06.03.2014 Views

Neger Ethiopia Issue 2

Neger Ethiopia Issue 2

Neger Ethiopia Issue 2

SHOW MORE
SHOW LESS

You also want an ePaper? Increase the reach of your titles

YUMPU automatically turns print PDFs into web optimized ePapers that Google loves.

5 የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2 ነገረ-ኢትዮጵያ<br />

ፖለቲካ<br />

‹‹መንግስት›› አሳልፎ የሰጠው<br />

ሉዓላዊነት<br />

ጌታቸው ሺፈራው<br />

ለአንድ አገር ሉዓላዊነት ቁልፍ<br />

ከሚባሉት ጉዳዮች መካከል<br />

ወሰን ዋነኛው መመዘኛ ነው፡፡<br />

የወሰን/የድንበር ጉዳይ ድንበር<br />

ብቻ ሳይሆን ከድንበሩ ጋር<br />

ያለውን ታሪካዊ ሂደትም ይጨምራል፡<br />

፡ ለአንድ መንግስትና ትውልድ የቀደሙ<br />

አባቶች ያኖሩትን ድንበር የመቆጣጠርና<br />

መጠበቅ ታሪካዊ ግዴታቸው ነው፡፡<br />

የውጭ አሊያም ሌላ ሀይል የኖረውን<br />

የአገሪቱን ድንበር የሚደፍር አሊያም<br />

የሚያስቀይር ከሆነ የአገሪቱ ሉዓላዊነት<br />

አደጋ ውስጥ ወድቋል ማለት ነው፡<br />

፡ የአንዲት አገርና ህዝቧ ያለ ድንበር/<br />

ወሰን ሊኖር አይችልም፡፡ አገሪቱ ብቻዋን<br />

መሆን እንደማትችል ሁሉ ክብሯን፣<br />

ታሪኳን፣ የዕለት ተዕለት እንቅስቀቃሴዋ፣<br />

ደህንነቷ ላይ ድንበር ከፍተኛ አስተዋጽኦ<br />

ይኖረዋል፡፡<br />

የወሰን አለመከበር ወይንም ሌላ ችግር<br />

እኒህን ሁሉ ጉዳዮች የሚያዛባ ይሆናል፡፡<br />

ለዚህም ነው ሌሎች አገራት ከሚሰጡት<br />

እውቅና ይልቅ ድንበር የአንድ አገር<br />

በተጨባጭ /የሚታይ/ ሉዓላዊነት<br />

መገለጫ ነው የሚባለው፡፡ ድንበር<br />

ዋነኛው የሉዓላዊነት አካል ስለመሆኑ<br />

የኢትዮጵያ ህዝብ ሲበድሉት የኖሩት<br />

አገዛዞች ‹‹አገርህ ተደፈረች›› ሲሉት<br />

ለጊዜውም ቢሆን ልዩነቱን ወደጎን ትቶ<br />

ዳር ድንበር ሊያስከበር ሲተም መኖሩ<br />

ትልቅ ማስረጃ ነው፡፡ በተቃራኒው<br />

መንግስታቱ ለሉዓላዊነት የህዝብን ያህል<br />

ቁርጠኛ ሆነው አልተገኙም፡፡ በዚህ በኩል<br />

ደግሞ ኢህአዴግ ሉዓላዊነትን አሳልፎ<br />

በመስጠት ወደር አልረገኘለትም፡፡<br />

አንድ አገር ሉዓላዊ የምትሆነው አሊያም<br />

ይህ ክብር የሚቀጥለው ድንበሯን፣<br />

ታሪኳንና የህዝብን ጥቅም አስጠብቆ<br />

የሚኖር አገር ወዳድ መንግስት ሲኖራት<br />

ብቻ ነው፡፡ በዚህ በኩል የአሁኗ<br />

ኢትዮጵያ አልታደለችም፡፡ የአገርን<br />

ጥቅም፣ በደምና በአጥንት የተገነባን<br />

ታሪክና ድንበር አሳልፎ የሚሰጥ አካል<br />

ባለበት የአገሪቱ ሉዓላዊነት አደጋ<br />

ውስጥ ይገባል፡፡ ሉዓላዊነት የአንዲት<br />

አገር ከሌሎች አገራት ጋር ሲነጻጸር<br />

ያላት እኩል ክብር፣ ህጋዊ ሰውነት<br />

እንደመሆኑ መንግስት የሚባለው አካል<br />

ወሰኗን ባልተገባ መንገድ ለሌሎች<br />

አሳልፎ የሚሰጥ ወይንም የሚወሰድበት<br />

ከሆነ ሉዓላዊነቷ ተደፍሯል ማለት ነው፡<br />

፡ ህወሓት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት<br />

ማስደፈር የጀመረው ገና በርሃ በነበረበት<br />

ወቅት ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት ከማንም<br />

ቀድሞ በየጊዜው ሰራዊት ወደ ሶማሊያ<br />

የሚልከው ህወሓት ያኔ ገና በርሃ እያለ<br />

ተስፋፊውን የሶማሊያ መንግስት እስከ<br />

ድሬዳዋ ድረስ መንገድ መምራቱን<br />

እንደ አስግደ ያሉት የቀድሞው የቡድኑ<br />

አባላት እማኝነታቸውን በይቅርታ መልክ<br />

ገልጸዋል፡፡<br />

ህወሓት እንደ ፖለቲካ ቡድን<br />

ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ኤርትራ<br />

