Neger Ethiopia Issue 2
Neger Ethiopia Issue 2
Neger Ethiopia Issue 2
Create successful ePaper yourself
Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.
ነገረ-ኢትዮጵያ<br />
ቅፅ 1 ቁጥር 2<br />
የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም.<br />
16<br />
ኢህአዴግ ተሸንፏል!<br />
(የጉዞ ማስታወሻ)<br />
ጌታቸው ሺፈራው<br />
ዛሬ የማወራው በምርጫ ስለመሸነፍ<br />
አይደለም፡፡ በምርጫ መሸነፍማ ወግ<br />
ነው፡፡ በተለይ ምርጫን ፍትሃዊና<br />
ዋነኛው የስልጣን ምንጭ አድርጎ<br />
ሽንፈቱን በጸጋ ለተቀበለ ‹‹ሽንፈቱ››<br />
አሸናፊነት በሆነ ነበር፡፡ ኢህአዴግ<br />
ይህኛውን ወግ አላገኘውም፡<br />
፡ እንዲያውም አስከፊው ሽንፈት<br />
ሳያውቁት፣ በግድ መሸነፍ ሳይሆን<br />
አይቀርም፡፡ አዎ ኢህአዴግ ይህን<br />
ሽንፈት ተከናንቦታል፡፡ ኢህአዴግ<br />
ይህንን ሽንፈቱን ለመሸፈን ለ23<br />
አመታት በግድ መግዛትን መርጧል፡፡<br />
ከ1997 በኋላ ተቃዋሚዎች<br />
ቢዳከሙም፣ ህዝብ በፖለቲካው ተስፋ<br />
ቆርጦ ‹‹ዝም ብሎ ለመገዛት›› የቆረጠ<br />
ቢመስልም ኢህአዴግ ግን ሽንፈቱን<br />
ይደብቅልኛል ያለውን ወከባና ጥርነፋ<br />
አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ ባለፉት ጥቂት<br />
ወራት ደግሞ በፖለቲካው መስክ<br />
መነቃቃቶች እየታዩ ነው፡፡ ይህኛው<br />
‹‹ዝም›› ያለው ህዝብ ኢህአዴግን<br />
እንደማይፈልግ፣ ኢህአዴግ ምንም<br />
ያህል የመጨቆንና የማታለል አቅም<br />
ቢኖረውም የህዝብን ልብ መግዛት<br />
አለመቻሉንና መሸነፉን የሚያሳይ<br />
ነው፡፡ ኢህአዴግ ለመሸነፉ እጅግ<br />
በርካታ ማሳያዎችን ማንሳት ይቻላል፡<br />
፡ አሁን ግን ለሱዳን አሳልፎ ከሰጠው<br />
መሬት ጋር በተያያዘ ያለው ጉዳይ<br />
ላይ ብቻ ማተኮር ወደድኩ!<br />
ፓርቲ የጎንደር ጉዞ<br />
የሰማያዊ<br />
ሰማያዊ ፓርቲ ወደ ጎንደር ከማቅናቱ<br />
በፊት በጽ/ቤቱ በድንበሩ ጉዳይ ጥናት<br />
ካደረጉት መካከል ብቸኛው የሆኑትን<br />
ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያምን<br />
በመጋበዝ ህዝብን አወያይቶ ነበር፡፡<br />
በዚህ ውይይት ወቅት ፕሮፌሰሩን<br />
ጨምሮ ተሰብሳቢዎቹ ‹‹ኢህአዴግ<br />
አገር ሻጭ›› መሆኑን ተናግረዋል፡<br />
