06.03.2014 Views

Neger Ethiopia Issue 2

Neger Ethiopia Issue 2

Neger Ethiopia Issue 2

SHOW MORE
SHOW LESS

Create successful ePaper yourself

Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.

ነገረ-ኢትዮጵያ<br />

ቅፅ 1 ቁጥር 2<br />

የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም.<br />

16<br />

ኢህአዴግ ተሸንፏል!<br />

(የጉዞ ማስታወሻ)<br />

ጌታቸው ሺፈራው<br />

ዛሬ የማወራው በምርጫ ስለመሸነፍ<br />

አይደለም፡፡ በምርጫ መሸነፍማ ወግ<br />

ነው፡፡ በተለይ ምርጫን ፍትሃዊና<br />

ዋነኛው የስልጣን ምንጭ አድርጎ<br />

ሽንፈቱን በጸጋ ለተቀበለ ‹‹ሽንፈቱ››<br />

አሸናፊነት በሆነ ነበር፡፡ ኢህአዴግ<br />

ይህኛውን ወግ አላገኘውም፡<br />

፡ እንዲያውም አስከፊው ሽንፈት<br />

ሳያውቁት፣ በግድ መሸነፍ ሳይሆን<br />

አይቀርም፡፡ አዎ ኢህአዴግ ይህን<br />

ሽንፈት ተከናንቦታል፡፡ ኢህአዴግ<br />

ይህንን ሽንፈቱን ለመሸፈን ለ23<br />

አመታት በግድ መግዛትን መርጧል፡፡<br />

ከ1997 በኋላ ተቃዋሚዎች<br />

ቢዳከሙም፣ ህዝብ በፖለቲካው ተስፋ<br />

ቆርጦ ‹‹ዝም ብሎ ለመገዛት›› የቆረጠ<br />

ቢመስልም ኢህአዴግ ግን ሽንፈቱን<br />

ይደብቅልኛል ያለውን ወከባና ጥርነፋ<br />

አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ ባለፉት ጥቂት<br />

ወራት ደግሞ በፖለቲካው መስክ<br />

መነቃቃቶች እየታዩ ነው፡፡ ይህኛው<br />

‹‹ዝም›› ያለው ህዝብ ኢህአዴግን<br />

እንደማይፈልግ፣ ኢህአዴግ ምንም<br />

ያህል የመጨቆንና የማታለል አቅም<br />

ቢኖረውም የህዝብን ልብ መግዛት<br />

አለመቻሉንና መሸነፉን የሚያሳይ<br />

ነው፡፡ ኢህአዴግ ለመሸነፉ እጅግ<br />

በርካታ ማሳያዎችን ማንሳት ይቻላል፡<br />

፡ አሁን ግን ለሱዳን አሳልፎ ከሰጠው<br />

መሬት ጋር በተያያዘ ያለው ጉዳይ<br />

ላይ ብቻ ማተኮር ወደድኩ!<br />

ፓርቲ የጎንደር ጉዞ<br />

የሰማያዊ<br />

ሰማያዊ ፓርቲ ወደ ጎንደር ከማቅናቱ<br />

በፊት በጽ/ቤቱ በድንበሩ ጉዳይ ጥናት<br />

ካደረጉት መካከል ብቸኛው የሆኑትን<br />

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያምን<br />

በመጋበዝ ህዝብን አወያይቶ ነበር፡፡<br />

በዚህ ውይይት ወቅት ፕሮፌሰሩን<br />

ጨምሮ ተሰብሳቢዎቹ ‹‹ኢህአዴግ<br />

