡ ታዲያ መኢአድ በአንድነት<br />
በኩል የመጣውን አረና ትግራይን እንዴት<br />
ሊያደርገው ይሆን?) ያም ሆነ ይህ ጉዳዩ<br />
የሚያሳየን የውህደትን አግላይነት ነው፡፡<br />
ከመኢአድ አቋም ለመረዳት እንደሚቻለው<br />
ፓርቲው ለውህደት በሩን የሚከፍተው<br />
ጠንካራ ጥበቃዎችን ከፊት አቁሞ ነው፡<br />
፡ ስለሆነም ውህደት የራሱ ጠንካራ ጎኖች<br />
እንዳሉት ሆኖ፣ እንደ አሸን የፈሉትን<br />
የፖለቲካ ድርጅቶች በጋራ አስተባብሮ ወደ<br />
አንድ የማምጣቱ ነገር ውስን መሆኑን<br />
ነው፡፡<br />
በአብዛኛው የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች<br />
የጋራ የሆነ የሚታገሉት ኃይል አላቸው፤<br />
እሱም ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ ነው፡<br />
፡ እነዚህ ፓርቲዎች የየራሳቸው የተለያየ<br />
ዓላማን አንግበው የሚንቀሳቀሱ ቢሆኑም<br />
የወል ጉዳይ እስካላቸው ድረስ ግን መተባበር<br />
ወደ ገፅ 6 ይዞራል
ነገረ-ኢትዮጵያ ቅፅ 1 ቁጥር 2 የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. 4<br />
ከዚህ በታች የቀረበው ጽሑፍ የሰማያዊ ፓርቲ ፕሬዚዳንት ኢ/ር ይልቃል<br />
ጌትነት ፓርቲያቸው ጥር 25 ቀን 2006 ዓ.ም በጎንደር ከተማ ባካሄደው<br />
ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ያደረጉት ንግግር ነው፡፡<br />
‹‹አገርን ከመቁረስ በላይ ምንም ነገር<br />
ሊመጣብን አይችልም››<br />
በዚህ ትውልድ እዚህ<br />
ደረጃ ላይ ባለ ነገር<br />
መነጋገራችን አሳፋሪና<br />
አዋራጅ ነው፡፡ ሰው<br />
ከአባቱ የተሻለ ነገር<br />
እየሰራ፣ የነበረውን<br />
እያሻሻለ፣ አገሩን<br />
እያሻሻለ መሄድ ሲገባው<br />
በአሁኑ ወቅት አገሩን እየቆረሰ የሚሸጥ<br />
ጉደኛ መንግስት መጥቶብናል፡፡ እንዲህ<br />
ያለውን ነገር በአንድ ላይ ቆመን፣<br />
ተባብረን፣ መልክ ካላስያዝነው በስተቀር<br />
አምባገነን ለስልጣኑ ሲል የማይሰጠው<br />
ነገር ስለሌለ፤ ከዚህ በኋላ በፍርሃት፣<br />
በመሸማቀቅ፣ ከስራዬ እሰናበታለሁ<br />
በሚል፣ አምስት ለአንድ ይህን<br />
ያደርገኛል እየተባለ የሚፈራ ከሆነ<br />
በአገር ላይም የማንኖርበት ደረጃ ላይ<br />
እንደርሳለን፡፡<br />
ስለዚህ እነሱ የሚሉትን ከሰማን<br />
ዘላለም ሊገዙን ይሞክራሉ፤ ክብራችን<br />
ጨምሮ ሁሉን ነገራችንን አሳልፈን<br />
እንድንሰጣቸው ይፈልጋሉ፤ ቅዳሜ<br />
(ጥር 24) ቀንና ሌሊቱን ሙሉ የእኛን<br />
ጓደኞች አስረዋቸዋል፡፡ ጥር 22ትም<br />
ከቀኑ አምስት ሰዓት እስከ ምሽቱ<br />
አስራ ሁለት ሰዓት አስረዋቸው፡፡ ነገር<br />
ግን የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና<br />
አባላት ከዓላማቸው፣በከሃሳባቸውና<br />
እውነት ይዘው ከተነሱበት መንገድ<br />
አንድም ፈቀቅ አይሉም፡፡ ምን ጊዜም<br />
ቢሆን የኢትዮጵያ ጉዳይ ትልቅ ስራ<br />
እያለ፣ የተለያየ የኑሮ ሁኔታ እያለ<br />
ሁሉንም ነገር ተቋቁመው የሰማያዊ<br />
ፓርቲ ወጣቶች ከረዕቡ ዕለት ጀምረው<br />
በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የደህንነቶችን<br />
ወከባ፣ ያለውን አፈና እየተቋቋሙ<br />
ለሰላማዊ ሰልፉ ስላበቁን በሰማያዊ<br />
ፓርቲ ስም ከልብ አመሰግናለሁ፡፡<br />
ለኢትዮጵያ ወጣቶች ሁሌም የምናገረው<br />
ነገር ቢኖር አምባገነን መንግስት<br />
ያስረኛል፣ ይህን ያደርገኛል፣ ከዚህ<br />
ስሄድ ይህኛው ነገር ይመጣብኛል<br />
ከተባለ ትግል ሊኖር እንደማይችል<br />
ነው፡፡ ትግል ከተባለ የሚመጣውን<br />
ሁሉ ዋጋ እየተከፈለ ነው፡፡ የቋረኛው<br />
ቴዎድሮስ ልጅ ስንሆን እኮ፤ እሱ<br />
ክብሬን አላስደፍርም ብሎ ሽጉጡን<br />
ጠጥቶ የተሰዋ ሰው አለ እያልን<br />
ነው በየ ዘፈኑ የምናነሳው፡፡ ታዲያ<br />
ይህንን ክብር የነበረው ሰው መሬቱና<br />
ዳር ድንበሩ ሲወሰድበት፣ ዝም ብሎ<br />
የሚያይ ከሆነ ይህ ትውልድ በታሪክ<br />
ይጠየቃል፡፡ የምንጠየቀው ደግሞ የዚህ<br />
ትውልድ አባላት ብቻ አይደለንም፡<br />
፡ እነዛን አጥንታቸውን ከስክሰው፣<br />
ደማቸውን አፍስሰው አገራችን<br />
ያቆዩዋትን ታሪክ ብኩርናም መሸጥ<br />
ነው፡፡ እነዚህን አባቶቻችንም መክዳት<br />
ነው፡፡ በዚህ ዘመን የእኛን ትውልድ<br />
አሳልፈን መስጠታችንም እራሳችን<br />
መክዳት ነው፡፡ የወደፊቱን ትውልድ<br />
ሃላፊነትም መካድ ነው፡፡ ስለዚህ አሁን<br />
እኛ የምናደርገው ለድንበራችን መከበር<br />
ጠንክረን ከሰራን የአባቶቻችን ታሪክ<br />
እናስጠብቃለን፡፡ የእኛንም የወደፊት<br />
ታሪክ እናስጠብቃለን፡፡ ወደፊት<br />
የሚመጡትን ልጆችም በሙሉ ልብ<br />
እንዲኖሩ እናደርጋለን፡፡<br />
አሁን ግን ዝም ብለን ይህን ሁሉ<br />
ነገር ካለፍን ስለ ቴዎድሮስ መዝፈን<br />
አይቻልም፤ ከዚህ በኋላ ስለ አጼ<br />
ዮሃንስ መዝፈን አይቻልም፡፡ መዝፈን<br />
የምንችለው የእነሱን ክብር የሚያስጠብቅ<br />
ትውልድ መሆን ከቻልን ብቻ ነው፡<br />
፡ ይህንን የማያደርግ ትውልድ ከሆነ<br />
አፋራም ትውልድ ነው፣ ብኩርናውን<br />
ሽጧል፣ አባቶቻችን አዋርዷል፣ራሱንም<br />
አዋርዷል፣ ቀጣዩ ትውልድም በእሱ<br />
ምክንያት አንገቱን ደፍቶ እንዲኖር<br />
አድርጓል ማለት ነው፡፡<br />
ስለዚህ ይህ የአገር ጉዳይ ቀላል ጉዳይ<br />
አይደለም፡፡ አባቶቻችን የደሙበት ነው፡<br />
፡ አጥንት የተከሰከሰበት ነው፡፡ ክብራችን<br />
ብለን ለነጻነት የቆምንበት ነው፡፡ ለዚህ<br />
የሚደረገው ትግል እንደማንኛውም<br />
ትግል በቀላሉ የሚታይ አይደለም፡<br />
፡ ለእኔ ዴሞክራሲና መልካም<br />
አስተዳደር ቅንጦት ነው፡፡ አገርን<br />
ከመቁረስ በላይ ግን ሌላ ምንም ነገር<br />
ሊመጣብን አይችልም፡፡ ይህንን ጉዳይ<br />
ዝም ብለን የምናይ ከሆነ አሁን ያለው<br />
የኢትዮጵያ ትውልድ በታሪክ ፊት<br />
እንዳፈረ ይኖራል፡፡ ስለሆነም ወገኖቼ!<br />
አምባገነኖች ይሄዳሉ፣ ትውልድ<br />
ይሄዳል፣ አገርና ህዝብ ግን ዘላለም<br />
ይኖራል፡፡ በዚህ ለዘላለም በሚኖር<br />
አገርና ህዝብ ክብራችን ጠብቀን መኖር<br />
አለብን፡፡<br />
የኢትዮጵያ ልጆች ሁሉ ለአፍሪካም<br />
ሆነ ለዓለም የነጻነት ምሳሌ ነን፡፡<br />
አባቶቻችን የነጻነት ምሳሌዎች ናቸው፡<br />
፡ እኛም በየትኛውም ዓለም ልባችንን<br />
ሞልተንና ቀና ብለን የምንሄደው<br />
አባቶቻችን በከፈሉት መስዕዋትነት<br />
ነው፡፡ ይህንን ብኩርናችንን፣<br />
ነጻነታችንን፣ ተምሳሌትነታችንን<br />
አሳልፈን እንዳንሰጥ የሚሆነውን ሁሉ<br />
በንቃት እንድንከታተል አሳስባለሁ፡<br />
፡ ስልጣን ላይ ያሉት ሰዎች ለአንድ<br />
ሰሞን ስልጣን፣ ለአንድ ሰሞን ገንዘብና<br />
ለሚያልፍ ነገር ብለው ይህን ሁሉ<br />
በደል ከመፈጸምና ራሳቸውን ከታሪክ<br />
ተጠያቂነት ጠብቀው፣ ቆም ብለው<br />
ጉዳዩን ሃላፊነት በተሞላበት መንገድ<br />
እንዲያዩትና ከህዝብ ጋር ግልጽ<br />
ውይይት አድርገው የህዝብን ታሪክና<br />
አንድነት ሳያናጉ የኢትዮጵያን ብሄራዊ<br />
ጥቅም አስከብረው ከማፈርና ከውርደት<br />
እንዲድኑ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ!!<br />
መመረጥ በሌላው ድክመት...<br />
አጠናክሮ የፕሮፓጋንዳ ብቻ ሳይሆን የተግባር<br />
ታጋይ ሆኖ ለመውጣት የሚያስችል ሥራ<br />
በየፓርዎቹ በተግባር መታየት መቻል አለበት፡<br />
፡ የፓርቲ መሪዎች ቢመረጡ በተሻለ ሀገር<br />
የመምራት አቅሙም እውቀቱም ያላቸው<br />
መሆኑን ፓርቲ ውስጥ በሚሰጡት አመራርና<br />
በሚያስመዘግቡት ለውጥ ማሳየት መቻል<br />
ይኖርባቸዋል፡፡<br />
በሕዝቡ የተባበሩ ጥያቄ በተለያዩ ግዜያት<br />
የተፈጠሩ መተባበሮች የእንቧይ ካብ እየሆኑ<br />
ወይ ኀብረት ሳናይ ወይ አንድና ሁለት ጠንካራ<br />
ፓርቲ ሳናይ 21 ዓመታትን ቆጠርን፡፡ ምርጫ<br />
2002 ያስተባበራቸው የምርጫ 97ን ውጤት<br />
መናዳቸው አስቆጭቶአቸው በምርጫ 2007<br />
የተሻለ ነገር ለመስራት የሚያስችል ዝግጅት<br />
ሊያደርጉ በሚገባቸው ወቅት ስለምርጫ<br />
እያሰቡ መሆናቸውን እንኳን የሚጠቁም ነገር<br />
አይታይም፡፡ ይህም በራስ ብቃት ተወዳዳሪ<br />
መሆንን ያለሙ አለመሆናቸውን ያሳያል፡፡<br />
የአመለካከት ጥራት፣ ድርጃታዊ ብቃት፣<br />
ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው አሰራር<br />
የውይይት ባህል የዳበረበት ዴሞክራሲያዊ<br />
አሰራር የሚስተዋልበት ጠንካራ የህዝብን<br />
ይሁንታ ያተረፈ ፓርቲ መፍጠር ብዙ ዋጋ<br />
የሚያስከፍል ከባድ ስራ ነው፡፡ የሌላውን<br />
ጉድለት እያወሩ የሕዝብን ብሶት እየነካኩ<br />
ለመመረጥ ማሰብ ግን ቀላል ግን ተፈላጊውን<br />
ውጤት የማያስገኝ መንገድ ነው፡፡ በመተባበር<br />
ካባ ተሸፍኖ መቅረብም እንዲሁ፡፡<br />
ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ በተዋቂ ግለሰብነት<br />
በመሰረቱትና ኋላም የአንድነት ሊቀመንበር<br />
በመሆናቸው በነበራቸው የመድረክ ተሳትፎ<br />
ከተገነዘቡት ተነስተው «….በአሁኑ ሁኔታ<br />
ከተጠቀሱት ድርጅቶች ለመዋሀድ በጣም ከባድ<br />
ነው ያስቸግራል፡፡ ወደ ውህደት ለመምጣት<br />
ብዙ ውይይቶች ብሎም አብሮ መስራ<br />
ያስፈልጋል፤ መተዋወቅ አለብን፡፡ የድሮው<br />
ቁስሎች መረሳት አለባቸው፡፡» (ኢትዮ ምህዳር<br />
ታህሣሥ 30/2006) በማለት የተናገሩት<br />
በተግባር ካዩት ተነስተውና እውነትነቱ<br />
የሚያጠያይቅ አይደለም፡፡ ስለሆነም በውህደት<br />
ካርድ ለመጫወት የሚያስቡ ፖለቲከኞች<br />
በርግጥ ለውጥ አልመው ለዛም የሚያበቃ<br />
ድርጅታዊ ብቃት ፈጥረው ሳይሆን በእድሜ<br />
ከ ገፅ 13 የዞረ<br />
ማራዘሚያነት ለመጠቀም ነውና ለመርጫ<br />
2007 የሚፈይደው የለም፡፡<br />
ስለሆነም በርግጥ ለለውጥ የሚታገሉና<br />
ተቀዋሚ እየተባሉ በዚህም የሚገኘውን<br />
እየቀማመሱ መኖርን የመረጡ ይለዩ፡፡<br />
የመጀመሪያዎቹ ሰላማዊ ትግል ያለምርጫ<br />
ምርጫ ያለብቃት እንደማይሳካ የለውጥ<br />
መገኛው መንገድም ምርጫ መሆኑን አምነው<br />
ምርጫ 2007 ከተበላሸ በህዝቡ ዘንድ ሊፈጠር<br />
የሚችለውን የመጨረሻ ተስፋ መቁረጥ<br />
ከወዲሁ ገምተው ሕዝብ ተስፋ በቆረጠበት<br />
ሀገር ሰላማዊ ትግል ፋይዳ እንደማይኖረውም<br />
ተገንዝበው ሌላ ሌላውን ጨዋታቸውን<br />
ሁሉ አቁመው በ2007 ምርጫ ውጤት<br />
ለማምጣት ምን እናድርግ የሚል ምክክር<br />
ሊጀምሩና በምርጫው ውጤት ለማስመዝገብ<br />
የሚያበቃቸውን አቅም በተናጠልም ሆነ<br />
በጋራ ለመገንባት መስራት ይጠበቅባቸዋል፡፡<br />
መመረጥ የሚቻለው የመራጩን ቀልብ መሳብ<br />
የሚችል ብቃት ላይ ሲገኙ ነውና፡፡<br />
ጊዜ ቆሞ አይጠብቅም ምርጫ 2007<br />
እየቀረበ ነው፡፡ ኢህአዴግ ለምርጫ መስራት<br />
የጀመረው 99.6 በመቶ ባሸነፈበት ምርጫ<br />
ማግስት ነው፡፡ ከተቃውሞው ሰፈር የሚሰማ<br />
ነገር የለም፣ ሕዝቡ ሁሉንም በትዝብትና<br />
በአረምሞ በዝምታ እያስተዋለ ነው፡፡ ለጽሁፌ<br />
ማሳረጊያነት ሎሬት ጸጋየ ገብረ መድህን<br />
ከምርጫ 97 በፊት የካቲት 1/97 ከታተመችው<br />
ጦቢያ መጽሔት ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስ<br />
ከተናገረው ልዋስ (አንቱ ያላልኩበት<br />
ምክንያት ለአንባቢያን ግልጽ ይመስለኛል፡፡)<br />
{የሕዝብን እውነት በልብ ሳይቋጥሩ ሕዝብ<br />
ግንባር ፊት መቆም እንደ ወያኔ ድፍረት<br />
ሕዝብን ማርከስ ነው፡፡ መተባበር ያቃተው<br />
‹ኀብረትና ቅንጅት› ደግሞ ሕዝብን<br />
ሊያስተባብር አይችልም፡፡ አለንልህ የሚሉት<br />
ፖለቲከኞች ርስ በርሳቸው ሲጠላለፉ እያየ<br />
ሕዝቡ በመራራ ትዝብት ያስተውላቸዋል፡፡<br />
አይቆስሉ ቁስለት ማለት የኢትዮጵያ ሕዝብ<br />
ቁስለት ነው፡፡ አይችሉ መቻል ማለትም<br />
የኢትዮጵያ ሕዝብ መቻል ነው፡፡ ‹‹በላይ እሳት<br />
በታች እሳት› እንደ ድፎ ዳቦ እየነደደ በፅናቱ<br />
ብቻ ሳይሆን ሕዝቡ በትእዝብቱም ቀድሞናል፡<br />
፡} ነፍሱን ይማረውና ሎሬት ዛሬ ቢኖር ምን<br />
ይል ነበር!
5 የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2 ነገረ-ኢትዮጵያ<br />
ፖለቲካ<br />
‹‹መንግስት›› አሳልፎ የሰጠው<br />
ሉዓላዊነት<br />
ጌታቸው ሺፈራው<br />
ለአንድ አገር ሉዓላዊነት ቁልፍ<br />
ከሚባሉት ጉዳዮች መካከል<br />
ወሰን ዋነኛው መመዘኛ ነው፡፡<br />
የወሰን/የድንበር ጉዳይ ድንበር<br />
ብቻ ሳይሆን ከድንበሩ ጋር<br />
ያለውን ታሪካዊ ሂደትም ይጨምራል፡<br />
፡ ለአንድ መንግስትና ትውልድ የቀደሙ<br />
አባቶች ያኖሩትን ድንበር የመቆጣጠርና<br />
መጠበቅ ታሪካዊ ግዴታቸው ነው፡፡<br />
የውጭ አሊያም ሌላ ሀይል የኖረውን<br />
የአገሪቱን ድንበር የሚደፍር አሊያም<br />
የሚያስቀይር ከሆነ የአገሪቱ ሉዓላዊነት<br />
አደጋ ውስጥ ወድቋል ማለት ነው፡<br />
፡ የአንዲት አገርና ህዝቧ ያለ ድንበር/<br />
ወሰን ሊኖር አይችልም፡፡ አገሪቱ ብቻዋን<br />
መሆን እንደማትችል ሁሉ ክብሯን፣<br />
ታሪኳን፣ የዕለት ተዕለት እንቅስቀቃሴዋ፣<br />
ደህንነቷ ላይ ድንበር ከፍተኛ አስተዋጽኦ<br />
ይኖረዋል፡፡<br />
የወሰን አለመከበር ወይንም ሌላ ችግር<br />
እኒህን ሁሉ ጉዳዮች የሚያዛባ ይሆናል፡፡<br />
ለዚህም ነው ሌሎች አገራት ከሚሰጡት<br />
እውቅና ይልቅ ድንበር የአንድ አገር<br />
በተጨባጭ /የሚታይ/ ሉዓላዊነት<br />
መገለጫ ነው የሚባለው፡፡ ድንበር<br />
ዋነኛው የሉዓላዊነት አካል ስለመሆኑ<br />
የኢትዮጵያ ህዝብ ሲበድሉት የኖሩት<br />
አገዛዞች ‹‹አገርህ ተደፈረች›› ሲሉት<br />
ለጊዜውም ቢሆን ልዩነቱን ወደጎን ትቶ<br />
ዳር ድንበር ሊያስከበር ሲተም መኖሩ<br />
ትልቅ ማስረጃ ነው፡፡ በተቃራኒው<br />
መንግስታቱ ለሉዓላዊነት የህዝብን ያህል<br />
ቁርጠኛ ሆነው አልተገኙም፡፡ በዚህ በኩል<br />
ደግሞ ኢህአዴግ ሉዓላዊነትን አሳልፎ<br />
በመስጠት ወደር አልረገኘለትም፡፡<br />
አንድ አገር ሉዓላዊ የምትሆነው አሊያም<br />
ይህ ክብር የሚቀጥለው ድንበሯን፣<br />
ታሪኳንና የህዝብን ጥቅም አስጠብቆ<br />
የሚኖር አገር ወዳድ መንግስት ሲኖራት<br />
ብቻ ነው፡፡ በዚህ በኩል የአሁኗ<br />
ኢትዮጵያ አልታደለችም፡፡ የአገርን<br />
ጥቅም፣ በደምና በአጥንት የተገነባን<br />
ታሪክና ድንበር አሳልፎ የሚሰጥ አካል<br />
ባለበት የአገሪቱ ሉዓላዊነት አደጋ<br />
ውስጥ ይገባል፡፡ ሉዓላዊነት የአንዲት<br />
አገር ከሌሎች አገራት ጋር ሲነጻጸር<br />
ያላት እኩል ክብር፣ ህጋዊ ሰውነት<br />
እንደመሆኑ መንግስት የሚባለው አካል<br />
ወሰኗን ባልተገባ መንገድ ለሌሎች<br />
አሳልፎ የሚሰጥ ወይንም የሚወሰድበት<br />
ከሆነ ሉዓላዊነቷ ተደፍሯል ማለት ነው፡<br />
፡ ህወሓት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት<br />
ማስደፈር የጀመረው ገና በርሃ በነበረበት<br />
ወቅት ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት ከማንም<br />
ቀድሞ በየጊዜው ሰራዊት ወደ ሶማሊያ<br />
የሚልከው ህወሓት ያኔ ገና በርሃ እያለ<br />
ተስፋፊውን የሶማሊያ መንግስት እስከ<br />
ድሬዳዋ ድረስ መንገድ መምራቱን<br />
እንደ አስግደ ያሉት የቀድሞው የቡድኑ<br />
አባላት እማኝነታቸውን በይቅርታ መልክ<br />
ገልጸዋል፡፡<br />
ህወሓት እንደ ፖለቲካ ቡድን<br />
ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ኤርትራ<br />
የኢትዮጵያ ቅኝ ግዛት እንደሆነችና ነጻ<br />
መውጣት እንዳለባት ሲሰብክ ኖራል፡፡<br />
ህወሓት ‹‹አሸባሪ›› በነበረበት በዛ ወቅት<br />
የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ<br />
መለስ ዜናዊ ስለ ኤርትራ ጉዳይ ሁለት<br />
መጽኃፍትን ጽፈዋል፡፡ ‹‹የኤርትራ<br />
ህዝብ ትግል ከየት ወደየት›› በተሰኘው<br />
መጽኃፋቸውም ኤርትራን ከኢትዮጵያ<br />
ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌላት<br />
ነጻ አገር መሆኗን አውጀዋል፡፡ አቶ<br />
መለስና ህወሓት ይህን በሚሉበት ወቅት<br />
በርካታ የኤርትራ ተወላጆች በአገሪቱ<br />
አሁን ህወሓት ለሌሎች የግንባሩ አባል<br />
ፓርቲዎች አሳልፎ የማይሰጣቸው ቁልፍ<br />
ስልጣን እንደነበራቸው አይዘነጋም፡፡<br />
ገና ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ኤርትራን<br />
ከኢትዮጵያ መነጠልን አላማው አድርጎ<br />
የተነሳው ህወሓት ደርግን አሸንፎ ቤተ-<br />
መንግስት ሲገባ የወሰደው እርምጃ<br />
የዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ ኤርትራን<br />
እውቅና እንዲሰጥ ማድረግ ነበር፡፡ ይህም<br />
ኢህአዴግን የዋናዋ አገር ገዥ ሆኖ<br />
የአገሪቱ ክፍልን በፈቃደኝነት ያስገነጠለ<br />
(ሉዓላዊነቷን አሳልፎ የሰጠ) ብቸኛው<br />
ፓርቲ ሳያደርገው አይቀርም፡፡ ኤርትራን<br />
በገዛ እጁ ያስገነጠለው ህወሓት/ኢህአዴግ<br />
ከሻዕቢያ ጋር የነበረው ፍቅር ሲያልቅ<br />
የአገሩ ሉዓላዊነት ተላልፎ የተሰጠበት<br />
የኢትዮጵያ ህዝብ በደሉን ለጊዜው ወደጎን<br />
ትቶ ዳር ድንበሩን ለማስከበር ሲነሳ አገዛዙ<br />
የማይጨነቅለትን ሉዓላዊነት ለማስከበር<br />
እንደማይደክመው አሳይቷል፡፡ ጦርነቱ<br />
በኢትዮጵያ ህዝብ አሸናፊነት ከተጠናቀቀ<br />
በኋላም ቢሆን ህወሓት የለመደውን<br />
ሉዓላዊነት አሳልፎ የመስጠት ልክፍት<br />
ደግሞታል፡፡ ይህ አልበቃው ሲልም<br />
ህዝብ ከእሱ በላይ ለአገሪቱ ሉዓላዊነት<br />
እንደሚጨነቅ ጠንቅቆ ስለሚያውቅም<br />
‹‹ባድመን አግኝተናል!›› በሚል ህዝብን<br />
አሞኝቷል፡፡ ይህም ህወሓት/ኢህአዴግ<br />
ከሉዓላዊነት ጋር ያላውን ተቃርኖ<br />
በጉልህ የሚያሳይ ነው፡፡<br />
የኢህአዴግና የሉዓላዊነት ተቃርኖ<br />
አሁንም ቀጥሏል፡፡ ከስድስትና ሰባት<br />
አመታት ጀምሮ የኢትዮጵያን መሬት<br />
አሳልፎ ለሱዳን ለመስጠት በድብቅ<br />
እየተዋዋለ መሆኑ ሲነገር ቆይቷል፡<br />
፡ በቅርቡ ደግሞ ‹‹ሱዳን ትሪብዩን››<br />
የተባለው የሱዳን ጋዜጣ ‹‹ለም መሬታችን<br />
አገኘን!›› የሚል ዜና ማውጣቱን ተከትሎ<br />
ኢህአዴግ መሬቱን ለመስረከብ መቃረቡን<br />
አመላክቷል፡፡ የአንድ አገር መንግስት<br />
የአገሪቱን ድንበር ማስጠበቅና ማስከበር፣<br />
የዜጎቹን ጥቅም ማስከበር ሲኖርበት<br />
ለራሱ ግላዊ ጥቅም፣ ህጋዊ መሰረት<br />
በሌለው መንገድ የአገሩን ወሰንና ድንበር<br />
አሳልፎ የሚሰጥ ከሆነ በአገር ውስጥ<br />
የሌሎች ወኪል ሆኖ የአገርን ሉዓላዊነት<br />
እየደፈረ ከመሆን ውጭ ሌላ ሊባልለት<br />
አይችልም፡፡<br />
ይህ የ‹‹መንግስት›› ተግባር ልክ ቅኝ<br />
ገዥዎቹ የራሳቸው ታማኞች (ባንዳዎች)<br />
እንደነበሯቸው ማለት ነው፡፡ አንዲት<br />
በመንግስት ስር የምትገኝ አገር ሉዓላዊ<br />
የምትባለው ይህ መንግስት የአገሪቱን<br />
ወሰንና ሌሎች ጥቅሟን በህጋዊ መንገድ<br />
መቆጣጠርና ማስተዳደር ከቻለና<br />
በጥቅምም ይሁን በአቅም ማነስ ለውጭ<br />
ሀይል የአገሪቱን ጥቅም፣ ክብር፣ ወሰን<br />
አሳልፎ የማይሰጥ ከሆነ ብቻ ነው፡፡<br />
አገሪቱን ሁለመናው ነገር ተቆጣጥሮና<br />
እያስተዳደረም ቢሆን በውጭ ሀይል<br />
ተጽዕኖ ውሳኔ የሚያስተላልፍ፣<br />
የአገሪቱን ጥቅም አሳልፎ የሚሰጥ<br />
ከሆነ የአገሪቱ ሉዓላዊነቷ ተደፍሯል፡<br />
፡ የኢትዮጵያን መሬት ለሱዳን አሳልፎ<br />
ለመስጠት እየተደራደረ ያለው ኢህአዴግ<br />
የአገርን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ፣ ለህዝብ<br />
ጥቅም በመቆም ከሚታወቅ ‹‹መንግስት››<br />
ከተባለ አካል ይልቅ በሚገዛት አገር<br />
ውስጥ ለሱዳን ጥቅም የቆመ መሆኑን<br />
አሳይቷል፡፡<br />
አንድ አገር ሉዓላዊ ነው የሚባለው<br />
የአገሪቱን ዜጎች ከውጭ ጥቃት<br />
የሚከላከል አካል (መንግስት) ካለ ብቻ<br />
ቢሆንም የሱዳን ኢትዮጵያ ድንበር<br />
ችግር ከተከሰተ በኋላ በመተማና<br />
አካባቢው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን<br />
ለሱዳን የደህንነት ኃይሎች ተላልፈው<br />
ተሰጥተዋል፡፡ ከስድስትና ሰባት አመት<br />
በፊት ደንብር አካባቢ የነበረው የኢትዮጵያ<br />
ሰራዊት ወደኋላ አፈግፍጎ አርሶ አደሮቹ<br />
ከሱዳን የጸጥታ ሀይሎች ጋር ፊት ለፊት<br />
እንዲጋፈጡ ተፈርዶባቸው እንደነበር<br />
በጊዜው ተዘግቧል፡፡ አሁንም ቢሆን<br />
የሱዳን እስር ቤት ውስጥ የሚማቅቁ፣<br />
ሀብትና ንብረታቸው የሚዘረፍና<br />
በርካታ ሰብዓዊ ጥሰት የሚፈጸምባቸው<br />
መኖራቸው እየተነገረ ነው፡፡ ይህን ሁሉ<br />
የሚያደርገው ከኢትዮጵያ መንግስት<br />
ይሁንታን ያገኘው የሱዳን የደህነነት<br />
ሀይል ነው፡፡ በዚህ ረገድ መንግስት<br />
የመጀመሪያውን ህዝብን ከውጭ ጥቃት<br />
የመከላከል የሉዓላዊነት መርህ አሳልፎ<br />
ሰጥቷል፡፡ የራሱ ህዝብ በውጭ ሃይል<br />
አደጋ እየደረሰበት ዝም ማለት ብቻ<br />
ሳይሆን ሱዳኖች ኢትዮጵያውያንን<br />
እንዲያስለቅቁ የፈቀደው መንግስት<br />
የመጀመሪያው የአገሪቱን ሉዓላዊነት<br />
አሳልፎ የሰጠ አካል ነው፡፡<br />
የዓለም አቀፍ ህግን የጣሰው<br />
ድብቅ ስምምነት<br />
የአንድ መንግስት ዋነኛው<br />
ተግባር አገር ውስጥ ህዝብን<br />
የሚያስተዳድርበትን፣ አገሪቱ ከውጭ<br />
አካላት ጋር የምትገናኝበትንና ጥቅሟን<br />
የምታስከብርበት ህግና አግባብ የአገሪቱን<br />
ጥቅም በሚያስከብር መንገድ መቅረጽ፣<br />
ማስከበርና መተግብር ነው፡፡ ዓለም<br />
አቀፍ ህግ ከእዚህ መካከል አንዱ ነው፡<br />
፡ ኢትዮጵያ ከፈረመቻቸው ዓለም<br />
አቀፍ የድንበር ስምምነቶች መካከል<br />
ደግሞ አብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገራት ነጻ<br />
ከወጡ በኋላ የተፈራረሙት ‹‹የካይሮ<br />
ስምምነት›› በአብነት ይጠቀሳል፡፡<br />
አንድ አይነት ቋንቋ የሚናገሩ የአፍሪካ<br />
ህዝቦች ለቅኝ ገዥዎች በሚመችና<br />
ዘፈቀደ ድንበር ተከፋፍለው ተገዝተዋል፡<br />
፡ አንዳንዶቹ ደግሞ ግልጽ ከሆነው<br />
ይልቅ በየጊዜው የሚቀየሩ የቅኝ ገዥ<br />
አስተዳዳሪዎች፣ እርስ በእርሳቸው<br />
በሚወዳደሩ የምዕራባዊያን አገራት<br />
እንዲሁም የአገር ውስጥ ወኪሎች<br />
(ባንዳዎች) ግራ የሚያጋባ ድንበር መሰረት<br />
ተከፋፋለው ኖረዋል፡፡ ለአብነት ያህል<br />
በሁለትና ሶስት የቅኝ ገዥዎች፣ እነዚህ<br />
አገራትን ወክለው፣ አሊያም ለእነዚህ<br />
አገራት ወኪል ሆነው ለየራሳቸው ጥቅም<br />
ከተሸነሸኑት በርካታ ወሰኖች መካከል<br />
አንዲት አገር በስተመጨረሻ ነጻ ስትወጣ<br />
የያዘችውን ይዛ እንድትቀጥል ነው<br />
የተደረገው፡፡ ይህ ግልጽነት የጎደለው<br />
ድንበር፣ የድንበር ክለላም ለግጭት<br />
መሰረት እንደሚሆን የታመነበት የአፍሪካ<br />
አገራት ነጻ ከመውጣታቸው አስቀድሞ<br />
ነው፡፡ በተለይም የተለያዩ አካላትና<br />
ግለሰቦች የየራሳቸውንና ለራሳቸው<br />
የሚጠቅመውን ድንበር የሚያቀርቡ<br />
መሆኑ ግጭቱን የባሰ እንደሚያደርገው<br />
ታምኖበታል፡፡ ይህም በመሆኑ የአፍሪካ<br />
ህብረት ቻርተር ከጸደቀ ከአመት በኋላ<br />
ይህን ችግር ለመቅረፍ የአፍሪካ አንድነት<br />
ድርጅት በካይሮ ተገኝቶ ቀኝ ገዥዎች<br />
ተክለውት የሄዱትን የድንበር ችግር<br />
ይፈታል ያለውን ስምምነት አጽድቋል፡፡<br />
የዚህ ስምምነት አላማ በቅኝ ግዛት ወቅት<br />
በቅኝ ገዥዎች፣ በግለሰቦች፣ በአገርም<br />
ሆነ በውጭ ቡድኖች አማካኝነት በዘፈቀደ<br />
የተከለሉ ድንበሮች የሚያመጡትን ችግር<br />
ለመቅረፍ የአፍሪካ አገራት ነጻ ሲወጡ<br />
የያዙትን ወሰን ይዘው እንዲቀጥሉ<br />
ማድረግ ነው፡፡ ሌሎች አገራትም<br />
የጎረቤቶቻቸውንም ሆነ የሌሎች ነጻ<br />
ሲወጡ የነበራቸውን ድንበር ማክበር<br />
እንዳለባቸው የሚያሳይ ነው፡፡ ይህ ህግ<br />
እ.ኤ.አ በ1963 በጸደቀው የአፍሪካ ህብረት<br />