፡ ሁሉም እንደ መንግስት ሳይሆን<br />
የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት አሳልፎ<br />
ለመስጠት የተነሳ አንዳች ባዕድ<br />
ሀይል እንደሆነ ተግባብቶበታል፡፡<br />
የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች<br />
ደግሞ ይህን የፕሮፌሰር መስፍንና<br />
የሌሎችን ጥናት እንዲሁም<br />
መረጃዎች በግብዓትነት ወስደው<br />
ሉዓላዊነታቸውን ለማስከበር ወደ<br />
ጎንደር ለማቅናት በዝግጅት ላይ<br />
ነበሩ፡፡<br />
ሰማያዊ ወደ ጎንደር ሲያቀናም<br />
ኢህአዴግ መሸነፉን በጉልህ<br />
ተመልክቻለሁ፡፡ አድርባይ ደህንነትና<br />
ፖሊስ የማይፈሩት ወጣቶች<br />
ወደሚታሰሩበት፣ ወደሚደበደቡበትና<br />
መስዕዋትነት ወደሚያስከፍል ተልዕኮ<br />
ሳይሆን ለሰርግ አሊያም ለሌላ<br />
ቅንጦች የሚጓዙ ያህል ደስተኞች<br />
ነበሩ፡፡ ሰላማዊ ሰልፍ በሚወገዝበት<br />
ስርዓት አብዛኛዎቹ ወጣቶች ‹‹እኔ<br />
አልቀርም!›› በማለት የፓርቲውን<br />
አመራሮች ሲለምኑ፣ በመቅረታቸው<br />
ቅር መሰኘታቸው ስርዓቱ<br />
ሊያስገባቸው ከሚፈልገው የፍርሃት<br />
አዙሪት ሰብረው መውጣታቸውን<br />
የሚያሳይ ነው፡፡<br />
ወከባ<br />
የተሸናፊው<br />
የተሸነፈ የሚወስደው እርምጃ<br />
ግብታዊ ነው፡፡ ተረጋግቶ መፍትሄ<br />
ከመስጠት ይልቅ ማዋከብ፣ መደናበር<br />
ልዩ ባህሪው ነው፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ<br />
ልዑካን ወደ ጎንደር አቅንተው<br />
እንደገና አዲስ አበባ እስኪመለሱ<br />
ያጋጠማቸውም ይህ የተሸናፊዎች<br />
እርምጃ ነው፡፡ ወከባው የጀመረው<br />
የጎጃሟ ሉማሜ ከተማ ላይ ነው፡<br />
፡ ከአዲስ አበባ ጀምሮ በርካታ<br />
የትራፊክ ፖሊሶች እየገላመጡ<br />
ቢያሳልፉንም ከላይ አንዳች<br />
ትዕዛዝ የተሰጣት የምትመስለዋ<br />
የሉማሜዋ የትራፊክ ፖሊስ ግን<br />
በቀላሉ የምታሳልፈን አልነበረችም፡<br />
፡ መውጫው የምትቆዩበትን ቀን<br />
በግልጽ አላስቀመጠም በሚል ሰንካላ<br />
ምክንያት መኪናችን አስቆመች፡<br />
፡ ካልተቀጣችሁ አትሄዱም በማለቷ<br />
ላለመዘግየት ‹‹ቅጣታችን›› ቶሎ<br />
መክፈልን ወሰንን፡፡ ምን አልባትም<br />
ከ‹‹በላይ አካል›› ትዕዛዙ የመጣላት<br />
የምትመስለው የትራፊክ ፖሊስ<br />
ውሳኔ ግን ቢሮ ውስጥ የነበረውን<br />
አለቃዋንም ያስገረመ ነበር፡፡<br />