አገር ሻጭ›› መሆኑን ተናግረዋል፡<br />

፡ ሁሉም እንደ መንግስት ሳይሆን<br />

የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት አሳልፎ<br />

ለመስጠት የተነሳ አንዳች ባዕድ<br />

ሀይል እንደሆነ ተግባብቶበታል፡፡<br />

የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች<br />

ደግሞ ይህን የፕሮፌሰር መስፍንና<br />

የሌሎችን ጥናት እንዲሁም<br />

መረጃዎች በግብዓትነት ወስደው<br />

ሉዓላዊነታቸውን ለማስከበር ወደ<br />

ጎንደር ለማቅናት በዝግጅት ላይ<br />

ነበሩ፡፡<br />

ሰማያዊ ወደ ጎንደር ሲያቀናም<br />

ኢህአዴግ መሸነፉን በጉልህ<br />

ተመልክቻለሁ፡፡ አድርባይ ደህንነትና<br />

ፖሊስ የማይፈሩት ወጣቶች<br />

ወደሚታሰሩበት፣ ወደሚደበደቡበትና<br />

መስዕዋትነት ወደሚያስከፍል ተልዕኮ<br />

ሳይሆን ለሰርግ አሊያም ለሌላ<br />

ቅንጦች የሚጓዙ ያህል ደስተኞች<br />

ነበሩ፡፡ ሰላማዊ ሰልፍ በሚወገዝበት<br />

ስርዓት አብዛኛዎቹ ወጣቶች ‹‹እኔ<br />

አልቀርም!›› በማለት የፓርቲውን<br />

አመራሮች ሲለምኑ፣ በመቅረታቸው<br />

ቅር መሰኘታቸው ስርዓቱ<br />

ሊያስገባቸው ከሚፈልገው የፍርሃት<br />

አዙሪት ሰብረው መውጣታቸውን<br />

የሚያሳይ ነው፡፡<br />

ወከባ<br />

የተሸናፊው<br />

የተሸነፈ የሚወስደው እርምጃ<br />

ግብታዊ ነው፡፡ ተረጋግቶ መፍትሄ<br />

ከመስጠት ይልቅ ማዋከብ፣ መደናበር<br />

ልዩ ባህሪው ነው፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ<br />

ልዑካን ወደ ጎንደር አቅንተው<br />

እንደገና አዲስ አበባ እስኪመለሱ<br />

ያጋጠማቸውም ይህ የተሸናፊዎች<br />

እርምጃ ነው፡፡ ወከባው የጀመረው<br />

የጎጃሟ ሉማሜ ከተማ ላይ ነው፡<br />

፡ ከአዲስ አበባ ጀምሮ በርካታ<br />

የትራፊክ ፖሊሶች እየገላመጡ<br />

ቢያሳልፉንም ከላይ አንዳች<br />

ትዕዛዝ የተሰጣት የምትመስለዋ<br />

የሉማሜዋ የትራፊክ ፖሊስ ግን<br />

በቀላሉ የምታሳልፈን አልነበረችም፡<br />

፡ መውጫው የምትቆዩበትን ቀን<br />

በግልጽ አላስቀመጠም በሚል ሰንካላ<br />

ምክንያት መኪናችን አስቆመች፡<br />

፡ ካልተቀጣችሁ አትሄዱም በማለቷ<br />

ላለመዘግየት ‹‹ቅጣታችን›› ቶሎ<br />

መክፈልን ወሰንን፡፡ ምን አልባትም<br />

ከ‹‹በላይ አካል›› ትዕዛዙ የመጣላት<br />

የምትመስለው የትራፊክ ፖሊስ<br />

ውሳኔ ግን ቢሮ ውስጥ የነበረውን<br />

አለቃዋንም ያስገረመ ነበር፡፡<br />