ቻርተር ላይም በግልጽ ተቀምጧል፡<br />
፡ የ1963 ቻርተር እንዲሁም በሀምሌ<br />
1964 የተፈረመው ስምምነት “to respect<br />
the frontiers existing on their<br />
achievement of independence”<br />
ወይንም አገራት ነጻ ሲወጡ የነበራቸውን<br />
ወሰን/ድንበር የማክበር ግዴታን አጽንኦት<br />
ሰጥቶ አስቀምጧል፡፡ ይህ ችግር አሁንም<br />
ድረስ ባለመቀረፉ የአሁኑ አዲሱ<br />
የአፍሪካ ህብረት ቻርተርም በአንቀጽ<br />
4(b) ‹‹respect of borders existing<br />
on achievement of independence››<br />
ወይንም አገራት ነጻነት ሲያገኙ<br />
የነበራቸውን ድንበር ማክበርን የሚለውን<br />
መርህ በቀዳሚነት አስቀምጦታል፡፡<br />
የአፍሪካ ህብረት ሚኒስትሮች እ.ኤ.አ<br />
በየካቲት 25 2010 አዲስ አበባ ላይ<br />
‹‹DECLARATION ON THE AF-<br />
RICAN UNION BORDER PRO-<br />
GRAMME AND THE MODALI-<br />
TIES FOR THE PURSUIT AND<br />
ACCELERATION OF ITS IMPLE-<br />
MENTATION›› የሚል ሰነድ በህብረቱ<br />
ስም ተፈራርመዋል፡፡ ሰነዱ ግጭትን<br />
ለመከላከል፣ ህብረትን ለማጠናከር ያለመ<br />
ነው፡፡ ይህ ስምምነት መሰረቱ ያደረገው<br />
‹‹አገራት ነጻ ሲወጡ የያዙትን ድንበር<br />
ይዘው መቀጠል፣ የሌሎቹንም ማክበር<br />
ይኖርባቸዋል›› ከሚለው የካይሮው<br />
ስምምነትን የመነጨ ነው፡፡<br />
በአሁኑ ወቅት ለሱዳን ይሰጣል የተባለው<br />
መሬትን ስምምነት እ.ኤ.አ በ1902 እና<br />
በ1907 እንደተደረገ ታሪክ ያስረዳል፡<br />
፡ ሆኖም መንግስታቱ መካከል ይህ<br />
በእውን ሳይተገበር መቅረት ብቻ ሳይሆን<br />
ሻለቃ ጉይን የተባለው የእንግሊዝ አዛዥ<br />
መንግስታቱ ከተስማሙበትም ውጭ<br />
ብቻውን ያሰመረው መሆኑ ይታወቃል፡<br />
፡ ያም ሆኖ ሱዳን ነጻ ስትወጣ የያዘችው<br />
ድንበር የዚህን የሻለቃ ድንበር አይደለም፡<br />
፡ የአፍሪካ አንድነት ቻርተር፣ የካይሮ<br />
ስምምነት፣ የአፍሪካ ህብረት ቻርተርና<br />
እዚህን መርሆች መሰረት አድርገው<br />
በየጊዜው በድንበር ጉዳይ የሚወጡ ህጎች<br />
እያሉ በአሁኑ ወቅት እነዚህን ህጎች<br />
በሚጻረር መልኩ ሱዳን ነጻ ስትወጣ<br />
ከነበራት ድንበር ወደ ኢትዮጵያ እስከ<br />
40 ኪሎ ሜትር የሚገባ መሬት ሊሰጣት<br />
መሆኑ ይፋ ሆኗል፡፡<br />
የካይሮን ስምምነት፣ የአፍሪካ ህብረት<br />
ቻርተርና ሌሎችንም ከሁለቱ የሚመነጩ<br />
የድንበር ህጎች በሚጻረር መልኩ<br />
የሚተገበር ተግባር ይበልጡን አስገራሚ<br />
የአንድ መንግስት ዋነኛው ተግባር አገር ውስጥ ህዝብን የሚያስተዳድርበትን፣ አገሪቱ ከውጭ<br />
አካላት ጋር የምትገናኝበትንና ጥቅሟን የምታስከብርበት ህግና አግባብ የአገሪቱን ጥቅም<br />
በሚያስከብር መንገድ መቅረጽ፣ ማስከበርና መተግብር ነው፡፡ ዓለም አቀፍ ህግ ከእዚህ መካከል<br />
አንዱ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ከፈረመቻቸው ዓለም አቀፍ የድንበር ስምምነቶች መካከል ደግሞ<br />
አብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገራት ነጻ ከወጡ በኋላ የተፈራረሙት ‹‹የካይሮ ስምምነት›› በአብነት<br />
ይጠቀሳል፡፡<br />
የሚሆነው ሌሎቹ ቅኝ ግዛት ስር<br />
በነበሩበት ወቅት የራሷ ወሰን የነበራት<br />
የህብረቱ መስራችና መቀመጫ ኢትዮጵያ<br />
ላይ መሆኑ ነው፡፡ ህግጋቱን ጥሶ<br />
የአገሪቱን መሬት ከድሮው እንደለመደው<br />
መሬትን ብቻ ሳይሆን ‹‹ሉዓላዊነትን››<br />
ለሌሎች በገጸ በረከትነት የሚያስረክበው<br />
ደግሞ ኢትዮጵያን እወክላለሁ በሚለው<br />
‹‹መንግስት›› መሆኑ ኢህአዴግ<br />
ከሉዓላዊነት ጋር ምን ያህል እንደተጣላ<br />
የሚያሳይ ነው፡፡<br />
ሱዳኖችን ጨምሮ መሬቱ ለሱዳን<br />
መሰጠት እንዳለበት ለሚያምነው<br />
ኢህአዴግ ዋነኛው መከራከሪያ<br />
ብሪታኒያና አጼ ምኒልክ በድንበሩ ጉዳይ<br />
ቢዋዋሉም መሬቱ በኢትዮጵያ ቁጥጥር<br />
ስር መቆየቱን ነው የሚያነሱት፡፡ በጉዳዩ<br />
ጥናት ካደረጉት አምስት ኢትዮጵያውያን<br />
መካከል በህይወት የሚገኙት ፕ/ር<br />
መስፍን ወ/ማሪያም ጥር 17/ 2006<br />
ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ ተገኝተው<br />
እንዳስረዱት፤ አሁን በኢትዮጵያና ሱዳን<br />
መካከል አጨቃጫቂ ነው የሚባለውን<br />
ድንበር የከለለው ሻለቃ ጉይን የተባለው<br />
የእንግሊዝ አዛዥ ብቻውን ሆኖ ነበር፡፡<br />
በወቅቱ ኢትዮጵያ ወኪል አልነበራትምና<br />
ስምምነቱ አይገዛትም ማለት ነው፡<br />
፡ ሻለቃው እንዳፈተተው በሚከልልበት<br />
ወቅትም ቢሆን የድንበር ለውጥ<br />
በመደረጉ ድንበሩ ወደ ሱዳን ገባ<br />
ብሎ እንደሚከለል ደብዳቤ ደርሶታል፡<br />
፡ ሆኖም ሻለቃው ከብሪታኒያ ክልል<br />
ካለችው ውጭ ወደ ኢትዮጵያ መሬት<br />
ገብቶ የራሱን ዘፈቀደ ድንበር አስቀምጦ<br />
አልፏል፡፡ ይህ ሆኖ እያለ ኢትዮጵያን<br />
ወክያለሁ የሚለው ኢህአዴግ በዚህ<br />
በተዛባ ህግ፣ አንድ የቅኝ ገዥ መኮነን<br />
ያሰመረውን የተሳሳተና ያልተገባ ድንበር<br />
የሚቀበል ከሆነ ምን አልባትም ለራሱ<br />
ጥቅም ሲል ብቻ ተጠቀመበት እንጂ<br />
ለስልጣን የማይጠቅመው ቢሆን የአባይን<br />
ስምምነትንም መቀበሉ የማይቀር<br />
እንደነበር ነው የሚያሳየው፡፡<br />
አሁን ለሱዳን ይሰጣል የተባለው መሬት<br />
የኢትዮጵያ አካል በነበረበት ወቅት<br />
ሱዳን ገና ነጻ አልወጣችም፡፡ በመሆኑም<br />
ከአፍሪካ አንድነት ቻርተር ጀምሮ፣<br />
በካይሮ ስምምነት፣ በአዲሱ የአፍሪካ<br />
ህብረት ቻርተርና በየጊዜው ድንበርን<br />
በተመለከተ በሚወጡት ህጎች መሰረት<br />
ድንበሩ የኢትዮጵያ እንጂ የሱዳን ሊሆን<br />
አይችልም፡፡ ከመቶ አመት በፊት በአንድ<br />
የቅኝ ገዥ መኮነን የተደረገን የመከለል<br />
ሙከራ እውነት አድርጎ ለሌላኛው አገር<br />
አሳልፎ መስጠት ከአንድ አገር መንግስት<br />
የሚጠበቅ አይደለም፡፡ ኢህአዴግ<br />
ኢትዮጵያ ውስጥ ስልጣን የያዘበት<br />
ጊዜ ዓለም ከጦርነት ይልቅ ወደ ሰላም<br />
የመጣችበትና በህግ የምትመራበት ነው፡<br />
፡ በዚህ ዘመን የአንድ አገርን ሉዓላዊነት<br />
ለማስጠበቅ ፈተናዎች የማይበዙበት<br />
ዘመን ነው፡፡ ከዚህ ይልቅ በርካታ<br />
የኢትዮጵያ መንግስታት የአገሪቱን<br />
ሉዓላዊነት የሚፈታተኑ አጋጣሚዎችን<br />
በጽናት አልፈዋል፡፡<br />
ኢህአዴግ በጣሊያን ወረራም ሆነ በሌሎች<br />
የአገሪቱ ሉዓላዊነት ጥያቄ ውስጥ<br />
በገባበት ወቅት ገዥ ቢሆን ኖሮ ራሱ<br />
ምንዳ እስካገኘ ድረስ ሙሉ በሙሉም<br />
ይሁን የውጭ ሀይሎች በሚፈልጉት<br />
መልኩ አገሪቱን አሳልፎ ይሰጥ እንደነበር<br />
ለመገመት አይከብድም፡፡ በእርግጥ<br />
አሁንም ቢሆን ሉዓላዊነትን አሳልፎ<br />
መስጠቱ ለሱዳን በሚሰጠው መሬት<br />
ይቆማል ተብሎ የሚገመት አይደለም፡<br />
፡ ፕ/ር መስፍን ውይይቱን በመሩበት<br />
ወቅት ለህዝብ መልሰው የጠየቁት<br />
ጥያቄም ‹‹ኢህአዴግ በቀጣይነት አሳልፎ<br />
የሚሰጠው የትኛውን መሬት ይሆን?››<br />
የሚል ነበር፡፡ ከተሳታፊዎችም ‹‹አዲስ<br />
አበባንስ መቼ ያስከልሏት ይሆን?››<br />
የሚል ጥያቄ ተነስቷል፡፡ ይህ እንግዲህ<br />
ኢህአዴግ ምን ያህል ለሉዓላዊነት<br />
የማይጨነቅ መሆኑና በጉዳዩ ታማኝነቱን<br />
ማጣቱን በግልጽ የሚያሳይ ሀቅ ነው፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ ቅፅ 1 ቁጥር 2 የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. 6<br />
ውህደት ወይስ ትብብር...<br />
ይችላሉ ማለት ነው፡፡ ትብብር አቃፊ<br />
ነው፡፡ የጎሳ ፓርቲውም ሆነ ህብረ-<br />
ብሄራዊው ፓርቲ በጋራ ጉዳዮች ላይ<br />
ተባብረው ከመስራት የሚያግዳቸው<br />
ነገር ሊኖር አይችልም፡፡<br />
በዚህ ረገድ ሰማያዊ ፓርቲ ከማናቸውም<br />
ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ጋር በትብብር<br />
ለመስራት ፍላጎቱ እንደሆነ ሲገልጽ<br />
ይደመጣል፡፡ ፓርቲው እንደሚለው፣<br />
ከውህደት በፊት የሚቀድሙ የቤት<br />
ስራዎችን መስራት ተገቢ ነው፤<br />
ለዚህም ትብብር ከውህደት ይቀድማል<br />
የሚል አቋም አለው፡፡<br />
በእርግጥም አሁን ላይ የፖለቲካ<br />
ፓርቲዎች ተቀራርበው በበለጠ<br />
በትብብር በመስራት ኃይላቸውን<br />
ማጠናከር ይገባቸዋል፡፡ ይህ አሁን ላይ<br />
በትብብር የሚጀምሩት ግንኙነትም<br />
ቀስ በቀስ ወደ ውህደት ሊያመራቸው<br />
ይችላል፤ ለውህደት የሚያደርሱ<br />
ስራዎችንም በዚያው ደረጃ በደረጃ<br />
እያከናወኑ መሄድ ይቻላል፡፡ በዚህ<br />
መልኩ የሚመጣ ውህደትም ዘላቂ<br />
እንደሚሆን መገመት ይቻላል፡፡ ያም<br />
ካልሆነ ደግሞ በትብብር መስራትን<br />
በመቀጠል አቅምን አጎልብቶ ወደ<br />
መሪነት መሸጋገር ትክክለኛ አካሄድ<br />
ይሆናል፡፡<br />
ከ ገፅ 3 የዞረ<br />
ከጅጋ ቋሪት ያለው የትራንፖርት ችግር<br />
ተገልጋዮችን ለስቃይ መዳረጉ ተገለፀ<br />
ጅጋ:- በምዕራብ ጎጃም ዞን ከጅጋ ከተማ<br />
እስከ ቋሪት ያለው የትራንስፖርት<br />
አገልግሎት ችግር ህዝቡን እያሰቃየ<br />
ነው ሲሉ ተሳፋሪዎች ገለጹ፡፡<br />
አራትና አምስት እጥፍ ክፍያ<br />
እንድንከፍል እንገደዳለን ያሉት<br />
ተሳፋሪዎች ‹በህገ-ወጥነት ተመዘበርን መንግስት<br />
ስርዓት ሊያስይዝልን ይገባል› የሚል ጥያቄ ስንጠይቅ<br />
ካልፈለጋችሁ አለመሳፈር ትችላላችሁ የሚል መልስ<br />
ከመንግስት አካላት ይሰጠናል ሲሉ ቅሬታቸውን<br />
ገልጸዋል፡፡<br />
24 ሰው የመጫን አቅም ያላቸው የአረጁና የወላለቁ<br />
መኪኖች እስከ 104 ሰው ድረስ ሲጭኑ ለህዝብ<br />
ህይወት በመቆርቆር እርምጃ የሚወስድ የመንግስት<br />
አካል አለመኖሩ እጅግ አሳዛኝ ነው ያሉት ተሳፋሪዎቹ፣<br />
የዚህን ህዝብ ሰቆቃና እንግልት ለማን አቤት እንደምንል<br />
አናውቅም ብለዋል፡፡<br />
መንግስት የመደባቸው ትራፊክ ፖሊሶች እንዲሁም<br />
የመንገድና ትራንስፖርት ሠራተኞች ተሳፋሪው<br />
ምንም አይነት መብት እንደሌለው ጫና ከማሳደርና<br />
የተሳፋሪውን ሰቆቃ ከማራዘም ውጭ በምንም ዓይነት<br />
ሁኔታ ግዴታቸውን ሲወጡ አናይም ብለዋል፡፡<br />
ጥቂት የወላለቁና ከጥቅም ውጭ የሆኑ መኪኖች<br />
የተመደቡለት ይህ መስመር መንግስት የዘነጋውና<br />
አመቱን ሙሉ ተሳፋሪ ህዝብ የሚንገላታበት ቦታ ሆኗል<br />
ሲሉ ያነጋገርናቸው ተሳፋሪዎች ጨምረው ገልፀዋል፡፡<br />
ፋሽስት ገዳይ ባየር...<br />
ታውቋል! ቀጥሏል! ቀጥሏል! ቀጥሏል! ወራሪው<br />
በማንአህሎኝነት መንፈስ ተረጋግቶ ተቀምጧል!<br />
ጀግናው ተሰማ እርገጤ አሁን ከወራሪው<br />
ኃይል ሰፈር በጣም ተጠግቷል! ብዙም ሳይቆይ<br />
ተኩስ ከፈተበት! ወራሪው ኃይል የሚይዘውና<br />
የሚጨብጠውን አጥቷል! ሆኖም ለጥቂት<br />
ደቂቃዎች ተታኩሷል! ወዲያው ግን ፈርጥጧል!<br />
ከጨለንቆ ደብረ ሲና ገብቷል! የጀግናው አርበኛ<br />
ተሰማ እርገጤ ድል አድራጊነት አሁንም<br />
ተረጋገጠ! ይህ በታሪካችን የጥንታዊት ኢትዮጵያ<br />
የጀግኖች አርበኞች የትግልና ድል ቀጥታ ድምጽ<br />
ነው! ከሸዋ ጠቅላይ ግዛት ጨለንቆ ከተባለ<br />
የውጊያ ሜዳ! መስከረም 19 ቀን 1929 ዓ.ም!<br />
ይህ ለዛሬው ወር ተረኛ ትውልድ የተላለፈ<br />
የጀግኖች አርበኞች ኢትዮጵያን የማዳን ተጋድሎ<br />
ታሪክ ቀጥታ ድምጽ ነው! ከአርበኝነት ገድላችን<br />
የተወሰደ!<br />
መስከረም አልቋል፡፡ ጥቅምትም አልፏል! አሁን<br />
በህዳር ወር ውስጥ መሆናችን ይመዝገብልን!<br />
ጀግናው አርበኛ ተሰማ እርገጤ አሁን ጉደ<br />
በረት ወረዳ የፋሽስት ወራሪ ኃይል የመሸገበትን<br />
ቦታ በመስክ መረጃ ለይቷል! ወራሪው ኃይል<br />
ከመሸገበት መንደር ደረሷል! አርበኞች ምድብ<br />
የውጊያ መስመራቸውን ይዘዋል! ከጥቂት<br />
ጊዜያት በኋላ እሳት ይዘንባል! አርበኞች ወደ<br />
ምሽጉ ተጠግተዋል! በጣም ቀርበዋል! ጊዜ<br />
አላጠፉም! የቅድሚያ ተነሳሽነት ወስደዋል!<br />
ወዲያው ጦርነቱ ተጋግሎ ቀጠለ! ጀግናው አርበኛ<br />
ተሰማ እርገጤ በርካታ የፋሽስት ኢጣሊያ ወራሪ<br />
ኢትዮጵያ ለምን ...<br />
ለማጣፈጥ ሲባል አዲስ ሰበካ ተጀምሯል። እኛ<br />
የምናካሂደው ትጥቅ ትግል የማንዴላ አይነት<br />
ትጥቅ ትግል ነው የሚል ማጭበርበሪያ። ጦርነት<br />
ጦርነት ነው። ይህን አባባል የሚያስተጋባው<br />
ቡድን በአንድ በኩል ተከታዮቹ መከተላቸውን<br />
እንዲቀጥሉ ለማድረግ ሲሆን በሌላ በኩል<br />
ደግሞ ሰላማዊ ትግል ካደረሰበት ትኩሳት<br />
ለጊዜው እረፍት ለማግኘት በሰላማዊ ትግል<br />
ንድፈ አሳብ ተማሪዎች እና ደጋፋዊዎች ላይ<br />
የከፈተው የማሸማቀቅ የስነ ልቦና ጦርነት ነው።<br />
መለስ ዜናዊ በምርጫ 97 የተቃሚው አሳብ<br />
የህዝብ ድጋፍ እያገኘ መሄዱን ሲያስተውል<br />
ደጋፊዎቹን ለማረጋጋት እና ተቃዋሚውን<br />
ለማሸማቀቅ ኢንተርሃምዌይ እስከማለት ደረሶ<br />
እንደነበር አስታውሳለሁ። አምባገነኖች ብዙ<br />
ከ ገፅ 8 የዞረ<br />
ኃይል ተዋጊዎችን በጥቂት ጊዜያት ከአፈር ጋር<br />
አዋህዷቸዋል! ታላቅ ጦርነት ሆነ! ከኢትዮጵያ<br />
ጀግኖች አስራ ሁለት አርበኞች በዚሁ ጦርነት<br />
ተሰውተዋል፡፡ በጀግንነት ወደ ታሪክ ወርደዋል!<br />
ጦርነቱ ቀኑን ሙሉ ቀጥሎ ውሏል! በዚህ<br />
ጦርነት ጀግናው ተሰማ እርገጤ በትከሻው ላይ<br />
በሁለት ጥይት ተመትቶ ቆስሏል፡፡ ብዙ ደምም<br />
ፈስሶታል! ጀግናው ተሰማ እርገጤ እስከ ጦርነቱ<br />
ፍጻሜ ዘጠኝ ጊዜ መቁሰሉ ታውቋል! የጉደ በረት<br />
ጦርነት እስከ ሌሊት ድረስ ቀጥሏል! በዚሁ<br />
ጦርነት ሰባ አምስት የፋሽስት ኢጣሊያ ወራሪ<br />
ኃይል መኮንኖችና ወታደሮች ተገድለዋል!<br />
ቆራጡ አርበኛ ተሰማ እርገጤ በአምስቱ<br />
የፋሽስት ኢጣሊያ ወረራ ዓመታት የተዋጋባቸው<br />
የጦር ሜዳዎች በጣም ብዙ ናቸው! በዚህም<br />
መሰረት ጥር ወር በ1929 ዓ.ም ባደረገው ውጊያ<br />
በርካታ የወራሪው ተዋጊዎችን በሞት ቀንሷል!<br />
እንዲሁም በየካቲት ወር 1929 ዓ.ም በሞፈር<br />
ውሃ ላይ በተደረገው ጦርነት ብዙ ፋስስቶችን<br />
ገድሏል! በዚህ ብቻም አላበቃም! በመጋቢት ወር<br />
1929 ዓ.ም ገዘት በተባለ ቦታ ጦርነት አድርጎ<br />
በርካታ የወራሪው ኃይል አባላትን ደምስሷል!<br />
አሁንም በመቀጠል በሚያዚያ ወር 1929<br />
ዓ.ም በመንዝ ውስጥ ወይራ ገበያ በተባለ ቦታ<br />
የተደራጀውን የወራሪውን ኃይል ተዋጊ ድባቅ<br />
መትቷል! የጦር መሳሪያም ማርኳል! ጀግናው<br />
አርበኛ ተሰማ እርገጤ አሁንም በጽኑ የውጊያ<br />
ስነ-ልቦና ይስተዋላል! ቀጥሏል! ግንባሩን ሳያጥፍ<br />
ቀን ከሌት ይዋጋል! በዚህ ሂደት ሐምሌ 18<br />
ከ ገፅ 9 የዞረ<br />
ይላሉ። የሚሉት ሁሉ ግን ከአጭር ጊዜ<br />
መፍትሄነት ባሻገር አይረዳቸውም። ይሄም ያን<br />
አይነት የስነ ልቦና ጦርነት ነው። የአለም ህዝብ<br />
ለማንዴላ ክብር የለገሰው ጠበንጃ በማንሳቱ<br />
አይደለም። በሃውልቱም ላይ የሚጻፈው ጦረኛ<br />
መሆኑ አይደለም።<br />
ቤተሰቡም እስከ ልጅ ልጆቹ ድረስ በአደባባይ<br />
ስለማንዴላ የሚሰብኩት ሰላማዊነቱን እና<br />
በሰላማዊ መንገድ አፓርታይድን እንዳፈረሰ<br />
ነው። አፓርታይድ የፈረሰው በትጥቅ ትግል<br />
አይደለም። የደቡብ አፍሪካ የመጀመሪያው<br />
ጥቁር ፕሬዘዳንት ሊሆን የቻለው በትጥቅ<br />
ትግል አይደለም። ጥቁር እና ነጭ ደቡብ<br />
አፍሪካውያን በህብረት ያደረጉት ሰላማዊ<br />
ትግል መዘንጋት የለበትም። ታዋቂ ጥቁር እና<br />
እና 22 ቀን 1929 ዓ.ም ግንደ በረት ላይ ክልቤ<br />
በተባለ ቦታ ተዋግቶ ድል ማድረጉን የአርበኝነት<br />
ታሪኩ ያመለክታል፡፡ በመቀጠልም ሺኖ በተባለ<br />
ቦታ ተዋግቶ አኩሪ ውጤት አስመዝግቧል!<br />
ቆፍጣናው አርበኛ ተሰማ እርገጤ በመቀጠልም<br />
በሰላሌ አውራጃ ውስጥ ኩዩ ጊዮርጊስ በተባለ<br />
ቦታ ከወራሪው ኃይል ጋር ተዋግቶ ድል<br />
አስመዝግቧል! ለሁለት ቀናት በተካሄደው በዚሁ<br />
ጦርነት በርካታ የወራሪው ኃይል ተዋጊዎቹን<br />
መግደሉ ታውቋል! እንዲሁም መስከረም 12<br />
ቀን 1930 ዓ.ም ተዋግቶ ወራሪው ኃይል<br />
እንዲፈረጥጥ አድርጓል! በተመሳሳይ መልኩ<br />
መስከረም 15 ቀን 1930 ዓ.ም ተዋግቶ ድል<br />
ተቀዳጅቷል!<br />
ጅግናው አርበኛ ተሰማ እርገጤ እስከ ጦርነቱ<br />
ፍጻሜ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ውስጥ በወራሜ<br />
በላሎ ምድር በአይት በተጉለት ወረዳ አምባ<br />
ሞሻ፣ በከሴ ቆላ አቦ ጉር ህዳባይ፣ በላሎ<br />
ምድር ኪደር በምሐይና በአንጉቦላ ቀበሌዎች<br />
እየተዘዋወረ ከፍተኛ ጀብዱ ፈጽመዋል!<br />
የታወቀው ጀግና ተሰማ እርገጤ ከድል በኋላ<br />
የአምስት ዓመት የአርበኝነት ኒሻን ባለአምስት<br />
ዘንባባ ተሸልሟል! እንዲሁም የድል ኮከብ<br />
ሜዳይ አግኝቷል! በተመሳሳይ መልኩ የቅዱስ<br />
ጊዮርጊስ ሜዳይ ባለሁለት ዘንባባ ተሸልሟል፡፡<br />
ጀግናው የኢትዮጵያ ልጅ ተሰማ እርገጤ ከአባቱ<br />
ከባሻ እርገጤ ሀብተ-ገብርኤልና ከእናቱ ወይዘሮ<br />
ወለተ አረጋይ ጨድድ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት<br />
በይፋት ውስጥ ሐር አምባ በተባለ ቀበሌ በ1888<br />
ነጭ ደቡብ አፍሪካውያን አርቲስቶች የአለምን<br />
ህዝብ በአፓርታይድ ላይ ለማስተባበር<br />
ያደረጉት ቀጣይነት ያለው አለም አቀፍ<br />
ሰላማዊ ዘመቻቸው መዘንጋት የለበትም።<br />
ማንዴላን ለማስፈታት እና አፓርታይድን<br />
ለማስፈታት የአለም ህዝብ ያደረገው ሰላማዊ<br />
ትግል መዘንጋት የለበትም። በማንዴላ<br />
ሃውልት ላይ የሚጻፈው የጦር አበጋዝነቱ እና<br />
የገደለው ሰው ቁጥር ሳይሆን ማንዴላ ከእስር<br />
ቤት ከወጣ በኋላ የፈጸመው ነው።<br />
በመጨረሻ ወደ ኢትዮጵያ ልመለስ እና<br />
ጽሁፌን ልደምድም። ሰላማዊ ትግል ሰላማዊ<br />
ሰልፍ ማድረግ ብቻ አይደለም። ሰላማዊ<br />
ትግል በምርጫ መሳተፍ ብቻ አይደለም።<br />
ሰላማዊ ትግል በአደባባይ ወጥቶ መቃወም<br />
ዓ.ም ተወለደ፡፡ በልጅነቱ አማርኛ ተምሯል፡<br />
፡ ማይጨው ዘምቷል! ግዳጁን ተወጥቷል!<br />
ከማይጨው መልስ የይፋትን ህዝብ ለጦርነት<br />
አስተባብሯል! ቆፍጣናው ጀግና ተሰማ እርገጤ<br />
ሰኔ 23 ቀን 1964 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት<br />
ተለይቷል፡፡ ጀግናው ተሰማ እርገጤ በህይወት<br />
ዘመኑ ሰባት ልጆችን አፍርቷል፡፡ ጀግናው<br />
አርበኛ ተሰማ እርገጤ ከዚህ ዓለም በሞት ሲለይ<br />
ባህላዊ ወታደራዊ ማዕረጉ ደጃዝማች እንደነበር<br />
ታውቋል!<br />
ውድ የኢትዮጵያ ወጣት ሆይ በቀደምት<br />
የኢትዮጵያ ጀግኖች መስዋዕትነት ታፍራና<br />
ተከብራ የኖረችው ሀገራችን ተዋርዳለች! ሀገር<br />
ለመሸጥ ደላላ ኮሚሽን ተቋቁሟል! ስለዚህ<br />
ወጣቱ ትውልድ የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ<br />
ጠንቅቆ በማወቅ ህሊናዊ ሁኔታዎችን ለማሳደግ<br />
ሊነሳ ይገባል! እርግጥ ነው ሀገርን ጠብቆ<br />
በክብር ለመጪው ትውልድ ማስረከብ የዜጎች<br />
ሁሉ ግዴታ ይሆናል፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያን<br />
ከጠቅላላ ውድቀት ለማዳን በቁርጠኝነትና በዓላማ<br />
ጽናት በተግባር እንነሳ! ክብር ለቆራጡ አርበኛ<br />
ለደጃዝማች ተሰማ እርገጤ! ክብር በአምስቱ<br />
የፋሽስት ኢጣሊያ ወረራ ዓመታት በዱር<br />
በገደሉ ለወደቁ ጀግኖች! ክብር ዛሬም ከዕለታዊ<br />
ጥቅምና ጊዜያዊ ተድላ ርቀው ለኢትዮጵያ ነጻነት<br />
በመታገል ላይ ለሚገኙ ቆራጦች! ኢትዮጵያዊ<br />
ብሄርተኝነት ያሸንፋል!<br />
ብቻ አይደለም። ሰላማዊ ትግል እነዚህን ሁሉ<br />
ማድረግ ነው። በተጨማሪ ሰላማዊ ትግል<br />
ህዝብን የራሱ ነፃ አውጭ በማድረግ (1)<br />
በስልጣን ላይ የሚገኝን አምባገነን መንግስት<br />
አስወግዶ ህዝብን የመንግስት ስልጣን ባለቤት<br />
ማድረግን፣ (2) መፈንቅለ መንግስት ቢነሳ<br />
ትብብር መንፈግ፣ (3) እንደ ህውሃት/<br />
ኢህአዴግ ከጫካ ወይንም ከጎረቤት አገር<br />
(ኤርትራን ጨምሮ) ተነስቶ ልውረርህ የሚል<br />
ቡድን ቢመጣ ህዝባዊ መከላከል (Civil Resistance)<br />
ማድረግን ያካትታል። ሰላማዊ<br />
ትግልን በሚመለከት ግንዝቤያችን ሰፋ ያለ<br />
መሆን አለበት። የቀድሞው የመንግስት<br />
ሽግግር ባህላችን ደደብ ነው። ብልህ ሰዎች<br />
አይከተሉትም።<br />
እንዲሆን በማሰብ ፓርቲው ቀኑን መዘከር አስፈላጊ<br />
መሆኑን ያምናል ብለዋል፡፡ በዕለቱ በሁለቱም<br />
ፕሮግራሞች ላይ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ እንዲሳተፍ<br />
አቶ ብርሃኑ ጥሪ አቅርበዋል፡፡<br />
ሰማያዊ ፓርቲ በ2005 ዓ.ም ጣሊያኖች በወገኖቻችን<br />
ላይ ከፍተኛ በደል የፈጸመውን ሮዶልፍ ግራዚያኒ<br />
በትውልድ ከተማው ‹የጀግና› ሐውልት በማቆም<br />
ዕውቅና መስጠታቸውን በመቃወም ሰላማዊ የተቃውሞ<br />
ሰልፍ በአዲስ አበባ መጥራቱን ተከትሎ በቦታው የተገኙ<br />
አባላቱ ለእስር መዳረጋቸው የሚታወስ ነው፡፡<br />
በጎንደር በተካሄደው...<br />
ከ ገፅ 1 የዞረ<br />
ያስተባበሩት የአካባቢው የፓርቲው መዋቅር አካላት<br />
ደህንነቶች ለቤተሰቦቻቸው ደውለው እያስፈራሩዋቸው<br />
መሆኑን የፓርቲው የዞን ሰብሳቢ አቶ አግባው ሰጠኝ<br />
ለዝግጅት ክፍላችን ገልጸዋል፡፡<br />
ፓርቲው ጥር 25 በጎንደር ከተማ መስቀል አደባባይ<br />
በጠራው ሰልፍ፣ የኢትዮ-ሱዳን የድንበር ማካለል<br />
ሂደትን በተመለከተ መንግስት ለህዝብ ጉዳዩን ግልጽ<br />
እንዲያደርግና ሉዓላዊነትን እንዲያከብርና እንዲያስከብፈር<br />
መጠየቁ ይታወሳል፡፡
7 የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2 ነገረ-ኢትዮጵያ<br />
መሬት ያስቆረሱት የመለስና ተከታዮቹ<br />
እኩይ ስምምነቶች<br />
አለማየሁ ገ/ማርያም (ፕ/ር)<br />
የአሁኑ አስገራሚ ጊዜ ሸክስፒር፣ ‹ጁሊየስ<br />
ቄሳር› በሚለው ፅሁፉ ላይ ለተናገረው አነጋገር<br />
ልዩ ትርጉም ይሰጠዋል፣ “ሰዎች የሰሩት ተንኮል<br />
ከመቃበራቸው በላይ ህያው ሆኖ ይኖራል” ብሎ<br />
ነበር ሸክስፒር፡፡ በአሁኑ ጊዜ አቶ መለስ ዜናዊ<br />
በህይወት በነበሩበት ጊዜ ከሰሩት ተንኮሎችና<br />
ጭራቃዊነት የሞላው አስቀያሚ ተግባር ውርስ<br />
ጋር ፊት ለፊት ተፋጥጠን እንገኛለን፡፡ የኢትዮጵያ<br />
ሉዓላዊ የግዛት አካል ተቆርሶ እንደገና ለሽያጭ<br />
ለሱዳን ቀርቧል፡፡ ይህንንም ጭራቃዊነት ተንኮል<br />
የቀበሮ ባህታውያኑ “የድንበር ማካለል“ ብለው<br />
ይጠሩታል፡፡ እኔ ደግሞ ድንበር መቁረስ፣<br />
መቆራረስ፣ መሽረፍ እና መሸራረፍ ብዬ<br />
እጠራዋለሁ፡፡ ባጭሩ ኢትዮጵያን ለቅርጫ<br />
ማቅረብ እለዋለሁ… ደግሞ ለሰላሳ ቁርጥራጭ<br />
የመዳብ ዲናሮች! እ.ኤ.አ በ2008 “የኢትዮጵያ<br />
ጋሻ“ ተብሎ በሚጠራው የሰሜን አሜሪካ የሲቪል<br />
ማህበረሰብ ስብስብ ጉባኤ ላይ በመገኘት የእናት<br />
አገር ኢትዮጵያን ሉዓላዊነት መጠበቅ በሚል<br />
ርዕስ ስሜትን የሚቀሰቅስ ንግግር አድርጌ ነበር፡፡<br />
አቶ መለስ የአሰብን ወደብ አሳልፈው በሰጡበት<br />
ወቅት ዝምታን በመምረጣችን ወደብ አልባ<br />
የመሆንን ዋጋ ከፍለናል፡፡ እ.ኤ.አ በ1998 ባድመ<br />
ተወረረች፣ እናም የ80,000 ኢትዮጵያውያን<br />
ህይወትን የበላ መስዋዕትነት ተከፍሎ<br />
ጠላቶቻችን ከግዛታችን እንዲወጡ ተደረገ፡<br />
፡ ሆኖም ግን አቶ መለስ በብርሃን ፍጥነት<br />
ተገልብጠው የኢትዮጵያን አንጸባራቂ የጦር<br />
ሜዳ ድል ቀልብሰው የዲፕሎማሲያዊ ሽንፈትን<br />
በመጋት በእርቅ ሰበብ ስም ባድመን ለወራሪው<br />
ኃይል አሳልፈው ለመስጠት ስምምነት አደረጉ…<br />
(ዛሬ) በምዕራብ ኢትዮጵያ የሚኖሩ ወገኖቻችን<br />
በግልጽ እንደነገሩን የአያት ቅድመአያቶቻቸውን<br />
መሬት እና መኖሪያ ቤታቸውን ሳይቀር አቶ<br />
