06.03.2014 Views

Neger Ethiopia Issue 2

Neger Ethiopia Issue 2

Neger Ethiopia Issue 2

SHOW MORE
SHOW LESS

You also want an ePaper? Increase the reach of your titles

YUMPU automatically turns print PDFs into web optimized ePapers that Google loves.

1 የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2 ነገረ-ኢትዮጵያ<br />

ነገረ-ኢትዮጵያ<br />

ስለ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊያን እንናገራለን!<br />

ቅፅ 1 ቁጥር 2 አርብ የካቲት 7 2006 ዓ.ም. ዋጋ 8.00<br />

ማርቆስ ሀጎሶች እና<br />

ዳሮ ነጋሾች ዛሬም<br />

ያስፈልጉናል!<br />

‹‹መንግስት›› አሳልፎ<br />

የሰጠው ሉዓላዊነት<br />

12 5<br />

መሬት<br />

ያስቆረሱት<br />

የመለስና<br />

ተከታዮቹ እኩይ<br />

ስምምነቶች<br />

7<br />

ውህደት ወይስ ትብብር?<br />

3<br />

ውህደት በተናጠል በውጠ-ፓርቲ ትግል ፈተና ውስጥ የገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎች መሪዎች ከቀውስ ማምለጫ ወይም አጀንዳ<br />

ማስቀየሻ ሊሆን አይገባም፡፡ በተጨማሪም አንድ ፓርቲ ከገጠመው የገንዘብ እጥረት አሊያም የቢሮ ኪራይ ችግር ለመውጣት<br />

ዘው ብሎ የሚገባበት ጉዳይ መሆን አይኖርበትም፡፡ በሩጫ የሚደረግ ውህደት ውጤቱ ...<br />

ሰማያዊ ፓርቲ ‹የካቲት 12›ን በሰማዕታቱ<br />

ሐውልት በመገኘት ሊዘክር ነው<br />

አዲስ አበባ:- ሰማያዊ ፓርቲ<br />

በዳግም የጣሊያን ወረራ ወቅት<br />

በፋሽስት ግራዚያኒ ትዕዛዝ<br />

በአዲስ አበባ ብቻ ከ30,000 በላይ<br />

ንጹሃን በግፍ የተጨፈጨፉበትን<br />

የየካቲት 12 ሰማዕታት ቀን<br />

በተለያዩ ፕሮግራሞች ሊዘክር<br />

መሆኑን አስታወቀ፡፡<br />

የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት<br />

ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ተክለያሬድ<br />

እንዳስታወቁት፣ ሰማያዊ ፓርቲ<br />

የየካቲት 12 ሰማዕታት ቀንን<br />

ምክንያት በማድረግ በጽ/ቤቱ<br />

የፓናል ውይይት ያካሂዳል፤<br />

በተጨማሪም ስድስት ኪሎ<br />

በሚገኘው የሰማዕታት መታሰቢያ<br />

ሐውልት በዕለቱ በመገኘት<br />

ሰማዕታቱን የመዘከርና የአበባ<br />

ጉንጉን የማስቀመጥ ስነ-ስርዓት<br />

ያከናውናል፡፡<br />

እንደ አቶ ብርሃኑ ገለጻ፣<br />

ፓርቲው ፕሮግራሞችን<br />

ያዘጋጀበት ዋና ዓላማ ሰማዕታቱ<br />

የተሰውት ለሀገር አንድነትና<br />

ሉዓላዊነት ሲሉ ከመሆኑ ጋር<br />

በተገናኘ ሰማዕትነታቸውን<br />

ለትውልድ ለማስተላለፍ ነው፡፡<br />

ቀኑ በአብዛኛው በጥንታዊት<br />

ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች<br />

ብቻ የተወሰነ እየሆነ መምጣቱን<br />

ያወሱት አቶ ብርሃኑ፣<br />

የሰማዕታት ቀን በመላው ህዝብ<br />

ዘንድ የሚታወስ ታላቅ ቀን<br />

ወደ ገፅ 6 ይዞራል<br />

በጎንደር በተካሄደው ሰልፍ የተሳተፉ ወከባ<br />

እየደረሰባቸው መሆኑን አስታወቁ<br />

ሰማያዊ ፓርቲ ጥር 25 ቀን 2006<br />

ዓ.ም ‹የኢትዮጵያ መንግስት መሬት<br />

በድብቅ ለሱዳን አሳልፎ ለመስጠት<br />

እየተዘጋጀ መሆኑን› ተከትሎ<br />

የጠራውን ሰላማዊ የተቃውሞ<br />

ሰልፍ ያስተባበሩና በሰልፉ የተሳተፉ<br />

ወጣቶች ከሰልፉ በኋላም በደህንነት<br />

አካላት ወከባ እየደረሰባቸው መሆኑን<br />

ለነገረ-ኢትዮጵያ አስታውቀዋል፡፡<br />

በሰልፉ ወቅት ህዝብ ወደ ሰልፉ<br />

እንዳይቀላቀል ከመከልከል ባለፈ ፎቶ<br />

ግራፍ በማንሳትና ክትትል በማድረግ<br />

ሲያስፈራሩ የዋሉት የደህንነት አባላት<br />

ሰልፉ ከተጠናቀቀ በኋላ የተሳታፊ<br />

ወጣቶችን የቀበሌ መታወቂያ<br />

የቀሟቸው ሲሆን ወጣቶቹ ጥር<br />

26 መታወቂያቸውን ለመቀበል<br />

ወደ ቀበሌ ባቀኑበት ወቅትም<br />

በድጋሚ በመንግስት ላይ የተጠራ<br />

ሰልፍ እንዳይሳተፉ ማስፈራሪያ<br />

እንደደረሰባቸው ገልጸዋል፡፡<br />

በተመሳሳይ በጎንደር ሰልፉን<br />

ወደ ገፅ 6 ይዞራል<br />

መመረጥ በሌላው<br />

ድክመት<br />

ኢህአዴግ ተሸንፏል!<br />

(የጉዞ ማስታወሻ)<br />

13<br />

ሳይሆን በራስ ጥንካሬ<br />

16


ነገረ-ኢትዮጵያ ቅፅ 1 ቁጥር 2 የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. 2<br />

ርዕሰ አንቀጽ<br />

ስለ ሀገርና ወገን የሚታገሉትን ማዋከቡ ይቁም!<br />

ከዚህ በፊት በተለያዩ ጊዜያት ለሀገርና ለወገን<br />

ተቆርቁረው ጥቅማችንን ለማስጠበቅና<br />

ድምጻችንን ለማሰማት በተነሱ ወገኖች ላይ<br />

ከመንግስት የተሰጠው ምላሽ ያልተጠበቀ<br />

እንደነበርና ይህንንም በተለያዬ ጊዜ ብዙዎች<br />

በአገኙት አጋጣሚ ሁሉ መግለጻቸው ይታወቃል፡፡<br />

በእርግጥም በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያገባኛል ብሎ የመሰለውንና<br />

ለሀገር ይጠቅማል ያለውን አቋም በአደባባይ በሚገልጽ<br />

ማንኛውም አካል ላይ የተወሰደው እና እየተወሰደ ያለው<br />

እርምጃ አደናጋሪም አሳፋሪም ነበር፤ ነውም፡፡<br />

ለአብነትም ሰማያዊ ፓርቲ በ2005 ዓ.ም ጣሊያኖች<br />

በወገኖቻችን ላይ ከፍተኛ በደል የፈጸመውን ሮዶልፍ<br />

ግራዚያኒ በትውልድ ከተማው ‹የጀግና› ሐውልት በማቆም<br />

ዕውቅና መስጠታቸውን በመቃወም ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ<br />

በአዲስ አበባ መጥራቱ የሚታወስ ነው፡፡ ሆኖም ግን መንግስት<br />

ከፋሽስቱ ግራዚያኒ ታሪክ ጎን የቆመ በሚያስመስለው መልኩ<br />

ለተቃውሞ ሰልፍ የወጡትን ሰዎች ለቃቅሞ አስሯቸው ነበር፡<br />

፡ ድብደባና እንግልትም አድርሶባቸዋል፡፡<br />

እንዲሁ በሌላ ጊዜ የሳውዲ አረቢያ መንግስት እንጀራ<br />

ፍለጋ ከሀገራቸው የተሰደዱትን ኢትዮጵያዊያን በአስቸኳይ<br />

ሳውዲን ለቀው እንዲወጡ ማድረጉንና ሂደቱም ሰብዓዊነት<br />

በጎደለው ሁኔታ መከናወኑን በመቃወም በዚህ በሀገር ቤት<br />

ስለ ወገኖቻቸው እንግልት ጥብቅና በመቆም ተቃውሞ ባሰሙ<br />

የሰማያዊ ፓርቲ አባላት እና መላ ሀገርና ወገንን ብለው ሰልፍ<br />

የወጡ ዜጎቻችንን በአዲስ አበባ የሳወዲ ኤምባሲ አካባቢ<br />

መንግስት የወሰደባቸው የድብደባና የእንግልት እርምጃ<br />

የሚያሳፍር ሆኖ አልፏል፡፡<br />

ይህም ብቻ ሳይሆን አንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ<br />

(አንድነት) የሚሊዮኖች ድምጽ ለፍትህና ለነጻነት በሚል<br />

መርህ ፀረ-ሽብር ህጉ አፋኝና የማጥቂያ መሳሪያ ነው፣<br />

ስለዚህም መሻሻል አሊያም መሰረዝ ይገባዋል ብሎ የድጋፍ<br />

ፊርማ በሚያሰባስብበት ወቅት በአባላቱ ላይ የተለያዩ<br />

እንግልቶች ሲፈጸምባቸው እንደነበር በተደጋጋሚ ገልጾዋል፡፡<br />

በተጨማሪም የፖለቲካ እና የህሊና እስረኞች ይፈቱ ብለው<br />

በተለያየ መልኩ ህጋዊና ሰላማዊ ጥያቄ ባነሱና ለዚህም<br />

ተግባራዊነት በተንቀሳቀሱ ሀገርና ወገን ወዳዶች ላይ<br />

የሚደርሰው ጫና አሌ የማይባል ነው፡፡<br />

ይህ ሁሉ እንዳለ ሆኖ ደግሞ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ሰማያዊ<br />

ፓርቲ የኢትዮ-ሱዳን የድንበር መሬትን አስመልክቶ ያለው<br />

የመንግስት አካሄድ ግልጽና ተጠያቂነት የሰፈነበት መሆን<br />

እንደሚገባውና ሂደቱንም ዜጎች በየጊዜው እንዲያውቁ<br />

እንዲህም ተብሏል<br />

‹‹መኳንንቶች ሲሻሩ ህዝብ ይሆናሉ፡፡››<br />

አለቃ ዘነብ፣ የዳግማዊ አጼ ቴዎድሮስ ጸሐፊ ትዕዛዝ፤<br />

‹‹ሀገር የጋራ ነው፤ ሀይማኖት የግል ነው፡፡››<br />

ቀዳማዊ አጼ ኃ/ስላሴ፤<br />

መደረግ እንዳለበት በተለያየ መንገድ መጠየቁን ተከትሎ፣<br />

በአባላቱ ላይ ሰፊ የእመቃና የእስር ዘመቻ ተክፍቶባቸው<br />

አይተናል፡፡ ፓርቲው የድንበር መሬቱን ጉዳይ አስመልክቶ<br />

በጎንደር ከተማ ባካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ በተሳተፉ<br />

ሀገር ወዳድ ዜጎችና በፓርቲው አባላት ላይ የተወሰደው<br />

የማሳደድ እርምጃ ዛሬም እንደትናንቱ አሳፋሪነቱ ጎልቶ<br />

ታይቷል፡፡ ገና ሰልፉን በተመለከተ ለከተማዋ ህዝብ የቅስቀሳ<br />

ስራ በወጡ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎቹ ላይ የተጀመረው<br />

ግልጽ የማደናቀፍ ስራ እስከ ሰልፉ ማጠናቀቂያ ቀን ድረስ<br />

የቀጠለ እንደነበር ለመመልከት ችለናል፡፡<br />

ማንም ሰው በቀላሉ ሊረዳው እንደሚችለው በሰላማዊ<br />

የተቃውሞ ሰልፉ ላይ የተነሳው ጉዳይ የሀገር ጉዳይ ነው፡፡<br />

ቢሆን ቢሆን በሀገር ጉዳይ ላይ የፖለቲካ ልዩነታችን ተወግዶ<br />

ወይም ለጊዜው ልዩነቱን ወደ ጎን ገፍተን በአንድነት ብንቆም<br />

እሰየው ነበር፡፡ በዚህም የኢህአዴግ አባላትና ደጋፊዎቻቸው<br />

ሳይቀር በበላይ አለቃዎቻቸው ዘንድ በስውር እየተካሄደ<br />

ነው ስለሚባለው የሀገርን ጥቅም አሳልፎ የመስጠት እኩይ<br />

ተግባር ላይ ግልጽነት እንዲፈጠርና የህዝብ ይሁንታን በተጋፋ<br />

መልኩ እንዳይካሄድ ለመጠየቅ ሰማያዊ ፓርቲ የተጠራውን<br />

የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ በተቀላቀሉ ነበር፡፡<br />

ይህ ካልሆነ ግን ስለሀገር ብለው ድምጻቸውን ከፍ አድርገው<br />

በሚያሰሙ ሰላማዊ ኢትዮጵያዊያን ላይ ያልተገባና ህገ-ወጥ<br />

ተግባር መፈጸምና ከመሬት ቆራሾች ጋር ማበር አሊያም<br />

በዝምታ ማለፍ ነገ በህግ ዛሬ በህሊና ከመጠየቅ እንደማያድን<br />

ልብ ማለት ይገባል፡፡<br />

ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ የማካሄድም ሆነ በተደራጀ<br />

መልኩ የተለያዩ ጥያቄዎችን የማሰማት እንዲሁም ሀሳብን<br />

በነጻነት የማራመድ መብት በህገ-መንግስቱ ተደንግጎ እያለ<br />

በማናለብኝነት ህግን ጥሶ ዜጎችን ማንገላታት ከመንግስት<br />

ማናቸውም አካላት ፈጽሞ የማይጠበቅ ድርጊት መሆኑን<br />

ደጋግመን ማስታወስ እንወዳለን፡፡ አሁን መንግስት የማዋከብና<br />

የማሳደድ እርምጃ እየወሰደባቸው ያሉ አያሌ ኢትዮጵያዊያን<br />

እያነሷቸው ያሉት ጉዳዮች ተራ የፖለቲካ ፍጆታ ከማጋበስ<br />

ጋር የማይገናኙ፣ በአንጻሩ ግን የሀገርና የህዝብ ተቆርቋሪነትን<br />

የሚያሳዩ እንቅስቃሴዎች እንደሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ስለ ሀገርና<br />

ወገን የሚታገሉትን መሸለም እንጂ ማዋከብ የማይገባና<br />

ኢ-ዴሞክራሲያዊነት ነው፡፡<br />

በእርግጥም ከህዝብና ከሀገር ጥቅም ጋር ተጋጭቶ ዜጎችን<br />

ማሳደድ አምባገነንነትና ግዴለሽነት ነው፡፡ ስለሆነም እንዲህ<br />

አይነቱ የመንግስት አካሄድ ሀገር ያለ ተቆርቋሪና ሃይ ባይ<br />

እንድትቀርና ዜጎች በሀገራቸው እና በወገኖቻቸው ላይ<br />

በሚደርስ ማናቸውም አይነት ጥቃት ግዴለሽ እንዲሆኑ<br />

የሚገፋ ኃላፊነት የጎደለው ድርጊት በመሆኑ በአስቸኳይ<br />

ሊቆም ይገባዋል እንላለን፡፡<br />

‹‹ከጠላትህ ጋር ሰላም ለመፍጠር ከፈለክ፣ ከጠላትህ ጋር መስራት ይኖርብሃል፤ ይህንን ጊዜ አጋርህ ይሆናል፡፡››<br />

ኔልሰን ማንዴላ፤<br />

‹‹ከትልቅ ወይም ከትንሽ መወለድ ሙያ አይደለም፤ ራስን ለታላቅ ታሪክ መውለድ ግን ሙያ ነው፡፡››<br />

ዳግማዊ አጤ ምኒልክ (እምዬ)፤<br />

‹‹እኛ ኢትዮጵያዊያን ሁለት ቃል አንወድም፡፡ ለወዳጅነት የፈለጉኝን እፈልጋቸዋለሁ፤ እንዲያቃልሉኝ ግን ፈጽሞ አልፈቅድም፡<br />

፡››<br />

ሻምበል አብዲሳ አጋ፣ ስመጥር አርበኛ፤<br />

አንደኛ ዓመት ቅጽ 1. ቁጥር 2<br />

ነገረ-ኢትዮጵያ ጋዜጣ ጥር 2006 ዓ.ም<br />

ተመሰረተች፡፡ ነገረ-ኢትዮጵያ በሰማያዊ<br />

ፓርቲ አሳታሚነት የምትታተም<br />

ፖለቲካዊ፣ ወቅታዊ፣ ማህበራዊና<br />

ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን የምትዳስስ<br />

በየሳምንቱ አርብ የምትወጣ ጋዜጣ ናት፡፡<br />

ጋዜጣዋ ሚዛናዊና ነጻ ሆና የማገልገል<br />

መርህ አላት፤ ማንኛውም ሀሳብ በነጻነት<br />

የሚስተናገድባትና የሚንሸራሸርባት<br />

እንድትሆን እንፈልጋለን፡፡ ገዥው<br />

ፓርቲም ቢሆን አቋሙንና ፖሊሲውን<br />

ለመግለጽ ቢፈልግ የሰፊ ሚዲያ ባለቤት<br />

ነው ብለን ዕድሉን አንነፍገውም፤ በራችን<br />

ለሁሉም ክፍት ነው፡፡<br />

የአሳታሚ አድራሻ:- የካ ክ/ከተማ ቀበሌ 09/10<br />

ቤት ቁ.460<br />

E-mail:- info@semayawiparty.org<br />

P.O.Box: 180298<br />

ዋና አዘጋጅ<br />

ጌታቸው ሺፈራው<br />

የካ ክ/ከተማ ቀበሌ 01/02<br />

ቤት ቁ. 07/859/14<br />

E-mail:-gecholink@gmail.com<br />

ስልክ ቁጥር:- 09-10-45-99-32<br />

ምክትል ዋና አዘጋጅ<br />

በላይ ማናዬ<br />

የካ ክ/ከተማ ቀበሌ 01/02<br />

ቤት ቁ.099<br />

E-mail:- belaymb@gmail.com<br />

ስልክ ቁጥር:-09-20-19-09-72<br />

አምደኞች<br />

ፕ/ር አለማየሁ ገ/ማርያም<br />

ታዴዎስ ታንቱ<br />

ታምራት ታረቀኝ<br />

አፈወርቅ በደዊ<br />

እያስፔድ ተስፋዬ


3 የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2 ነገረ-ኢትዮጵያ<br />

ልብ አድርጉ<br />

ውህደት ወይስ ትብብር?<br />

በላይ ማናዬ<br />

ሀገር አቀፉ ምርጫ 2007 እየደረሰ ነው፤<br />

ምርጫን ተከትሎ የሚስተዋለው የፖለቲካ<br />

ግለትም በትንሹም ቢሆን ከወዲሁ ለብ<br />

ማለት የጀመረ ይመስላል፤ የት መሽገው<br />

እንደከረሙ ጠፍተውብን የነበሩ የፖለቲካ<br />

ፓርቲዎችም አንገታቸውን ብቅ ለማድረግ<br />

እየሞከሩ እንደሆነ መታዘብ ይቻላል፡፡<br />

በሀገራችን በፓርቲዎች የቁጥር ብዛት ረገድ<br />

ችግር የለም ማለት ይቻላል፡፡ ባለፈው<br />

ምርጫ 2002 እንኳ ወደ 90 የሚጠጉ<br />

ፓርቲዎች እንደነበሩ ይታወቃል፡፡<br />

በእርግጥም አሁን ላይ ኢትዮጵያ<br />

ውስጥ በቁጥር በጣም ብዙ የፖለቲካ<br />

ፓርቲዎች ተመዝግበው ይገኛሉ፤<br />

(በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚንቀሳቀሱትን<br />

ህብረ-ብሄር ፓርቲዎችም፣ ጎሳን ወይም<br />

አንድን ብሄረሰብ ማዕከል አድርገው<br />

የሚንቀሳቀሱትንም ማለቴ ነው)፡፡ ለአብነት<br />

በሁለተኛው ረድፍ ላይ ከሚመደቡት እንኳ<br />

ብናይ ለኦሮሞ ህዝብ እንታገላለን የሚሉት<br />

ከ10 በላይ፣ ጉራጌ 5፣ አርጎባ 3፣ ሀረሪ<br />

3 እና ሌሎችም በተመሳሳይ በርካቶች<br />

አሉ፡፡ በዚህም ከአጠቃላይ የፓርቲዎች<br />

ቁጥር አብላጫውን ሀገር አቀፍ ያልሆኑት<br />

ፓርቲዎች ይዘው ይገኛሉ፡፡ (የምዝገባ<br />

ፍቃዱን ወስዶ ዳናው የሚጠፋውም ጥቂት<br />

የሚባል አይደለም፡፡)<br />

ይህ ቁጥሩ የበዛ የፓርቲዎች እንቅስቃሴ<br />

ያለው ደግሞ በተቃውሞው ጎራ በኩል<br />

ነው፡፡ እንዲህ አይነቱ የፓርቲዎች አካሄድ<br />

ማንን እንደሚጠቅም ሳይታለም የተፈታ<br />

ነው፡፡ በምርጫ ወቅት የህዝብን ድምጽ<br />

በመከፋፈል የትኛውም ተቃዋሚ ፓርቲ<br />

አብላጫ ድምጽ በቀላሉ እንዳያገኝ በማድረግ<br />

ለገዥው ፓርቲ በተዘዋዋሪ ይጠቅመዋል፡<br />

፡ ስለሆነም እንዲህ ባለ ወቅት ተቃዋሚ<br />

ፓርቲዎች በሁለት አማራጮች ላይ<br />

ይንጠለጠላሉ፤ አንድም በቁጥር የበዙትን<br />

ፓርቲዎች ወደ አንድ ኃይል ማምጣት<br />

ላይ፣ አሊያም በተናጠልም ቢሆን በሀገር<br />

አቀፍ ደረጃ ጎልቶ ለመውጣት የሚያስችልን<br />

አቅም ፈጥሮ ገዥው ፓርቲንም ሆነ<br />

ሌሎች ተወዳዳሪዎችን ተፎካክሮ ለማሸነፍ<br />

የሚያስችልን እንቅስቃሴ ማድረግ፡፡<br />

በተግባር እንቅስቃሴ ላይ ያሉትን የተለያዩ<br />

ፓርቲዎች ወደ አንድ ኃይል አምጥቶ<br />

ወደ ምርጫ መግባት በባለፉት የምርጫ<br />

ተሞክሮዎቻችን ላይ አይተናል፤ (ቅንጅትን<br />

በ97፣ መድረክን በ2002 መጥቀስ ይቻላል፡፡<br />

) ያለፉት ሂደቶችና ተሞክሮዎች የራሳቸው<br />

ጥንካሬና ድክመት እንደነበረባቸው መካድ<br />

አይቻልም፡፡ ያም ሆነ ይህ ግን አሁን<br />

ሌላ የታሪክ ምዕራፍ ላይ እንገኛለን፡<br />

፡ ቀደም ብዬ እንደጠቀስኩት ምርጫ<br />

2007 እየደረሰ ነው፡፡ ስለሆነም አሁን<br />

ፓርቲዎች የበለጠ ለስራ የሚነሱበት ጊዜ<br />

ነው፤ በተናጠልም፣ በትብብርም፡፡ ከዚህ<br />

ጋር ተያይዞ በዚህ ሰሞን ስለ ፓርቲዎች<br />

ውህደትም የሚያነሱት በዝተዋል፡፡ ይህን<br />

የውህደት ጉዳይ እንደሚከተለው ለማየት<br />

እንሞከራለን፡፡<br />

ውህደት እንዴት?<br />

በአጭሩ ውህደት አንድ መሆን ማለት<br />

ነው፡፡ ከውህደት በፊት ያለው የተናጠል<br />

ህጋዊ ህልውና አክትሞ አዲስ ፓርቲ<br />

በአንድ ላይ መመስረት ነው ውህደት፡<br />

፡ አንድ ለመሆን ደግሞ፣ አንድ ለመሆን<br />

የሚያስችሉ ሁኔታዎች መኖር አለባቸው፡<br />

፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለመዋህድ የፖለቲካ<br />

ፕሮግራማቸው መመሳሰልና መቀራረብ<br />

ይኖርበታል፡፡ ከዚህም በላይ ግን ፓርቲዎቹ<br />

ለመዋህድ ፍላጎት ማሳየት የግድ ነው፤<br />

በውህደቱ ሂደትና ከውህደት በኋላ<br />

ስለሚኖረው እንቅስቃሴም የተሻለ መስራት<br />

እንደሚችሉ ሊያምኑበት ይገባል፡፡ በዚህም<br />

ማን ከማን ጋር መዋህድ እንደሚችል<br />

ካላቸው የፖለቲካ ፕሮግራም፣ የውህደት<br />

ፍላጎትና በመዋህዳቸው ሊያመጡት<br />

የሚችሉትን ውጤት ገምግመው፣ ወይ<br />

ወደ ውህደት ይገባሉ አሊያም በራሳቸው<br />

መስመር ጠንክረው ለመስራት ውሳኔ<br />

ያስተላልፋሉ፡፡<br />

ከሰሞኑ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት<br />

ድርጅት (መኢአድ) እና አንድነት<br />

ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት)<br />

በአስቸኳይ ለመዋህድ እየሰሩ እንደሆነ<br />

ገልጸዋል፡፡ ፓርቲዎቹ ጥር 25 ቀን 2006<br />

ዓ.ም መአህድ/መኢአድ የተመሰረተበትን<br />

22ኛ አመት በዓል በጽ/ቤቱ ባከበረበት ወቅት<br />

እንደገለጹት፣ ሁለቱ ፓርቲዎች በፍጥነት<br />

ወደ ውህደት ለመምጣት መወሰናቸውን<br />

በይፋ በመሪዎቻቸው በኩል ግልጽ<br />

አድርገዋል፡፡ የመኢአድ ፓርቲ ፕሬዚዳንት<br />

አቶ አበባው መሐሪ ፓርቲያቸው መኢአድ<br />

ከአንድነት ፓርቲ ጋር መዋሃድ ፍላጎቱ<br />

መሆኑን ተናግረዋል፡፡<br />

በተመሳሳይ በቀድሞ ፓርቲያቸው 22ኛ<br />

አመት ክብረ በዓል ላይ የተገኙት የአንድነት<br />

ፓርቲ ፕሬዚዳንት ኢ/ር ግዛቸው ሺፈራው<br />

በበኩላቸው ፓርቲያቸው ከመኢአድ ጋር<br />

መዋሃድ ፍላጎቱ መሆኑን ገልጸው፣<br />

በ15 ቀናት ውስጥ ውህደቱ እውን ሊሆን<br />

እንደሚችልም ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡<br />

ፓርቲዎቹ ይህን ይበሉ እንጂ (በዕለቱ<br />

በነበረው የመድረክ ሞቅታ እንዳይሆን<br />

እሰጋለሁ) በዚህ ፍጥነት ሊዋሀዱ<br />

የሚችሉበት ሁኔታ ውስጥ እንዳልሆኑ<br />

ጠቋሚ ምልክቶች መኖራቸውን መካድ<br />

አይቻልም፡፡<br />

ውህደት መቼ?<br />

ውህደት ምርጫ ስለቀረበ የሚከናወን<br />

የይድረስ ይድረስ ስራ እንዳልሆነ እሙን<br />

ነው፡፡ በተቃራኒው ግን በሀገራችን የነበሩ፤<br />

ያሉ ፓርቲዎች ውህደት የሚታያቸው<br />

ምርጫ ሲቃረብ መሆኑ አለመታደል ነው፡፡<br />

አንዳንዶቹ ሂደቱን ቀድመው ቢጀምሩትም<br />

ሲያጓትቱ ሲያጓትቱ እስከ ምርጫ መቃረቢያ<br />

ድረስ ያደርሱታል፡፡ የመኢአድና የአንድነት<br />

ውህደት እውን ቢሆን የሚወድ ብዙ ነው፡<br />

፡ ዳሩ ግን ውህደቱ መሆን የነበረበት<br />

(በእውነት ኢ/ር ግዛቸው እንዳሉት በ15<br />

ቀናት ውስጥ የሚከናወን ከሆነ ወይም<br />

ቢሆን ኖሮ) እንዲህ በሩጫ አሁን ላይ<br />

አይደለም፤ (በ15 ቀናት ውስጥ የሚደረግ<br />

ውህደት የፖለቲካ ፓርቲዎች ሳይሆን….)፡<br />

፡ ይህ ውህደት ከምርጫ 2002 ማግስት<br />

ቢሆን በተገባ ነበር፡፡<br />

ውህደት በተናጠል በውጠ-ፓርቲ ትግል<br />

ፈተና ውስጥ የገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎች<br />

መሪዎች ከቀውስ ማምለጫ ወይም አጀንዳ<br />

ማስቀየሻ ሊሆን አይገባም፡፡ በተጨማሪም<br />

አንድ ፓርቲ ከገጠመው የገንዘብ እጥረት<br />

አሊያም የቢሮ ኪራይ ችግር ለመውጣት<br />

ዘው ብሎ የሚገባበት ጉዳይ መሆን<br />

አይኖርበትም፡፡ በሩጫ የሚደረግ ውህደት<br />

ውጤቱ ምን ሊሆን እንደሚችል ለማንም<br />

የተሰወረ አይሆንም፡፡<br />

እናም ውህደት በቂ ጊዜ ወስዶ መጤን<br />

ያለበት ትልቅ የፖለቲካ ስራ ነው፡፡<br />

እርግጥ ነው ህዝቡ ፓርቲዎቹ እንዲዋህዱ<br />

ይፈልጋል፡፡ ከዚህ በላይ ግን አብዛኛው<br />

ህዝብ ፓርቲዎች ተዋህደው እንዲዘልቁና<br />

ለውጥ እንዲያመጡ እንደሚሻ ግልጽ ነው፡<br />

፡ ለዚህ ደግሞ ከጅምሩ የሰከነ የውህደት<br />

ሂደት መኖሩ ግድ ይላል፡፡<br />

የውህደት ፈተናዎች<br />

የፖለቲካ ፓርቲዎችን ወደ ውህደት<br />

ማምጣት፣ ከውህደት በኋላም ተስማምቶ<br />

መቀጠል ትልቅ ፈተና አለው፡፡ በተለይም<br />

እንዲህ በአጭር ጊዜ ውህደትን እናመጣለን<br />

ብለው ሰርጋቸውን ከሚያፋጥኑ ሰዎች<br />

ወደ ፊት የሚሆነውን በስጋት መመልከት<br />

ግርምትን የሚፈጥር ጉዳይ አይሆንም፡<br />

፡ በተዋሃጆቹም በኩል የእነቶሎ ቶሎ<br />

ቤት…እንዳይሆን መጠንቀቁ የሚበጅ ነው፡<br />

፡ ምርጫ ስለደረሰ ብቻ በፍጥነት ውህደትን<br />

ማከናወን ሊኖረው የሚችለውን ፈተና<br />

ሊያስረሳን አይገባም፡፡ ሰርገኛ መጣ በርበሬ<br />

ቀንጥስ እንዳይሆን መጠንቀቁ የብልሆች<br />

ምርጫ ነው፡፡<br />

በእርግጥም ውህደት የጥቂት ግለሰቦች<br />

ወይም የፖለቲካ ፓርቲዎች መሪዎች<br />

ፍላጎትና ተግባር ብቻ አይደለም፡፡ ከዚያ<br />

ይልቅ የሚዋሃዱት ፓርቲዎች አባላት<br />

(ጠቅላላ ጉባኤ በሚገባ ተወያይቶበት<br />

ውሳኔ ማሳለፍን ይጠይቃል፤) በየደረጃው<br />

ሰፊ ጊዜ ሰጥተው ጉዳዩን ሊወያዩበትና<br />

ሊያጤኑት ግድ ይላል፡፡ ይህን ለማድረግ<br />

የሚያስችላቸው ጊዜም ሊሰጣቸው<br />

እንደሚገባ እሙን ነው፡፡ በሌላ አነጋገር<br />

ውህደቱ ከጅምሩ እሰከ ፍጻሜው አባላትንም<br />

ማዕከል ያደረገ መሆን ይኖርበታል፡፡ ይህ<br />

ሳይሆን ቀርቶ ውህደቱ የጥቂቶች ስራ<br />

ከሆነ፣ አንድም ውህደቱ እውን አይሆንም፣<br />

እውን ከሆነም ዘላቂነቱ አጠራጣሪ ከመሆን<br />

አይድንም፡፡<br />

የውህድ ፓርቲው መሪ<br />

ሌላው ፈተና ውህደቱ ከተፈጸመ በኋላ<br />

የውህድ ፓርቲው (አዲሱ ፓርቲ) መሪ<br />

ማን ይሁን የሚለው ጉዳይ ነው፡፡ የዚህ<br />

ፈተና ምንጭ ውህደቱን ከመሰረቱት<br />

ፓርቲዎች ወገን ሁሉም የቀድሞ ፓርቲው<br />

መሪ፣ የአዲሱ ውህድ ፓርቲ መሪም<br />

ሆኖ እንዲዘልቅለትና ቡድናዊ ጥቅሙን<br />

እንዲያስከብርለት የመፈለጉ ጫና ነው፡፡<br />

በዚህም ሁሉም የየራሱን የቀደመ የትግል<br />

ታሪክና የአደረጃጀት ስፋት እያነሳ ስልጣኑ<br />

እንደሚገባው መሞገቱ ስለማይቀር ነው፡፡<br />

እንዲህ አይነቱ ጉዳይ ደግሞ ማን የተሻለ<br />

መምራት ይችላል ሳይሆን፣ ማን የውህድ<br />

ፓርቲው መሪነት ይገባዋል ወደሚል<br />

ሰንካላ ምክንያት ይገፋናል፡፡<br />

በተመሳሳይ ውህደቱ ከሚከናወንበት<br />

ወቅት አንስቶ፣ ውህደቱ ሊያመጣባቸው<br />

የሚችለውን ከጥቅማ ጥቅምና ስልጣን<br />

ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን ማጣት በማጤን<br />

ቅሬታ የሚሰማቸው ግለሰቦችም ሌላኛዎቹ<br />

ፈተናዎች መሆናቸው የማይቀር ነው፡<br />

፡ ከሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ<br />

ፓርቲዎች ወደ አንድ ሲመጡ፣ ቀድሞ<br />

በተናጠል የነበረውን የስራ አስፈጻሚ ያህል<br />

ቁጥር ሊያካትት አይችልም፡፡ በዚህ ጊዜ<br />

ተቀናሾች መኖራቸው ግድ ነው፤ እዚህ<br />

ጋር የሚነሳው ጉዳይ የመቀነሻ መስፈርቶቹ<br />

ናቸው፡፡ ያም ሆነ ይህ በአዲሱ ፓርቲ<br />

የሚደረገው የስልጣን ሽግሽግ በውህደት<br />

ወቅትና ከውህደት በኋላ ከሚገጥሙ<br />

ፈተናዎች መካከል መሆኑ የማይቀር ነው፡፡<br />

በሌላ በኩል ደግሞ ከውህደት በኋላም፣<br />

ከግል የስልጣን ጥማቸው ጋር በተገናኘ<br />

በስልጣን ተዋረድ ውስጥ ሁለተኛ ሰው<br />

ሆነው ለመስራት የማይፈልጉና ሁሌም ከኔ<br />

በላይ ላሳር ባዮች አይጠፉም፡፡ በዚህም፣<br />

እንዲህ አይነት ግለሰቦች አንዴ ከፖለቲካ<br />

ሲርቁ፣ ሌላ ጊዜ ያችኑ የመሪነት ቦታ<br />

ሲሰጣቸው ወደ መድረኩ ብቅ የሚሉ<br />

ናቸው፡፡ የእነዚህ ግለሰቦች የስልጣን ጥም<br />

የመሪነት ቦታ የነፈጋቸውን ፓርቲ ለቅቀው<br />

ወደ ሌላ ፓርቲ እስከመሄድ የሚያደርሳቸው<br />

ነው፡፡ ስለሆነም እነዚህን መሰል ግለሰቦች<br />

ዛሬ ስለውህደት አብዝተው ቢሰብኩም<br />

ያችኑ የመሪነት ቦታ የሚያሳጣቸው ጉዳይ<br />

ሲመጣ ሲያቀነቅኑት የነበረውን ዓላማ<br />

ረስተው የውህደቱ እንቅፋት ከመሆን<br />

ላይመለሱ ይችላሉ፡፡<br />

ደካማ የቀደመ የፖለቲካ ፓርቲዎች ውህደት<br />

ተሞክሮ ያለን ከመሆኑ ጋር ተያይዞ<br />

(በቅንጅቱ መፍረስ የተፈጠረ መንፈስን<br />

ማስታወስ ይበቃል፤) በህዝቡ ዘንድ ያለው<br />

ተስፋ የመቁረጥ ስሜትም እንደ አንድ ሌላ<br />

ፈተና ሊወሰድ የሚችል ነው፡፡ ፈጥኖ ወደ<br />

ውህደት የመግባትን ያህል ከውህደት በኋላ<br />

ተስማምቶ የመቀጠሉ ፈተናም ከባድ ነው፡<br />

፡ ስለሆነም መዋሃዱ መልካም ሆኖ፣ ነገር<br />

ግን አሁንም ከውህደት በፊት መሰራት<br />

ያለባቸው የቤት ስራዎች በጊዜ ከተከናወኑ<br />

በኋላ ቢሆን የተሻለ ውጤት ይኖረዋል፡፡<br />

አሁን ላይ ውህደት ወይስ ትብብር?<br />

ቀደም ብሎ እንደተጠቀሰው ውህደትን<br />

ለማከናወን የተዋሃጅ ፓርቲዎች ፕሮግራም<br />

ተመሳሳይ ወይም ተቀራራቢ መሆን<br />

ይኖርበታል፡፡ በዚህም አንድ ፓርቲ ከሌላው<br />

ጋር ለመዋሃድ መሰሉን ወይም ቢጤውን<br />

መፈለግ ግድ ይለዋል፤ ይህም የሚሆነው<br />

የሌላኛው ፓርቲ ፍላጎት ሲጨመርበት<br />

ነው፡፡ እናም ውህደት አግላይ ጎንም<br />

እንዳለው መገንዘብ ይቻላል፡፡ ለአብነትም<br />

የመኢአድ ሊቀመንበር አቶ አበባው መሐሪ<br />

የፓርቲያቸውን አቋም በሚከተለው መልኩ<br />

ገልጸውታል፡፡<br />

‹‹መኢአድ በኢትዮጵያ አንድነት ላይ<br />

ከማያምኑ የብሄር (የጎሳ) የፖለቲካ<br />

ድርጅቶች፣ በኢትዮጵያ አንድነት ላይ<br />

አልደራደርም በማለት፣ በውህደት ደረጃ<br />

አብሮ ለመስራት እቸገራለሁ የሚለው በቂ<br />

ምክንያት ስላለው ነው፡፡›› (አንድነት ከአረና<br />

ትግራይ ጋር ለመዋሀድ ንግግር መጀመሩ<br />

የሚታወቅ ነው፡፡ ታዲያ መኢአድ በአንድነት<br />

በኩል የመጣውን አረና ትግራይን እንዴት<br />

ሊያደርገው ይሆን?) ያም ሆነ ይህ ጉዳዩ<br />

የሚያሳየን የውህደትን አግላይነት ነው፡፡<br />

ከመኢአድ አቋም ለመረዳት እንደሚቻለው<br />

ፓርቲው ለውህደት በሩን የሚከፍተው<br />

ጠንካራ ጥበቃዎችን ከፊት አቁሞ ነው፡<br />

፡ ስለሆነም ውህደት የራሱ ጠንካራ ጎኖች<br />

እንዳሉት ሆኖ፣ እንደ አሸን የፈሉትን<br />

የፖለቲካ ድርጅቶች በጋራ አስተባብሮ ወደ<br />

አንድ የማምጣቱ ነገር ውስን መሆኑን<br />

ነው፡፡<br />

በአብዛኛው የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች<br />

የጋራ የሆነ የሚታገሉት ኃይል አላቸው፤<br />

እሱም ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ ነው፡<br />

፡ እነዚህ ፓርቲዎች የየራሳቸው የተለያየ<br />

ዓላማን አንግበው የሚንቀሳቀሱ ቢሆኑም<br />

የወል ጉዳይ እስካላቸው ድረስ ግን መተባበር<br />

ወደ ገፅ 6 ይዞራል


ነገረ-ኢትዮጵያ ቅፅ 1 ቁጥር 2 የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. 4<br />