ለመክፈል ወደ አለቃዋ ቢሮ ያቀኑት<br />

የልዑካኑ አባላት እንዳረጋገጡልን<br />

የትራፊክ ፖሊሷ ያቀረበችው ሰንካላ<br />

ምክንያት ለማስቀጣት ይቅርና<br />

ለተግሳጽ የሚያበቃ አልነበረም፡፡<br />

መስዋትነት ወደሚያስከፍል<br />

ተልዕኮ ሳይሆን ወደ አንዳች ደስታ<br />

ቦታ የሚያቀኑ የሚመስሉት<br />

የልዑካኑ አባላት መንገዱን በሙሉ<br />

የአገራቸውንና የፓርቲያቸውን<br />

መዝሙር በመዘመር፣ እንዲሁም<br />

በመቀላለድና በመሳሳቅ ጉዟቸውን<br />

ቀጥለዋል፡፡ ይህን ደስታቸውን<br />

ከጥቂት አመታት በፊት በርካታ<br />

ወጭ ፈሶበት በጥቂት አመት ውስጥ<br />

የፈረሰው ቻይና ሰራሽ መንገድ እንኳ<br />

አላቀዘቀዘውም፡፡ ሆኖም የመኪናችንን<br />

ፍጥነት በእጅጉ ቀንሶታል፡፡ በዚህም<br />

ምክንያት በጊዜ መግባት ሲገባን<br />

ግማሹን ሌሊት ሁሉ ለመጓዝ<br />

ተገደናል፡፡<br />

አይደለም ሰማያዊን የግንባሩን አባላት<br />

የማያምነው ኢህአዴግ የልዑካኑንና<br />

ከልዑካኑ ጋር የሚገናኙትን አካላት<br />

በቅርብ እርቀት መከታተሉ የሚጠበቅ<br />

ነው፡፡ ስለሆነም የት እንደደረስን፣<br />

መቼ ጎንደር እንደምንገባና<br />

ሌሎች መረጃዎችን ለአገሪቱ<br />

ሳይሆን ለስልጣን ማራዘሚያ<br />

በሚጠቀምባቸው የደህንነት<br />

ተቋማቱ ሊያዳምጥ እንደሚችል<br />

ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ ይህን<br />

እያወቅንም ቢሆን እኛ እንደልባችን<br />

እናወራለን፡፡ የት እንደደረስን፣ መቼ<br />

እንደምንገባና ሌሎች መረጃዎችንንም<br />

በነጻነት እንለዋወጣለን፡፡ በተለይ<br />

ጎንደር ከሚገኘው የፓርቲው<br />

ቅርንጫፍና ቀድመው ወደ ጎንደር<br />

ካቀኑት የፓርቲው አመራሮች ጋር<br />

እነዚህን መረጃዎች በተከታታይ<br />

ተለዋውጠናል፡፡<br />

ጎንደር ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ላይ<br />

ደረስን፡፡ እነዚህን መረጃዎች<br />

ሲያዳምጥ የነበረው ገዥው ፓርቲ<br />

የተሸናፊ እርምጃ ሊወስድ እንደነበር<br />

የሰማነው ግን በነጋታው ጠዋት ላይ<br />

ነው፡፡ እንፍራንዝ የተባለችውን ከተማ<br />

እኛ ያለፍናት ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት<br />

አካባቢ ነው፡፡ ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት<br />

አካባቢ ‹‹ሰማያዊ ነው!›› ተብሎ<br />

መኪና መዘረፉን የነገረን በአካባቢው<br />

የሚገኝ አንድ የሰማያዊ ፓርቲ ደጋፊ<br />