መለስ ለሱዳኑ አምባገነን [በዓለም አቀፉ<br />
የወንጀለኞች ፍርድ ቤት በወንጀል ለሚፈለጉት<br />
እና ከፍትህ ለማምለጥ እራሳቸውን በመደበቅ<br />
ተወሽቀው ላሉት] መሪ ኦማር አልባሽር<br />
አሳልፈው ለመስጠት በሚስጥር ስምምነት<br />
ፈጽመዋል…ያንን ንግግር ካደረግሁ ከስድስት<br />
ዓመታት በኋላ እንኳን በሚያሳዝን ሁኔታ እናት<br />
አገራችንን ለመበታተን አቶ መለስ ከበረሃ ውስጥ<br />
ነድፈው ያመጡትን ጭራቃዊ ዕቅድ እኩይ<br />
ምግባር ለመቀልበስ ባለመቻላችን አዝናለሁ፡፡<br />
አቶ መለስ አሁን በህይወት የሉም፣ ሆኖም ግን<br />
እኛን እንዲያጠፋ ጥለውት ከሄዱት ተንኮላቸው<br />
ስራቸው ጋር ፊት ለፊት ተጋትረናል፡፡ “መልካም<br />
ሰዎች ዝም ስላሉና ምንም ባላማድረ ጋቸው<br />
ይሆን ተንኮል የሚበረታው” የሚለው አባባል<br />
እውነታነት አለውን? በመጨረሻም ተንኮልና<br />
ጭራቃዊነት ድል ተጎናጽፏልን?<br />
ኢትዮጵያ በአቶ መለስ ዜናዊ ቅርጫ መግባት<br />
እ.ኤ.አ ዴሴምበር 2013 የሱዳን የውጭ ጉዳይ<br />
ሚኒስትር የሆኑት ዓሊ ካርቲ የኢትዮጵያ<br />
እና የሱዳን ገዥ አካላቶች “ፋሻጋ እየተባለ<br />
በሚጠራው አካባቢ የነበረውን የድንበር<br />
አለመግባባት እና በሌሎች አካቢዎችም ያሉትን<br />
የድንበር ማካለል ስራዎችንም በሰላማዊ<br />
መንገድ ለማጠናቀቅ ስምምነት አድርገናል“<br />
በማለት በግልጽ ተናግረዋል፡፡ ስለሁለቱ አገር<br />
መሪዎች አስመልክቶ ካርቲ እንዲህ ብለዋል፣<br />
“የመጨረሻውን የማካለል ስራ ለመተግበር<br />
ታሪካዊ ስምምነት አድርገናል፡፡“ የሱዳን የውጭ<br />
ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት በኢትዮጵያ እና<br />
በሱዳን መካከል ያሉትን “የድንበር ውዝግቦች”<br />
በማስመልከት ለሚቀርቡ አስተያየቶች ሁሉ<br />
ምንም ዓይነት ሀሳብ እንደማይቀበል ጠቅሶ<br />
ሲናገር፣ “በጠረፉ በተወሰኑ የወሰን ድንበር ነጥብ<br />
ቦታዎች ላይ“ በጣም ቀላል የሆኑ አለመግባባቶች<br />
ከመኖር በስተቀር ሌላ ችግር እንደሌለ አስረግጠው<br />
ተናግረዋል፡፡ ባለፉት ሳምንታት የኢትዮጵያ<br />
የውጭ ግንኙነት መምሪያ እንደ ዔሌ አንገቱን<br />
ብቅ ጥልቅ እያደረገ በድብቅነት እና ማደናገር<br />
በተላበሰ ስልት/strategy “የድንበር ማካለሉን<br />
ጉዳይ“ እና “መጠነ-ሰፊ ጠቀሜታ“ አላቸው እያለ<br />
ከበሮ የሚደልቅላቸውን “የደህንነት ትብብር<br />
ስምምነት፣ የኢኮኖሚ፣ የግብርና፣ የትምህርት<br />
እና የባህል“ “የስትራቴጅክ ስምምነት ማዕቀፍ“<br />
በማለት በሚጠራቸው ጉዳዮች ላይ እምነት<br />
እንዲያድርብን የፕሮፓጋንዳ ዘመቻዎችን<br />
በመሰለቅ ጊዜውን በከንቱ አሳልፏል፡፡<br />
እ.ኤ.አ በ2001 “ለድንበር ውዝግቡ” ይሰጡ<br />
የነበሩት ምክንያቶች አሁን እየተሰጡ ካሉት<br />
ምክንያቶች ፍጹም የተለዩ ነበሩ፡፡ በዚያን ጊዜ<br />
የሱዳን ገዥ አካል እንደገለጸው የድንበር ማካለሉ<br />
ስራ አስፈላጊነቱ “የአልቃዳሪፍን ግዛት በሰሜን<br />
ኢትዮጵያ ከሚገኘው የትግራይ ግዛት ጋር<br />
‘ለማልማት እና ለማቆራኘት‘ የሚል ነበር…<br />
ሁለቱ አካባቢዎች በጣም ለም የነበሩ ሲሆኑ፣<br />
ከዚህም በላይ አልቃዳሪፍ ለሱዳን የዳቦ ቅርጫት<br />
ተደርጎ የሚቆጠር ነበር… ከአልቃዳሪፍ እስከ<br />
መቀሌ ያለው የመኪና መንገድ…እየተጠገነ እና<br />
ደረጃው ከፍ እየተደረገ ነው… የትግራይ ግዛት<br />
ከዚህ በመነሳት በዚህ በኩል ወደ ቀይ ባህር<br />
የሚያሸጋግረው ዕድል ስለሚያገኝ እና አልቃዳሪፍ<br />
ደግሞ ከፖርት ሱዳን ጋር የሚያገናኘው ስለሆነ<br />
ተቃሚ ይሆናል፡፡ በዚህም መሰረት ፖርት ሱዳን<br />
ለመቀሌ በኤርትራ ግዛት ከሚገኘው የአሰብ<br />
ወደብ እና በሶማሌ ግዛት ከሚገኘው የበርበራ<br />
ወደብ የበለጠ ቅርብ ትሆናለች…“ የሚል ነበር፡፡<br />
እ.ኤ.አ በ2008 አቶ መለስ ዜናዊ ከሱዳን ጋር<br />
የተደረገውን “ስምምነት” አስመልክቶ በውሸት<br />
ባህር ውስጥ እየተንቦጫረቁ የጭቃ ጅራፋቸውን<br />
ማጮህ ጀመሩ፡፡ በዚያው ዓመት በግንቦት ወር<br />
ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው<br />
ሙልጭ አድርጎ በመካድ ለመጀመሪያ ጊዜ<br />
አንድም ጋት የሚሆን የኢትዮጵያን መሬት<br />
ለሱዳን አሳልፎ ለመስጠት የተደረገ ስምምነት<br />
የለም የሚል መግለጫ ሰጠ፡፡ ያ መግለጫ<br />
በውጭ የሚገኙትን “የዜና አውታሮች” እና<br />
“ኃላፊነት የማይሰማቸው” በበሬ ወለደ የፈጠራ<br />
ወሬ የተሰማሩ ሽብር እና ፍርሀትን በህብረተሰቡ<br />
ዘንድ የሚነዙ አሸባሪዎች ናቸው በማለት<br />
ከሷቸው ነበር፡፡ የሱዳን ባለስልጣኖች ግን ያንን<br />
መግለጫ በሚጻረር መልኩ “ከኢትዮጵያ መሬት<br />
እንዳገኙ“ በይፋ በአደባባይ ተናግረዋል፡፡ በግንቦት<br />
አጋማሽ አቶ መለስ እና አጫፋሪዎቻቸው<br />
የመሬት ማደሉን ሚስጥር ደብቀው ማቆየት<br />
ባለመቻላቸው ወደ ቀድሞው ታሪካቸው<br />
ለመመለስ ተገደዋል፡፡ በድንበር ማካለሉ ወቅት<br />
አንዳንድ የቅድመ ስራ እንቅስቃሴዎች ብቻ<br />
እንደተከናወኑ፣ እናም የተጠናቀቀ ነገር የለም<br />
በማለት በግልጽ ተናግረዋል፡፡ በቀናት ጊዜ<br />
ውስጥ አቶ መለስ እና አጫፋሪዎቻቸው ሌላ<br />
አዲስ ቅጥፈትን ፈብርከው ብቅ አሉ፡፡ የሆነው<br />
“ቀደም ሲል በንጉሱ እና በደርግ ዘመን ከሱዳን<br />
ጋር የተደረጉ ስምምነቶችን ተግባራዊ አደረግን”<br />
ብለው ጭራ ቀረሽ ዉሸት ፈጠሩ፡፡<br />
የኢትዮ ሱዳን የድንበር ጉዳይ ኮሚቴ ጉዳዩን<br />
በግልጽ ሲያቀርበው እና በተጨባጭ በድንበሩ<br />
ባሉ አካባቢዎች ላይ ምን እየተደረገ እንዳለ ይፋ<br />
ሲያደርግ እስከ አፍ ጢሙ ተቀብትቶ/ሞልቶ<br />
የነበረው የውሸት ጎተራ መፈረካከስ ጀመረ፡፡<br />
በአቶ መለስ ለሱዳን መሬት ዕደላ ፖሊሲ<br />
ምክንያት የተጎዱ ዜጎቻችን ለአሜሪካ ድምጽ<br />
የአማርኛው አገልግሎት እና ለሌሎች ዓለም<br />
አቀፍ ብዙሃን መገናኛ ተቋማት ቃለመጠይቅ<br />
መስጠት ጀመሩ፡፡ በመሬት ዕደላው ምክንያት<br />
ቀጥተኛ ተጎጅ የሆኑ ወገኖቻችን አያት ቅደመ<br />
አያቶቻቸው ጠብቀው ያቆዩት መሬት በሱዳን<br />
ኃይሎች እየተወረረ ይዞታቸው ሲወሰድባቸው<br />
እና ከቀያቸው እና እትብቶቻቸው ከተቀበሩባቸው<br />
ቦታዎች ሲባረሩ የነበረውን ሁኔታ በመረረ<br />
አኳኋን የተሰማቸውን ቅሬታ በሰፊው ማሰማት<br />
ጀመሩ፡፡ የእርሻ መሳሪያዎቻቸው እና የመገልገያ<br />
ቁሳቁሶች በሱዳን ወራሪ ኃይሎች መወረሱን<br />
ገለፁ:: እንዲሁም በርካታ ኢትዮጵያውያን<br />
በሱዳን እስር ቤቶችም ታስረው እንዲማቅቁ<br />
አስታወቁ፡፡ በዚያን ጊዜ አቶ መለስ ምንም<br />
ምርጫ አልነበራቸውም፣ በግዴታ ሳይወዱ<br />
መሬት ለመስጠት ከሱዳን ጋር መፈራረማቸውን<br />
ለማመን ተገደዋል፡፡ እ.ኤ.አ በሜይ 2008<br />
አቶ መለስ ከኦማር አልባሽር ጋር ያደረጉትን<br />
ስምምነት እንዲህ በማለት ይፋ አድርገዋል፣ “እኛ<br />
ኢትዮጵያውያን እና የሱዳን መንግስት የድንበር<br />
ማካለሉ ስራ በሚሰራበት ወቅት ከሁሉቱም<br />
ወገን አንድም ዜጋ እንዳይፈናቀል ለማድረግ<br />
ስምምነት ተፈራርመናል… በ1996 የወሰድነውን<br />
መሬት መልሰን ለሱዳን ሰጥተናል፣ ይህ መሬት<br />
ከ1996 ዓ.ም በፊት የሱዳን ገበሬዎች ይዞታ<br />
ነበር፡፡ አንዳንድ የብዙሃን መገናኛ ተቋማት<br />
እንደሚያናፍሱት ሳይሆን በድንበሩ ዙሪያ አካባቢ<br />
አንድም የተፈናቀለ ዜጋ የለም፡፡” እ.ኤ.አ በ2008<br />
በዊክሊስ (የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ አመራር<br />
ሚስጥር ሰነድ) ሌላ ወሳኝ የሆኑ መረጃዎች<br />
ይፋ ተደርገዋል፡፡ “የቀድሞው የህዝባዊ ወያኔ<br />
ሃርነት ትግራይ ማዕከለዊ ኮሚቴ አባል እና<br />
የቀድሞው የመከላከያ ሚኒስትር የነበሩት አቶ<br />
ስዬ አብርሃ እንዲህ በማለት ተናግረዋል፣ ‘አቶ<br />
መለስ በኢትዮጵያ እና በሱዳን መካከል ተፈጥሮ<br />
የነበረውን የድንበር ውዝግብ ውጥረት ለማርገብ<br />
ጥረት በሚያደርጉበት ወቅት “ለአማራ ክልል<br />
ትልቅ ዋጋ ሊያስከፍል የሚችል ግዙፍ መሬት“<br />
አቶ መለስ ለሱዳን ሰጥተዋል፡፡ እናም የአቶ<br />
መለስ አገዛዝ “በድብቅ ይዞ ለማቆየት ሞክሯል”<br />
አሉ አቶ ስዬ አብርሃ::<br />
ቀደም ሲል አቶ መለስ፣ አሁን ደግሞ የዕኩይ<br />
ምግባር ውርስ አጫፋሪዎቻቸው ያንን ስምምነት<br />
“በድብቅ ይዘው ለማቆየት” በመውተርተር እና<br />
በመዳከር ላይ ይገኛሉ፡፡ ሆኖም ግን እ.ኤ.አ<br />
በ2008 አቶ መለስ ከኦማር አልባሽር ጋር<br />
ባደረጉት ስምምነት ላይ የሰጡት መግለጫ<br />
አንዳንድ ጠቃሚ ምልክቶችን ይሰጣል፡፡<br />
እራሳቸው አቶ መለስ ባመኑት እ.ኤ.አ በግንቦት<br />
2008 በእርሳቸው እና በኦማር አልባሽር መካከል<br />
በተደረገው “የመሬት መስጠት ስምምነት”<br />
ዝርዝር የስምምነቱን ሁኔታ የሚያመላክት<br />
መሆኑ የሚያጣያይቅ አይደለም፡፡ “የስምምነቱን”<br />
ሁኔታ ስናጠናው አቶ መለስ በስምምነት መዝገቡ<br />
ላይ በርካታ ጠቃሚ ማስረጃዎችን አስቀምጠዋል፡<br />
፡ “ስምምነቱ” 1ኛ) መሬቱ በሚሰጥባቸው<br />
አካባቢዎች ሰዎችን ሊያፈናቅል የሚችል ጥያቄ<br />
መነሳት እንደሌለበት 2ኛ) ከድንበር ማካለሉ<br />
ጉዳይ ጋር በተያያዘ መልኩ ከማካለል ስራው<br />
ጋር ተያይዞ ጉዳት የሚደርስባቸውን ሰዎች<br />
ጥቅሞች የማስጠበቅ ሁኔታ መኖር እንዳለበት<br />
3ኛ) በኢትጵያውያን ገበሬዎች በህገወጥነት<br />
መልክ ተይዞ የነበረ የተባለውን መሬት ለሱዳን<br />
ገበሬዎች የባለቤትነት መብትን ማስጠበቅ 4ኛ)<br />
በ1996 ዓ.ም በህገወጥ መልክ በኢትዮጵያውያን<br />
ተይዞ የነበረውን መሬት ለሱዳናውያን መመለስ<br />
የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡<br />
በአቶ መለስ ፈቃድ እና አዛዥነት በእራሳቸው እና<br />
በኦማር አልባሽር የተፈረመው መሬት የመስጠት<br />
ስምምነት “የ1902 የግዌን መስመር/Gwen<br />
Line of 1902” (የ1902 የአንግሊዝ-ኢትዮጵያ<br />
ስምምነት) እየተባለ የሚጠራው “በኢትዮጵያ<br />
እና በሱዳን መካከል ያለውን ድንበር” መስመር<br />
ማስያዝ ከሚለው ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት<br />
እንደሌለው መገንዘብ ሊሰመርበት የሚገባ ጉዳይ<br />
ነው፡፡ እንደዚሁም እ.ኤ.አ ከ1974 በፊት በንጉሱ<br />
ዘመን እና በደርግ ዘመን ከ1995 እስከ 1991<br />
ድረስ የተረቀቁ እና የተፈረሙ የድንበር መካለል<br />
ወይም ደግሞ መፍትሄ መስጠት ስምምነቶች ካሉ<br />
ከዚህ ስምምነት ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት<br />
የላቸውም፡፡ እ.ኤ.አ ከ1996 መጀመሪያ አካባቢ<br />
ጀምሮ አቶ መለስ በእራሳቸው ፈቃድ ከድንበር<br />
እና ተመሳሳይ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ መልኩ<br />
ያደረጉት “ስምምነት” በአቶ መለስ ግላዊ አተያይ<br />
የሱዳን መሬት በኢትዮጵያውያን በኃይል የተቀማ<br />
ነው በማለት በግላቸው ያደረጉት ህገወጥ እርምጃ<br />
እንጅ ሌላ ምንም ዓይነት ማስረጃ የሌለው<br />
እርባናቢሰ ስብከት መሆኑ በውል ሊጤን ይገባል፡<br />
፡<br />
የኢትዮጵያን “ግዙፍ መሬቶች” በድብቅ እና<br />
ለህዝብ ይፋ ሳያደርጉ በሚስጥር ለሱዳን<br />
የሚሰጡበት፡፡<br />
ምንድን ነው?<br />
የድንበር “ስምምነት” ምክንያቱ<br />
አቶ መለስ እና አቶ ኃይለማርያም በአጠቃላይ<br />
“በድንበር ስምምነቱ” ዙሪያ እያቀረቡት የነበረው<br />
እና ያለው የውሸት ፍብረካ ድሪቶ ሪፖርት<br />
እውነታውን ለመደበቅ ከሚሽመደመደው ድሁር<br />
አስተሳሰባቸው ያለፈ ፋይዳ አይኖረዎም፡<br />
፡ እውነተኛው የድንበር መስጠት ስምምነት<br />
እ.ኤ.አ በ2008 ተጠናቁአል፡፡ በምንም ዓይነት<br />
መልኩ ቢሆን አቶ መለስ “ግዙፍ የሆነ<br />
መሬት ከአማራ ክልል” ቆርሰው ፈርመው፣<br />
አትመው እና አሽገው ለሱዳን መስጠታቸውና<br />
በድብቅ “በድብቅ ተይዞ እንዲቆይ” መጣራቸው<br />
የሚያጠያየቅ ጉዳይ አይደለም፡፡ እ.ኤ.አ በ2014<br />
የኢትዮጵያ የይስሙላው ጠቅላይ ሚኒስትር<br />
አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የአቶ መለስን የበከተ<br />
ውሸት እንደተለመደው “በሀሰት መጋረጃ<br />
ደብቀው” ለዘላለም ለማቆየት በማሰብ ሌላ ዘርዘር<br />
ያለ ፖለቲካዊ ድራማ ለመተወን በመውተርተር<br />
ላይ ይገኛሉ፡፡ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ እና<br />
ጌቶቻቸው የኢትዮጵያን ህዝብ ሊያታልሉ፣<br />
ሊያጭበረብሩ እና በውሸት ሊደልሉ የሚችሉ<br />
ይመስላቸዋል፡፡ እነዚህ የዕኩይ ምግባር ባለቤቶች<br />
መሬትን ያህል ነገር በድብቅ ሸፍኖ የመስጠት<br />
ጨዋታቸውን ኢትዮጵያውያን የማያውቁ እና<br />
የማይገነዘቡ ሞኞች አድርገው ይቆጥራሉ፡<br />
፡ እነርሱ ይህን የሞኝነት ጨዋታቸውን<br />
እንደፈለጉ መጫወት ይችላሉ፣ ሆኖም ግን<br />
አቶ ኃይለማርያም አንድ ጥያቄ እንዲመልሱልኝ<br />
እፈልጋለሁ፣ ይኸውም “ ‘ከአማራ ክልል ግዙፍ<br />
መሬቶችን ቆርሰው የሰጡት’ “ድብቅ የሚስጥር<br />
ስምምነቶችን የት እንዳስቀመጧቸው ሊያሳዩኝ<br />
ይችላሉን? አቶ መለስ እ.ኤ.አ በ2008 እና<br />
አሁን ደግሞ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ እና<br />
የዕኩይ ምግባር አጋሮችዎ የድብቅ ስምምነቶችን<br />
ከህዝብ ፊት ደብቃችሁ ከፊታችሁ ላይ የውሸት<br />
መጋረጃ በማድረግ ለመዝለቅ የምትፈልጉት<br />
ለምንድን ነው?” ከአገር መሬት ቆርሳችሁ<br />
ለባዕድ አገር ስትሰጡ በአገሪቱ ህገመንግስት<br />
ስልጣን ለተሰጠው ፓርላማ (ለተወካዮች ምክር<br />
ቤት) ተብዬው ለይስሙላ እንኳን ቢሆን መቅረብ<br />
የለበትምን“? ህገመንግስቱ የሚለው ሌላ የስርዓቱ<br />
ቁንጮዎች የሚያደርጉት ሌላ! አራምባ እና ቆቦ!<br />
ከላይ ለቀረቡት ጥያቄዎች መልሱ ቀላል ነው፣<br />
እ.ኤ.አ 2008 አቶ መለስ የተናገሩለት “የሚስጥር<br />
ስምምነት“ እና አሁን ደግሞ አቶ ኃይለማርያም<br />
እያነበነቡት እንዳለው አይደለም እውነታው፡፡<br />
ህዝብ ግብር እየከፈለ በሚያስተዳድራቸው መገናኛ<br />
ብዙሀን ብቅ እያሉ በእብሪት የሚያሰራጩት<br />
ነጭ ውሸት ነው፡፡ በእርግጥ አቶ መለስ ይዋሻሉ<br />
ማለት “መለስ ወይስ መቀልበስ” መጠሪያ<br />
ስማቸው ነው፡፡ ሁሉም አፍጥጠዉ ይዋሻሉ፡<br />
፡ አቶ መለስ እና አቶ ኃይለማርያም ከኦማር<br />
አልባሽር ጋር በስምምነቶች ላይ ያስቀመጧቸው<br />
ቃላት፣ ሀረጎች እና ዓረፍተ ነገሮች ወደ እውነት<br />
ተግባርነት የሚሸጋገሩ ከሆነ ከዚህ ጋር ተያይዘው<br />
የሚመጡ አደጋዎች ምን ሊሆኑ ይችላሉ?<br />
በእውነት እነዚህ የኢትዮጵያን ሉዓላዊ የግዛት<br />
አንድነት በመዳፈር መሬቱን እየቆረሱ ለመስጠት<br />
ተፅፈው ተፈረመው የተደበቁ ስምምነቶች የአቶ<br />
መለስን እና የአቶ ኃይለማርያምን ቀጣፊነት<br />
ወደ ገፅ 15 ይዞራል
ነገረ-ኢትዮጵያ ቅፅ 1 ቁጥር 2 የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. 8<br />
ዝክረ ታሪክ<br />
ፋሽስት ገዳይ ባየር በራሪ፣<br />
ድንግል ጠብመንጃ በደም ነካሪ<br />
ከፉከራ ስነ-ቃል የተወሰደ<br />
ታዴዎስ ታንቱ<br />
የመ.ሣ.ቁጥር 43414<br />
የኢትዮጵያ ሰራዊት በታላቅ ጀግንነት<br />
ከፍተኛ መስዋዕትነት ከፍሏል!<br />
ከአውሮፕላን የዘነበውን የመርዝ<br />
ጭስ መቋቋም ግን ሳይችል ቀርቷል፡<br />
፡ በምክንያቱ ምክንያት የፋሽስት<br />
ኢጣሊያ ወራሪ ኃይል የበላይነትን<br />
ተቀዳጅቷል፡፡ በአሸናፊነት ስነ-ልቦና<br />
ታይቷል፡፡ የማይጨው ጊዜያዊ ድል<br />
ፈጽሞ እንደማይቀለበስ ተስፋ ሰንቋል!<br />
የአድዋ ጀግኖች ቀጥታ ተወላጆች<br />
መሆናችንን ማስታወስ እንኳን<br />
ተስኖታል፡፡ በዕብሪት የኢትዮጵያን<br />
መሬት ረግጧል፡፡ ወደ አዲስ አበባ<br />
ይገሰግሳል! ይገሰግሳል! ይገሰግሳል!<br />
ይገሰግሳል! አሁን ደሴ ገብቷል! ቀዳማዊ<br />
ኃይለ ስላሴ መሰደዳቸውን ሰምቷል፡<br />
፡ ዋና ከተማችንን በቶሎ ለመያዝ<br />
ቋምጧል! ከፊቱ ሊቆም የሚችል<br />
ጀግና ከቶም ሊኖር እንደማይችል<br />
ገምቷል! ጊዜአዊ ድል ዘላለማዊ<br />
አሸናፊነትን እንደማይወክል ለመገንዘብ<br />
አስተውሎት ጎድሎታል! የማን<br />
አህሎኝነት መንፈስ ለብሷል! ባሁኑ<br />
ሰዓት ሮቤ ደርሷል፡፡ ይግተለተላል!<br />
ይግተለተላል! ይግተለተላል! እንዲህ<br />
በቀላሉ ኢትዮጵያን ቅኝ ግዛት ማድረግ<br />
የሚችል መስሎታል፡፡ እርግጥ ነው!<br />
ከማይጨው ጦርነት ወዲህ የከፋ ነገር<br />
ሳያጋጥመው መጥቷል፡፡ ይህ ሁኔታ<br />
ሊቀጥል እንደማይችል ግን በጥቂት<br />
ጊዜያት ውስጥ ይታያል! ማን ለማን<br />
ይገዛል? የጀግኖች መሬት የፋሽስቶች<br />
መቃብር ይሆናል! የማይቀር እውነት<br />
በተግባር ይረጋገጣል! የጥንታዊት<br />
ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች በመንገዱ<br />
ግራና ቀኝ ተነጥፈዋል፡፡ በነፍስ ወከፍ<br />
ጦር መሳሪያ ቆርጠው ተነስተዋል!<br />
ድም! ድም! ድም! ዱዋ! ዱዋ! ዱዋ!<br />
የኢትዮጵያ አርበኞች የቅድሚያ<br />
ተነሳሽነት ወስደዋል! አከታትለው<br />
ተኩሰዋል! ቆራጡ የኢትዮጵያ ጀግና<br />
ተሰማ እርገጤ ክንዱን ሳይንተራስ<br />
የፋሽስት ኢጣሊያ ወራሪ ኃይል<br />
በኢትዮጵያ ምድር ተረጋግቶ ሊኖር<br />
እንደማይችል ከአቋም ተነስቶ ወደ<br />
ተግባር ገብቷል! የጦረኛ ዘር የጀግና<br />
ልጅ እሱ ማንን ይፈራል? ጦርነቱ<br />
አሁን ተጋግሏል! ከክብሩ ይልቅ<br />
ሆዱን የሚወድድ ከእንሰሳ ይመደባል!<br />
ከማንም ህይወት የሀገር ህልውና<br />
ይቀድማል! የነጻነትን ትርጉም<br />
የሚያውቅ ለነፍሱ አይሰስትም!<br />
ለጀግና ሞት ሰርጉ ነው! የጥንታዊት<br />
ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች<br />
ቆርጠዋል! በደፈጣ ውጊያ የበላይነትን<br />
ጨብጠዋል! የፋሽስት ኢጣሊያ ወራሪ<br />
ኃይል ተዋጊዎች ተረፍርፈዋል!<br />
በማያውቁት መንገድ አውቀው<br />
መጥተዋል! መጥተውም አልቀዋል!<br />
የሰውን ፈላጊ የራሱን ያጣል! ጦርነቱ<br />
ሌሊትም ቀጥሏል! ጀግና መች ሞት<br />
ይፈራል! ጦርነቱ ተጋግሏል! የፋሽስት<br />
ኢጣሊያ ወራሪ ኃይል ተዋጊዎች<br />
ተጠቅተዋል! የእሳት ራት ሆነዋል!<br />
አሁንም ግን በመፍጨርጨር ሂደት<br />
ገፍተዋል! የኢትዮጵያ ጀግኖች ደግሞ<br />
ከማሸነፍ ያነሰ ውጤት ላለማስመዝገብ<br />
ወስነዋል! ሰባት መኪና ሙሉ የነበረው<br />
የፋሽስት ኢጣሊያ ወራሪ ኃይል አሁን<br />
በጣም መንምኗል! ታሪክ ይመሰክራል!<br />
የወገን ትግል በድል ተጠናቅቋል!<br />
ጀግናው አርበኛ ተሰማ እርገጤ ወገንን<br />
አኮራ! ይህ በታሪካችን የጥንታዊት<br />
ኢትዮጵያ የጀግኖች አርበኞች የትግልና<br />
ድል ቀጥታ ድምጽ ነው! ከሸዋ ጠቅላይ<br />
ግዛት ከደብረ ሲና ጦር ሜዳ! ግንቦት<br />
23 ቀን 1928 ዓ.ም፡፡<br />
ቆፍጣናው የኢትዮጵያ አንበሳ ተሰማ<br />
እርገጤ አሁንም በከፍተኛ የውጊያ<br />
ስነ-ልቦና ይስተዋላል! ጀግናው አርበኛ<br />
ተሰማ እርገጤ ከውስን የውጊያ<br />
ሜዳ መልስ ረግቶ የሚቀመጥ ሰው<br />
አልነበረም፡፡ የፋሽስት ኢጣሊያ ወራሪ<br />
ኃይል ለአንዴና ለዘለዓለም ኢትዮጵያን<br />
ለቅቆ እነዲወጣ ለማድረግ ጽኑ የግዳጅ<br />
አቋም ይዟል፡፡ የተፈለገው መስዋዕትነት<br />
ሁሉ ይከፈላል! ጀግና ከነጻነት<br />
ያነሰ ነገር አይፈልግም! ለዓላማው<br />
ደግሞ እስከ ህይወት መስዋዕትነት<br />
ይዘልቃል፡፡ ቆራጡ የጦር ሰው ተሰማ<br />
እርገጤ አሁን በተጠንቀቅ ቆሟል!<br />
ከመስክ ስምሪት የተገኙ መረጃዎችን<br />
ይተነትናል፡፡ ከኢትዮጵያ የቁርጥ<br />
ቀን ጀግኖች ጋር በስፋት የሀሳብ<br />
ልውውጥ አድርጓል! በጥቂት ጊዜያት<br />
ውስጥ ተጨባጭ ተኩስ ይከፈታል!<br />
የኢትዮጵያ አርበኞች ወደ ወራሪው<br />
ኃይል በቀጥታ ተጠግተዋል! ወራሪው<br />
ኃይል በቀጥታ ወደ አዲስ አበባ<br />
ሲተምም ይታያል! ለጊዜው በውጊያ<br />
ስነ-ልቦና ላይ እንዳልነበረ ታውቋል!<br />
ጀግኖቹ የኢትዮጵያ አርበኞች አሁን<br />
ለወራሪው ኃይል የጉዞ መስመር<br />
በጣም ቀርበዋል! ድም! ድም! ድም!<br />
ዱዋ! ዱዋ! ዱዋ! ጀግኖቹ የኢትዮጵያ<br />
አርበኞች ቅድሚያ ተነሳሽነቱን<br />
በተግባር ወስደዋል፡፡ የፋሽስት ኢጣሊያ<br />
ወራሪ ኃይል ተደነባብሯል! ሆኖም<br />
የአጸፋ ተኩስ ለማሰማት የደቂቃ<br />
ክፍልፋይ ጊዜ በቅቶት ተገኝቷል፡፡<br />
ማይጨው ላይ የነበረው የኢትዮጵያ<br />
ሰራዊት በሙሉ የመጣበት ያህል<br />
ደንግጧል! ሳያስበው አስቦ ያደፈጠ<br />
ጀግና አጋጥሞታል! ተኩሱ ቀልጧል!<br />
እንደ ፈንድሻ ይንጣጣል፡፡ ለሰዓታት<br />
ቀጥሏል! የፋሽስት ኢጣሊያ ወራሪ<br />
ኃይል ድባቅ ተመትቷል! ድል በትግል<br />
ተመዝግቧል! ታሪክ ይናገራል! ይህ<br />
በታሪካችን የጥንታዊት ኢትዮጵያ<br />
የጀግኖች አርበኞች የጦርነትና የድል<br />
ቀጥታ ድምጽ ነው! ከሸዋ ጠቅላይ<br />
ግዛት ከጣርማ በር የጦር ሜዳ! ሐምሌ<br />
5 ቀን 1928 ዓ.ም፡፡<br />
ውድ የኢትዮጵያ ጀግና ተሰማ እርገጤ<br />
ከፍልሚያ በኋላ አሁንም ሌላ ፍልሚያ<br />
ይጠብቀዋል! ወሳኙን ድል ለማምጣት<br />
ቆርጦ ተነስቷል! በየቀኑ በፍቃደኝነት<br />
ወደ አርበኝነት የገቡ ወጣቶች<br />
የጦር መሳሪያ እንዲታጠቁ ጥረት<br />
ያደርጋል! ወራሪው ኃይል ዘመናዊ<br />
የጦር መሳሪያ ታጥቋል! ከኢትዮጵያ<br />
አርበኞች አንዳንዶቹ ጠብመንጃ<br />
እንዳልነበራቸው ታውቋል! ብሄራዊ<br />
ስሜት የህሊና እረፍት ነስቷቸው<br />
ቤታቸውን አቃጥለው በሬዎቻቸውን<br />
ሸጠው፣ እርሻቸውን ትተው ከጀግኖች<br />
ጋር ተቀላቅለዋል! ጦር፣ ጋሻና ጎራዴ<br />
ብቻ የያዙም ተስተውለዋል! የተቃጠለ<br />
ብሄራዊ ስሜት ደግሞ ከጦር መሳሪያም<br />
ይልቃል! እርግጥ ነው! የማያቅማማ<br />
ልብ ፈጠነም ዘገየ ለድል ያበቃል!<br />
ጀግናው አርበኛ ተሰማ እርገጤ አሁን<br />
ከመስክ ስምሪት ወታደራዊ መረጃ<br />
ደርሶታል! የፋሽስት ኢጣሊያ ወራሪ<br />
ኃይል ተዋጊዎች በቅርብ የሰፈሩበትን<br />
ቦታ ለይቶ አውቆታል! ጀግና ለፋሽስት<br />
ጊዜ አይሰጥም! ቆራጡ አርበኛ<br />
ወራሪው ኃይል ዘመናዊ የጦር መሳሪያ ታጥቋል! ከኢትዮጵያ አርበኞች አንዳንዶቹ ጠብመንጃ<br />
እንዳልነበራቸው ታውቋል! ብሄራዊ ስሜት የህሊና እረፍት ነስቷቸው ቤታቸውን አቃጥለው<br />
በሬዎቻቸውን ሸጠው፣ እርሻቸውን ትተው ከጀግኖች ጋር ተቀላቅለዋል! ጦር፣ ጋሻና ጎራዴ ብቻ<br />
የያዙም ተስተውለዋል! የተቃጠለ ብሄራዊ ስሜት ደግሞ ከጦር መሳሪያም ይልቃል! እርግጥ<br />
ነው! የማያቅማማ ልብ ፈጠነም ዘገየ ለድል ያበቃል!<br />
ተሰማ እርገጤ አሁን ተንቀሳቅሷል፡<br />
፡ አርበኞች ምድብ መስመራቸውን<br />
ይዘዋል! ተጠጋግቶ መጓዝ ክልክል<br />
ነው! ተፈነጣጥሮ በቅርብ ርቀት<br />
እየተጠባበቁ መጓዝ የግድ ይላል፡<br />
፡ ሁሉም በየምድብ መስመራቸው<br />
ጉዟቸውን ቀጥለዋል!<br />
ጀግናው ተሰማ እርገጤ ከጥቂት<br />
አርበኞች ጋር ወራሪው ኃይል<br />
ከሰፈረበት ግራ አቅጣጫውን ይዟል!<br />
አርበኞች የነፍስ ወከፍ የጦር<br />
መሳሪያቸውን ታጥቀዋል! ጀግናው<br />
ተሰማ እርገጤ ዘወትር በጥቂት<br />
መስዋዕትነት ታላቅ ድል ለማስመዝገብ<br />
በቁርጠኝነትና በዓላማ ጽናት ይዋጋል!<br />
የተቃጠለ ብሄራዊ ስሜት ተላብሷል!<br />
ማቅማማት አያውቅም! መስዋዕት<br />
መሆን ወይም ድል! አርበኛ ሲሰዋ<br />
በእልህ የውጊያ ዝግጁነት መንፈሱ<br />
ይነሳሳል! የፋሽስት ኢጣሊያ ወራሪ<br />
ኃይል የኢትዮጵያን መሬት ለቅቆ<br />
እስካልወጣ ለአፍታም ጦርነቱን<br />
ላለማቆም ቆርጧል! ጥቁር በነጭ<br />
እንዴት ይገዛል? የአድዋ ጀግኖች<br />
አጥንት እሾህ ሆኖ ይውጋን! ለጣሊያን<br />
ፈጽሞ አንገዛም! ይህ የአርበኞች ድምጽ<br />
ነው! ኢትዮጵያ ጀግና ነበራት! ነበራት!<br />
ነበራት! አሁን ቆራጦቹ የጥንታዊት<br />
ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች የፋሽስት<br />