ከዚህ በታች የቀረበው ጽሑፍ የሰማያዊ ፓርቲ ፕሬዚዳንት ኢ/ር ይልቃል<br />

ጌትነት ፓርቲያቸው ጥር 25 ቀን 2006 ዓ.ም በጎንደር ከተማ ባካሄደው<br />

ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ያደረጉት ንግግር ነው፡፡<br />

‹‹አገርን ከመቁረስ በላይ ምንም ነገር<br />

ሊመጣብን አይችልም››<br />

በዚህ ትውልድ እዚህ<br />

ደረጃ ላይ ባለ ነገር<br />

መነጋገራችን አሳፋሪና<br />

አዋራጅ ነው፡፡ ሰው<br />

ከአባቱ የተሻለ ነገር<br />

እየሰራ፣ የነበረውን<br />

እያሻሻለ፣ አገሩን<br />

እያሻሻለ መሄድ ሲገባው<br />

በአሁኑ ወቅት አገሩን እየቆረሰ የሚሸጥ<br />

ጉደኛ መንግስት መጥቶብናል፡፡ እንዲህ<br />

ያለውን ነገር በአንድ ላይ ቆመን፣<br />

ተባብረን፣ መልክ ካላስያዝነው በስተቀር<br />

አምባገነን ለስልጣኑ ሲል የማይሰጠው<br />

ነገር ስለሌለ፤ ከዚህ በኋላ በፍርሃት፣<br />

በመሸማቀቅ፣ ከስራዬ እሰናበታለሁ<br />

በሚል፣ አምስት ለአንድ ይህን<br />

ያደርገኛል እየተባለ የሚፈራ ከሆነ<br />

በአገር ላይም የማንኖርበት ደረጃ ላይ<br />

እንደርሳለን፡፡<br />

ስለዚህ እነሱ የሚሉትን ከሰማን<br />

ዘላለም ሊገዙን ይሞክራሉ፤ ክብራችን<br />

ጨምሮ ሁሉን ነገራችንን አሳልፈን<br />

እንድንሰጣቸው ይፈልጋሉ፤ ቅዳሜ<br />

(ጥር 24) ቀንና ሌሊቱን ሙሉ የእኛን<br />

ጓደኞች አስረዋቸዋል፡፡ ጥር 22ትም<br />

ከቀኑ አምስት ሰዓት እስከ ምሽቱ<br />

አስራ ሁለት ሰዓት አስረዋቸው፡፡ ነገር<br />

ግን የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና<br />

አባላት ከዓላማቸው፣በከሃሳባቸውና<br />

እውነት ይዘው ከተነሱበት መንገድ<br />

አንድም ፈቀቅ አይሉም፡፡ ምን ጊዜም<br />

ቢሆን የኢትዮጵያ ጉዳይ ትልቅ ስራ<br />

እያለ፣ የተለያየ የኑሮ ሁኔታ እያለ<br />

ሁሉንም ነገር ተቋቁመው የሰማያዊ<br />

ፓርቲ ወጣቶች ከረዕቡ ዕለት ጀምረው<br />

በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የደህንነቶችን<br />

ወከባ፣ ያለውን አፈና እየተቋቋሙ<br />

ለሰላማዊ ሰልፉ ስላበቁን በሰማያዊ<br />

ፓርቲ ስም ከልብ አመሰግናለሁ፡፡<br />

ለኢትዮጵያ ወጣቶች ሁሌም የምናገረው<br />

ነገር ቢኖር አምባገነን መንግስት<br />

ያስረኛል፣ ይህን ያደርገኛል፣ ከዚህ<br />

ስሄድ ይህኛው ነገር ይመጣብኛል<br />

ከተባለ ትግል ሊኖር እንደማይችል<br />

ነው፡፡ ትግል ከተባለ የሚመጣውን<br />

ሁሉ ዋጋ እየተከፈለ ነው፡፡ የቋረኛው<br />

ቴዎድሮስ ልጅ ስንሆን እኮ፤ እሱ<br />

ክብሬን አላስደፍርም ብሎ ሽጉጡን<br />

ጠጥቶ የተሰዋ ሰው አለ እያልን<br />

ነው በየ ዘፈኑ የምናነሳው፡፡ ታዲያ<br />

ይህንን ክብር የነበረው ሰው መሬቱና<br />

ዳር ድንበሩ ሲወሰድበት፣ ዝም ብሎ<br />

የሚያይ ከሆነ ይህ ትውልድ በታሪክ<br />

ይጠየቃል፡፡ የምንጠየቀው ደግሞ የዚህ<br />

ትውልድ አባላት ብቻ አይደለንም፡<br />

፡ እነዛን አጥንታቸውን ከስክሰው፣<br />

ደማቸውን አፍስሰው አገራችን<br />

ያቆዩዋትን ታሪክ ብኩርናም መሸጥ<br />

ነው፡፡ እነዚህን አባቶቻችንም መክዳት<br />

ነው፡፡ በዚህ ዘመን የእኛን ትውልድ<br />

አሳልፈን መስጠታችንም እራሳችን<br />

መክዳት ነው፡፡ የወደፊቱን ትውልድ<br />

ሃላፊነትም መካድ ነው፡፡ ስለዚህ አሁን<br />

እኛ የምናደርገው ለድንበራችን መከበር<br />

ጠንክረን ከሰራን የአባቶቻችን ታሪክ<br />

እናስጠብቃለን፡፡ የእኛንም የወደፊት<br />

ታሪክ እናስጠብቃለን፡፡ ወደፊት<br />

የሚመጡትን ልጆችም በሙሉ ልብ<br />

እንዲኖሩ እናደርጋለን፡፡<br />

አሁን ግን ዝም ብለን ይህን ሁሉ<br />

ነገር ካለፍን ስለ ቴዎድሮስ መዝፈን<br />

አይቻልም፤ ከዚህ በኋላ ስለ አጼ<br />

ዮሃንስ መዝፈን አይቻልም፡፡ መዝፈን<br />

የምንችለው የእነሱን ክብር የሚያስጠብቅ<br />

ትውልድ መሆን ከቻልን ብቻ ነው፡<br />

፡ ይህንን የማያደርግ ትውልድ ከሆነ<br />

አፋራም ትውልድ ነው፣ ብኩርናውን<br />

ሽጧል፣ አባቶቻችን አዋርዷል፣ራሱንም<br />

አዋርዷል፣ ቀጣዩ ትውልድም በእሱ<br />

ምክንያት አንገቱን ደፍቶ እንዲኖር<br />

አድርጓል ማለት ነው፡፡<br />

ስለዚህ ይህ የአገር ጉዳይ ቀላል ጉዳይ<br />

አይደለም፡፡ አባቶቻችን የደሙበት ነው፡<br />

፡ አጥንት የተከሰከሰበት ነው፡፡ ክብራችን<br />

ብለን ለነጻነት የቆምንበት ነው፡፡ ለዚህ<br />

የሚደረገው ትግል እንደማንኛውም<br />

ትግል በቀላሉ የሚታይ አይደለም፡<br />

፡ ለእኔ ዴሞክራሲና መልካም<br />

አስተዳደር ቅንጦት ነው፡፡ አገርን<br />

ከመቁረስ በላይ ግን ሌላ ምንም ነገር<br />

ሊመጣብን አይችልም፡፡ ይህንን ጉዳይ<br />

ዝም ብለን የምናይ ከሆነ አሁን ያለው<br />

የኢትዮጵያ ትውልድ በታሪክ ፊት<br />

እንዳፈረ ይኖራል፡፡ ስለሆነም ወገኖቼ!<br />

አምባገነኖች ይሄዳሉ፣ ትውልድ<br />

ይሄዳል፣ አገርና ህዝብ ግን ዘላለም<br />

ይኖራል፡፡ በዚህ ለዘላለም በሚኖር<br />

አገርና ህዝብ ክብራችን ጠብቀን መኖር<br />

አለብን፡፡<br />

የኢትዮጵያ ልጆች ሁሉ ለአፍሪካም<br />

ሆነ ለዓለም የነጻነት ምሳሌ ነን፡፡<br />

አባቶቻችን የነጻነት ምሳሌዎች ናቸው፡<br />

፡ እኛም በየትኛውም ዓለም ልባችንን<br />

ሞልተንና ቀና ብለን የምንሄደው<br />

አባቶቻችን በከፈሉት መስዕዋትነት<br />

ነው፡፡ ይህንን ብኩርናችንን፣<br />

ነጻነታችንን፣ ተምሳሌትነታችንን<br />

አሳልፈን እንዳንሰጥ የሚሆነውን ሁሉ<br />

በንቃት እንድንከታተል አሳስባለሁ፡<br />

፡ ስልጣን ላይ ያሉት ሰዎች ለአንድ<br />

ሰሞን ስልጣን፣ ለአንድ ሰሞን ገንዘብና<br />

ለሚያልፍ ነገር ብለው ይህን ሁሉ<br />

በደል ከመፈጸምና ራሳቸውን ከታሪክ<br />

ተጠያቂነት ጠብቀው፣ ቆም ብለው<br />

ጉዳዩን ሃላፊነት በተሞላበት መንገድ<br />

እንዲያዩትና ከህዝብ ጋር ግልጽ<br />

ውይይት አድርገው የህዝብን ታሪክና<br />

አንድነት ሳያናጉ የኢትዮጵያን ብሄራዊ<br />

ጥቅም አስከብረው ከማፈርና ከውርደት<br />

እንዲድኑ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ!!<br />

መመረጥ በሌላው ድክመት...<br />

አጠናክሮ የፕሮፓጋንዳ ብቻ ሳይሆን የተግባር<br />

ታጋይ ሆኖ ለመውጣት የሚያስችል ሥራ<br />

በየፓርዎቹ በተግባር መታየት መቻል አለበት፡<br />

፡ የፓርቲ መሪዎች ቢመረጡ በተሻለ ሀገር<br />

የመምራት አቅሙም እውቀቱም ያላቸው<br />

መሆኑን ፓርቲ ውስጥ በሚሰጡት አመራርና<br />

በሚያስመዘግቡት ለውጥ ማሳየት መቻል<br />

ይኖርባቸዋል፡፡<br />

በሕዝቡ የተባበሩ ጥያቄ በተለያዩ ግዜያት<br />

የተፈጠሩ መተባበሮች የእንቧይ ካብ እየሆኑ<br />

ወይ ኀብረት ሳናይ ወይ አንድና ሁለት ጠንካራ<br />

ፓርቲ ሳናይ 21 ዓመታትን ቆጠርን፡፡ ምርጫ<br />

2002 ያስተባበራቸው የምርጫ 97ን ውጤት<br />

መናዳቸው አስቆጭቶአቸው በምርጫ 2007<br />

የተሻለ ነገር ለመስራት የሚያስችል ዝግጅት<br />

ሊያደርጉ በሚገባቸው ወቅት ስለምርጫ<br />

እያሰቡ መሆናቸውን እንኳን የሚጠቁም ነገር<br />

አይታይም፡፡ ይህም በራስ ብቃት ተወዳዳሪ<br />

መሆንን ያለሙ አለመሆናቸውን ያሳያል፡፡<br />

የአመለካከት ጥራት፣ ድርጃታዊ ብቃት፣<br />

ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው አሰራር<br />

የውይይት ባህል የዳበረበት ዴሞክራሲያዊ<br />

አሰራር የሚስተዋልበት ጠንካራ የህዝብን<br />

ይሁንታ ያተረፈ ፓርቲ መፍጠር ብዙ ዋጋ<br />

የሚያስከፍል ከባድ ስራ ነው፡፡ የሌላውን<br />

ጉድለት እያወሩ የሕዝብን ብሶት እየነካኩ<br />

ለመመረጥ ማሰብ ግን ቀላል ግን ተፈላጊውን<br />

ውጤት የማያስገኝ መንገድ ነው፡፡ በመተባበር<br />

ካባ ተሸፍኖ መቅረብም እንዲሁ፡፡<br />

ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ በተዋቂ ግለሰብነት<br />

በመሰረቱትና ኋላም የአንድነት ሊቀመንበር<br />

በመሆናቸው በነበራቸው የመድረክ ተሳትፎ<br />

ከተገነዘቡት ተነስተው «….በአሁኑ ሁኔታ<br />

ከተጠቀሱት ድርጅቶች ለመዋሀድ በጣም ከባድ<br />

ነው ያስቸግራል፡፡ ወደ ውህደት ለመምጣት<br />

ብዙ ውይይቶች ብሎም አብሮ መስራ<br />

ያስፈልጋል፤ መተዋወቅ አለብን፡፡ የድሮው<br />

ቁስሎች መረሳት አለባቸው፡፡» (ኢትዮ ምህዳር<br />

ታህሣሥ 30/2006) በማለት የተናገሩት<br />

በተግባር ካዩት ተነስተውና እውነትነቱ<br />

የሚያጠያይቅ አይደለም፡፡ ስለሆነም በውህደት<br />

ካርድ ለመጫወት የሚያስቡ ፖለቲከኞች<br />

በርግጥ ለውጥ አልመው ለዛም የሚያበቃ<br />

ድርጅታዊ ብቃት ፈጥረው ሳይሆን በእድሜ<br />

ከ ገፅ 13 የዞረ<br />

ማራዘሚያነት ለመጠቀም ነውና ለመርጫ<br />

2007 የሚፈይደው የለም፡፡<br />

ስለሆነም በርግጥ ለለውጥ የሚታገሉና<br />

ተቀዋሚ እየተባሉ በዚህም የሚገኘውን<br />

እየቀማመሱ መኖርን የመረጡ ይለዩ፡፡<br />

የመጀመሪያዎቹ ሰላማዊ ትግል ያለምርጫ<br />

ምርጫ ያለብቃት እንደማይሳካ የለውጥ<br />

መገኛው መንገድም ምርጫ መሆኑን አምነው<br />

ምርጫ 2007 ከተበላሸ በህዝቡ ዘንድ ሊፈጠር<br />

የሚችለውን የመጨረሻ ተስፋ መቁረጥ<br />

ከወዲሁ ገምተው ሕዝብ ተስፋ በቆረጠበት<br />

ሀገር ሰላማዊ ትግል ፋይዳ እንደማይኖረውም<br />

ተገንዝበው ሌላ ሌላውን ጨዋታቸውን<br />

ሁሉ አቁመው በ2007 ምርጫ ውጤት<br />

ለማምጣት ምን እናድርግ የሚል ምክክር<br />

ሊጀምሩና በምርጫው ውጤት ለማስመዝገብ<br />

የሚያበቃቸውን አቅም በተናጠልም ሆነ<br />

በጋራ ለመገንባት መስራት ይጠበቅባቸዋል፡፡<br />

መመረጥ የሚቻለው የመራጩን ቀልብ መሳብ<br />

የሚችል ብቃት ላይ ሲገኙ ነውና፡፡<br />

ጊዜ ቆሞ አይጠብቅም ምርጫ 2007<br />

እየቀረበ ነው፡፡ ኢህአዴግ ለምርጫ መስራት<br />

የጀመረው 99.6 በመቶ ባሸነፈበት ምርጫ<br />

ማግስት ነው፡፡ ከተቃውሞው ሰፈር የሚሰማ<br />

ነገር የለም፣ ሕዝቡ ሁሉንም በትዝብትና<br />

በአረምሞ በዝምታ እያስተዋለ ነው፡፡ ለጽሁፌ<br />

ማሳረጊያነት ሎሬት ጸጋየ ገብረ መድህን<br />

ከምርጫ 97 በፊት የካቲት 1/97 ከታተመችው<br />

ጦቢያ መጽሔት ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስ<br />

ከተናገረው ልዋስ (አንቱ ያላልኩበት<br />

ምክንያት ለአንባቢያን ግልጽ ይመስለኛል፡፡)<br />

{የሕዝብን እውነት በልብ ሳይቋጥሩ ሕዝብ<br />

ግንባር ፊት መቆም እንደ ወያኔ ድፍረት<br />

ሕዝብን ማርከስ ነው፡፡ መተባበር ያቃተው<br />

‹ኀብረትና ቅንጅት› ደግሞ ሕዝብን<br />

ሊያስተባብር አይችልም፡፡ አለንልህ የሚሉት<br />

ፖለቲከኞች ርስ በርሳቸው ሲጠላለፉ እያየ<br />

ሕዝቡ በመራራ ትዝብት ያስተውላቸዋል፡፡<br />

አይቆስሉ ቁስለት ማለት የኢትዮጵያ ሕዝብ<br />

ቁስለት ነው፡፡ አይችሉ መቻል ማለትም<br />

የኢትዮጵያ ሕዝብ መቻል ነው፡፡ ‹‹በላይ እሳት<br />

በታች እሳት› እንደ ድፎ ዳቦ እየነደደ በፅናቱ<br />

ብቻ ሳይሆን ሕዝቡ በትእዝብቱም ቀድሞናል፡<br />

፡} ነፍሱን ይማረውና ሎሬት ዛሬ ቢኖር ምን<br />

ይል ነበር!


5 የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2 ነገረ-ኢትዮጵያ<br />

ፖለቲካ<br />

‹‹መንግስት›› አሳልፎ የሰጠው<br />

ሉዓላዊነት<br />

ጌታቸው ሺፈራው<br />

ለአንድ አገር ሉዓላዊነት ቁልፍ<br />

ከሚባሉት ጉዳዮች መካከል<br />

ወሰን ዋነኛው መመዘኛ ነው፡፡<br />

የወሰን/የድንበር ጉዳይ ድንበር<br />

ብቻ ሳይሆን ከድንበሩ ጋር<br />

ያለውን ታሪካዊ ሂደትም ይጨምራል፡<br />

፡ ለአንድ መንግስትና ትውልድ የቀደሙ<br />

አባቶች ያኖሩትን ድንበር የመቆጣጠርና<br />

መጠበቅ ታሪካዊ ግዴታቸው ነው፡፡<br />

የውጭ አሊያም ሌላ ሀይል የኖረውን<br />

የአገሪቱን ድንበር የሚደፍር አሊያም<br />

የሚያስቀይር ከሆነ የአገሪቱ ሉዓላዊነት<br />

አደጋ ውስጥ ወድቋል ማለት ነው፡<br />

፡ የአንዲት አገርና ህዝቧ ያለ ድንበር/<br />

ወሰን ሊኖር አይችልም፡፡ አገሪቱ ብቻዋን<br />

መሆን እንደማትችል ሁሉ ክብሯን፣<br />

ታሪኳን፣ የዕለት ተዕለት እንቅስቀቃሴዋ፣<br />

ደህንነቷ ላይ ድንበር ከፍተኛ አስተዋጽኦ<br />

ይኖረዋል፡፡<br />

የወሰን አለመከበር ወይንም ሌላ ችግር<br />

እኒህን ሁሉ ጉዳዮች የሚያዛባ ይሆናል፡፡<br />

ለዚህም ነው ሌሎች አገራት ከሚሰጡት<br />

እውቅና ይልቅ ድንበር የአንድ አገር<br />

በተጨባጭ /የሚታይ/ ሉዓላዊነት<br />

መገለጫ ነው የሚባለው፡፡ ድንበር<br />

ዋነኛው የሉዓላዊነት አካል ስለመሆኑ<br />

የኢትዮጵያ ህዝብ ሲበድሉት የኖሩት<br />

አገዛዞች ‹‹አገርህ ተደፈረች›› ሲሉት<br />

ለጊዜውም ቢሆን ልዩነቱን ወደጎን ትቶ<br />

ዳር ድንበር ሊያስከበር ሲተም መኖሩ<br />

ትልቅ ማስረጃ ነው፡፡ በተቃራኒው<br />

መንግስታቱ ለሉዓላዊነት የህዝብን ያህል<br />

ቁርጠኛ ሆነው አልተገኙም፡፡ በዚህ በኩል<br />

ደግሞ ኢህአዴግ ሉዓላዊነትን አሳልፎ<br />

በመስጠት ወደር አልረገኘለትም፡፡<br />

አንድ አገር ሉዓላዊ የምትሆነው አሊያም<br />

ይህ ክብር የሚቀጥለው ድንበሯን፣<br />

ታሪኳንና የህዝብን ጥቅም አስጠብቆ<br />

የሚኖር አገር ወዳድ መንግስት ሲኖራት<br />

ብቻ ነው፡፡ በዚህ በኩል የአሁኗ<br />

ኢትዮጵያ አልታደለችም፡፡ የአገርን<br />

ጥቅም፣ በደምና በአጥንት የተገነባን<br />

ታሪክና ድንበር አሳልፎ የሚሰጥ አካል<br />

ባለበት የአገሪቱ ሉዓላዊነት አደጋ<br />

ውስጥ ይገባል፡፡ ሉዓላዊነት የአንዲት<br />

አገር ከሌሎች አገራት ጋር ሲነጻጸር<br />

ያላት እኩል ክብር፣ ህጋዊ ሰውነት<br />

እንደመሆኑ መንግስት የሚባለው አካል<br />

ወሰኗን ባልተገባ መንገድ ለሌሎች<br />

አሳልፎ የሚሰጥ ወይንም የሚወሰድበት<br />

ከሆነ ሉዓላዊነቷ ተደፍሯል ማለት ነው፡<br />

፡ ህወሓት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት<br />

ማስደፈር የጀመረው ገና በርሃ በነበረበት<br />

ወቅት ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት ከማንም<br />

ቀድሞ በየጊዜው ሰራዊት ወደ ሶማሊያ<br />

የሚልከው ህወሓት ያኔ ገና በርሃ እያለ<br />

ተስፋፊውን የሶማሊያ መንግስት እስከ<br />

ድሬዳዋ ድረስ መንገድ መምራቱን<br />

እንደ አስግደ ያሉት የቀድሞው የቡድኑ<br />

አባላት እማኝነታቸውን በይቅርታ መልክ<br />

ገልጸዋል፡፡<br />

ህወሓት እንደ ፖለቲካ ቡድን<br />

ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ኤርትራ<br />

የኢትዮጵያ ቅኝ ግዛት እንደሆነችና ነጻ<br />

መውጣት እንዳለባት ሲሰብክ ኖራል፡፡<br />

ህወሓት ‹‹አሸባሪ›› በነበረበት በዛ ወቅት<br />

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ<br />

መለስ ዜናዊ ስለ ኤርትራ ጉዳይ ሁለት<br />

መጽኃፍትን ጽፈዋል፡፡ ‹‹የኤርትራ<br />

ህዝብ ትግል ከየት ወደየት›› በተሰኘው<br />

መጽኃፋቸውም ኤርትራን ከኢትዮጵያ<br />

ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌላት<br />

ነጻ አገር መሆኗን አውጀዋል፡፡ አቶ<br />

መለስና ህወሓት ይህን በሚሉበት ወቅት<br />

በርካታ የኤርትራ ተወላጆች በአገሪቱ<br />

አሁን ህወሓት ለሌሎች የግንባሩ አባል<br />

ፓርቲዎች አሳልፎ የማይሰጣቸው ቁልፍ<br />

ስልጣን እንደነበራቸው አይዘነጋም፡፡<br />

ገና ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ኤርትራን<br />

ከኢትዮጵያ መነጠልን አላማው አድርጎ<br />

የተነሳው ህወሓት ደርግን አሸንፎ ቤተ-<br />

መንግስት ሲገባ የወሰደው እርምጃ<br />

የዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ ኤርትራን<br />

እውቅና እንዲሰጥ ማድረግ ነበር፡፡ ይህም<br />

ኢህአዴግን የዋናዋ አገር ገዥ ሆኖ<br />

የአገሪቱ ክፍልን በፈቃደኝነት ያስገነጠለ<br />

(ሉዓላዊነቷን አሳልፎ የሰጠ) ብቸኛው<br />

ፓርቲ ሳያደርገው አይቀርም፡፡ ኤርትራን<br />

በገዛ እጁ ያስገነጠለው ህወሓት/ኢህአዴግ<br />

ከሻዕቢያ ጋር የነበረው ፍቅር ሲያልቅ<br />

የአገሩ ሉዓላዊነት ተላልፎ የተሰጠበት<br />

የኢትዮጵያ ህዝብ በደሉን ለጊዜው ወደጎን<br />

ትቶ ዳር ድንበሩን ለማስከበር ሲነሳ አገዛዙ<br />

የማይጨነቅለትን ሉዓላዊነት ለማስከበር<br />

እንደማይደክመው አሳይቷል፡፡ ጦርነቱ<br />

በኢትዮጵያ ህዝብ አሸናፊነት ከተጠናቀቀ<br />

በኋላም ቢሆን ህወሓት የለመደውን<br />

ሉዓላዊነት አሳልፎ የመስጠት ልክፍት<br />

ደግሞታል፡፡ ይህ አልበቃው ሲልም<br />

ህዝብ ከእሱ በላይ ለአገሪቱ ሉዓላዊነት<br />

እንደሚጨነቅ ጠንቅቆ ስለሚያውቅም<br />

‹‹ባድመን አግኝተናል!›› በሚል ህዝብን<br />

አሞኝቷል፡፡ ይህም ህወሓት/ኢህአዴግ<br />

ከሉዓላዊነት ጋር ያላውን ተቃርኖ<br />

በጉልህ የሚያሳይ ነው፡፡<br />

የኢህአዴግና የሉዓላዊነት ተቃርኖ<br />

አሁንም ቀጥሏል፡፡ ከስድስትና ሰባት<br />

አመታት ጀምሮ የኢትዮጵያን መሬት<br />

አሳልፎ ለሱዳን ለመስጠት በድብቅ<br />

እየተዋዋለ መሆኑ ሲነገር ቆይቷል፡<br />

፡ በቅርቡ ደግሞ ‹‹ሱዳን ትሪብዩን››<br />

የተባለው የሱዳን ጋዜጣ ‹‹ለም መሬታችን<br />

አገኘን!›› የሚል ዜና ማውጣቱን ተከትሎ<br />

ኢህአዴግ መሬቱን ለመስረከብ መቃረቡን<br />

አመላክቷል፡፡ የአንድ አገር መንግስት<br />

የአገሪቱን ድንበር ማስጠበቅና ማስከበር፣<br />

የዜጎቹን ጥቅም ማስከበር ሲኖርበት<br />

ለራሱ ግላዊ ጥቅም፣ ህጋዊ መሰረት<br />

በሌለው መንገድ የአገሩን ወሰንና ድንበር<br />

አሳልፎ የሚሰጥ ከሆነ በአገር ውስጥ<br />

የሌሎች ወኪል ሆኖ የአገርን ሉዓላዊነት<br />

እየደፈረ ከመሆን ውጭ ሌላ ሊባልለት<br />

አይችልም፡፡<br />

ይህ የ‹‹መንግስት›› ተግባር ልክ ቅኝ<br />

ገዥዎቹ የራሳቸው ታማኞች (ባንዳዎች)<br />

እንደነበሯቸው ማለት ነው፡፡ አንዲት<br />

በመንግስት ስር የምትገኝ አገር ሉዓላዊ<br />

የምትባለው ይህ መንግስት የአገሪቱን<br />

ወሰንና ሌሎች ጥቅሟን በህጋዊ መንገድ<br />

መቆጣጠርና ማስተዳደር ከቻለና<br />

በጥቅምም ይሁን በአቅም ማነስ ለውጭ<br />

ሀይል የአገሪቱን ጥቅም፣ ክብር፣ ወሰን<br />

አሳልፎ የማይሰጥ ከሆነ ብቻ ነው፡፡<br />

አገሪቱን ሁለመናው ነገር ተቆጣጥሮና<br />

እያስተዳደረም ቢሆን በውጭ ሀይል<br />

ተጽዕኖ ውሳኔ የሚያስተላልፍ፣<br />

የአገሪቱን ጥቅም አሳልፎ የሚሰጥ<br />

ከሆነ የአገሪቱ ሉዓላዊነቷ ተደፍሯል፡<br />

፡ የኢትዮጵያን መሬት ለሱዳን አሳልፎ<br />

ለመስጠት እየተደራደረ ያለው ኢህአዴግ<br />

የአገርን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ፣ ለህዝብ<br />

ጥቅም በመቆም ከሚታወቅ ‹‹መንግስት››<br />

ከተባለ አካል ይልቅ በሚገዛት አገር<br />

ውስጥ ለሱዳን ጥቅም የቆመ መሆኑን<br />

አሳይቷል፡፡<br />

አንድ አገር ሉዓላዊ ነው የሚባለው<br />

የአገሪቱን ዜጎች ከውጭ ጥቃት<br />

የሚከላከል አካል (መንግስት) ካለ ብቻ<br />

ቢሆንም የሱዳን ኢትዮጵያ ድንበር<br />

ችግር ከተከሰተ በኋላ በመተማና<br />

አካባቢው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን<br />

ለሱዳን የደህንነት ኃይሎች ተላልፈው<br />

ተሰጥተዋል፡፡ ከስድስትና ሰባት አመት<br />

በፊት ደንብር አካባቢ የነበረው የኢትዮጵያ<br />

ሰራዊት ወደኋላ አፈግፍጎ አርሶ አደሮቹ<br />

ከሱዳን የጸጥታ ሀይሎች ጋር ፊት ለፊት<br />

እንዲጋፈጡ ተፈርዶባቸው እንደነበር<br />

በጊዜው ተዘግቧል፡፡ አሁንም ቢሆን<br />

የሱዳን እስር ቤት ውስጥ የሚማቅቁ፣<br />

ሀብትና ንብረታቸው የሚዘረፍና<br />

በርካታ ሰብዓዊ ጥሰት የሚፈጸምባቸው<br />

መኖራቸው እየተነገረ ነው፡፡ ይህን ሁሉ<br />

የሚያደርገው ከኢትዮጵያ መንግስት<br />

ይሁንታን ያገኘው የሱዳን የደህነነት<br />

ሀይል ነው፡፡ በዚህ ረገድ መንግስት<br />

የመጀመሪያውን ህዝብን ከውጭ ጥቃት<br />

የመከላከል የሉዓላዊነት መርህ አሳልፎ<br />

ሰጥቷል፡፡ የራሱ ህዝብ በውጭ ሃይል<br />

አደጋ እየደረሰበት ዝም ማለት ብቻ<br />

ሳይሆን ሱዳኖች ኢትዮጵያውያንን<br />

እንዲያስለቅቁ የፈቀደው መንግስት<br />

የመጀመሪያው የአገሪቱን ሉዓላዊነት<br />

አሳልፎ የሰጠ አካል ነው፡፡<br />

የዓለም አቀፍ ህግን የጣሰው<br />

ድብቅ ስምምነት<br />

የአንድ መንግስት ዋነኛው<br />

ተግባር አገር ውስጥ ህዝብን<br />

የሚያስተዳድርበትን፣ አገሪቱ ከውጭ<br />

አካላት ጋር የምትገናኝበትንና ጥቅሟን<br />

የምታስከብርበት ህግና አግባብ የአገሪቱን<br />

ጥቅም በሚያስከብር መንገድ መቅረጽ፣<br />

ማስከበርና መተግብር ነው፡፡ ዓለም<br />

አቀፍ ህግ ከእዚህ መካከል አንዱ ነው፡<br />

፡ ኢትዮጵያ ከፈረመቻቸው ዓለም<br />

አቀፍ የድንበር ስምምነቶች መካከል<br />

ደግሞ አብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገራት ነጻ<br />

ከወጡ በኋላ የተፈራረሙት ‹‹የካይሮ<br />

ስምምነት›› በአብነት ይጠቀሳል፡፡<br />

አንድ አይነት ቋንቋ የሚናገሩ የአፍሪካ<br />

ህዝቦች ለቅኝ ገዥዎች በሚመችና<br />

ዘፈቀደ ድንበር ተከፋፍለው ተገዝተዋል፡<br />

፡ አንዳንዶቹ ደግሞ ግልጽ ከሆነው<br />

ይልቅ በየጊዜው የሚቀየሩ የቅኝ ገዥ<br />

አስተዳዳሪዎች፣ እርስ በእርሳቸው<br />

በሚወዳደሩ የምዕራባዊያን አገራት<br />

እንዲሁም የአገር ውስጥ ወኪሎች<br />

(ባንዳዎች) ግራ የሚያጋባ ድንበር መሰረት<br />

ተከፋፋለው ኖረዋል፡፡ ለአብነት ያህል<br />

በሁለትና ሶስት የቅኝ ገዥዎች፣ እነዚህ<br />

አገራትን ወክለው፣ አሊያም ለእነዚህ<br />

አገራት ወኪል ሆነው ለየራሳቸው ጥቅም<br />

ከተሸነሸኑት በርካታ ወሰኖች መካከል<br />

አንዲት አገር በስተመጨረሻ ነጻ ስትወጣ<br />

የያዘችውን ይዛ እንድትቀጥል ነው<br />

የተደረገው፡፡ ይህ ግልጽነት የጎደለው<br />

ድንበር፣ የድንበር ክለላም ለግጭት<br />

መሰረት እንደሚሆን የታመነበት የአፍሪካ<br />

አገራት ነጻ ከመውጣታቸው አስቀድሞ<br />

ነው፡፡ በተለይም የተለያዩ አካላትና<br />

ግለሰቦች የየራሳቸውንና ለራሳቸው<br />

የሚጠቅመውን ድንበር የሚያቀርቡ<br />

መሆኑ ግጭቱን የባሰ እንደሚያደርገው<br />

ታምኖበታል፡፡ ይህም በመሆኑ የአፍሪካ<br />

ህብረት ቻርተር ከጸደቀ ከአመት በኋላ<br />

ይህን ችግር ለመቅረፍ የአፍሪካ አንድነት<br />

ድርጅት በካይሮ ተገኝቶ ቀኝ ገዥዎች<br />

ተክለውት የሄዱትን የድንበር ችግር<br />

ይፈታል ያለውን ስምምነት አጽድቋል፡፡<br />

የዚህ ስምምነት አላማ በቅኝ ግዛት ወቅት<br />

በቅኝ ገዥዎች፣ በግለሰቦች፣ በአገርም<br />

ሆነ በውጭ ቡድኖች አማካኝነት በዘፈቀደ<br />

የተከለሉ ድንበሮች የሚያመጡትን ችግር<br />

ለመቅረፍ የአፍሪካ አገራት ነጻ ሲወጡ<br />

የያዙትን ወሰን ይዘው እንዲቀጥሉ<br />

ማድረግ ነው፡፡ ሌሎች አገራትም<br />

የጎረቤቶቻቸውንም ሆነ የሌሎች ነጻ<br />

ሲወጡ የነበራቸውን ድንበር ማክበር<br />

እንዳለባቸው የሚያሳይ ነው፡፡ ይህ ህግ<br />

እ.ኤ.አ በ1963 በጸደቀው የአፍሪካ ህብረት<br />

ቻርተር ላይም በግልጽ ተቀምጧል፡<br />

፡ የ1963 ቻርተር እንዲሁም በሀምሌ<br />

1964 የተፈረመው ስምምነት “to respect<br />

the frontiers existing on their<br />

achievement of independence”<br />

ወይንም አገራት ነጻ ሲወጡ የነበራቸውን<br />

ወሰን/ድንበር የማክበር ግዴታን አጽንኦት<br />

ሰጥቶ አስቀምጧል፡፡ ይህ ችግር አሁንም<br />

ድረስ ባለመቀረፉ የአሁኑ አዲሱ<br />

የአፍሪካ ህብረት ቻርተርም በአንቀጽ<br />

4(b) ‹‹respect of borders existing<br />

on achievement of independence››<br />

ወይንም አገራት ነጻነት ሲያገኙ<br />

የነበራቸውን ድንበር ማክበርን የሚለውን<br />

መርህ በቀዳሚነት አስቀምጦታል፡፡<br />

የአፍሪካ ህብረት ሚኒስትሮች እ.ኤ.አ<br />

በየካቲት 25 2010 አዲስ አበባ ላይ<br />

‹‹DECLARATION ON THE AF-<br />

RICAN UNION BORDER PRO-<br />

GRAMME AND THE MODALI-<br />

TIES FOR THE PURSUIT AND<br />

ACCELERATION OF ITS IMPLE-<br />

MENTATION›› የሚል ሰነድ በህብረቱ<br />

ስም ተፈራርመዋል፡፡ ሰነዱ ግጭትን<br />

ለመከላከል፣ ህብረትን ለማጠናከር ያለመ<br />

ነው፡፡ ይህ ስምምነት መሰረቱ ያደረገው<br />

‹‹አገራት ነጻ ሲወጡ የያዙትን ድንበር<br />

ይዘው መቀጠል፣ የሌሎቹንም ማክበር<br />

ይኖርባቸዋል›› ከሚለው የካይሮው<br />

ስምምነትን የመነጨ ነው፡፡<br />

በአሁኑ ወቅት ለሱዳን ይሰጣል የተባለው<br />

መሬትን ስምምነት እ.ኤ.አ በ1902 እና<br />

በ1907 እንደተደረገ ታሪክ ያስረዳል፡<br />

፡ ሆኖም መንግስታቱ መካከል ይህ<br />

በእውን ሳይተገበር መቅረት ብቻ ሳይሆን<br />

ሻለቃ ጉይን የተባለው የእንግሊዝ አዛዥ<br />

መንግስታቱ ከተስማሙበትም ውጭ<br />

ብቻውን ያሰመረው መሆኑ ይታወቃል፡<br />

፡ ያም ሆኖ ሱዳን ነጻ ስትወጣ የያዘችው<br />

ድንበር የዚህን የሻለቃ ድንበር አይደለም፡<br />

፡ የአፍሪካ አንድነት ቻርተር፣ የካይሮ<br />

ስምምነት፣ የአፍሪካ ህብረት ቻርተርና<br />

እዚህን መርሆች መሰረት አድርገው<br />

በየጊዜው በድንበር ጉዳይ የሚወጡ ህጎች<br />

እያሉ በአሁኑ ወቅት እነዚህን ህጎች<br />

በሚጻረር መልኩ ሱዳን ነጻ ስትወጣ<br />

ከነበራት ድንበር ወደ ኢትዮጵያ እስከ<br />

40 ኪሎ ሜትር የሚገባ መሬት ሊሰጣት<br />

መሆኑ ይፋ ሆኗል፡፡<br />

የካይሮን ስምምነት፣ የአፍሪካ ህብረት<br />

ቻርተርና ሌሎችንም ከሁለቱ የሚመነጩ<br />

የድንበር ህጎች በሚጻረር መልኩ<br />

የሚተገበር ተግባር ይበልጡን አስገራሚ<br />

የአንድ መንግስት ዋነኛው ተግባር አገር ውስጥ ህዝብን የሚያስተዳድርበትን፣ አገሪቱ ከውጭ<br />

አካላት ጋር የምትገናኝበትንና ጥቅሟን የምታስከብርበት ህግና አግባብ የአገሪቱን ጥቅም<br />

በሚያስከብር መንገድ መቅረጽ፣ ማስከበርና መተግብር ነው፡፡ ዓለም አቀፍ ህግ ከእዚህ መካከል<br />

አንዱ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ከፈረመቻቸው ዓለም አቀፍ የድንበር ስምምነቶች መካከል ደግሞ<br />

አብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገራት ነጻ ከወጡ በኋላ የተፈራረሙት ‹‹የካይሮ ስምምነት›› በአብነት<br />

ይጠቀሳል፡፡<br />

የሚሆነው ሌሎቹ ቅኝ ግዛት ስር<br />

በነበሩበት ወቅት የራሷ ወሰን የነበራት<br />

የህብረቱ መስራችና መቀመጫ ኢትዮጵያ<br />

ላይ መሆኑ ነው፡፡ ህግጋቱን ጥሶ<br />

የአገሪቱን መሬት ከድሮው እንደለመደው<br />

መሬትን ብቻ ሳይሆን ‹‹ሉዓላዊነትን››<br />

ለሌሎች በገጸ በረከትነት የሚያስረክበው<br />

ደግሞ ኢትዮጵያን እወክላለሁ በሚለው<br />

‹‹መንግስት›› መሆኑ ኢህአዴግ<br />

ከሉዓላዊነት ጋር ምን ያህል እንደተጣላ<br />

የሚያሳይ ነው፡፡<br />

ሱዳኖችን ጨምሮ መሬቱ ለሱዳን<br />

መሰጠት እንዳለበት ለሚያምነው<br />

ኢህአዴግ ዋነኛው መከራከሪያ<br />

ብሪታኒያና አጼ ምኒልክ በድንበሩ ጉዳይ<br />

ቢዋዋሉም መሬቱ በኢትዮጵያ ቁጥጥር<br />

ስር መቆየቱን ነው የሚያነሱት፡፡ በጉዳዩ<br />

ጥናት ካደረጉት አምስት ኢትዮጵያውያን<br />

መካከል በህይወት የሚገኙት ፕ/ር<br />

መስፍን ወ/ማሪያም ጥር 17/ 2006<br />

ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ ተገኝተው<br />

እንዳስረዱት፤ አሁን በኢትዮጵያና ሱዳን<br />

መካከል አጨቃጫቂ ነው የሚባለውን<br />

ድንበር የከለለው ሻለቃ ጉይን የተባለው<br />

የእንግሊዝ አዛዥ ብቻውን ሆኖ ነበር፡፡<br />

በወቅቱ ኢትዮጵያ ወኪል አልነበራትምና<br />

ስምምነቱ አይገዛትም ማለት ነው፡<br />

፡ ሻለቃው እንዳፈተተው በሚከልልበት<br />

ወቅትም ቢሆን የድንበር ለውጥ<br />

በመደረጉ ድንበሩ ወደ ሱዳን ገባ<br />

ብሎ እንደሚከለል ደብዳቤ ደርሶታል፡<br />

፡ ሆኖም ሻለቃው ከብሪታኒያ ክልል<br />

ካለችው ውጭ ወደ ኢትዮጵያ መሬት<br />

ገብቶ የራሱን ዘፈቀደ ድንበር አስቀምጦ<br />

አልፏል፡፡ ይህ ሆኖ እያለ ኢትዮጵያን<br />

ወክያለሁ የሚለው ኢህአዴግ በዚህ<br />

በተዛባ ህግ፣ አንድ የቅኝ ገዥ መኮነን<br />

ያሰመረውን የተሳሳተና ያልተገባ ድንበር<br />

የሚቀበል ከሆነ ምን አልባትም ለራሱ<br />

ጥቅም ሲል ብቻ ተጠቀመበት እንጂ<br />

ለስልጣን የማይጠቅመው ቢሆን የአባይን<br />

ስምምነትንም መቀበሉ የማይቀር<br />

እንደነበር ነው የሚያሳየው፡፡<br />

አሁን ለሱዳን ይሰጣል የተባለው መሬት<br />

የኢትዮጵያ አካል በነበረበት ወቅት<br />

ሱዳን ገና ነጻ አልወጣችም፡፡ በመሆኑም<br />

ከአፍሪካ አንድነት ቻርተር ጀምሮ፣<br />

በካይሮ ስምምነት፣ በአዲሱ የአፍሪካ<br />

ህብረት ቻርተርና በየጊዜው ድንበርን<br />

በተመለከተ በሚወጡት ህጎች መሰረት<br />

ድንበሩ የኢትዮጵያ እንጂ የሱዳን ሊሆን<br />

አይችልም፡፡ ከመቶ አመት በፊት በአንድ<br />

የቅኝ ገዥ መኮነን የተደረገን የመከለል<br />

ሙከራ እውነት አድርጎ ለሌላኛው አገር<br />

አሳልፎ መስጠት ከአንድ አገር መንግስት<br />

የሚጠበቅ አይደለም፡፡ ኢህአዴግ<br />

ኢትዮጵያ ውስጥ ስልጣን የያዘበት<br />

ጊዜ ዓለም ከጦርነት ይልቅ ወደ ሰላም<br />

የመጣችበትና በህግ የምትመራበት ነው፡<br />

፡ በዚህ ዘመን የአንድ አገርን ሉዓላዊነት<br />

ለማስጠበቅ ፈተናዎች የማይበዙበት<br />

ዘመን ነው፡፡ ከዚህ ይልቅ በርካታ<br />

የኢትዮጵያ መንግስታት የአገሪቱን<br />

ሉዓላዊነት የሚፈታተኑ አጋጣሚዎችን<br />

በጽናት አልፈዋል፡፡<br />

ኢህአዴግ በጣሊያን ወረራም ሆነ በሌሎች<br />

የአገሪቱ ሉዓላዊነት ጥያቄ ውስጥ<br />

በገባበት ወቅት ገዥ ቢሆን ኖሮ ራሱ<br />

ምንዳ እስካገኘ ድረስ ሙሉ በሙሉም<br />

ይሁን የውጭ ሀይሎች በሚፈልጉት<br />

መልኩ አገሪቱን አሳልፎ ይሰጥ እንደነበር<br />

ለመገመት አይከብድም፡፡ በእርግጥ<br />

አሁንም ቢሆን ሉዓላዊነትን አሳልፎ<br />

መስጠቱ ለሱዳን በሚሰጠው መሬት<br />

ይቆማል ተብሎ የሚገመት አይደለም፡<br />

፡ ፕ/ር መስፍን ውይይቱን በመሩበት<br />

ወቅት ለህዝብ መልሰው የጠየቁት<br />

ጥያቄም ‹‹ኢህአዴግ በቀጣይነት አሳልፎ<br />

የሚሰጠው የትኛውን መሬት ይሆን?››<br />

የሚል ነበር፡፡ ከተሳታፊዎችም ‹‹አዲስ<br />

አበባንስ መቼ ያስከልሏት ይሆን?››<br />

የሚል ጥያቄ ተነስቷል፡፡ ይህ እንግዲህ<br />

ኢህአዴግ ምን ያህል ለሉዓላዊነት<br />

የማይጨነቅ መሆኑና በጉዳዩ ታማኝነቱን<br />

ማጣቱን በግልጽ የሚያሳይ ሀቅ ነው፡፡


ነገረ-ኢትዮጵያ ቅፅ 1 ቁጥር 2 የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. 6<br />