ነው፡፡ አዎ የተሸነፈ የሚወስደውን<br />

እርምጃ አያውቅም፡፡ ለማመዛዘን<br />

ጊዜም ሆነ ብቃት አይኖረውም፡፡<br />

ወከባው ጎንደር ከደረስን በኋላም<br />

ቢሆን አላቆመም፡፡ ካድሬዎች<br />

ያረፍንበትን ሆቴል ማጨናነቅ ዋነኛ<br />

ስራቸው ሆነ፡፡ ከዚህም አልፈው<br />

‹‹እነዚህን ሰዎች አስወጡልን!››<br />

እስከማለት መድረሳቸውን በግልጽ<br />

ሰምተናል፡፡ በሌላ በኩል የሰላማዊ<br />

ሰልፉ እንዲካሄድ ባለመፈለጋቸው<br />

አንቀበልም ከማለትም አልፈው<br />

ሲደበቁ የሰነበቱት የጎንደር ከተማ<br />

አስተዳደር ባለስልጣናት የሰማያዊ<br />

ወጣቶች ገፍተው ከገቡበት እውነት<br />

ጋር መፋጠጥ የግድ ሆኖባቸዋል፡፡<br />

ሀሙስ ጥር 22 ስድስት ሰዓት ላይ<br />

ሰው የሚበዛባት አራዳ ለቅስቀሳ<br />

ተመርጣለች፡፡ ከየት እንደመጡ<br />

ያልታወቁት የሰማያዊ ወጣቶች<br />

በፍጥነት ወረቀቶችን ለህዝብ<br />

ማድረስ ጀመሩ፡፡ መኪና ላይ ሆነው<br />

መሬቱን አሳልፈው እንደማይሰጡ<br />

ህዝብን ቀሰቀሱ፡፡ ቅስቀሳውን ከአራዳ<br />

እስከ መስቀል አደባባይ በፍጥነት<br />

አከናወኑ፡፡ ምን አልባት እስራት<br />

ካለ ህዝብ በስፋት ከሚያይበት<br />

የመስቀል አደባባይ ላይ መታሰሩ<br />

አዋጭ እንደሚሆን ታምኖበታል፡<br />

፡ እንደተገመተው የተደናገጡት<br />

የከተማው ባለስልጣናት መስቀል<br />

አደባባይ ላይ እየቀሰቀሱ የነበሩትን<br />

ወጣቶች ለማስቆም ጥረት አደረጉ፡<br />

፡ ማስቆም የፈለጉበት መንገድ ግን<br />

የሚያስገርም ነበር፡፡<br />

ልክ ሉማሜ ላይ እንዳደረጉት<br />

የላኩት የትራፊክ ፖሊስ ነው፡፡ ምን<br />

አልባትም መኪናቸውን ከተቀሙ<br />

እንቅስቃሴው ይገታል ከሚል እሳቤ<br />

ሳይሆን አይቀርም፡፡ ጎንደር ላይ ግን<br />

በቀላሉ የሚሳካ አልነበረም፡፡ ሲቪል<br />

የለበሱ የትራፊክ ፖሊሶች ሳይቀሩ<br />

ለወጣቶቹና ተሸናፊዎች ላስደፈሩት<br />

ሉዓላዊነት ዘብ ቆመው ታይተዋል፡<br />

፡ ቅስቀሳውን እንዲያስቆሙ<br />

የተላኩት ፖሊሶች መኪናው ምን<br />

እንዳጠፋ ንገሩን ሲባሉ ምክንያት<br />

አልነበራቸውም፡፡ ግን ‹‹ከበላይ<br />

አካል›› ይዛችኋቸው ኑ መባላቸውን<br />

ብቻ ነው በተደጋጋሚ የሚገልጹት፡፡<br />

ቅስቀሳ ላይ የነበሩት ወጣቶች ከታሰሩ በኋላ የኢትዮጵያ ፖሊስ የሚታወቅበትን ድብደባና ዘለፋ አልፈጸመም፡<br />

፡ ይህ ግን የፖሊሶቹ ደግነት ብቻ አልነበረም፡፡ የከተማ አስተዳደሩ አንዳች ቅርቃር ውስጥ መግባቱን ራሱ<br />

አስመስክሯል፡፡ ወጣቶቹ እስር ቤት እያሉ ከቀናት በፊት የማሳወቂያ ደብዳቤውን አልቀበልም ያሉት አካላት<br />