ኢጣሊያ ወራሪ ኃይል ተዋጊ ከሰፈረበት<br />
ቦታ ደርሰዋል! ሁሉም በምድብ<br />
መስመራቸው ከተኩስ ቦታቸው ላይ<br />
ተገኝተዋል፡፡ የወራሪውን ኃይል ሰፈር<br />
ከብበዋል! ለተኩስ ዝግጁ! ለግድያ<br />
ዝግጁ! ለምርኮ ዝግጁ! የኢትዮጵያ<br />
ጀግና መቼ ፈርቶ ያውቃል? ድም!<br />
ድም! ድም! ዱዋ! ዱዋ! ዱዋ!<br />
ጦርነቱ በኢትዮጵያ ጀግኖች ቅድሚያ<br />
ተነሳሽነት ተከፍቷል! ወራሪው<br />
ኀይል የአጸፋ ተኩስ ከፍቷል! አሁን<br />
መከበባቸውን አውቀዋል፡፡ የተፋፋመ<br />
ተኩስ ቀጥሏል! እሳት ይዘንባል!<br />
ጀግና ለክብሩ ቆርጧል! የፋሽስት<br />
ወራሪ ኃይል ለማምለጥ ይተኩሳል!<br />
የኢትዮጵያ አርበኞች ደግሞ የወራሪው<br />
ኃይል ተዋጊዎችን በነበሩበት ከአፈር<br />
ጋር ለማዋሀድ በተግባር ተነስተዋል!<br />
ጦርነቱ በተከፈተ በጥቂት ጊዜያት<br />
ውስጥ በወራሪው ኃይል ላይ ከፍተኛ<br />
ጉዳት ደርሷል! የኢትዮጵያ አርበኞች<br />
የበላይነት ይዘዋል! ተኩሱ ቀጥሏል!<br />
ይህ የታሪክ ድምጽ ነው! በአሁኑ<br />
ሰዓት በኢትዮጵያ ታሪክ በሸዋ ጠቅላይ<br />
ግዛት ውስጥ በልበላ በተባለ ቦታ<br />
ከጀግኖች አርበኞች ጋር በተፋፋመ<br />
ጦርነት መካከል ቆመናል!<br />
በርካታ የፋሽስት ወራሪ ኃይል<br />
ተዋጊዎች ተደምስሰዋል! አንዳንዶች<br />
ተሾሎክልከው አምልጠዋል፡፡ የነበሩበት<br />
ድንኳን ነድዷል! ሬሳ ተዝረክርኮ<br />
ይታያል! በማያጠራጥር መልኩ<br />
አርበኞች ድልን ተጎናጽፈዋል! ቆራጡ<br />
አርበኞ ተሰማ እርገጤ እንደ አንበሳ<br />
ይጎማለላል! ባሁኑ ሰዓት በየቦታው<br />
የተዝረከረከውን የወራሪው ፋሽስት<br />
ሬሳ በየአቅጣጫው ያስተውላል!<br />
ቆራጡ የህዝብ ባለአደራና የሀገር<br />
ባለውለታ ተሰማ እርገጤ በዚሁ<br />
በበልበላ ጦርነት ጣሊያኖችን የገደለ<br />
ከመሆኑም በላይ በርካታ የፋሽስት<br />
ተዋጊ ባንዳዎችን እንደ ገብስ አጭዷል!<br />
የጦር መሳሪያዎችንም ማርኳል!<br />
ድል አድራጊው የኢትዮጵያ አርበኛ<br />
አሁን ወራሪው ኃይል ሲፈረጥጥ<br />
ያዝረከረከውን የጦር መሳሪያ<br />
በመሰብሰብ ሂደት ላይ ይታያል!<br />
አንዳንድ አርበኞች ከወራሪው ኃይል<br />
ተዋጊዎች ሬሳ ወገብ ላይ ዝናር ሲፈቱ<br />
ይስተዋላል! ይህ የታሪክ ድምጽ ነው!<br />
የኢትዮጵያ አርበኞች ከፋሽስቶች<br />
ሬሳ ላይ የጦር መሳሪያ ከመፍታት<br />
በስተቀር ልብስ ፈጽሞ አይገፍፉም!<br />
ነውር ነው! ይህ በታሪካችን<br />
ለአንድነታቸው፣ ለሉዓላዊነታቸው፣<br />
እንዲሁም ለሐይማኖታቸው ቀናዒ<br />
የነበሩ የጥንታዊት ኢትዮጵያ የጀግኖች<br />
አርበኞች የጦርነትና የድል ድምጽ<br />
ነው! ከሸዋ ጠቅላይ ግዛት ከበልበላ<br />
ጦር ሜዳ! ጳጉሜ 2 ቀን 1928 ዓ.ም!<br />
ቆፍጣናው አርበኛ ተሰማ እርገጤ<br />
አሁን በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ውስጥ<br />
ግፋይታ በተባለ መንድር ድርጅታዊ<br />
አቅሙን በማጎልበት ስራ ተጠምዷል!<br />
ወጣቶች ወደ አርበኝነት እንዲገቡ<br />
በተከታታይ ይቀሰቅሳል! በምስጢር<br />
የጦር መሳሪያ ይሸምታል! በከፍተኛ<br />
ደረጃ በውጊያ ስነ-ልቦና ላይ ይስተዋላል!<br />
የፋሽስት ወራሪ ኃይል ግን ጀግናው<br />
ተሰማ እርገጤ የነበረበትን ቦታ<br />
ለይቶ አውቋል! ባንዳ ሹክ ብሎታል!<br />
በዚህን ጊዜ ወራሪው ኃይል ጀግናውን<br />
ተሰማ እርገጤን ለመግደል ቆርጦ<br />
መነሳቱ ተሰማ! ቆፍጣናው ተዋጊ<br />
ተሰማ እርገጤ መረጃው ደርሶታል!<br />
ታዲያ ምን ሊያደር ይችላል?<br />
ቆፍጣናው ተዋጊ ተሰማ እርገጤ<br />
ማድረግ የነበረበትን መቼ አጣ?<br />
በቅድሚያ ገዥ መሬት ይዞ ጠበቀው!<br />
ወራሪው ኃይል አሁን እየትግተለተለ<br />
መጥቶዋል! አርበኛው ተሰማ እርገጤ<br />
ዳቦ በማር ይገምጣል! ወራሪው ኃይል<br />
ተጠግቷል! የኢትዮጵያ አርበኞች ከሳር<br />
ጋር ሳር መስለዋል! ወራሪው በአሰራር<br />
ቀድሟል! ባንዳ ቀድሟል! ጣሊያኖች<br />
ወደ ኋላ ቀርተዋል! መገናኛ መሳሪያ<br />
ይዘዋል! ከጦር መሳሪያ ደግሞ ሽጉጥ<br />
ብቻ ታጥቀዋል! የወራሪው ኃይል<br />
ተዋጊዎች በአሰራር አሁንም ወደ<br />
ፊት ሲጠጉ ይስተዋላል! ድም! ድም!<br />
ድም! ዱዋ! ዱዋ! ዱዋ! የወራሪውን<br />
ኃይል ተዋጊዎች በአሰራር ጉዞ<br />
ከርቀት ዒላማቸው ውስጥ አስገብተው<br />
ይጠባበቁ የነበሩት ጀግኖቹ የኢትዮጵያ<br />
አርበኞች በቅድሚያ ተነሳሽነት ተኩስ<br />
ከፍተዋል! ከፊት የነበሩ ባንዳዎችን<br />
መትተው ጥለዋል! ከወራሪው ኃይል<br />
የአጸፋ ተኩስ በኋላ ጦርነቱ ወዲያው<br />
ተጋግሏል! ነገር ግን ረጅም ሰዓት<br />
አልፈጅም! ቆራጦቹ የኢትዮጵያ<br />
አርበኞች ወዲያው አጥቅተው<br />
የበላይነትን ጨብጠዋል! ጀግናው<br />
አርበኛ ተሰማ እርገጤ የፈረጠጠውን<br />
ባንዳ እያሳደደ ከአፈር ጋር ያዋህድ<br />
ገባ! በርካታ የነፍስ ወከፍ የጦር<br />
መሳሪያዎችንም ማርኳል! ጦርነቱ<br />
በኢትዮጵያ ጀግኖች ድል አድራጊነት<br />
ተጠናቀቀ! ይህ የጥንታዊት ኢትዮጵያ<br />
ጀግኖች አርበኞች ቀጥታ የታሪክ<br />
ድምጽ ነው! ከሸዋ ጠቅላይ ግዛት<br />
ግፋይታ ከተባለ ውጊያ መስክ በቀጥታ<br />
ለዛሬው ተረኛ ትውልድ የሚተላለፍ<br />
የታሪክ ድምጽ ነው! መስከረም 15<br />
ቀን 1929 ዓ.ም!<br />
ቆራጡ የጦር ሰው ተሰማ እርገጤ<br />
ፈጽሞ ሊበገር አልቻለም! በዚህ<br />
ምክንያት የፋሽስት ኢጣሊያ ወራሪ<br />
ኃይል በጣም ተበሳጨ! ተበሳጭቶ<br />
ግን ዝም አላለም! ጀግናውን አርበኛ<br />
ተሰማ እርገጤን ይዞ ለሚያቀርብለት<br />
ከፍተኛ ሹመት እንደሚሰጠው አወጀ!<br />
በተጓዳኝም የአርበኛውን ዘመዶች<br />
ከየቦታው ለቃቅሞ አሰራቸው!<br />
አርበኛው ተሰማ እርገጤ ግን ከአቋሙ<br />
ፍንክች ሳይል ቀርቷል! በሀገር ፍቅር<br />
የተቃጠለው ጀግናው አርበኛ ተሰማ<br />
እርገጤ ከአንድ ድል በኋላ ፋታ<br />
ሳያገኝ ወዲያው ለጦርነት ይዘጋጃል!<br />
ወራሪው ኃይል የግድ ኢትዮጵያን<br />
ለቅቆ መውጣት አለበት፡፡ መፍትሔው<br />
ደግሞ ጦርነት ብቻ መሆኑን አጥብቆ<br />
ያምናል! ይህ የኢትዮጵያ አርበኞች<br />
የማይቀለበስ ውሳኔ ነው! ቆራጡ<br />
አርበኛ ተሰማ እርገጤ አሁን ጨለንቆ<br />
በተባለው ቦታ የሰፈረውን የፋሽሰት<br />
ወራሪ ለመደምሰስ በጉዞ ላይ መሆኑ<br />
ወደ ገፅ 6 ይዞራል
9 የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2 ነገረ-ኢትዮጵያ<br />
ኢትዮጵያ ለምን ኋላ ቀረች?<br />
ክፍል ሁለት<br />
ግርማ ሞገስ<br />
●የኢትዮጵያ የመንግስት ስልጣን<br />
ሽግግር ባህሏ<br />
ለዘጠኝ መቶ አመቶች ላላነሰ ጊዜ<br />
ኢትዮጵያ በዘመናዊ (Secular)<br />
ትምህርት እና ትምህርቱን ተከትሎ<br />
ለሚመጣ ዘመናዊነት እና ስልጣኔ<br />
ጀርባዋን መስጠቷ ለኋላ መቅረቷ<br />
አንዱ አውራ ምክንያት እንደነበር<br />
ባለፈው አንብበናል። በእንቅርት ላይ<br />
ጆሮ ደግፍ እንዲሉ ደግሞ ቢያንስ<br />
ቢያንስ ከአክሱም ስልጣኔ መውደቅ<br />
ወዲህ ጀምሮ አምባገነኑ ህውሃት/<br />
ኢህአዴግ በ1983 ዓ.ም. ስልጣን<br />
እስከጨበጠበት ጊዜ ድረስ በእርስ<br />
በርስ ጦርነት ይፈጸም የነበረው<br />
የመንግስት ሽግግር ባህሏ ኢትዮጵያን<br />
እጅ እና እግሯን ተብትቦ ስለስልጣኔ<br />
የምታስብበት መተንፈሻ ጊዜ እንኳን<br />
እንዳይኖራት አድርጓት ነበር። ስለዚህ<br />
ኢትዮጵያ ከውጭ ወረራ ረጅም<br />
የነፃነት ዘመን ቢኖራትም በስልጣኔ<br />
እንዳትገፋ ያደረጋት ሁለተኛው<br />
አውራ ምክንያት በእርስ በርስ ጦርነት<br />
የሚፈጸመው የመንግስት ሽግግር<br />
ባህሏ ነበር ማለት ይቻላል። በዚህ<br />
ጉዳይ ላይ ተክለ ፃዲክ መኩሪያ፣<br />
ባህሩ ዘውዴ፣ ሃሮልድ ማርኪውስ<br />
እና ፓንክረስት የመሳሰሉ የታሪክ<br />
ምሑራን ብዙ ጽፈውታል።<br />
የመንግስት ሽግግር ባህሏም በበኩሉ<br />
ከስልጣኔ እንድትርቅ አድርጓል።<br />
ለምን ያህል ጊዜ (ስንት አመቶች)?<br />
ግምት መስጠት እንችላለን?<br />
እንሞክር! በኢትዮጵያ ሲደረግ<br />
የነበረው የመንግስት ሽግግር<br />
ታሪካችን ሁለት አኪያሄዶች ነበሩት።<br />
አንደኛው አኪያሄድ ከአንድ ዝርያ<br />
ወደ ሌላ ዝርያ የሚደረግ የመንግስት<br />
ሽግግር ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ<br />
በአንድ ዝርያ ውስጥ ከአባት ወደ<br />
ልጅ የሚፈጸም የመንግስት ስልጣን<br />
ሽግግር ነበር። ሁለቱም አይነት<br />
የመንግስት ሽግግሮች ከጦርነት ነፃ<br />
አልነበሩም። በጦርነቶቹ መካከል<br />
ልዩነት ካለም የጦርነቱ አስከፊነት<br />
መጠነ እና የጦርነቱ እድሜ ብቻ<br />
ነበር።<br />
ለጥናት እንዲያመቸን ካፄ ኢዛና<br />
(321 ዓ.ም.) በፊት ለመንግስት<br />
ሽግግር (ለስልጣን) የተደረጉትን<br />
የእርስ በርስ ጦርነቶች በሙሉ<br />
ከግምት አናስገባም። ጥናታችንን<br />
ይበልጥ ቀላል ለማድረግ ስንል ካፄ<br />
ኢዛና ወዲህ ተሞክረው ያልተሳኩትን<br />
ቁጥር ስፍር የሌላቸው ለመንግስት<br />
ሽግግር የተደረጉ የእርስ በርስ<br />
ጦርነቶች በሙሉ ወደጎን እንተዋለን።<br />
ጥናታችን ካፄ ኢዛና ወዲህ በተደረጉት<br />
የተሳኩ የመንግስት ሽግግሮች ላይ<br />
ያተኩራል። ስለዚህ በ321 ዓ.ም.<br />
በስልጣን ላይ ከነበረው ካፄ ኢዛና<br />
ዘመነ መንግስት ጀምረን እስከ በ1983<br />
ዓ.ም. በእርስ በርስ ጦርነት ስልጣን<br />
የጨበጠው አምባገነኑ የህውሃት/<br />
ኢህአዴግ መንግስት ድረስ ከነበሩት<br />
1662 አመቶች ውስጥ የመንግስት<br />
ሽግግር ባህሏ ስንት አመቶች እጅ<br />
እና እግሯን ተብትቦ በማሰር ስልጣኔ<br />
ከውስጥም እንዳታበቅል እንዳደረጋት<br />
አጠቃላይ ግምት ለመስጠት<br />
እንሞክራለን። እያንዳንዱ የመንግስት<br />
ሽግግር ባህላችን ጦርነት የፈጀው<br />
ጊዜ በዝርዝር ተጽፎ የተላለፈልን<br />
መረጃ የለንም። ለግዜው ማድረግ<br />
የምንችለው እነ ተክለ ፃዲቅ ጽፈው<br />
ካወረሱን ትረካ ግምት ለመውሰድ<br />
መሞከር ነው። እያንዳንዱ የተሳካውም<br />
ያልተሳካውም የመንግስት ሽግግር<br />
የፈጀውን ጊዜ አመት በአመት<br />
የማስላቱን ስራ ለመጪው ትውልድ<br />
ታሪክ ተመራማሪዎች እንተዋለን።<br />
ካፄ ኢዛና (321 ዓ.ም.) ወዲህ<br />
የተደረጉትን ዋናዎቹን የመንግስት<br />
ሽግግሮች<br />
እንደሚከተለው<br />
መከፋፈል እንችላለን፣ (1) ከኢዛና<br />
ዝርያዎች ወደ ንግስት ዮዲት (ቤተ<br />
እስራኤሎች) ዝርያዎች፣ (2) ከቤተ<br />
እስራኤሎች ወደ ላስታው መራ ተክለ<br />
ሃይማኖት (ዛጉዌ ስረወ መንግስት)<br />
ዝርያዎች፣ (3) በ1262 ከላስታ<br />
አገዎች ወደ ሸዋው ይኩኖ አምላክ<br />
ዝርያዎች፣ (4) በ1523 ዓ.ም. ያፄ<br />
ይኩኖ አምላክ ዝርያ ከነበረው ልብነ<br />
ድንግል ወደ ይማም አህመድ (ግራኝ<br />
በሚል የሚታወቁት እና በአባታቸው<br />
የኦጋዴ በእናታቸው ደግሞ የሐረር<br />
ተወላጅ የሆኑት)፣ (4) በጎንደር ካፄ<br />
ገላውዲዎስ 1533-1552) እስከ ዐፄ<br />
እዮዋስ (1747-1761) (በአባት የቋራ<br />
አማራ በእናት ደግሞ የየጁ ኦሮሞ)፣<br />
(5) ከራስ ስሑል እስከ የየጁው<br />
ትንሹ ራስ ዐሊ (ዘመነ መሳፍንት)፣<br />
(5) ካፄ ቴዎድሮስ (1847-1860)<br />
እስከ ሰቆጣው ዐፄ ተክለ ጊዮርጊስ<br />
(1860-1864) ከዚያ ወደ ተምቤኑ<br />
ዐፄ ዮሐንስ (1864-1881) ከዚያ<br />
ወደ ሸዋው ምኒልክ (1882-1906)፣<br />
(6) ከምንሊክ ወደ ልጅ ልጃቸው<br />
ልጅ እያሱ ከዚያ ወደ ምኒልክ ሴት<br />
ልጅ ዘውዲቱ ከዚያ ወደ ኃይለስላሴ<br />
ከዚያ ወደ ደርግ ከዚያ ወደ ህውሃት/<br />
ኢህአዴግ። እነዚህ የመንግስት<br />
ሽግግሮች በሙሉ የተጠናቀቁት<br />
በእርስ በርስ ጦርነት እና ሽብር<br />
ነበር።<br />
ከአባት ወደ ልጅ የተደረጉ የመንግስት<br />
ሽግግሮችም ከሁከት እና ከእርስ በርስ<br />
ጦርነቶች የጸዱ ስላልነበሩ ሁከቱን<br />
እና ጦርነቱን ለመቀነስ ነገስታቱ<br />
ልጆቻቸውን በጠባቂ በሚከተሉት<br />
እስርቤቶች ሆነው የንጉስነት<br />
ተራቸውን (እድላቸውን) እንዲጠብቁ<br />
አድርገዋል። (1) ደብረ ዳሞ አምባ<br />
እስር ቤት፥ በአክሱም ዘመነ መንግስት<br />
በዙፋን ላይ የሚገኘው ንጉሱ ታመመ<br />
በተባለ ቁጥር በቤተ ዘመድ ውስጥ<br />
“ዙፋን ይገባኛል” “ተረኛው እኔ<br />
ነኝ” የሚሉ ሁከቶች እና ጦርነቶች<br />
ይነሱ ነበር። ስለዚህ ይኽን ሁከት<br />
እና የርስ በርስ ጦርነት ለማስወገድ<br />
ነገስታቱ ልጆቻቸውን እና በቅርብ<br />
ከሚዛመዱዋቸው የሚወለዱትን<br />
ጨምረው በትግራይ ከአዲግራት<br />
በስተ ምዕራብ በሚገኘው ደብረ ዳሞ<br />
አምባ ጠባቂ ተደርጎላቸው የንግስና<br />
ተራቸውን እንዲጠብቁ ይደረግ<br />
እንደነበር ተክለ ፃዲቅ መኩሪያ<br />
ይገልጻል።<br />
ከሠርፀ ዘድንግል ወደ ፋሲል አባት (ዐፄ ሱስነየስ) የተደረገው የመንግስት ሽግግር በቀጣይነት የርስ በርስ<br />
ጦርነት ዘመን ነበር። ሠርፀ ሲሞት ለትንሽ ልጁ አቆብ (1590-1595) አወረሰ። የአጎቱ ልጆች ዙፋን<br />
ለኛ ይገባል የሚል ጦርነት ከፍተው ዙፋኑ ከአቆብ ወደ ዘድንግል (1595-1596) ከዚያ ከዘድንግል<br />
እንደገና ወደ ያእቆብ (1596-1598) ከዚያ በመጨረሻ ወደ ፋሲል አባት ሱስነየስ<br />
(1598-1625) የተሸጋገረው በድምሩ 10 አመቶች የርስ በርስ ጦርነት ከተደረገ ቧላ ነበር።<br />
(2) ግሸን አምባ እስር ቤት፣<br />
የአክሱም ነገስታትን ልማድ<br />
በመከተል የላስታዎቹ ነገስታትም<br />
ተመሳሳይ ችግር ለማስወገድ ከደሴ<br />
በስተምዕራብ ግሸን አምባ ይባል<br />
የነበረውን ተራራማ ቦታ ለእስር ቤት<br />
ተጠቅመውበታል። (3) ግሸን አምባ<br />
እስር ቤት (እንደገና)፣ የአክሱምን<br />
እና የላስታን ነገስታት ልማድ<br />
በመከተል እስከ ልብነ ድንግል ድረስ<br />
የነበሩት የሸዋ ነገስታትም ይህንኑ<br />
ግሸን አምባን እንደ እስር ቤት<br />
ተጠቅመዋል። በግሸን አምባ የነበሩት<br />
የነገስታት ዝርያዎች በሙሉ<br />
በእስር ላይ ሳሉ በልብነ ድንግል<br />
እና በይማም አህመድ መካከል<br />
የተካሄደው እንደፈጃቸው ተክለ<br />
ፃዲቅ መኩሪያ እና የውጭ ታሪክ<br />
ጸሐፊዎች ጽፈዋል። (4) ወህኒ<br />
ተራራ እስር ቤት፣ በጎንደር ዘመነ<br />
መንግስት ደግሞ ካፄ ፋሲል ጀምሮ<br />
ከጎንደር በስተ ምዕራብ የሚገኘውን<br />
ወህኒ ተራራን ለተመሳሳይ ተግባር<br />
ነገስታቱ ተጠቅመዋል።<br />
ለጥቀን ከኢዛና ዘመነ መንግስት<br />
(321 ዓ.ም.) እስከ ህውሃት/ኢህአዴግ<br />
ስልጣን እስከጨበጠበት 1883<br />
ዓ.ም. ድረስ ከተደረጉት የመንግስት<br />
ሽግግሮች ውስጥ አለፍ አለፍ እያልን<br />
ጥቂት ምሳሌዎች እንመለከታለን፣<br />
(1) ወደኋላ መለስ ብለን የንግስት<br />
ዮዲትን ዘመን ብናይ ከመንግስት<br />
ስልጣን በፊት 50 አመቶች ግድም<br />
እና በስልጣን ዘመኗ ደግሞ 40<br />
አመቶች በድምሩ 90 አመቶች<br />
የጦርነት ዘመን እንደነበሩ ተጽፎ<br />
እናያለን።<br />
(2) በቱርክ እና ግብጽ የታገዙት<br />
የይማም አህመድ ዘመንንም<br />
ብንወስድ በቱርክ ወታደራዊ<br />
የበላይነትን ከማግኘታቸው በፊት<br />
እና ወታደራዊ የበላይነትን የያዙበት<br />
አመቶች እንዲሁም ፖርቱጋሎች<br />
ክርስቲያኖችን አግዘው የተዋጉበት<br />
አመቶች በድምሩ ከ30 አመቶች<br />
በላይ ይሆናል።<br />
(3) ከሠርፀ ዘድንግል ወደ ፋሲል<br />
አባት (ዐፄ ሱስነየስ) የተደረገው<br />
የመንግስት ሽግግር በቀጣይነት የርስ<br />
በርስ ጦርነት ዘመን ነበር። ሠርፀ<br />
ሲሞት ለትንሽ ልጁ አቆብ (1590-<br />
1595) አወረሰ። የአጎቱ ልጆች ዙፋን<br />
ለኛ ይገባል የሚል ጦርነት ከፍተው<br />
ዙፋኑ ከአቆብ ወደ ዘድንግል (1595-<br />
1596) ከዚያ ከዘድንግል እንደገና<br />
ወደ ያእቆብ (1596-1598) ከዚያ<br />
በመጨረሻ ወደ ፋሲል አባት ሱስነየስ<br />
(1598-1625) የተሸጋገረው በድምሩ<br />
10 አመቶች የርስ በርስ ጦርነት<br />
ከተደረገ ቧላ ነበር። ምናልባትም<br />
ለዚህ ነበር ፋሲል ዮሐንስ ከተባለው<br />
ልጁ በስተቀር የቀሩትን ልጆቹን እና<br />
ሌሎች ዘመዶቹን ወደ ተራራ ወህኒን<br />
የላከው።<br />
(4) ታላቁ እያሱ ከተገደለበት (1698)<br />
ጊዜ ጀምሮ ባባቱ ቋራ በእናቱ የጁ<br />
የሆነው ዐፄ እዮአስ እስከተገደለበት<br />
1761 ዓ.ም. ድረስ የነበሩት 63<br />
አመቶች የማያቋርጥ የእርስ በርስ<br />
ጦርነት አመቶች ነበሩ።<br />
(5) በ1761 ዓ.ም. ዘመነ መሳፍንት<br />
ከተነሳ ወዲህ እስከ ወደቀበት 1847<br />
ዓ.ም. ድረስ 86 አመቶች ሲኖሩ ከዚያ<br />
ውስጥ የየጁው ራስ ጉግሳ በገዙበት<br />
ዘመን ከነበረው ትንሽ መረጋጋት<br />
በስተቀር ሰላም አልነበረም።<br />
(6) ከዚያም ያፄ ቴዎድሮስ ዘመን<br />
(1847-1860) ማለቂያ ባልነበረው<br />
የማስገበር ዘመቻ ተጠምዶ ስለነበር<br />
እስከ ፍጻሜያቸው ድረስ የነበሩት 13<br />
አመቶች የመንግስት ሽግግር የእርስ<br />
በርስ ጦርነት አመቶች ነበሩ።<br />
(7) ያፄ ተክለ ጊዮርጊስ 4 አመቶችም<br />
የጦርነት ዘመን ነበሩ።<br />
(8) ያፄ ዮሐንስ ዘመን (1864-1881)<br />
በግብጾች እና በቅኝ ገዢዋ ኢጣሊያ<br />
ጦርነቶች ከመጠመዱ ባሻገር<br />
ለስልጣን ከውስጥ የሚያፈነግጠው<br />
ጥቂጥት አልነበረም። በዚህ የተነሳ<br />
ዮሐንስ መጨረሻ መተማ ላይ<br />
እስከሞቱበት ጊዜ ድረስ በቤተ<br />
መንግስታቸው ያደሩባቸው ቀኖች<br />
በጣም ጥቂት ነበሩ።<br />
(9) ከምኒሊክ ዘመነ መንግስት<br />
(1882/9-1906/13) እስከ ምኒልክ<br />
ፍጻሜ (1906/13) ድረስ የተወሰነ<br />
የሰላም ጊዜ ቢኖርም ከዚያ እስከ<br />
ኃይለስላሴ ንጉሰ ነገስት (1922/30-<br />
1967/75) ያልተቋረጠ የመንግስት<br />
ሽግግር ጦርነቶች ተካሂደዋል።<br />
የምኒልክን ዙፋን ወራሽ የልጅ<br />
እያሱ ዘመን (1906/13-1919/27)<br />
ከመንግስት የተፈነቀለው በብዙ<br />
የርስ በርስ ደም መፋሰስ ነበር።<br />
ከዚያም ወደ ኃይለስላሴ ንግስና<br />
በተደረገው የመንግስት ሽግግር<br />
ሂደት የልጅ እያሱን ደጋፊዎች፣<br />
የንግስት ዘውዲቱን (1919/27-<br />
1922/30) ደጋፊዎች፣ የምኒልክን<br />
ባለቤት የእቴጌ ጣይቱን ደጋፊዎች<br />
የማጽዳት በርካታ የርስ በርስ ጦርነት<br />
ተፈጽሟል።<br />
የኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ ከርካሳ<br />
አውሮፕላን የመጀመሪያ ስራ<br />
ለመንግስት ሽግግር በጎንደር<br />
ተቃዋሚዎች ላይ ቦንብ መጣል<br />
እንደነበር እና የኢትዮጵያ<br />
የመጀመሪያው ታንክም በአዲስ አበባ<br />
ለተመሳሳይ ጉዳይ ስራ ላይ ውለው<br />
እንደነበር ባህሩ ዘውዴ ያመለክታል።<br />
የኃይለስላሴን የመጨረሻዎቹ አመቶች<br />
የእርስ በርስ ጦርነቶች ብንጨምር<br />
ከምኒልክ ዘመነ መንግስት ጅማሬ<br />
እስከ ኃይለስላሴ ዘመነ መንግስት<br />
ፍጻሜ ድረስ በግምት 16+4=20<br />
አመቶች የጦርነት አመቶች ብሎ<br />
መውሰድ ይቻላል)<br />
(10) የደርግ 17 አመቶች ከዘመነ<br />
መሳፍንት በባሰ ደረጃ ከ7 በላይ<br />
የሚሆኑ ኢትዮጵያዊ ድርጅቶች<br />
እርስ በርስ ተዋግተዋል።<br />
ስለዚህ ካፄ ኢዛና ከነገሰበት ከ321<br />
ዓ.ም. እስከ በ1983 ዓ.ም. ድረስ<br />
ከነበሩት 1662 አመቶች ውስጥ<br />
የተሳኩት የመንግስት ሽግግሮች<br />
በግምት ከ360 እስከ 400 አመቶች<br />
ያህል ጊዜው ወስደዋል ብንል ስህተት<br />
አይመስለኝም።<br />
በ400 አመቶች ላይ ያልተሳኩት<br />
የመንግስት ሽግግሮች የወሰዱት ጊዜ<br />
ቢጨመርስ? በዚያ ላይ ኢትዮጵያ<br />
ከቱርኮች እና ከኢጣሊያ ጋር<br />
ያደረገቻቸው ጦርነቶች የወሰዱት<br />
ጊዜ ቢጨመርስ?<br />
እንደ እኔ ከሆነ በአጠቃላይ በትንሹ<br />
ከ500 አመቶች ላላነሰ ጊዜ ኢትዮጵያ<br />
እጅ እና እግሯ በጦርነት ተተብትቦ<br />
ከአገር ውስጥ ስልጣኔ እንዳይበቅል<br />
ተደርጓል። ትንሽ የሰላም ጊዜ<br />
እና ጥሩ መሪ ሲገኝ የሚደረገው<br />
እድገትም ለጥቀው በሚካሄዱ<br />
ጦርነቶች ይወድማሉ። አገሪቱ ወደ<br />
ኋላ ትሄዳለች። ይህን የእርስ በርስ<br />
ጦርነት አውዳሚነት እና ጎታችነት<br />
ጸባይ አስመልክቶ ተክለ ፃዲቅ<br />
መኩሪያ ካፄ ልብነ ድንግል እስከ<br />
ዐፄ ቴዎድሮስ በሚለው መጽሐፉ<br />
የታላቁ እያሱን ዘመን እንደ ምሳሌ<br />
በመውሰድ በታላቁ እያሱ በዘመን<br />
የገነባው በሙሉ ከታላቁ እያሱ በኋላ<br />
በመጡት የርስ በርስ ጦርነቶች<br />
መውደማቸውን ይተርካል።<br />
የመንግስት ሽግግር እርስ በርስ<br />
ጦርነት ታሪካችን ኢትዮጵያችንን<br />
ወደ ኋላ የማስቀረት እንጂ ወደ<br />
ስልጣኔ የማራመድ ሚና ተጫውቶ<br />
እንደማያውቅ ግልጽ ይመስለኛል።<br />
የመንግስት ሽግግር ባህላችን ብዙ<br />
ጊዜ አቃጥሏል ኢትዮጵያ ወደፊት<br />
እንዳትራመድ በማድረግ። ከዚህ በኋላ<br />
ኢትዮጵያ በስልጣኔ ብዙ እርቀዋት<br />
የሄዱትን አገሮች ለመድረስ የርቀት<br />
ቅነሳ ስራ ላይ በትጋት መሰማራት<br />
አለባት። ወደ ስልጣኔ መንደር<br />
የሚያደርሱ ብዙ ስራዎች በትጋት<br />
መስራት ይጠበቅባታል። ለመንግስት<br />
ሽግግር የሚደረግ የ’እርስ በርስ<br />
ጦርነት ግን አንዱ አይደለም።<br />
በቅርቡ ደግሞ ትጥቅ ትግል<br />
ወደ ገፅ 6 ይዞራል
ነገረ-ኢትዮጵያ<br />
ቅፅ 1 ቁጥር 2<br />
የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም.<br />
10<br />
የአስር ሳንቲም ኢኮኖሚ ወፖለቲካ<br />
አ በላይ ማናዬ<br />
ያስር በምዕራብ ጎጃም ዞን ባህር ዳር ዙሪያ<br />
ወረዳ ነዋሪ ነበር፤ አሁን ጠቅልሎ የከተማ<br />
ነዋሪ ሆኗል፣ ባህር ዳር፡፡ አሁን ላይ ያስር<br />
እኔ ነኝ ያለ የናጠጠ ሃብታም ነጋዴ ነው፡<br />
፡ ያስር የሚለው ስሙም ተቀይሯል፡፡<br />
ለዚህ ጽሑፍ ብቻ የድሮ ስሙን ተጠቅመን<br />
እንቀጥላለን፡፡<br />
ያስር የሚለውን ስም ያወጡለት<br />
በተወለደባት ትንሽ የገጠር ከተማ ከልጅነት<br />
ጊዜው ጀምሮ ይሰራው ከነበረው የንግድ<br />
(ችርቻሮ) ስራ ጋር በተያያዘ ነበር፤ አንዱን<br />
ጥሎ አንዱን ያነሳበት ከነበረው የችርቻሮ<br />
ገበያው፡፡ በለጋነቱ፣ ገና የችርቻሮ ንግድን<br />
‹ሀ› ብሎ ሲጀምር ወላጅ እናቱን (አባቱ<br />
በህይወት የሉም) የጠየቃት ሀምሳ ሳንቲም<br />
ብቻ እንደነበር ያስር ዛሬ ላይ በትውስታ<br />
ይናገራል፡፡ ብላቴናው ያስር ከዕናቱ ባገኛት<br />
ሀምሳ ሳንቲም ትንንሽ የዕለት ከዕለት<br />
የህብረተሰቡ መገልገያዎችን እና የህጻናትን<br />
ጥያቄዎች ‹ማስቀየሻ› ጣፋጭ ነገሮችን<br />
እያዞረ በገበያ ግርግር መሐል ይሸጥ ጀመር፡<br />
፡ በተለይም መርፌ፣ ከረሚላ፣ ማስቲካ፣<br />
ምላጭ፣ ክር፣ መርፌቁልፍ፣ አዝራር እና<br />
የመሳሰሉትን ሸቀጣ ሸቀጦች ለገበያተኛው<br />
እዚያው ባለበት ቦታ ይዞ ከተፍ በማለት<br />
ታወቀ፡፡ ትንሽ ጊዜ ሲዘዋወር ካልታዬ<br />
እንኳ ‹ያስር የት ሄደ› ባዩ ይበረክታል፡፡<br />
ይህ ፈጣንና ፍልቅልቅ ብላቴና ያለችውን<br />
ትንሽ ሳንቲም በፍጥነት እየተገለገለ<br />
መጠኗ ከዕለት ወደ ዕለት እንድትጨምር<br />
አደረጋት፡፡ በተለይ ቅዳሜ ዕለት ለያስር<br />
የሞት የሽረት ቀኑ ነበረች፤ ሞቅ ባለው<br />
ገበያ ውሰጥ እየተሹለከለከ ችርቻሮውን<br />
የሚያቀላጥፍባት ቀን ቅዳሜ ናት፡፡ ወዲያው<br />
ከአንድ ደንበኛው ሱቅ ሸቀጦችን ይገዛል፤<br />
ወዲያው በገበያተኛው መሀል እየተሹለከለከ<br />
ያጣራል፡፡ ማንም ይግዛው ማን፣ ምንም<br />
ይሽጥ ምን ያስር ጋር ያለው ዋጋ ያው<br />
አስር ሳንቲም ብቻ ነበር፤ መርፌ ባስር<br />
ሁለት ገዝቶ ከሆነ ባስር አንድ ይሸጣል፡፡<br />
በቃ ይህ የያስር ገበያ ነው፡፡ ለያስር ከአስር<br />
ሳንቲም በላይ ወጭ አውጥቶ ዕቃ መግዛት<br />