ውህደት ወይስ ትብብር...<br />

ይችላሉ ማለት ነው፡፡ ትብብር አቃፊ<br />

ነው፡፡ የጎሳ ፓርቲውም ሆነ ህብረ-<br />

ብሄራዊው ፓርቲ በጋራ ጉዳዮች ላይ<br />

ተባብረው ከመስራት የሚያግዳቸው<br />

ነገር ሊኖር አይችልም፡፡<br />

በዚህ ረገድ ሰማያዊ ፓርቲ ከማናቸውም<br />

ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ጋር በትብብር<br />

ለመስራት ፍላጎቱ እንደሆነ ሲገልጽ<br />

ይደመጣል፡፡ ፓርቲው እንደሚለው፣<br />

ከውህደት በፊት የሚቀድሙ የቤት<br />

ስራዎችን መስራት ተገቢ ነው፤<br />

ለዚህም ትብብር ከውህደት ይቀድማል<br />

የሚል አቋም አለው፡፡<br />

በእርግጥም አሁን ላይ የፖለቲካ<br />

ፓርቲዎች ተቀራርበው በበለጠ<br />

በትብብር በመስራት ኃይላቸውን<br />

ማጠናከር ይገባቸዋል፡፡ ይህ አሁን ላይ<br />

በትብብር የሚጀምሩት ግንኙነትም<br />

ቀስ በቀስ ወደ ውህደት ሊያመራቸው<br />

ይችላል፤ ለውህደት የሚያደርሱ<br />

ስራዎችንም በዚያው ደረጃ በደረጃ<br />

እያከናወኑ መሄድ ይቻላል፡፡ በዚህ<br />

መልኩ የሚመጣ ውህደትም ዘላቂ<br />

እንደሚሆን መገመት ይቻላል፡፡ ያም<br />

ካልሆነ ደግሞ በትብብር መስራትን<br />

በመቀጠል አቅምን አጎልብቶ ወደ<br />

መሪነት መሸጋገር ትክክለኛ አካሄድ<br />

ይሆናል፡፡<br />

ከ ገፅ 3 የዞረ<br />

ከጅጋ ቋሪት ያለው የትራንፖርት ችግር<br />

ተገልጋዮችን ለስቃይ መዳረጉ ተገለፀ<br />

ጅጋ:- በምዕራብ ጎጃም ዞን ከጅጋ ከተማ<br />

እስከ ቋሪት ያለው የትራንስፖርት<br />

አገልግሎት ችግር ህዝቡን እያሰቃየ<br />

ነው ሲሉ ተሳፋሪዎች ገለጹ፡፡<br />

አራትና አምስት እጥፍ ክፍያ<br />

እንድንከፍል እንገደዳለን ያሉት<br />

ተሳፋሪዎች ‹በህገ-ወጥነት ተመዘበርን መንግስት<br />

ስርዓት ሊያስይዝልን ይገባል› የሚል ጥያቄ ስንጠይቅ<br />

ካልፈለጋችሁ አለመሳፈር ትችላላችሁ የሚል መልስ<br />

ከመንግስት አካላት ይሰጠናል ሲሉ ቅሬታቸውን<br />

ገልጸዋል፡፡<br />

24 ሰው የመጫን አቅም ያላቸው የአረጁና የወላለቁ<br />

መኪኖች እስከ 104 ሰው ድረስ ሲጭኑ ለህዝብ<br />

ህይወት በመቆርቆር እርምጃ የሚወስድ የመንግስት<br />

አካል አለመኖሩ እጅግ አሳዛኝ ነው ያሉት ተሳፋሪዎቹ፣<br />

የዚህን ህዝብ ሰቆቃና እንግልት ለማን አቤት እንደምንል<br />

አናውቅም ብለዋል፡፡<br />

መንግስት የመደባቸው ትራፊክ ፖሊሶች እንዲሁም<br />

የመንገድና ትራንስፖርት ሠራተኞች ተሳፋሪው<br />

ምንም አይነት መብት እንደሌለው ጫና ከማሳደርና<br />

የተሳፋሪውን ሰቆቃ ከማራዘም ውጭ በምንም ዓይነት<br />

ሁኔታ ግዴታቸውን ሲወጡ አናይም ብለዋል፡፡<br />

ጥቂት የወላለቁና ከጥቅም ውጭ የሆኑ መኪኖች<br />

የተመደቡለት ይህ መስመር መንግስት የዘነጋውና<br />

አመቱን ሙሉ ተሳፋሪ ህዝብ የሚንገላታበት ቦታ ሆኗል<br />

ሲሉ ያነጋገርናቸው ተሳፋሪዎች ጨምረው ገልፀዋል፡፡<br />

ፋሽስት ገዳይ ባየር...<br />

ታውቋል! ቀጥሏል! ቀጥሏል! ቀጥሏል! ወራሪው<br />

በማንአህሎኝነት መንፈስ ተረጋግቶ ተቀምጧል!<br />

ጀግናው ተሰማ እርገጤ አሁን ከወራሪው<br />

ኃይል ሰፈር በጣም ተጠግቷል! ብዙም ሳይቆይ<br />

ተኩስ ከፈተበት! ወራሪው ኃይል የሚይዘውና<br />

የሚጨብጠውን አጥቷል! ሆኖም ለጥቂት<br />

ደቂቃዎች ተታኩሷል! ወዲያው ግን ፈርጥጧል!<br />

ከጨለንቆ ደብረ ሲና ገብቷል! የጀግናው አርበኛ<br />

ተሰማ እርገጤ ድል አድራጊነት አሁንም<br />

ተረጋገጠ! ይህ በታሪካችን የጥንታዊት ኢትዮጵያ<br />

የጀግኖች አርበኞች የትግልና ድል ቀጥታ ድምጽ<br />

ነው! ከሸዋ ጠቅላይ ግዛት ጨለንቆ ከተባለ<br />

የውጊያ ሜዳ! መስከረም 19 ቀን 1929 ዓ.ም!<br />

ይህ ለዛሬው ወር ተረኛ ትውልድ የተላለፈ<br />

የጀግኖች አርበኞች ኢትዮጵያን የማዳን ተጋድሎ<br />

ታሪክ ቀጥታ ድምጽ ነው! ከአርበኝነት ገድላችን<br />

የተወሰደ!<br />

መስከረም አልቋል፡፡ ጥቅምትም አልፏል! አሁን<br />

በህዳር ወር ውስጥ መሆናችን ይመዝገብልን!<br />

ጀግናው አርበኛ ተሰማ እርገጤ አሁን ጉደ<br />

በረት ወረዳ የፋሽስት ወራሪ ኃይል የመሸገበትን<br />

ቦታ በመስክ መረጃ ለይቷል! ወራሪው ኃይል<br />

ከመሸገበት መንደር ደረሷል! አርበኞች ምድብ<br />

የውጊያ መስመራቸውን ይዘዋል! ከጥቂት<br />

ጊዜያት በኋላ እሳት ይዘንባል! አርበኞች ወደ<br />

ምሽጉ ተጠግተዋል! በጣም ቀርበዋል! ጊዜ<br />

አላጠፉም! የቅድሚያ ተነሳሽነት ወስደዋል!<br />

ወዲያው ጦርነቱ ተጋግሎ ቀጠለ! ጀግናው አርበኛ<br />

ተሰማ እርገጤ በርካታ የፋሽስት ኢጣሊያ ወራሪ<br />

ኢትዮጵያ ለምን ...<br />

ለማጣፈጥ ሲባል አዲስ ሰበካ ተጀምሯል። እኛ<br />

የምናካሂደው ትጥቅ ትግል የማንዴላ አይነት<br />

ትጥቅ ትግል ነው የሚል ማጭበርበሪያ። ጦርነት<br />

ጦርነት ነው። ይህን አባባል የሚያስተጋባው<br />

ቡድን በአንድ በኩል ተከታዮቹ መከተላቸውን<br />

እንዲቀጥሉ ለማድረግ ሲሆን በሌላ በኩል<br />

ደግሞ ሰላማዊ ትግል ካደረሰበት ትኩሳት<br />

ለጊዜው እረፍት ለማግኘት በሰላማዊ ትግል<br />

ንድፈ አሳብ ተማሪዎች እና ደጋፋዊዎች ላይ<br />

የከፈተው የማሸማቀቅ የስነ ልቦና ጦርነት ነው።<br />

መለስ ዜናዊ በምርጫ 97 የተቃሚው አሳብ<br />

የህዝብ ድጋፍ እያገኘ መሄዱን ሲያስተውል<br />

ደጋፊዎቹን ለማረጋጋት እና ተቃዋሚውን<br />

ለማሸማቀቅ ኢንተርሃምዌይ እስከማለት ደረሶ<br />

እንደነበር አስታውሳለሁ። አምባገነኖች ብዙ<br />

ከ ገፅ 8 የዞረ<br />

ኃይል ተዋጊዎችን በጥቂት ጊዜያት ከአፈር ጋር<br />

አዋህዷቸዋል! ታላቅ ጦርነት ሆነ! ከኢትዮጵያ<br />

ጀግኖች አስራ ሁለት አርበኞች በዚሁ ጦርነት<br />

ተሰውተዋል፡፡ በጀግንነት ወደ ታሪክ ወርደዋል!<br />

ጦርነቱ ቀኑን ሙሉ ቀጥሎ ውሏል! በዚህ<br />

ጦርነት ጀግናው ተሰማ እርገጤ በትከሻው ላይ<br />

በሁለት ጥይት ተመትቶ ቆስሏል፡፡ ብዙ ደምም<br />

ፈስሶታል! ጀግናው ተሰማ እርገጤ እስከ ጦርነቱ<br />

ፍጻሜ ዘጠኝ ጊዜ መቁሰሉ ታውቋል! የጉደ በረት<br />

ጦርነት እስከ ሌሊት ድረስ ቀጥሏል! በዚሁ<br />

ጦርነት ሰባ አምስት የፋሽስት ኢጣሊያ ወራሪ<br />

ኃይል መኮንኖችና ወታደሮች ተገድለዋል!<br />

ቆራጡ አርበኛ ተሰማ እርገጤ በአምስቱ<br />

የፋሽስት ኢጣሊያ ወረራ ዓመታት የተዋጋባቸው<br />

የጦር ሜዳዎች በጣም ብዙ ናቸው! በዚህም<br />

መሰረት ጥር ወር በ1929 ዓ.ም ባደረገው ውጊያ<br />

በርካታ የወራሪው ተዋጊዎችን በሞት ቀንሷል!<br />

እንዲሁም በየካቲት ወር 1929 ዓ.ም በሞፈር<br />

ውሃ ላይ በተደረገው ጦርነት ብዙ ፋስስቶችን<br />

ገድሏል! በዚህ ብቻም አላበቃም! በመጋቢት ወር<br />

1929 ዓ.ም ገዘት በተባለ ቦታ ጦርነት አድርጎ<br />

በርካታ የወራሪው ኃይል አባላትን ደምስሷል!<br />

አሁንም በመቀጠል በሚያዚያ ወር 1929<br />

ዓ.ም በመንዝ ውስጥ ወይራ ገበያ በተባለ ቦታ<br />

የተደራጀውን የወራሪውን ኃይል ተዋጊ ድባቅ<br />

መትቷል! የጦር መሳሪያም ማርኳል! ጀግናው<br />

አርበኛ ተሰማ እርገጤ አሁንም በጽኑ የውጊያ<br />

ስነ-ልቦና ይስተዋላል! ቀጥሏል! ግንባሩን ሳያጥፍ<br />

ቀን ከሌት ይዋጋል! በዚህ ሂደት ሐምሌ 18<br />

ከ ገፅ 9 የዞረ<br />

ይላሉ። የሚሉት ሁሉ ግን ከአጭር ጊዜ<br />

መፍትሄነት ባሻገር አይረዳቸውም። ይሄም ያን<br />

አይነት የስነ ልቦና ጦርነት ነው። የአለም ህዝብ<br />

ለማንዴላ ክብር የለገሰው ጠበንጃ በማንሳቱ<br />

አይደለም። በሃውልቱም ላይ የሚጻፈው ጦረኛ<br />

መሆኑ አይደለም።<br />

ቤተሰቡም እስከ ልጅ ልጆቹ ድረስ በአደባባይ<br />

ስለማንዴላ የሚሰብኩት ሰላማዊነቱን እና<br />

በሰላማዊ መንገድ አፓርታይድን እንዳፈረሰ<br />

ነው። አፓርታይድ የፈረሰው በትጥቅ ትግል<br />

አይደለም። የደቡብ አፍሪካ የመጀመሪያው<br />

ጥቁር ፕሬዘዳንት ሊሆን የቻለው በትጥቅ<br />

ትግል አይደለም። ጥቁር እና ነጭ ደቡብ<br />

አፍሪካውያን በህብረት ያደረጉት ሰላማዊ<br />

ትግል መዘንጋት የለበትም። ታዋቂ ጥቁር እና<br />

እና 22 ቀን 1929 ዓ.ም ግንደ በረት ላይ ክልቤ<br />

በተባለ ቦታ ተዋግቶ ድል ማድረጉን የአርበኝነት<br />

ታሪኩ ያመለክታል፡፡ በመቀጠልም ሺኖ በተባለ<br />

ቦታ ተዋግቶ አኩሪ ውጤት አስመዝግቧል!<br />

ቆፍጣናው አርበኛ ተሰማ እርገጤ በመቀጠልም<br />

በሰላሌ አውራጃ ውስጥ ኩዩ ጊዮርጊስ በተባለ<br />

ቦታ ከወራሪው ኃይል ጋር ተዋግቶ ድል<br />

አስመዝግቧል! ለሁለት ቀናት በተካሄደው በዚሁ<br />

ጦርነት በርካታ የወራሪው ኃይል ተዋጊዎቹን<br />

መግደሉ ታውቋል! እንዲሁም መስከረም 12<br />

ቀን 1930 ዓ.ም ተዋግቶ ወራሪው ኃይል<br />

እንዲፈረጥጥ አድርጓል! በተመሳሳይ መልኩ<br />

መስከረም 15 ቀን 1930 ዓ.ም ተዋግቶ ድል<br />

ተቀዳጅቷል!<br />

ጅግናው አርበኛ ተሰማ እርገጤ እስከ ጦርነቱ<br />

ፍጻሜ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ውስጥ በወራሜ<br />

በላሎ ምድር በአይት በተጉለት ወረዳ አምባ<br />

ሞሻ፣ በከሴ ቆላ አቦ ጉር ህዳባይ፣ በላሎ<br />

ምድር ኪደር በምሐይና በአንጉቦላ ቀበሌዎች<br />

እየተዘዋወረ ከፍተኛ ጀብዱ ፈጽመዋል!<br />

የታወቀው ጀግና ተሰማ እርገጤ ከድል በኋላ<br />

የአምስት ዓመት የአርበኝነት ኒሻን ባለአምስት<br />

ዘንባባ ተሸልሟል! እንዲሁም የድል ኮከብ<br />

ሜዳይ አግኝቷል! በተመሳሳይ መልኩ የቅዱስ<br />

ጊዮርጊስ ሜዳይ ባለሁለት ዘንባባ ተሸልሟል፡፡<br />

ጀግናው የኢትዮጵያ ልጅ ተሰማ እርገጤ ከአባቱ<br />

ከባሻ እርገጤ ሀብተ-ገብርኤልና ከእናቱ ወይዘሮ<br />

ወለተ አረጋይ ጨድድ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት<br />

በይፋት ውስጥ ሐር አምባ በተባለ ቀበሌ በ1888<br />

ነጭ ደቡብ አፍሪካውያን አርቲስቶች የአለምን<br />

ህዝብ በአፓርታይድ ላይ ለማስተባበር<br />

ያደረጉት ቀጣይነት ያለው አለም አቀፍ<br />

ሰላማዊ ዘመቻቸው መዘንጋት የለበትም።<br />

ማንዴላን ለማስፈታት እና አፓርታይድን<br />

ለማስፈታት የአለም ህዝብ ያደረገው ሰላማዊ<br />

ትግል መዘንጋት የለበትም። በማንዴላ<br />

ሃውልት ላይ የሚጻፈው የጦር አበጋዝነቱ እና<br />

የገደለው ሰው ቁጥር ሳይሆን ማንዴላ ከእስር<br />

ቤት ከወጣ በኋላ የፈጸመው ነው።<br />

በመጨረሻ ወደ ኢትዮጵያ ልመለስ እና<br />

ጽሁፌን ልደምድም። ሰላማዊ ትግል ሰላማዊ<br />

ሰልፍ ማድረግ ብቻ አይደለም። ሰላማዊ<br />

ትግል በምርጫ መሳተፍ ብቻ አይደለም።<br />

ሰላማዊ ትግል በአደባባይ ወጥቶ መቃወም<br />

ዓ.ም ተወለደ፡፡ በልጅነቱ አማርኛ ተምሯል፡<br />

፡ ማይጨው ዘምቷል! ግዳጁን ተወጥቷል!<br />

ከማይጨው መልስ የይፋትን ህዝብ ለጦርነት<br />

አስተባብሯል! ቆፍጣናው ጀግና ተሰማ እርገጤ<br />

ሰኔ 23 ቀን 1964 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት<br />

ተለይቷል፡፡ ጀግናው ተሰማ እርገጤ በህይወት<br />

ዘመኑ ሰባት ልጆችን አፍርቷል፡፡ ጀግናው<br />

አርበኛ ተሰማ እርገጤ ከዚህ ዓለም በሞት ሲለይ<br />

ባህላዊ ወታደራዊ ማዕረጉ ደጃዝማች እንደነበር<br />

ታውቋል!<br />

ውድ የኢትዮጵያ ወጣት ሆይ በቀደምት<br />

የኢትዮጵያ ጀግኖች መስዋዕትነት ታፍራና<br />

ተከብራ የኖረችው ሀገራችን ተዋርዳለች! ሀገር<br />

ለመሸጥ ደላላ ኮሚሽን ተቋቁሟል! ስለዚህ<br />

ወጣቱ ትውልድ የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ<br />

ጠንቅቆ በማወቅ ህሊናዊ ሁኔታዎችን ለማሳደግ<br />

ሊነሳ ይገባል! እርግጥ ነው ሀገርን ጠብቆ<br />

በክብር ለመጪው ትውልድ ማስረከብ የዜጎች<br />

ሁሉ ግዴታ ይሆናል፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያን<br />

ከጠቅላላ ውድቀት ለማዳን በቁርጠኝነትና በዓላማ<br />

ጽናት በተግባር እንነሳ! ክብር ለቆራጡ አርበኛ<br />

ለደጃዝማች ተሰማ እርገጤ! ክብር በአምስቱ<br />

የፋሽስት ኢጣሊያ ወረራ ዓመታት በዱር<br />

በገደሉ ለወደቁ ጀግኖች! ክብር ዛሬም ከዕለታዊ<br />

ጥቅምና ጊዜያዊ ተድላ ርቀው ለኢትዮጵያ ነጻነት<br />

በመታገል ላይ ለሚገኙ ቆራጦች! ኢትዮጵያዊ<br />

ብሄርተኝነት ያሸንፋል!<br />

ብቻ አይደለም። ሰላማዊ ትግል እነዚህን ሁሉ<br />

ማድረግ ነው። በተጨማሪ ሰላማዊ ትግል<br />

ህዝብን የራሱ ነፃ አውጭ በማድረግ (1)<br />

በስልጣን ላይ የሚገኝን አምባገነን መንግስት<br />

አስወግዶ ህዝብን የመንግስት ስልጣን ባለቤት<br />

ማድረግን፣ (2) መፈንቅለ መንግስት ቢነሳ<br />

ትብብር መንፈግ፣ (3) እንደ ህውሃት/<br />

ኢህአዴግ ከጫካ ወይንም ከጎረቤት አገር<br />

(ኤርትራን ጨምሮ) ተነስቶ ልውረርህ የሚል<br />

ቡድን ቢመጣ ህዝባዊ መከላከል (Civil Resistance)<br />

ማድረግን ያካትታል። ሰላማዊ<br />

ትግልን በሚመለከት ግንዝቤያችን ሰፋ ያለ<br />

መሆን አለበት። የቀድሞው የመንግስት<br />

ሽግግር ባህላችን ደደብ ነው። ብልህ ሰዎች<br />

አይከተሉትም።<br />

እንዲሆን በማሰብ ፓርቲው ቀኑን መዘከር አስፈላጊ<br />

መሆኑን ያምናል ብለዋል፡፡ በዕለቱ በሁለቱም<br />

ፕሮግራሞች ላይ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ እንዲሳተፍ<br />

አቶ ብርሃኑ ጥሪ አቅርበዋል፡፡<br />

ሰማያዊ ፓርቲ በ2005 ዓ.ም ጣሊያኖች በወገኖቻችን<br />

ላይ ከፍተኛ በደል የፈጸመውን ሮዶልፍ ግራዚያኒ<br />

በትውልድ ከተማው ‹የጀግና› ሐውልት በማቆም<br />

ዕውቅና መስጠታቸውን በመቃወም ሰላማዊ የተቃውሞ<br />

ሰልፍ በአዲስ አበባ መጥራቱን ተከትሎ በቦታው የተገኙ<br />

አባላቱ ለእስር መዳረጋቸው የሚታወስ ነው፡፡<br />

በጎንደር በተካሄደው...<br />

ከ ገፅ 1 የዞረ<br />

ያስተባበሩት የአካባቢው የፓርቲው መዋቅር አካላት<br />

ደህንነቶች ለቤተሰቦቻቸው ደውለው እያስፈራሩዋቸው<br />

መሆኑን የፓርቲው የዞን ሰብሳቢ አቶ አግባው ሰጠኝ<br />

ለዝግጅት ክፍላችን ገልጸዋል፡፡<br />

ፓርቲው ጥር 25 በጎንደር ከተማ መስቀል አደባባይ<br />

በጠራው ሰልፍ፣ የኢትዮ-ሱዳን የድንበር ማካለል<br />

ሂደትን በተመለከተ መንግስት ለህዝብ ጉዳዩን ግልጽ<br />

እንዲያደርግና ሉዓላዊነትን እንዲያከብርና እንዲያስከብፈር<br />

መጠየቁ ይታወሳል፡፡


7 የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2 ነገረ-ኢትዮጵያ<br />

መሬት ያስቆረሱት የመለስና ተከታዮቹ<br />

እኩይ ስምምነቶች<br />

አለማየሁ ገ/ማርያም (ፕ/ር)<br />

የአሁኑ አስገራሚ ጊዜ ሸክስፒር፣ ‹ጁሊየስ<br />

ቄሳር› በሚለው ፅሁፉ ላይ ለተናገረው አነጋገር<br />

ልዩ ትርጉም ይሰጠዋል፣ “ሰዎች የሰሩት ተንኮል<br />

ከመቃበራቸው በላይ ህያው ሆኖ ይኖራል” ብሎ<br />

ነበር ሸክስፒር፡፡ በአሁኑ ጊዜ አቶ መለስ ዜናዊ<br />

በህይወት በነበሩበት ጊዜ ከሰሩት ተንኮሎችና<br />

ጭራቃዊነት የሞላው አስቀያሚ ተግባር ውርስ<br />

ጋር ፊት ለፊት ተፋጥጠን እንገኛለን፡፡ የኢትዮጵያ<br />

ሉዓላዊ የግዛት አካል ተቆርሶ እንደገና ለሽያጭ<br />

ለሱዳን ቀርቧል፡፡ ይህንንም ጭራቃዊነት ተንኮል<br />

የቀበሮ ባህታውያኑ “የድንበር ማካለል“ ብለው<br />

ይጠሩታል፡፡ እኔ ደግሞ ድንበር መቁረስ፣<br />

መቆራረስ፣ መሽረፍ እና መሸራረፍ ብዬ<br />

እጠራዋለሁ፡፡ ባጭሩ ኢትዮጵያን ለቅርጫ<br />

ማቅረብ እለዋለሁ… ደግሞ ለሰላሳ ቁርጥራጭ<br />

የመዳብ ዲናሮች! እ.ኤ.አ በ2008 “የኢትዮጵያ<br />

ጋሻ“ ተብሎ በሚጠራው የሰሜን አሜሪካ የሲቪል<br />

ማህበረሰብ ስብስብ ጉባኤ ላይ በመገኘት የእናት<br />

አገር ኢትዮጵያን ሉዓላዊነት መጠበቅ በሚል<br />

ርዕስ ስሜትን የሚቀሰቅስ ንግግር አድርጌ ነበር፡፡<br />

አቶ መለስ የአሰብን ወደብ አሳልፈው በሰጡበት<br />

ወቅት ዝምታን በመምረጣችን ወደብ አልባ<br />

የመሆንን ዋጋ ከፍለናል፡፡ እ.ኤ.አ በ1998 ባድመ<br />

ተወረረች፣ እናም የ80,000 ኢትዮጵያውያን<br />

ህይወትን የበላ መስዋዕትነት ተከፍሎ<br />

ጠላቶቻችን ከግዛታችን እንዲወጡ ተደረገ፡<br />

፡ ሆኖም ግን አቶ መለስ በብርሃን ፍጥነት<br />

ተገልብጠው የኢትዮጵያን አንጸባራቂ የጦር<br />

ሜዳ ድል ቀልብሰው የዲፕሎማሲያዊ ሽንፈትን<br />

በመጋት በእርቅ ሰበብ ስም ባድመን ለወራሪው<br />

ኃይል አሳልፈው ለመስጠት ስምምነት አደረጉ…<br />

(ዛሬ) በምዕራብ ኢትዮጵያ የሚኖሩ ወገኖቻችን<br />

በግልጽ እንደነገሩን የአያት ቅድመአያቶቻቸውን<br />

መሬት እና መኖሪያ ቤታቸውን ሳይቀር አቶ<br />

መለስ ለሱዳኑ አምባገነን [በዓለም አቀፉ<br />

የወንጀለኞች ፍርድ ቤት በወንጀል ለሚፈለጉት<br />

እና ከፍትህ ለማምለጥ እራሳቸውን በመደበቅ<br />

ተወሽቀው ላሉት] መሪ ኦማር አልባሽር<br />

አሳልፈው ለመስጠት በሚስጥር ስምምነት<br />

ፈጽመዋል…ያንን ንግግር ካደረግሁ ከስድስት<br />

ዓመታት በኋላ እንኳን በሚያሳዝን ሁኔታ እናት<br />

አገራችንን ለመበታተን አቶ መለስ ከበረሃ ውስጥ<br />

ነድፈው ያመጡትን ጭራቃዊ ዕቅድ እኩይ<br />

ምግባር ለመቀልበስ ባለመቻላችን አዝናለሁ፡፡<br />

አቶ መለስ አሁን በህይወት የሉም፣ ሆኖም ግን<br />

እኛን እንዲያጠፋ ጥለውት ከሄዱት ተንኮላቸው<br />

ስራቸው ጋር ፊት ለፊት ተጋትረናል፡፡ “መልካም<br />

ሰዎች ዝም ስላሉና ምንም ባላማድረ ጋቸው<br />

ይሆን ተንኮል የሚበረታው” የሚለው አባባል<br />

እውነታነት አለውን? በመጨረሻም ተንኮልና<br />

ጭራቃዊነት ድል ተጎናጽፏልን?<br />

ኢትዮጵያ በአቶ መለስ ዜናዊ ቅርጫ መግባት<br />

እ.ኤ.አ ዴሴምበር 2013 የሱዳን የውጭ ጉዳይ<br />

ሚኒስትር የሆኑት ዓሊ ካርቲ የኢትዮጵያ<br />

እና የሱዳን ገዥ አካላቶች “ፋሻጋ እየተባለ<br />

በሚጠራው አካባቢ የነበረውን የድንበር<br />

አለመግባባት እና በሌሎች አካቢዎችም ያሉትን<br />

የድንበር ማካለል ስራዎችንም በሰላማዊ<br />

መንገድ ለማጠናቀቅ ስምምነት አድርገናል“<br />

በማለት በግልጽ ተናግረዋል፡፡ ስለሁለቱ አገር<br />

መሪዎች አስመልክቶ ካርቲ እንዲህ ብለዋል፣<br />

“የመጨረሻውን የማካለል ስራ ለመተግበር<br />

ታሪካዊ ስምምነት አድርገናል፡፡“ የሱዳን የውጭ<br />

ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት በኢትዮጵያ እና<br />

በሱዳን መካከል ያሉትን “የድንበር ውዝግቦች”<br />

በማስመልከት ለሚቀርቡ አስተያየቶች ሁሉ<br />

ምንም ዓይነት ሀሳብ እንደማይቀበል ጠቅሶ<br />

ሲናገር፣ “በጠረፉ በተወሰኑ የወሰን ድንበር ነጥብ<br />

ቦታዎች ላይ“ በጣም ቀላል የሆኑ አለመግባባቶች<br />

ከመኖር በስተቀር ሌላ ችግር እንደሌለ አስረግጠው<br />

ተናግረዋል፡፡ ባለፉት ሳምንታት የኢትዮጵያ<br />

የውጭ ግንኙነት መምሪያ እንደ ዔሌ አንገቱን<br />

ብቅ ጥልቅ እያደረገ በድብቅነት እና ማደናገር<br />

በተላበሰ ስልት/strategy “የድንበር ማካለሉን<br />

ጉዳይ“ እና “መጠነ-ሰፊ ጠቀሜታ“ አላቸው እያለ<br />

ከበሮ የሚደልቅላቸውን “የደህንነት ትብብር<br />

ስምምነት፣ የኢኮኖሚ፣ የግብርና፣ የትምህርት<br />

እና የባህል“ “የስትራቴጅክ ስምምነት ማዕቀፍ“<br />

በማለት በሚጠራቸው ጉዳዮች ላይ እምነት<br />

እንዲያድርብን የፕሮፓጋንዳ ዘመቻዎችን<br />

በመሰለቅ ጊዜውን በከንቱ አሳልፏል፡፡<br />

እ.ኤ.አ በ2001 “ለድንበር ውዝግቡ” ይሰጡ<br />

የነበሩት ምክንያቶች አሁን እየተሰጡ ካሉት<br />

ምክንያቶች ፍጹም የተለዩ ነበሩ፡፡ በዚያን ጊዜ<br />

የሱዳን ገዥ አካል እንደገለጸው የድንበር ማካለሉ<br />

ስራ አስፈላጊነቱ “የአልቃዳሪፍን ግዛት በሰሜን<br />

ኢትዮጵያ ከሚገኘው የትግራይ ግዛት ጋር<br />

‘ለማልማት እና ለማቆራኘት‘ የሚል ነበር…<br />

ሁለቱ አካባቢዎች በጣም ለም የነበሩ ሲሆኑ፣<br />

ከዚህም በላይ አልቃዳሪፍ ለሱዳን የዳቦ ቅርጫት<br />

ተደርጎ የሚቆጠር ነበር… ከአልቃዳሪፍ እስከ<br />

መቀሌ ያለው የመኪና መንገድ…እየተጠገነ እና<br />

ደረጃው ከፍ እየተደረገ ነው… የትግራይ ግዛት<br />

ከዚህ በመነሳት በዚህ በኩል ወደ ቀይ ባህር<br />

የሚያሸጋግረው ዕድል ስለሚያገኝ እና አልቃዳሪፍ<br />

ደግሞ ከፖርት ሱዳን ጋር የሚያገናኘው ስለሆነ<br />

ተቃሚ ይሆናል፡፡ በዚህም መሰረት ፖርት ሱዳን<br />

ለመቀሌ በኤርትራ ግዛት ከሚገኘው የአሰብ<br />

ወደብ እና በሶማሌ ግዛት ከሚገኘው የበርበራ<br />

ወደብ የበለጠ ቅርብ ትሆናለች…“ የሚል ነበር፡፡<br />

እ.ኤ.አ በ2008 አቶ መለስ ዜናዊ ከሱዳን ጋር<br />

የተደረገውን “ስምምነት” አስመልክቶ በውሸት<br />

ባህር ውስጥ እየተንቦጫረቁ የጭቃ ጅራፋቸውን<br />

ማጮህ ጀመሩ፡፡ በዚያው ዓመት በግንቦት ወር<br />

ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው<br />

ሙልጭ አድርጎ በመካድ ለመጀመሪያ ጊዜ<br />

አንድም ጋት የሚሆን የኢትዮጵያን መሬት<br />

ለሱዳን አሳልፎ ለመስጠት የተደረገ ስምምነት<br />

የለም የሚል መግለጫ ሰጠ፡፡ ያ መግለጫ<br />

በውጭ የሚገኙትን “የዜና አውታሮች” እና<br />

“ኃላፊነት የማይሰማቸው” በበሬ ወለደ የፈጠራ<br />

ወሬ የተሰማሩ ሽብር እና ፍርሀትን በህብረተሰቡ<br />

ዘንድ የሚነዙ አሸባሪዎች ናቸው በማለት<br />

ከሷቸው ነበር፡፡ የሱዳን ባለስልጣኖች ግን ያንን<br />

መግለጫ በሚጻረር መልኩ “ከኢትዮጵያ መሬት<br />

እንዳገኙ“ በይፋ በአደባባይ ተናግረዋል፡፡ በግንቦት<br />

አጋማሽ አቶ መለስ እና አጫፋሪዎቻቸው<br />

የመሬት ማደሉን ሚስጥር ደብቀው ማቆየት<br />

ባለመቻላቸው ወደ ቀድሞው ታሪካቸው<br />

ለመመለስ ተገደዋል፡፡ በድንበር ማካለሉ ወቅት<br />

አንዳንድ የቅድመ ስራ እንቅስቃሴዎች ብቻ<br />

እንደተከናወኑ፣ እናም የተጠናቀቀ ነገር የለም<br />

በማለት በግልጽ ተናግረዋል፡፡ በቀናት ጊዜ<br />

ውስጥ አቶ መለስ እና አጫፋሪዎቻቸው ሌላ<br />

አዲስ ቅጥፈትን ፈብርከው ብቅ አሉ፡፡ የሆነው<br />

“ቀደም ሲል በንጉሱ እና በደርግ ዘመን ከሱዳን<br />

ጋር የተደረጉ ስምምነቶችን ተግባራዊ አደረግን”<br />

ብለው ጭራ ቀረሽ ዉሸት ፈጠሩ፡፡<br />

የኢትዮ ሱዳን የድንበር ጉዳይ ኮሚቴ ጉዳዩን<br />

በግልጽ ሲያቀርበው እና በተጨባጭ በድንበሩ<br />

ባሉ አካባቢዎች ላይ ምን እየተደረገ እንዳለ ይፋ<br />

ሲያደርግ እስከ አፍ ጢሙ ተቀብትቶ/ሞልቶ<br />

የነበረው የውሸት ጎተራ መፈረካከስ ጀመረ፡፡<br />

በአቶ መለስ ለሱዳን መሬት ዕደላ ፖሊሲ<br />

ምክንያት የተጎዱ ዜጎቻችን ለአሜሪካ ድምጽ<br />

የአማርኛው አገልግሎት እና ለሌሎች ዓለም<br />

አቀፍ ብዙሃን መገናኛ ተቋማት ቃለመጠይቅ<br />

መስጠት ጀመሩ፡፡ በመሬት ዕደላው ምክንያት<br />

ቀጥተኛ ተጎጅ የሆኑ ወገኖቻችን አያት ቅደመ<br />

አያቶቻቸው ጠብቀው ያቆዩት መሬት በሱዳን<br />

ኃይሎች እየተወረረ ይዞታቸው ሲወሰድባቸው<br />

እና ከቀያቸው እና እትብቶቻቸው ከተቀበሩባቸው<br />

ቦታዎች ሲባረሩ የነበረውን ሁኔታ በመረረ<br />

አኳኋን የተሰማቸውን ቅሬታ በሰፊው ማሰማት<br />

ጀመሩ፡፡ የእርሻ መሳሪያዎቻቸው እና የመገልገያ<br />

ቁሳቁሶች በሱዳን ወራሪ ኃይሎች መወረሱን<br />

ገለፁ:: እንዲሁም በርካታ ኢትዮጵያውያን<br />

በሱዳን እስር ቤቶችም ታስረው እንዲማቅቁ<br />

አስታወቁ፡፡ በዚያን ጊዜ አቶ መለስ ምንም<br />

ምርጫ አልነበራቸውም፣ በግዴታ ሳይወዱ<br />

መሬት ለመስጠት ከሱዳን ጋር መፈራረማቸውን<br />

ለማመን ተገደዋል፡፡ እ.ኤ.አ በሜይ 2008<br />

አቶ መለስ ከኦማር አልባሽር ጋር ያደረጉትን<br />

ስምምነት እንዲህ በማለት ይፋ አድርገዋል፣ “እኛ<br />

ኢትዮጵያውያን እና የሱዳን መንግስት የድንበር<br />

ማካለሉ ስራ በሚሰራበት ወቅት ከሁሉቱም<br />

ወገን አንድም ዜጋ እንዳይፈናቀል ለማድረግ<br />

ስምምነት ተፈራርመናል… በ1996 የወሰድነውን<br />

መሬት መልሰን ለሱዳን ሰጥተናል፣ ይህ መሬት<br />

ከ1996 ዓ.ም በፊት የሱዳን ገበሬዎች ይዞታ<br />

ነበር፡፡ አንዳንድ የብዙሃን መገናኛ ተቋማት<br />

እንደሚያናፍሱት ሳይሆን በድንበሩ ዙሪያ አካባቢ<br />

አንድም የተፈናቀለ ዜጋ የለም፡፡” እ.ኤ.አ በ2008<br />

በዊክሊስ (የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ አመራር<br />

ሚስጥር ሰነድ) ሌላ ወሳኝ የሆኑ መረጃዎች<br />

ይፋ ተደርገዋል፡፡ “የቀድሞው የህዝባዊ ወያኔ<br />

ሃርነት ትግራይ ማዕከለዊ ኮሚቴ አባል እና<br />

የቀድሞው የመከላከያ ሚኒስትር የነበሩት አቶ<br />

ስዬ አብርሃ እንዲህ በማለት ተናግረዋል፣ ‘አቶ<br />

መለስ በኢትዮጵያ እና በሱዳን መካከል ተፈጥሮ<br />

የነበረውን የድንበር ውዝግብ ውጥረት ለማርገብ<br />

ጥረት በሚያደርጉበት ወቅት “ለአማራ ክልል<br />

ትልቅ ዋጋ ሊያስከፍል የሚችል ግዙፍ መሬት“<br />

አቶ መለስ ለሱዳን ሰጥተዋል፡፡ እናም የአቶ<br />

መለስ አገዛዝ “በድብቅ ይዞ ለማቆየት ሞክሯል”<br />

አሉ አቶ ስዬ አብርሃ::<br />

ቀደም ሲል አቶ መለስ፣ አሁን ደግሞ የዕኩይ<br />

ምግባር ውርስ አጫፋሪዎቻቸው ያንን ስምምነት<br />

“በድብቅ ይዘው ለማቆየት” በመውተርተር እና<br />

በመዳከር ላይ ይገኛሉ፡፡ ሆኖም ግን እ.ኤ.አ<br />

በ2008 አቶ መለስ ከኦማር አልባሽር ጋር<br />

ባደረጉት ስምምነት ላይ የሰጡት መግለጫ<br />

አንዳንድ ጠቃሚ ምልክቶችን ይሰጣል፡፡<br />

እራሳቸው አቶ መለስ ባመኑት እ.ኤ.አ በግንቦት<br />

2008 በእርሳቸው እና በኦማር አልባሽር መካከል<br />

በተደረገው “የመሬት መስጠት ስምምነት”<br />

ዝርዝር የስምምነቱን ሁኔታ የሚያመላክት<br />

መሆኑ የሚያጣያይቅ አይደለም፡፡ “የስምምነቱን”<br />

ሁኔታ ስናጠናው አቶ መለስ በስምምነት መዝገቡ<br />

ላይ በርካታ ጠቃሚ ማስረጃዎችን አስቀምጠዋል፡<br />

፡ “ስምምነቱ” 1ኛ) መሬቱ በሚሰጥባቸው<br />

አካባቢዎች ሰዎችን ሊያፈናቅል የሚችል ጥያቄ<br />

መነሳት እንደሌለበት 2ኛ) ከድንበር ማካለሉ<br />

ጉዳይ ጋር በተያያዘ መልኩ ከማካለል ስራው<br />

ጋር ተያይዞ ጉዳት የሚደርስባቸውን ሰዎች<br />

ጥቅሞች የማስጠበቅ ሁኔታ መኖር እንዳለበት<br />

3ኛ) በኢትጵያውያን ገበሬዎች በህገወጥነት<br />

መልክ ተይዞ የነበረ የተባለውን መሬት ለሱዳን<br />

ገበሬዎች የባለቤትነት መብትን ማስጠበቅ 4ኛ)<br />

በ1996 ዓ.ም በህገወጥ መልክ በኢትዮጵያውያን<br />

ተይዞ የነበረውን መሬት ለሱዳናውያን መመለስ<br />

የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡<br />

በአቶ መለስ ፈቃድ እና አዛዥነት በእራሳቸው እና<br />

በኦማር አልባሽር የተፈረመው መሬት የመስጠት<br />

ስምምነት “የ1902 የግዌን መስመር/Gwen<br />

Line of 1902” (የ1902 የአንግሊዝ-ኢትዮጵያ<br />

ስምምነት) እየተባለ የሚጠራው “በኢትዮጵያ<br />

እና በሱዳን መካከል ያለውን ድንበር” መስመር<br />

ማስያዝ ከሚለው ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት<br />

እንደሌለው መገንዘብ ሊሰመርበት የሚገባ ጉዳይ<br />

ነው፡፡ እንደዚሁም እ.ኤ.አ ከ1974 በፊት በንጉሱ<br />

ዘመን እና በደርግ ዘመን ከ1995 እስከ 1991<br />

ድረስ የተረቀቁ እና የተፈረሙ የድንበር መካለል<br />

ወይም ደግሞ መፍትሄ መስጠት ስምምነቶች ካሉ<br />

ከዚህ ስምምነት ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት<br />

የላቸውም፡፡ እ.ኤ.አ ከ1996 መጀመሪያ አካባቢ<br />

ጀምሮ አቶ መለስ በእራሳቸው ፈቃድ ከድንበር<br />

እና ተመሳሳይ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ መልኩ<br />

ያደረጉት “ስምምነት” በአቶ መለስ ግላዊ አተያይ<br />

የሱዳን መሬት በኢትዮጵያውያን በኃይል የተቀማ<br />

ነው በማለት በግላቸው ያደረጉት ህገወጥ እርምጃ<br />

እንጅ ሌላ ምንም ዓይነት ማስረጃ የሌለው<br />

እርባናቢሰ ስብከት መሆኑ በውል ሊጤን ይገባል፡<br />

፡<br />

የኢትዮጵያን “ግዙፍ መሬቶች” በድብቅ እና<br />

ለህዝብ ይፋ ሳያደርጉ በሚስጥር ለሱዳን<br />

የሚሰጡበት፡፡<br />

ምንድን ነው?<br />

የድንበር “ስምምነት” ምክንያቱ<br />

አቶ መለስ እና አቶ ኃይለማርያም በአጠቃላይ<br />

“በድንበር ስምምነቱ” ዙሪያ እያቀረቡት የነበረው<br />

እና ያለው የውሸት ፍብረካ ድሪቶ ሪፖርት<br />

እውነታውን ለመደበቅ ከሚሽመደመደው ድሁር<br />

አስተሳሰባቸው ያለፈ ፋይዳ አይኖረዎም፡<br />

፡ እውነተኛው የድንበር መስጠት ስምምነት<br />

እ.ኤ.አ በ2008 ተጠናቁአል፡፡ በምንም ዓይነት<br />

መልኩ ቢሆን አቶ መለስ “ግዙፍ የሆነ<br />

መሬት ከአማራ ክልል” ቆርሰው ፈርመው፣<br />

አትመው እና አሽገው ለሱዳን መስጠታቸውና<br />

በድብቅ “በድብቅ ተይዞ እንዲቆይ” መጣራቸው<br />

የሚያጠያየቅ ጉዳይ አይደለም፡፡ እ.ኤ.አ በ2014<br />

የኢትዮጵያ የይስሙላው ጠቅላይ ሚኒስትር<br />

አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የአቶ መለስን የበከተ<br />

ውሸት እንደተለመደው “በሀሰት መጋረጃ<br />

ደብቀው” ለዘላለም ለማቆየት በማሰብ ሌላ ዘርዘር<br />

ያለ ፖለቲካዊ ድራማ ለመተወን በመውተርተር<br />

ላይ ይገኛሉ፡፡ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ እና<br />

ጌቶቻቸው የኢትዮጵያን ህዝብ ሊያታልሉ፣<br />

ሊያጭበረብሩ እና በውሸት ሊደልሉ የሚችሉ<br />

ይመስላቸዋል፡፡ እነዚህ የዕኩይ ምግባር ባለቤቶች<br />

መሬትን ያህል ነገር በድብቅ ሸፍኖ የመስጠት<br />

ጨዋታቸውን ኢትዮጵያውያን የማያውቁ እና<br />

የማይገነዘቡ ሞኞች አድርገው ይቆጥራሉ፡<br />

፡ እነርሱ ይህን የሞኝነት ጨዋታቸውን<br />

እንደፈለጉ መጫወት ይችላሉ፣ ሆኖም ግን<br />

አቶ ኃይለማርያም አንድ ጥያቄ እንዲመልሱልኝ<br />

እፈልጋለሁ፣ ይኸውም “ ‘ከአማራ ክልል ግዙፍ<br />

መሬቶችን ቆርሰው የሰጡት’ “ድብቅ የሚስጥር<br />

ስምምነቶችን የት እንዳስቀመጧቸው ሊያሳዩኝ<br />

ይችላሉን? አቶ መለስ እ.ኤ.አ በ2008 እና<br />

አሁን ደግሞ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ እና<br />

የዕኩይ ምግባር አጋሮችዎ የድብቅ ስምምነቶችን<br />

ከህዝብ ፊት ደብቃችሁ ከፊታችሁ ላይ የውሸት<br />

መጋረጃ በማድረግ ለመዝለቅ የምትፈልጉት<br />

ለምንድን ነው?” ከአገር መሬት ቆርሳችሁ<br />

ለባዕድ አገር ስትሰጡ በአገሪቱ ህገመንግስት<br />

ስልጣን ለተሰጠው ፓርላማ (ለተወካዮች ምክር<br />

ቤት) ተብዬው ለይስሙላ እንኳን ቢሆን መቅረብ<br />

የለበትምን“? ህገመንግስቱ የሚለው ሌላ የስርዓቱ<br />

ቁንጮዎች የሚያደርጉት ሌላ! አራምባ እና ቆቦ!<br />

ከላይ ለቀረቡት ጥያቄዎች መልሱ ቀላል ነው፣<br />

እ.ኤ.አ 2008 አቶ መለስ የተናገሩለት “የሚስጥር<br />

ስምምነት“ እና አሁን ደግሞ አቶ ኃይለማርያም<br />

እያነበነቡት እንዳለው አይደለም እውነታው፡፡<br />

ህዝብ ግብር እየከፈለ በሚያስተዳድራቸው መገናኛ<br />

ብዙሀን ብቅ እያሉ በእብሪት የሚያሰራጩት<br />

ነጭ ውሸት ነው፡፡ በእርግጥ አቶ መለስ ይዋሻሉ<br />

ማለት “መለስ ወይስ መቀልበስ” መጠሪያ<br />

ስማቸው ነው፡፡ ሁሉም አፍጥጠዉ ይዋሻሉ፡<br />

፡ አቶ መለስ እና አቶ ኃይለማርያም ከኦማር<br />

አልባሽር ጋር በስምምነቶች ላይ ያስቀመጧቸው<br />

ቃላት፣ ሀረጎች እና ዓረፍተ ነገሮች ወደ እውነት<br />

ተግባርነት የሚሸጋገሩ ከሆነ ከዚህ ጋር ተያይዘው<br />

የሚመጡ አደጋዎች ምን ሊሆኑ ይችላሉ?<br />

በእውነት እነዚህ የኢትዮጵያን ሉዓላዊ የግዛት<br />

አንድነት በመዳፈር መሬቱን እየቆረሱ ለመስጠት<br />

ተፅፈው ተፈረመው የተደበቁ ስምምነቶች የአቶ<br />

መለስን እና የአቶ ኃይለማርያምን ቀጣፊነት<br />

ወደ ገፅ 15 ይዞራል


ነገረ-ኢትዮጵያ ቅፅ 1 ቁጥር 2 የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. 8<br />