ለመክፈል ወደ አለቃዋ ቢሮ ያቀኑት<br />
የልዑካኑ አባላት እንዳረጋገጡልን<br />
የትራፊክ ፖሊሷ ያቀረበችው ሰንካላ<br />
ምክንያት ለማስቀጣት ይቅርና<br />
ለተግሳጽ የሚያበቃ አልነበረም፡፡<br />
መስዋትነት ወደሚያስከፍል<br />
ተልዕኮ ሳይሆን ወደ አንዳች ደስታ<br />
ቦታ የሚያቀኑ የሚመስሉት<br />
የልዑካኑ አባላት መንገዱን በሙሉ<br />
የአገራቸውንና የፓርቲያቸውን<br />
መዝሙር በመዘመር፣ እንዲሁም<br />
በመቀላለድና በመሳሳቅ ጉዟቸውን<br />
ቀጥለዋል፡፡ ይህን ደስታቸውን<br />
ከጥቂት አመታት በፊት በርካታ<br />
ወጭ ፈሶበት በጥቂት አመት ውስጥ<br />
የፈረሰው ቻይና ሰራሽ መንገድ እንኳ<br />
አላቀዘቀዘውም፡፡ ሆኖም የመኪናችንን<br />
ፍጥነት በእጅጉ ቀንሶታል፡፡ በዚህም<br />
ምክንያት በጊዜ መግባት ሲገባን<br />
ግማሹን ሌሊት ሁሉ ለመጓዝ<br />
ተገደናል፡፡<br />
አይደለም ሰማያዊን የግንባሩን አባላት<br />
የማያምነው ኢህአዴግ የልዑካኑንና<br />
ከልዑካኑ ጋር የሚገናኙትን አካላት<br />
በቅርብ እርቀት መከታተሉ የሚጠበቅ<br />
ነው፡፡ ስለሆነም የት እንደደረስን፣<br />
መቼ ጎንደር እንደምንገባና<br />
ሌሎች መረጃዎችን ለአገሪቱ<br />
ሳይሆን ለስልጣን ማራዘሚያ<br />
በሚጠቀምባቸው የደህንነት<br />
ተቋማቱ ሊያዳምጥ እንደሚችል<br />
ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ ይህን<br />
እያወቅንም ቢሆን እኛ እንደልባችን<br />
እናወራለን፡፡ የት እንደደረስን፣ መቼ<br />
እንደምንገባና ሌሎች መረጃዎችንንም<br />
በነጻነት እንለዋወጣለን፡፡ በተለይ<br />
ጎንደር ከሚገኘው የፓርቲው<br />
ቅርንጫፍና ቀድመው ወደ ጎንደር<br />
ካቀኑት የፓርቲው አመራሮች ጋር<br />
እነዚህን መረጃዎች በተከታታይ<br />
ተለዋውጠናል፡፡<br />
ጎንደር ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ላይ<br />
ደረስን፡፡ እነዚህን መረጃዎች<br />
ሲያዳምጥ የነበረው ገዥው ፓርቲ<br />
የተሸናፊ እርምጃ ሊወስድ እንደነበር<br />
የሰማነው ግን በነጋታው ጠዋት ላይ<br />
ነው፡፡ እንፍራንዝ የተባለችውን ከተማ<br />
እኛ ያለፍናት ከሌሊቱ ስድስት ሰዓት<br />
አካባቢ ነው፡፡ ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት<br />
አካባቢ ‹‹ሰማያዊ ነው!›› ተብሎ<br />
መኪና መዘረፉን የነገረን በአካባቢው<br />
የሚገኝ አንድ የሰማያዊ ፓርቲ ደጋፊ<br />