ኪሳራ ነው፤ ምክንያቱም ሰዎች ካስር<br />
ሳንቲም ውጭ ባለ ዋጋ አይገዙትም ነበር፡፡<br />
እንዲህ እንዲህ እያለ ያስር ከአስር<br />
ሳንቲም ጋር ጋብቻ መሰረተ፤ ጋብቻውም<br />
ተመቸው፤ ብዙ ትርፍ ይዞለትም መጣ፡<br />
፡ የገንዘብ ትርፍ ብቻ ሳይሆን ያላሰበውን<br />
ዕውቅናም አተረፈለት፤ ይህም እናቱ<br />
ያወጣችለትን ስም እንኳ አስቀየረው፡<br />
፡ ሁሉም ሰው ከዕሱ ዕቃ ሲገዛ ባስር<br />
ሳንቲም ብቻ በመሆኑ የብላቴናውን ስም<br />
ያስር አሉት፣ ገበያተኞቹ፡፡ እሱም ስሙ<br />
ተመቸው፤ ድንገት ገበያተኛውን ጠጋ<br />
እያለ ‹ያስር!...ያስር!...ያስር አለ!› ይል<br />
ጀመር፡፡ ገበያተኛውም ‹ያስር መርፌ›፣<br />
‹ያስር ከረሚላ›፣ ‹ያስር አዝራር›፣ ‹ያስር<br />
መርፌቁልፍ›…እያለ ይሸምተው ነበር፡<br />
፡ ስሙ ያስር፣ የሚሸጣቸው ነገሮች<br />
ዋጋቸው አስር ሳንቲም፤ መልካምና ለያስር<br />
የተመቼው ስምሙ ጋብቻ ሆነ፡፡<br />
አሁን ያስርን በቀድሞ ስሙ የሚጠራው<br />
ሰው ጠፋ፤ ምናልባት እናቱም ብትሆን<br />
ከዚህ ሁሉ በላይ ግን ያጣነው ትልቅ ጸጋ አለ፤ መብትን አሳልፎ<br />
መስጠት፤ (የአስር ሳንቲም ፖለቲካ ልንለው እንችላለን)፡፡<br />
ይህ ከገንዘቡም በላይ ነው፡፡ ባለታክሲዎች (ረዳቶች) በራሳቸው<br />
ጊዜ የታክሲን ታሪፍ 2 ብር ከ90 የነበረውን ዋጋ 3 ብር<br />
አድርገውታል፡፡ ከስንት አንድ ሰው መልስ ሲጠይቃቸው እንኳ<br />
ይገላምጡታል፤ በተጨማሪም ሳንቲሙን ያለአግባብና ስርዓት<br />
በጎደለው መልኩ ሲወረውሩለት ይታያል፡፡ ለምን ተጠየኩ<br />
እንደማለት! ይህም መጀመሪያ እኛው ራሳችን ያስለመድናቸው<br />
ነገር በመሆኑ ነው፤ ‹ቀድሞ ነበር እንጂ…› የሚሉት ብሂል<br />
መሆኑ ነው፡፡<br />
የምታስታውሰው አትመስልም፤ ‹ያስር›<br />
የሉታል ‹አቤት!› ይላል፡፡ ያስር ኑሮው፣<br />
ገቢው ተሻሻለ፡፡ ከራሱ የትምህር ቤት ወጭ<br />
አልፎ ለእናቱ ደራሽ ሆነ፤ ከነበሩበት የከፋ<br />
ድህነት ውስጥ አውጥቶ ማገገሚያ ክፍል<br />
ውስጥ ጨመራቸው፡፡ ቀስ በቀስ የያስር<br />
ግብይት ከአስር ሳንቲም ከፍ እያለ መሄዱ<br />
አልቀረም ነበር፤ ቢሆንም ግን ስሙ፣<br />
መጠሪያው አሁንም ያው ያስር ነበር፡፡<br />
ያስር በዚህ ስም እየተጠራ፣ ንግዱን ግን<br />
እያስፋፋ ለዓመታት ዘለቀ፤ በዓዕምሮም<br />
ሆነ በአካል እያደገና እየጎለበተም መጣ፤<br />
ገቢውም ደረጀ፡፡<br />
የያስር ህይወት ከአስር ሳንቲም ጋር<br />
የተቆራኘች ሆና የዘለቀችው ለአጭር<br />
ጊዜ ብቻ አይደለም፤ ዛሬም ያስር እና<br />
አስር ሳንቲም ቁርኝታቸው ጥብቅ ነው፡<br />
፡ የዛሬው የናጠጠ ነጋዴነት፣ የዛሬው<br />
የተትረፈረፈ ሃብትና ንብረት ባለቤትነት፣<br />
የዛሬው ክብርና ሞገስ፣ የዛሬው በተደላደለ<br />
ሁኔታ ህይወትን ቤተሰብን መምራት<br />
መሰረታቸው አስር ሳንቲም ናት፡፡ በአስር<br />
ሳንቲም ነግዶ አትርፏል፤ በአስር ሳንቲም<br />
ዕውቅናን አግኝቷል፡፡ የሚገርመው ያስር<br />
በደንበኞቹ ዘንድ ታማኝና ቅን ነበር፤ ዛሬም<br />
ድረስ እንዲያ እንደሆነ ይነገርለታል፡፡<br />
በተተመነው ዋጋ ነግዶ ከማትረፍ ውጭ<br />
በሌላ ነገር አይታማም ይሉታል ደንበኞች፡፡<br />
አሁን ላይ ያስር ሀብታምና በርካታ<br />
ካፒታል የሚያንቀሳቅስ ነጋዴ ነው፤ ከዚህ<br />
ያደረሰችውን አስር ሳንቲም ግን አይንቃትም፡<br />
፡ አስር ሳንቲም ለማትረፍ ትናንት ብቻ<br />
ሳይሆን ዛሬም ከመነገድ ወደ ኋላ አይልም፡<br />
፡ አውቆ ካልሆነ በቀር አስር ሳንቲምን<br />
ንቆ መልስ ከመቀበል አይመለስም፤<br />
ምክንያቱም ዋጋዋን ያውቃታል፡፡ ‹‹አስር<br />
ሳንቲም ትንሽ መስላ የምትታዬን ዋጋዋን<br />
በሚገባ ካልተረዳንና ህይወትን የመለወጥ<br />
አቅሟን ካላወቅን ነው፤ እኔ በአስር ሳንቲም<br />
በምሸጠው መርፌ አይደለም እንዴ የተቀደደ<br />
ልብስህን ሰፍተህ ገመናህን የምትሸፍነው?<br />
ባስር ሳንቲም በገዛኸው መርፌ አይደለም<br />
እንዴ ለስቃይ የዳረገህን እሾህ ከእግርህ<br />
ነቅሰህ የምታወጣው? ታዲያ አስር ሳንቲም<br />
ዋጋዋ ትልቅ አይደለም ወይ?›› በማለት<br />
ይጠይቃል ያስር፡፡<br />
ብዙዎቻችን ወደ አዲስ አበባ ታክሲዎች<br />
ዘው ብለን ገብተን የአስር ሳንቲምን ዋጋና<br />
ከሳንቲሟ ጋራ እያጣን ያለነውን ውድ<br />
ጸጋ ካየን ግን ያስር ለአስር ሳንቲም ካለው<br />
ግንዛቤ በእጅጉ የተለዬ ሆኖ እናገኘዋልን፡<br />
፡ በየጊዜው ዋጋው እየተከለሰ የሚገኘው<br />
የታክሲ የአንድ ፌርማታ ጉዞ ክፍያ ወይም<br />
ታሪፍ ብዙ ነገሮችን እያሳየን ይገኛል፡<br />
፡ ላለፉት ሁለት ወራት ስራ ላይ ባለው<br />
ታሪፍ መሰረት የሁለት ፌርማታ ዋጋ 2<br />
ብር ከ90 ሳንቲም ነው፡፡ ለሶስት ብር አስር<br />
ሳንቲም የጎደለው ማለት ነው፡፡ ይህቺ አስር<br />
ሳንቲም ናት እንግዲህ መነጋገሪያችን፡፡<br />
ብዙ ተሳፋሪዎች 3 ብር ከፍለው መልስ<br />
አይቀበሉም፤ መልሳቸው ደግሞ አስር<br />
ሳንቲም ናት፡፡ ብዙ የታክሲ ረዳቶች<br />
(ወያላዎች) 3 ብር ተቀብለው መልስ<br />
አይሰጡም፤ መልሱ ደግሞ አስር<br />
ሳንቲም ናት፡፡ ግን ለምን? በጥናት ላይ<br />
የተመሰረተም ባይሆን ብዙዎቹ ተሳፋሪዎች<br />
አስር ሳንቲምን ከመናቅ የመነጨ ሊሆን<br />
ይችላል መልሳቸውን የማይጠይቁት፡፡ ብዙ<br />
የታክሲ ረዳቶች አስር ሳንቲምን ለማስቀረት<br />
ካላቸው ፍላጎት (በቀን ምን ያህል ገንዘብ<br />
ማስቀረት እንደሚችሉ ያውቃሉና) አሊያም<br />
ጠያቂ ከሌለ በማለት ሊሆን ይችላል መልስ<br />
የማይሰጡት፡፡ ሁለቱም ወገኖች ግን ተገቢ<br />
ያልሆነ አረዳድ ውስጥ የገቡ ናቸው፡፡ አስር<br />
ሳንቲም ዋጋ አላት፤ አስር ሳንቲም ገንዘብ<br />
ናት፡፡<br />
ቀደም ብለን ያነሳነው ያስር በአስር<br />
ሳንቲም ትልቅ ደቋና ደፍኖባታል፤ ትልቅ<br />
ቁምነገር ከውኖባታል፡፡ ስለዚህም አስር<br />
ሳንቲም ትንሽ አይደለችም፡፡ ተሳፋሪዎች<br />
ንቀዋትም ሆነ በሌላ ምክንያት ታክሲ<br />
ውስጥ ትተዋት የሚወርዱት አስር<br />
ሳንቲም ተጠራቅማ የጎጆን ቀዳዳ መድፈን<br />
ይቻላታል፤ ቢነግዱባት አትርፋ ቤት<br />
ለመስራት ትበቃለች (የያስርን እውነታ ልብ<br />
ይሏል)፡፡ አንድ ተሳፋሪ በቀን 20 ሳንቲም<br />
ታክሲ ውስጥ ትቶ ቢወርድ በወር ውስጥ<br />
6 ብር ያጣል ማለት ነው፡፡ ይህ ስድስት<br />
ብር ለአንድ የኔ ቢጤ አራት ዳቦ ሊገዛለት<br />
የሚችል ገንዘብ ነው፡፡ ለተቸገሩት ወገኖች<br />
የሚውልን (ከእጅ ላይ ያለችን ሳንቲም<br />
መስጠት ታክሲ ላይ ጥሎ እንደመውረድ<br />
ባይቀልም) ገንዘብ እንዲሁ መተው አጓጉል<br />
መቀናጣት ሊሆን ይችላል፡፡<br />
ከዚህ ሁሉ በላይ ግን ያጣነው ትልቅ ጸጋ<br />
አለ፤ መብትን አሳልፎ መስጠት፤ (የአስር<br />
ሳንቲም ፖለቲካ ልንለው እንችላለን)፡፡<br />
ይህ ከገንዘቡም በላይ ነው፡፡ ባለታክሲዎች<br />
(ረዳቶች) በራሳቸው ጊዜ የታክሲን ታሪፍ<br />
2 ብር ከ90 የነበረውን ዋጋ 3 ብር<br />
አድርገውታል፡፡ ከስንት አንድ ሰው መልስ<br />
ሲጠይቃቸው እንኳ ይገላምጡታል፤<br />
በተጨማሪም ሳንቲሙን ያለአግባብና<br />
ስርዓት በጎደለው መልኩ ሲወረውሩለት<br />
ይታያል፡፡ ለምን ተጠየኩ እንደማለት! ይህም<br />
መጀመሪያ እኛው ራሳችን ያስለመድናቸው<br />
ነገር በመሆኑ ነው፤ ‹ቀድሞ ነበር እንጂ…›<br />
የሚሉት ብሂል መሆኑ ነው፡፡<br />
በእጃችን ያለን ነገር መልቀቅ በኋላ<br />
እንደማስመለስ ቀላል አይደለም፡፡ አሁን<br />
ላይ ንቀን የምንተዋት እያንዳንዷ ነገር<br />
ዘግይታ ብዙ ዋጋ ታስከፍለናለች፡፡<br />
ካለመጠየቅ ደጃዝማችነት ይቀራል እንዲሉ<br />
አበው ስለመብታችን የመቆርቆር ንቃት፣<br />
መብታችንን ማስከበር ላይ ድክመት<br />
ይታይብናል፡፡ ከተነጠቅን ወዲያ መጮህ<br />
ብቻ ሳይሆን ቀድሞውንም አሳልፎ<br />
ላለመስጠት መጣር ተገቢ ነው፡፡ ዛሬ አስር<br />
ሳንቲም የወሰደብን ሰው ነገ ቤታችንም<br />
ለመውሰድ ወደ ኋላ ሊል አይችልም፡<br />
፡ ይህ የአስር ሳንቲም ጉዳይ አይደለም፤<br />
ይህ የክብር ጉዳይ ነው፡፡ ግለሰቦችም ሆነ<br />
መንግስታት በማናለብኝነት የሚነጥቁን<br />
የእኛ የሆኑ ነገሮች ሁሉ መነሻቸው<br />
የእኛ አለመጠየቅና ለመብታችን ጥብቅና<br />
አለመቆም ነው፡፡<br />
ዛሬ ቀበሌ ላይ የመናገር መብትህን የነፈገህ<br />
የቀበሌ አስተዳዳሪ ዝም ከተባለ የሐገር<br />
መሪም ሆኖ ጨቋኝና የለየለት አምባገነን<br />
መሆኑ የታወቀ ነው፤ ዛሬ ጨቋኝነቱን<br />
ቀበሌ ላይ የነገርነውና የታገልነው ሰው ሀገር<br />
የመምራት ዕድሉን አግኝቶ ስልጣን ላይ<br />
ቢወጣ የህዝብን ጉልበት የተረዳ ለመሆኑ<br />
ሳይታለም የተፈታ ጉዳይ ነው፡፡ እናም፣<br />
የእኛ ለመብቶቻችንና ለገንዘባችን ቸልተኛ<br />
መሆን አምባገነንና ስግብግብ መሪዎችን<br />
ለመፍጠራችን እማኝ ነው፡፡ የመብት ትንሽ<br />
የለውም፤ መብት የክበር ጉዳይም ነው፡፡<br />
ስንደፈር በትንሹ ነው፣ በትልቁ ነው ልንል<br />
አንችልም፡፡ ጭብጡ ያለው መርሁ ላይ<br />
ነው፡፡ መብቱን በእንዝላልነት አሳልፎ የሰጠ<br />
ሰው መልሶ ሲጠይቅም አያምርበትም፡፡
11የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2<br />
የኔ-ሐሳብ<br />
ነገረ-ኢትዮጵያ<br />
እንደሀገር መግባባት የተሳነን ‹ባቢሎናውያን›<br />
ትሁን ተስፋ<br />
ባቢሎናውያን በስልጣኔ ከመራቀቃቸው<br />
የተነሳ ወደ ሰማይ ህንጻ በመገንባት<br />
አምላካቸው ጋር መድረስ ፈለጉ፡፡ ይህ<br />
ስራቸው ያላስደሰተው አምላክም ይግባቡበት<br />
የነበረውን ቋንቋቸውን ደበላለቀባቸው፡<br />
፡ ከቋንቋቸው መደበላለቅ የተነሳ መግባባት<br />
ተስኗቸው አካፋ የተጠየቀው ዶማ፣ ድንጋይ<br />
የተጠየቀው ጭቃ፣ ሚስማር የተጠየቀው<br />
አጠና እያቀረበ መግባባት ባለመቻላቸው<br />
የገነቡት ሰማይ ጠቀስ ህንጻ ከግቡ ሳይደርስ<br />
ሊፈርስ ችሏል፡፡<br />
ሁሌም ይህን ታሪክ ሳስታውስ የሀገሬ<br />
ልጆች መግባባት አለመቻል ይታወሰኝና<br />
ምን አልባት ቋንቋችን ተደበላልቆ ይሆን<br />
እንድል ያስገድደኛል፡፡ በብሄራዊ ደረጃ<br />
መግባባት ከማይችሉ ሀገራት መካከል<br />
ኢትዮጵያ በቀዳሚነት ትጠቀሳለች ብል<br />
ማጋነን አይሆንም፡፡ ኢትዮጵያውያን እንደ<br />
ሀገር ከምንግባባባቸው ነገሮች ይልቅ<br />
የማንግባባባቸው ጉዳዮቻችን ብልጫውን<br />
ይወስዳሉ፡፡ በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ<br />
ያለመግባባታችን ጥግ መራራቅ ነው፡፡ ከዚህ<br />
ያለመግባባት ችግራችን የተነሳ የተጣባን<br />
ልዩነትን በጉልበትና በጠብ-መንጃ የመፍታት<br />
አባዜ ያለመግባባታችንን ወደ ጫፍ<br />
በመለጠጥ ወደ መጠፋፋት ሲገፋን ኑሯል፡<br />
፡ በጠረጴዛ ዙሪያ ማለቅ የሚገባው ልዩነት<br />
የተራዘመ ብጥብጥና ግድያ ካስከተለ በኋላ<br />
አንዱ ጉልበታም በሌላ ጉልበታም እየተተካ<br />
እዚህ ደርሰናል፡፡ ዓለም አንድ መንደር እየሆነ<br />
በመጣበት በዚህ ጊዜ የእኛ መንደሮች ግን<br />
የዓለም ጥግ ላይ ያሉ የምድር ዋልታዎችን<br />
ያክል ተራርቀዋል፡፡<br />
ቀጥዬ ለምን መግባባት ተሳነን፣<br />
ላለመግባባታችን ተጠያቂው ማን ነው፣<br />
የማንግባባባቸው ጉዳዮች የትኞቹ ናቸው?<br />
እና የመሳሰሉትን ጉዳዮች በማሳያዎች<br />
ለመዳሰስ እሞክራለሁ፡፡<br />
ማሳያ አንድ፡- ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት<br />
የሀገራችን የፖለቲካ ልሂቃን ኢትዮጵያና<br />
ኢትዮጵያዊነትን የሚያዩበት መነጽር<br />
የተንሸዋረረ መሆኑ ላለመግባባታችን እንደ<br />
ምክንያት ሆኖ ይነሳል፡፡ አንዳንድ ምሁራን<br />
ኢትዮጵያዊነትን የሀበሻነት (አማርኛና<br />
ትግርኛ ተናጋሪዎች) መገለጫ ብቻ<br />
አድርገው ይወስዱታል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ<br />
የሚመጣው የኢትዮጵያ ታሪክ ነው፡፡<br />
የኢትዮጵያ ታሪክ በአንዳንዶቹ አምስት ሺህ<br />
ዘመን ድረስ ሲለጠጥ በሌሎቹ ደግሞ ወደ<br />
መቶ አመት ይኮማተራል፡፡ የአምስት ሺህ<br />
ዘመን ታሪክ ተብሎ የሚጠቀሰው የኖህ ልጅ<br />
ካም ወደ ኢትዮጵያ መምጣት ጋር ተያይዞ<br />
ያለው ሲሆን፣ በዚህም ኢትዮጵያ ተብላ<br />
በመጽሀፍ ቅዱስም ሆነ በሌሎች መጽሀፍት<br />
የምትጠቀሰው ሀገር ከግብጽ በታች ያለውን<br />
የአፍሪካ ምድር ትይዛለች፡፡<br />
በበተቃራኒው ደግሞ የመቶ አመት ታሪክ<br />
ባለቤት የሚያደርጓት አሉ፡፡ ለመቶ አመቱ<br />
ክርክር የሚጠቀሰው የቀድሞው ጠቅላይ<br />
ሚንስትር የአቶ መለስ ትርክት ነው፡፡ አቶ<br />
መለስ ጫካ መነበሩበት ዘመን ”የኤርትራ<br />
ህዝብ ትግል ከየት ወዴት” በሚል<br />
ርዕስ ያሳተሙት መጽሀፍ ‹‹ኢትዮጵያ<br />
የመቶ አመት ታሪክ ነው ያላት›› ይልና<br />
የኢትዮጵያ ፈጣሪ ንጉስ ምኒልክ እንደሆኑ<br />
ለማስረዳት ያጣጥራል፡፡ መከራከሪያቸውን<br />
ያጠናክርላቸው ዘንድም ‹‹የአክሱም ሀውልት<br />
ለወላይታው ምኑ ነው?›› ሲሉ ይጠይቃሉ፡፡<br />
ዳሩ ግን የአክሱም ሀውልት ሲገነባ ወላይታው<br />
አስተዋጽኦ ማድረጉን ዘንግተውት አይደለም፤<br />
‹ኢትዮጵያ ቅኝ ገዥ ነች› ወደሚል ሀላፊነት<br />
የጎደለው መከራከሪያ ለመግፋት እንጂ፡፡ ከዚህ<br />
ጋር በተያያዘ አንዳንድ የኦሮሞ ልሂቃን ቅኝ<br />
ተገዝተናል እንገነጠላለን የሚሉት ሌላው<br />
ኢትዮጵያዊነት ላይ የተደነቀረ ሳንካ ነው፡፡<br />
በነዚህ ምሁራን ትርክት መሰረት ኢትዮጵያ<br />
ቅኝ ገዥ ነች፤ ኢትዮጵያዊነትም በግድ<br />
የተጫነብን ቀንበር ስለሆነ አንቀበለውም<br />
ወደሚል ጫፍ ይለጠጣል፡፡ ይህንን<br />
የኢትዮጵያን ቅኝ ገዥነት ለማስረዳትም<br />
ጎሰኝነትን አጥብቆ በማጓን ኢትዮጵያዊነትን<br />
መገዳደር መገለጫው ያደርጉታል፡፡ ብቻ<br />
ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት የተወሰነው<br />
ህዝብ ፍላጎት ብቻ በማስመሰል እውነቱን<br />
ለማድበስበስና አውቆ ላለመግባባት የቆረጥን<br />
እንመስላለን፡፡<br />
አንዳንድ የስልጣን ጥም የተጣባቸው ግለሰቦች<br />
ልክ እንደ ኤርትራው መሪ ኢሳያስ አፈወርቂ<br />
“ባርነት ወይስ ነጻነት” በሚል የማወናበጃ<br />
ምርጫ ትንንሽ ግዛቶችን መፍጠር ይፈልጋሉ፡<br />
፡ በዚህም የተነሳ ሳንግባባ እንደወንድማማች<br />
ሳንተያይ የጎሪጥ እንደተዳባን እዚህ ደርሰናል፡<br />
፡ እዚህ ላይ መሰመር ያለበት ያለመግባባቱ<br />
ጉዳይ የፖለቲካ ልሂቅ ነኝ በሚለው እንጅ<br />
በሌላው ህዝብ ዘንድ የሌለ መሆኑን ነው፡<br />
፡ ብቻ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት እንዲህ<br />
ሳያግባባን አለን፡፡<br />
ማሳያ ሁለት፡- ወደብና የባህር በር<br />
ኢትዮጵያ ለብዙ ዘመን ጠላት ሲያፈራባትና<br />
ሲያዋጋት የኖረው የባህር በሯ መሆኑ<br />
ይታወቃል፡፡ ይህን የባህር በር ለመያዝ<br />
በተደረገው ተጋድሎ አባቶቻችን ብዙ<br />
ጀብዱ ፈጽመዋል፡፡ ይህን የዘነጋው አቶ<br />
መለስ ዜናዊ ግን አሰብን አሳልፎ ሰጥቷል፡<br />
፡ ስለጉዳዩ ሲጠየቅም፣ “የባህር በር<br />
የተስፋፊወችና የጦርነት ናፋቂወች ወሬ<br />
ነው፤ አንድ ሀገር ለማደግ የግድ የባህር<br />
በር አያስፈልጋትም፤ ኢሳያስ አፈወርቂ<br />
ከፈለገ ግመሎቹን ያጠጣበት”፡፡ ጠቅላይ<br />
ሚንስትሩ ይህን ቢሉም ወደባችን አሳልፈን<br />
በመስጠታችን ብቻ ለጅቡቲ በቀን ከሶስት<br />
ሚሊዮን ዶላር በላይ እንደምንከፍል<br />
አጥተውት አይደለም፡፡ ከምንከፍለው ዶላር<br />
በተጨማሪ የራሳችን ሚስጥር የሚባል ነገር<br />
ሊኖረን አይችልም፤ በተለይ የጦር መሳሪያን<br />
በተመለከተ፡፡ በነገራችን ላይ ለጂቡቲ ወደብ<br />
የምንከፍለው ዶላር አባይን ለመገደብ ቢውል<br />
በአመት ከስድስት ወር ውስጥ የሚወጣው<br />
ብቻ ይበቃን ነበር፡፡ አሁንም ልብ ማለት<br />
የምንችለው ኢህአዴጎች ይህን ቢሉም አሰብን<br />
አንጋጦ የሚያይ ዜጋ መኖሩ እሙን ነው፡<br />
፡ በመሆኑም የወደብ ጥያቄ ላለመግባባታችን<br />
አንዱ ምክንያት ነው፡፡<br />
ማሳያ ሦስት፡- የአድዋ ድል<br />
የአድዋ ድል ለጥቁር የሰው ዘር ሁሉ የነጻነት<br />
ተምሳሌት መሆኑ የሚዘነጋ አይደለም፡፡ እነ<br />
አብርሃም ሊንከን እነ ማልኮን ኤክስን ጨምሮ<br />
ብዙ ለጥቁር ህዝቦች ነጻነት የታገሉ ሰዎች<br />
ጥቁር ነጭን ሊያሸንፍ እንደሚችል ትምህርት<br />
ያገኙት ከአድዋ መሆኑ ጸሀይ የሞቀው ሀቅ<br />
ነው፡፡ ይህ የጥቁሮች የመብት እንቅስቃሴ<br />
ኢትዮጵያኒዝም ተብሎም ይጠራል፡<br />
፡ ኢትዮጵያ አድዋ ላይ ድል ማድረጓን<br />
ተከትሎ እንደ ታላቋ ጽዮናዊት ኢየሩሳሌም<br />
ወደ ኢትዮጵያ ሀይማኖታዊ ጉዞ የሚያደርጉ<br />
ጥቁሮች ተበራከቱ፡፡ የሀይቲው ቤኒቶ<br />
ሲልቪያን እና የምዕራብ ኢንዲያው ጆሴፍ<br />
ቪታሊየን ወደ ተስፋይቱ ምድር ኢትዮጵያ<br />
ጉዞ ያደረጉ የመጀመሪያቹ ጥቁሮች ናቸው፡፡<br />
እነሱን በመከተል እንደ ቡከር ቲ.ዋሽንግተን፣<br />
አይዳ ቢ.ዌልስ፣ ደብሊዩ ኢ.ቢ ዱበይሰን<br />
የመሳሰሉ ታዋቂ ጥቁር አፍሪካውያን ስለ<br />
አድዋ እና የኢትዮጵያ የነጻነት ተምሳሌትነት<br />
በስፋት ማውራት ጀመሩ፡፡<br />
ከተወሰኑ ትውልዶች በኋላ “በራስ<br />
ተፈሪያን” ስያሜ የሚደረገው ጉዞም የአድዋ<br />
ተጽዕኖ ውጤት ነው፡፡ አድዋ ሲነሳ አብሮ<br />
የሚነሳ ሀገራዊ አንድነታችን ነው፡፡ ይህ<br />
የጥቁሮች ሁሉ መኩሪያ የሆነ ድል ግን<br />
እኛን ባለቤቶቹን ሊያግባባን አልቻለም፡<br />
፡ አድዋ ኢትዮጵያንም በአለም ብቸኛዋ<br />
በነጭ ቅኝ ያልተገዛች ሀገር ያደርጋታል፡፡<br />
እዚህ ላይ በታሪክ ቅኝ ያልተገዙ የአፍሪካ<br />
ሀገራት እየተባሉ ሲጠቀሱ የምንሰማቸው<br />
ላይቤሪያንና ኢትዮጵያን ቢሆንም የላይቤሪያ<br />
ቅኝ አለመገዛት ግን ብዙም የሚያከራክር<br />
አይደለም፡፡ ምክንያቱም ላይቤሪያ ተብሎ<br />
የሚጠራው ሀገር ከአሜሪካ በተመለሱ<br />
‹ባሪያዎች› የተገነባች ሀገር ስለሆነች እንደ<br />
ነጻ ሀገር ለመጥቀስም የሚያስኬድ ስላልሆ<br />
ነው፡፡ ይህ ልንኮራበት የሚገባን ታሪካችን<br />
እንደውም ለኤርትራውያን ተገንጣዮች<br />
የሚያሳፍር ተደርጎ ይቆጠራል፡፡ ምኒልክ<br />
አድዋ ላይ ተመልሰው ኤርትራን ለጣልያን<br />
አሳልፈው ሰጡብን የሚለው ትርክት ለእነዚህ<br />
ተገንጣዮች እንደ መልካም የመጫወቻ ካርድ<br />
አገልግሎአቸዋል፡፡ ሻቢያና ህወሓት ጫካ<br />
በነበሩበት ወቅት ወታደር ለመመልመል<br />
“የአድዋን ታሪክ ትቀበላለህ አትቀበልም”<br />
የሚል መስፈርት እንደነበራቸው የትናንት<br />
ትዝታ ነው፡፡ ለማነኛውም የአድዋ ድል<br />
ሌላኛው ያለመግባባታችን ምንጭ መሆኑ<br />
አልቀረም፡፡<br />
ማሳያ አራት፡- ሰንደቅ አላማ<br />
ሰንደቁ አላማ አንዱ የአንድ ሀገር መለያ<br />
ነው፡፡ ኢትዮጵያ በዚህ የታደለች ነበረች፡<br />
፡ አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ሰንደቃችን<br />
የነጻነታችን ምልክት የአንድነታችን<br />
ተምሳሌት ሆኖ ለብዙ ዘመን ኖሯል፡፡<br />
ነገር ግን በየጊዜው የሚነሱት አምባገነኖች<br />
የራሳቸውን ምልክት ሲለጥፉበትና ህዝቡም<br />
አርማውን በግድ እንዲቀበል ሲገፉት መኖሩ<br />
ሀቅ ነው፡፡ የቅርብ ጊዜዎቹን ብንወስድ እንኳ<br />
ንጉሱ የይሁዳ አንበሳ ምልክት ሲለጥፉበት፣<br />
ደርግ በበኩሉ የማያውቀውን የሶሻሊዝም<br />
መዶሻ ለብዶበት ነበር፡፡ ቀጥሎም ኢህአዴግ<br />
ታጋይ መሪው ‹‹ባንዲራ ጨርቅ ነው›› ብሎ<br />
በቀደደለት ክፍተት ተጠቅሞ የበሶ መቋጠሪያ<br />
አድርጎት አዲስ አበባ እንደገባ ትናንት<br />
የነበሩት ይመሰክራሉ፡፡<br />
ባንዲራ ጨርቅ ነው የሚለው የአቶ መለስ<br />
አባባልም ኢህአዴግን ምን ያክል ዋጋ<br />
እንዳስከፈለው የሚታወስ ነው፡፡ ኢህአዴግም<br />
ጨርቅ ባለው ባንዲራው ላይ ኮከብ መሀሉ<br />
ላይ ሰፍቶ የእኩልነትና የመከባበር ምልክት<br />
ነው እያለን ነው፡፡ መቸም ኮከብ በምን<br />
መልኩ የአንድነትና የመከባበር ምልክት<br />
እንደሚሆን ኢህአዴግም ሊያውቀው<br />
አይችልም፡፡ ለማንኛውም ይህ ሰንደቁ መሀል<br />
ላይ የተሰፋው ሰማያዊ ኮከብ ለልዩነታችን<br />
እንደ ምክንያት ሆኖ አገልግሏል፡፡ ባለኮከብ<br />
ሰንደቅ አንቀበልም ያሉ ኢትዮጵያውያን<br />
በተለያየ ክብረ በአላት ላይ ኮከብ የሌለውን<br />
ባንዲራ መጠቀማቸው ያሳሰበው ኢህአዴግ<br />
የባንዲራ አጠቃቀም አዋጅ እስከማውጣት<br />
ድረስ ተገዷል፡፡ የሰንደቅ አላማ ቀንም ማክበር<br />
ሰንደቁ አላማ አንዱ የአንድ ሀገር መለያ ነው፡፡ ኢትዮጵያ በዚህ የታደለች ነበረች፡፡<br />
አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ሰንደቃችን የነጻነታችን ምልክት የአንድነታችን ተምሳሌት ሆኖ<br />
ለብዙ ዘመን ኖሯል፡፡ ነገር ግን በየጊዜው የሚነሱት አምባገነኖች የራሳቸውን ምልክት<br />
ሲለጥፉበትና ህዝቡም አርማውን በግድ እንዲቀበል ሲገፉት መኖሩ ሀቅ ነው፡፡ የቅርብ<br />
ጊዜዎቹን ብንወስድ እንኳ ንጉሱ የይሁዳ አንበሳ ምልክት ሲለጥፉበት፣ ደርግ በበኩሉ<br />
የማያውቀውን የሶሻሊዝም መዶሻ ለብዶበት ነበር፡፡ ቀጥሎም ኢህአዴግ ታጋይ መሪው<br />
‹‹ባንዲራ ጨርቅ ነው›› ብሎ በቀደደለት ክፍተት ተጠቅሞ የበሶ መቋጠሪያ<br />
አድርጎት አዲስ አበባ እንደገባ ትናንት የነበሩት ይመሰክራሉ፡፡<br />
ጀምሯል፡፡ ይህ አዋጅ ሰንደቅ አላማውን<br />
በመኪና ላይ ማውለብለብ የሚችለው<br />
ጠቅላይ ሚንስትር፣ የሀገሪቱ ርዕሰ ብሄርና<br />
አምባሳደሮች እንደሆኑ ቢጠቅስም በዘልማድ<br />
የሚታየው ግን አፈር ጫኝ መኪና ሳይቀር<br />
ሲያንጠለጥለው ነው፡፡ የሚገርመው እኛ<br />
ሰንደቅ አላማችንን ላለመግባባት ይህን ያክል<br />
ስንለጥጠው አብዛኛዎቹ የአፍሪካ ሀገራት<br />
ግን አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ሰንደቁን በተለያየ<br />
መልክ ሲጠቀሙበት እናያለን፡፡ ምክንያቱ<br />
ደግሞ እኛ እንደ ሀገር ሊያግባባን የሚችል<br />
ባንዲራ የለንም የሚል ነው፡፡<br />
ማሳያ አምስት፡- ህገ-መንግስት<br />
የአንድ ሀገር መንግስት ህዝቦቹን<br />
ያስተዳድርበት ዘንድ ህገ መንግስት<br />
ያስፈልገዋል፡፡ በዚህ ህገ መንግስት ውስጥ<br />
ህዝቦች ያላቸው መብትና ግዴታወች<br />
እንዲሁም መንግስት ያለው ስልጣን በህግ<br />
ተገድቦ ይሰጠዋል፡፡ ይህ የሚሆንበት<br />
ምክንያት የመንግስትን ፈላጭ ቆራጭነት<br />
ሚና ለመገደብ ሲባል ነው፡፡ አብዛኛውን ጊዜ<br />
መሪወች የስልጣን እድሜያቸውን ለማራዘም<br />
ሲሉ እንደፈለጉ እንዳይሆኑ ሲባል በህገ<br />
መንግስት ይታሰራሉ፡፡ በሀገራችን የህገ-<br />
መንግስት ታሪክ ውስጥ እስከ አሁን<br />
ከተቀረጹት ህገ መንግስቶች ሁሉ የተሻለ<br />
የሰብአዊም ይሁን የዴሞክራሲያዊ መብቶችን<br />
በማካተት የ1987 ዓ.ምቱ ህገ መንግስት<br />
የተሻለ ነው፡፡ ይህ ማለት ግን ህገ መንግስቱ<br />
እንከን አልባ ነው ማለት አይደለም፡፡<br />
በተለይም አንዳንድ ድንጋጌዎች የልዩነት<br />
መፈጠሪያ ሁነው እናገኛቸዋለን፡፡ ለምሳሌ<br />
የህገ-መንግስቱ አንቀጽ 39 ለሀገር አንድነት<br />
እንቅፋት ነው፣ ስለዚህ ህገ መንግስቱ<br />
በሚፈቅደው መሰረት ይሻሻል የሚል ጥያቄ<br />
ማንሳት በሀገር ክህደት ሊያስከስስ ይችላል፡<br />
፡ ይህ እንኳን ባይሆን የአድሃሪነት ታርጋ<br />
ሊያስለጥፍ ይችላል፡፡<br />
ሌላው የመሬት ባለቤትነት መብትን<br />
የሚያትተው አንቀጽ ነው፡፡ መሬት<br />
የመንግስት ነው፤ ሊሽጥም ሆነ ሊለወጥ<br />
አይችልም የሚለው የኢህአዴግ ግትር<br />
አቋም፣ መሬት የህዝብ መሆን አለበት<br />
ከሚለው የተቃራኒ አቋም ጋር መላተሙ<br />
በህገ-መንግስቱ ላይ ያለውን ልዩነት ሰማይ<br />
እንዲነካ ያደርገዋል፡፡ መሬት የሚሸጠውና<br />
የሚለወጠው በኢህአዴግ መቃብር ላይ ነው<br />
የሚለውን የኢህአዴግ ትንታኔ ነቃፊዎች<br />
የመሬት መሸጥንና መለወጥን ሃሳብ<br />
ለማንበር የግድ ኢህአዴግን መቃብር ውስጥ<br />
መጨመር ግድ ነው ብለው ሊገፉ ይችላሉ፡<br />
፡ በዚህም ህገ መንግስታችን የልዩነት ሰበብ<br />
ከመሆን አልተረፈም፡፡<br />
ማሳያ ስድስት፡- የፍትህና የጸጥታ ተቋማት<br />
አብዛኛውን ጊዜ የሀገራችን የፍትህ<br />
ተቋማት ሁሉንም ሊያስማማ የሚችል<br />
ስራ ሲሰሩ አይታዩም፡፡ እነዚህን የፍትህና<br />