አመናጭቀው የመለሷቸውን ሰዎች አስጠርተው ተለማምጠዋል፡፡<br />

የሰማያዊ ወጣቶች ደግሞ ጥፋታችንን<br />

ካልነገራችሁን ቅስቀሳውን አናቆምም<br />

ካለንበትም አንንቀሳቀስም አሉ፡፡<br />

ቅስቀሳውን የደገፈው ህዝብም ቢሆን<br />

ተመሳሳይ አቋም ያዘ፡፡ ቅስቀሳውን<br />

ሲከታተል ከነበረው ህዝብ ‹‹ከህዝብ<br />

ጋር እንዳትቀያየሙ›› የሚል<br />

ምክር የተሰጣቸውና ወትሮውንም<br />

ያላመኑበት የትራፊክ ፖሊሶች<br />

መለሳለስ ጀመሩ፡፡ ትንሽ ቆይተው<br />

የወጣቶቹን ቅስቀሳና ከፖሊስ ጋር<br />

የሚያደርጉትን ትዕይንት እንደ ህዝብ<br />

ታድመዋል፡፡<br />

የከተማው አስተዳደር ግን ቅስቀሳው<br />

መቆም እንዳለበት ቆርጧል፡፡<br />

በመሆኑም የትራፊክ ፖሊሶችን ተክቶ<br />

ፖሊስ ተላከ፡፡ ኢህአዴግ ከምንም<br />

በላይ የሚፈራው መረጃን ነው፡<br />

፡ በመሆኑም የፖሊሶች የመጀመሪያ<br />

ኢላማ የሆነው ፎቶ ግራፍ<br />

የሚያነሳው ወጣት ነበር፡፡ ካሜራውን<br />

ለመንጠቅ ሲሞክሩ ግን ከሰማያዊ<br />

ልጆች ከፍተኛ ትግል ገጠማቸው፡<br />

፡ ፖሊስና ወጣቶቹ ተናነቁ፡፡ ህዝብ<br />

ተሰበሰበ፡፡ ወጣቶቹ ህግ አያከብርም<br />

የሚሉት ኢህአዴግ የላካቸውን<br />

ፖሊሶች እየተፋለሙ ‹‹በህግ አምላክ!<br />

በህግ አምላክ!›› ይላሉ፡፡ በህግ ሳይሆን<br />

በጉልበት ቅስቀሳውን እንዲያስቆሙ<br />

የተላኩት ፖሊሶች ግን ከዚህ በላይ<br />

መታገል አልፈለጉም፡፡ አዎ! ከበላይ<br />

አካል ከተሰጣቸው ይልቅ ‹‹በህግ<br />

አምላክ›› ሲባሉ ተደናግጠው ቆሙ፡<br />

፡ ጎንደር ላይ በህግ አምላክ ተከበረ፡<br />

፡ የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች በቀላሉ<br />

እጅ የሚሰጡ አልነበሩም፡፡ እናም<br />

አምነውበት ሳይሆን ከበላይ አካል<br />

የተላኩት ፖሊሶች ያለ ግድ በውድ<br />

ለሰማያዊ ወጣቶች ካሜራውን ለቀቁ፡፡<br />

አሁን ኢህአዴግ ተሸንፏል፡፡ ወጣቶቹ<br />

ደግሞ በአሸናፊነት ይዘምራሉ፡፡<br />

ተከብረሽ የኖርሽው በአባቶቻችን<br />

ደም፣<br />

በአባቶቻችን ደም፣<br />

እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውደም<br />

ያስደፈረሽ ይውደም፣<br />

……….<br />

‹‹የትግል ጉዞ ታሪካዊ፣<br />

ዓላማው ፍጹም ህዝባዊ፣<br />

ራዕያችንም ኢትዮጵያዊ…››<br />

ያም ሆኖ ፖሊሶቹ ‹‹ይዛችኋቸው<br />

ኑ!›› የተባሉትን ትዕዛዝ አልረሱም፡፡<br />