ነው፡፡ አዎ የተሸነፈ የሚወስደውን<br />
እርምጃ አያውቅም፡፡ ለማመዛዘን<br />
ጊዜም ሆነ ብቃት አይኖረውም፡፡<br />
ወከባው ጎንደር ከደረስን በኋላም<br />
ቢሆን አላቆመም፡፡ ካድሬዎች<br />
ያረፍንበትን ሆቴል ማጨናነቅ ዋነኛ<br />
ስራቸው ሆነ፡፡ ከዚህም አልፈው<br />
‹‹እነዚህን ሰዎች አስወጡልን!››<br />
እስከማለት መድረሳቸውን በግልጽ<br />
ሰምተናል፡፡ በሌላ በኩል የሰላማዊ<br />
ሰልፉ እንዲካሄድ ባለመፈለጋቸው<br />
አንቀበልም ከማለትም አልፈው<br />
ሲደበቁ የሰነበቱት የጎንደር ከተማ<br />
አስተዳደር ባለስልጣናት የሰማያዊ<br />
ወጣቶች ገፍተው ከገቡበት እውነት<br />
ጋር መፋጠጥ የግድ ሆኖባቸዋል፡፡<br />
ሀሙስ ጥር 22 ስድስት ሰዓት ላይ<br />
ሰው የሚበዛባት አራዳ ለቅስቀሳ<br />
ተመርጣለች፡፡ ከየት እንደመጡ<br />
ያልታወቁት የሰማያዊ ወጣቶች<br />
በፍጥነት ወረቀቶችን ለህዝብ<br />
ማድረስ ጀመሩ፡፡ መኪና ላይ ሆነው<br />
መሬቱን አሳልፈው እንደማይሰጡ<br />
ህዝብን ቀሰቀሱ፡፡ ቅስቀሳውን ከአራዳ<br />
እስከ መስቀል አደባባይ በፍጥነት<br />
አከናወኑ፡፡ ምን አልባት እስራት<br />
ካለ ህዝብ በስፋት ከሚያይበት<br />
የመስቀል አደባባይ ላይ መታሰሩ<br />
አዋጭ እንደሚሆን ታምኖበታል፡<br />
፡ እንደተገመተው የተደናገጡት<br />
የከተማው ባለስልጣናት መስቀል<br />
አደባባይ ላይ እየቀሰቀሱ የነበሩትን<br />
ወጣቶች ለማስቆም ጥረት አደረጉ፡<br />
፡ ማስቆም የፈለጉበት መንገድ ግን<br />
የሚያስገርም ነበር፡፡<br />
ልክ ሉማሜ ላይ እንዳደረጉት<br />
የላኩት የትራፊክ ፖሊስ ነው፡፡ ምን<br />
አልባትም መኪናቸውን ከተቀሙ<br />
እንቅስቃሴው ይገታል ከሚል እሳቤ<br />
ሳይሆን አይቀርም፡፡ ጎንደር ላይ ግን<br />
በቀላሉ የሚሳካ አልነበረም፡፡ ሲቪል<br />
የለበሱ የትራፊክ ፖሊሶች ሳይቀሩ<br />
ለወጣቶቹና ተሸናፊዎች ላስደፈሩት<br />
ሉዓላዊነት ዘብ ቆመው ታይተዋል፡<br />
፡ ቅስቀሳውን እንዲያስቆሙ<br />
የተላኩት ፖሊሶች መኪናው ምን<br />
እንዳጠፋ ንገሩን ሲባሉ ምክንያት<br />
አልነበራቸውም፡፡ ግን ‹‹ከበላይ<br />
አካል›› ይዛችኋቸው ኑ መባላቸውን<br />
ብቻ ነው በተደጋጋሚ የሚገልጹት፡፡<br />
ቅስቀሳ ላይ የነበሩት ወጣቶች ከታሰሩ በኋላ የኢትዮጵያ ፖሊስ የሚታወቅበትን ድብደባና ዘለፋ አልፈጸመም፡<br />
፡ ይህ ግን የፖሊሶቹ ደግነት ብቻ አልነበረም፡፡ የከተማ አስተዳደሩ አንዳች ቅርቃር ውስጥ መግባቱን ራሱ<br />