የጸጥታ ተቋማት ስራ በምንዳስስበት ወቅት<br />
የምናገኘው እውነት በጣም አስደንጋጭ ነው፡<br />
፡ ለምሳሌ የሀገር ደህንነትና መረጃ ማዕከል<br />
ስራው የሀገሩን ህልውና መጠበቅ ሆኖ ሳለ<br />
የሚሰራው ስራ ግን ከአንድ የህዝብ ድርጅት<br />
የሚጠበቅ አይደለም፡፡ የኢህአዴግን ህልውና<br />
ለመጠበቅ የተቋቋመ በሚመስል መልኩ<br />
ለኢህአዴግ ያሰጋሉ ያላቸውን ግለሰቦችና<br />
ድርጅቶች እየተከታተለ ማደንና ማስፈራራት<br />
ግፋ ሲልም አፍኖ በመውሰድ አሳፋሪ<br />
ተግባርና እርምጃ ያለ ምንም ፍርድ በራሱ<br />
ሲወስድ ስናይ ተቋሙ የኢህአዴግ የግል<br />
ንብረት ነው እንዴ ያስብላል፡፡<br />
በተጨማሪም ፖሊሶች በተለያየ ወቅት<br />
የወሰዱትን እርምጃ በመንተራስ ስራቸው<br />
ግብር እየከፈለ የቀጠራቸውን ምስኪን ድሀ<br />
መደብደብ ነው እንዴ ብለን እስክንጠይቅ<br />
ያደርሰናል፡፡ ለምሳሌ ያክል በ97 ምርጫ<br />
የተነሳውን አለመግባባት ተከትሎ በመለስ<br />
ዜናዊ ቀጭን ትዕዛዝ መከላከያችንና የፖሊስ<br />
ሀይሉ የወሰደው የእመቃ እርምጃ ከህዝቡ<br />
ጋር እንዲቃቃር አድርጎታል፡፡ በዚህ የተነሳ<br />
ወደ ገፅ 15 ይዞራል
ነገረ-ኢትዮጵያ<br />
ቅፅ 1 ቁጥር 2<br />
ማርቆስ ሀጎሶች እና ዳሮ ነጋሾች ዛሬም<br />
የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም.<br />
ያስፈልጉናል!<br />
-የመንግስት ሰራተኛው እና መምህሩ የደሞዝ ጭማሪ ያስፈልገዋል!<br />
12<br />
እያስፔድ ተስፋዬ<br />
ዓለም አቀፍ ደረጃ የሰራተኛ<br />
ማህበራት እንዴት፣ መቼና ለምን<br />
ተመሰረቱ? ስለምን ታገሉ? ምንስ<br />
አስገኙ? የሚለውን ታሪክ ለመዳሰስ<br />
ቦታውም ጊዜውም አይበቃንም፡፡<br />
የእነዚህ ማህበራት መፈጠር በዓለም<br />
አቀፍ ደረጃ አድካሚ የነበረው የስራ<br />
ሰዓት ወደ 8 ሰዓት ዝቅ እንዲል<br />
መደረግን ጨምሮ ብዙ ለውጦች<br />
አምጥቷል፡፡ የዛሬው ትኩረታችን<br />
ግን የሚሆነው በሀገራችን ከኢሰአማ<br />
አንስቶ እስከ ኢሰማኮ ያለውን<br />
የሰራተኛ ማህበር የመብት ትግል<br />
ታሪክና ዘንድሮም ያላከተመውን<br />
የሰራተኛውን ክፍል (በተለይ<br />
የመንግስት ሰራተኞች) ሰቆቃ እና<br />
ስቃይ በአጭሩ መዳሰስ ነው፡፡<br />
በኃይለስላሴ ዘመን<br />
በሀገራችን ኢትዮጵያ የሰራተኛ<br />
ማህበራት ለመጀመሪያ ጊዜ<br />
የተመሰረቱት በአፄ ኃይለስላሴ<br />
ዘመነ መንግስት ነው፡፡ የታሪክ<br />
ሰነዶች እንደሚጠቁሙት<br />
የመጀመሪያው የሰራተኛ ማህበር<br />
ተብሎ ሊጠቀስ የሚችለው በ1939<br />
የተመሰረተው የኢትዮጵያ ባቡር<br />
ጣቢያ ሰራተኞች ማህበር ነው፡፡<br />
ከዚህ በኋላ ለመመስረት የተሞከሩ<br />
የሰራተኛ ማህበራት በስርአቱ<br />
ከፍተኛ አፈና ይካሄድባቸው የነበሩ<br />
ሲሆን የሰራተኛው መሪዎችም<br />
እስር እና ግድያ ይፈፀምባቸው<br />
ነበር፡፡ የኋላ ኋላም ቢሆን የአፄው<br />
ስርአት ለሰራተኛ ማህበራት<br />
እውቅና በመስጠት ኢሰአማ<br />
(የኢትዮጵያ ሰራተኞች አንድነት<br />
ማህበር) እንዲመሰረት ቢያደርግም፤<br />
የኢሰአማን የበላይ አመራር<br />
የኃይለስላሴ መንግስትና የአሜሪካ<br />
መንግስት (በሲ.አይ.ኤ) አማካኝነት<br />
በቁጥጥራቸው ስር አድርገውት<br />
ነበር፡፡<br />
እናም የልባቸው ያልሞላው የበታች<br />
ሰራተኞች እና ማህበራት የመጀመሪያ<br />
ትግላቸው እነዚህ የአገዛዙ ቀኝ<br />
እጅ የነበሩትን አመራሮች (በየነ<br />
ሰለሞን- ፕሬዝዳንት፣ አለም አብዲ-<br />
ም/ክ ፕሬዝዳንት እና ፍስሀፂዮን-<br />
ፀሀፊ) ማስወገድና በእውነተኛ<br />
የሰራተኛው መሪዎች መተካት ነበር፡<br />
፡ በተጨማሪም የስራው ሁኔታ እና<br />
የመነሻ ደሞዝ እንዲሻሻል የሚሉ<br />
ጥያቄዎችን አንግበው ይታገሉ<br />
ነበር፡፡ በስተመጨረሻም የሰራተኛው<br />
መሪዎች በወቅቱ ከኃይለስላሴ አገዛዝ<br />
ጋር የሞት የሽረት ትንቅንቅ ውስጥ<br />
ከነበሩት ተማሪዎች ጋር ግንኑነትን<br />
ፈጥረው ለስርአቱ ፈታኝ ሆነው<br />
እንደነበር ታሪክ ያስረዳል፡፡<br />
በወቅቱ የሰራተኞች ቁጥር<br />
እንደዛሬው የትየለሌ አይሁን እንጂ<br />
ጥቂቶችም ቢሆኑ ለመብታቸው<br />
እና ለአላማቸው ቆራጦች ነበሩ፡<br />
፡ አብዮቱ በፈነዳበት በ1966 ዓ.ም<br />
አካባቢ በኢሰአማ ስር ተመዝግበው<br />
ይገኙ የነበሩ ሰራተኞች ቁጥር ወደ<br />
100 ሺህ ይደርስ ነበር፡፡ አፈናው<br />
እና ጭቆናው ሊያስቀረው ያልቻለው<br />
አብዮት እንዲነሳ የሰራተኛ ማህበሩ<br />
ያደረገው አስተዋፅኦም በቀላሉ<br />
የሚገመት አይደለም፡፡<br />
በ”ጊዜያዊ” ወታደራዊ መንግስት<br />
ደርግ ዘመን<br />
ከኃይለስላሴ መውረድ እና<br />
“ጊዜያዊ” ወታደራዊው መንግስት<br />
ወደ ስልጣን መምጣት በኋላም<br />
ቢሆን የሰራተኛውን መብት<br />
ለማስከበር ከሚደረጉ ትግሎች<br />
በተጨማሪ በይፋ ጊዜያዊ ህዝባዊ<br />
መንግስት እንዲመሰረት የሚጠይቁ<br />
መግለጫዎችንና የዴሞክራሲያዊ<br />
መብቶች መከበርን የሚደግፉ<br />
መግለጫዎችን በማውጣት<br />
በኢትዮጵያ ፖለቲካ ታሪክ ውስጥ<br />
ጉልህ ሚና ተጫውቷል፡፡<br />
የሰራተኛ ማህበሩ የጊዜያዊ ህዝባዊ<br />
መንግስት ይመስረት ጥያቄን<br />
ማንሳት ያልተዋጠለት ደርግ<br />
እንደ ኃይለስላሴ ሁሉ የሰራተኛ<br />
መሪዎችን ማሰርንና መግደልን<br />
ስራዬ ብሎ ተያያዘው፡፡ በተለይም<br />
ኢሰአማ (የሰራተኛው ማህበር)<br />
ከመስከረም 8 እስከ 11 ባደረገው<br />
የሶስት ቀናት ጉባኤ መንግስት<br />
የሰራተኞች መሪዎችንና ሌሎች<br />
የፖለቲካ እስረኞችን እንዲፈታ፣<br />
በዴሞክራሲያዊ መብት ላይ<br />
የተጫነው ገደብ እንዲነሳ፣ ጊዜያዊ<br />
ህዝባዊ መንግስት እንዲመሰረት<br />
የሚጠይቅ መግለጫ ማውጣቱን<br />
ተከትሎ መስከረም 16 ቀን<br />
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኞች<br />
ማህበር አባላት የጉባኤውን ውሳኔ<br />
ለሰራተኞች በሚያድሉበት ጊዜ<br />
ወታደሮች በወሰዱባቸው የማጥቃት<br />
እርምጃ 8 ሰዎች መግደላቸው<br />
እና በ20ዎች ማቁሰላቸው የሚረሳ<br />
አይደለም፡፡ ደርግም “በኢትዮጵያ<br />
አየር መንገድ መስሪያ ቤት ውስጥ<br />
ፀረ አብዮት ፅሁፍ ሲበትን የነበረ ሰው<br />
እንዳያዝ በማወካቸው ወታደሮች<br />
ተኩስ ለመክፈት ተገደዱ” በማለት<br />
በይፋ ለማስተባበል ሞክሮ ነበር፡፡<br />
ማርቆስ ሀጎስ<br />
ማርቆስ የደርግ ሰለባ ከሆኑት<br />
የሰራተኛው ግንባር ቀደም መሪዎች<br />
አንዱ ነበር፡፡ ከኃይለስላሴ ዘመን<br />
ጀምሮ ለሰራተኛው መብት እና<br />
ለኢትዮጵያ ህዝብ መብት ሲታገል<br />
የቆየው ማርቆስ እሱ በሃላፊነት<br />
የሚመራው የሰራተኛ ማህበር<br />
ለደርጉ በስልጣን ላይ ተደላድሎ<br />
መቀመጥ አመቺ ሆኖ ስላልተገኘ<br />
ገና በጠዋቱ ነበር ለእስር የተዳረገው፡<br />
፡ በእስርም እያለ ከፍተኛ ስቃይ<br />
ከተቀበሉ የሰራተኛው መሪዎች<br />
አንዱ ነው፡፡ አንዳንዴም ከድብደባው<br />
የተነሳ ብዙ ደም ይፈሰው ስለነበር<br />
የወቅቱ የደህንነት ሹም ዳንኤል<br />
አስፋው ማርቆስን ወንበር<br />
እንዳታበላሽ መሬት ላይ ቁጭ በል<br />
ሲል ያዘው ነበር፡፡ አንዳንዴም ደም<br />
በደም ከሆነ በኋላ በእስረኞች መሀል<br />
እያዞሩት ይሄ ነው ንጉስ የሚሆነው<br />
እያሉ ያፌዙበት ነበር፡፡ በመጨረሻም<br />
ማርቆስ ሰማዕት ሆኖ ከመሞቱ<br />
በፊት እጅግ አስቀያሚ እንደሆነ<br />
ወደሚነገርለት ወደ ማይጨው ጦር<br />
ሰፈር እስር ቤት ተዘዋውሮ ነበር፡፡<br />
የሰራተኛው መሪዎችን በማሰርና<br />
በመግደል ያልተመለሰው ደርግ<br />
የሰራተኛው ማህበርን በነፃነት<br />
እንዳይንቀሳቀስ ስላደረገው<br />
ሰራተኛው በግልፅ መደራጀቱን<br />
በመተው በህዕቡ የላባደር ማህበርን<br />
(ኢላማ) በመመስረት ለሰራተኛው<br />
መብት መከበር የሚደረገውን ትግል<br />
አጧጧፈው፡፡<br />
ዳሮ ነጋሽ<br />
ዳሮ ነጋሽ የደርጉን አፈና ለመቋቋም<br />
ሲባል በህቡዕ የተደራጀው<br />
የኢትዮጵያ ላብአደሮች ማህበር<br />
መሪዎች መካከል አንዷ ነበረች፡፡<br />
የብርሀንና ሰላም ማተሚያ መስሪያ<br />
ቤት ሰራተኛ የነበረችው ዳሮ ነጋሽ<br />
የ5 ልጆች እናት የነበረች ቢሆንም<br />
ለሰራተኛው መብት መከበር<br />
ከመታገል ግን ወደ ኋላ ሊያስቀራት<br />
አልቻለም ነበር፡፡ ቤቷን ሳይቀር<br />
ለህቡዕ ስብሰባዎች ማካሄጃነት ክፍት<br />
ያደረገችው ዳሮ ቆራጥ እና በአላማዋ<br />
ፅኑ ሴት ነበረች፡፡ የዜጎች መደራጀት<br />
ያስበረግገው የነበረው ደርግም የ 9<br />
ወር እርጉዝ እና የ 5 ልጆች እናት<br />
የነበረችውን ዳሮ ነጋሽን ያለ ምንም<br />
ርህራሄ በጥይት ደብድቦ ገደላት፡፡<br />
ዳሮ ነጋሽ ለሰራተኛው እና ለሰፊው<br />
ህዝብ መብት ሰማዕት የሆነች ጀግና<br />
ነበረች፡፡<br />
ደርግ እንዲህ ያሉ አሰቃቂ<br />
እርምጃዎችን በማህበራቱ እና<br />
በማህበራቱ መሪዎች ላይ ይውሰድ<br />
እንጂ ሰራተኛው ለመብቱ<br />
የሚያደርገውን ትግል ሊያስቆመው<br />
አልቻለም፡፡<br />
በተለያዩ ወቅቶች የስራ ማቆም<br />
አድማ፣ የስራ ማለዘብ (ማቀዝቀዝ)፣<br />
የማሺን መስበር ወዘተ ያሉ<br />
የትግል ስልቶችን በመጠቀም<br />
ሰራተኞች መብታቸውን ለማስከበር<br />
እስከመጨረሻው ታግለዋል፡፡<br />
በህወሓት/ኢህአዴግ ዘመን<br />
በዘመነ ደርግ ለመብታቸው መከበር<br />
ከፍተኛ ተጋድሎ ያደርጉ የነበሩት<br />
ማህበራት በዘመነ ህወሓት/ኢህአዴግ<br />
ዘመንም ቢሆን የትግላቸውን ፍሬ፤<br />
የመብታቸውን መከበር ሊጎናፀፉ<br />
አልቻሉም፡፡ እስርና ስደትና ግድያው<br />
አሁንም ቀጠለ፡፡<br />
ዳዊ ኢብራሂም (የሰራተኛ ማህበር<br />
ፕሬዝዳንት የነበረ)<br />
ህወሓት/ኢህአዴግ ስልጣን<br />
እንደያዘ እንዳለፉት ስርአቶች<br />
ሁሉ የሰራተኛ ማህበሩን በራሱ<br />
ቁጥጥር ስር ለማድረግ ቢፈልግም<br />
በወቅቱ የሰራተኛ ማህበሩ መሪዎች<br />
የነበሩት በተለይም ፕሬዝዳንቱ ዳዊ<br />
ኢብራሂም የሚቀመሱ አልሆኑም፡<br />
፡ ስለዚህም አመራሮቹን ከማሰር<br />
እና ከማስፈራራት አልፎ የተለያዩ<br />
አሻጥሮችን መስራቱ የቅርብ ጊዜ<br />
ትውስታ ነው፡፡ በመጨረሻም ጫናው<br />
የበዛባቸው የማህበሩ ፕሬዝዳንት<br />
ዳዊ ኢብራሂም በሞያሌ በኬንያ<br />
አድርገው ሊሰደዱ በቅተዋል፡፡<br />
አሰፋ ማሩ (የመምህራን ማህበር<br />
ፕሬዝዳንት የነበረ)<br />
ህወሓት/ኢህአዴግ ያመጣውን<br />
የትምህርት ፖሊሲ በግልፅ<br />
የተቃወመው የመምህራን ማህበርም<br />
የደረሰው እጣ ፋንታ ያለፉት<br />
ስርአቶች ያደርጉ ከነበረው የተለየ<br />
አይደለም፡፡ የመምህራን ማህበር<br />
ነፃነት ለድርድር እንደማይቀርብ<br />
ግልፅ ያደረገው አመራርም<br />
የተወገደበት መንገድ አነጋጋሪና<br />
ጊዜ የሚፈታው ጉዳይ ነው፡፡<br />
የመምህራን ማህበሩ ፕሬዝዳንት<br />
የነበረው አሰፋ ማሩ ከቤቱ ወጥቶ<br />
በእግሩ በሚጓዝበት ወቅት በቀን<br />
በአደባባይ በጥይት ተገድሏል፡፡<br />
አሁንስ? ኢሰማኮ?<br />
አሁን ያለው የሰራተኛ ማህበር<br />
ለሰራተኛው መብት መከበር<br />
የሚታገል ነፃ ማህበር ነው<br />
ወይስ የህወሓት/ኢህአዴግን<br />
ፖሊሲ እንደወረደ የሚያስፈፅም<br />
የስርአቱ ቀኝ እጅ? በኃይለስላሴ<br />
ዘመን የሰራተኛ ማህበሩ የመነሻ<br />
ደሞዝ ይስተካከል ሲል ያቀረበው<br />
ጥያቄ ዛሬስ ቢሆን ተሻሽሏል???<br />
በመንግስት መስሪያ ቤት ውስጥ<br />
በዲግሪ ተመርቆ የሚቀጠር ሰራተኛ<br />
የመነሻ ደሞዙ 1499 ብር ብቻ<br />
ነው፡፡ በ800 ብሩ ቤት ተከራየ<br />
ብንል...ለትራንስፖርት 300 ብር<br />
አወጣ ብንል በቀረችው ብር ወሩን<br />
የሚዘልቀው እንዴት ነው? ምንስ<br />
እየተመገበ ነው የሚዘልቀው? ይህ<br />
ሰው ቤተሰብ ያለው ከሆነ ደግሞ<br />
የልጆች ቀለብ የልጆች ት/ቤት<br />
ወዘተ ይጠብቀዋል፡፡ ይህ የመነሻ<br />
ደሞዝ ለአመታት ሳይጨምር<br />
ሲቆይ የሰራተኛ ማህበሩ አንዳችም<br />
ተቃውሞ አሰምቶ አያውቅም!<br />
በዚህም ማህበሩ የስርአቱ ቀኝ<br />
እጅ እንጂ ሰራተኛውን የሚወክል<br />
እንዳልሆነ ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፡፡<br />
ምን ይደረግ?<br />
ሰራተኛው አሁን ያለው ማህበር<br />
እንደማይወክለው ካወቀና<br />
አይወክለኝም ብሎ ካለ ህጉ<br />
በሚፈቅድለት መሰረት ሌላ የሰራተኛ<br />
ማህበር ማቋቋም ይችላል፡፡ ህጉ<br />
በአንድ መስሪያ ቤት ውስጥ ከአንድ<br />
በላይ የሆኑ ማህበሮችን ማቋቋም<br />
እንደሚቻል በግልፅ ቢያስቀምጥም<br />
በአንድ በኩል ከፍርሀት በሌላ<br />
በኩል ደግሞ ካለው አፈና እና ጫና<br />
የተነሳ በአንድ መስሪያ ቤት ውስጥ<br />
ከተለመደው ማህበር ውጪ ሌላ<br />
ማህበር ለማቋቋም ጥረት ሲደረግ<br />
አይታይም፡፡ ሰራተኛው በተናጠል<br />
የሚደረግ መብትን የማስከበር<br />
ስራ የትም እንደማያደርስ አውቆ<br />
ባመቸው መንገድ ሊደራጅ ይገባል፡፡<br />
በግልፅ ተደራጅቼ መብቴን<br />
ለማስከበር ያለው ሁኔታ አመቺ ነው<br />
ብሎ ካመነ በግልፅ ሊደራጅ አሊያም<br />
በግልፅ ለመደራጀት የሚያስችል<br />
ነፃና አመቺ ሁኔታ የለም ካለ ደግሞ<br />
ልክ ነው ባለው መንገድ ተደራጅቶ<br />
መብቱን ማስከበር የሰራተኛው<br />
ሀላፊነት ነው፡፡ ሁሉም በቤቱ<br />
ተቀምጦ ቢያጉረመርም በአንድ<br />
ላይ ተደራጅቶ እስካልተነሳ ድረስ<br />
የሚያመጣው ለውጥ አይኖርም!<br />
ሰራተኛው ተደራጅቶ ምን ያድርግ፣<br />
የተባለ እንደሆነ መብቱን ለማስከበር<br />
ሲል የስራ ማቆም አድማ! ያ<br />
ያልተሳካ እንደሆነ እንኳን የስራ<br />
ማለዘብ (ማቀዝቀዝ) ወዘተ ያሉ<br />
የትግል ስልቶችን በመጠቀም ቆራጥ<br />
እርምጃን መውሰድ ይኖርበታል፡፡<br />
የዘመናችን ማርቆስ ሀጎስ ሆይ ተነሳ!<br />
የዘመናችን ዳሮ ነጋሽ ሆይ ተነሺ!!!<br />
ሁልጊዜም ቢሆን ትግል ከፊት ሆነው<br />
የሚመሩ ቆራጦችን ይጠይቃል!<br />
ዛሬም ከልጆቿ በፊት የሰራተኛውን<br />
እና የሰፊውን ህዝብ መብት መከበር<br />
ቅድሚያ የምትሰጥ ጀግና ደፋር<br />
ዳሮ ነጋሽ ታስፈልገናለች፡፡ ዛሬም<br />
ለሰራተኛው መብት መከበር እና<br />
ለሰፊው ህዝብ ጥቅም ሲል ህይወቱን<br />
ሊሰጥ የቆረጠ ጀግና ደፋር ማርቆስ<br />
ሀጎስ ያስፈልገናል፡፡ አንቺ/አንተ<br />
እንዳትሆኚ/ን ምን ይከለክልሻል/<br />
ሃል?
13የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2<br />
ነገረ-ኢትዮጵያ<br />
መመረጥ በሌላው ድክመት<br />
ሳይሆን በራስ ጥንካሬ<br />
ታምራት ታረቀኝ<br />
ፓርቲ የሚመሰረተው ለሀገር ይበጃሉ<br />
ተብሎ የታመነባቸው ፖለቲካዊ፣<br />
ኢኮኖሚዊና ማህበራዊ ዓላማዎች<br />
ተቀርጸውና እቅድ ተዘጋጅቶ<br />
የአፈጻጸም ስልትም ተነደፎ ነው፡፡<br />
አንድ ፓርቲ የሚኖሩት ሁለት ዋንኛ<br />
ሰነዶች ፕሮግራምና መተዳደሪያ<br />
ደንብም የሚያሳዩት ይህንኑ<br />
ነው፡፡ ፕሮግራሙ ዓላማውን<br />
መተዳደሪያ ደንቡ የአሰራር ሥልቱን<br />
ያመለክታሉ፡፡ ፓርቲው በፕሮግራሙ<br />
የሰፈረውን ዓላማውን ገቢራዊ<br />
ማድረግ የሚችለው የመንግሥትነት<br />
ሥልጣን ሲያገኝ ነው፡፡ ስለዚህም<br />
ነው የፖለቲካ ፓርቲ ዋንኛ ትግል<br />
የሥልጣን ጥያቄ የሚሆነው፡፡<br />
ለዓላማው ከግብ መድረስ<br />
የሚታገልበትን መንገድ ሠላማዊ<br />
ያደረገ ፓርቲ የሥልጣን ጥያቄውን<br />
ለማሳካት የሚጠቀምበት አንድና<br />
ብቸኛ መንገድ ደግሞ ምርጫ ነው፡<br />
፡ ነጻ ትክክለኛና ወቅታዊ ምርጫ፡<br />
፡ ይህ ዓይነቱ ምርጫ እውን<br />
ሊሆን የሚችለውም ዴሞክራሲያዊ<br />
ሥርዓት በአስተማማኝ መገንባት<br />
ሲቻል፣ አልያም በሥልጣን<br />
ላይ ያለው መንግስት አጠቃላይ<br />
ሁኔታዎችን ተገንዝቦ ራሱን<br />
በመለወጥ ወይንም በውስጥና<br />
በውጪ ተጽእኖ ተንበርክኮ ዓለም<br />
አቀፍ መስፈርቶችን የሚያሟላ<br />
ምርጫ ለማካሄድና ውጤቱንም<br />
በጸጋ ለመቀበል ሲዘጋጅ ነው፡፡<br />
ስለሆነም አንድ ፓርቲ ዓላማውን<br />
ተፈጻሚ ለማድረግ የሚያስፈልገውን<br />
ሥልጣን በትክክልና በአስተማማኝ<br />
ሁኔታ ለመጨበጥ በሀገሪቱ<br />
አስተማማኝ የዴሞክራሲያዊ<br />
ሥርዓት መሰረት እንዲጣል ይህ<br />
ካልሆነም ነጻና ፍትሀዊ ምርጫ<br />
ለማካሄድ የሚያሰችሉ ሁኔታዎች<br />
እንዲሟሉ መታገል ቀዳሚ ተግባሩ<br />
ይሆናል፡፡<br />
በምርጫው ማግሥት ውጤቱ<br />
በአሳዛኝ ሁኔታ ቢበላሽም ቅንጅት<br />
ከዚህ አንጻር በየታሪክ ወቅቶች<br />
የሚነሳ ተግባር አከናውኗል፡፡<br />
ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት አልነበረም፣<br />
ምርጫ ቦርድ አልተለወጠም፣<br />
የፖለቲካ ምህዳሩ ጠቧልና<br />
ከኢህአዴግ ጋር ካላተደራደርን ብሎ<br />
ልመናም ሆነ ምልጃ አላቀረበም፡፡<br />
በአጭር ግዜ እንቅስቃሴ መታመንን<br />
አተረፈና የሠላማዊ ትግሉ ዋንኛ<br />
ኃይል የሆነውን ሕዝብ በአንድ<br />
መንፈስ በቁርጠኝነት ለማሰለፍ<br />
ቻለ፣ እናም ያንን በዚህ ትውልድ<br />
ድጋሜ ስለመታየቱ ማንም ርግጠኛ<br />
ሆኖ ሊናገር የማይችለውን ዓለምን<br />
«….ኢህአዴግ መስተጋብሩን<br />
ጠብቆ በማያቋርጥ ሁኔታ እያሸነፈ<br />
መቀጠል ያለበት ድርጅት ነው፤<br />
መስተጋብሩን ጠብቆ በማያቋርጥ<br />
ሁኔታ የህዝቡን ልብ ይዞ፣ የህዝብ<br />
ልብ የሚያዘው በማያቋርጥ የልማት<br />
እንቅስቃሴ፣ በማያቋርጥ የህዝቡን<br />
ፍላጎት የማርካት እንቅስቃሴ፣<br />
በማያቋረጥ መልካም አስተዳደርን<br />
የመገንባት እንቅስቃሴዎች ነው፣<br />
ከዚህ ውጪ የሚመጣ አይደለም፣<br />
በታሪክ ማሸነፍ አይቻልም፣ ማሸነፍ<br />
የሚቻለው በተጨባጭ ተግባር ብቻ<br />
ነው፣ ምርጫን በታሪክ ማሸነፍ<br />
አይቻልም…» በማለት የተናገሩት<br />
የኢህአዴግ የእለት ተእለት<br />
እንቅስቃሴ ምርጫን መሰረት ያደረገ<br />
መሆኑን ያሳያል፡፡<br />
በአንጻሩ አብዛኛዎቹ ተቀዋሚዎች<br />
ለመመረጥ ኢህአዴግ ሕዛባዊ<br />
ተቀባይነት ስለሌለው ነጻ ምርጫ<br />
ከተካሄደ ሕዝቡ ተቀዋሚዎችን ነው<br />
የሚመርጠው በማለት የራሳቸውን<br />
ጥንካሬ ገንብተውና አስተማማኝ<br />
አማራጭ ሆነው በመቅረብ ሳይሆን<br />
በኢህአዴግ ድክመት እንመረጣለን<br />
ብለው የሚያስቡ በመሆናቸው<br />
ምርጫ የሚታሰባቸው ምርጫ ቦርድ<br />
የግዜ ሰሌዳ ሲያወጣ ነው፡፡ በዛች<br />
አጭር ግዜ በሚደረግ ዝግጅት ወደ<br />
ምርጫ መግባት ደግሞ ውጤት<br />
አያመጣም፡፡ የተሸነፍነው ምርጫው<br />
ተጭበርብሮ ነው ምርጫ ቦርድ<br />
ገለልተኛ ባለመሆኑ ነው በደል<br />
ተፈጽሞብን ነው ወዘተ የሚሉ<br />
ክሶችም ከባዶ ጩኸትነት ሊያልፉ<br />
አይችሉም፡፡ አንደ ፕ/ር መድሀኔ<br />
ታደሰ አባባል ምርጫ ሁለት<br />
ዓመትም ሲቀረው ይጨበረበራልና<br />
ስለ ምርጫ የሚሰራው የቀደመው<br />
ምርጫ በተካሄደ ማግስት ጀምሮ<br />
መሆን አለበት፡፡ ይህ ጉዳይ ሲነሳ<br />
ቅንጅት በስድስት ወር ግዜ አይደለም<br />
ወይ ለማሸነፍ የበቃው የሚል<br />
መከራከሪያ ለማቅረብ የሚዳዳቸው<br />
አሉ፡፡ ይህን የሚሉ ፖለቲከኞች፣<br />
1. ከላይ የጠቀስኳቸው አፈ<br />
ጉባኤ አባዱላ ገመዳ እንዳሉት<br />
ምርጫን በተጨባጭ ተግባር እንጂ<br />
በታሪክ ማሸነፍ ማይቻል መሆኑን፣<br />
2. ቅንጅትን ለአሸናፊነት<br />
ያበቁትን መንገዶች ሁሉ ኢህአዴግ<br />
ከምርጫው ማግስት ጀምሮ<br />
የዘጋቸው መሆኑን፣<br />
3. በቅንጅት ምስረታና<br />
በምርጫ 97 መካከል የነበረው<br />
ግዜ ስድስት ወራት ብቻ ቢሆኑም<br />
ቅንጅትን የመሰረቱት በተለይ<br />
መኢአድና ኢዴፓ በረዥም ግዜ ሰፊ<br />
የምርጫ ስራ የሰሩና በቂ ዝግጅት<br />
ያደረጉ መሆኑን የዘነጉ ናቸው፡፡<br />
በምርጫ ውጤታማ ተወዳዳሪ<br />
ለመሆን የሚያስብ ፓርቲ በቅድሚያ<br />
በራሱ ጥንካሬ ለመመረጥ አልሞ<br />
የእለት ተእለት እንቀስቃሴው<br />
በመራጩ ልብ ውስጥ የሚገባና<br />
መታመንን የሚያስገኝለት እንዲሆን<br />
መስራት አለበት፡፡ ስለሆነም<br />
ሀገራዊና ዓለም ዓቀፋዊ ተጨባጭ<br />
ሁኔታዎችን ከፕሮግራሙ ጋር<br />
በማገናዘብ የአጭርና የረዥም ጊዜ<br />
እቅድ አዘጋጅቶ ለአፈጻጸሙም<br />
ግልጽ የሆነ የአሰራር ስልት ነድፎ<br />
የሚታይና የሚታመን እንቅሰቃሴ<br />
ማድረግ ይኖርበታል፡፡ በቢሮ<br />
ከትሞ፣ ከመግለጫ የዘለለ ተግባር<br />
ሳያሳዩ ከርሞ ሰዉ በኢህአዴግ<br />
አገዛዝ ተሰላችቷል ለውጥ ይፈልጋል<br />
በመሆኑም ተቀዋሚዎችን<br />
ይመርጣል በሚል እሳቤ ብቻ<br />
በምርጫ ሰሞን ብቅ በማለት ወንዝ<br />
በሌለበት ድልድይ አሰራለሁ አይነት<br />
ቅስቀሳ ማካሄድና ከእኔ በላይ ለሀገር<br />
አሳቢ ለህዝብ ሰሪ አይርኖም የሚል<br />
ፕሮፓጋንዳም እንበለው የምርጫ<br />
ቅሰቀሳ ማካሄድ ባዶ ጩኸት ነው<br />
የሚሆነው፡፡<br />
በየደረጃው የሚገኙት የፓርቲው<br />
መሪዎችና አባላት ማንነትና<br />
የተግባር እንዴትነት ብሎም<br />
በዕጩነት የሚያቀርባቸው<br />
ተወዳዳሪዎች ማንነት በምርጫው<br />
ውጤት ለማምጣት ወሳኝ ናቸው፡<br />
፡ እስከ መስዋዕትነት በሚጠይቀው<br />
ሠላማዊ ትግል ውስጥ የትወልድ<br />
ድርሻቸውን ሊያበረክቱ በበጎ<br />
ፈቃደኝነት የተሰለፉ አባላቱ የጠበቀ<br />
የዓላማ ትስሰርና የመንፈስ አንድነት<br />
አንዲሁም መተማመን ሲኖራቸው፣<br />
በመኖሪያ አካባቢያቸውም ሆነ<br />
በሥራ ቦታቸው በሥነ ምግባራቸው<br />
የተከበሩ በስራቸውም የተወደዱ<br />
ሲሆኑ የመራጩን ሕዝብ ቀልብ<br />
በመሳብ ፓርውን ለውጤት<br />
ያበቁታል፡፡ ይህ ሳይሆን ተቀዋሚ<br />
በመሆን ብቻ እንመረጣለን ብሎ<br />
ማሰብ ምርቻን በታሪክ ማሸነፍ<br />
እንደማይቻል ያለመገንዘብ ነውና<br />
ምርጫ 2007 እንደ ምርጫ 2007<br />
እንዳይሆን ያሰጋል፡፡<br />
ፓርቲዎች በየግል ተጠናክረው<br />
በጋራ ተማምነው በስፋት መክረውን<br />
በረዥሙ አቅደው ሳይሆን ተባብረን<br />
ከታየን ሕዝቡ ይመርጠናል በሚል<br />
ብቻ በምርጫ ሰሞን የሚካሄድ<br />
የመተባበር ሆይ ሆይታም ጥንካሬ<br />
ፈጥሮ አስተማማኝ አማራጭ<br />
ሆኖ ከመቅረብ የሚነሳ ባለመሆኑ<br />
ለውጤት አያበቃም፡፡ እንደምንም<br />
ተደጋግፈን ከፊት ለፊታችን ያለውን<br />
ግዙፍ ተራራ መናድ የሚለው<br />
የኋላ መሰረት የዛሬ ጥንካሬ የፊት<br />
ራዕይ የሌለው ሥልጣንን ብቻ<br />
አስቦ የሚነሳ መደጋገፍ ፈጥረው<br />
ለምርጫ ቢቀርቡም የሚፈጥሩት<br />
መጎነታተል(በቅንጅትም<br />
በመድረክም የታየ ነው) ደካማ<br />
አቅማቸውን ይበልጥ ያዳክመውና<br />
ለኢህአዴግ አሸናፊነት ምቹ ሁኔታ<br />
ይፈጥሩለታል፡፡<br />
ዛሬ ትናንት አይደለም ነገሮች ተለዋውጠዋል፣ ጠንክሮ በመገኘት<br />
እንጂ በሌላው ድክመት ለመመረጥ ማለም ግዜ አልፎበታል፡<br />
፡ ኢህአዴግን ደካማ አድርጎ ማሰብም በራሱ ትልቅ ድክመት<br />
ይመስለኛል፡፡ በደቂቃ ውስጥ መረጃ ለሚሊዮኖች በሚደርስበት<br />
ዘመን በተግባር ሆኖ ሳይሆን በፕሮፓጋንዳ መስሎ በመቅረብ<br />
ለውጤት መብቃት የሚቻል አይደለም፡፡<br />
በየግላቸው ድርጅታዊ ብቃት<br />
ሳይፈጥሩ በጋራም በቅጡ<br />
መክረው የጋራ እቅድ ሳይነድፉና<br />
ሆነው ሳይሆን መስለው ለምርጫ<br />
በመቅረብ በጥረታቸው ሳይሆን<br />
በሕዝቡ ለውጥ ፈላጊነትና ታሪክ<br />
ሰሪነት ለአሸናፊነት ቢበቁ ውጤቱን<br />
አሰጠብቀው በስምምነት የሥልጣን<br />
ክፍፍል አድርገው በምርጫ ያገኙትን<br />
ውጤት ወደ ተግባር በመለወጥ<br />
ሕዝቡ በድምጹ የሰጣቸውን ኃላፊነት<br />
መወጣት መቻላቸው ያጠራጥራል፡<br />
፡ ምክንያቱም ወደ ምርጫ የገቡት<br />
ጥንካሬ ፈጥረው የህዝብን አመኔታ<br />
አትርፈው ሳይሆን በመተባበር ሽፋን<br />
በመሆኑ ነው፡፡<br />
አንድነቱ የጠነከረ፣ በሚያራምደው<br />
ዓላማ በእኩል ደረጃ እምነት<br />
ያለው፣ በፓርቲ ዲስፕሊንና በንጹህ<br />
ሰብአዊ ፍቅር የተሳሰረ፣ እሰከ<br />
መስዋእትነት አብሮ ለመዝለቅ<br />
የተማመነ ከአባለቱም ሆነ ከመራጩ<br />