ዝክረ ታሪክ<br />

ፋሽስት ገዳይ ባየር በራሪ፣<br />

ድንግል ጠብመንጃ በደም ነካሪ<br />

ከፉከራ ስነ-ቃል የተወሰደ<br />

ታዴዎስ ታንቱ<br />

የመ.ሣ.ቁጥር 43414<br />

የኢትዮጵያ ሰራዊት በታላቅ ጀግንነት<br />

ከፍተኛ መስዋዕትነት ከፍሏል!<br />

ከአውሮፕላን የዘነበውን የመርዝ<br />

ጭስ መቋቋም ግን ሳይችል ቀርቷል፡<br />

፡ በምክንያቱ ምክንያት የፋሽስት<br />

ኢጣሊያ ወራሪ ኃይል የበላይነትን<br />

ተቀዳጅቷል፡፡ በአሸናፊነት ስነ-ልቦና<br />

ታይቷል፡፡ የማይጨው ጊዜያዊ ድል<br />

ፈጽሞ እንደማይቀለበስ ተስፋ ሰንቋል!<br />

የአድዋ ጀግኖች ቀጥታ ተወላጆች<br />

መሆናችንን ማስታወስ እንኳን<br />

ተስኖታል፡፡ በዕብሪት የኢትዮጵያን<br />

መሬት ረግጧል፡፡ ወደ አዲስ አበባ<br />

ይገሰግሳል! ይገሰግሳል! ይገሰግሳል!<br />

ይገሰግሳል! አሁን ደሴ ገብቷል! ቀዳማዊ<br />

ኃይለ ስላሴ መሰደዳቸውን ሰምቷል፡<br />

፡ ዋና ከተማችንን በቶሎ ለመያዝ<br />

ቋምጧል! ከፊቱ ሊቆም የሚችል<br />

ጀግና ከቶም ሊኖር እንደማይችል<br />

ገምቷል! ጊዜአዊ ድል ዘላለማዊ<br />

አሸናፊነትን እንደማይወክል ለመገንዘብ<br />

አስተውሎት ጎድሎታል! የማን<br />

አህሎኝነት መንፈስ ለብሷል! ባሁኑ<br />

ሰዓት ሮቤ ደርሷል፡፡ ይግተለተላል!<br />

ይግተለተላል! ይግተለተላል! እንዲህ<br />

በቀላሉ ኢትዮጵያን ቅኝ ግዛት ማድረግ<br />

የሚችል መስሎታል፡፡ እርግጥ ነው!<br />

ከማይጨው ጦርነት ወዲህ የከፋ ነገር<br />

ሳያጋጥመው መጥቷል፡፡ ይህ ሁኔታ<br />

ሊቀጥል እንደማይችል ግን በጥቂት<br />

ጊዜያት ውስጥ ይታያል! ማን ለማን<br />

ይገዛል? የጀግኖች መሬት የፋሽስቶች<br />

መቃብር ይሆናል! የማይቀር እውነት<br />

በተግባር ይረጋገጣል! የጥንታዊት<br />

ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች በመንገዱ<br />

ግራና ቀኝ ተነጥፈዋል፡፡ በነፍስ ወከፍ<br />

ጦር መሳሪያ ቆርጠው ተነስተዋል!<br />

ድም! ድም! ድም! ዱዋ! ዱዋ! ዱዋ!<br />

የኢትዮጵያ አርበኞች የቅድሚያ<br />

ተነሳሽነት ወስደዋል! አከታትለው<br />

ተኩሰዋል! ቆራጡ የኢትዮጵያ ጀግና<br />

ተሰማ እርገጤ ክንዱን ሳይንተራስ<br />

የፋሽስት ኢጣሊያ ወራሪ ኃይል<br />

በኢትዮጵያ ምድር ተረጋግቶ ሊኖር<br />

እንደማይችል ከአቋም ተነስቶ ወደ<br />

ተግባር ገብቷል! የጦረኛ ዘር የጀግና<br />

ልጅ እሱ ማንን ይፈራል? ጦርነቱ<br />

አሁን ተጋግሏል! ከክብሩ ይልቅ<br />

ሆዱን የሚወድድ ከእንሰሳ ይመደባል!<br />

ከማንም ህይወት የሀገር ህልውና<br />

ይቀድማል! የነጻነትን ትርጉም<br />

የሚያውቅ ለነፍሱ አይሰስትም!<br />

ለጀግና ሞት ሰርጉ ነው! የጥንታዊት<br />

ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች<br />

ቆርጠዋል! በደፈጣ ውጊያ የበላይነትን<br />

ጨብጠዋል! የፋሽስት ኢጣሊያ ወራሪ<br />

ኃይል ተዋጊዎች ተረፍርፈዋል!<br />

በማያውቁት መንገድ አውቀው<br />

መጥተዋል! መጥተውም አልቀዋል!<br />

የሰውን ፈላጊ የራሱን ያጣል! ጦርነቱ<br />

ሌሊትም ቀጥሏል! ጀግና መች ሞት<br />

ይፈራል! ጦርነቱ ተጋግሏል! የፋሽስት<br />

ኢጣሊያ ወራሪ ኃይል ተዋጊዎች<br />

ተጠቅተዋል! የእሳት ራት ሆነዋል!<br />

አሁንም ግን በመፍጨርጨር ሂደት<br />

ገፍተዋል! የኢትዮጵያ ጀግኖች ደግሞ<br />

ከማሸነፍ ያነሰ ውጤት ላለማስመዝገብ<br />

ወስነዋል! ሰባት መኪና ሙሉ የነበረው<br />

የፋሽስት ኢጣሊያ ወራሪ ኃይል አሁን<br />

በጣም መንምኗል! ታሪክ ይመሰክራል!<br />

የወገን ትግል በድል ተጠናቅቋል!<br />

ጀግናው አርበኛ ተሰማ እርገጤ ወገንን<br />

አኮራ! ይህ በታሪካችን የጥንታዊት<br />

ኢትዮጵያ የጀግኖች አርበኞች የትግልና<br />

ድል ቀጥታ ድምጽ ነው! ከሸዋ ጠቅላይ<br />

ግዛት ከደብረ ሲና ጦር ሜዳ! ግንቦት<br />

23 ቀን 1928 ዓ.ም፡፡<br />

ቆፍጣናው የኢትዮጵያ አንበሳ ተሰማ<br />

እርገጤ አሁንም በከፍተኛ የውጊያ<br />

ስነ-ልቦና ይስተዋላል! ጀግናው አርበኛ<br />

ተሰማ እርገጤ ከውስን የውጊያ<br />

ሜዳ መልስ ረግቶ የሚቀመጥ ሰው<br />

አልነበረም፡፡ የፋሽስት ኢጣሊያ ወራሪ<br />

ኃይል ለአንዴና ለዘለዓለም ኢትዮጵያን<br />

ለቅቆ እነዲወጣ ለማድረግ ጽኑ የግዳጅ<br />

አቋም ይዟል፡፡ የተፈለገው መስዋዕትነት<br />

ሁሉ ይከፈላል! ጀግና ከነጻነት<br />

ያነሰ ነገር አይፈልግም! ለዓላማው<br />

ደግሞ እስከ ህይወት መስዋዕትነት<br />

ይዘልቃል፡፡ ቆራጡ የጦር ሰው ተሰማ<br />

እርገጤ አሁን በተጠንቀቅ ቆሟል!<br />

ከመስክ ስምሪት የተገኙ መረጃዎችን<br />

ይተነትናል፡፡ ከኢትዮጵያ የቁርጥ<br />

ቀን ጀግኖች ጋር በስፋት የሀሳብ<br />

ልውውጥ አድርጓል! በጥቂት ጊዜያት<br />

ውስጥ ተጨባጭ ተኩስ ይከፈታል!<br />

የኢትዮጵያ አርበኞች ወደ ወራሪው<br />

ኃይል በቀጥታ ተጠግተዋል! ወራሪው<br />

ኃይል በቀጥታ ወደ አዲስ አበባ<br />

ሲተምም ይታያል! ለጊዜው በውጊያ<br />

ስነ-ልቦና ላይ እንዳልነበረ ታውቋል!<br />

ጀግኖቹ የኢትዮጵያ አርበኞች አሁን<br />

ለወራሪው ኃይል የጉዞ መስመር<br />

በጣም ቀርበዋል! ድም! ድም! ድም!<br />

ዱዋ! ዱዋ! ዱዋ! ጀግኖቹ የኢትዮጵያ<br />

አርበኞች ቅድሚያ ተነሳሽነቱን<br />

በተግባር ወስደዋል፡፡ የፋሽስት ኢጣሊያ<br />

ወራሪ ኃይል ተደነባብሯል! ሆኖም<br />

የአጸፋ ተኩስ ለማሰማት የደቂቃ<br />

ክፍልፋይ ጊዜ በቅቶት ተገኝቷል፡፡<br />

ማይጨው ላይ የነበረው የኢትዮጵያ<br />

ሰራዊት በሙሉ የመጣበት ያህል<br />

ደንግጧል! ሳያስበው አስቦ ያደፈጠ<br />

ጀግና አጋጥሞታል! ተኩሱ ቀልጧል!<br />

እንደ ፈንድሻ ይንጣጣል፡፡ ለሰዓታት<br />

ቀጥሏል! የፋሽስት ኢጣሊያ ወራሪ<br />

ኃይል ድባቅ ተመትቷል! ድል በትግል<br />

ተመዝግቧል! ታሪክ ይናገራል! ይህ<br />

በታሪካችን የጥንታዊት ኢትዮጵያ<br />

የጀግኖች አርበኞች የጦርነትና የድል<br />

ቀጥታ ድምጽ ነው! ከሸዋ ጠቅላይ<br />

ግዛት ከጣርማ በር የጦር ሜዳ! ሐምሌ<br />

5 ቀን 1928 ዓ.ም፡፡<br />

ውድ የኢትዮጵያ ጀግና ተሰማ እርገጤ<br />

ከፍልሚያ በኋላ አሁንም ሌላ ፍልሚያ<br />

ይጠብቀዋል! ወሳኙን ድል ለማምጣት<br />

ቆርጦ ተነስቷል! በየቀኑ በፍቃደኝነት<br />

ወደ አርበኝነት የገቡ ወጣቶች<br />

የጦር መሳሪያ እንዲታጠቁ ጥረት<br />

ያደርጋል! ወራሪው ኃይል ዘመናዊ<br />

የጦር መሳሪያ ታጥቋል! ከኢትዮጵያ<br />

አርበኞች አንዳንዶቹ ጠብመንጃ<br />

እንዳልነበራቸው ታውቋል! ብሄራዊ<br />

ስሜት የህሊና እረፍት ነስቷቸው<br />

ቤታቸውን አቃጥለው በሬዎቻቸውን<br />

ሸጠው፣ እርሻቸውን ትተው ከጀግኖች<br />

ጋር ተቀላቅለዋል! ጦር፣ ጋሻና ጎራዴ<br />

ብቻ የያዙም ተስተውለዋል! የተቃጠለ<br />

ብሄራዊ ስሜት ደግሞ ከጦር መሳሪያም<br />

ይልቃል! እርግጥ ነው! የማያቅማማ<br />

ልብ ፈጠነም ዘገየ ለድል ያበቃል!<br />

ጀግናው አርበኛ ተሰማ እርገጤ አሁን<br />

ከመስክ ስምሪት ወታደራዊ መረጃ<br />

ደርሶታል! የፋሽስት ኢጣሊያ ወራሪ<br />

ኃይል ተዋጊዎች በቅርብ የሰፈሩበትን<br />

ቦታ ለይቶ አውቆታል! ጀግና ለፋሽስት<br />

ጊዜ አይሰጥም! ቆራጡ አርበኛ<br />

ወራሪው ኃይል ዘመናዊ የጦር መሳሪያ ታጥቋል! ከኢትዮጵያ አርበኞች አንዳንዶቹ ጠብመንጃ<br />

እንዳልነበራቸው ታውቋል! ብሄራዊ ስሜት የህሊና እረፍት ነስቷቸው ቤታቸውን አቃጥለው<br />

በሬዎቻቸውን ሸጠው፣ እርሻቸውን ትተው ከጀግኖች ጋር ተቀላቅለዋል! ጦር፣ ጋሻና ጎራዴ ብቻ<br />

የያዙም ተስተውለዋል! የተቃጠለ ብሄራዊ ስሜት ደግሞ ከጦር መሳሪያም ይልቃል! እርግጥ<br />

ነው! የማያቅማማ ልብ ፈጠነም ዘገየ ለድል ያበቃል!<br />

ተሰማ እርገጤ አሁን ተንቀሳቅሷል፡<br />

፡ አርበኞች ምድብ መስመራቸውን<br />

ይዘዋል! ተጠጋግቶ መጓዝ ክልክል<br />

ነው! ተፈነጣጥሮ በቅርብ ርቀት<br />

እየተጠባበቁ መጓዝ የግድ ይላል፡<br />

፡ ሁሉም በየምድብ መስመራቸው<br />

ጉዟቸውን ቀጥለዋል!<br />

ጀግናው ተሰማ እርገጤ ከጥቂት<br />

አርበኞች ጋር ወራሪው ኃይል<br />

ከሰፈረበት ግራ አቅጣጫውን ይዟል!<br />

አርበኞች የነፍስ ወከፍ የጦር<br />

መሳሪያቸውን ታጥቀዋል! ጀግናው<br />

ተሰማ እርገጤ ዘወትር በጥቂት<br />

መስዋዕትነት ታላቅ ድል ለማስመዝገብ<br />

በቁርጠኝነትና በዓላማ ጽናት ይዋጋል!<br />

የተቃጠለ ብሄራዊ ስሜት ተላብሷል!<br />

ማቅማማት አያውቅም! መስዋዕት<br />

መሆን ወይም ድል! አርበኛ ሲሰዋ<br />

በእልህ የውጊያ ዝግጁነት መንፈሱ<br />

ይነሳሳል! የፋሽስት ኢጣሊያ ወራሪ<br />

ኃይል የኢትዮጵያን መሬት ለቅቆ<br />

እስካልወጣ ለአፍታም ጦርነቱን<br />

ላለማቆም ቆርጧል! ጥቁር በነጭ<br />

እንዴት ይገዛል? የአድዋ ጀግኖች<br />

አጥንት እሾህ ሆኖ ይውጋን! ለጣሊያን<br />

ፈጽሞ አንገዛም! ይህ የአርበኞች ድምጽ<br />

ነው! ኢትዮጵያ ጀግና ነበራት! ነበራት!<br />

ነበራት! አሁን ቆራጦቹ የጥንታዊት<br />

ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች የፋሽስት<br />

ኢጣሊያ ወራሪ ኃይል ተዋጊ ከሰፈረበት<br />

ቦታ ደርሰዋል! ሁሉም በምድብ<br />

መስመራቸው ከተኩስ ቦታቸው ላይ<br />

ተገኝተዋል፡፡ የወራሪውን ኃይል ሰፈር<br />

ከብበዋል! ለተኩስ ዝግጁ! ለግድያ<br />

ዝግጁ! ለምርኮ ዝግጁ! የኢትዮጵያ<br />

ጀግና መቼ ፈርቶ ያውቃል? ድም!<br />

ድም! ድም! ዱዋ! ዱዋ! ዱዋ!<br />

ጦርነቱ በኢትዮጵያ ጀግኖች ቅድሚያ<br />

ተነሳሽነት ተከፍቷል! ወራሪው<br />

ኀይል የአጸፋ ተኩስ ከፍቷል! አሁን<br />

መከበባቸውን አውቀዋል፡፡ የተፋፋመ<br />

ተኩስ ቀጥሏል! እሳት ይዘንባል!<br />

ጀግና ለክብሩ ቆርጧል! የፋሽስት<br />

ወራሪ ኃይል ለማምለጥ ይተኩሳል!<br />

የኢትዮጵያ አርበኞች ደግሞ የወራሪው<br />

ኃይል ተዋጊዎችን በነበሩበት ከአፈር<br />

ጋር ለማዋሀድ በተግባር ተነስተዋል!<br />

ጦርነቱ በተከፈተ በጥቂት ጊዜያት<br />

ውስጥ በወራሪው ኃይል ላይ ከፍተኛ<br />

ጉዳት ደርሷል! የኢትዮጵያ አርበኞች<br />

የበላይነት ይዘዋል! ተኩሱ ቀጥሏል!<br />

ይህ የታሪክ ድምጽ ነው! በአሁኑ<br />

ሰዓት በኢትዮጵያ ታሪክ በሸዋ ጠቅላይ<br />

ግዛት ውስጥ በልበላ በተባለ ቦታ<br />

ከጀግኖች አርበኞች ጋር በተፋፋመ<br />

ጦርነት መካከል ቆመናል!<br />

በርካታ የፋሽስት ወራሪ ኃይል<br />

ተዋጊዎች ተደምስሰዋል! አንዳንዶች<br />

ተሾሎክልከው አምልጠዋል፡፡ የነበሩበት<br />

ድንኳን ነድዷል! ሬሳ ተዝረክርኮ<br />

ይታያል! በማያጠራጥር መልኩ<br />

አርበኞች ድልን ተጎናጽፈዋል! ቆራጡ<br />

አርበኞ ተሰማ እርገጤ እንደ አንበሳ<br />

ይጎማለላል! ባሁኑ ሰዓት በየቦታው<br />

የተዝረከረከውን የወራሪው ፋሽስት<br />

ሬሳ በየአቅጣጫው ያስተውላል!<br />

ቆራጡ የህዝብ ባለአደራና የሀገር<br />

ባለውለታ ተሰማ እርገጤ በዚሁ<br />

በበልበላ ጦርነት ጣሊያኖችን የገደለ<br />

ከመሆኑም በላይ በርካታ የፋሽስት<br />

ተዋጊ ባንዳዎችን እንደ ገብስ አጭዷል!<br />

የጦር መሳሪያዎችንም ማርኳል!<br />

ድል አድራጊው የኢትዮጵያ አርበኛ<br />

አሁን ወራሪው ኃይል ሲፈረጥጥ<br />

ያዝረከረከውን የጦር መሳሪያ<br />

በመሰብሰብ ሂደት ላይ ይታያል!<br />

አንዳንድ አርበኞች ከወራሪው ኃይል<br />

ተዋጊዎች ሬሳ ወገብ ላይ ዝናር ሲፈቱ<br />

ይስተዋላል! ይህ የታሪክ ድምጽ ነው!<br />

የኢትዮጵያ አርበኞች ከፋሽስቶች<br />

ሬሳ ላይ የጦር መሳሪያ ከመፍታት<br />

በስተቀር ልብስ ፈጽሞ አይገፍፉም!<br />

ነውር ነው! ይህ በታሪካችን<br />

ለአንድነታቸው፣ ለሉዓላዊነታቸው፣<br />

እንዲሁም ለሐይማኖታቸው ቀናዒ<br />

የነበሩ የጥንታዊት ኢትዮጵያ የጀግኖች<br />

አርበኞች የጦርነትና የድል ድምጽ<br />

ነው! ከሸዋ ጠቅላይ ግዛት ከበልበላ<br />

ጦር ሜዳ! ጳጉሜ 2 ቀን 1928 ዓ.ም!<br />

ቆፍጣናው አርበኛ ተሰማ እርገጤ<br />

አሁን በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ውስጥ<br />

ግፋይታ በተባለ መንድር ድርጅታዊ<br />

አቅሙን በማጎልበት ስራ ተጠምዷል!<br />

ወጣቶች ወደ አርበኝነት እንዲገቡ<br />

በተከታታይ ይቀሰቅሳል! በምስጢር<br />

የጦር መሳሪያ ይሸምታል! በከፍተኛ<br />

ደረጃ በውጊያ ስነ-ልቦና ላይ ይስተዋላል!<br />

የፋሽስት ወራሪ ኃይል ግን ጀግናው<br />

ተሰማ እርገጤ የነበረበትን ቦታ<br />

ለይቶ አውቋል! ባንዳ ሹክ ብሎታል!<br />

በዚህን ጊዜ ወራሪው ኃይል ጀግናውን<br />

ተሰማ እርገጤን ለመግደል ቆርጦ<br />

መነሳቱ ተሰማ! ቆፍጣናው ተዋጊ<br />

ተሰማ እርገጤ መረጃው ደርሶታል!<br />

ታዲያ ምን ሊያደር ይችላል?<br />

ቆፍጣናው ተዋጊ ተሰማ እርገጤ<br />

ማድረግ የነበረበትን መቼ አጣ?<br />

በቅድሚያ ገዥ መሬት ይዞ ጠበቀው!<br />

ወራሪው ኃይል አሁን እየትግተለተለ<br />

መጥቶዋል! አርበኛው ተሰማ እርገጤ<br />

ዳቦ በማር ይገምጣል! ወራሪው ኃይል<br />

ተጠግቷል! የኢትዮጵያ አርበኞች ከሳር<br />

ጋር ሳር መስለዋል! ወራሪው በአሰራር<br />

ቀድሟል! ባንዳ ቀድሟል! ጣሊያኖች<br />

ወደ ኋላ ቀርተዋል! መገናኛ መሳሪያ<br />

ይዘዋል! ከጦር መሳሪያ ደግሞ ሽጉጥ<br />

ብቻ ታጥቀዋል! የወራሪው ኃይል<br />

ተዋጊዎች በአሰራር አሁንም ወደ<br />

ፊት ሲጠጉ ይስተዋላል! ድም! ድም!<br />

ድም! ዱዋ! ዱዋ! ዱዋ! የወራሪውን<br />

ኃይል ተዋጊዎች በአሰራር ጉዞ<br />

ከርቀት ዒላማቸው ውስጥ አስገብተው<br />

ይጠባበቁ የነበሩት ጀግኖቹ የኢትዮጵያ<br />

አርበኞች በቅድሚያ ተነሳሽነት ተኩስ<br />

ከፍተዋል! ከፊት የነበሩ ባንዳዎችን<br />

መትተው ጥለዋል! ከወራሪው ኃይል<br />

የአጸፋ ተኩስ በኋላ ጦርነቱ ወዲያው<br />

ተጋግሏል! ነገር ግን ረጅም ሰዓት<br />

አልፈጅም! ቆራጦቹ የኢትዮጵያ<br />

አርበኞች ወዲያው አጥቅተው<br />

የበላይነትን ጨብጠዋል! ጀግናው<br />

አርበኛ ተሰማ እርገጤ የፈረጠጠውን<br />

ባንዳ እያሳደደ ከአፈር ጋር ያዋህድ<br />

ገባ! በርካታ የነፍስ ወከፍ የጦር<br />

መሳሪያዎችንም ማርኳል! ጦርነቱ<br />

በኢትዮጵያ ጀግኖች ድል አድራጊነት<br />

ተጠናቀቀ! ይህ የጥንታዊት ኢትዮጵያ<br />

ጀግኖች አርበኞች ቀጥታ የታሪክ<br />

ድምጽ ነው! ከሸዋ ጠቅላይ ግዛት<br />

ግፋይታ ከተባለ ውጊያ መስክ በቀጥታ<br />

ለዛሬው ተረኛ ትውልድ የሚተላለፍ<br />

የታሪክ ድምጽ ነው! መስከረም 15<br />

ቀን 1929 ዓ.ም!<br />

ቆራጡ የጦር ሰው ተሰማ እርገጤ<br />

ፈጽሞ ሊበገር አልቻለም! በዚህ<br />

ምክንያት የፋሽስት ኢጣሊያ ወራሪ<br />

ኃይል በጣም ተበሳጨ! ተበሳጭቶ<br />

ግን ዝም አላለም! ጀግናውን አርበኛ<br />

ተሰማ እርገጤን ይዞ ለሚያቀርብለት<br />

ከፍተኛ ሹመት እንደሚሰጠው አወጀ!<br />

በተጓዳኝም የአርበኛውን ዘመዶች<br />

ከየቦታው ለቃቅሞ አሰራቸው!<br />

አርበኛው ተሰማ እርገጤ ግን ከአቋሙ<br />

ፍንክች ሳይል ቀርቷል! በሀገር ፍቅር<br />

የተቃጠለው ጀግናው አርበኛ ተሰማ<br />

እርገጤ ከአንድ ድል በኋላ ፋታ<br />

ሳያገኝ ወዲያው ለጦርነት ይዘጋጃል!<br />

ወራሪው ኃይል የግድ ኢትዮጵያን<br />

ለቅቆ መውጣት አለበት፡፡ መፍትሔው<br />

ደግሞ ጦርነት ብቻ መሆኑን አጥብቆ<br />

ያምናል! ይህ የኢትዮጵያ አርበኞች<br />

የማይቀለበስ ውሳኔ ነው! ቆራጡ<br />

አርበኛ ተሰማ እርገጤ አሁን ጨለንቆ<br />

በተባለው ቦታ የሰፈረውን የፋሽሰት<br />

ወራሪ ለመደምሰስ በጉዞ ላይ መሆኑ<br />

ወደ ገፅ 6 ይዞራል


9 የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2 ነገረ-ኢትዮጵያ<br />

ኢትዮጵያ ለምን ኋላ ቀረች?<br />

ክፍል ሁለት<br />

ግርማ ሞገስ<br />

●የኢትዮጵያ የመንግስት ስልጣን<br />

ሽግግር ባህሏ<br />

ለዘጠኝ መቶ አመቶች ላላነሰ ጊዜ<br />

ኢትዮጵያ በዘመናዊ (Secular)<br />

ትምህርት እና ትምህርቱን ተከትሎ<br />

ለሚመጣ ዘመናዊነት እና ስልጣኔ<br />

ጀርባዋን መስጠቷ ለኋላ መቅረቷ<br />

አንዱ አውራ ምክንያት እንደነበር<br />

ባለፈው አንብበናል። በእንቅርት ላይ<br />

ጆሮ ደግፍ እንዲሉ ደግሞ ቢያንስ<br />

ቢያንስ ከአክሱም ስልጣኔ መውደቅ<br />

ወዲህ ጀምሮ አምባገነኑ ህውሃት/<br />

ኢህአዴግ በ1983 ዓ.ም. ስልጣን<br />

እስከጨበጠበት ጊዜ ድረስ በእርስ<br />

በርስ ጦርነት ይፈጸም የነበረው<br />

የመንግስት ሽግግር ባህሏ ኢትዮጵያን<br />

እጅ እና እግሯን ተብትቦ ስለስልጣኔ<br />

የምታስብበት መተንፈሻ ጊዜ እንኳን<br />

እንዳይኖራት አድርጓት ነበር። ስለዚህ<br />

ኢትዮጵያ ከውጭ ወረራ ረጅም<br />

የነፃነት ዘመን ቢኖራትም በስልጣኔ<br />

እንዳትገፋ ያደረጋት ሁለተኛው<br />

አውራ ምክንያት በእርስ በርስ ጦርነት<br />

የሚፈጸመው የመንግስት ሽግግር<br />

ባህሏ ነበር ማለት ይቻላል። በዚህ<br />

ጉዳይ ላይ ተክለ ፃዲክ መኩሪያ፣<br />

ባህሩ ዘውዴ፣ ሃሮልድ ማርኪውስ<br />

እና ፓንክረስት የመሳሰሉ የታሪክ<br />

ምሑራን ብዙ ጽፈውታል።<br />

የመንግስት ሽግግር ባህሏም በበኩሉ<br />

ከስልጣኔ እንድትርቅ አድርጓል።<br />

ለምን ያህል ጊዜ (ስንት አመቶች)?<br />

ግምት መስጠት እንችላለን?<br />

እንሞክር! በኢትዮጵያ ሲደረግ<br />

የነበረው የመንግስት ሽግግር<br />

ታሪካችን ሁለት አኪያሄዶች ነበሩት።<br />

አንደኛው አኪያሄድ ከአንድ ዝርያ<br />

ወደ ሌላ ዝርያ የሚደረግ የመንግስት<br />

ሽግግር ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ<br />

በአንድ ዝርያ ውስጥ ከአባት ወደ<br />

ልጅ የሚፈጸም የመንግስት ስልጣን<br />

ሽግግር ነበር። ሁለቱም አይነት<br />

የመንግስት ሽግግሮች ከጦርነት ነፃ<br />

አልነበሩም። በጦርነቶቹ መካከል<br />

ልዩነት ካለም የጦርነቱ አስከፊነት<br />

መጠነ እና የጦርነቱ እድሜ ብቻ<br />

ነበር።<br />

ለጥናት እንዲያመቸን ካፄ ኢዛና<br />

(321 ዓ.ም.) በፊት ለመንግስት<br />

ሽግግር (ለስልጣን) የተደረጉትን<br />

የእርስ በርስ ጦርነቶች በሙሉ<br />

ከግምት አናስገባም። ጥናታችንን<br />

ይበልጥ ቀላል ለማድረግ ስንል ካፄ<br />

ኢዛና ወዲህ ተሞክረው ያልተሳኩትን<br />

ቁጥር ስፍር የሌላቸው ለመንግስት<br />

ሽግግር የተደረጉ የእርስ በርስ<br />

ጦርነቶች በሙሉ ወደጎን እንተዋለን።<br />

ጥናታችን ካፄ ኢዛና ወዲህ በተደረጉት<br />

የተሳኩ የመንግስት ሽግግሮች ላይ<br />

ያተኩራል። ስለዚህ በ321 ዓ.ም.<br />

በስልጣን ላይ ከነበረው ካፄ ኢዛና<br />

ዘመነ መንግስት ጀምረን እስከ በ1983<br />

ዓ.ም. በእርስ በርስ ጦርነት ስልጣን<br />

የጨበጠው አምባገነኑ የህውሃት/<br />

ኢህአዴግ መንግስት ድረስ ከነበሩት<br />

1662 አመቶች ውስጥ የመንግስት<br />

ሽግግር ባህሏ ስንት አመቶች እጅ<br />

እና እግሯን ተብትቦ በማሰር ስልጣኔ<br />

ከውስጥም እንዳታበቅል እንዳደረጋት<br />

አጠቃላይ ግምት ለመስጠት<br />

እንሞክራለን። እያንዳንዱ የመንግስት<br />

ሽግግር ባህላችን ጦርነት የፈጀው<br />

ጊዜ በዝርዝር ተጽፎ የተላለፈልን<br />

መረጃ የለንም። ለግዜው ማድረግ<br />

የምንችለው እነ ተክለ ፃዲቅ ጽፈው<br />

ካወረሱን ትረካ ግምት ለመውሰድ<br />

መሞከር ነው። እያንዳንዱ የተሳካውም<br />

ያልተሳካውም የመንግስት ሽግግር<br />

የፈጀውን ጊዜ አመት በአመት<br />

የማስላቱን ስራ ለመጪው ትውልድ<br />

ታሪክ ተመራማሪዎች እንተዋለን።<br />

ካፄ ኢዛና (321 ዓ.ም.) ወዲህ<br />

የተደረጉትን ዋናዎቹን የመንግስት<br />

ሽግግሮች<br />

እንደሚከተለው<br />

መከፋፈል እንችላለን፣ (1) ከኢዛና<br />

ዝርያዎች ወደ ንግስት ዮዲት (ቤተ<br />

እስራኤሎች) ዝርያዎች፣ (2) ከቤተ<br />

እስራኤሎች ወደ ላስታው መራ ተክለ<br />

ሃይማኖት (ዛጉዌ ስረወ መንግስት)<br />

ዝርያዎች፣ (3) በ1262 ከላስታ<br />

አገዎች ወደ ሸዋው ይኩኖ አምላክ<br />

ዝርያዎች፣ (4) በ1523 ዓ.ም. ያፄ<br />

ይኩኖ አምላክ ዝርያ ከነበረው ልብነ<br />

ድንግል ወደ ይማም አህመድ (ግራኝ<br />

በሚል የሚታወቁት እና በአባታቸው<br />

የኦጋዴ በእናታቸው ደግሞ የሐረር<br />

ተወላጅ የሆኑት)፣ (4) በጎንደር ካፄ<br />

ገላውዲዎስ 1533-1552) እስከ ዐፄ<br />

እዮዋስ (1747-1761) (በአባት የቋራ<br />

አማራ በእናት ደግሞ የየጁ ኦሮሞ)፣<br />

(5) ከራስ ስሑል እስከ የየጁው<br />

ትንሹ ራስ ዐሊ (ዘመነ መሳፍንት)፣<br />

(5) ካፄ ቴዎድሮስ (1847-1860)<br />

እስከ ሰቆጣው ዐፄ ተክለ ጊዮርጊስ<br />

(1860-1864) ከዚያ ወደ ተምቤኑ<br />

ዐፄ ዮሐንስ (1864-1881) ከዚያ<br />

ወደ ሸዋው ምኒልክ (1882-1906)፣<br />

(6) ከምንሊክ ወደ ልጅ ልጃቸው<br />

ልጅ እያሱ ከዚያ ወደ ምኒልክ ሴት<br />

ልጅ ዘውዲቱ ከዚያ ወደ ኃይለስላሴ<br />

ከዚያ ወደ ደርግ ከዚያ ወደ ህውሃት/<br />

ኢህአዴግ። እነዚህ የመንግስት<br />

ሽግግሮች በሙሉ የተጠናቀቁት<br />

በእርስ በርስ ጦርነት እና ሽብር<br />

ነበር።<br />

ከአባት ወደ ልጅ የተደረጉ የመንግስት<br />

ሽግግሮችም ከሁከት እና ከእርስ በርስ<br />

ጦርነቶች የጸዱ ስላልነበሩ ሁከቱን<br />

እና ጦርነቱን ለመቀነስ ነገስታቱ<br />

ልጆቻቸውን በጠባቂ በሚከተሉት<br />

እስርቤቶች ሆነው የንጉስነት<br />

ተራቸውን (እድላቸውን) እንዲጠብቁ<br />

አድርገዋል። (1) ደብረ ዳሞ አምባ<br />

እስር ቤት፥ በአክሱም ዘመነ መንግስት<br />

በዙፋን ላይ የሚገኘው ንጉሱ ታመመ<br />

በተባለ ቁጥር በቤተ ዘመድ ውስጥ<br />

“ዙፋን ይገባኛል” “ተረኛው እኔ<br />

ነኝ” የሚሉ ሁከቶች እና ጦርነቶች<br />

ይነሱ ነበር። ስለዚህ ይኽን ሁከት<br />

እና የርስ በርስ ጦርነት ለማስወገድ<br />

ነገስታቱ ልጆቻቸውን እና በቅርብ<br />

ከሚዛመዱዋቸው የሚወለዱትን<br />

ጨምረው በትግራይ ከአዲግራት<br />

በስተ ምዕራብ በሚገኘው ደብረ ዳሞ<br />

አምባ ጠባቂ ተደርጎላቸው የንግስና<br />

ተራቸውን እንዲጠብቁ ይደረግ<br />

እንደነበር ተክለ ፃዲቅ መኩሪያ<br />

ይገልጻል።<br />

ከሠርፀ ዘድንግል ወደ ፋሲል አባት (ዐፄ ሱስነየስ) የተደረገው የመንግስት ሽግግር በቀጣይነት የርስ በርስ<br />

ጦርነት ዘመን ነበር። ሠርፀ ሲሞት ለትንሽ ልጁ አቆብ (1590-1595) አወረሰ። የአጎቱ ልጆች ዙፋን<br />

ለኛ ይገባል የሚል ጦርነት ከፍተው ዙፋኑ ከአቆብ ወደ ዘድንግል (1595-1596) ከዚያ ከዘድንግል<br />

እንደገና ወደ ያእቆብ (1596-1598) ከዚያ በመጨረሻ ወደ ፋሲል አባት ሱስነየስ<br />

(1598-1625) የተሸጋገረው በድምሩ 10 አመቶች የርስ በርስ ጦርነት ከተደረገ ቧላ ነበር።<br />

(2) ግሸን አምባ እስር ቤት፣<br />

የአክሱም ነገስታትን ልማድ<br />

በመከተል የላስታዎቹ ነገስታትም<br />

ተመሳሳይ ችግር ለማስወገድ ከደሴ<br />

በስተምዕራብ ግሸን አምባ ይባል<br />

የነበረውን ተራራማ ቦታ ለእስር ቤት<br />

ተጠቅመውበታል። (3) ግሸን አምባ<br />

እስር ቤት (እንደገና)፣ የአክሱምን<br />

እና የላስታን ነገስታት ልማድ<br />

በመከተል እስከ ልብነ ድንግል ድረስ<br />

የነበሩት የሸዋ ነገስታትም ይህንኑ<br />

ግሸን አምባን እንደ እስር ቤት<br />

ተጠቅመዋል። በግሸን አምባ የነበሩት<br />

የነገስታት ዝርያዎች በሙሉ<br />

በእስር ላይ ሳሉ በልብነ ድንግል<br />

እና በይማም አህመድ መካከል<br />

የተካሄደው እንደፈጃቸው ተክለ<br />

ፃዲቅ መኩሪያ እና የውጭ ታሪክ<br />

ጸሐፊዎች ጽፈዋል። (4) ወህኒ<br />

ተራራ እስር ቤት፣ በጎንደር ዘመነ<br />

መንግስት ደግሞ ካፄ ፋሲል ጀምሮ<br />

ከጎንደር በስተ ምዕራብ የሚገኘውን<br />

ወህኒ ተራራን ለተመሳሳይ ተግባር<br />

ነገስታቱ ተጠቅመዋል።<br />

ለጥቀን ከኢዛና ዘመነ መንግስት<br />

(321 ዓ.ም.) እስከ ህውሃት/ኢህአዴግ<br />

ስልጣን እስከጨበጠበት 1883<br />

ዓ.ም. ድረስ ከተደረጉት የመንግስት<br />

ሽግግሮች ውስጥ አለፍ አለፍ እያልን<br />