ወጣቶቹ በመኪና ተጫኑ፡፡ ከፖሊሶቹ<br />

ጋር ሆነው ግን ወረቀት ከመበተን፣<br />

በሞንታርቮ ከመቀስቀስ ያገዳቸው<br />

አካል አልነበረም፡፡ እንዲያውም ወደ<br />

ፖሊስ ጣቢያው የሚያደርሰውን<br />

ረዥም መንገድ ይዘው ሲጓዙ<br />

ፖሊሶቹ ሰላማዊ ሰልፉ እንዲካሄድ<br />

ፍላጎት እንደነበራቸው ያሳያል፡፡<br />

ቅስቀሳ ላይ የነበሩት ወጣቶች<br />

ከታሰሩ በኋላ የኢትዮጵያ ፖሊስ<br />

የሚታወቅበትን ድብደባና ዘለፋ<br />

አልፈጸመም፡፡ ይህ ግን የፖሊሶቹ<br />

ደግነት ብቻ አልነበረም፡፡ የከተማ<br />

አስተዳደሩ አንዳች ቅርቃር ውስጥ<br />

መግባቱን ራሱ አስመስክሯል፡፡<br />

ወጣቶቹ እስር ቤት እያሉ ከቀናት<br />

በፊት የማሳወቂያ ደብዳቤውን<br />

አልቀበልም ያሉት አካላት<br />

አመናጭቀው የመለሷቸውን ሰዎች<br />

አስጠርተው ተለማምጠዋል፡፡<br />

በአንድ በኩል ተርበትብተው መደራደር<br />

የሚፈልጉት የጎንደር አስተዳደር<br />

ሰዎች በሌላ በኩል ማዋከባቸውን<br />

ግን አላቆሙም፡፡ የታሰሩት ቢፈቱም<br />

ቅስቀሳውን ለማሰናከል መሳሪያዎቹ<br />

በፖሊስ እንደተያዙ ቆይተዋል፡፡<br />

የመቀስቀሻ መሳሪያዎቹ በፖሊስ<br />

እጅ በመውደቃቸውና ለአንዳንድ<br />

ጥንቃቄዎች ሲባል አርብ ጥር 23<br />

ወረቀት መበተንና ሌሎች ግልጽ<br />

ቅስቀሳዎች አልነበሩም፡፡ ይህም<br />

በስጋት የተዋጡት የከተማው<br />

አስተዳደር አካላትን አስጨንቋል፡<br />

፡ እናም በተቀላቀለ ስሜት ደውለው<br />

‹‹ምነው ጠፋችሁ!›› እስከማለት<br />

ደርሰዋል፡፡ ቅዳሜ ጥር 24 ኮሌጅና<br />

አዘዞ ለቅስቀሳ ተመርጠዋል፡፡<br />

ለቅስቀሳ የወጡት ወጣቶች ኮሌጅና<br />

ዩኒቨርሲቲው አካባቢን በፍጥነት<br />

ከቀሰቀሱ በኋላ ወደ አዘዞ ሲደርሱ<br />

ፖሊስ አስቁሟቸዋል፡፡<br />

የሰማያዊ ፓርቲ ልዑካን ወደ ጎንደር<br />

ካቀኑበት ጊዜ ጀምሮ ከወትሮው በተለየ<br />

መልኩ ኢንተርኔትና ስልክ ተቋርጦ<br />

ለረዥም ሰዓት መቆየት ጀምሯል፡<br />

፡ ከዚህ ባሻገር ከሆቴሉ ጎን የሚገኝ<br />

ቤት በእሳት ተያያዘ ተብሎ ጥይት<br />

በመተኮስ ጫጫታ ለመፍጠርና<br />

መብራት በማጥፋት ለማደናገጥም<br />

ተሞክሯል፡፡ ተቃጠለ የተባለው<br />

ቤት ከሆቴሉ ጎን ቢሆንም ምንም<br />

አይነት ጭስ፣ የእሳት ምልክትና ሽታ<br />

አልነበረውም፡፡ ወዲያውኑ ደግሞ<br />

ጠፋ ተባለ! በቅስቀሳ ላይ የነበሩት<br />

ወጣቶች አዘዞ ላይ በተያዙበት ወቅት<br />

ወደ ገፅ 15 ይዞራል

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!