ሕዝብ አመኔታን ያተረፈ አመራር<br />
እንዲሁም በዓላማው የጸና ሞራሉ<br />
የተገነባና በመንፈስ የጠነከረ አባል<br />
መኖር ለአንድ ፓርቲ ዓላማ<br />
መሳካትም ሆነ ተባብሮ በምርጫ<br />
ለመሰለፍ በእጅጉ ወሳኝ ናቸው፡<br />
፡ ይህ በምርጫ ለማሸነፍ ወሳኝ<br />
የሆነ የፓርቲ ጥንካሬ ማሳያ በአንድ<br />
ሰሞን የሚገነባ አለመሆኑ ምርጫን<br />
የረዥም ግዜ ስራ ከሚያደርጉት<br />
ምክንያቶች አንዱ ይሆናል፡፡<br />
በተለይ የፓርቲው አመራር በአደባባይ<br />
ስለ ፍቅር እየሰበከ በፓርቲው<br />
ውስጥ ጥላቻን የሚያነግስ ከሆነ፣<br />
ስለ አንድነት እያዜመ ተለያይቶ<br />
የሚቆም ከሆነ፣ ሥልጣን ላይ ካለው<br />
ፓርቲ ጋር መነጋገር እሻለሁ እያለ<br />
በሀሳብ ከሚለዩ የአመራር አባላትም<br />
ሆነ ጥያቄ ከሚያነሱ አባላት ጋር<br />
ለመነጋገር የማይደፍር ከሆነ፣<br />
ዘመናት ላስቆጠረው የሀገራችን<br />
ችግር ዋናው መፍትሄ ብሔራዊ<br />
እርቅ ነው ብሎ በፕሮግራሙ አስፍሮ<br />
ይህንኑ በአደባባይ እየተናገረና<br />
ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር<br />
የሚያስችል ጉባኤ አሰፈላጊነትን<br />
እየጠየቀ፣ በፓርቲው ውስጥ<br />
የሚፈጠሩ ጥቃቅን ልዩነቶችን<br />
በውይይት መፍታትና በእርቅ<br />
ማድረቅ የማይችል ከሆነ ወ.ዘ.ተ<br />
እንኳን በመራጩ ሕዝብ ዘንድ<br />
በአባላቱም መታመንና መከበርን<br />
ሊያተርፍ አይችልም፡፡ አመራሩ<br />
ካልታመነ ደግሞ ፓርቲው ሊታመን<br />
አይችልም፡፡ የማይታመን ደግሞ<br />
አይመረጥም፡፡<br />
ዛሬ ትናንት አይደለም ነገሮች<br />
ተለዋውጠዋል፣ ጠንክሮ በመገኘት<br />
እንጂ በሌላው ድክመት ለመመረጥ<br />
ማለም ግዜ አልፎበታል፡፡<br />
ኢህአዴግን ደካማ አድርጎ ማሰብም<br />
በራሱ ትልቅ ድክመት ይመስለኛል፡<br />
፡ በደቂቃ ውስጥ መረጃ ለሚሊዮኖች<br />
በሚደርስበት ዘመን በተግባር ሆኖ<br />
ሳይሆን በፕሮፓጋንዳ መስሎ<br />
በመቅረብ ለውጤት መብቃት<br />
የሚቻል አይደለም፡፡<br />
ፖለቲከኞቹ ከደረሰባቸውም<br />
ካደረሱትም መማር ባይችሉም<br />
ሕዝቡ ከሁሉም አቅጣጫ ከደረሰበትና<br />
ከሚደርስበት ችግር፣ በየጊዜውም<br />
ከሚያይና ከሚሰማው እንዲሁም<br />
21 ዓመታት ለውጥ ካላመጣውና<br />
መስዋዕትነቱ ግን ካልተቋረጠው<br />
ትግል ብዙ ተምሯል፡፡ ተፎካካሪ<br />
ፓርቲዎች ትግላቸው ለውጤት<br />
ባያበቃውም ዳፋቸው እያዳፋው ብዙ<br />
መከራ አይቷል፣ ስለሆነም ምንም<br />
ማድረግ ባይችል በሚታወቅበት<br />
ዝምታው ይሸኛል፡፡<br />
በመሆኑም ሕዝብን የሠላማዊ<br />
ትግሉ ተሳታፊ ብቻ ሳይሆን<br />
ባለቤት ለማድረግና በምርጫ 2007<br />
ለውጥ ለማምጣት ራስን አጥርቶና<br />
ወደ ገፅ 15 ይዞራል
ነገረ-ኢትዮጵያ<br />
ሰማያዊ<br />
ቅፅ 1 ቁጥር 2<br />
የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም.<br />
ይህ ገጽ በሰማያዊ ፓርቲ አዘጋጅነት የሚቀርብ ሲሆን፣ ፓርቲው ፕሮግራሙንና<br />
አላማውን ለአባላትና ደጋፊዎቹ የሚያደርስበት ነው፡፡<br />
14<br />
መንደርደሪያ<br />
ሰማያዊ ፓርቲ በዘር፣ በሃይማኖት በቋንቋ በፆታና በሌሎች<br />
ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መመዘኛዎች በዜጎች መካከል<br />
ልዩነት ሳያደርግ በማደራጀት የኢትዮጵያን ህዝቡ የሥልጣን<br />
ባለቤትነት ለማረጋገጥ ይታገላል፡፡<br />
ሰማያዊ ፓርቲ ለምን<br />
ተመሰረተ?<br />
ሀገራችን ኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ አኩሪ ታሪክ፣ ቀደምት<br />
የሥልጣኔ ባለቤትና ከ3000 ዘመን በላይ የመንግስትነት<br />
ታሪክ ያላት ታላቅ ሀገር ናት፡፡ የሰው ልጅ ዛሬ ለደረሰበት<br />
የዕድገትና የስልጣኔ ደረጃ መሰረት የሆኑ ቁሳዊና መንፈሳዊ<br />
ትውፊቶችን በማበርከት ለዓለም ስልጣኔ ታላቅ አስተዋፅዖ<br />
አበርክታለች፡፡ በየዘመናቱ ነፃነቷን ለማጥፋት የወረሯትን<br />
የውጭ ተስፋፊዎችና ቅኝ ገዥዎች በተደጋጋሚ ጊዜ ድል<br />
በማድረግ ነፃነቷንና ሉዓላዊነቷንም አስከብራ ኖራለች፡<br />
፡ ሀገራችንን በእብሪት ለመውረር የመጣውን የኢጣሊያን<br />
ወራሪ በመደምሰስ በዓለም ለመጀመሪ ጊዜ ጥቁር የሰው ልጅ<br />
ዘር ነጭ ወራሪዎችን ማሸነፍ እንደሚችል በአድዋ ታሪካዊ<br />
ድል ያስመሰከረች ብቸኛ የጥቁር ሰው ዘር መኩሪያና<br />
መመኪያ ሃገር ነች፡፡<br />
ቅኝ ገዥዎችና ኢምፔሪያሊስቶች አፍሪካን ለመቀራመትና<br />
የተፈጥሮ ሃብቷን ለመዝረፍ ያደረጉትን ስምምነት ተከትሎ<br />
አፍሪካን በቅኝ ግዛት ስር ለማዋል በተደረገው ወረራ<br />
ተስፋፊዎችን በመመከት በቅኝ ገዥዎች ሥር ያልወደቀችና<br />
ለመላዉ ጥቁር ሕዝብ የነፃነት ተምሳሌት ሐገር ነች፡፡<br />
አብዛኛዎቹ አፍሪካዊ ሀገሮች ድንበሮቻቸውና ማንነታቸው<br />
በቅኝ ገዥዎች ፍላጎት እንዲወሰን ሲደረግ ሀገራችን<br />
ወራሪዎችን በመቋቋም የራሷን የድንበር ወሰንና ማንነት<br />
በራሷ መወሰን የቻለች ብቸኛዋ አፍሪካዊ ሀገር ናት፡፡<br />
ሀገራችን የበርካታ ገፀ ምድርና ከርሰ ምድር ኃብት፣ አስደናቂ<br />
የተፈጥሮ ውበትና የሰው ልጅ ቀደምት ስልጣኔ መገለጫ<br />
የሆኑ ቅርሶች ባለቤት፣ ሰፊ መሬትና የሰው ኃይል ያሏት<br />
ታላቅ ሐገር ናት፡፡ ሀገራችን የተለያዩ የአየር ፀባያት ባለቤት<br />
ስትሆን ለሰው ልጅ መኖሪያና ለአዝርዕት መብቀያ ተስማሚ<br />
ተፈጥሮ በሰፊው የተለገሳት ሀገር ናት፡፡ በርካታ በጥቅም<br />
ላይ የዋሉና ገና ያልተነኩ የተፈጥሮ ስጦታየፈሰሰባትም<br />
ምድር ናት፡፡<br />
ሆኖም የዚህ አኩሪ ታሪክ፤ ባህልና የተፈጥሮ ሃብት<br />
ባለቤት የሆነች ሃገራችን ዛሬ በቀሪው የዓለም ሕዝብ ፊት<br />
የምትታወቀው በርሃብተኝነት፣ በተመፅዋችነት፣ በስደትና<br />
በእርስ በእርስ ጦርነት ባለቤትነቷ ነው፡፡ የሰው ልጅ ዛሬ<br />
ከረደሰበት የአስተዳደርና የኢኮኖሚ እድገት ደረጃ እንዳንደርስ<br />
ያደረገን በሃገራችን ተንሰራፈተው በቆዩና አሁንም ባሉ<br />
የአስተዳደርና የፖለቲካ ሥርዓት ብልሹነቶች ምክንያት<br />
ነው ብለን እናምናለን፡፡ ዛሬ ኢትዮጵያ በፖለቲካ እድገት<br />
ብቻ ሳይሆን በኢኮኖሚና በማህበራዊ እድገትም የዓለም<br />
ሃገራት የመጨረሻዎቹ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ ሕዝቧ የዘር፣<br />
የሃይማኖት፣ የቋንቋና የባህል ልዩነቶችን ተቀብሎ ለበርካታ<br />
ዘምናት ተቻችሎ የኖረ ቢሆንም ዛሬ እርስ በእርስ በጥርጣሬ<br />
እንዲተያይና አንድነቱ እንዲላላ እየተደረገ ነው፡፡ ሃገራችን<br />
በተቀበለቻቸውና ባፀደቀቻቸው ዓለም አቀፍ ህጎች እንዲሁም<br />
በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት እውቅና ያገኙ ሰብአዊና<br />
ዲሞክራሲያዊ መብቶች የሚያከብራቸውና የሚጠብቃቸው<br />
ባለቤት አጥተዋል፡፡ የኢኮኖሚ መርሃችንም በጥናትና<br />
በአስተማማኝ መሠረት ላይ ያልተጣለ በመሆኑ ካለንበት<br />
የድሕነት አዘቅት ሊያወጣን አልቻለም፡፡ ፍትኃዊ የንብረት<br />
ስርጭትና የሥራ እድል ባለመኖሩ በኢትዮጵያውያን መካከል<br />
ያለው የኑሮ ደረጃ እጅግ እየተራራቀ መጥቷል፡፡ ዜጎችም<br />
የዜግነት እኩልነት ክብራችን ተነፍገን አብዛኛዎቻችን<br />
በሃገራችን ጉዳይ ባይተዋር ሆነናል፡፡<br />
ዛሬ የዚህ ትውልድ አካል የሆንን ዜጎች ይህንን የተዛባ<br />
አካሄድ የመቀየርና ሃገራችንን የተሻለች ሃገር የማድረግ<br />
ኃላፊነት አለብን ብለን እናምናለን፡፡ በመሆኑም የሰማያዊ<br />
ፓርቲያችን ራዕይ፣ ተልዕኮና ዓላማ ለሃገራችን ካለን ጥልቅ<br />
ፍቅር፣ለፍትሃዊ አስተዳደር መስፈን ካለን ፅኑዕ እምነትና<br />
ከሰው ልጅ ምክንታዊ አስተሳሰብ ይመነጫሉ፡፡ ፍትሕ<br />
እንዲሰፍን የምንፈልግ ሃገራችንንም በእውነት የምንወድ<br />
ከሆነና በሰው ልጅ ምክንያታዊ አስተሳሰብ የምንገዛ ከሆነ<br />
ችግሮቻችን በሰላማዊ መንገድ፣ በመነጋገር፣ በመደማመጥና<br />
በመግባባት ብሔራዊ እርቅና መከባበርን በመፍጠር የሚፈቱ<br />
ናቸው ብለን እናምናለን፡፡<br />
ፓርቲያችን በሃገሪቱ ህገ-መንግስት መሠረት በሰላማዊ<br />
መንገድ የፖለቲካ ትግል በማድረግ የኢትዮጵያ ሕዝብ<br />
ከውስብስብና ፈርጀ ብዙ ችግሮች ተላቆ እያንዳንዱ ዜጋ<br />
በነፃነት ሃሳቡን የመግለፅ፣ የመደራጀት፣ የፈለገውን<br />
የመደገፍና የመቃወም፣ በፈለገው ሙያና የሥራ መስክ<br />
የመሰማራት፣ ሃብት የማፍራትና የሃብቱ ባለቤት የመሆን<br />
እንዲሁም የግል ስብዕናውን የማሳደግ መብቱ የተረጋገጠ<br />
እንዲሆን እንታገላለን፡፡ ሐገራችን ከድህነትና ከጦርነት<br />
የተላቀቀች፣ ፍትሕና ሰላም የሰፈነባት እንድትሆን የፖለቲካ<br />
ሥልጣን በመያዝ የዜግነት ድርሻችንን ለመወጣትና<br />
ራዕያችንን እውን ለማድረግ ሰማያዊ ፓርቲያችንን<br />
መስርተናል፡፡<br />
ሰማያዊ ፓርቲ ራዕዩን እውን ለማድረግ፤<br />
ሀ. ፓርቲያችን የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መርሆችን<br />
ይከተላል፡፡<br />
ለ. በሰማያዊ ፓርቲ ፕሮግራም ውስጥ ለተካተቱ<br />
አንዳንድ ጉዳዮች ተፈፃሚነት የሕገ-መንግሥቱ አንዳንድ<br />
ድንጋጌዎችን ህገ-መንግስቱ ባስቀመጠው የህገ-መንግስት<br />
ማሻሻያ መርሆች መሰረት ማሻሻል አስፈላጊ መሆኑን ታሳቢ<br />
ተደርጓል፡፡<br />
መ. ዓላም ዛሬ ከደረሰችበት የሥልጣኔ ደረጃና ከሰው<br />
ልጅ ምክንያታዊ አስተሳሰብ በመነሳት ከሰላማዊ ትግል<br />
ውጭ በሃገራችን የተረጋጋ የፖለቲካ ሥርዓትን መገንባት<br />
አይቻልም ብለን እናምናለን፡፡ ስለዚህ ፓርቲያችን በሰላማዊ<br />
የትግል ስልት የፖለቲካ ሥልጣን ለመያዝ ይታገላል፡፡<br />
የፖርቲው ስያሜና ትርጓሜ፤<br />
የፓርቲው ስያሜ “ሰማያዊ ፓርቲ” በአህፅዕሮት “ሰማያዊ”<br />
በእንግሊዝኛው አጠራር “BLUE PARTY” ሲሆን<br />
ትርጓሜውም ሰማያዊ ቀለም የሰላም፣ የተስፋና የአንድነት<br />
መገለጫ በመሆኑና ፓርቲያቸንም ሰላም ተስፋና አንድነት<br />
በሃገራችን እንዲሰፍን ያለውን የፀና እምነት መግለፅ ነው፡፡<br />
የፓርቲው ዓርማ፡-<br />
ከመሃል በጠባብ ክብ የሚጀምርና ሌሎች እየሰፉ<br />
የሚሄዱ ክቦቹ ሲኖሩት በደማቅ ሰማያዊና ውሃ ሰማያዊ<br />
ቀለሞች በመፈራረቅ የሚቀባ በጨርቅ ወይም በሌላ ቁስ<br />
ላይ የሚያርፍ ምልክት ይሆናል፡፡ የዓርማው ቀለማት<br />
የፓርቲያችንን ስያሜና ትርጉም የሚያሳዩ ሲሆን ከትንሽ<br />
ጀምሮ እየሰፉ የሚሄዱት ክብ ምልክቶች ደግሞ ጥቂት<br />
ሆነን ጀምረን እየበዛን እንደምንሄድ ለማሳየት ነው፡፡<br />
የፓርቲው ሀገራዊ ዕይታ<br />
ሀ. ኢትዮጵያ ሀገራችን በኢትዮጵያ ህዝብ ሙሉ<br />
ገዥነት ስር የሚገኘውን መሬት፣ ውሃ፣ የአየር ክልል፣<br />
በከርሰ ምድርና በከርሰ ውኃ የሚገኘው ሃብት፣ በአየር<br />
ክልሉ ያለው የድምፅና የምስል ሞገድ ባለቤት ሉዓላዊ ሀገር<br />
ናት፡፡<br />
ለ. የኢትዮጵያ ያልተመለሱ የድንበርና የይገባኛል<br />
ጥያቄዎች መኖራቸው እንደተጠበቀ ሆኖ የኢትዮጵያ<br />
ሉዓላዊ የአስተዳደር ወሰን አሁን በኢትዮጵያ መንግስት ሥር<br />
የሚገኘውና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የተመዘገበዉ<br />
ክልል ነው፡፡<br />
ሐ. በኢትዮጵያ ውስጥና በውጭ ሃገራት የሚኖሩ<br />
ኢትዮጵያውያን በአንድነት የኢትዮጵያ ሕዝብ ናቸው፡፡<br />
መ. የኢትዮጵያ ሕዝብም በኢትዮጵያ ጉዳይ ባለሙሉ<br />
የሥልጣን ባለቤት ነው፡፡ ሃገሪቱን የማስተዳደር ሥልጣን<br />
ከሕዝብ ይመነጫል፡፡<br />
ሠ. የኢትዮጵያ አንድነትም ሆነ ሉዓላዊነት<br />
አይነጣጠሉም፤ለሌላም አይለቀቁም፡፡<br />
ረ. ኢትዮጵያውያን በግል ያላቸው የዜግነት መብትም<br />
ሆነ በወል የሚጋሩት የህግ፣ የፖለቲካ የማህበራዊና<br />
የባህል መብት የአንድነታቸው ዓይነተኛ መሰረት ነው፡፡<br />
ሰ. ኢትዮጵያ ሀገራችን የረጅም ጊዜ አኩሪ ታሪክ፣<br />
የበርካታ ገፀ-ምድርና ከርሰ-ምድር ሃብት ባለቤት፣ አስደናቂ<br />
የተፈጥሮ ውበትና የሰው ልጅ ቀደምት ሥልጣኔ መገለጫ<br />
የሆኑ ቅርሶች ያሏት ታላቅ ሃገር ናት፡፡<br />
ሸ. ሃገራችን ኢትዮጵያ በተለያዩ ባህል፣ ሃይማኖት፣<br />
ቋንቋ፣ ወግና ሥርዓት አሸብርቃ የኖረች፣ በብዙ ዓይነት<br />
ሃረጎች ተሳስረውና በታሪክ ተቆራኝተው የጋራ አመለካከትና<br />
ኢትዮጵያዊ ማንነትን በማዳበር ለዘመናት ተቻችለውና<br />
ተከባብረው በአንድነት የኖሩ ዜጎች ሃገር ናት፡፡ እነዚህ<br />
ዜጎች በየዘመናቱ የተለያዩ አስተዳደራዊ በደልና ጭቆና<br />
ደርሶባቸዋል፡፡ ዛሬም ቢሆን የዜጎች የአስተዳደርና<br />
የፍትህ ጥያቄ በአግባቡ አልተፈታም ወይም መብታቸው<br />
አልተከበረም፡፡ በመሆኑም ሁሉም ዜጎች የዜግነት<br />
መብታቸው እንዲከበርና በሃገር ጉዳይ ላይ ተገቢው ድርሻና<br />
ተሳትፎ እንዲኖራቸው አሁንም ፅኑዕ ትግል የሚያስፈልጋት<br />
ሃገር ናት፡፡<br />
ራዕይ<br />
የዜጎች ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ሙሉ በሙሉ<br />
የተከበሩባት፤ ለሕዝብ ፍላጎት መሟላት በኃላፊነትና<br />
በተጠያቂነት መንፈስ የሚሰራ መልካም አስተዳደርና የህግ<br />
የበላይነት የተረጋገጠባት፤ የኢኮኖሚና ማሕበራዊ ብልፅግና<br />
የሰፈነባት፤ ለዜጎቿ ሁሉ አለኝታና መኩሪያ የሆነች፤ለዓለም<br />
ሕዝብ መልካም ግንኙነት የበኩሏን አስተዋፅዖ የምታደርግ<br />
ኢትዮጵያን ማየት ነው፡፡<br />
ዓላማ<br />
ሀ. የዜጎች ዲሞክራሲያዊና ሰብዓዊ መብቶች<br />
እንዲከበሩና ተፈፃሚም ኢንዲሆኑ በጽናት መቆም፡፡<br />
ለ. ለዜጎች አስተማማኝ የማሕበራዊ ደህንነት<br />
ዋስትና አገልግሎት ማቅረብ፡፡<br />
ሐ. የፖለቲካ ፓርቲዎችና ግለሰቦች ነፃ፣ ፍትሃዊና<br />
ትክክለኛ በሆነ መንገድ ተወዳድረው የፖለቲካ ሥልጣን<br />
የሚይዙበት የምርጫ ሥርዓት መመስረት፡፡<br />
መ. ራዕዩን ተግባራዊ ለማድረግ በነፃና ፍትኃዊ<br />
ምርጫ በህዝብ ድምፅ የፖለቲካ ሥልጣንመያዝ<br />
ሠ. ሀቀኛ፣ ብቃትና ተጠያቂነት ባለው አመራር<br />
አማካኝነት ታታሪና የፈጠራ ችሎታ ያላቸው ዜጎች<br />
መፍጠር፡፡<br />
ረ. የሕብረተሰቡን የፖለቲካ ግንዛቤ በማሳደግ ዜጎች<br />
በሃገራቸው ጉዳይ በንቃት እንዲሳተፉ፣ ግዴታቸውንና<br />
ኃላፊነታቸውንም እንዲወጡ ማድረግ፡፡<br />
ሰ. የእያንዳንዱን ዜጋ ችሎታ በማሳደግ በሃገርና<br />
በዓለም ደረጃ ብቁ ተወዳዳሪ ለመሆን ያለውን ምኞት<br />
ማሳካት፡፡<br />
ሸ. ከሀገራቸው ውጭ ያሉ ኢትዮጵያውያን ሰብዓዊና<br />
ቁሳዊ አቅማቸውን ለሃገራቸው ልማት እንዲያውሉና<br />
ለሕዝብም ቁሳዊና መንፈሳዊ ሕይወት መሻሻል የበኩላቸውን<br />
አስተዋፅዖ ማበርከት የሚችሉበት የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና<br />
የማሕበራዊ ሥርዓት መመስረት፡፡<br />
ቀ. ዓለምን ለመረዳትም ሆነ የዓለም ሕብረተሰብ<br />
በአግባቡ እንዲረዳው ማድረግ የሚችልና በነፃነት የሚያስብ<br />
ሕብረተሰብ መመስረት፡፡<br />
በ. የኢትዮጵያ ወጣት ትውልድ በራሱና በወረሰው<br />
መልካም ነገር እንዲኮራና በሕይወቱ ውስጥ ተስፋ<br />
እንዲኖረውና ለከፍተኛ ግብ እንዲሰራ ማደፋፈር፡፡<br />
ተልዕኮ<br />
ተልዕኮአችን ዓላማችንን ማሳካት ሆኖ በተለይ በሀገራችን<br />
ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲሰፍንና የሕግ የበላይነት<br />
እንዲረጋገጥ ዋስትና የሚሰጥ ከሕዝብ፣ በሕዝብ፣ ለሕዝብ<br />
የቆመ መንግስት በሰላማዊ መንገድ መመስረት ነው፡፡<br />
ርዕዮተ ዓለም<br />
እጅግ ውድ የሆነው የሰው ልጅ ሃብት ነፃነቱ በመሆኑ<br />
ሰማያዊ ፓርቲ ለግለሰብ ነፃነት ቅድሚያ ይሰጣል፡፡ ዜጎች<br />
በቡድን ሊያከናዉኗቸው የሚፈልጓቸው እንደ ሃይማኖት፣<br />
ልማዶች፣ ቋንቋ፣ ማህበሮች እና የመሳሰሉት የጋራ<br />
መብቶች የግለሰብን በነፃነት የመወሰን መብት ሳይሸረሽሩ<br />
እንዲከበሩ የህግ ጥበቃ እንደሚያስፈልጋቸው ያምናል፡፡<br />
በመሆኑም ሰማያዊ ፓርቲ በለዘብተኛ ሊብራል ዲሞክራሲ<br />
መሰረታዊ መርሆች ይመራል፡፡<br />
ትኩረት<br />
ሰማያዊ ፓርቲ በኢትዮጵያ ውስጥ 51% ያህል ቁጥር<br />
ያላቸውን ሴቶች ወደ ፖለቲካው መድረክ እንዲመጡ<br />
ቅድሚያ በመስጠት ይሠራል፡፡ በተጨማሪም እድሜው ከ35<br />
ዓመት በታች የሆነውና 70% የሚሆነውን የኢትዮጵያን<br />
ህዝብ ቁጥር የያዘው ወጣቱ ትውልድ የኢትዮጵያን ፖለቲካ<br />
ወደፊት ለማራመድ ከፍተኛ አሰተዋፅኦ አለው ብሎ<br />
ፓርቲያችን ያምናል፡፡ ከፍተኛ ተኩረትም ለወጣቱ ትውልድ<br />
ይሰጣል፡፡ ይህንንም በተግባር ለማሣየት የፓርቲው<br />
አብዛኛው አማራሮች የዚህ ትውልድ አካል ናቸው ፡፡<br />
ዋና ዋና እንቅስቃሴዎች<br />
1. ሰማያዊ ፓርቲ በምርጫ ቦርድ የተነፈገውን<br />
የምስክር ወረቀት በህግና በትግሉ ከቦርዱ ወረቀት በፊት<br />
ራሱን ህጋዊ አካል አድርጓል<br />
2. ፓርቲው ራሱን ከህዝብና ከደጋፊዎቹ<br />
ለማስተዋወቅ በርካታ የውይይት መርሃ ግብሮችን አካሂዷል፡<br />
፡<br />
3. ለፓርቲው ድጋፍ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ያዘጋጀው<br />
የራት ግብዣ ፕሮግራም በመንግስት ካድሬዎች ጫና<br />
ተስተጓጉሏል፡፡<br />
4. “ውይይትና መነጋገርን እንለማመድ” በሚል<br />
ርዕስ “መክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ ታሪክ” በተሰኘው የፕ/ሮ<br />
መስፍን ወልደማርም መፅሀፍ ላይ ውይይት እንዲደረግ<br />
በብሔራዊ ቲአትር ባዘጋጀው ዝግጅት ከሁለት ሺህ በላይ<br />
ተገኝቶ እንዲወያይ እድል ፈጥሯል፡፡<br />
5. ለፋሽስቱ ግራዚኒ ሐውልትና የመታሰቢያ<br />
መናፈሻ ቦታ እንዲሰራለት መደረጉን በመቃወም ሰላማዊ<br />
ሰልፍ በማድረጉ አባላቱን አመራሮቹ ወደ አስር ቤት<br />
እንዲወረወሩ ተደርገዋል፡፡<br />
6. በሚናገሩት ቋንቋ መለየት ምክንያት በቤኔሻንጉል<br />
ለዘመናት ከኖሩበት የተፈናቀሉ ወገኖቻችንን እቦታቸው<br />
ድረስ በመሔድ ጎብኝቷል፤ አወያይቷል፡፡<br />
7. በሐገራችን የሰፈነውን አምባገነንት፣ የሰብዓዊና<br />
ዲሞክራሲያዊ መብት ጥሰት፣ የዜጎችን መፈናቀልና<br />
የመንግስትን በሐይማኖት ጣልቃ መግባት በመቃወም<br />
ለስምንት አመታት የተነፈገውን የሰላማዊ ሰልፍ መብት<br />
በመመለስ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ አድርጓል፡፡<br />
ለበለጠ መረጃ የፓርቲያችንን ድ-ገፅ www.Semayawiparty.org<br />
ይጎብኙ፡፡ ወይም Facebook BlueParty<strong>Ethiopia</strong><br />
ላይክ ፔጅ semayawiparty ይከታተሉ፡፡<br />
አድራሻ፡- ሰማያዊ ፓርቲ<br />
ቁጥር፡ C/A619<br />
ፖ.ሳ. ቁ 180298<br />
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ<br />
ስልክ +251116514240<br />
አቢሲኒያ ባንክ ተንቀሳቃሽ ሂሳብ
15የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2<br />
ነገረ-ኢትዮጵያ<br />
እንደሀገር መግባባት ...<br />
ከ ገፅ 11 የዞረ<br />
የጸጥታ ሀይሉ ከህዝብ ተነጥሎ የኢህአዴግ<br />
የግል ንብረት እስኪመስል ድረስ ተለያይቷል፡<br />
፡<br />
ሌላው ደግሞ የፍትህ ተቋማት የምንላቸው<br />
ድርጅቶቻችን ናቸው፡፡ አብዛኛውን ጊዜ<br />
በሀገራችን የታዩ የፍርድ ሂደቶች የተመሩት<br />
በነጻ የዳኝነት ሂደት ሳይሆን በአለቃዎቻቸው<br />
በጎ ፈቃድ መሆኑ ጸሐይ የሞቀው ሀቅ ነው፡<br />
፡ ይህን መከራከሪያችን የሚያጠናክርልን<br />
የ1997 የቅንጅት አመራሮችና አባላት ላይ<br />
የተበየነው የእስር ፍርድ ነው፡፡ ጠቅላይ<br />
ሚንስትር መለስ ዜናዊ በፓርላማ ቀርበው<br />
እስከሞት ፍርድ ሊያስቀጣ የሚችል ወንጀል<br />
አግኝተንባቸዋል ብለው ተናግረው ነበር፡<br />
፡ ይህንን ተከትሎ ፍርድ ቤት መመላለሱ<br />
የሰለቻት ዳኛ ብርቱካን ሚዴቅሳ እንዲህ ስትል<br />
ተናግራ ነበር፡፡ “ለምን ታመላልሱናላችሁ፤<br />
መለስ ዜናዊ የሞት ፍርድ ፈርዶብን አይደል<br />
እንዴ!? ወስዳችሁ ግደሉን እንጂ፡፡” በቅርብ<br />
እነ እስክንድር ነጋን ጨምሮ በአንዱዓለም<br />
አራጌ፣ በሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ<br />
ኮሚቴወች ላይ የተወሰደው የጥፋተኝነት<br />
ውሳኔም ከቀድሞው የተለየ አይደለም፡<br />
፡ በዚህም ምክንያት በሀገራችን የፍትህ<br />
ተቋማት ላይ መግባባት ሆድና ጀርባ ሆኗል፡፡<br />
ማሳያ ሰባት፡- ዘውግ ተኮር ፌደራሊዝም<br />
የህገ መንግስቱ አንቀጽ 39 እንዲህ ይላል፤<br />
‹‹የራስን እድል በራስ መወሰን እስከ<br />
መገንጠል››፡፡ በዚህ አንቀጽ መሰረት ክልሎች<br />
እራሳቸውን በራሳቸው ያስተዳድራሉ፤<br />
ከፈለጉም መገንጠል መብታቸው ነው፡<br />
፡ በግሌ ‹እስከ መገንጠል› ብሎ መብት<br />
ምን እንደሆነ ባይገባኝም የፌደራል ስርዓት<br />
መኖሩን ግን አጥብቄ እፈልገዋለሁ፡፡ ‹እስከ<br />
መገንጠል› የሚለው ሀረግ መግባቱ ግን<br />
ላለመግባባታችን አንዱ ማሳያ ነው፡፡<br />
ማሳያ ስምንት፡- ምርጫና የምርጫ ቦርድ<br />
ለአንድ ሀገር በዴሞክራሲ መበልጸግ<br />
የምርጫ ቦርድ ገለልተኛነት ወሳኝ ሚና<br />
አለው፡፡ የምርጫ ቦርድ ሃላፊነቱን በአግባቡ<br />
ከተወጣ አጭበርባሪዎችና ኮረጆ ገልባጮች<br />
ቦታ የላቸውም፡፡ ይህን አሰራር በሀገራችን<br />
ለማስፈን ጅምሩ እንኳን የለም ለማለት<br />
ያስደፍራል፡፡ የምርጫ ቦርድ አመራሮችም<br />
ሹመታቸው በቀጥታ ከመንግስት መሆኑ<br />
ለገዥው ተባባሪነታቸው መንገድ ከፋች ነው፡<br />
፡ ምርጫ ቦርድ የገዥውን ፓርቲ የሙቀት<br />
ልክ እየለካ የሚሰራ መሆኑ የታየ እውነት<br />
ነው፡፡ በዚህ የተባባሪነት አመሉ ገዥው<br />
ኮረጆ ሲገለብጥ ምርጫ ቦርድ የምርጫ<br />
ውጤት ተቀበሉ በሚል ተቃዋሚዎችን<br />
ያባብላል፤ ካልተሳካት ደግሞ ያስፈራራል፡፡<br />
ስለሆነም ምርጫ ቦርድ ሌላኛው እንደ ሀገር<br />
ያለመግባባታችን ምክንያት ሆኖ ሊጠቀስ<br />
ይችላል፡፡<br />
በአጠቃላይ ሀገሬ ኢትዮጵያ የዚህ ክፍለ<br />
ዘመን ዳግማዊ ባቢሎን እየሆነች ነው፡<br />
፡ ይህን በቋፍ ላይ ያለ አለመግባባት በጊዜ<br />
ካልፈታን እጣ ፋንታችን እንደ ባቢሎን ህንጻ<br />
መፈራረስ ከመሆን አያልፍም፡፡ አምላክ<br />
አያድርገው እላለሁ!<br />
እውነትና ህዝብ ያሸንፋል! ኢትዮጵያ<br />
ለዘላለም በክብር ትኑር!!!<br />
ኢህአዴግ ተሸንፏል...<br />
ከ ገፅ 16 የዞረ<br />
እንደተለመደው ወዲያውኑ ኢንተርኔትና<br />
ስልክ እንዲጠፋ ተደረገ፡፡<br />
አሁን ሰላማዊ ሰልፉ እየተቃረበ እንደመሆኑ<br />
የከተማውን አስተዳደር ይበልጡን ፈርቷል፡<br />
፡ ሰልፉ እንደማይቀር ከሰማያዊ ወጣቶች<br />
ድፍረትና ቆራጥነት ተረድተዋል፡፡<br />
በመሆኑም የከተማውን ነዋሪ በመሰብሰብ<br />
ማስፈራራት ነበረባቸው፡፡ ለዚህም ሰማያዊ<br />
ፓርቲን ስም እየለጠፉ ህዝቡን ለማራቅ<br />
ከመሞከር ባለፈ ‹‹ልጆቻችን ሰላማዊ ሰልፉ<br />
ላይ ቢሳተፉ በጥይት ይመታሉ!›› ብለው<br />
እስከማስፈራራት ደርሰዋል፡፡ የተሸናፊዎቹ<br />
አቅም ይህ ነው፡፡ ሰላማዊ ሰልፉ ሊደረግ<br />
10 ደቂቃ ሲቀረው ደግሞ በየ መግቢያው<br />
የተደረደሩት ፖሊሶች ህዝብን ወደ መስቀል<br />
አደባባይ እንዳይሄድ ሲያግዱ ተስተውለዋል፡<br />
፡ በሰላማዊ ሰልፉ ወቅትም የቀበሌ ካድሬዎች<br />
ከሰልፉ በኋላ በመሆን ህዝቡን በመቅረጽ<br />
ለማስፈራራት ሞክረዋል፡፡ በእርግጥ ከዚህ<br />
አልፈው ሰላማዊ ሰልፉ ከተጠናቀቀ በኋላ<br />
እርምጃ እየወሰዱ መሆናቸውም ተሰምቷል፡<br />
፡ ሰላማዊ ሰልፉ ካበቃ በኋላ በቅርብ<br />
እርቀት ሲከታተሉ የነበሩት ካድሬዎች<br />
በሰልፉ ላይ የተሳተፉትን ወጣቶች የቀበሌ<br />
መታወቂያ ቀምተዋል፡፡ ወደ ቀበሌ ሄደው<br />
መታወቂያቸውን በተቀበሉበት ወቅትም<br />
ዳግመኛ ሰማያዊም ሆነ ሌሎች ፓርቲዎች<br />
በሚጠሩት ሰልፍ እንዳይሳተፉ ማስጠንቀቂያ<br />
ተሰጥቷቸዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ሰልፉን<br />
ያስተባበሩት የጎንደር የፓርቲው አባላትና<br />
ቤተሰቦቻቸው ላይ ደህንነቶች እየደወሉ<br />
ሲያስፈራሩዋቸው ሰንብተዋል፡፡<br />
ሰላማዊ ሰልፉ ተደርጎም ቢሆን ማዋከቡ እንደማይቆም ቀድመው የተገነዘቡት የፓርቲው<br />