ጥቂት ምሳሌዎች እንመለከታለን፣<br />

(1) ወደኋላ መለስ ብለን የንግስት<br />

ዮዲትን ዘመን ብናይ ከመንግስት<br />

ስልጣን በፊት 50 አመቶች ግድም<br />

እና በስልጣን ዘመኗ ደግሞ 40<br />

አመቶች በድምሩ 90 አመቶች<br />

የጦርነት ዘመን እንደነበሩ ተጽፎ<br />

እናያለን።<br />

(2) በቱርክ እና ግብጽ የታገዙት<br />

የይማም አህመድ ዘመንንም<br />

ብንወስድ በቱርክ ወታደራዊ<br />

የበላይነትን ከማግኘታቸው በፊት<br />

እና ወታደራዊ የበላይነትን የያዙበት<br />

አመቶች እንዲሁም ፖርቱጋሎች<br />

ክርስቲያኖችን አግዘው የተዋጉበት<br />

አመቶች በድምሩ ከ30 አመቶች<br />

በላይ ይሆናል።<br />

(3) ከሠርፀ ዘድንግል ወደ ፋሲል<br />

አባት (ዐፄ ሱስነየስ) የተደረገው<br />

የመንግስት ሽግግር በቀጣይነት የርስ<br />

በርስ ጦርነት ዘመን ነበር። ሠርፀ<br />

ሲሞት ለትንሽ ልጁ አቆብ (1590-<br />

1595) አወረሰ። የአጎቱ ልጆች ዙፋን<br />

ለኛ ይገባል የሚል ጦርነት ከፍተው<br />

ዙፋኑ ከአቆብ ወደ ዘድንግል (1595-<br />

1596) ከዚያ ከዘድንግል እንደገና<br />

ወደ ያእቆብ (1596-1598) ከዚያ<br />

በመጨረሻ ወደ ፋሲል አባት ሱስነየስ<br />

(1598-1625) የተሸጋገረው በድምሩ<br />

10 አመቶች የርስ በርስ ጦርነት<br />

ከተደረገ ቧላ ነበር። ምናልባትም<br />

ለዚህ ነበር ፋሲል ዮሐንስ ከተባለው<br />

ልጁ በስተቀር የቀሩትን ልጆቹን እና<br />

ሌሎች ዘመዶቹን ወደ ተራራ ወህኒን<br />

የላከው።<br />

(4) ታላቁ እያሱ ከተገደለበት (1698)<br />

ጊዜ ጀምሮ ባባቱ ቋራ በእናቱ የጁ<br />

የሆነው ዐፄ እዮአስ እስከተገደለበት<br />

1761 ዓ.ም. ድረስ የነበሩት 63<br />

አመቶች የማያቋርጥ የእርስ በርስ<br />

ጦርነት አመቶች ነበሩ።<br />

(5) በ1761 ዓ.ም. ዘመነ መሳፍንት<br />

ከተነሳ ወዲህ እስከ ወደቀበት 1847<br />

ዓ.ም. ድረስ 86 አመቶች ሲኖሩ ከዚያ<br />

ውስጥ የየጁው ራስ ጉግሳ በገዙበት<br />

ዘመን ከነበረው ትንሽ መረጋጋት<br />

በስተቀር ሰላም አልነበረም።<br />

(6) ከዚያም ያፄ ቴዎድሮስ ዘመን<br />

(1847-1860) ማለቂያ ባልነበረው<br />

የማስገበር ዘመቻ ተጠምዶ ስለነበር<br />

እስከ ፍጻሜያቸው ድረስ የነበሩት 13<br />

አመቶች የመንግስት ሽግግር የእርስ<br />

በርስ ጦርነት አመቶች ነበሩ።<br />

(7) ያፄ ተክለ ጊዮርጊስ 4 አመቶችም<br />

የጦርነት ዘመን ነበሩ።<br />

(8) ያፄ ዮሐንስ ዘመን (1864-1881)<br />

በግብጾች እና በቅኝ ገዢዋ ኢጣሊያ<br />

ጦርነቶች ከመጠመዱ ባሻገር<br />

ለስልጣን ከውስጥ የሚያፈነግጠው<br />

ጥቂጥት አልነበረም። በዚህ የተነሳ<br />

ዮሐንስ መጨረሻ መተማ ላይ<br />

እስከሞቱበት ጊዜ ድረስ በቤተ<br />

መንግስታቸው ያደሩባቸው ቀኖች<br />

በጣም ጥቂት ነበሩ።<br />

(9) ከምኒሊክ ዘመነ መንግስት<br />

(1882/9-1906/13) እስከ ምኒልክ<br />

ፍጻሜ (1906/13) ድረስ የተወሰነ<br />

የሰላም ጊዜ ቢኖርም ከዚያ እስከ<br />

ኃይለስላሴ ንጉሰ ነገስት (1922/30-<br />

1967/75) ያልተቋረጠ የመንግስት<br />

ሽግግር ጦርነቶች ተካሂደዋል።<br />

የምኒልክን ዙፋን ወራሽ የልጅ<br />

እያሱ ዘመን (1906/13-1919/27)<br />

ከመንግስት የተፈነቀለው በብዙ<br />

የርስ በርስ ደም መፋሰስ ነበር።<br />

ከዚያም ወደ ኃይለስላሴ ንግስና<br />

በተደረገው የመንግስት ሽግግር<br />

ሂደት የልጅ እያሱን ደጋፊዎች፣<br />

የንግስት ዘውዲቱን (1919/27-<br />

1922/30) ደጋፊዎች፣ የምኒልክን<br />

ባለቤት የእቴጌ ጣይቱን ደጋፊዎች<br />

የማጽዳት በርካታ የርስ በርስ ጦርነት<br />

ተፈጽሟል።<br />

የኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ ከርካሳ<br />

አውሮፕላን የመጀመሪያ ስራ<br />

ለመንግስት ሽግግር በጎንደር<br />

ተቃዋሚዎች ላይ ቦንብ መጣል<br />

እንደነበር እና የኢትዮጵያ<br />

የመጀመሪያው ታንክም በአዲስ አበባ<br />

ለተመሳሳይ ጉዳይ ስራ ላይ ውለው<br />

እንደነበር ባህሩ ዘውዴ ያመለክታል።<br />

የኃይለስላሴን የመጨረሻዎቹ አመቶች<br />

የእርስ በርስ ጦርነቶች ብንጨምር<br />

ከምኒልክ ዘመነ መንግስት ጅማሬ<br />

እስከ ኃይለስላሴ ዘመነ መንግስት<br />

ፍጻሜ ድረስ በግምት 16+4=20<br />

አመቶች የጦርነት አመቶች ብሎ<br />

መውሰድ ይቻላል)<br />

(10) የደርግ 17 አመቶች ከዘመነ<br />

መሳፍንት በባሰ ደረጃ ከ7 በላይ<br />

የሚሆኑ ኢትዮጵያዊ ድርጅቶች<br />

እርስ በርስ ተዋግተዋል።<br />

ስለዚህ ካፄ ኢዛና ከነገሰበት ከ321<br />

ዓ.ም. እስከ በ1983 ዓ.ም. ድረስ<br />

ከነበሩት 1662 አመቶች ውስጥ<br />

የተሳኩት የመንግስት ሽግግሮች<br />

በግምት ከ360 እስከ 400 አመቶች<br />

ያህል ጊዜው ወስደዋል ብንል ስህተት<br />

አይመስለኝም።<br />

በ400 አመቶች ላይ ያልተሳኩት<br />

የመንግስት ሽግግሮች የወሰዱት ጊዜ<br />

ቢጨመርስ? በዚያ ላይ ኢትዮጵያ<br />

ከቱርኮች እና ከኢጣሊያ ጋር<br />

ያደረገቻቸው ጦርነቶች የወሰዱት<br />

ጊዜ ቢጨመርስ?<br />

እንደ እኔ ከሆነ በአጠቃላይ በትንሹ<br />

ከ500 አመቶች ላላነሰ ጊዜ ኢትዮጵያ<br />

እጅ እና እግሯ በጦርነት ተተብትቦ<br />

ከአገር ውስጥ ስልጣኔ እንዳይበቅል<br />

ተደርጓል። ትንሽ የሰላም ጊዜ<br />

እና ጥሩ መሪ ሲገኝ የሚደረገው<br />

እድገትም ለጥቀው በሚካሄዱ<br />

ጦርነቶች ይወድማሉ። አገሪቱ ወደ<br />

ኋላ ትሄዳለች። ይህን የእርስ በርስ<br />

ጦርነት አውዳሚነት እና ጎታችነት<br />

ጸባይ አስመልክቶ ተክለ ፃዲቅ<br />

መኩሪያ ካፄ ልብነ ድንግል እስከ<br />

ዐፄ ቴዎድሮስ በሚለው መጽሐፉ<br />

የታላቁ እያሱን ዘመን እንደ ምሳሌ<br />

በመውሰድ በታላቁ እያሱ በዘመን<br />

የገነባው በሙሉ ከታላቁ እያሱ በኋላ<br />

በመጡት የርስ በርስ ጦርነቶች<br />

መውደማቸውን ይተርካል።<br />

የመንግስት ሽግግር እርስ በርስ<br />

ጦርነት ታሪካችን ኢትዮጵያችንን<br />

ወደ ኋላ የማስቀረት እንጂ ወደ<br />

ስልጣኔ የማራመድ ሚና ተጫውቶ<br />

እንደማያውቅ ግልጽ ይመስለኛል።<br />

የመንግስት ሽግግር ባህላችን ብዙ<br />

ጊዜ አቃጥሏል ኢትዮጵያ ወደፊት<br />

እንዳትራመድ በማድረግ። ከዚህ በኋላ<br />

ኢትዮጵያ በስልጣኔ ብዙ እርቀዋት<br />

የሄዱትን አገሮች ለመድረስ የርቀት<br />

ቅነሳ ስራ ላይ በትጋት መሰማራት<br />

አለባት። ወደ ስልጣኔ መንደር<br />

የሚያደርሱ ብዙ ስራዎች በትጋት<br />

መስራት ይጠበቅባታል። ለመንግስት<br />

ሽግግር የሚደረግ የ’እርስ በርስ<br />

ጦርነት ግን አንዱ አይደለም።<br />

በቅርቡ ደግሞ ትጥቅ ትግል<br />

ወደ ገፅ 6 ይዞራል


ነገረ-ኢትዮጵያ<br />

ቅፅ 1 ቁጥር 2<br />

የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም.<br />

10<br />

የአስር ሳንቲም ኢኮኖሚ ወፖለቲካ<br />

አ በላይ ማናዬ<br />

ያስር በምዕራብ ጎጃም ዞን ባህር ዳር ዙሪያ<br />

ወረዳ ነዋሪ ነበር፤ አሁን ጠቅልሎ የከተማ<br />

ነዋሪ ሆኗል፣ ባህር ዳር፡፡ አሁን ላይ ያስር<br />

እኔ ነኝ ያለ የናጠጠ ሃብታም ነጋዴ ነው፡<br />

፡ ያስር የሚለው ስሙም ተቀይሯል፡፡<br />

ለዚህ ጽሑፍ ብቻ የድሮ ስሙን ተጠቅመን<br />

እንቀጥላለን፡፡<br />

ያስር የሚለውን ስም ያወጡለት<br />

በተወለደባት ትንሽ የገጠር ከተማ ከልጅነት<br />

ጊዜው ጀምሮ ይሰራው ከነበረው የንግድ<br />

(ችርቻሮ) ስራ ጋር በተያያዘ ነበር፤ አንዱን<br />

ጥሎ አንዱን ያነሳበት ከነበረው የችርቻሮ<br />

ገበያው፡፡ በለጋነቱ፣ ገና የችርቻሮ ንግድን<br />

‹ሀ› ብሎ ሲጀምር ወላጅ እናቱን (አባቱ<br />

በህይወት የሉም) የጠየቃት ሀምሳ ሳንቲም<br />

ብቻ እንደነበር ያስር ዛሬ ላይ በትውስታ<br />

ይናገራል፡፡ ብላቴናው ያስር ከዕናቱ ባገኛት<br />

ሀምሳ ሳንቲም ትንንሽ የዕለት ከዕለት<br />

የህብረተሰቡ መገልገያዎችን እና የህጻናትን<br />

ጥያቄዎች ‹ማስቀየሻ› ጣፋጭ ነገሮችን<br />

እያዞረ በገበያ ግርግር መሐል ይሸጥ ጀመር፡<br />

፡ በተለይም መርፌ፣ ከረሚላ፣ ማስቲካ፣<br />

ምላጭ፣ ክር፣ መርፌቁልፍ፣ አዝራር እና<br />

የመሳሰሉትን ሸቀጣ ሸቀጦች ለገበያተኛው<br />

እዚያው ባለበት ቦታ ይዞ ከተፍ በማለት<br />

ታወቀ፡፡ ትንሽ ጊዜ ሲዘዋወር ካልታዬ<br />

እንኳ ‹ያስር የት ሄደ› ባዩ ይበረክታል፡፡<br />

ይህ ፈጣንና ፍልቅልቅ ብላቴና ያለችውን<br />

ትንሽ ሳንቲም በፍጥነት እየተገለገለ<br />

መጠኗ ከዕለት ወደ ዕለት እንድትጨምር<br />

አደረጋት፡፡ በተለይ ቅዳሜ ዕለት ለያስር<br />

የሞት የሽረት ቀኑ ነበረች፤ ሞቅ ባለው<br />

ገበያ ውሰጥ እየተሹለከለከ ችርቻሮውን<br />

የሚያቀላጥፍባት ቀን ቅዳሜ ናት፡፡ ወዲያው<br />

ከአንድ ደንበኛው ሱቅ ሸቀጦችን ይገዛል፤<br />

ወዲያው በገበያተኛው መሀል እየተሹለከለከ<br />

ያጣራል፡፡ ማንም ይግዛው ማን፣ ምንም<br />

ይሽጥ ምን ያስር ጋር ያለው ዋጋ ያው<br />

አስር ሳንቲም ብቻ ነበር፤ መርፌ ባስር<br />

ሁለት ገዝቶ ከሆነ ባስር አንድ ይሸጣል፡፡<br />

በቃ ይህ የያስር ገበያ ነው፡፡ ለያስር ከአስር<br />

ሳንቲም በላይ ወጭ አውጥቶ ዕቃ መግዛት<br />

ኪሳራ ነው፤ ምክንያቱም ሰዎች ካስር<br />

ሳንቲም ውጭ ባለ ዋጋ አይገዙትም ነበር፡፡<br />

እንዲህ እንዲህ እያለ ያስር ከአስር<br />

ሳንቲም ጋር ጋብቻ መሰረተ፤ ጋብቻውም<br />

ተመቸው፤ ብዙ ትርፍ ይዞለትም መጣ፡<br />

፡ የገንዘብ ትርፍ ብቻ ሳይሆን ያላሰበውን<br />

ዕውቅናም አተረፈለት፤ ይህም እናቱ<br />

ያወጣችለትን ስም እንኳ አስቀየረው፡<br />

፡ ሁሉም ሰው ከዕሱ ዕቃ ሲገዛ ባስር<br />

ሳንቲም ብቻ በመሆኑ የብላቴናውን ስም<br />

ያስር አሉት፣ ገበያተኞቹ፡፡ እሱም ስሙ<br />

ተመቸው፤ ድንገት ገበያተኛውን ጠጋ<br />

እያለ ‹ያስር!...ያስር!...ያስር አለ!› ይል<br />

ጀመር፡፡ ገበያተኛውም ‹ያስር መርፌ›፣<br />

‹ያስር ከረሚላ›፣ ‹ያስር አዝራር›፣ ‹ያስር<br />

መርፌቁልፍ›…እያለ ይሸምተው ነበር፡<br />

፡ ስሙ ያስር፣ የሚሸጣቸው ነገሮች<br />

ዋጋቸው አስር ሳንቲም፤ መልካምና ለያስር<br />

የተመቼው ስምሙ ጋብቻ ሆነ፡፡<br />

አሁን ያስርን በቀድሞ ስሙ የሚጠራው<br />

ሰው ጠፋ፤ ምናልባት እናቱም ብትሆን<br />

ከዚህ ሁሉ በላይ ግን ያጣነው ትልቅ ጸጋ አለ፤ መብትን አሳልፎ<br />

መስጠት፤ (የአስር ሳንቲም ፖለቲካ ልንለው እንችላለን)፡፡<br />

ይህ ከገንዘቡም በላይ ነው፡፡ ባለታክሲዎች (ረዳቶች) በራሳቸው<br />

ጊዜ የታክሲን ታሪፍ 2 ብር ከ90 የነበረውን ዋጋ 3 ብር<br />

አድርገውታል፡፡ ከስንት አንድ ሰው መልስ ሲጠይቃቸው እንኳ<br />

ይገላምጡታል፤ በተጨማሪም ሳንቲሙን ያለአግባብና ስርዓት<br />

በጎደለው መልኩ ሲወረውሩለት ይታያል፡፡ ለምን ተጠየኩ<br />

እንደማለት! ይህም መጀመሪያ እኛው ራሳችን ያስለመድናቸው<br />

ነገር በመሆኑ ነው፤ ‹ቀድሞ ነበር እንጂ…› የሚሉት ብሂል<br />

መሆኑ ነው፡፡<br />

የምታስታውሰው አትመስልም፤ ‹ያስር›<br />

የሉታል ‹አቤት!› ይላል፡፡ ያስር ኑሮው፣<br />

ገቢው ተሻሻለ፡፡ ከራሱ የትምህር ቤት ወጭ<br />

አልፎ ለእናቱ ደራሽ ሆነ፤ ከነበሩበት የከፋ<br />

ድህነት ውስጥ አውጥቶ ማገገሚያ ክፍል<br />

ውስጥ ጨመራቸው፡፡ ቀስ በቀስ የያስር<br />

ግብይት ከአስር ሳንቲም ከፍ እያለ መሄዱ<br />

አልቀረም ነበር፤ ቢሆንም ግን ስሙ፣<br />

መጠሪያው አሁንም ያው ያስር ነበር፡፡<br />

ያስር በዚህ ስም እየተጠራ፣ ንግዱን ግን<br />

እያስፋፋ ለዓመታት ዘለቀ፤ በዓዕምሮም<br />

ሆነ በአካል እያደገና እየጎለበተም መጣ፤<br />

ገቢውም ደረጀ፡፡<br />

የያስር ህይወት ከአስር ሳንቲም ጋር<br />

የተቆራኘች ሆና የዘለቀችው ለአጭር<br />

ጊዜ ብቻ አይደለም፤ ዛሬም ያስር እና<br />

አስር ሳንቲም ቁርኝታቸው ጥብቅ ነው፡<br />

፡ የዛሬው የናጠጠ ነጋዴነት፣ የዛሬው<br />

የተትረፈረፈ ሃብትና ንብረት ባለቤትነት፣<br />

የዛሬው ክብርና ሞገስ፣ የዛሬው በተደላደለ<br />

ሁኔታ ህይወትን ቤተሰብን መምራት<br />

መሰረታቸው አስር ሳንቲም ናት፡፡ በአስር<br />

ሳንቲም ነግዶ አትርፏል፤ በአስር ሳንቲም<br />

ዕውቅናን አግኝቷል፡፡ የሚገርመው ያስር<br />

በደንበኞቹ ዘንድ ታማኝና ቅን ነበር፤ ዛሬም<br />

ድረስ እንዲያ እንደሆነ ይነገርለታል፡፡<br />

በተተመነው ዋጋ ነግዶ ከማትረፍ ውጭ<br />

በሌላ ነገር አይታማም ይሉታል ደንበኞች፡፡<br />

አሁን ላይ ያስር ሀብታምና በርካታ<br />

ካፒታል የሚያንቀሳቅስ ነጋዴ ነው፤ ከዚህ<br />

ያደረሰችውን አስር ሳንቲም ግን አይንቃትም፡<br />

፡ አስር ሳንቲም ለማትረፍ ትናንት ብቻ<br />

ሳይሆን ዛሬም ከመነገድ ወደ ኋላ አይልም፡<br />

፡ አውቆ ካልሆነ በቀር አስር ሳንቲምን<br />

ንቆ መልስ ከመቀበል አይመለስም፤<br />

ምክንያቱም ዋጋዋን ያውቃታል፡፡ ‹‹አስር<br />

ሳንቲም ትንሽ መስላ የምትታዬን ዋጋዋን<br />

በሚገባ ካልተረዳንና ህይወትን የመለወጥ<br />

አቅሟን ካላወቅን ነው፤ እኔ በአስር ሳንቲም<br />

በምሸጠው መርፌ አይደለም እንዴ የተቀደደ<br />

ልብስህን ሰፍተህ ገመናህን የምትሸፍነው?<br />

ባስር ሳንቲም በገዛኸው መርፌ አይደለም<br />

እንዴ ለስቃይ የዳረገህን እሾህ ከእግርህ<br />

ነቅሰህ የምታወጣው? ታዲያ አስር ሳንቲም<br />

ዋጋዋ ትልቅ አይደለም ወይ?›› በማለት<br />

ይጠይቃል ያስር፡፡<br />

ብዙዎቻችን ወደ አዲስ አበባ ታክሲዎች<br />

ዘው ብለን ገብተን የአስር ሳንቲምን ዋጋና<br />

ከሳንቲሟ ጋራ እያጣን ያለነውን ውድ<br />

ጸጋ ካየን ግን ያስር ለአስር ሳንቲም ካለው<br />

ግንዛቤ በእጅጉ የተለዬ ሆኖ እናገኘዋልን፡<br />

፡ በየጊዜው ዋጋው እየተከለሰ የሚገኘው<br />

የታክሲ የአንድ ፌርማታ ጉዞ ክፍያ ወይም<br />

ታሪፍ ብዙ ነገሮችን እያሳየን ይገኛል፡<br />

፡ ላለፉት ሁለት ወራት ስራ ላይ ባለው<br />

ታሪፍ መሰረት የሁለት ፌርማታ ዋጋ 2<br />

ብር ከ90 ሳንቲም ነው፡፡ ለሶስት ብር አስር<br />

ሳንቲም የጎደለው ማለት ነው፡፡ ይህቺ አስር<br />

ሳንቲም ናት እንግዲህ መነጋገሪያችን፡፡<br />

ብዙ ተሳፋሪዎች 3 ብር ከፍለው መልስ<br />

አይቀበሉም፤ መልሳቸው ደግሞ አስር<br />

ሳንቲም ናት፡፡ ብዙ የታክሲ ረዳቶች<br />

(ወያላዎች) 3 ብር ተቀብለው መልስ<br />

አይሰጡም፤ መልሱ ደግሞ አስር<br />

ሳንቲም ናት፡፡ ግን ለምን? በጥናት ላይ<br />

የተመሰረተም ባይሆን ብዙዎቹ ተሳፋሪዎች<br />

አስር ሳንቲምን ከመናቅ የመነጨ ሊሆን<br />

ይችላል መልሳቸውን የማይጠይቁት፡፡ ብዙ<br />

የታክሲ ረዳቶች አስር ሳንቲምን ለማስቀረት<br />

ካላቸው ፍላጎት (በቀን ምን ያህል ገንዘብ<br />

ማስቀረት እንደሚችሉ ያውቃሉና) አሊያም<br />

ጠያቂ ከሌለ በማለት ሊሆን ይችላል መልስ<br />

የማይሰጡት፡፡ ሁለቱም ወገኖች ግን ተገቢ<br />

ያልሆነ አረዳድ ውስጥ የገቡ ናቸው፡፡ አስር<br />

ሳንቲም ዋጋ አላት፤ አስር ሳንቲም ገንዘብ<br />

ናት፡፡<br />

ቀደም ብለን ያነሳነው ያስር በአስር<br />

ሳንቲም ትልቅ ደቋና ደፍኖባታል፤ ትልቅ<br />

ቁምነገር ከውኖባታል፡፡ ስለዚህም አስር<br />

ሳንቲም ትንሽ አይደለችም፡፡ ተሳፋሪዎች<br />

ንቀዋትም ሆነ በሌላ ምክንያት ታክሲ<br />

ውስጥ ትተዋት የሚወርዱት አስር<br />

ሳንቲም ተጠራቅማ የጎጆን ቀዳዳ መድፈን<br />

ይቻላታል፤ ቢነግዱባት አትርፋ ቤት<br />

ለመስራት ትበቃለች (የያስርን እውነታ ልብ<br />

ይሏል)፡፡ አንድ ተሳፋሪ በቀን 20 ሳንቲም<br />

ታክሲ ውስጥ ትቶ ቢወርድ በወር ውስጥ<br />

6 ብር ያጣል ማለት ነው፡፡ ይህ ስድስት<br />

ብር ለአንድ የኔ ቢጤ አራት ዳቦ ሊገዛለት<br />

የሚችል ገንዘብ ነው፡፡ ለተቸገሩት ወገኖች<br />

የሚውልን (ከእጅ ላይ ያለችን ሳንቲም<br />

መስጠት ታክሲ ላይ ጥሎ እንደመውረድ<br />

ባይቀልም) ገንዘብ እንዲሁ መተው አጓጉል<br />

መቀናጣት ሊሆን ይችላል፡፡<br />

ከዚህ ሁሉ በላይ ግን ያጣነው ትልቅ ጸጋ<br />

አለ፤ መብትን አሳልፎ መስጠት፤ (የአስር<br />

ሳንቲም ፖለቲካ ልንለው እንችላለን)፡፡<br />

ይህ ከገንዘቡም በላይ ነው፡፡ ባለታክሲዎች<br />

(ረዳቶች) በራሳቸው ጊዜ የታክሲን ታሪፍ<br />

2 ብር ከ90 የነበረውን ዋጋ 3 ብር<br />

አድርገውታል፡፡ ከስንት አንድ ሰው መልስ<br />

ሲጠይቃቸው እንኳ ይገላምጡታል፤<br />

በተጨማሪም ሳንቲሙን ያለአግባብና<br />

ስርዓት በጎደለው መልኩ ሲወረውሩለት<br />

ይታያል፡፡ ለምን ተጠየኩ እንደማለት! ይህም<br />

መጀመሪያ እኛው ራሳችን ያስለመድናቸው<br />

ነገር በመሆኑ ነው፤ ‹ቀድሞ ነበር እንጂ…›<br />

የሚሉት ብሂል መሆኑ ነው፡፡<br />

በእጃችን ያለን ነገር መልቀቅ በኋላ<br />

እንደማስመለስ ቀላል አይደለም፡፡ አሁን<br />

ላይ ንቀን የምንተዋት እያንዳንዷ ነገር<br />

ዘግይታ ብዙ ዋጋ ታስከፍለናለች፡፡<br />

ካለመጠየቅ ደጃዝማችነት ይቀራል እንዲሉ<br />

አበው ስለመብታችን የመቆርቆር ንቃት፣<br />

መብታችንን ማስከበር ላይ ድክመት<br />

ይታይብናል፡፡ ከተነጠቅን ወዲያ መጮህ<br />

ብቻ ሳይሆን ቀድሞውንም አሳልፎ<br />

ላለመስጠት መጣር ተገቢ ነው፡፡ ዛሬ አስር<br />

ሳንቲም የወሰደብን ሰው ነገ ቤታችንም<br />

ለመውሰድ ወደ ኋላ ሊል አይችልም፡<br />

፡ ይህ የአስር ሳንቲም ጉዳይ አይደለም፤<br />

ይህ የክብር ጉዳይ ነው፡፡ ግለሰቦችም ሆነ<br />

መንግስታት በማናለብኝነት የሚነጥቁን<br />

የእኛ የሆኑ ነገሮች ሁሉ መነሻቸው<br />

የእኛ አለመጠየቅና ለመብታችን ጥብቅና<br />

አለመቆም ነው፡፡<br />

ዛሬ ቀበሌ ላይ የመናገር መብትህን የነፈገህ<br />

የቀበሌ አስተዳዳሪ ዝም ከተባለ የሐገር<br />

መሪም ሆኖ ጨቋኝና የለየለት አምባገነን<br />

መሆኑ የታወቀ ነው፤ ዛሬ ጨቋኝነቱን<br />

ቀበሌ ላይ የነገርነውና የታገልነው ሰው ሀገር<br />

የመምራት ዕድሉን አግኝቶ ስልጣን ላይ<br />

ቢወጣ የህዝብን ጉልበት የተረዳ ለመሆኑ<br />

ሳይታለም የተፈታ ጉዳይ ነው፡፡ እናም፣<br />

የእኛ ለመብቶቻችንና ለገንዘባችን ቸልተኛ<br />

መሆን አምባገነንና ስግብግብ መሪዎችን<br />

ለመፍጠራችን እማኝ ነው፡፡ የመብት ትንሽ<br />

የለውም፤ መብት የክበር ጉዳይም ነው፡፡<br />

ስንደፈር በትንሹ ነው፣ በትልቁ ነው ልንል<br />

አንችልም፡፡ ጭብጡ ያለው መርሁ ላይ<br />

ነው፡፡ መብቱን በእንዝላልነት አሳልፎ የሰጠ<br />

ሰው መልሶ ሲጠይቅም አያምርበትም፡፡


11የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2<br />

የኔ-ሐሳብ<br />

ነገረ-ኢትዮጵያ<br />

እንደሀገር መግባባት የተሳነን ‹ባቢሎናውያን›<br />

ትሁን ተስፋ<br />

ባቢሎናውያን በስልጣኔ ከመራቀቃቸው<br />

የተነሳ ወደ ሰማይ ህንጻ በመገንባት<br />

አምላካቸው ጋር መድረስ ፈለጉ፡፡ ይህ<br />

ስራቸው ያላስደሰተው አምላክም ይግባቡበት<br />

የነበረውን ቋንቋቸውን ደበላለቀባቸው፡<br />

፡ ከቋንቋቸው መደበላለቅ የተነሳ መግባባት<br />

ተስኗቸው አካፋ የተጠየቀው ዶማ፣ ድንጋይ<br />

የተጠየቀው ጭቃ፣ ሚስማር የተጠየቀው<br />

አጠና እያቀረበ መግባባት ባለመቻላቸው<br />

የገነቡት ሰማይ ጠቀስ ህንጻ ከግቡ ሳይደርስ<br />

ሊፈርስ ችሏል፡፡<br />

ሁሌም ይህን ታሪክ ሳስታውስ የሀገሬ<br />

ልጆች መግባባት አለመቻል ይታወሰኝና<br />

ምን አልባት ቋንቋችን ተደበላልቆ ይሆን<br />

እንድል ያስገድደኛል፡፡ በብሄራዊ ደረጃ<br />

መግባባት ከማይችሉ ሀገራት መካከል<br />

ኢትዮጵያ በቀዳሚነት ትጠቀሳለች ብል<br />

ማጋነን አይሆንም፡፡ ኢትዮጵያውያን እንደ<br />

ሀገር ከምንግባባባቸው ነገሮች ይልቅ<br />

የማንግባባባቸው ጉዳዮቻችን ብልጫውን<br />

ይወስዳሉ፡፡ በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ<br />

ያለመግባባታችን ጥግ መራራቅ ነው፡፡ ከዚህ<br />

ያለመግባባት ችግራችን የተነሳ የተጣባን<br />

ልዩነትን በጉልበትና በጠብ-መንጃ የመፍታት<br />

አባዜ ያለመግባባታችንን ወደ ጫፍ<br />

በመለጠጥ ወደ መጠፋፋት ሲገፋን ኑሯል፡<br />

፡ በጠረጴዛ ዙሪያ ማለቅ የሚገባው ልዩነት<br />

የተራዘመ ብጥብጥና ግድያ ካስከተለ በኋላ<br />

አንዱ ጉልበታም በሌላ ጉልበታም እየተተካ<br />

እዚህ ደርሰናል፡፡ ዓለም አንድ መንደር እየሆነ<br />

በመጣበት በዚህ ጊዜ የእኛ መንደሮች ግን<br />

የዓለም ጥግ ላይ ያሉ የምድር ዋልታዎችን<br />

ያክል ተራርቀዋል፡፡<br />

ቀጥዬ ለምን መግባባት ተሳነን፣<br />

ላለመግባባታችን ተጠያቂው ማን ነው፣<br />

የማንግባባባቸው ጉዳዮች የትኞቹ ናቸው?<br />

እና የመሳሰሉትን ጉዳዮች በማሳያዎች<br />

ለመዳሰስ እሞክራለሁ፡፡<br />

ማሳያ አንድ፡- ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት<br />

የሀገራችን የፖለቲካ ልሂቃን ኢትዮጵያና<br />

ኢትዮጵያዊነትን የሚያዩበት መነጽር<br />

የተንሸዋረረ መሆኑ ላለመግባባታችን እንደ<br />

ምክንያት ሆኖ ይነሳል፡፡ አንዳንድ ምሁራን<br />

ኢትዮጵያዊነትን የሀበሻነት (አማርኛና<br />

ትግርኛ ተናጋሪዎች) መገለጫ ብቻ<br />

አድርገው ይወስዱታል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ<br />

የሚመጣው የኢትዮጵያ ታሪክ ነው፡፡<br />

የኢትዮጵያ ታሪክ በአንዳንዶቹ አምስት ሺህ<br />

ዘመን ድረስ ሲለጠጥ በሌሎቹ ደግሞ ወደ<br />

መቶ አመት ይኮማተራል፡፡ የአምስት ሺህ<br />

ዘመን ታሪክ ተብሎ የሚጠቀሰው የኖህ ልጅ<br />

ካም ወደ ኢትዮጵያ መምጣት ጋር ተያይዞ<br />

ያለው ሲሆን፣ በዚህም ኢትዮጵያ ተብላ<br />

በመጽሀፍ ቅዱስም ሆነ በሌሎች መጽሀፍት<br />

የምትጠቀሰው ሀገር ከግብጽ በታች ያለውን<br />

የአፍሪካ ምድር ትይዛለች፡፡<br />

በበተቃራኒው ደግሞ የመቶ አመት ታሪክ<br />

ባለቤት የሚያደርጓት አሉ፡፡ ለመቶ አመቱ<br />

ክርክር የሚጠቀሰው የቀድሞው ጠቅላይ<br />

ሚንስትር የአቶ መለስ ትርክት ነው፡፡ አቶ<br />

መለስ ጫካ መነበሩበት ዘመን ”የኤርትራ<br />

ህዝብ ትግል ከየት ወዴት” በሚል<br />

ርዕስ ያሳተሙት መጽሀፍ ‹‹ኢትዮጵያ<br />

የመቶ አመት ታሪክ ነው ያላት›› ይልና<br />

የኢትዮጵያ ፈጣሪ ንጉስ ምኒልክ እንደሆኑ<br />

ለማስረዳት ያጣጥራል፡፡ መከራከሪያቸውን<br />

ያጠናክርላቸው ዘንድም ‹‹የአክሱም ሀውልት<br />

ለወላይታው ምኑ ነው?›› ሲሉ ይጠይቃሉ፡፡<br />

ዳሩ ግን የአክሱም ሀውልት ሲገነባ ወላይታው<br />

አስተዋጽኦ ማድረጉን ዘንግተውት አይደለም፤<br />

‹ኢትዮጵያ ቅኝ ገዥ ነች› ወደሚል ሀላፊነት<br />

የጎደለው መከራከሪያ ለመግፋት እንጂ፡፡ ከዚህ<br />

ጋር በተያያዘ አንዳንድ የኦሮሞ ልሂቃን ቅኝ<br />

ተገዝተናል እንገነጠላለን የሚሉት ሌላው<br />

ኢትዮጵያዊነት ላይ የተደነቀረ ሳንካ ነው፡፡<br />

በነዚህ ምሁራን ትርክት መሰረት ኢትዮጵያ<br />

ቅኝ ገዥ ነች፤ ኢትዮጵያዊነትም በግድ<br />

የተጫነብን ቀንበር ስለሆነ አንቀበለውም<br />

ወደሚል ጫፍ ይለጠጣል፡፡ ይህንን<br />

የኢትዮጵያን ቅኝ ገዥነት ለማስረዳትም<br />

ጎሰኝነትን አጥብቆ በማጓን ኢትዮጵያዊነትን<br />

መገዳደር መገለጫው ያደርጉታል፡፡ ብቻ<br />

ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት የተወሰነው<br />

ህዝብ ፍላጎት ብቻ በማስመሰል እውነቱን<br />

ለማድበስበስና አውቆ ላለመግባባት የቆረጥን<br />

እንመስላለን፡፡<br />

አንዳንድ የስልጣን ጥም የተጣባቸው ግለሰቦች<br />

ልክ እንደ ኤርትራው መሪ ኢሳያስ አፈወርቂ<br />

“ባርነት ወይስ ነጻነት” በሚል የማወናበጃ<br />

ምርጫ ትንንሽ ግዛቶችን መፍጠር ይፈልጋሉ፡<br />

፡ በዚህም የተነሳ ሳንግባባ እንደወንድማማች<br />

ሳንተያይ የጎሪጥ እንደተዳባን እዚህ ደርሰናል፡<br />

፡ እዚህ ላይ መሰመር ያለበት ያለመግባባቱ<br />

ጉዳይ የፖለቲካ ልሂቅ ነኝ በሚለው እንጅ<br />

በሌላው ህዝብ ዘንድ የሌለ መሆኑን ነው፡<br />

፡ ብቻ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት እንዲህ<br />

ሳያግባባን አለን፡፡<br />

ማሳያ ሁለት፡- ወደብና የባህር በር<br />

ኢትዮጵያ ለብዙ ዘመን ጠላት ሲያፈራባትና<br />