አስመስክሯል፡፡ ወጣቶቹ እስር ቤት እያሉ ከቀናት በፊት የማሳወቂያ ደብዳቤውን አልቀበልም ያሉት አካላት<br />
አመናጭቀው የመለሷቸውን ሰዎች አስጠርተው ተለማምጠዋል፡፡<br />
የሰማያዊ ወጣቶች ደግሞ ጥፋታችንን<br />
ካልነገራችሁን ቅስቀሳውን አናቆምም<br />
ካለንበትም አንንቀሳቀስም አሉ፡፡<br />
ቅስቀሳውን የደገፈው ህዝብም ቢሆን<br />
ተመሳሳይ አቋም ያዘ፡፡ ቅስቀሳውን<br />
ሲከታተል ከነበረው ህዝብ ‹‹ከህዝብ<br />
ጋር እንዳትቀያየሙ›› የሚል<br />
ምክር የተሰጣቸውና ወትሮውንም<br />
ያላመኑበት የትራፊክ ፖሊሶች<br />
መለሳለስ ጀመሩ፡፡ ትንሽ ቆይተው<br />
የወጣቶቹን ቅስቀሳና ከፖሊስ ጋር<br />
የሚያደርጉትን ትዕይንት እንደ ህዝብ<br />
ታድመዋል፡፡<br />
የከተማው አስተዳደር ግን ቅስቀሳው<br />
መቆም እንዳለበት ቆርጧል፡፡<br />
በመሆኑም የትራፊክ ፖሊሶችን ተክቶ<br />
ፖሊስ ተላከ፡፡ ኢህአዴግ ከምንም<br />
በላይ የሚፈራው መረጃን ነው፡<br />
፡ በመሆኑም የፖሊሶች የመጀመሪያ<br />
ኢላማ የሆነው ፎቶ ግራፍ<br />
የሚያነሳው ወጣት ነበር፡፡ ካሜራውን<br />
ለመንጠቅ ሲሞክሩ ግን ከሰማያዊ<br />
ልጆች ከፍተኛ ትግል ገጠማቸው፡<br />
፡ ፖሊስና ወጣቶቹ ተናነቁ፡፡ ህዝብ<br />
ተሰበሰበ፡፡ ወጣቶቹ ህግ አያከብርም<br />
የሚሉት ኢህአዴግ የላካቸውን<br />
ፖሊሶች እየተፋለሙ ‹‹በህግ አምላክ!<br />
በህግ አምላክ!›› ይላሉ፡፡ በህግ ሳይሆን<br />
በጉልበት ቅስቀሳውን እንዲያስቆሙ<br />
የተላኩት ፖሊሶች ግን ከዚህ በላይ<br />
መታገል አልፈለጉም፡፡ አዎ! ከበላይ<br />
አካል ከተሰጣቸው ይልቅ ‹‹በህግ<br />
አምላክ›› ሲባሉ ተደናግጠው ቆሙ፡<br />
፡ ጎንደር ላይ በህግ አምላክ ተከበረ፡<br />
፡ የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች በቀላሉ<br />
እጅ የሚሰጡ አልነበሩም፡፡ እናም<br />
አምነውበት ሳይሆን ከበላይ አካል<br />
የተላኩት ፖሊሶች ያለ ግድ በውድ<br />
ለሰማያዊ ወጣቶች ካሜራውን ለቀቁ፡፡<br />
አሁን ኢህአዴግ ተሸንፏል፡፡ ወጣቶቹ<br />
ደግሞ በአሸናፊነት ይዘምራሉ፡፡<br />
ተከብረሽ የኖርሽው በአባቶቻችን<br />
ደም፣<br />
በአባቶቻችን ደም፣<br />
እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውደም<br />
ያስደፈረሽ ይውደም፣<br />
……….<br />
‹‹የትግል ጉዞ ታሪካዊ፣<br />
ዓላማው ፍጹም ህዝባዊ፣<br />
ራዕያችንም ኢትዮጵያዊ…››<br />
ያም ሆኖ ፖሊሶቹ ‹‹ይዛችኋቸው<br />