አመራሮች ጎንደርን ቶሎ መልቀቅን እንዳለባቸው አምነዋል፡፡ እናም ሰላማዊ ሰልፉ<br />
ከተጠናቀቀ ከሁለት ሰዓት በኋላ ጉዞ ወደ አዲስ አበባ ተጀመረ፡፡ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች<br />
መሬቱን ለማስመለስ የተደረገውን ግፊት ቢያደንቁም ሰማያዊ በመመለሱ ከመጠን በላይ<br />
የሚቆራረጠው የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎት ጋብ እንደሚል በግልጽ ይናገሩ ነበር፡<br />
፡ ሰላማዊ ሰልፉ በሰላም መካሄዱ ያናደደው የሚመስለው ገዥው ፓርቲ ግን ከጎንደርም<br />
ውጭም እየተከተለ መተንኮሱን አላቆመም፡፡ አዲስ አበባ ለመድረስ ጥቂት ኪሎ ሜትሮች<br />
ሲቀሩንም ቢሆን ‹‹ከበላይ አካል›› ትዕዛዝ የተላለፈላቸው የሚመስሉት የትራፊክ<br />
ፖሊሶች ደብረ ጽጌ ላይ በመሳሪያ አስቆሙን፣ አስጸያፊ ስድብምና ማስፈራራትም<br />
ተጨመረበት፡፡<br />
ሆኖም በሰልፉ የተገኙት ወጣቶችም ይህን<br />
የአካባቢው ቅርንጫፍ በደረሰባቸው ወከባ<br />
አለመደናገጣቸውን ደውለው ነግረውኛል፡፡<br />
ለሰላማዊ ሰልፉ በሄድንበት ወቅት ጎንደር<br />
ውስጥ ካገኘኋቸው የኢህአዴግ አባላት<br />
መካከል አብዛኛዎቹ መሬቱ ለባዕድ ተላልፎ<br />
መሰጠቱን ከመቃወም አልፈው በጉዳዩ<br />
ከተቃዋሚዎች ጋር አብረው ለመስራት<br />
ፍላጎት እንዳላቸው ተረድቻለሁ፡፡ ደብድቡ<br />
ተብለው የተላኩት ፖሊሶችና የከተማው<br />
አስተዳደርም እንደ ፌደራል መንግስቱ<br />
ግትር አቋም አለመውሰዱ የሽንፈቱ አንድ<br />
አካል ነው ማለት ይቻላል፡፡<br />
ወደ አዲስ አበባ<br />
ጉዞ<br />
ሰላማዊ ሰልፉ ተደርጎም ቢሆን ማዋከቡ<br />
እንደማይቆም ቀድመው የተገነዘቡት<br />
የፓርቲው አመራሮች ጎንደርን ቶሎ<br />
መልቀቅን እንዳለባቸው አምነዋል፡፡ እናም<br />
ሰላማዊ ሰልፉ ከተጠናቀቀ ከሁለት ሰዓት<br />
በኋላ ጉዞ ወደ አዲስ አበባ ተጀመረ፡<br />
፡ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች መሬቱን<br />
ለማስመለስ የተደረገውን ግፊት ቢያደንቁም<br />
ሰማያዊ በመመለሱ ከመጠን በላይ<br />
የሚቆራረጠው የስልክና የኢንተርኔት<br />
አገልግሎት ጋብ እንደሚል በግልጽ ይናገሩ<br />
ነበር፡፡ ሰላማዊ ሰልፉ በሰላም መካሄዱ<br />
ያናደደው የሚመስለው ገዥው ፓርቲ ግን<br />
ከጎንደርም ውጭም እየተከተለ መተንኮሱን<br />
አላቆመም፡፡ አዲስ አበባ ለመድረስ ጥቂት<br />
ኪሎ ሜትሮች ሲቀሩንም ቢሆን ‹‹ከበላይ<br />
አካል›› ትዕዛዝ የተላለፈላቸው የሚመስሉት<br />
የትራፊክ ፖሊሶች ደብረ ጽጌ ላይ<br />
በመሳሪያ አስቆሙን፣ አስጸያፊ ስድብምና<br />
ማስፈራራትም ተጨመረበት፡፡<br />
ይህ ሁሉ ወከባ ግን ልዑካኑን አላስደነገጠም፡<br />
፡ ወደ ጎንደር ጉዞ ከጀመሩበት ወቅት አንስቶ<br />
ወጣቶቹ በድፍረት ከተሸናፊው መንግስት<br />
ጋር ፊት ለፊት ተጋፍጠዋል፡፡ ደብረ ጽጌ<br />
ላይም ያደረጉት ተመሳሳይ ነው፡፡ ትራፊክ<br />
ፖሊሶች መኪናውን ወደ ጣቢያ እንዲወስድ<br />
ሲወተውቱት የሰነበተውና ከልዑካኑ ጋር<br />
ሁለቱንም ቀን የታሰረው ሾፌር ደብረ ጽጌ<br />
ላይም ልክ እንደ ሰማያዊ ወጣቶች መብቱን<br />
አሳልፎ ላለመስጠት ያለውን ቁርጠኝነት<br />
አሳየ፡፡ የልዑካኑ አባላት መሳሪያ አውጥቶ<br />
‹‹እበትንሃለሁ!›› ላለው ፖሊስ ደረታቸውን<br />
ሰጡ፤ አጸያፊ ስድብ የተሳደበውን<br />
አፋጠጡት! አሁን ልዑካኑን ለማስቆም<br />
የጣሩት ፖሊሶች እንደገና መደናገጥ<br />
ጀምረዋል፡፡ የከተማው ህዝብ ወጣቶቹና<br />
የትራፊክ ፖሊስ የሚያደርጉትን ክርክር<br />
እየተመለከተ ተስብስቧል፡፡<br />
የሰማያዊ ወጣቶች ዋናው ሰላማዊ ሰልፍ<br />
ከመደረጉ በፊት መስቀል አደባባይና አዘዞ<br />
ላይ ፖሊስ ሲያስቆማቸው ሲይዛቸው<br />
በመዘመር፣ ህጉን በማስረዳት ህዝብን<br />
ሰብስበዋል፡፡ በጽናታቸውና በድፍረታቸው<br />
ፖሊሶቹን ሳይቀር አስገርመዋል፡፡ ደብረ<br />
ጽጌ ላይ በመሳሪያ ለማስቆም ሲጥርም<br />
ሌላ ሰላማዊ ሰልፍ አድርገዋል፣ ህዝብን<br />
ሰብስበው ስለመብቱ አስተምረዋል፡<br />
፡ ከፖሊስ ጋር እየተከራከሩ፣ ህዝብን<br />
ሰብስበው እያስተማሩም ለቀሪው ህዝብ<br />
በስልክና በማህበራዊ ድህረ ገጾች ትዕይንቱን<br />
ማካፈላቸውን ቀጥለዋል፡፡ በተለይ በፌስ<br />
ቡክ ዜናው በስፋት መዳረስ ጀምሯል፡፡<br />
ይህን ሁሉ ያልጠበቁት ትራፊክ ፖሊሶችን<br />
የላኩት የበላይ አካላትም ይሁኑ የከተማው<br />
ካድሬዎች ወጣቶቹን ለመልቀቅ ተገድደዋል፡<br />
፡ ለኢህአዴግ ሌላ ሽንፈት! ለሰማያዊ<br />
ወጣቶች ሌላ ድል! ከድል በኋላም የድል<br />
መዝሙር!<br />
ተከብረሽ የኖርሽው በአባቶቻችን ደም፣<br />
በአባቶቻችን ደም፣<br />
እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውደም<br />
ያስደፈረሽ ይውደም፣<br />
……….<br />
‹‹የትግል ጉዞ ታሪካዊ፣<br />
ዓላማው ፍጹም ህዝባዊ፣<br />
ራዕያችንም ኢትዮጵያዊ…››<br />
መሬት ያስቆረሱት...<br />
ከ ገፅ 7 የዞረ<br />
የሚያስረዱ መረጃዎች ሊሆኑ አይችሉምን?<br />
ድብቅነት በኢትዮጵያ በመግዛት ላይ ላለው<br />
ገዥው አካል ዋና መለያ ባህሪው ነው፡፡ ነገሮችን<br />
ደብቆ በመያዝ እያንዳንዱን በማሞኘት ላይ<br />
ይገኛሉ፡፡ አቶ መለስ በህይወት በነበሩበት ጊዜ<br />
እና በአሁኑ ጊዜ ያሉት ሎሌዎቻቸው ደግሞ<br />
የቅብብሎሽ ዱላውን ከጌታቸው ራዕይ በመቀበል<br />
በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እያሳዩ ያሉት ንቀት<br />
የህዝቡን ምንነት ሳይገመግሙ እና ሳይረዱ<br />
በራቁት ገላው ላይ ሱፍ እየጎተቱ መሆኑን<br />
በውል ሊያጤኑት ይገባል፡፡ አቶ መለስ እና<br />
ጋሻጃግሬዎቻቸው አሰብን እና ባድመን በቤሣ<br />
ቁርጥራጮች ካስረከቡ በኋላ ዝምታ ብቻ<br />
መልስ ስላገኙ ከዚያ ነገር አንድ ቁም ነገር<br />
ተምረዋል፡፡ ይኸውም ኢትዮጵያውያንን እና<br />
የኢትዮጵያን ግዛት የእነርሱ የግል እንደፈለጉ<br />
የሚለውጧት፣ የሚሸጧት የህግ ተጠያቂነት<br />
የሌለበት የግል ንብረታቸው መሆኗን አረጋገጡ፡<br />
፡በመለስ/ኃይለማርያም ከምዕራብ ኢትዮጵያ<br />
የግዛት አንድነት መሬት በመቁረስ ለሱዳን<br />
ለመስጠት የሚደረግ ማንኛውም “ስምምነት”<br />
ህገመንግስታዊ አይደለም፡፡ እ.ኤ.አ. ወደ 2008<br />
መለስ ብለን ስናይ አቶ መለስ የኢትዮጵያን<br />
መሬት ቆርሰው ለሱዳን ወይም ደግሞ ለማንም<br />
ቢሆን ለመስጠት ህጋዊ ስልጣን የላቸውም ብዬ<br />
ተከራክሬ ነበር፡፡<br />
ዛሬም ቢሆን አቶ ኃይለማርያም የኢትዮጵያን<br />
መሬት ቆርሰው ለሱዳን የመስጠት ህጋዊ<br />
መብትም ሆነ ስልጣን የላቸውም፡፡ ይህንን ካልኩ<br />
ዘንድ አቶ መለስ “ከአማራ ክልል ግዙፍ የሆነ<br />
መሬት” ቆርሰው ለሱዳን ለመስጠት “ስምምነት”<br />
እንደተፈራረሙ አጠያያቂ ነገር አይደለም፡<br />
፡ አቶ ኃይለማርያም እና ጌቶቻቸው ይህን<br />
ህገወጥ የመሬት ዕደላ ዕኩይ ተግባራቸውን<br />
“የስልታዊ/ስትራቴጂክ ስምምነት ማዕቀፍ”<br />
በማለት የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ በመክፈት ጣፋጭ<br />
በማስመሰል በማር የተለወሰ መርዛቸውን<br />
ሊግቱን ይፈልጋሉ፡፡ እውነታው ግን በአሁኑ<br />
ጊዜ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ያለው ገዥ አካል<br />
ምንም ዓይነት የኢትዮጵያን መሬት ለሱዳንም<br />
ሆነ ለማንም ሌላ አገር አሳልፎ የመስጠት ህገ<br />
መንግስታዊም ሆነ ዓለም አቀፋዊ መብትም<br />
ስልጣንም የለዉም፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ<br />
ሊታይ የሚችለው ይህ የተካሄደው የድብቅ<br />
ስምምነት የኢትዮጵያን ህገ መንግስት አንቀጽ<br />
12 የሚጻረር ስለሆነ የህገ መንግስት ጥያቄን<br />
ያስነሳል፡፡ አቶ መለስ በህይወት በነበሩበት ጊዜ<br />
እና እርሳቸውን ተክተው በመስራት ላይ ያሉት<br />
የአሁኖቹ ገዥዎቻችን ከኢትዮጵያ ህዝብ እና<br />
ከተወካዮች ምክር ቤት በሸፍጥ ደብቀው ከኦማር<br />
አልባሽር ጋር ያደረጉትን የሚስጥር “ስምምነት”<br />
እየተባለ የሚጠራውን ተግባራዊ ለማድረግ<br />
ይፍጨረጨራሉ፡፡ በኢትዮጵያ ህገ መንግስት<br />
አንቀጽ 12 ስር (“የመንግስት የስራ ድርሻ<br />
እና ተጠያቂነት“) እንዲህ ይላል፣ “መንግስት<br />
ተጣያቂነት እና ለህዝብ ግልጽነት ባለበት ሁኔታ<br />
ስራውን ይሰራል… ማንም የህዝብ ባለስልጣን<br />
ወይም ተመራጭ በህግ የተሰጠውን ስልጣን<br />
በህግ አግባብ ካልተጠቀመ ተጠያቂ ይሆናል፡<br />
፡” አቶ መለስ እና ተኪዎቻቸው “የህዝብ<br />
ባለስልጣን” እንደመሆናቸው መጠን ግልጽነት<br />
እና ተጠያቂነት ባለበት ሁኔታ ስራቸውን<br />
ለማከናወን ህገ መንግስታዊ ግዴታ አለባቸው፡<br />
፡ ለህዝብ ሳይቀርብ እና የስምምነቱ ሁኔታም<br />
በዝርዝር ምን እንደሆነ ሳይታወቅ እንዲሁም<br />
ህጋዊ ስልጣን የተሰጠው የተወካዮች ምክር<br />
ቤት ሳያጸድቀው የአገርን የግዛት አንድነት<br />
በመጣስ መሬት ቆርሶ ለሌላ አገር ለመስጠት<br />
በእራስ ፈቃድ የሚደረግ የሚስጥር ስምምነት<br />
የህገመንግስቱን አንቀጽ 12 ይጻረራል፣ ሙሉ<br />
በሙሉም ህገ መንግስቱን ይደፈጥጣል፡፡<br />
ኢትዮጵያ ለዘላለም በክብር ትኑር!<br />
(ሳምንት ይቀጥላል…)
ነገረ-ኢትዮጵያ<br />
ቅፅ 1 ቁጥር 2<br />
የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም.<br />
16<br />
ኢህአዴግ ተሸንፏል!<br />
(የጉዞ ማስታወሻ)<br />
ጌታቸው ሺፈራው<br />
ዛሬ የማወራው በምርጫ ስለመሸነፍ<br />
አይደለም፡፡ በምርጫ መሸነፍማ ወግ<br />
ነው፡፡ በተለይ ምርጫን ፍትሃዊና<br />
ዋነኛው የስልጣን ምንጭ አድርጎ<br />
ሽንፈቱን በጸጋ ለተቀበለ ‹‹ሽንፈቱ››<br />
አሸናፊነት በሆነ ነበር፡፡ ኢህአዴግ<br />
ይህኛውን ወግ አላገኘውም፡<br />
፡ እንዲያውም አስከፊው ሽንፈት<br />
ሳያውቁት፣ በግድ መሸነፍ ሳይሆን<br />
አይቀርም፡፡ አዎ ኢህአዴግ ይህን<br />
ሽንፈት ተከናንቦታል፡፡ ኢህአዴግ<br />
ይህንን ሽንፈቱን ለመሸፈን ለ23<br />
አመታት በግድ መግዛትን መርጧል፡፡<br />
ከ1997 በኋላ ተቃዋሚዎች<br />
ቢዳከሙም፣ ህዝብ በፖለቲካው ተስፋ<br />
ቆርጦ ‹‹ዝም ብሎ ለመገዛት›› የቆረጠ<br />
ቢመስልም ኢህአዴግ ግን ሽንፈቱን<br />
ይደብቅልኛል ያለውን ወከባና ጥርነፋ<br />
አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ ባለፉት ጥቂት<br />
ወራት ደግሞ በፖለቲካው መስክ<br />
መነቃቃቶች እየታዩ ነው፡፡ ይህኛው<br />
‹‹ዝም›› ያለው ህዝብ ኢህአዴግን<br />
እንደማይፈልግ፣ ኢህአዴግ ምንም<br />
ያህል የመጨቆንና የማታለል አቅም<br />
ቢኖረውም የህዝብን ልብ መግዛት<br />
አለመቻሉንና መሸነፉን የሚያሳይ<br />
ነው፡፡ ኢህአዴግ ለመሸነፉ እጅግ<br />
በርካታ ማሳያዎችን ማንሳት ይቻላል፡<br />
፡ አሁን ግን ለሱዳን አሳልፎ ከሰጠው<br />
መሬት ጋር በተያያዘ ያለው ጉዳይ<br />
ላይ ብቻ ማተኮር ወደድኩ!<br />
ፓርቲ የጎንደር ጉዞ<br />
የሰማያዊ<br />
ሰማያዊ ፓርቲ ወደ ጎንደር ከማቅናቱ<br />
በፊት በጽ/ቤቱ በድንበሩ ጉዳይ ጥናት<br />
ካደረጉት መካከል ብቸኛው የሆኑትን<br />
ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያምን<br />
በመጋበዝ ህዝብን አወያይቶ ነበር፡፡<br />
በዚህ ውይይት ወቅት ፕሮፌሰሩን<br />
ጨምሮ ተሰብሳቢዎቹ ‹‹ኢህአዴግ<br />
አገር ሻጭ›› መሆኑን ተናግረዋል፡<br />
፡ ሁሉም እንደ መንግስት ሳይሆን<br />
የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት አሳልፎ<br />
ለመስጠት የተነሳ አንዳች ባዕድ<br />
ሀይል እንደሆነ ተግባብቶበታል፡፡<br />
የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች<br />
ደግሞ ይህን የፕሮፌሰር መስፍንና<br />
የሌሎችን ጥናት እንዲሁም<br />
መረጃዎች በግብዓትነት ወስደው<br />
ሉዓላዊነታቸውን ለማስከበር ወደ<br />
ጎንደር ለማቅናት በዝግጅት ላይ<br />
ነበሩ፡፡<br />
ሰማያዊ ወደ ጎንደር ሲያቀናም<br />
ኢህአዴግ መሸነፉን በጉልህ<br />
ተመልክቻለሁ፡፡ አድርባይ ደህንነትና<br />
ፖሊስ የማይፈሩት ወጣቶች<br />
ወደሚታሰሩበት፣ ወደሚደበደቡበትና<br />
መስዕዋትነት ወደሚያስከፍል ተልዕኮ<br />
ሳይሆን ለሰርግ አሊያም ለሌላ<br />
ቅንጦች የሚጓዙ ያህል ደስተኞች<br />
ነበሩ፡፡ ሰላማዊ ሰልፍ በሚወገዝበት<br />
ስርዓት አብዛኛዎቹ ወጣቶች ‹‹እኔ<br />
አልቀርም!›› በማለት የፓርቲውን<br />
አመራሮች ሲለምኑ፣ በመቅረታቸው<br />
ቅር መሰኘታቸው ስርዓቱ<br />
ሊያስገባቸው ከሚፈልገው የፍርሃት<br />
አዙሪት ሰብረው መውጣታቸውን<br />
የሚያሳይ ነው፡፡<br />
ወከባ<br />
የተሸናፊው<br />
የተሸነፈ የሚወስደው እርምጃ<br />
ግብታዊ ነው፡፡ ተረጋግቶ መፍትሄ<br />
ከመስጠት ይልቅ ማዋከብ፣ መደናበር<br />
ልዩ ባህሪው ነው፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ<br />
ልዑካን ወደ ጎንደር አቅንተው<br />
እንደገና አዲስ አበባ እስኪመለሱ<br />
ያጋጠማቸውም ይህ የተሸናፊዎች<br />
እርምጃ ነው፡፡ ወከባው የጀመረው<br />
የጎጃሟ ሉማሜ ከተማ ላይ ነው፡<br />
፡ ከአዲስ አበባ ጀምሮ በርካታ<br />
የትራፊክ ፖሊሶች እየገላመጡ<br />
ቢያሳልፉንም ከላይ አንዳች<br />
ትዕዛዝ የተሰጣት የምትመስለዋ<br />
የሉማሜዋ የትራፊክ ፖሊስ ግን<br />
በቀላሉ የምታሳልፈን አልነበረችም፡<br />
፡ መውጫው የምትቆዩበትን ቀን<br />
በግልጽ አላስቀመጠም በሚል ሰንካላ<br />
ምክንያት መኪናችን አስቆመች፡<br />
፡ ካልተቀጣችሁ አትሄዱም በማለቷ<br />
ላለመዘግየት ‹‹ቅጣታችን›› ቶሎ<br />
መክፈልን ወሰንን፡፡ ምን አልባትም<br />
ከ‹‹በላይ አካል›› ትዕዛዙ የመጣላት<br />
የምትመስለው የትራፊክ ፖሊስ<br />
ውሳኔ ግን ቢሮ ውስጥ የነበረውን<br />
አለቃዋንም ያስገረመ ነበር፡፡<br />
ለመክፈል ወደ አለቃዋ ቢሮ ያቀኑት<br />
የልዑካኑ አባላት እንዳረጋገጡልን<br />
የትራፊክ ፖሊሷ ያቀረበችው ሰንካላ<br />
ምክንያት ለማስቀጣት ይቅርና<br />
ለተግሳጽ የሚያበቃ አልነበረም፡፡<br />
መስዋትነት ወደሚያስከፍል<br />
ተልዕኮ ሳይሆን ወደ አንዳች ደስታ<br />
ቦታ የሚያቀኑ የሚመስሉት<br />
የልዑካኑ አባላት መንገዱን በሙሉ<br />
የአገራቸውንና የፓርቲያቸውን<br />
መዝሙር በመዘመር፣ እንዲሁም<br />
በመቀላለድና በመሳሳቅ ጉዟቸውን<br />
ቀጥለዋል፡፡ ይህን ደስታቸውን<br />
ከጥቂት አመታት በፊት በርካታ<br />
ወጭ ፈሶበት በጥቂት አመት ውስጥ<br />
የፈረሰው ቻይና ሰራሽ መንገድ እንኳ<br />
አላቀዘቀዘውም፡፡ ሆኖም የመኪናችንን<br />
ፍጥነት በእጅጉ ቀንሶታል፡፡ በዚህም<br />
ምክንያት በጊዜ መግባት ሲገባን<br />
ግማሹን ሌሊት ሁሉ ለመጓዝ<br />
ተገደናል፡፡<br />
አይደለም ሰማያዊን የግንባሩን አባላት<br />
የማያምነው ኢህአዴግ የልዑካኑንና<br />
ከልዑካኑ ጋር የሚገናኙትን አካላት<br />
በቅርብ እርቀት መከታተሉ የሚጠበቅ<br />
ነው፡፡ ስለሆነም የት እንደደረስን፣<br />
መቼ ጎንደር እንደምንገባና<br />
ሌሎች መረጃዎችን ለአገሪቱ<br />
ሳይሆን ለስልጣን ማራዘሚያ<br />
በሚጠቀምባቸው የደህንነት<br />
ተቋማቱ ሊያዳምጥ እንደሚችል<br />
ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ ይህን<br />
እያወቅንም ቢሆን እኛ እንደልባችን<br />
እናወራለን፡፡ የት እንደደረስን፣ መቼ<br />
እንደምንገባና ሌሎች መረጃዎችንንም<br />
በነጻነት እንለዋወጣለን፡፡ በተለይ<br />
ጎንደር ከሚገኘው የፓርቲው<br />
ቅርንጫፍና ቀድመው ወደ ጎንደር<br />
ካቀኑት የፓርቲው አመራሮች ጋር<br />
እነዚህን መረጃዎች በተከታታይ<br />
ተለዋውጠናል፡፡<br />
ጎንደር ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ላይ<br />
ደረስን፡፡ እነዚህን መረጃዎች<br />
ሲያዳምጥ የነበረው ገዥው ፓርቲ<br />
የተሸናፊ እርምጃ ሊወስድ እንደነበር<br />
የሰማነው ግን በነጋታው ጠዋት ላይ<br />
ነው፡፡ እንፍራንዝ የተባለችውን ከተማ<br />
እኛ ያለፍናት ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት<br />
አካባቢ ነው፡፡ ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት<br />
አካባቢ ‹‹ሰማያዊ ነው!›› ተብሎ<br />
መኪና መዘረፉን የነገረን በአካባቢው<br />
የሚገኝ አንድ የሰማያዊ ፓርቲ ደጋፊ<br />
ነው፡፡ አዎ የተሸነፈ የሚወስደውን<br />
እርምጃ አያውቅም፡፡ ለማመዛዘን<br />
ጊዜም ሆነ ብቃት አይኖረውም፡፡<br />
ወከባው ጎንደር ከደረስን በኋላም<br />
ቢሆን አላቆመም፡፡ ካድሬዎች<br />
ያረፍንበትን ሆቴል ማጨናነቅ ዋነኛ<br />
ስራቸው ሆነ፡፡ ከዚህም አልፈው<br />
‹‹እነዚህን ሰዎች አስወጡልን!››<br />
እስከማለት መድረሳቸውን በግልጽ<br />
ሰምተናል፡፡ በሌላ በኩል የሰላማዊ<br />
ሰልፉ እንዲካሄድ ባለመፈለጋቸው<br />
አንቀበልም ከማለትም አልፈው<br />
ሲደበቁ የሰነበቱት የጎንደር ከተማ<br />
አስተዳደር ባለስልጣናት የሰማያዊ<br />
ወጣቶች ገፍተው ከገቡበት እውነት<br />
ጋር መፋጠጥ የግድ ሆኖባቸዋል፡፡<br />
ሀሙስ ጥር 22 ስድስት ሰዓት ላይ<br />
ሰው የሚበዛባት አራዳ ለቅስቀሳ<br />
ተመርጣለች፡፡ ከየት እንደመጡ<br />
ያልታወቁት የሰማያዊ ወጣቶች<br />
በፍጥነት ወረቀቶችን ለህዝብ<br />
ማድረስ ጀመሩ፡፡ መኪና ላይ ሆነው<br />
መሬቱን አሳልፈው እንደማይሰጡ<br />
ህዝብን ቀሰቀሱ፡፡ ቅስቀሳውን ከአራዳ<br />
እስከ መስቀል አደባባይ በፍጥነት<br />
አከናወኑ፡፡ ምን አልባት እስራት<br />
ካለ ህዝብ በስፋት ከሚያይበት<br />
የመስቀል አደባባይ ላይ መታሰሩ<br />
አዋጭ እንደሚሆን ታምኖበታል፡<br />
፡ እንደተገመተው የተደናገጡት<br />
የከተማው ባለስልጣናት መስቀል<br />
አደባባይ ላይ እየቀሰቀሱ የነበሩትን<br />
ወጣቶች ለማስቆም ጥረት አደረጉ፡<br />
፡ ማስቆም የፈለጉበት መንገድ ግን<br />
የሚያስገርም ነበር፡፡<br />
ልክ ሉማሜ ላይ እንዳደረጉት<br />
የላኩት የትራፊክ ፖሊስ ነው፡፡ ምን<br />
አልባትም መኪናቸውን ከተቀሙ<br />
እንቅስቃሴው ይገታል ከሚል እሳቤ<br />
ሳይሆን አይቀርም፡፡ ጎንደር ላይ ግን<br />
በቀላሉ የሚሳካ አልነበረም፡፡ ሲቪል<br />
የለበሱ የትራፊክ ፖሊሶች ሳይቀሩ<br />
ለወጣቶቹና ተሸናፊዎች ላስደፈሩት<br />
ሉዓላዊነት ዘብ ቆመው ታይተዋል፡<br />
፡ ቅስቀሳውን እንዲያስቆሙ<br />
የተላኩት ፖሊሶች መኪናው ምን<br />
እንዳጠፋ ንገሩን ሲባሉ ምክንያት<br />
አልነበራቸውም፡፡ ግን ‹‹ከበላይ<br />
አካል›› ይዛችኋቸው ኑ መባላቸውን<br />
ብቻ ነው በተደጋጋሚ የሚገልጹት፡፡<br />
ቅስቀሳ ላይ የነበሩት ወጣቶች ከታሰሩ በኋላ የኢትዮጵያ ፖሊስ የሚታወቅበትን ድብደባና ዘለፋ አልፈጸመም፡<br />
፡ ይህ ግን የፖሊሶቹ ደግነት ብቻ አልነበረም፡፡ የከተማ አስተዳደሩ አንዳች ቅርቃር ውስጥ መግባቱን ራሱ<br />
አስመስክሯል፡፡ ወጣቶቹ እስር ቤት እያሉ ከቀናት በፊት የማሳወቂያ ደብዳቤውን አልቀበልም ያሉት አካላት<br />
አመናጭቀው የመለሷቸውን ሰዎች አስጠርተው ተለማምጠዋል፡፡<br />
የሰማያዊ ወጣቶች ደግሞ ጥፋታችንን<br />
ካልነገራችሁን ቅስቀሳውን አናቆምም<br />
ካለንበትም አንንቀሳቀስም አሉ፡፡<br />
ቅስቀሳውን የደገፈው ህዝብም ቢሆን<br />
ተመሳሳይ አቋም ያዘ፡፡ ቅስቀሳውን<br />
ሲከታተል ከነበረው ህዝብ ‹‹ከህዝብ<br />
ጋር እንዳትቀያየሙ›› የሚል<br />
ምክር የተሰጣቸውና ወትሮውንም<br />
ያላመኑበት የትራፊክ ፖሊሶች<br />
መለሳለስ ጀመሩ፡፡ ትንሽ ቆይተው<br />
የወጣቶቹን ቅስቀሳና ከፖሊስ ጋር<br />
የሚያደርጉትን ትዕይንት እንደ ህዝብ<br />
ታድመዋል፡፡<br />
የከተማው አስተዳደር ግን ቅስቀሳው<br />
መቆም እንዳለበት ቆርጧል፡፡<br />
በመሆኑም የትራፊክ ፖሊሶችን ተክቶ<br />
ፖሊስ ተላከ፡፡ ኢህአዴግ ከምንም<br />
በላይ የሚፈራው መረጃን ነው፡<br />
፡ በመሆኑም የፖሊሶች የመጀመሪያ<br />
ኢላማ የሆነው ፎቶ ግራፍ<br />
የሚያነሳው ወጣት ነበር፡፡ ካሜራውን<br />
ለመንጠቅ ሲሞክሩ ግን ከሰማያዊ<br />
ልጆች ከፍተኛ ትግል ገጠማቸው፡<br />
፡ ፖሊስና ወጣቶቹ ተናነቁ፡፡ ህዝብ<br />
ተሰበሰበ፡፡ ወጣቶቹ ህግ አያከብርም<br />
የሚሉት ኢህአዴግ የላካቸውን<br />
ፖሊሶች እየተፋለሙ ‹‹በህግ አምላክ!<br />
በህግ አምላክ!›› ይላሉ፡፡ በህግ ሳይሆን<br />
በጉልበት ቅስቀሳውን እንዲያስቆሙ<br />
የተላኩት ፖሊሶች ግን ከዚህ በላይ<br />
መታገል አልፈለጉም፡፡ አዎ! ከበላይ<br />
አካል ከተሰጣቸው ይልቅ ‹‹በህግ<br />
አምላክ›› ሲባሉ ተደናግጠው ቆሙ፡<br />
፡ ጎንደር ላይ በህግ አምላክ ተከበረ፡<br />
፡ የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች በቀላሉ<br />
እጅ የሚሰጡ አልነበሩም፡፡ እናም<br />
አምነውበት ሳይሆን ከበላይ አካል<br />
የተላኩት ፖሊሶች ያለ ግድ በውድ<br />
ለሰማያዊ ወጣቶች ካሜራውን ለቀቁ፡፡<br />
አሁን ኢህአዴግ ተሸንፏል፡፡ ወጣቶቹ<br />
ደግሞ በአሸናፊነት ይዘምራሉ፡፡<br />
ተከብረሽ የኖርሽው በአባቶቻችን<br />
ደም፣<br />
በአባቶቻችን ደም፣<br />
እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውደም<br />
ያስደፈረሽ ይውደም፣<br />
……….<br />
‹‹የትግል ጉዞ ታሪካዊ፣<br />
ዓላማው ፍጹም ህዝባዊ፣<br />
ራዕያችንም ኢትዮጵያዊ…››<br />
ያም ሆኖ ፖሊሶቹ ‹‹ይዛችኋቸው<br />
ኑ!›› የተባሉትን ትዕዛዝ አልረሱም፡፡<br />
ወጣቶቹ በመኪና ተጫኑ፡፡ ከፖሊሶቹ<br />
ጋር ሆነው ግን ወረቀት ከመበተን፣<br />
በሞንታርቮ ከመቀስቀስ ያገዳቸው<br />
አካል አልነበረም፡፡ እንዲያውም ወደ<br />
ፖሊስ ጣቢያው የሚያደርሰውን<br />
ረዥም መንገድ ይዘው ሲጓዙ<br />
ፖሊሶቹ ሰላማዊ ሰልፉ እንዲካሄድ<br />
ፍላጎት እንደነበራቸው ያሳያል፡፡<br />
ቅስቀሳ ላይ የነበሩት ወጣቶች<br />
ከታሰሩ በኋላ የኢትዮጵያ ፖሊስ<br />
የሚታወቅበትን ድብደባና ዘለፋ<br />
አልፈጸመም፡፡ ይህ ግን የፖሊሶቹ<br />
ደግነት ብቻ አልነበረም፡፡ የከተማ<br />
አስተዳደሩ አንዳች ቅርቃር ውስጥ<br />
መግባቱን ራሱ አስመስክሯል፡፡<br />
ወጣቶቹ እስር ቤት እያሉ ከቀናት<br />
በፊት የማሳወቂያ ደብዳቤውን<br />
አልቀበልም ያሉት አካላት<br />
አመናጭቀው የመለሷቸውን ሰዎች<br />
አስጠርተው ተለማምጠዋል፡፡<br />
በአንድ በኩል ተርበትብተው መደራደር<br />
የሚፈልጉት የጎንደር አስተዳደር<br />
ሰዎች በሌላ በኩል ማዋከባቸውን<br />
ግን አላቆሙም፡፡ የታሰሩት ቢፈቱም<br />
ቅስቀሳውን ለማሰናከል መሳሪያዎቹ<br />
በፖሊስ እንደተያዙ ቆይተዋል፡፡<br />
የመቀስቀሻ መሳሪያዎቹ በፖሊስ<br />
እጅ በመውደቃቸውና ለአንዳንድ<br />
ጥንቃቄዎች ሲባል አርብ ጥር 23<br />
ወረቀት መበተንና ሌሎች ግልጽ<br />
ቅስቀሳዎች አልነበሩም፡፡ ይህም<br />
በስጋት የተዋጡት የከተማው<br />
አስተዳደር አካላትን አስጨንቋል፡<br />
፡ እናም በተቀላቀለ ስሜት ደውለው<br />
‹‹ምነው ጠፋችሁ!›› እስከማለት<br />
ደርሰዋል፡፡ ቅዳሜ ጥር 24 ኮሌጅና<br />
አዘዞ ለቅስቀሳ ተመርጠዋል፡፡<br />
ለቅስቀሳ የወጡት ወጣቶች ኮሌጅና<br />
ዩኒቨርሲቲው አካባቢን በፍጥነት<br />
ከቀሰቀሱ በኋላ ወደ አዘዞ ሲደርሱ<br />
ፖሊስ አስቁሟቸዋል፡፡<br />
የሰማያዊ ፓርቲ ልዑካን ወደ ጎንደር<br />
ካቀኑበት ጊዜ ጀምሮ ከወትሮው በተለየ<br />
መልኩ ኢንተርኔትና ስልክ ተቋርጦ<br />
ለረዥም ሰዓት መቆየት ጀምሯል፡<br />
፡ ከዚህ ባሻገር ከሆቴሉ ጎን የሚገኝ<br />
ቤት በእሳት ተያያዘ ተብሎ ጥይት<br />
በመተኮስ ጫጫታ ለመፍጠርና<br />
መብራት በማጥፋት ለማደናገጥም<br />
ተሞክሯል፡፡ ተቃጠለ የተባለው<br />
ቤት ከሆቴሉ ጎን ቢሆንም ምንም<br />
አይነት ጭስ፣ የእሳት ምልክትና ሽታ<br />
አልነበረውም፡፡ ወዲያውኑ ደግሞ<br />
ጠፋ ተባለ! በቅስቀሳ ላይ የነበሩት<br />
ወጣቶች አዘዞ ላይ በተያዙበት ወቅት<br />
ወደ ገፅ 15 ይዞራል