ሲያዋጋት የኖረው የባህር በሯ መሆኑ<br />

ይታወቃል፡፡ ይህን የባህር በር ለመያዝ<br />

በተደረገው ተጋድሎ አባቶቻችን ብዙ<br />

ጀብዱ ፈጽመዋል፡፡ ይህን የዘነጋው አቶ<br />

መለስ ዜናዊ ግን አሰብን አሳልፎ ሰጥቷል፡<br />

፡ ስለጉዳዩ ሲጠየቅም፣ “የባህር በር<br />

የተስፋፊወችና የጦርነት ናፋቂወች ወሬ<br />

ነው፤ አንድ ሀገር ለማደግ የግድ የባህር<br />

በር አያስፈልጋትም፤ ኢሳያስ አፈወርቂ<br />

ከፈለገ ግመሎቹን ያጠጣበት”፡፡ ጠቅላይ<br />

ሚንስትሩ ይህን ቢሉም ወደባችን አሳልፈን<br />

በመስጠታችን ብቻ ለጅቡቲ በቀን ከሶስት<br />

ሚሊዮን ዶላር በላይ እንደምንከፍል<br />

አጥተውት አይደለም፡፡ ከምንከፍለው ዶላር<br />

በተጨማሪ የራሳችን ሚስጥር የሚባል ነገር<br />

ሊኖረን አይችልም፤ በተለይ የጦር መሳሪያን<br />

በተመለከተ፡፡ በነገራችን ላይ ለጂቡቲ ወደብ<br />

የምንከፍለው ዶላር አባይን ለመገደብ ቢውል<br />

በአመት ከስድስት ወር ውስጥ የሚወጣው<br />

ብቻ ይበቃን ነበር፡፡ አሁንም ልብ ማለት<br />

የምንችለው ኢህአዴጎች ይህን ቢሉም አሰብን<br />

አንጋጦ የሚያይ ዜጋ መኖሩ እሙን ነው፡<br />

፡ በመሆኑም የወደብ ጥያቄ ላለመግባባታችን<br />

አንዱ ምክንያት ነው፡፡<br />

ማሳያ ሦስት፡- የአድዋ ድል<br />

የአድዋ ድል ለጥቁር የሰው ዘር ሁሉ የነጻነት<br />

ተምሳሌት መሆኑ የሚዘነጋ አይደለም፡፡ እነ<br />

አብርሃም ሊንከን እነ ማልኮን ኤክስን ጨምሮ<br />

ብዙ ለጥቁር ህዝቦች ነጻነት የታገሉ ሰዎች<br />

ጥቁር ነጭን ሊያሸንፍ እንደሚችል ትምህርት<br />

ያገኙት ከአድዋ መሆኑ ጸሀይ የሞቀው ሀቅ<br />

ነው፡፡ ይህ የጥቁሮች የመብት እንቅስቃሴ<br />

ኢትዮጵያኒዝም ተብሎም ይጠራል፡<br />

፡ ኢትዮጵያ አድዋ ላይ ድል ማድረጓን<br />

ተከትሎ እንደ ታላቋ ጽዮናዊት ኢየሩሳሌም<br />

ወደ ኢትዮጵያ ሀይማኖታዊ ጉዞ የሚያደርጉ<br />

ጥቁሮች ተበራከቱ፡፡ የሀይቲው ቤኒቶ<br />

ሲልቪያን እና የምዕራብ ኢንዲያው ጆሴፍ<br />

ቪታሊየን ወደ ተስፋይቱ ምድር ኢትዮጵያ<br />

ጉዞ ያደረጉ የመጀመሪያቹ ጥቁሮች ናቸው፡፡<br />

እነሱን በመከተል እንደ ቡከር ቲ.ዋሽንግተን፣<br />

አይዳ ቢ.ዌልስ፣ ደብሊዩ ኢ.ቢ ዱበይሰን<br />

የመሳሰሉ ታዋቂ ጥቁር አፍሪካውያን ስለ<br />

አድዋ እና የኢትዮጵያ የነጻነት ተምሳሌትነት<br />

በስፋት ማውራት ጀመሩ፡፡<br />

ከተወሰኑ ትውልዶች በኋላ “በራስ<br />

ተፈሪያን” ስያሜ የሚደረገው ጉዞም የአድዋ<br />

ተጽዕኖ ውጤት ነው፡፡ አድዋ ሲነሳ አብሮ<br />

የሚነሳ ሀገራዊ አንድነታችን ነው፡፡ ይህ<br />

የጥቁሮች ሁሉ መኩሪያ የሆነ ድል ግን<br />

እኛን ባለቤቶቹን ሊያግባባን አልቻለም፡<br />

፡ አድዋ ኢትዮጵያንም በአለም ብቸኛዋ<br />

በነጭ ቅኝ ያልተገዛች ሀገር ያደርጋታል፡፡<br />

እዚህ ላይ በታሪክ ቅኝ ያልተገዙ የአፍሪካ<br />

ሀገራት እየተባሉ ሲጠቀሱ የምንሰማቸው<br />

ላይቤሪያንና ኢትዮጵያን ቢሆንም የላይቤሪያ<br />

ቅኝ አለመገዛት ግን ብዙም የሚያከራክር<br />

አይደለም፡፡ ምክንያቱም ላይቤሪያ ተብሎ<br />

የሚጠራው ሀገር ከአሜሪካ በተመለሱ<br />

‹ባሪያዎች› የተገነባች ሀገር ስለሆነች እንደ<br />

ነጻ ሀገር ለመጥቀስም የሚያስኬድ ስላልሆ<br />

ነው፡፡ ይህ ልንኮራበት የሚገባን ታሪካችን<br />

እንደውም ለኤርትራውያን ተገንጣዮች<br />

የሚያሳፍር ተደርጎ ይቆጠራል፡፡ ምኒልክ<br />

አድዋ ላይ ተመልሰው ኤርትራን ለጣልያን<br />

አሳልፈው ሰጡብን የሚለው ትርክት ለእነዚህ<br />

ተገንጣዮች እንደ መልካም የመጫወቻ ካርድ<br />

አገልግሎአቸዋል፡፡ ሻቢያና ህወሓት ጫካ<br />

በነበሩበት ወቅት ወታደር ለመመልመል<br />

“የአድዋን ታሪክ ትቀበላለህ አትቀበልም”<br />

የሚል መስፈርት እንደነበራቸው የትናንት<br />

ትዝታ ነው፡፡ ለማነኛውም የአድዋ ድል<br />

ሌላኛው ያለመግባባታችን ምንጭ መሆኑ<br />

አልቀረም፡፡<br />

ማሳያ አራት፡- ሰንደቅ አላማ<br />

ሰንደቁ አላማ አንዱ የአንድ ሀገር መለያ<br />

ነው፡፡ ኢትዮጵያ በዚህ የታደለች ነበረች፡<br />

፡ አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ሰንደቃችን<br />

የነጻነታችን ምልክት የአንድነታችን<br />

ተምሳሌት ሆኖ ለብዙ ዘመን ኖሯል፡፡<br />

ነገር ግን በየጊዜው የሚነሱት አምባገነኖች<br />

የራሳቸውን ምልክት ሲለጥፉበትና ህዝቡም<br />

አርማውን በግድ እንዲቀበል ሲገፉት መኖሩ<br />

ሀቅ ነው፡፡ የቅርብ ጊዜዎቹን ብንወስድ እንኳ<br />

ንጉሱ የይሁዳ አንበሳ ምልክት ሲለጥፉበት፣<br />

ደርግ በበኩሉ የማያውቀውን የሶሻሊዝም<br />

መዶሻ ለብዶበት ነበር፡፡ ቀጥሎም ኢህአዴግ<br />

ታጋይ መሪው ‹‹ባንዲራ ጨርቅ ነው›› ብሎ<br />

በቀደደለት ክፍተት ተጠቅሞ የበሶ መቋጠሪያ<br />

አድርጎት አዲስ አበባ እንደገባ ትናንት<br />

የነበሩት ይመሰክራሉ፡፡<br />

ባንዲራ ጨርቅ ነው የሚለው የአቶ መለስ<br />

አባባልም ኢህአዴግን ምን ያክል ዋጋ<br />

እንዳስከፈለው የሚታወስ ነው፡፡ ኢህአዴግም<br />

ጨርቅ ባለው ባንዲራው ላይ ኮከብ መሀሉ<br />

ላይ ሰፍቶ የእኩልነትና የመከባበር ምልክት<br />

ነው እያለን ነው፡፡ መቸም ኮከብ በምን<br />

መልኩ የአንድነትና የመከባበር ምልክት<br />

እንደሚሆን ኢህአዴግም ሊያውቀው<br />

አይችልም፡፡ ለማንኛውም ይህ ሰንደቁ መሀል<br />

ላይ የተሰፋው ሰማያዊ ኮከብ ለልዩነታችን<br />

እንደ ምክንያት ሆኖ አገልግሏል፡፡ ባለኮከብ<br />

ሰንደቅ አንቀበልም ያሉ ኢትዮጵያውያን<br />

በተለያየ ክብረ በአላት ላይ ኮከብ የሌለውን<br />

ባንዲራ መጠቀማቸው ያሳሰበው ኢህአዴግ<br />

የባንዲራ አጠቃቀም አዋጅ እስከማውጣት<br />

ድረስ ተገዷል፡፡ የሰንደቅ አላማ ቀንም ማክበር<br />

ሰንደቁ አላማ አንዱ የአንድ ሀገር መለያ ነው፡፡ ኢትዮጵያ በዚህ የታደለች ነበረች፡፡<br />

አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ሰንደቃችን የነጻነታችን ምልክት የአንድነታችን ተምሳሌት ሆኖ<br />

ለብዙ ዘመን ኖሯል፡፡ ነገር ግን በየጊዜው የሚነሱት አምባገነኖች የራሳቸውን ምልክት<br />

ሲለጥፉበትና ህዝቡም አርማውን በግድ እንዲቀበል ሲገፉት መኖሩ ሀቅ ነው፡፡ የቅርብ<br />

ጊዜዎቹን ብንወስድ እንኳ ንጉሱ የይሁዳ አንበሳ ምልክት ሲለጥፉበት፣ ደርግ በበኩሉ<br />

የማያውቀውን የሶሻሊዝም መዶሻ ለብዶበት ነበር፡፡ ቀጥሎም ኢህአዴግ ታጋይ መሪው<br />

‹‹ባንዲራ ጨርቅ ነው›› ብሎ በቀደደለት ክፍተት ተጠቅሞ የበሶ መቋጠሪያ<br />

አድርጎት አዲስ አበባ እንደገባ ትናንት የነበሩት ይመሰክራሉ፡፡<br />

ጀምሯል፡፡ ይህ አዋጅ ሰንደቅ አላማውን<br />

በመኪና ላይ ማውለብለብ የሚችለው<br />

ጠቅላይ ሚንስትር፣ የሀገሪቱ ርዕሰ ብሄርና<br />

አምባሳደሮች እንደሆኑ ቢጠቅስም በዘልማድ<br />

የሚታየው ግን አፈር ጫኝ መኪና ሳይቀር<br />

ሲያንጠለጥለው ነው፡፡ የሚገርመው እኛ<br />

ሰንደቅ አላማችንን ላለመግባባት ይህን ያክል<br />

ስንለጥጠው አብዛኛዎቹ የአፍሪካ ሀገራት<br />

ግን አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ሰንደቁን በተለያየ<br />

መልክ ሲጠቀሙበት እናያለን፡፡ ምክንያቱ<br />

ደግሞ እኛ እንደ ሀገር ሊያግባባን የሚችል<br />

ባንዲራ የለንም የሚል ነው፡፡<br />

ማሳያ አምስት፡- ህገ-መንግስት<br />

የአንድ ሀገር መንግስት ህዝቦቹን<br />

ያስተዳድርበት ዘንድ ህገ መንግስት<br />

ያስፈልገዋል፡፡ በዚህ ህገ መንግስት ውስጥ<br />

ህዝቦች ያላቸው መብትና ግዴታወች<br />

እንዲሁም መንግስት ያለው ስልጣን በህግ<br />

ተገድቦ ይሰጠዋል፡፡ ይህ የሚሆንበት<br />

ምክንያት የመንግስትን ፈላጭ ቆራጭነት<br />

ሚና ለመገደብ ሲባል ነው፡፡ አብዛኛውን ጊዜ<br />

መሪወች የስልጣን እድሜያቸውን ለማራዘም<br />

ሲሉ እንደፈለጉ እንዳይሆኑ ሲባል በህገ<br />

መንግስት ይታሰራሉ፡፡ በሀገራችን የህገ-<br />

መንግስት ታሪክ ውስጥ እስከ አሁን<br />

ከተቀረጹት ህገ መንግስቶች ሁሉ የተሻለ<br />

የሰብአዊም ይሁን የዴሞክራሲያዊ መብቶችን<br />

በማካተት የ1987 ዓ.ምቱ ህገ መንግስት<br />

የተሻለ ነው፡፡ ይህ ማለት ግን ህገ መንግስቱ<br />

እንከን አልባ ነው ማለት አይደለም፡፡<br />

በተለይም አንዳንድ ድንጋጌዎች የልዩነት<br />

መፈጠሪያ ሁነው እናገኛቸዋለን፡፡ ለምሳሌ<br />

የህገ-መንግስቱ አንቀጽ 39 ለሀገር አንድነት<br />

እንቅፋት ነው፣ ስለዚህ ህገ መንግስቱ<br />

በሚፈቅደው መሰረት ይሻሻል የሚል ጥያቄ<br />

ማንሳት በሀገር ክህደት ሊያስከስስ ይችላል፡<br />

፡ ይህ እንኳን ባይሆን የአድሃሪነት ታርጋ<br />

ሊያስለጥፍ ይችላል፡፡<br />

ሌላው የመሬት ባለቤትነት መብትን<br />

የሚያትተው አንቀጽ ነው፡፡ መሬት<br />

የመንግስት ነው፤ ሊሽጥም ሆነ ሊለወጥ<br />

አይችልም የሚለው የኢህአዴግ ግትር<br />

አቋም፣ መሬት የህዝብ መሆን አለበት<br />

ከሚለው የተቃራኒ አቋም ጋር መላተሙ<br />

በህገ-መንግስቱ ላይ ያለውን ልዩነት ሰማይ<br />

እንዲነካ ያደርገዋል፡፡ መሬት የሚሸጠውና<br />

የሚለወጠው በኢህአዴግ መቃብር ላይ ነው<br />

የሚለውን የኢህአዴግ ትንታኔ ነቃፊዎች<br />

የመሬት መሸጥንና መለወጥን ሃሳብ<br />

ለማንበር የግድ ኢህአዴግን መቃብር ውስጥ<br />

መጨመር ግድ ነው ብለው ሊገፉ ይችላሉ፡<br />

፡ በዚህም ህገ መንግስታችን የልዩነት ሰበብ<br />

ከመሆን አልተረፈም፡፡<br />

ማሳያ ስድስት፡- የፍትህና የጸጥታ ተቋማት<br />

አብዛኛውን ጊዜ የሀገራችን የፍትህ<br />

ተቋማት ሁሉንም ሊያስማማ የሚችል<br />

ስራ ሲሰሩ አይታዩም፡፡ እነዚህን የፍትህና<br />

የጸጥታ ተቋማት ስራ በምንዳስስበት ወቅት<br />

የምናገኘው እውነት በጣም አስደንጋጭ ነው፡<br />

፡ ለምሳሌ የሀገር ደህንነትና መረጃ ማዕከል<br />

ስራው የሀገሩን ህልውና መጠበቅ ሆኖ ሳለ<br />

የሚሰራው ስራ ግን ከአንድ የህዝብ ድርጅት<br />

የሚጠበቅ አይደለም፡፡ የኢህአዴግን ህልውና<br />

ለመጠበቅ የተቋቋመ በሚመስል መልኩ<br />

ለኢህአዴግ ያሰጋሉ ያላቸውን ግለሰቦችና<br />

ድርጅቶች እየተከታተለ ማደንና ማስፈራራት<br />

ግፋ ሲልም አፍኖ በመውሰድ አሳፋሪ<br />

ተግባርና እርምጃ ያለ ምንም ፍርድ በራሱ<br />

ሲወስድ ስናይ ተቋሙ የኢህአዴግ የግል<br />

ንብረት ነው እንዴ ያስብላል፡፡<br />

በተጨማሪም ፖሊሶች በተለያየ ወቅት<br />

የወሰዱትን እርምጃ በመንተራስ ስራቸው<br />

ግብር እየከፈለ የቀጠራቸውን ምስኪን ድሀ<br />

መደብደብ ነው እንዴ ብለን እስክንጠይቅ<br />

ያደርሰናል፡፡ ለምሳሌ ያክል በ97 ምርጫ<br />

የተነሳውን አለመግባባት ተከትሎ በመለስ<br />

ዜናዊ ቀጭን ትዕዛዝ መከላከያችንና የፖሊስ<br />

ሀይሉ የወሰደው የእመቃ እርምጃ ከህዝቡ<br />

ጋር እንዲቃቃር አድርጎታል፡፡ በዚህ የተነሳ<br />

ወደ ገፅ 15 ይዞራል


ነገረ-ኢትዮጵያ<br />

ቅፅ 1 ቁጥር 2<br />

ማርቆስ ሀጎሶች እና ዳሮ ነጋሾች ዛሬም<br />

የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም.<br />

ያስፈልጉናል!<br />

-የመንግስት ሰራተኛው እና መምህሩ የደሞዝ ጭማሪ ያስፈልገዋል!<br />

12<br />

እያስፔድ ተስፋዬ<br />

ዓለም አቀፍ ደረጃ የሰራተኛ<br />

ማህበራት እንዴት፣ መቼና ለምን<br />

ተመሰረቱ? ስለምን ታገሉ? ምንስ<br />

አስገኙ? የሚለውን ታሪክ ለመዳሰስ<br />

ቦታውም ጊዜውም አይበቃንም፡፡<br />

የእነዚህ ማህበራት መፈጠር በዓለም<br />

አቀፍ ደረጃ አድካሚ የነበረው የስራ<br />

ሰዓት ወደ 8 ሰዓት ዝቅ እንዲል<br />

መደረግን ጨምሮ ብዙ ለውጦች<br />

አምጥቷል፡፡ የዛሬው ትኩረታችን<br />

ግን የሚሆነው በሀገራችን ከኢሰአማ<br />

አንስቶ እስከ ኢሰማኮ ያለውን<br />

የሰራተኛ ማህበር የመብት ትግል<br />

ታሪክና ዘንድሮም ያላከተመውን<br />

የሰራተኛውን ክፍል (በተለይ<br />

የመንግስት ሰራተኞች) ሰቆቃ እና<br />

ስቃይ በአጭሩ መዳሰስ ነው፡፡<br />

በኃይለስላሴ ዘመን<br />

በሀገራችን ኢትዮጵያ የሰራተኛ<br />

ማህበራት ለመጀመሪያ ጊዜ<br />

የተመሰረቱት በአፄ ኃይለስላሴ<br />

ዘመነ መንግስት ነው፡፡ የታሪክ<br />

ሰነዶች እንደሚጠቁሙት<br />

የመጀመሪያው የሰራተኛ ማህበር<br />

ተብሎ ሊጠቀስ የሚችለው በ1939<br />

የተመሰረተው የኢትዮጵያ ባቡር<br />

ጣቢያ ሰራተኞች ማህበር ነው፡፡<br />

ከዚህ በኋላ ለመመስረት የተሞከሩ<br />

የሰራተኛ ማህበራት በስርአቱ<br />

ከፍተኛ አፈና ይካሄድባቸው የነበሩ<br />

ሲሆን የሰራተኛው መሪዎችም<br />

እስር እና ግድያ ይፈፀምባቸው<br />

ነበር፡፡ የኋላ ኋላም ቢሆን የአፄው<br />

ስርአት ለሰራተኛ ማህበራት<br />

እውቅና በመስጠት ኢሰአማ<br />

(የኢትዮጵያ ሰራተኞች አንድነት<br />

ማህበር) እንዲመሰረት ቢያደርግም፤<br />

የኢሰአማን የበላይ አመራር<br />

የኃይለስላሴ መንግስትና የአሜሪካ<br />

መንግስት (በሲ.አይ.ኤ) አማካኝነት<br />

በቁጥጥራቸው ስር አድርገውት<br />

ነበር፡፡<br />

እናም የልባቸው ያልሞላው የበታች<br />

ሰራተኞች እና ማህበራት የመጀመሪያ<br />

ትግላቸው እነዚህ የአገዛዙ ቀኝ<br />

እጅ የነበሩትን አመራሮች (በየነ<br />

ሰለሞን- ፕሬዝዳንት፣ አለም አብዲ-<br />

ም/ክ ፕሬዝዳንት እና ፍስሀፂዮን-<br />

ፀሀፊ) ማስወገድና በእውነተኛ<br />

የሰራተኛው መሪዎች መተካት ነበር፡<br />

፡ በተጨማሪም የስራው ሁኔታ እና<br />

የመነሻ ደሞዝ እንዲሻሻል የሚሉ<br />

ጥያቄዎችን አንግበው ይታገሉ<br />

ነበር፡፡ በስተመጨረሻም የሰራተኛው<br />

መሪዎች በወቅቱ ከኃይለስላሴ አገዛዝ<br />

ጋር የሞት የሽረት ትንቅንቅ ውስጥ<br />

ከነበሩት ተማሪዎች ጋር ግንኑነትን<br />

ፈጥረው ለስርአቱ ፈታኝ ሆነው<br />

እንደነበር ታሪክ ያስረዳል፡፡<br />

በወቅቱ የሰራተኞች ቁጥር<br />

እንደዛሬው የትየለሌ አይሁን እንጂ<br />

ጥቂቶችም ቢሆኑ ለመብታቸው<br />

እና ለአላማቸው ቆራጦች ነበሩ፡<br />

፡ አብዮቱ በፈነዳበት በ1966 ዓ.ም<br />

አካባቢ በኢሰአማ ስር ተመዝግበው<br />

ይገኙ የነበሩ ሰራተኞች ቁጥር ወደ<br />

100 ሺህ ይደርስ ነበር፡፡ አፈናው<br />

እና ጭቆናው ሊያስቀረው ያልቻለው<br />

አብዮት እንዲነሳ የሰራተኛ ማህበሩ<br />

ያደረገው አስተዋፅኦም በቀላሉ<br />

የሚገመት አይደለም፡፡<br />

በ”ጊዜያዊ” ወታደራዊ መንግስት<br />

ደርግ ዘመን<br />

ከኃይለስላሴ መውረድ እና<br />

“ጊዜያዊ” ወታደራዊው መንግስት<br />

ወደ ስልጣን መምጣት በኋላም<br />

ቢሆን የሰራተኛውን መብት<br />

ለማስከበር ከሚደረጉ ትግሎች<br />

በተጨማሪ በይፋ ጊዜያዊ ህዝባዊ<br />

መንግስት እንዲመሰረት የሚጠይቁ<br />

መግለጫዎችንና የዴሞክራሲያዊ<br />

መብቶች መከበርን የሚደግፉ<br />

መግለጫዎችን በማውጣት<br />

በኢትዮጵያ ፖለቲካ ታሪክ ውስጥ<br />

ጉልህ ሚና ተጫውቷል፡፡<br />

የሰራተኛ ማህበሩ የጊዜያዊ ህዝባዊ<br />

መንግስት ይመስረት ጥያቄን<br />

ማንሳት ያልተዋጠለት ደርግ<br />

እንደ ኃይለስላሴ ሁሉ የሰራተኛ<br />

መሪዎችን ማሰርንና መግደልን<br />

ስራዬ ብሎ ተያያዘው፡፡ በተለይም<br />

ኢሰአማ (የሰራተኛው ማህበር)<br />

ከመስከረም 8 እስከ 11 ባደረገው<br />

የሶስት ቀናት ጉባኤ መንግስት<br />

የሰራተኞች መሪዎችንና ሌሎች<br />

የፖለቲካ እስረኞችን እንዲፈታ፣<br />

በዴሞክራሲያዊ መብት ላይ<br />

የተጫነው ገደብ እንዲነሳ፣ ጊዜያዊ<br />

ህዝባዊ መንግስት እንዲመሰረት<br />

የሚጠይቅ መግለጫ ማውጣቱን<br />

ተከትሎ መስከረም 16 ቀን<br />

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኞች<br />

ማህበር አባላት የጉባኤውን ውሳኔ<br />

ለሰራተኞች በሚያድሉበት ጊዜ<br />

ወታደሮች በወሰዱባቸው የማጥቃት<br />

እርምጃ 8 ሰዎች መግደላቸው<br />

እና በ20ዎች ማቁሰላቸው የሚረሳ<br />

አይደለም፡፡ ደርግም “በኢትዮጵያ<br />

አየር መንገድ መስሪያ ቤት ውስጥ<br />

ፀረ አብዮት ፅሁፍ ሲበትን የነበረ ሰው<br />

እንዳያዝ በማወካቸው ወታደሮች<br />

ተኩስ ለመክፈት ተገደዱ” በማለት<br />

በይፋ ለማስተባበል ሞክሮ ነበር፡፡<br />

ማርቆስ ሀጎስ<br />

ማርቆስ የደርግ ሰለባ ከሆኑት<br />

የሰራተኛው ግንባር ቀደም መሪዎች<br />

አንዱ ነበር፡፡ ከኃይለስላሴ ዘመን<br />

ጀምሮ ለሰራተኛው መብት እና<br />

ለኢትዮጵያ ህዝብ መብት ሲታገል<br />

የቆየው ማርቆስ እሱ በሃላፊነት<br />

የሚመራው የሰራተኛ ማህበር<br />

ለደርጉ በስልጣን ላይ ተደላድሎ<br />

መቀመጥ አመቺ ሆኖ ስላልተገኘ<br />

ገና በጠዋቱ ነበር ለእስር የተዳረገው፡<br />

፡ በእስርም እያለ ከፍተኛ ስቃይ<br />

ከተቀበሉ የሰራተኛው መሪዎች<br />

አንዱ ነው፡፡ አንዳንዴም ከድብደባው<br />

የተነሳ ብዙ ደም ይፈሰው ስለነበር<br />

የወቅቱ የደህንነት ሹም ዳንኤል<br />

አስፋው ማርቆስን ወንበር<br />

እንዳታበላሽ መሬት ላይ ቁጭ በል<br />

ሲል ያዘው ነበር፡፡ አንዳንዴም ደም<br />

በደም ከሆነ በኋላ በእስረኞች መሀል<br />

እያዞሩት ይሄ ነው ንጉስ የሚሆነው<br />

እያሉ ያፌዙበት ነበር፡፡ በመጨረሻም<br />

ማርቆስ ሰማዕት ሆኖ ከመሞቱ<br />

በፊት እጅግ አስቀያሚ እንደሆነ<br />

ወደሚነገርለት ወደ ማይጨው ጦር<br />

ሰፈር እስር ቤት ተዘዋውሮ ነበር፡፡<br />

የሰራተኛው መሪዎችን በማሰርና<br />

በመግደል ያልተመለሰው ደርግ<br />

የሰራተኛው ማህበርን በነፃነት<br />

እንዳይንቀሳቀስ ስላደረገው<br />

ሰራተኛው በግልፅ መደራጀቱን<br />

በመተው በህዕቡ የላባደር ማህበርን<br />

(ኢላማ) በመመስረት ለሰራተኛው<br />

መብት መከበር የሚደረገውን ትግል<br />

አጧጧፈው፡፡<br />

ዳሮ ነጋሽ<br />

ዳሮ ነጋሽ የደርጉን አፈና ለመቋቋም<br />

ሲባል በህቡዕ የተደራጀው<br />

የኢትዮጵያ ላብአደሮች ማህበር<br />

መሪዎች መካከል አንዷ ነበረች፡፡<br />

የብርሀንና ሰላም ማተሚያ መስሪያ<br />

ቤት ሰራተኛ የነበረችው ዳሮ ነጋሽ<br />

የ5 ልጆች እናት የነበረች ቢሆንም<br />

ለሰራተኛው መብት መከበር<br />

ከመታገል ግን ወደ ኋላ ሊያስቀራት<br />

አልቻለም ነበር፡፡ ቤቷን ሳይቀር<br />

ለህቡዕ ስብሰባዎች ማካሄጃነት ክፍት<br />

ያደረገችው ዳሮ ቆራጥ እና በአላማዋ<br />

ፅኑ ሴት ነበረች፡፡ የዜጎች መደራጀት<br />

ያስበረግገው የነበረው ደርግም የ 9<br />

ወር እርጉዝ እና የ 5 ልጆች እናት<br />

የነበረችውን ዳሮ ነጋሽን ያለ ምንም<br />

ርህራሄ በጥይት ደብድቦ ገደላት፡፡<br />

ዳሮ ነጋሽ ለሰራተኛው እና ለሰፊው<br />

ህዝብ መብት ሰማዕት የሆነች ጀግና<br />

ነበረች፡፡<br />

ደርግ እንዲህ ያሉ አሰቃቂ<br />

እርምጃዎችን በማህበራቱ እና<br />

በማህበራቱ መሪዎች ላይ ይውሰድ<br />

እንጂ ሰራተኛው ለመብቱ<br />

የሚያደርገውን ትግል ሊያስቆመው<br />

አልቻለም፡፡<br />

በተለያዩ ወቅቶች የስራ ማቆም<br />

አድማ፣ የስራ ማለዘብ (ማቀዝቀዝ)፣<br />

የማሺን መስበር ወዘተ ያሉ<br />

የትግል ስልቶችን በመጠቀም<br />

ሰራተኞች መብታቸውን ለማስከበር<br />

እስከመጨረሻው ታግለዋል፡፡<br />

በህወሓት/ኢህአዴግ ዘመን<br />

በዘመነ ደርግ ለመብታቸው መከበር<br />

ከፍተኛ ተጋድሎ ያደርጉ የነበሩት<br />

ማህበራት በዘመነ ህወሓት/ኢህአዴግ<br />

ዘመንም ቢሆን የትግላቸውን ፍሬ፤<br />

የመብታቸውን መከበር ሊጎናፀፉ<br />

አልቻሉም፡፡ እስርና ስደትና ግድያው<br />

አሁንም ቀጠለ፡፡<br />

ዳዊ ኢብራሂም (የሰራተኛ ማህበር<br />

ፕሬዝዳንት የነበረ)<br />

ህወሓት/ኢህአዴግ ስልጣን<br />

እንደያዘ እንዳለፉት ስርአቶች<br />

ሁሉ የሰራተኛ ማህበሩን በራሱ<br />

ቁጥጥር ስር ለማድረግ ቢፈልግም<br />

በወቅቱ የሰራተኛ ማህበሩ መሪዎች<br />

የነበሩት በተለይም ፕሬዝዳንቱ ዳዊ<br />

ኢብራሂም የሚቀመሱ አልሆኑም፡<br />

፡ ስለዚህም አመራሮቹን ከማሰር<br />

እና ከማስፈራራት አልፎ የተለያዩ<br />

አሻጥሮችን መስራቱ የቅርብ ጊዜ<br />

ትውስታ ነው፡፡ በመጨረሻም ጫናው<br />

የበዛባቸው የማህበሩ ፕሬዝዳንት<br />

ዳዊ ኢብራሂም በሞያሌ በኬንያ<br />

አድርገው ሊሰደዱ በቅተዋል፡፡<br />

አሰፋ ማሩ (የመምህራን ማህበር<br />

ፕሬዝዳንት የነበረ)<br />

ህወሓት/ኢህአዴግ ያመጣውን<br />

የትምህርት ፖሊሲ በግልፅ<br />

የተቃወመው የመምህራን ማህበርም<br />

የደረሰው እጣ ፋንታ ያለፉት<br />

ስርአቶች ያደርጉ ከነበረው የተለየ<br />

አይደለም፡፡ የመምህራን ማህበር<br />

ነፃነት ለድርድር እንደማይቀርብ<br />

ግልፅ ያደረገው አመራርም<br />

የተወገደበት መንገድ አነጋጋሪና<br />

ጊዜ የሚፈታው ጉዳይ ነው፡፡<br />

የመምህራን ማህበሩ ፕሬዝዳንት<br />

የነበረው አሰፋ ማሩ ከቤቱ ወጥቶ<br />

በእግሩ በሚጓዝበት ወቅት በቀን<br />

በአደባባይ በጥይት ተገድሏል፡፡<br />

አሁንስ? ኢሰማኮ?<br />

አሁን ያለው የሰራተኛ ማህበር<br />

ለሰራተኛው መብት መከበር<br />

የሚታገል ነፃ ማህበር ነው<br />

ወይስ የህወሓት/ኢህአዴግን<br />

ፖሊሲ እንደወረደ የሚያስፈፅም<br />

የስርአቱ ቀኝ እጅ? በኃይለስላሴ<br />

ዘመን የሰራተኛ ማህበሩ የመነሻ<br />

ደሞዝ ይስተካከል ሲል ያቀረበው<br />

ጥያቄ ዛሬስ ቢሆን ተሻሽሏል???<br />

በመንግስት መስሪያ ቤት ውስጥ<br />

በዲግሪ ተመርቆ የሚቀጠር ሰራተኛ<br />

የመነሻ ደሞዙ 1499 ብር ብቻ<br />

ነው፡፡ በ800 ብሩ ቤት ተከራየ<br />

ብንል...ለትራንስፖርት 300 ብር<br />

አወጣ ብንል በቀረችው ብር ወሩን<br />

የሚዘልቀው እንዴት ነው? ምንስ<br />

እየተመገበ ነው የሚዘልቀው? ይህ<br />

ሰው ቤተሰብ ያለው ከሆነ ደግሞ<br />

የልጆች ቀለብ የልጆች ት/ቤት<br />

ወዘተ ይጠብቀዋል፡፡ ይህ የመነሻ<br />

ደሞዝ ለአመታት ሳይጨምር<br />

ሲቆይ የሰራተኛ ማህበሩ አንዳችም<br />

ተቃውሞ አሰምቶ አያውቅም!<br />

በዚህም ማህበሩ የስርአቱ ቀኝ<br />

እጅ እንጂ ሰራተኛውን የሚወክል<br />

እንዳልሆነ ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፡፡<br />

ምን ይደረግ?<br />

ሰራተኛው አሁን ያለው ማህበር<br />

እንደማይወክለው ካወቀና<br />

አይወክለኝም ብሎ ካለ ህጉ<br />

በሚፈቅድለት መሰረት ሌላ የሰራተኛ<br />

ማህበር ማቋቋም ይችላል፡፡ ህጉ<br />

በአንድ መስሪያ ቤት ውስጥ ከአንድ<br />

በላይ የሆኑ ማህበሮችን ማቋቋም<br />

እንደሚቻል በግልፅ ቢያስቀምጥም<br />

በአንድ በኩል ከፍርሀት በሌላ<br />

በኩል ደግሞ ካለው አፈና እና ጫና<br />

የተነሳ በአንድ መስሪያ ቤት ውስጥ<br />

ከተለመደው ማህበር ውጪ ሌላ<br />

ማህበር ለማቋቋም ጥረት ሲደረግ<br />

አይታይም፡፡ ሰራተኛው በተናጠል<br />

የሚደረግ መብትን የማስከበር<br />

ስራ የትም እንደማያደርስ አውቆ<br />

ባመቸው መንገድ ሊደራጅ ይገባል፡፡<br />

በግልፅ ተደራጅቼ መብቴን<br />

ለማስከበር ያለው ሁኔታ አመቺ ነው<br />

ብሎ ካመነ በግልፅ ሊደራጅ አሊያም<br />

በግልፅ ለመደራጀት የሚያስችል<br />

ነፃና አመቺ ሁኔታ የለም ካለ ደግሞ<br />

ልክ ነው ባለው መንገድ ተደራጅቶ<br />

መብቱን ማስከበር የሰራተኛው<br />

ሀላፊነት ነው፡፡ ሁሉም በቤቱ<br />

ተቀምጦ ቢያጉረመርም በአንድ<br />

ላይ ተደራጅቶ እስካልተነሳ ድረስ<br />

የሚያመጣው ለውጥ አይኖርም!<br />

ሰራተኛው ተደራጅቶ ምን ያድርግ፣<br />

የተባለ እንደሆነ መብቱን ለማስከበር<br />

ሲል የስራ ማቆም አድማ! ያ<br />

ያልተሳካ እንደሆነ እንኳን የስራ<br />

ማለዘብ (ማቀዝቀዝ) ወዘተ ያሉ<br />

የትግል ስልቶችን በመጠቀም ቆራጥ<br />

እርምጃን መውሰድ ይኖርበታል፡፡<br />

የዘመናችን ማርቆስ ሀጎስ ሆይ ተነሳ!<br />

የዘመናችን ዳሮ ነጋሽ ሆይ ተነሺ!!!<br />

ሁልጊዜም ቢሆን ትግል ከፊት ሆነው<br />

የሚመሩ ቆራጦችን ይጠይቃል!<br />

ዛሬም ከልጆቿ በፊት የሰራተኛውን<br />

እና የሰፊውን ህዝብ መብት መከበር<br />

ቅድሚያ የምትሰጥ ጀግና ደፋር<br />

ዳሮ ነጋሽ ታስፈልገናለች፡፡ ዛሬም<br />

ለሰራተኛው መብት መከበር እና<br />

ለሰፊው ህዝብ ጥቅም ሲል ህይወቱን<br />

ሊሰጥ የቆረጠ ጀግና ደፋር ማርቆስ<br />

ሀጎስ ያስፈልገናል፡፡ አንቺ/አንተ<br />

እንዳትሆኚ/ን ምን ይከለክልሻል/<br />

ሃል?


13የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2<br />

ነገረ-ኢትዮጵያ<br />

መመረጥ በሌላው ድክመት<br />

ሳይሆን በራስ ጥንካሬ<br />

ታምራት ታረቀኝ<br />

ፓርቲ የሚመሰረተው ለሀገር ይበጃሉ<br />

ተብሎ የታመነባቸው ፖለቲካዊ፣<br />

ኢኮኖሚዊና ማህበራዊ ዓላማዎች<br />

ተቀርጸውና እቅድ ተዘጋጅቶ<br />

የአፈጻጸም ስልትም ተነደፎ ነው፡፡<br />

አንድ ፓርቲ የሚኖሩት ሁለት ዋንኛ<br />

ሰነዶች ፕሮግራምና መተዳደሪያ<br />

ደንብም የሚያሳዩት ይህንኑ<br />

ነው፡፡ ፕሮግራሙ ዓላማውን<br />

መተዳደሪያ ደንቡ የአሰራር ሥልቱን<br />

ያመለክታሉ፡፡ ፓርቲው በፕሮግራሙ<br />

የሰፈረውን ዓላማውን ገቢራዊ<br />

ማድረግ የሚችለው የመንግሥትነት<br />

ሥልጣን ሲያገኝ ነው፡፡ ስለዚህም<br />

ነው የፖለቲካ ፓርቲ ዋንኛ ትግል<br />

የሥልጣን ጥያቄ የሚሆነው፡፡<br />

ለዓላማው ከግብ መድረስ<br />

የሚታገልበትን መንገድ ሠላማዊ<br />

ያደረገ ፓርቲ የሥልጣን ጥያቄውን<br />

ለማሳካት የሚጠቀምበት አንድና<br />

ብቸኛ መንገድ ደግሞ ምርጫ ነው፡<br />

፡ ነጻ ትክክለኛና ወቅታዊ ምርጫ፡<br />

፡ ይህ ዓይነቱ ምርጫ እውን<br />

ሊሆን የሚችለውም ዴሞክራሲያዊ<br />

ሥርዓት በአስተማማኝ መገንባት<br />

ሲቻል፣ አልያም በሥልጣን<br />

ላይ ያለው መንግስት አጠቃላይ<br />

ሁኔታዎችን ተገንዝቦ ራሱን<br />

በመለወጥ ወይንም በውስጥና<br />

በውጪ ተጽእኖ ተንበርክኮ ዓለም<br />

አቀፍ መስፈርቶችን የሚያሟላ<br />

ምርጫ ለማካሄድና ውጤቱንም<br />

በጸጋ ለመቀበል ሲዘጋጅ ነው፡፡<br />

ስለሆነም አንድ ፓርቲ ዓላማውን<br />

ተፈጻሚ ለማድረግ የሚያስፈልገውን<br />

ሥልጣን በትክክልና በአስተማማኝ<br />

ሁኔታ ለመጨበጥ በሀገሪቱ<br />

አስተማማኝ የዴሞክራሲያዊ<br />

ሥርዓት መሰረት እንዲጣል ይህ<br />

ካልሆነም ነጻና ፍትሀዊ ምርጫ<br />

ለማካሄድ የሚያሰችሉ ሁኔታዎች<br />

እንዲሟሉ መታገል ቀዳሚ ተግባሩ<br />

ይሆናል፡፡<br />

በምርጫው ማግሥት ውጤቱ<br />

በአሳዛኝ ሁኔታ ቢበላሽም ቅንጅት<br />

ከዚህ አንጻር በየታሪክ ወቅቶች<br />

የሚነሳ ተግባር አከናውኗል፡፡<br />

ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት አልነበረም፣<br />

ምርጫ ቦርድ አልተለወጠም፣<br />

የፖለቲካ ምህዳሩ ጠቧልና<br />

ከኢህአዴግ ጋር ካላተደራደርን ብሎ<br />

ልመናም ሆነ ምልጃ አላቀረበም፡፡<br />

በአጭር ግዜ እንቅስቃሴ መታመንን<br />

አተረፈና የሠላማዊ ትግሉ ዋንኛ<br />

ኃይል የሆነውን ሕዝብ በአንድ<br />

መንፈስ በቁርጠኝነት ለማሰለፍ<br />

ቻለ፣ እናም ያንን በዚህ ትውልድ<br />

ድጋሜ ስለመታየቱ ማንም ርግጠኛ<br />

ሆኖ ሊናገር የማይችለውን ዓለምን<br />

«….ኢህአዴግ መስተጋብሩን<br />

ጠብቆ በማያቋርጥ ሁኔታ እያሸነፈ<br />

መቀጠል ያለበት ድርጅት ነው፤<br />

መስተጋብሩን ጠብቆ በማያቋርጥ<br />

ሁኔታ የህዝቡን ልብ ይዞ፣ የህዝብ<br />

ልብ የሚያዘው በማያቋርጥ የልማት<br />

እንቅስቃሴ፣ በማያቋርጥ የህዝቡን<br />

ፍላጎት የማርካት እንቅስቃሴ፣<br />

በማያቋረጥ መልካም አስተዳደርን<br />

የመገንባት እንቅስቃሴዎች ነው፣<br />

ከዚህ ውጪ የሚመጣ አይደለም፣<br />

በታሪክ ማሸነፍ አይቻልም፣ ማሸነፍ<br />

የሚቻለው በተጨባጭ ተግባር ብቻ<br />

ነው፣ ምርጫን በታሪክ ማሸነፍ<br />

አይቻልም…» በማለት የተናገሩት<br />

የኢህአዴግ የእለት ተእለት<br />

እንቅስቃሴ ምርጫን መሰረት ያደረገ<br />

መሆኑን ያሳያል፡፡<br />

በአንጻሩ አብዛኛዎቹ ተቀዋሚዎች<br />

ለመመረጥ ኢህአዴግ ሕዛባዊ<br />

ተቀባይነት ስለሌለው ነጻ ምርጫ<br />

ከተካሄደ ሕዝቡ ተቀዋሚዎችን ነው<br />

የሚመርጠው በማለት የራሳቸውን<br />

ጥንካሬ ገንብተውና አስተማማኝ<br />

አማራጭ ሆነው በመቅረብ ሳይሆን<br />

በኢህአዴግ ድክመት እንመረጣለን<br />

ብለው የሚያስቡ በመሆናቸው<br />

ምርጫ የሚታሰባቸው ምርጫ ቦርድ<br />

የግዜ ሰሌዳ ሲያወጣ ነው፡፡ በዛች<br />

አጭር ግዜ በሚደረግ ዝግጅት ወደ<br />

ምርጫ መግባት ደግሞ ውጤት<br />

አያመጣም፡፡ የተሸነፍነው ምርጫው<br />

ተጭበርብሮ ነው ምርጫ ቦርድ<br />

ገለልተኛ ባለመሆኑ ነው በደል<br />

ተፈጽሞብን ነው ወዘተ የሚሉ<br />

ክሶችም ከባዶ ጩኸትነት ሊያልፉ<br />

አይችሉም፡፡ አንደ ፕ/ር መድሀኔ<br />

ታደሰ አባባል ምርጫ ሁለት<br />

ዓመትም ሲቀረው ይጨበረበራልና<br />

ስለ ምርጫ የሚሰራው የቀደመው<br />

ምርጫ በተካሄደ ማግስት ጀምሮ<br />

መሆን አለበት፡፡ ይህ ጉዳይ ሲነሳ<br />

ቅንጅት በስድስት ወር ግዜ አይደለም<br />

ወይ ለማሸነፍ የበቃው የሚል<br />

መከራከሪያ ለማቅረብ የሚዳዳቸው<br />

አሉ፡፡ ይህን የሚሉ ፖለቲከኞች፣<br />

1. ከላይ የጠቀስኳቸው አፈ<br />

ጉባኤ አባዱላ ገመዳ እንዳሉት<br />

ምርጫን በተጨባጭ ተግባር እንጂ<br />

በታሪክ ማሸነፍ ማይቻል መሆኑን፣<br />

2. ቅንጅትን ለአሸናፊነት<br />

ያበቁትን መንገዶች ሁሉ ኢህአዴግ<br />

ከምርጫው ማግስት ጀምሮ<br />

የዘጋቸው መሆኑን፣<br />

3. በቅንጅት ምስረታና<br />

በምርጫ 97 መካከል የነበረው<br />

ግዜ ስድስት ወራት ብቻ ቢሆኑም<br />

ቅንጅትን የመሰረቱት በተለይ<br />

መኢአድና ኢዴፓ በረዥም ግዜ ሰፊ<br />

የምርጫ ስራ የሰሩና በቂ ዝግጅት<br />

ያደረጉ መሆኑን የዘነጉ ናቸው፡፡<br />

በምርጫ ውጤታማ ተወዳዳሪ<br />

ለመሆን የሚያስብ ፓርቲ በቅድሚያ<br />

በራሱ ጥንካሬ ለመመረጥ አልሞ<br />

የእለት ተእለት እንቀስቃሴው<br />

በመራጩ ልብ ውስጥ የሚገባና<br />

መታመንን የሚያስገኝለት እንዲሆን<br />

መስራት አለበት፡፡ ስለሆነም<br />

ሀገራዊና ዓለም ዓቀፋዊ ተጨባጭ<br />

ሁኔታዎችን ከፕሮግራሙ ጋር<br />

በማገናዘብ የአጭርና የረዥም ጊዜ<br />

እቅድ አዘጋጅቶ ለአፈጻጸሙም<br />

ግልጽ የሆነ የአሰራር ስልት ነድፎ<br />

የሚታይና የሚታመን እንቅሰቃሴ<br />

ማድረግ ይኖርበታል፡፡ በቢሮ<br />

ከትሞ፣ ከመግለጫ የዘለለ ተግባር<br />

ሳያሳዩ ከርሞ ሰዉ በኢህአዴግ<br />

አገዛዝ ተሰላችቷል ለውጥ ይፈልጋል<br />

በመሆኑም ተቀዋሚዎችን<br />

ይመርጣል በሚል እሳቤ ብቻ<br />

በምርጫ ሰሞን ብቅ በማለት ወንዝ<br />

በሌለበት ድልድይ አሰራለሁ አይነት<br />

ቅስቀሳ ማካሄድና ከእኔ በላይ ለሀገር<br />

አሳቢ ለህዝብ ሰሪ አይርኖም የሚል<br />

ፕሮፓጋንዳም እንበለው የምርጫ<br />

ቅሰቀሳ ማካሄድ ባዶ ጩኸት ነው<br />

የሚሆነው፡፡<br />

በየደረጃው የሚገኙት የፓርቲው<br />

መሪዎችና አባላት ማንነትና<br />

የተግባር እንዴትነት ብሎም<br />

በዕጩነት የሚያቀርባቸው<br />

ተወዳዳሪዎች ማንነት በምርጫው<br />

ውጤት ለማምጣት ወሳኝ ናቸው፡<br />

፡ እስከ መስዋዕትነት በሚጠይቀው<br />

ሠላማዊ ትግል ውስጥ የትወልድ<br />

ድርሻቸውን ሊያበረክቱ በበጎ<br />

ፈቃደኝነት የተሰለፉ አባላቱ የጠበቀ<br />

የዓላማ ትስሰርና የመንፈስ አንድነት<br />

አንዲሁም መተማመን ሲኖራቸው፣<br />

በመኖሪያ አካባቢያቸውም ሆነ<br />

በሥራ ቦታቸው በሥነ ምግባራቸው<br />

የተከበሩ በስራቸውም የተወደዱ<br />

ሲሆኑ የመራጩን ሕዝብ ቀልብ<br />

በመሳብ ፓርውን ለውጤት<br />

ያበቁታል፡፡ ይህ ሳይሆን ተቀዋሚ<br />

በመሆን ብቻ እንመረጣለን ብሎ<br />

ማሰብ ምርቻን በታሪክ ማሸነፍ<br />

እንደማይቻል ያለመገንዘብ ነውና<br />

ምርጫ 2007 እንደ ምርጫ 2007<br />

እንዳይሆን ያሰጋል፡፡<br />

ፓርቲዎች በየግል ተጠናክረው<br />

በጋራ ተማምነው በስፋት መክረውን<br />

በረዥሙ አቅደው ሳይሆን ተባብረን<br />

ከታየን ሕዝቡ ይመርጠናል በሚል<br />

ብቻ በምርጫ ሰሞን የሚካሄድ<br />

የመተባበር ሆይ ሆይታም ጥንካሬ<br />

ፈጥሮ አስተማማኝ አማራጭ<br />

ሆኖ ከመቅረብ የሚነሳ ባለመሆኑ<br />

ለውጤት አያበቃም፡፡ እንደምንም<br />

ተደጋግፈን ከፊት ለፊታችን ያለውን<br />

ግዙፍ ተራራ መናድ የሚለው<br />

የኋላ መሰረት የዛሬ ጥንካሬ የፊት<br />

ራዕይ የሌለው ሥልጣንን ብቻ<br />

አስቦ የሚነሳ መደጋገፍ ፈጥረው<br />

ለምርጫ ቢቀርቡም የሚፈጥሩት<br />

መጎነታተል(በቅንጅትም<br />

በመድረክም የታየ ነው) ደካማ<br />

አቅማቸውን ይበልጥ ያዳክመውና<br />

ለኢህአዴግ አሸናፊነት ምቹ ሁኔታ<br />

ይፈጥሩለታል፡፡<br />

ዛሬ ትናንት አይደለም ነገሮች ተለዋውጠዋል፣ ጠንክሮ በመገኘት<br />

እንጂ በሌላው ድክመት ለመመረጥ ማለም ግዜ አልፎበታል፡<br />

፡ ኢህአዴግን ደካማ አድርጎ ማሰብም በራሱ ትልቅ ድክመት<br />

ይመስለኛል፡፡ በደቂቃ ውስጥ መረጃ ለሚሊዮኖች በሚደርስበት<br />

ዘመን በተግባር ሆኖ ሳይሆን በፕሮፓጋንዳ መስሎ በመቅረብ<br />

ለውጤት መብቃት የሚቻል አይደለም፡፡<br />

በየግላቸው ድርጅታዊ ብቃት<br />

ሳይፈጥሩ በጋራም በቅጡ<br />

መክረው የጋራ እቅድ ሳይነድፉና<br />

ሆነው ሳይሆን መስለው ለምርጫ<br />

በመቅረብ በጥረታቸው ሳይሆን<br />

በሕዝቡ ለውጥ ፈላጊነትና ታሪክ<br />

ሰሪነት ለአሸናፊነት ቢበቁ ውጤቱን<br />

አሰጠብቀው በስምምነት የሥልጣን<br />

ክፍፍል አድርገው በምርጫ ያገኙትን<br />

ውጤት ወደ ተግባር በመለወጥ<br />

ሕዝቡ በድምጹ የሰጣቸውን ኃላፊነት<br />

መወጣት መቻላቸው ያጠራጥራል፡<br />

፡ ምክንያቱም ወደ ምርጫ የገቡት<br />

ጥንካሬ ፈጥረው የህዝብን አመኔታ<br />

አትርፈው ሳይሆን በመተባበር ሽፋን<br />

በመሆኑ ነው፡፡<br />

አንድነቱ የጠነከረ፣ በሚያራምደው<br />

ዓላማ በእኩል ደረጃ እምነት<br />

ያለው፣ በፓርቲ ዲስፕሊንና በንጹህ<br />

ሰብአዊ ፍቅር የተሳሰረ፣ እሰከ<br />

መስዋእትነት አብሮ ለመዝለቅ<br />

የተማመነ ከአባለቱም ሆነ ከመራጩ<br />

ሕዝብ አመኔታን ያተረፈ አመራር<br />

እንዲሁም በዓላማው የጸና ሞራሉ<br />

የተገነባና በመንፈስ የጠነከረ አባል<br />

መኖር ለአንድ ፓርቲ ዓላማ<br />

መሳካትም ሆነ ተባብሮ በምርጫ<br />

ለመሰለፍ በእጅጉ ወሳኝ ናቸው፡<br />

፡ ይህ በምርጫ ለማሸነፍ ወሳኝ<br />

የሆነ የፓርቲ ጥንካሬ ማሳያ በአንድ<br />

ሰሞን የሚገነባ አለመሆኑ ምርጫን<br />

የረዥም ግዜ ስራ ከሚያደርጉት<br />

ምክንያቶች አንዱ ይሆናል፡፡<br />

በተለይ የፓርቲው አመራር በአደባባይ<br />

ስለ ፍቅር እየሰበከ በፓርቲው<br />

ውስጥ ጥላቻን የሚያነግስ ከሆነ፣<br />

ስለ አንድነት እያዜመ ተለያይቶ<br />

የሚቆም ከሆነ፣ ሥልጣን ላይ ካለው<br />

ፓርቲ ጋር መነጋገር እሻለሁ እያለ<br />

በሀሳብ ከሚለዩ የአመራር አባላትም<br />

ሆነ ጥያቄ ከሚያነሱ አባላት ጋር<br />

ለመነጋገር የማይደፍር ከሆነ፣<br />

ዘመናት ላስቆጠረው የሀገራችን<br />

ችግር ዋናው መፍትሄ ብሔራዊ<br />

እርቅ ነው ብሎ በፕሮግራሙ አስፍሮ<br />

ይህንኑ በአደባባይ እየተናገረና<br />

ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር<br />

የሚያስችል ጉባኤ አሰፈላጊነትን<br />

እየጠየቀ፣ በፓርቲው ውስጥ<br />

የሚፈጠሩ ጥቃቅን ልዩነቶችን<br />

በውይይት መፍታትና በእርቅ<br />

ማድረቅ የማይችል ከሆነ ወ.ዘ.ተ<br />

እንኳን በመራጩ ሕዝብ ዘንድ<br />

በአባላቱም መታመንና መከበርን<br />

ሊያተርፍ አይችልም፡፡ አመራሩ<br />

ካልታመነ ደግሞ ፓርቲው ሊታመን<br />

አይችልም፡፡ የማይታመን ደግሞ<br />

አይመረጥም፡፡<br />

ዛሬ ትናንት አይደለም ነገሮች<br />

ተለዋውጠዋል፣ ጠንክሮ በመገኘት<br />

እንጂ በሌላው ድክመት ለመመረጥ<br />

ማለም ግዜ አልፎበታል፡፡<br />

ኢህአዴግን ደካማ አድርጎ ማሰብም<br />

በራሱ ትልቅ ድክመት ይመስለኛል፡<br />

፡ በደቂቃ ውስጥ መረጃ ለሚሊዮኖች<br />

በሚደርስበት ዘመን በተግባር ሆኖ<br />

ሳይሆን በፕሮፓጋንዳ መስሎ<br />

በመቅረብ ለውጤት መብቃት<br />

የሚቻል አይደለም፡፡<br />

ፖለቲከኞቹ ከደረሰባቸውም<br />

ካደረሱትም መማር ባይችሉም<br />

ሕዝቡ ከሁሉም አቅጣጫ ከደረሰበትና<br />

ከሚደርስበት ችግር፣ በየጊዜውም<br />

ከሚያይና ከሚሰማው እንዲሁም<br />

21 ዓመታት ለውጥ ካላመጣውና<br />

መስዋዕትነቱ ግን ካልተቋረጠው<br />

ትግል ብዙ ተምሯል፡፡ ተፎካካሪ<br />

ፓርቲዎች ትግላቸው ለውጤት<br />

ባያበቃውም ዳፋቸው እያዳፋው ብዙ<br />

መከራ አይቷል፣ ስለሆነም ምንም<br />

ማድረግ ባይችል በሚታወቅበት<br />

ዝምታው ይሸኛል፡፡<br />

በመሆኑም ሕዝብን የሠላማዊ<br />

ትግሉ ተሳታፊ ብቻ ሳይሆን<br />

ባለቤት ለማድረግና በምርጫ 2007<br />

ለውጥ ለማምጣት ራስን አጥርቶና<br />

ወደ ገፅ 15 ይዞራል


ነገረ-ኢትዮጵያ<br />

ሰማያዊ<br />

ቅፅ 1 ቁጥር 2<br />

የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም.<br />

ይህ ገጽ በሰማያዊ ፓርቲ አዘጋጅነት የሚቀርብ ሲሆን፣ ፓርቲው ፕሮግራሙንና<br />

አላማውን ለአባላትና ደጋፊዎቹ የሚያደርስበት ነው፡፡<br />

14<br />

መንደርደሪያ<br />

ሰማያዊ ፓርቲ በዘር፣ በሃይማኖት በቋንቋ በፆታና በሌሎች<br />

ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መመዘኛዎች በዜጎች መካከል<br />

ልዩነት ሳያደርግ በማደራጀት የኢትዮጵያን ህዝቡ የሥልጣን<br />

ባለቤትነት ለማረጋገጥ ይታገላል፡፡<br />

ሰማያዊ ፓርቲ ለምን<br />

ተመሰረተ?<br />

ሀገራችን ኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ አኩሪ ታሪክ፣ ቀደምት<br />

የሥልጣኔ ባለቤትና ከ3000 ዘመን በላይ የመንግስትነት<br />

ታሪክ ያላት ታላቅ ሀገር ናት፡፡ የሰው ልጅ ዛሬ ለደረሰበት<br />

የዕድገትና የስልጣኔ ደረጃ መሰረት የሆኑ ቁሳዊና መንፈሳዊ<br />

ትውፊቶችን በማበርከት ለዓለም ስልጣኔ ታላቅ አስተዋፅዖ<br />

አበርክታለች፡፡ በየዘመናቱ ነፃነቷን ለማጥፋት የወረሯትን<br />

የውጭ ተስፋፊዎችና ቅኝ ገዥዎች በተደጋጋሚ ጊዜ ድል<br />

በማድረግ ነፃነቷንና ሉዓላዊነቷንም አስከብራ ኖራለች፡<br />

፡ ሀገራችንን በእብሪት ለመውረር የመጣውን የኢጣሊያን<br />

ወራሪ በመደምሰስ በዓለም ለመጀመሪ ጊዜ ጥቁር የሰው ልጅ<br />

ዘር ነጭ ወራሪዎችን ማሸነፍ እንደሚችል በአድዋ ታሪካዊ<br />

ድል ያስመሰከረች ብቸኛ የጥቁር ሰው ዘር መኩሪያና<br />

መመኪያ ሃገር ነች፡፡<br />

ቅኝ ገዥዎችና ኢምፔሪያሊስቶች አፍሪካን ለመቀራመትና<br />

የተፈጥሮ ሃብቷን ለመዝረፍ ያደረጉትን ስምምነት ተከትሎ<br />

አፍሪካን በቅኝ ግዛት ስር ለማዋል በተደረገው ወረራ<br />

ተስፋፊዎችን በመመከት በቅኝ ገዥዎች ሥር ያልወደቀችና<br />

ለመላዉ ጥቁር ሕዝብ የነፃነት ተምሳሌት ሐገር ነች፡፡<br />

አብዛኛዎቹ አፍሪካዊ ሀገሮች ድንበሮቻቸውና ማንነታቸው<br />

በቅኝ ገዥዎች ፍላጎት እንዲወሰን ሲደረግ ሀገራችን<br />

ወራሪዎችን በመቋቋም የራሷን የድንበር ወሰንና ማንነት<br />

በራሷ መወሰን የቻለች ብቸኛዋ አፍሪካዊ ሀገር ናት፡፡<br />

ሀገራችን የበርካታ ገፀ ምድርና ከርሰ ምድር ኃብት፣ አስደናቂ<br />

የተፈጥሮ ውበትና የሰው ልጅ ቀደምት ስልጣኔ መገለጫ<br />

የሆኑ ቅርሶች ባለቤት፣ ሰፊ መሬትና የሰው ኃይል ያሏት<br />

ታላቅ ሐገር ናት፡፡ ሀገራችን የተለያዩ የአየር ፀባያት ባለቤት<br />

ስትሆን ለሰው ልጅ መኖሪያና ለአዝርዕት መብቀያ ተስማሚ<br />

ተፈጥሮ በሰፊው የተለገሳት ሀገር ናት፡፡ በርካታ በጥቅም<br />

ላይ የዋሉና ገና ያልተነኩ የተፈጥሮ ስጦታየፈሰሰባትም<br />

ምድር ናት፡፡<br />

ሆኖም የዚህ አኩሪ ታሪክ፤ ባህልና የተፈጥሮ ሃብት<br />

ባለቤት የሆነች ሃገራችን ዛሬ በቀሪው የዓለም ሕዝብ ፊት<br />

የምትታወቀው በርሃብተኝነት፣ በተመፅዋችነት፣ በስደትና<br />

በእርስ በእርስ ጦርነት ባለቤትነቷ ነው፡፡ የሰው ልጅ ዛሬ<br />

ከረደሰበት የአስተዳደርና የኢኮኖሚ እድገት ደረጃ እንዳንደርስ<br />

ያደረገን በሃገራችን ተንሰራፈተው በቆዩና አሁንም ባሉ<br />

የአስተዳደርና የፖለቲካ ሥርዓት ብልሹነቶች ምክንያት<br />

ነው ብለን እናምናለን፡፡ ዛሬ ኢትዮጵያ በፖለቲካ እድገት<br />

ብቻ ሳይሆን በኢኮኖሚና በማህበራዊ እድገትም የዓለም<br />

ሃገራት የመጨረሻዎቹ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡ ሕዝቧ የዘር፣<br />

የሃይማኖት፣ የቋንቋና የባህል ልዩነቶችን ተቀብሎ ለበርካታ<br />

ዘምናት ተቻችሎ የኖረ ቢሆንም ዛሬ እርስ በእርስ በጥርጣሬ<br />

እንዲተያይና አንድነቱ እንዲላላ እየተደረገ ነው፡፡ ሃገራችን<br />

በተቀበለቻቸውና ባፀደቀቻቸው ዓለም አቀፍ ህጎች እንዲሁም<br />

በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት እውቅና ያገኙ ሰብአዊና<br />

ዲሞክራሲያዊ መብቶች የሚያከብራቸውና የሚጠብቃቸው<br />

ባለቤት አጥተዋል፡፡ የኢኮኖሚ መርሃችንም በጥናትና<br />

በአስተማማኝ መሠረት ላይ ያልተጣለ በመሆኑ ካለንበት<br />

የድሕነት አዘቅት ሊያወጣን አልቻለም፡፡ ፍትኃዊ የንብረት<br />

ስርጭትና የሥራ እድል ባለመኖሩ በኢትዮጵያውያን መካከል<br />

ያለው የኑሮ ደረጃ እጅግ እየተራራቀ መጥቷል፡፡ ዜጎችም<br />

የዜግነት እኩልነት ክብራችን ተነፍገን አብዛኛዎቻችን<br />

በሃገራችን ጉዳይ ባይተዋር ሆነናል፡፡<br />

ዛሬ የዚህ ትውልድ አካል የሆንን ዜጎች ይህንን የተዛባ<br />

አካሄድ የመቀየርና ሃገራችንን የተሻለች ሃገር የማድረግ<br />

ኃላፊነት አለብን ብለን እናምናለን፡፡ በመሆኑም የሰማያዊ<br />

ፓርቲያችን ራዕይ፣ ተልዕኮና ዓላማ ለሃገራችን ካለን ጥልቅ<br />

ፍቅር፣ለፍትሃዊ አስተዳደር መስፈን ካለን ፅኑዕ እምነትና<br />

ከሰው ልጅ ምክንታዊ አስተሳሰብ ይመነጫሉ፡፡ ፍትሕ<br />

እንዲሰፍን የምንፈልግ ሃገራችንንም በእውነት የምንወድ<br />

ከሆነና በሰው ልጅ ምክንያታዊ አስተሳሰብ የምንገዛ ከሆነ<br />

ችግሮቻችን በሰላማዊ መንገድ፣ በመነጋገር፣ በመደማመጥና<br />

በመግባባት ብሔራዊ እርቅና መከባበርን በመፍጠር የሚፈቱ<br />

ናቸው ብለን እናምናለን፡፡<br />

ፓርቲያችን በሃገሪቱ ህገ-መንግስት መሠረት በሰላማዊ<br />

መንገድ የፖለቲካ ትግል በማድረግ የኢትዮጵያ ሕዝብ<br />

ከውስብስብና ፈርጀ ብዙ ችግሮች ተላቆ እያንዳንዱ ዜጋ<br />

በነፃነት ሃሳቡን የመግለፅ፣ የመደራጀት፣ የፈለገውን<br />

የመደገፍና የመቃወም፣ በፈለገው ሙያና የሥራ መስክ<br />

የመሰማራት፣ ሃብት የማፍራትና የሃብቱ ባለቤት የመሆን<br />

እንዲሁም የግል ስብዕናውን የማሳደግ መብቱ የተረጋገጠ<br />

እንዲሆን እንታገላለን፡፡ ሐገራችን ከድህነትና ከጦርነት<br />

የተላቀቀች፣ ፍትሕና ሰላም የሰፈነባት እንድትሆን የፖለቲካ<br />

ሥልጣን በመያዝ የዜግነት ድርሻችንን ለመወጣትና<br />

ራዕያችንን እውን ለማድረግ ሰማያዊ ፓርቲያችንን<br />

መስርተናል፡፡<br />

ሰማያዊ ፓርቲ ራዕዩን እውን ለማድረግ፤<br />

ሀ. ፓርቲያችን የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መርሆችን<br />

ይከተላል፡፡<br />

ለ. በሰማያዊ ፓርቲ ፕሮግራም ውስጥ ለተካተቱ<br />

አንዳንድ ጉዳዮች ተፈፃሚነት የሕገ-መንግሥቱ አንዳንድ<br />

ድንጋጌዎችን ህገ-መንግስቱ ባስቀመጠው የህገ-መንግስት<br />

ማሻሻያ መርሆች መሰረት ማሻሻል አስፈላጊ መሆኑን ታሳቢ<br />

ተደርጓል፡፡<br />

መ. ዓላም ዛሬ ከደረሰችበት የሥልጣኔ ደረጃና ከሰው<br />

ልጅ ምክንያታዊ አስተሳሰብ በመነሳት ከሰላማዊ ትግል<br />

ውጭ በሃገራችን የተረጋጋ የፖለቲካ ሥርዓትን መገንባት<br />

አይቻልም ብለን እናምናለን፡፡ ስለዚህ ፓርቲያችን በሰላማዊ<br />

የትግል ስልት የፖለቲካ ሥልጣን ለመያዝ ይታገላል፡፡<br />

የፖርቲው ስያሜና ትርጓሜ፤<br />

የፓርቲው ስያሜ “ሰማያዊ ፓርቲ” በአህፅዕሮት “ሰማያዊ”<br />

በእንግሊዝኛው አጠራር “BLUE PARTY” ሲሆን<br />

ትርጓሜውም ሰማያዊ ቀለም የሰላም፣ የተስፋና የአንድነት<br />

መገለጫ በመሆኑና ፓርቲያቸንም ሰላም ተስፋና አንድነት<br />

በሃገራችን እንዲሰፍን ያለውን የፀና እምነት መግለፅ ነው፡፡<br />

የፓርቲው ዓርማ፡-<br />

ከመሃል በጠባብ ክብ የሚጀምርና ሌሎች እየሰፉ<br />

የሚሄዱ ክቦቹ ሲኖሩት በደማቅ ሰማያዊና ውሃ ሰማያዊ<br />

ቀለሞች በመፈራረቅ የሚቀባ በጨርቅ ወይም በሌላ ቁስ<br />

ላይ የሚያርፍ ምልክት ይሆናል፡፡ የዓርማው ቀለማት<br />

የፓርቲያችንን ስያሜና ትርጉም የሚያሳዩ ሲሆን ከትንሽ<br />

ጀምሮ እየሰፉ የሚሄዱት ክብ ምልክቶች ደግሞ ጥቂት<br />

ሆነን ጀምረን እየበዛን እንደምንሄድ ለማሳየት ነው፡፡<br />

የፓርቲው ሀገራዊ ዕይታ<br />

ሀ. ኢትዮጵያ ሀገራችን በኢትዮጵያ ህዝብ ሙሉ<br />

ገዥነት ስር የሚገኘውን መሬት፣ ውሃ፣ የአየር ክልል፣<br />

በከርሰ ምድርና በከርሰ ውኃ የሚገኘው ሃብት፣ በአየር<br />

ክልሉ ያለው የድምፅና የምስል ሞገድ ባለቤት ሉዓላዊ ሀገር<br />

ናት፡፡<br />

ለ. የኢትዮጵያ ያልተመለሱ የድንበርና የይገባኛል<br />

ጥያቄዎች መኖራቸው እንደተጠበቀ ሆኖ የኢትዮጵያ<br />

ሉዓላዊ የአስተዳደር ወሰን አሁን በኢትዮጵያ መንግስት ሥር<br />

የሚገኘውና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የተመዘገበዉ<br />

ክልል ነው፡፡<br />

ሐ. በኢትዮጵያ ውስጥና በውጭ ሃገራት የሚኖሩ<br />

ኢትዮጵያውያን በአንድነት የኢትዮጵያ ሕዝብ ናቸው፡፡<br />

መ. የኢትዮጵያ ሕዝብም በኢትዮጵያ ጉዳይ ባለሙሉ<br />

የሥልጣን ባለቤት ነው፡፡ ሃገሪቱን የማስተዳደር ሥልጣን<br />

ከሕዝብ ይመነጫል፡፡<br />

ሠ. የኢትዮጵያ አንድነትም ሆነ ሉዓላዊነት<br />

አይነጣጠሉም፤ለሌላም አይለቀቁም፡፡<br />

ረ. ኢትዮጵያውያን በግል ያላቸው የዜግነት መብትም<br />

ሆነ በወል የሚጋሩት የህግ፣ የፖለቲካ የማህበራዊና<br />

የባህል መብት የአንድነታቸው ዓይነተኛ መሰረት ነው፡፡<br />

ሰ. ኢትዮጵያ ሀገራችን የረጅም ጊዜ አኩሪ ታሪክ፣<br />

የበርካታ ገፀ-ምድርና ከርሰ-ምድር ሃብት ባለቤት፣ አስደናቂ<br />

የተፈጥሮ ውበትና የሰው ልጅ ቀደምት ሥልጣኔ መገለጫ<br />

የሆኑ ቅርሶች ያሏት ታላቅ ሃገር ናት፡፡<br />

ሸ. ሃገራችን ኢትዮጵያ በተለያዩ ባህል፣ ሃይማኖት፣<br />

ቋንቋ፣ ወግና ሥርዓት አሸብርቃ የኖረች፣ በብዙ ዓይነት<br />

ሃረጎች ተሳስረውና በታሪክ ተቆራኝተው የጋራ አመለካከትና<br />

ኢትዮጵያዊ ማንነትን በማዳበር ለዘመናት ተቻችለውና<br />

ተከባብረው በአንድነት የኖሩ ዜጎች ሃገር ናት፡፡ እነዚህ<br />

ዜጎች በየዘመናቱ የተለያዩ አስተዳደራዊ በደልና ጭቆና<br />

ደርሶባቸዋል፡፡ ዛሬም ቢሆን የዜጎች የአስተዳደርና<br />

የፍትህ ጥያቄ በአግባቡ አልተፈታም ወይም መብታቸው<br />

አልተከበረም፡፡ በመሆኑም ሁሉም ዜጎች የዜግነት<br />

መብታቸው እንዲከበርና በሃገር ጉዳይ ላይ ተገቢው ድርሻና<br />

ተሳትፎ እንዲኖራቸው አሁንም ፅኑዕ ትግል የሚያስፈልጋት<br />

ሃገር ናት፡፡<br />

ራዕይ<br />

የዜጎች ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ሙሉ በሙሉ<br />

የተከበሩባት፤ ለሕዝብ ፍላጎት መሟላት በኃላፊነትና<br />

በተጠያቂነት መንፈስ የሚሰራ መልካም አስተዳደርና የህግ<br />

የበላይነት የተረጋገጠባት፤ የኢኮኖሚና ማሕበራዊ ብልፅግና<br />

የሰፈነባት፤ ለዜጎቿ ሁሉ አለኝታና መኩሪያ የሆነች፤ለዓለም<br />

ሕዝብ መልካም ግንኙነት የበኩሏን አስተዋፅዖ የምታደርግ<br />

ኢትዮጵያን ማየት ነው፡፡<br />

ዓላማ<br />

ሀ. የዜጎች ዲሞክራሲያዊና ሰብዓዊ መብቶች<br />

እንዲከበሩና ተፈፃሚም ኢንዲሆኑ በጽናት መቆም፡፡<br />

ለ. ለዜጎች አስተማማኝ የማሕበራዊ ደህንነት<br />

ዋስትና አገልግሎት ማቅረብ፡፡<br />

ሐ. የፖለቲካ ፓርቲዎችና ግለሰቦች ነፃ፣ ፍትሃዊና<br />

ትክክለኛ በሆነ መንገድ ተወዳድረው የፖለቲካ ሥልጣን<br />

የሚይዙበት የምርጫ ሥርዓት መመስረት፡፡<br />

መ. ራዕዩን ተግባራዊ ለማድረግ በነፃና ፍትኃዊ<br />

ምርጫ በህዝብ ድምፅ የፖለቲካ ሥልጣንመያዝ<br />

ሠ. ሀቀኛ፣ ብቃትና ተጠያቂነት ባለው አመራር<br />

አማካኝነት ታታሪና የፈጠራ ችሎታ ያላቸው ዜጎች<br />

መፍጠር፡፡<br />

ረ. የሕብረተሰቡን የፖለቲካ ግንዛቤ በማሳደግ ዜጎች<br />

በሃገራቸው ጉዳይ በንቃት እንዲሳተፉ፣ ግዴታቸውንና<br />

ኃላፊነታቸውንም እንዲወጡ ማድረግ፡፡<br />

ሰ. የእያንዳንዱን ዜጋ ችሎታ በማሳደግ በሃገርና<br />

በዓለም ደረጃ ብቁ ተወዳዳሪ ለመሆን ያለውን ምኞት<br />

ማሳካት፡፡<br />

ሸ. ከሀገራቸው ውጭ ያሉ ኢትዮጵያውያን ሰብዓዊና<br />

ቁሳዊ አቅማቸውን ለሃገራቸው ልማት እንዲያውሉና<br />

ለሕዝብም ቁሳዊና መንፈሳዊ ሕይወት መሻሻል የበኩላቸውን<br />

አስተዋፅዖ ማበርከት የሚችሉበት የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና<br />

የማሕበራዊ ሥርዓት መመስረት፡፡<br />

ቀ. ዓለምን ለመረዳትም ሆነ የዓለም ሕብረተሰብ<br />

በአግባቡ እንዲረዳው ማድረግ የሚችልና በነፃነት የሚያስብ<br />

ሕብረተሰብ መመስረት፡፡<br />

በ. የኢትዮጵያ ወጣት ትውልድ በራሱና በወረሰው<br />

መልካም ነገር እንዲኮራና በሕይወቱ ውስጥ ተስፋ<br />

እንዲኖረውና ለከፍተኛ ግብ እንዲሰራ ማደፋፈር፡፡<br />

ተልዕኮ<br />

ተልዕኮአችን ዓላማችንን ማሳካት ሆኖ በተለይ በሀገራችን<br />

ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲሰፍንና የሕግ የበላይነት<br />

እንዲረጋገጥ ዋስትና የሚሰጥ ከሕዝብ፣ በሕዝብ፣ ለሕዝብ<br />

የቆመ መንግስት በሰላማዊ መንገድ መመስረት ነው፡፡<br />

ርዕዮተ ዓለም<br />

እጅግ ውድ የሆነው የሰው ልጅ ሃብት ነፃነቱ በመሆኑ<br />

ሰማያዊ ፓርቲ ለግለሰብ ነፃነት ቅድሚያ ይሰጣል፡፡ ዜጎች<br />

በቡድን ሊያከናዉኗቸው የሚፈልጓቸው እንደ ሃይማኖት፣<br />

ልማዶች፣ ቋንቋ፣ ማህበሮች እና የመሳሰሉት የጋራ<br />

መብቶች የግለሰብን በነፃነት የመወሰን መብት ሳይሸረሽሩ<br />

እንዲከበሩ የህግ ጥበቃ እንደሚያስፈልጋቸው ያምናል፡፡<br />

በመሆኑም ሰማያዊ ፓርቲ በለዘብተኛ ሊብራል ዲሞክራሲ<br />

መሰረታዊ መርሆች ይመራል፡፡<br />

ትኩረት<br />

ሰማያዊ ፓርቲ በኢትዮጵያ ውስጥ 51% ያህል ቁጥር<br />

ያላቸውን ሴቶች ወደ ፖለቲካው መድረክ እንዲመጡ<br />

ቅድሚያ በመስጠት ይሠራል፡፡ በተጨማሪም እድሜው ከ35<br />

ዓመት በታች የሆነውና 70% የሚሆነውን የኢትዮጵያን<br />

ህዝብ ቁጥር የያዘው ወጣቱ ትውልድ የኢትዮጵያን ፖለቲካ<br />

ወደፊት ለማራመድ ከፍተኛ አሰተዋፅኦ አለው ብሎ<br />

ፓርቲያችን ያምናል፡፡ ከፍተኛ ተኩረትም ለወጣቱ ትውልድ<br />

ይሰጣል፡፡ ይህንንም በተግባር ለማሣየት የፓርቲው<br />

አብዛኛው አማራሮች የዚህ ትውልድ አካል ናቸው ፡፡<br />

ዋና ዋና እንቅስቃሴዎች<br />

1. ሰማያዊ ፓርቲ በምርጫ ቦርድ የተነፈገውን<br />

የምስክር ወረቀት በህግና በትግሉ ከቦርዱ ወረቀት በፊት<br />

ራሱን ህጋዊ አካል አድርጓል<br />

2. ፓርቲው ራሱን ከህዝብና ከደጋፊዎቹ<br />

ለማስተዋወቅ በርካታ የውይይት መርሃ ግብሮችን አካሂዷል፡<br />

፡<br />

3. ለፓርቲው ድጋፍ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ያዘጋጀው<br />

የራት ግብዣ ፕሮግራም በመንግስት ካድሬዎች ጫና<br />

ተስተጓጉሏል፡፡<br />

4. “ውይይትና መነጋገርን እንለማመድ” በሚል<br />

ርዕስ “መክሸፍ እንደ ኢትዮጵያ ታሪክ” በተሰኘው የፕ/ሮ<br />

መስፍን ወልደማርም መፅሀፍ ላይ ውይይት እንዲደረግ<br />

በብሔራዊ ቲአትር ባዘጋጀው ዝግጅት ከሁለት ሺህ በላይ<br />

ተገኝቶ እንዲወያይ እድል ፈጥሯል፡፡<br />

5. ለፋሽስቱ ግራዚኒ ሐውልትና የመታሰቢያ<br />

መናፈሻ ቦታ እንዲሰራለት መደረጉን በመቃወም ሰላማዊ<br />

ሰልፍ በማድረጉ አባላቱን አመራሮቹ ወደ አስር ቤት<br />

እንዲወረወሩ ተደርገዋል፡፡<br />

6. በሚናገሩት ቋንቋ መለየት ምክንያት በቤኔሻንጉል<br />

ለዘመናት ከኖሩበት የተፈናቀሉ ወገኖቻችንን እቦታቸው<br />

ድረስ በመሔድ ጎብኝቷል፤ አወያይቷል፡፡<br />

7. በሐገራችን የሰፈነውን አምባገነንት፣ የሰብዓዊና<br />

ዲሞክራሲያዊ መብት ጥሰት፣ የዜጎችን መፈናቀልና<br />

የመንግስትን በሐይማኖት ጣልቃ መግባት በመቃወም<br />

ለስምንት አመታት የተነፈገውን የሰላማዊ ሰልፍ መብት<br />

በመመለስ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ አድርጓል፡፡<br />

ለበለጠ መረጃ የፓርቲያችንን ድ-ገፅ www.Semayawiparty.org<br />

ይጎብኙ፡፡ ወይም Facebook BlueParty<strong>Ethiopia</strong><br />

ላይክ ፔጅ semayawiparty ይከታተሉ፡፡<br />

አድራሻ፡- ሰማያዊ ፓርቲ<br />

ቁጥር፡ C/A619<br />

ፖ.ሳ. ቁ 180298<br />

አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ<br />

ስልክ +251116514240<br />

አቢሲኒያ ባንክ ተንቀሳቃሽ ሂሳብ


15የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2<br />

ነገረ-ኢትዮጵያ<br />

እንደሀገር መግባባት ...<br />

ከ ገፅ 11 የዞረ<br />

የጸጥታ ሀይሉ ከህዝብ ተነጥሎ የኢህአዴግ<br />

የግል ንብረት እስኪመስል ድረስ ተለያይቷል፡<br />

፡<br />

ሌላው ደግሞ የፍትህ ተቋማት የምንላቸው<br />

ድርጅቶቻችን ናቸው፡፡ አብዛኛውን ጊዜ<br />

በሀገራችን የታዩ የፍርድ ሂደቶች የተመሩት<br />

በነጻ የዳኝነት ሂደት ሳይሆን በአለቃዎቻቸው<br />

በጎ ፈቃድ መሆኑ ጸሐይ የሞቀው ሀቅ ነው፡<br />

፡ ይህን መከራከሪያችን የሚያጠናክርልን<br />

የ1997 የቅንጅት አመራሮችና አባላት ላይ<br />

የተበየነው የእስር ፍርድ ነው፡፡ ጠቅላይ<br />

ሚንስትር መለስ ዜናዊ በፓርላማ ቀርበው<br />

እስከሞት ፍርድ ሊያስቀጣ የሚችል ወንጀል<br />

አግኝተንባቸዋል ብለው ተናግረው ነበር፡<br />

፡ ይህንን ተከትሎ ፍርድ ቤት መመላለሱ<br />

የሰለቻት ዳኛ ብርቱካን ሚዴቅሳ እንዲህ ስትል<br />

ተናግራ ነበር፡፡ “ለምን ታመላልሱናላችሁ፤<br />

መለስ ዜናዊ የሞት ፍርድ ፈርዶብን አይደል<br />

እንዴ!? ወስዳችሁ ግደሉን እንጂ፡፡” በቅርብ<br />

እነ እስክንድር ነጋን ጨምሮ በአንዱዓለም<br />

አራጌ፣ በሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ<br />

ኮሚቴወች ላይ የተወሰደው የጥፋተኝነት<br />

ውሳኔም ከቀድሞው የተለየ አይደለም፡<br />

፡ በዚህም ምክንያት በሀገራችን የፍትህ<br />

ተቋማት ላይ መግባባት ሆድና ጀርባ ሆኗል፡፡<br />

ማሳያ ሰባት፡- ዘውግ ተኮር ፌደራሊዝም<br />

የህገ መንግስቱ አንቀጽ 39 እንዲህ ይላል፤<br />

‹‹የራስን እድል በራስ መወሰን እስከ<br />

መገንጠል››፡፡ በዚህ አንቀጽ መሰረት ክልሎች<br />

እራሳቸውን በራሳቸው ያስተዳድራሉ፤<br />

ከፈለጉም መገንጠል መብታቸው ነው፡<br />

፡ በግሌ ‹እስከ መገንጠል› ብሎ መብት<br />

ምን እንደሆነ ባይገባኝም የፌደራል ስርዓት<br />

መኖሩን ግን አጥብቄ እፈልገዋለሁ፡፡ ‹እስከ<br />

መገንጠል› የሚለው ሀረግ መግባቱ ግን<br />

ላለመግባባታችን አንዱ ማሳያ ነው፡፡<br />

ማሳያ ስምንት፡- ምርጫና የምርጫ ቦርድ<br />

ለአንድ ሀገር በዴሞክራሲ መበልጸግ<br />

የምርጫ ቦርድ ገለልተኛነት ወሳኝ ሚና<br />

አለው፡፡ የምርጫ ቦርድ ሃላፊነቱን በአግባቡ<br />

ከተወጣ አጭበርባሪዎችና ኮረጆ ገልባጮች<br />

ቦታ የላቸውም፡፡ ይህን አሰራር በሀገራችን<br />

ለማስፈን ጅምሩ እንኳን የለም ለማለት<br />

ያስደፍራል፡፡ የምርጫ ቦርድ አመራሮችም<br />

ሹመታቸው በቀጥታ ከመንግስት መሆኑ<br />

ለገዥው ተባባሪነታቸው መንገድ ከፋች ነው፡<br />

፡ ምርጫ ቦርድ የገዥውን ፓርቲ የሙቀት<br />

ልክ እየለካ የሚሰራ መሆኑ የታየ እውነት<br />

ነው፡፡ በዚህ የተባባሪነት አመሉ ገዥው<br />

ኮረጆ ሲገለብጥ ምርጫ ቦርድ የምርጫ<br />

ውጤት ተቀበሉ በሚል ተቃዋሚዎችን<br />

ያባብላል፤ ካልተሳካት ደግሞ ያስፈራራል፡፡<br />

ስለሆነም ምርጫ ቦርድ ሌላኛው እንደ ሀገር<br />

ያለመግባባታችን ምክንያት ሆኖ ሊጠቀስ<br />

ይችላል፡፡<br />

በአጠቃላይ ሀገሬ ኢትዮጵያ የዚህ ክፍለ<br />

ዘመን ዳግማዊ ባቢሎን እየሆነች ነው፡<br />

፡ ይህን በቋፍ ላይ ያለ አለመግባባት በጊዜ<br />

ካልፈታን እጣ ፋንታችን እንደ ባቢሎን ህንጻ<br />

መፈራረስ ከመሆን አያልፍም፡፡ አምላክ<br />

አያድርገው እላለሁ!<br />

እውነትና ህዝብ ያሸንፋል! ኢትዮጵያ<br />

ለዘላለም በክብር ትኑር!!!<br />

ኢህአዴግ ተሸንፏል...<br />

ከ ገፅ 16 የዞረ<br />

እንደተለመደው ወዲያውኑ ኢንተርኔትና<br />

ስልክ እንዲጠፋ ተደረገ፡፡<br />

አሁን ሰላማዊ ሰልፉ እየተቃረበ እንደመሆኑ<br />

የከተማውን አስተዳደር ይበልጡን ፈርቷል፡<br />

፡ ሰልፉ እንደማይቀር ከሰማያዊ ወጣቶች<br />

ድፍረትና ቆራጥነት ተረድተዋል፡፡<br />

በመሆኑም የከተማውን ነዋሪ በመሰብሰብ<br />

ማስፈራራት ነበረባቸው፡፡ ለዚህም ሰማያዊ<br />

ፓርቲን ስም እየለጠፉ ህዝቡን ለማራቅ<br />

ከመሞከር ባለፈ ‹‹ልጆቻችን ሰላማዊ ሰልፉ<br />

ላይ ቢሳተፉ በጥይት ይመታሉ!›› ብለው<br />

እስከማስፈራራት ደርሰዋል፡፡ የተሸናፊዎቹ<br />

አቅም ይህ ነው፡፡ ሰላማዊ ሰልፉ ሊደረግ<br />

10 ደቂቃ ሲቀረው ደግሞ በየ መግቢያው<br />

የተደረደሩት ፖሊሶች ህዝብን ወደ መስቀል<br />

አደባባይ እንዳይሄድ ሲያግዱ ተስተውለዋል፡<br />

፡ በሰላማዊ ሰልፉ ወቅትም የቀበሌ ካድሬዎች<br />

ከሰልፉ በኋላ በመሆን ህዝቡን በመቅረጽ<br />

ለማስፈራራት ሞክረዋል፡፡ በእርግጥ ከዚህ<br />

አልፈው ሰላማዊ ሰልፉ ከተጠናቀቀ በኋላ<br />

እርምጃ እየወሰዱ መሆናቸውም ተሰምቷል፡<br />

፡ ሰላማዊ ሰልፉ ካበቃ በኋላ በቅርብ<br />

እርቀት ሲከታተሉ የነበሩት ካድሬዎች<br />

በሰልፉ ላይ የተሳተፉትን ወጣቶች የቀበሌ<br />

መታወቂያ ቀምተዋል፡፡ ወደ ቀበሌ ሄደው<br />

መታወቂያቸውን በተቀበሉበት ወቅትም<br />

ዳግመኛ ሰማያዊም ሆነ ሌሎች ፓርቲዎች<br />

በሚጠሩት ሰልፍ እንዳይሳተፉ ማስጠንቀቂያ<br />

ተሰጥቷቸዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ሰልፉን<br />

ያስተባበሩት የጎንደር የፓርቲው አባላትና<br />

ቤተሰቦቻቸው ላይ ደህንነቶች እየደወሉ<br />

ሲያስፈራሩዋቸው ሰንብተዋል፡፡<br />

ሰላማዊ ሰልፉ ተደርጎም ቢሆን ማዋከቡ እንደማይቆም ቀድመው የተገነዘቡት የፓርቲው<br />

አመራሮች ጎንደርን ቶሎ መልቀቅን እንዳለባቸው አምነዋል፡፡ እናም ሰላማዊ ሰልፉ<br />

ከተጠናቀቀ ከሁለት ሰዓት በኋላ ጉዞ ወደ አዲስ አበባ ተጀመረ፡፡ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች<br />