ኑ!›› የተባሉትን ትዕዛዝ አልረሱም፡፡<br />
ወጣቶቹ በመኪና ተጫኑ፡፡ ከፖሊሶቹ<br />
ጋር ሆነው ግን ወረቀት ከመበተን፣<br />
በሞንታርቮ ከመቀስቀስ ያገዳቸው<br />
አካል አልነበረም፡፡ እንዲያውም ወደ<br />
ፖሊስ ጣቢያው የሚያደርሰውን<br />
ረዥም መንገድ ይዘው ሲጓዙ<br />
ፖሊሶቹ ሰላማዊ ሰልፉ እንዲካሄድ<br />
ፍላጎት እንደነበራቸው ያሳያል፡፡<br />
ቅስቀሳ ላይ የነበሩት ወጣቶች<br />
ከታሰሩ በኋላ የኢትዮጵያ ፖሊስ<br />
የሚታወቅበትን ድብደባና ዘለፋ<br />
አልፈጸመም፡፡ ይህ ግን የፖሊሶቹ<br />
ደግነት ብቻ አልነበረም፡፡ የከተማ<br />
አስተዳደሩ አንዳች ቅርቃር ውስጥ<br />
መግባቱን ራሱ አስመስክሯል፡፡<br />
ወጣቶቹ እስር ቤት እያሉ ከቀናት<br />
በፊት የማሳወቂያ ደብዳቤውን<br />
አልቀበልም ያሉት አካላት<br />
አመናጭቀው የመለሷቸውን ሰዎች<br />
አስጠርተው ተለማምጠዋል፡፡<br />
በአንድ በኩል ተርበትብተው መደራደር<br />
የሚፈልጉት የጎንደር አስተዳደር<br />
ሰዎች በሌላ በኩል ማዋከባቸውን<br />
ግን አላቆሙም፡፡ የታሰሩት ቢፈቱም<br />
ቅስቀሳውን ለማሰናከል መሳሪያዎቹ<br />
በፖሊስ እንደተያዙ ቆይተዋል፡፡<br />
የመቀስቀሻ መሳሪያዎቹ በፖሊስ<br />
እጅ በመውደቃቸውና ለአንዳንድ<br />
ጥንቃቄዎች ሲባል አርብ ጥር 23<br />
ወረቀት መበተንና ሌሎች ግልጽ<br />
ቅስቀሳዎች አልነበሩም፡፡ ይህም<br />
በስጋት የተዋጡት የከተማው<br />
አስተዳደር አካላትን አስጨንቋል፡<br />
፡ እናም በተቀላቀለ ስሜት ደውለው<br />
‹‹ምነው ጠፋችሁ!›› እስከማለት<br />
ደርሰዋል፡፡ ቅዳሜ ጥር 24 ኮሌጅና<br />
አዘዞ ለቅስቀሳ ተመርጠዋል፡፡<br />
ለቅስቀሳ የወጡት ወጣቶች ኮሌጅና<br />
ዩኒቨርሲቲው አካባቢን በፍጥነት<br />
ከቀሰቀሱ በኋላ ወደ አዘዞ ሲደርሱ<br />
ፖሊስ አስቁሟቸዋል፡፡<br />
የሰማያዊ ፓርቲ ልዑካን ወደ ጎንደር<br />
ካቀኑበት ጊዜ ጀምሮ ከወትሮው በተለየ<br />
መልኩ ኢንተርኔትና ስልክ ተቋርጦ<br />
ለረዥም ሰዓት መቆየት ጀምሯል፡<br />
፡ ከዚህ ባሻገር ከሆቴሉ ጎን የሚገኝ<br />
ቤት በእሳት ተያያዘ ተብሎ ጥይት<br />
በመተኮስ ጫጫታ ለመፍጠርና<br />
መብራት በማጥፋት ለማደናገጥም<br />
ተሞክሯል፡፡ ተቃጠለ የተባለው<br />
ቤት ከሆቴሉ ጎን ቢሆንም ምንም<br />
አይነት ጭስ፣ የእሳት ምልክትና ሽታ<br />
አልነበረውም፡፡ ወዲያውኑ ደግሞ<br />
ጠፋ ተባለ! በቅስቀሳ ላይ የነበሩት<br />
ወጣቶች አዘዞ ላይ በተያዙበት ወቅት<br />
ወደ ገፅ 15 ይዞራል