መሬቱን ለማስመለስ የተደረገውን ግፊት ቢያደንቁም ሰማያዊ በመመለሱ ከመጠን በላይ<br />

የሚቆራረጠው የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎት ጋብ እንደሚል በግልጽ ይናገሩ ነበር፡<br />

፡ ሰላማዊ ሰልፉ በሰላም መካሄዱ ያናደደው የሚመስለው ገዥው ፓርቲ ግን ከጎንደርም<br />

ውጭም እየተከተለ መተንኮሱን አላቆመም፡፡ አዲስ አበባ ለመድረስ ጥቂት ኪሎ ሜትሮች<br />

ሲቀሩንም ቢሆን ‹‹ከበላይ አካል›› ትዕዛዝ የተላለፈላቸው የሚመስሉት የትራፊክ<br />

ፖሊሶች ደብረ ጽጌ ላይ በመሳሪያ አስቆሙን፣ አስጸያፊ ስድብምና ማስፈራራትም<br />

ተጨመረበት፡፡<br />

ሆኖም በሰልፉ የተገኙት ወጣቶችም ይህን<br />

የአካባቢው ቅርንጫፍ በደረሰባቸው ወከባ<br />

አለመደናገጣቸውን ደውለው ነግረውኛል፡፡<br />

ለሰላማዊ ሰልፉ በሄድንበት ወቅት ጎንደር<br />

ውስጥ ካገኘኋቸው የኢህአዴግ አባላት<br />

መካከል አብዛኛዎቹ መሬቱ ለባዕድ ተላልፎ<br />

መሰጠቱን ከመቃወም አልፈው በጉዳዩ<br />

ከተቃዋሚዎች ጋር አብረው ለመስራት<br />

ፍላጎት እንዳላቸው ተረድቻለሁ፡፡ ደብድቡ<br />

ተብለው የተላኩት ፖሊሶችና የከተማው<br />

አስተዳደርም እንደ ፌደራል መንግስቱ<br />

ግትር አቋም አለመውሰዱ የሽንፈቱ አንድ<br />

አካል ነው ማለት ይቻላል፡፡<br />

ወደ አዲስ አበባ<br />

ጉዞ<br />

ሰላማዊ ሰልፉ ተደርጎም ቢሆን ማዋከቡ<br />

እንደማይቆም ቀድመው የተገነዘቡት<br />

የፓርቲው አመራሮች ጎንደርን ቶሎ<br />

መልቀቅን እንዳለባቸው አምነዋል፡፡ እናም<br />

ሰላማዊ ሰልፉ ከተጠናቀቀ ከሁለት ሰዓት<br />

በኋላ ጉዞ ወደ አዲስ አበባ ተጀመረ፡<br />

፡ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች መሬቱን<br />

ለማስመለስ የተደረገውን ግፊት ቢያደንቁም<br />

ሰማያዊ በመመለሱ ከመጠን በላይ<br />

የሚቆራረጠው የስልክና የኢንተርኔት<br />

አገልግሎት ጋብ እንደሚል በግልጽ ይናገሩ<br />

ነበር፡፡ ሰላማዊ ሰልፉ በሰላም መካሄዱ<br />

ያናደደው የሚመስለው ገዥው ፓርቲ ግን<br />

ከጎንደርም ውጭም እየተከተለ መተንኮሱን<br />

አላቆመም፡፡ አዲስ አበባ ለመድረስ ጥቂት<br />

ኪሎ ሜትሮች ሲቀሩንም ቢሆን ‹‹ከበላይ<br />

አካል›› ትዕዛዝ የተላለፈላቸው የሚመስሉት<br />

የትራፊክ ፖሊሶች ደብረ ጽጌ ላይ<br />

በመሳሪያ አስቆሙን፣ አስጸያፊ ስድብምና<br />

ማስፈራራትም ተጨመረበት፡፡<br />

ይህ ሁሉ ወከባ ግን ልዑካኑን አላስደነገጠም፡<br />

፡ ወደ ጎንደር ጉዞ ከጀመሩበት ወቅት አንስቶ<br />

ወጣቶቹ በድፍረት ከተሸናፊው መንግስት<br />

ጋር ፊት ለፊት ተጋፍጠዋል፡፡ ደብረ ጽጌ<br />

ላይም ያደረጉት ተመሳሳይ ነው፡፡ ትራፊክ<br />

ፖሊሶች መኪናውን ወደ ጣቢያ እንዲወስድ<br />

ሲወተውቱት የሰነበተውና ከልዑካኑ ጋር<br />

ሁለቱንም ቀን የታሰረው ሾፌር ደብረ ጽጌ<br />

ላይም ልክ እንደ ሰማያዊ ወጣቶች መብቱን<br />

አሳልፎ ላለመስጠት ያለውን ቁርጠኝነት<br />

አሳየ፡፡ የልዑካኑ አባላት መሳሪያ አውጥቶ<br />

‹‹እበትንሃለሁ!›› ላለው ፖሊስ ደረታቸውን<br />

ሰጡ፤ አጸያፊ ስድብ የተሳደበውን<br />

አፋጠጡት! አሁን ልዑካኑን ለማስቆም<br />

የጣሩት ፖሊሶች እንደገና መደናገጥ<br />

ጀምረዋል፡፡ የከተማው ህዝብ ወጣቶቹና<br />

የትራፊክ ፖሊስ የሚያደርጉትን ክርክር<br />

እየተመለከተ ተስብስቧል፡፡<br />

የሰማያዊ ወጣቶች ዋናው ሰላማዊ ሰልፍ<br />

ከመደረጉ በፊት መስቀል አደባባይና አዘዞ<br />

ላይ ፖሊስ ሲያስቆማቸው ሲይዛቸው<br />

በመዘመር፣ ህጉን በማስረዳት ህዝብን<br />

ሰብስበዋል፡፡ በጽናታቸውና በድፍረታቸው<br />

ፖሊሶቹን ሳይቀር አስገርመዋል፡፡ ደብረ<br />

ጽጌ ላይ በመሳሪያ ለማስቆም ሲጥርም<br />

ሌላ ሰላማዊ ሰልፍ አድርገዋል፣ ህዝብን<br />

ሰብስበው ስለመብቱ አስተምረዋል፡<br />

፡ ከፖሊስ ጋር እየተከራከሩ፣ ህዝብን<br />

ሰብስበው እያስተማሩም ለቀሪው ህዝብ<br />

በስልክና በማህበራዊ ድህረ ገጾች ትዕይንቱን<br />

ማካፈላቸውን ቀጥለዋል፡፡ በተለይ በፌስ<br />

ቡክ ዜናው በስፋት መዳረስ ጀምሯል፡፡<br />

ይህን ሁሉ ያልጠበቁት ትራፊክ ፖሊሶችን<br />

የላኩት የበላይ አካላትም ይሁኑ የከተማው<br />

ካድሬዎች ወጣቶቹን ለመልቀቅ ተገድደዋል፡<br />

፡ ለኢህአዴግ ሌላ ሽንፈት! ለሰማያዊ<br />

ወጣቶች ሌላ ድል! ከድል በኋላም የድል<br />

መዝሙር!<br />

ተከብረሽ የኖርሽው በአባቶቻችን ደም፣<br />

በአባቶቻችን ደም፣<br />

እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውደም<br />

ያስደፈረሽ ይውደም፣<br />

……….<br />

‹‹የትግል ጉዞ ታሪካዊ፣<br />

ዓላማው ፍጹም ህዝባዊ፣<br />

ራዕያችንም ኢትዮጵያዊ…››<br />

መሬት ያስቆረሱት...<br />

ከ ገፅ 7 የዞረ<br />

የሚያስረዱ መረጃዎች ሊሆኑ አይችሉምን?<br />

ድብቅነት በኢትዮጵያ በመግዛት ላይ ላለው<br />

ገዥው አካል ዋና መለያ ባህሪው ነው፡፡ ነገሮችን<br />

ደብቆ በመያዝ እያንዳንዱን በማሞኘት ላይ<br />

ይገኛሉ፡፡ አቶ መለስ በህይወት በነበሩበት ጊዜ<br />

እና በአሁኑ ጊዜ ያሉት ሎሌዎቻቸው ደግሞ<br />

የቅብብሎሽ ዱላውን ከጌታቸው ራዕይ በመቀበል<br />

በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እያሳዩ ያሉት ንቀት<br />

የህዝቡን ምንነት ሳይገመግሙ እና ሳይረዱ<br />

በራቁት ገላው ላይ ሱፍ እየጎተቱ መሆኑን<br />

በውል ሊያጤኑት ይገባል፡፡ አቶ መለስ እና<br />

ጋሻጃግሬዎቻቸው አሰብን እና ባድመን በቤሣ<br />

ቁርጥራጮች ካስረከቡ በኋላ ዝምታ ብቻ<br />

መልስ ስላገኙ ከዚያ ነገር አንድ ቁም ነገር<br />

ተምረዋል፡፡ ይኸውም ኢትዮጵያውያንን እና<br />

የኢትዮጵያን ግዛት የእነርሱ የግል እንደፈለጉ<br />

የሚለውጧት፣ የሚሸጧት የህግ ተጠያቂነት<br />

የሌለበት የግል ንብረታቸው መሆኗን አረጋገጡ፡<br />

፡በመለስ/ኃይለማርያም ከምዕራብ ኢትዮጵያ<br />

የግዛት አንድነት መሬት በመቁረስ ለሱዳን<br />

ለመስጠት የሚደረግ ማንኛውም “ስምምነት”<br />

ህገመንግስታዊ አይደለም፡፡ እ.ኤ.አ. ወደ 2008<br />

መለስ ብለን ስናይ አቶ መለስ የኢትዮጵያን<br />

መሬት ቆርሰው ለሱዳን ወይም ደግሞ ለማንም<br />

ቢሆን ለመስጠት ህጋዊ ስልጣን የላቸውም ብዬ<br />

ተከራክሬ ነበር፡፡<br />

ዛሬም ቢሆን አቶ ኃይለማርያም የኢትዮጵያን<br />

መሬት ቆርሰው ለሱዳን የመስጠት ህጋዊ<br />

መብትም ሆነ ስልጣን የላቸውም፡፡ ይህንን ካልኩ<br />

ዘንድ አቶ መለስ “ከአማራ ክልል ግዙፍ የሆነ<br />

መሬት” ቆርሰው ለሱዳን ለመስጠት “ስምምነት”<br />

እንደተፈራረሙ አጠያያቂ ነገር አይደለም፡<br />

፡ አቶ ኃይለማርያም እና ጌቶቻቸው ይህን<br />

ህገወጥ የመሬት ዕደላ ዕኩይ ተግባራቸውን<br />

“የስልታዊ/ስትራቴጂክ ስምምነት ማዕቀፍ”<br />

በማለት የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ በመክፈት ጣፋጭ<br />

በማስመሰል በማር የተለወሰ መርዛቸውን<br />

ሊግቱን ይፈልጋሉ፡፡ እውነታው ግን በአሁኑ<br />

ጊዜ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ያለው ገዥ አካል<br />

ምንም ዓይነት የኢትዮጵያን መሬት ለሱዳንም<br />

ሆነ ለማንም ሌላ አገር አሳልፎ የመስጠት ህገ<br />

መንግስታዊም ሆነ ዓለም አቀፋዊ መብትም<br />

ስልጣንም የለዉም፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ<br />

ሊታይ የሚችለው ይህ የተካሄደው የድብቅ<br />

ስምምነት የኢትዮጵያን ህገ መንግስት አንቀጽ<br />

12 የሚጻረር ስለሆነ የህገ መንግስት ጥያቄን<br />

ያስነሳል፡፡ አቶ መለስ በህይወት በነበሩበት ጊዜ<br />

እና እርሳቸውን ተክተው በመስራት ላይ ያሉት<br />

የአሁኖቹ ገዥዎቻችን ከኢትዮጵያ ህዝብ እና<br />

ከተወካዮች ምክር ቤት በሸፍጥ ደብቀው ከኦማር<br />

አልባሽር ጋር ያደረጉትን የሚስጥር “ስምምነት”<br />

እየተባለ የሚጠራውን ተግባራዊ ለማድረግ<br />

ይፍጨረጨራሉ፡፡ በኢትዮጵያ ህገ መንግስት<br />

አንቀጽ 12 ስር (“የመንግስት የስራ ድርሻ<br />

እና ተጠያቂነት“) እንዲህ ይላል፣ “መንግስት<br />

ተጣያቂነት እና ለህዝብ ግልጽነት ባለበት ሁኔታ<br />

ስራውን ይሰራል… ማንም የህዝብ ባለስልጣን<br />

ወይም ተመራጭ በህግ የተሰጠውን ስልጣን<br />

በህግ አግባብ ካልተጠቀመ ተጠያቂ ይሆናል፡<br />

፡” አቶ መለስ እና ተኪዎቻቸው “የህዝብ<br />

ባለስልጣን” እንደመሆናቸው መጠን ግልጽነት<br />

እና ተጠያቂነት ባለበት ሁኔታ ስራቸውን<br />

ለማከናወን ህገ መንግስታዊ ግዴታ አለባቸው፡<br />

፡ ለህዝብ ሳይቀርብ እና የስምምነቱ ሁኔታም<br />

በዝርዝር ምን እንደሆነ ሳይታወቅ እንዲሁም<br />

ህጋዊ ስልጣን የተሰጠው የተወካዮች ምክር<br />

ቤት ሳያጸድቀው የአገርን የግዛት አንድነት<br />

በመጣስ መሬት ቆርሶ ለሌላ አገር ለመስጠት<br />

በእራስ ፈቃድ የሚደረግ የሚስጥር ስምምነት<br />

የህገመንግስቱን አንቀጽ 12 ይጻረራል፣ ሙሉ<br />

በሙሉም ህገ መንግስቱን ይደፈጥጣል፡፡<br />

ኢትዮጵያ ለዘላለም በክብር ትኑር!<br />

(ሳምንት ይቀጥላል…)


ነገረ-ኢትዮጵያ<br />

ቅፅ 1 ቁጥር 2<br />

የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም.<br />

16<br />

ኢህአዴግ ተሸንፏል!<br />

(የጉዞ ማስታወሻ)<br />

ጌታቸው ሺፈራው<br />

ዛሬ የማወራው በምርጫ ስለመሸነፍ<br />

አይደለም፡፡ በምርጫ መሸነፍማ ወግ<br />

ነው፡፡ በተለይ ምርጫን ፍትሃዊና<br />

ዋነኛው የስልጣን ምንጭ አድርጎ<br />

ሽንፈቱን በጸጋ ለተቀበለ ‹‹ሽንፈቱ››<br />

አሸናፊነት በሆነ ነበር፡፡ ኢህአዴግ<br />

ይህኛውን ወግ አላገኘውም፡<br />

፡ እንዲያውም አስከፊው ሽንፈት<br />

ሳያውቁት፣ በግድ መሸነፍ ሳይሆን<br />

አይቀርም፡፡ አዎ ኢህአዴግ ይህን<br />

ሽንፈት ተከናንቦታል፡፡ ኢህአዴግ<br />

ይህንን ሽንፈቱን ለመሸፈን ለ23<br />

አመታት በግድ መግዛትን መርጧል፡፡<br />

ከ1997 በኋላ ተቃዋሚዎች<br />

ቢዳከሙም፣ ህዝብ በፖለቲካው ተስፋ<br />

ቆርጦ ‹‹ዝም ብሎ ለመገዛት›› የቆረጠ<br />

ቢመስልም ኢህአዴግ ግን ሽንፈቱን<br />

ይደብቅልኛል ያለውን ወከባና ጥርነፋ<br />

አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ ባለፉት ጥቂት<br />

ወራት ደግሞ በፖለቲካው መስክ<br />

መነቃቃቶች እየታዩ ነው፡፡ ይህኛው<br />

‹‹ዝም›› ያለው ህዝብ ኢህአዴግን<br />

እንደማይፈልግ፣ ኢህአዴግ ምንም<br />

ያህል የመጨቆንና የማታለል አቅም<br />

ቢኖረውም የህዝብን ልብ መግዛት<br />

አለመቻሉንና መሸነፉን የሚያሳይ<br />

ነው፡፡ ኢህአዴግ ለመሸነፉ እጅግ<br />

በርካታ ማሳያዎችን ማንሳት ይቻላል፡<br />

፡ አሁን ግን ለሱዳን አሳልፎ ከሰጠው<br />

መሬት ጋር በተያያዘ ያለው ጉዳይ<br />

ላይ ብቻ ማተኮር ወደድኩ!<br />

ፓርቲ የጎንደር ጉዞ<br />

የሰማያዊ<br />

ሰማያዊ ፓርቲ ወደ ጎንደር ከማቅናቱ<br />

በፊት በጽ/ቤቱ በድንበሩ ጉዳይ ጥናት<br />

ካደረጉት መካከል ብቸኛው የሆኑትን<br />

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያምን<br />

በመጋበዝ ህዝብን አወያይቶ ነበር፡፡<br />

በዚህ ውይይት ወቅት ፕሮፌሰሩን<br />

ጨምሮ ተሰብሳቢዎቹ ‹‹ኢህአዴግ<br />

አገር ሻጭ›› መሆኑን ተናግረዋል፡<br />

፡ ሁሉም እንደ መንግስት ሳይሆን<br />

የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት አሳልፎ<br />

ለመስጠት የተነሳ አንዳች ባዕድ<br />

ሀይል እንደሆነ ተግባብቶበታል፡፡<br />

የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች<br />

ደግሞ ይህን የፕሮፌሰር መስፍንና<br />

የሌሎችን ጥናት እንዲሁም<br />

መረጃዎች በግብዓትነት ወስደው<br />

ሉዓላዊነታቸውን ለማስከበር ወደ<br />

ጎንደር ለማቅናት በዝግጅት ላይ<br />

ነበሩ፡፡<br />

ሰማያዊ ወደ ጎንደር ሲያቀናም<br />

ኢህአዴግ መሸነፉን በጉልህ<br />

ተመልክቻለሁ፡፡ አድርባይ ደህንነትና<br />

ፖሊስ የማይፈሩት ወጣቶች<br />

ወደሚታሰሩበት፣ ወደሚደበደቡበትና<br />

መስዕዋትነት ወደሚያስከፍል ተልዕኮ<br />

ሳይሆን ለሰርግ አሊያም ለሌላ<br />

ቅንጦች የሚጓዙ ያህል ደስተኞች<br />

ነበሩ፡፡ ሰላማዊ ሰልፍ በሚወገዝበት<br />

ስርዓት አብዛኛዎቹ ወጣቶች ‹‹እኔ<br />

አልቀርም!›› በማለት የፓርቲውን<br />

አመራሮች ሲለምኑ፣ በመቅረታቸው<br />

ቅር መሰኘታቸው ስርዓቱ<br />

ሊያስገባቸው ከሚፈልገው የፍርሃት<br />

አዙሪት ሰብረው መውጣታቸውን<br />

የሚያሳይ ነው፡፡<br />

ወከባ<br />

የተሸናፊው<br />

የተሸነፈ የሚወስደው እርምጃ<br />

ግብታዊ ነው፡፡ ተረጋግቶ መፍትሄ<br />

ከመስጠት ይልቅ ማዋከብ፣ መደናበር<br />

ልዩ ባህሪው ነው፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ<br />

ልዑካን ወደ ጎንደር አቅንተው<br />

እንደገና አዲስ አበባ እስኪመለሱ<br />

ያጋጠማቸውም ይህ የተሸናፊዎች<br />

እርምጃ ነው፡፡ ወከባው የጀመረው<br />

የጎጃሟ ሉማሜ ከተማ ላይ ነው፡<br />

፡ ከአዲስ አበባ ጀምሮ በርካታ<br />

የትራፊክ ፖሊሶች እየገላመጡ<br />

ቢያሳልፉንም ከላይ አንዳች<br />

ትዕዛዝ የተሰጣት የምትመስለዋ<br />

የሉማሜዋ የትራፊክ ፖሊስ ግን<br />

በቀላሉ የምታሳልፈን አልነበረችም፡<br />

፡ መውጫው የምትቆዩበትን ቀን<br />

በግልጽ አላስቀመጠም በሚል ሰንካላ<br />

ምክንያት መኪናችን አስቆመች፡<br />

፡ ካልተቀጣችሁ አትሄዱም በማለቷ<br />

ላለመዘግየት ‹‹ቅጣታችን›› ቶሎ<br />

መክፈልን ወሰንን፡፡ ምን አልባትም<br />

ከ‹‹በላይ አካል›› ትዕዛዙ የመጣላት<br />

የምትመስለው የትራፊክ ፖሊስ<br />

ውሳኔ ግን ቢሮ ውስጥ የነበረውን<br />

አለቃዋንም ያስገረመ ነበር፡፡<br />

ለመክፈል ወደ አለቃዋ ቢሮ ያቀኑት<br />

የልዑካኑ አባላት እንዳረጋገጡልን<br />

የትራፊክ ፖሊሷ ያቀረበችው ሰንካላ<br />

ምክንያት ለማስቀጣት ይቅርና<br />

ለተግሳጽ የሚያበቃ አልነበረም፡፡<br />

መስዋትነት ወደሚያስከፍል<br />

ተልዕኮ ሳይሆን ወደ አንዳች ደስታ<br />

ቦታ የሚያቀኑ የሚመስሉት<br />

የልዑካኑ አባላት መንገዱን በሙሉ<br />

የአገራቸውንና የፓርቲያቸውን<br />

መዝሙር በመዘመር፣ እንዲሁም<br />

በመቀላለድና በመሳሳቅ ጉዟቸውን<br />

ቀጥለዋል፡፡ ይህን ደስታቸውን<br />

ከጥቂት አመታት በፊት በርካታ<br />

ወጭ ፈሶበት በጥቂት አመት ውስጥ<br />

የፈረሰው ቻይና ሰራሽ መንገድ እንኳ<br />

አላቀዘቀዘውም፡፡ ሆኖም የመኪናችንን<br />

ፍጥነት በእጅጉ ቀንሶታል፡፡ በዚህም<br />

ምክንያት በጊዜ መግባት ሲገባን<br />

ግማሹን ሌሊት ሁሉ ለመጓዝ<br />

ተገደናል፡፡<br />

አይደለም ሰማያዊን የግንባሩን አባላት<br />

የማያምነው ኢህአዴግ የልዑካኑንና<br />

ከልዑካኑ ጋር የሚገናኙትን አካላት<br />

በቅርብ እርቀት መከታተሉ የሚጠበቅ<br />

ነው፡፡ ስለሆነም የት እንደደረስን፣<br />

መቼ ጎንደር እንደምንገባና<br />

ሌሎች መረጃዎችን ለአገሪቱ<br />

ሳይሆን ለስልጣን ማራዘሚያ<br />

በሚጠቀምባቸው የደህንነት<br />

ተቋማቱ ሊያዳምጥ እንደሚችል<br />

ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ ይህን<br />

እያወቅንም ቢሆን እኛ እንደልባችን<br />

እናወራለን፡፡ የት እንደደረስን፣ መቼ<br />

እንደምንገባና ሌሎች መረጃዎችንንም<br />

በነጻነት እንለዋወጣለን፡፡ በተለይ<br />

ጎንደር ከሚገኘው የፓርቲው<br />

ቅርንጫፍና ቀድመው ወደ ጎንደር<br />

ካቀኑት የፓርቲው አመራሮች ጋር<br />

እነዚህን መረጃዎች በተከታታይ<br />

ተለዋውጠናል፡፡<br />

ጎንደር ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ላይ<br />

ደረስን፡፡ እነዚህን መረጃዎች<br />

ሲያዳምጥ የነበረው ገዥው ፓርቲ<br />

የተሸናፊ እርምጃ ሊወስድ እንደነበር<br />

የሰማነው ግን በነጋታው ጠዋት ላይ<br />

ነው፡፡ እንፍራንዝ የተባለችውን ከተማ<br />

እኛ ያለፍናት ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት<br />

አካባቢ ነው፡፡ ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት<br />

አካባቢ ‹‹ሰማያዊ ነው!›› ተብሎ<br />

መኪና መዘረፉን የነገረን በአካባቢው<br />

የሚገኝ አንድ የሰማያዊ ፓርቲ ደጋፊ<br />

ነው፡፡ አዎ የተሸነፈ የሚወስደውን<br />

እርምጃ አያውቅም፡፡ ለማመዛዘን<br />

ጊዜም ሆነ ብቃት አይኖረውም፡፡<br />

ወከባው ጎንደር ከደረስን በኋላም<br />

ቢሆን አላቆመም፡፡ ካድሬዎች<br />

ያረፍንበትን ሆቴል ማጨናነቅ ዋነኛ<br />

ስራቸው ሆነ፡፡ ከዚህም አልፈው<br />

‹‹እነዚህን ሰዎች አስወጡልን!››<br />

እስከማለት መድረሳቸውን በግልጽ<br />

ሰምተናል፡፡ በሌላ በኩል የሰላማዊ<br />

ሰልፉ እንዲካሄድ ባለመፈለጋቸው<br />

አንቀበልም ከማለትም አልፈው<br />

ሲደበቁ የሰነበቱት የጎንደር ከተማ<br />

አስተዳደር ባለስልጣናት የሰማያዊ<br />

ወጣቶች ገፍተው ከገቡበት እውነት<br />

ጋር መፋጠጥ የግድ ሆኖባቸዋል፡፡<br />

ሀሙስ ጥር 22 ስድስት ሰዓት ላይ<br />

ሰው የሚበዛባት አራዳ ለቅስቀሳ<br />

ተመርጣለች፡፡ ከየት እንደመጡ<br />

ያልታወቁት የሰማያዊ ወጣቶች<br />

በፍጥነት ወረቀቶችን ለህዝብ<br />

ማድረስ ጀመሩ፡፡ መኪና ላይ ሆነው<br />

መሬቱን አሳልፈው እንደማይሰጡ<br />

ህዝብን ቀሰቀሱ፡፡ ቅስቀሳውን ከአራዳ<br />

እስከ መስቀል አደባባይ በፍጥነት<br />

አከናወኑ፡፡ ምን አልባት እስራት<br />

ካለ ህዝብ በስፋት ከሚያይበት<br />

የመስቀል አደባባይ ላይ መታሰሩ<br />

አዋጭ እንደሚሆን ታምኖበታል፡<br />

፡ እንደተገመተው የተደናገጡት<br />

የከተማው ባለስልጣናት መስቀል<br />

አደባባይ ላይ እየቀሰቀሱ የነበሩትን<br />

ወጣቶች ለማስቆም ጥረት አደረጉ፡<br />

፡ ማስቆም የፈለጉበት መንገድ ግን<br />

የሚያስገርም ነበር፡፡<br />

ልክ ሉማሜ ላይ እንዳደረጉት<br />

የላኩት የትራፊክ ፖሊስ ነው፡፡ ምን<br />

አልባትም መኪናቸውን ከተቀሙ<br />

እንቅስቃሴው ይገታል ከሚል እሳቤ<br />

ሳይሆን አይቀርም፡፡ ጎንደር ላይ ግን<br />

በቀላሉ የሚሳካ አልነበረም፡፡ ሲቪል<br />

የለበሱ የትራፊክ ፖሊሶች ሳይቀሩ<br />

ለወጣቶቹና ተሸናፊዎች ላስደፈሩት<br />

ሉዓላዊነት ዘብ ቆመው ታይተዋል፡<br />

፡ ቅስቀሳውን እንዲያስቆሙ<br />

የተላኩት ፖሊሶች መኪናው ምን<br />

እንዳጠፋ ንገሩን ሲባሉ ምክንያት<br />

አልነበራቸውም፡፡ ግን ‹‹ከበላይ<br />

አካል›› ይዛችኋቸው ኑ መባላቸውን<br />

ብቻ ነው በተደጋጋሚ የሚገልጹት፡፡<br />

ቅስቀሳ ላይ የነበሩት ወጣቶች ከታሰሩ በኋላ የኢትዮጵያ ፖሊስ የሚታወቅበትን ድብደባና ዘለፋ አልፈጸመም፡<br />

፡ ይህ ግን የፖሊሶቹ ደግነት ብቻ አልነበረም፡፡ የከተማ አስተዳደሩ አንዳች ቅርቃር ውስጥ መግባቱን ራሱ<br />

አስመስክሯል፡፡ ወጣቶቹ እስር ቤት እያሉ ከቀናት በፊት የማሳወቂያ ደብዳቤውን አልቀበልም ያሉት አካላት<br />

አመናጭቀው የመለሷቸውን ሰዎች አስጠርተው ተለማምጠዋል፡፡<br />

የሰማያዊ ወጣቶች ደግሞ ጥፋታችንን<br />

ካልነገራችሁን ቅስቀሳውን አናቆምም<br />

ካለንበትም አንንቀሳቀስም አሉ፡፡<br />

ቅስቀሳውን የደገፈው ህዝብም ቢሆን<br />

ተመሳሳይ አቋም ያዘ፡፡ ቅስቀሳውን<br />

ሲከታተል ከነበረው ህዝብ ‹‹ከህዝብ<br />

ጋር እንዳትቀያየሙ›› የሚል<br />

ምክር የተሰጣቸውና ወትሮውንም<br />

ያላመኑበት የትራፊክ ፖሊሶች<br />

መለሳለስ ጀመሩ፡፡ ትንሽ ቆይተው<br />

የወጣቶቹን ቅስቀሳና ከፖሊስ ጋር<br />

የሚያደርጉትን ትዕይንት እንደ ህዝብ<br />

ታድመዋል፡፡<br />

የከተማው አስተዳደር ግን ቅስቀሳው<br />

መቆም እንዳለበት ቆርጧል፡፡<br />

በመሆኑም የትራፊክ ፖሊሶችን ተክቶ<br />

ፖሊስ ተላከ፡፡ ኢህአዴግ ከምንም<br />

በላይ የሚፈራው መረጃን ነው፡<br />

፡ በመሆኑም የፖሊሶች የመጀመሪያ<br />

ኢላማ የሆነው ፎቶ ግራፍ<br />

የሚያነሳው ወጣት ነበር፡፡ ካሜራውን<br />

ለመንጠቅ ሲሞክሩ ግን ከሰማያዊ<br />

ልጆች ከፍተኛ ትግል ገጠማቸው፡<br />

፡ ፖሊስና ወጣቶቹ ተናነቁ፡፡ ህዝብ<br />

ተሰበሰበ፡፡ ወጣቶቹ ህግ አያከብርም<br />

የሚሉት ኢህአዴግ የላካቸውን<br />

ፖሊሶች እየተፋለሙ ‹‹በህግ አምላክ!<br />

በህግ አምላክ!›› ይላሉ፡፡ በህግ ሳይሆን<br />

በጉልበት ቅስቀሳውን እንዲያስቆሙ<br />

የተላኩት ፖሊሶች ግን ከዚህ በላይ<br />

መታገል አልፈለጉም፡፡ አዎ! ከበላይ<br />

አካል ከተሰጣቸው ይልቅ ‹‹በህግ<br />

አምላክ›› ሲባሉ ተደናግጠው ቆሙ፡<br />

፡ ጎንደር ላይ በህግ አምላክ ተከበረ፡<br />

፡ የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች በቀላሉ<br />

እጅ የሚሰጡ አልነበሩም፡፡ እናም<br />

አምነውበት ሳይሆን ከበላይ አካል<br />

የተላኩት ፖሊሶች ያለ ግድ በውድ<br />

ለሰማያዊ ወጣቶች ካሜራውን ለቀቁ፡፡<br />

አሁን ኢህአዴግ ተሸንፏል፡፡ ወጣቶቹ<br />

ደግሞ በአሸናፊነት ይዘምራሉ፡፡<br />

ተከብረሽ የኖርሽው በአባቶቻችን<br />

ደም፣<br />

በአባቶቻችን ደም፣<br />

እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውደም<br />

ያስደፈረሽ ይውደም፣<br />

……….<br />

‹‹የትግል ጉዞ ታሪካዊ፣<br />

ዓላማው ፍጹም ህዝባዊ፣<br />

ራዕያችንም ኢትዮጵያዊ…››<br />

ያም ሆኖ ፖሊሶቹ ‹‹ይዛችኋቸው<br />

ኑ!›› የተባሉትን ትዕዛዝ አልረሱም፡፡<br />

ወጣቶቹ በመኪና ተጫኑ፡፡ ከፖሊሶቹ<br />

ጋር ሆነው ግን ወረቀት ከመበተን፣<br />

በሞንታርቮ ከመቀስቀስ ያገዳቸው<br />

አካል አልነበረም፡፡ እንዲያውም ወደ<br />

ፖሊስ ጣቢያው የሚያደርሰውን<br />

ረዥም መንገድ ይዘው ሲጓዙ<br />

ፖሊሶቹ ሰላማዊ ሰልፉ እንዲካሄድ<br />

ፍላጎት እንደነበራቸው ያሳያል፡፡<br />

ቅስቀሳ ላይ የነበሩት ወጣቶች<br />

ከታሰሩ በኋላ የኢትዮጵያ ፖሊስ<br />

የሚታወቅበትን ድብደባና ዘለፋ<br />

አልፈጸመም፡፡ ይህ ግን የፖሊሶቹ<br />

ደግነት ብቻ አልነበረም፡፡ የከተማ<br />

አስተዳደሩ አንዳች ቅርቃር ውስጥ<br />

መግባቱን ራሱ አስመስክሯል፡፡<br />

ወጣቶቹ እስር ቤት እያሉ ከቀናት<br />

በፊት የማሳወቂያ ደብዳቤውን<br />

አልቀበልም ያሉት አካላት<br />

አመናጭቀው የመለሷቸውን ሰዎች<br />

አስጠርተው ተለማምጠዋል፡፡<br />

በአንድ በኩል ተርበትብተው መደራደር<br />

የሚፈልጉት የጎንደር አስተዳደር<br />

ሰዎች በሌላ በኩል ማዋከባቸውን<br />

ግን አላቆሙም፡፡ የታሰሩት ቢፈቱም<br />

ቅስቀሳውን ለማሰናከል መሳሪያዎቹ<br />

በፖሊስ እንደተያዙ ቆይተዋል፡፡<br />

የመቀስቀሻ መሳሪያዎቹ በፖሊስ<br />

እጅ በመውደቃቸውና ለአንዳንድ<br />

ጥንቃቄዎች ሲባል አርብ ጥር 23<br />

ወረቀት መበተንና ሌሎች ግልጽ<br />

ቅስቀሳዎች አልነበሩም፡፡ ይህም<br />

በስጋት የተዋጡት የከተማው<br />

አስተዳደር አካላትን አስጨንቋል፡<br />

፡ እናም በተቀላቀለ ስሜት ደውለው<br />

‹‹ምነው ጠፋችሁ!›› እስከማለት<br />

ደርሰዋል፡፡ ቅዳሜ ጥር 24 ኮሌጅና<br />

አዘዞ ለቅስቀሳ ተመርጠዋል፡፡<br />

ለቅስቀሳ የወጡት ወጣቶች ኮሌጅና<br />

ዩኒቨርሲቲው አካባቢን በፍጥነት<br />

ከቀሰቀሱ በኋላ ወደ አዘዞ ሲደርሱ<br />

ፖሊስ አስቁሟቸዋል፡፡<br />

የሰማያዊ ፓርቲ ልዑካን ወደ ጎንደር<br />

ካቀኑበት ጊዜ ጀምሮ ከወትሮው በተለየ<br />

መልኩ ኢንተርኔትና ስልክ ተቋርጦ<br />

ለረዥም ሰዓት መቆየት ጀምሯል፡<br />

፡ ከዚህ ባሻገር ከሆቴሉ ጎን የሚገኝ<br />

ቤት በእሳት ተያያዘ ተብሎ ጥይት<br />

በመተኮስ ጫጫታ ለመፍጠርና<br />

መብራት በማጥፋት ለማደናገጥም<br />

ተሞክሯል፡፡ ተቃጠለ የተባለው<br />

ቤት ከሆቴሉ ጎን ቢሆንም ምንም<br />

አይነት ጭስ፣ የእሳት ምልክትና ሽታ<br />

አልነበረውም፡፡ ወዲያውኑ ደግሞ<br />

ጠፋ ተባለ! በቅስቀሳ ላይ የነበሩት<br />

ወጣቶች አዘዞ ላይ በተያዙበት ወቅት<br />

ወደ ገፅ 15 ይዞራል

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!