የኢትዮጵያ ቅኝ ግዛት እንደሆነችና ነጻ<br />

መውጣት እንዳለባት ሲሰብክ ኖራል፡፡<br />

ህወሓት ‹‹አሸባሪ›› በነበረበት በዛ ወቅት<br />

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ<br />

መለስ ዜናዊ ስለ ኤርትራ ጉዳይ ሁለት<br />

መጽኃፍትን ጽፈዋል፡፡ ‹‹የኤርትራ<br />

ህዝብ ትግል ከየት ወደየት›› በተሰኘው<br />

መጽኃፋቸውም ኤርትራን ከኢትዮጵያ<br />

ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌላት<br />

ነጻ አገር መሆኗን አውጀዋል፡፡ አቶ<br />

መለስና ህወሓት ይህን በሚሉበት ወቅት<br />

በርካታ የኤርትራ ተወላጆች በአገሪቱ<br />

አሁን ህወሓት ለሌሎች የግንባሩ አባል<br />

ፓርቲዎች አሳልፎ የማይሰጣቸው ቁልፍ<br />

ስልጣን እንደነበራቸው አይዘነጋም፡፡<br />

ገና ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ኤርትራን<br />

ከኢትዮጵያ መነጠልን አላማው አድርጎ<br />

የተነሳው ህወሓት ደርግን አሸንፎ ቤተ-<br />

መንግስት ሲገባ የወሰደው እርምጃ<br />

የዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ ኤርትራን<br />

እውቅና እንዲሰጥ ማድረግ ነበር፡፡ ይህም<br />

ኢህአዴግን የዋናዋ አገር ገዥ ሆኖ<br />

የአገሪቱ ክፍልን በፈቃደኝነት ያስገነጠለ<br />

(ሉዓላዊነቷን አሳልፎ የሰጠ) ብቸኛው<br />

ፓርቲ ሳያደርገው አይቀርም፡፡ ኤርትራን<br />

በገዛ እጁ ያስገነጠለው ህወሓት/ኢህአዴግ<br />

ከሻዕቢያ ጋር የነበረው ፍቅር ሲያልቅ<br />

የአገሩ ሉዓላዊነት ተላልፎ የተሰጠበት<br />

የኢትዮጵያ ህዝብ በደሉን ለጊዜው ወደጎን<br />

ትቶ ዳር ድንበሩን ለማስከበር ሲነሳ አገዛዙ<br />

የማይጨነቅለትን ሉዓላዊነት ለማስከበር<br />

እንደማይደክመው አሳይቷል፡፡ ጦርነቱ<br />

በኢትዮጵያ ህዝብ አሸናፊነት ከተጠናቀቀ<br />

በኋላም ቢሆን ህወሓት የለመደውን<br />

ሉዓላዊነት አሳልፎ የመስጠት ልክፍት<br />

ደግሞታል፡፡ ይህ አልበቃው ሲልም<br />

ህዝብ ከእሱ በላይ ለአገሪቱ ሉዓላዊነት<br />

እንደሚጨነቅ ጠንቅቆ ስለሚያውቅም<br />

‹‹ባድመን አግኝተናል!›› በሚል ህዝብን<br />

አሞኝቷል፡፡ ይህም ህወሓት/ኢህአዴግ<br />

ከሉዓላዊነት ጋር ያላውን ተቃርኖ<br />

በጉልህ የሚያሳይ ነው፡፡<br />

የኢህአዴግና የሉዓላዊነት ተቃርኖ<br />

አሁንም ቀጥሏል፡፡ ከስድስትና ሰባት<br />

አመታት ጀምሮ የኢትዮጵያን መሬት<br />

አሳልፎ ለሱዳን ለመስጠት በድብቅ<br />

እየተዋዋለ መሆኑ ሲነገር ቆይቷል፡<br />

፡ በቅርቡ ደግሞ ‹‹ሱዳን ትሪብዩን››<br />

የተባለው የሱዳን ጋዜጣ ‹‹ለም መሬታችን<br />

አገኘን!›› የሚል ዜና ማውጣቱን ተከትሎ<br />

ኢህአዴግ መሬቱን ለመስረከብ መቃረቡን<br />

አመላክቷል፡፡ የአንድ አገር መንግስት<br />

የአገሪቱን ድንበር ማስጠበቅና ማስከበር፣<br />

የዜጎቹን ጥቅም ማስከበር ሲኖርበት<br />

ለራሱ ግላዊ ጥቅም፣ ህጋዊ መሰረት<br />

በሌለው መንገድ የአገሩን ወሰንና ድንበር<br />

አሳልፎ የሚሰጥ ከሆነ በአገር ውስጥ<br />

የሌሎች ወኪል ሆኖ የአገርን ሉዓላዊነት<br />

እየደፈረ ከመሆን ውጭ ሌላ ሊባልለት<br />

አይችልም፡፡<br />

ይህ የ‹‹መንግስት›› ተግባር ልክ ቅኝ<br />

ገዥዎቹ የራሳቸው ታማኞች (ባንዳዎች)<br />

እንደነበሯቸው ማለት ነው፡፡ አንዲት<br />

በመንግስት ስር የምትገኝ አገር ሉዓላዊ<br />

የምትባለው ይህ መንግስት የአገሪቱን<br />

ወሰንና ሌሎች ጥቅሟን በህጋዊ መንገድ<br />

መቆጣጠርና ማስተዳደር ከቻለና<br />

በጥቅምም ይሁን በአቅም ማነስ ለውጭ<br />

ሀይል የአገሪቱን ጥቅም፣ ክብር፣ ወሰን<br />

አሳልፎ የማይሰጥ ከሆነ ብቻ ነው፡፡<br />

አገሪቱን ሁለመናው ነገር ተቆጣጥሮና<br />

እያስተዳደረም ቢሆን በውጭ ሀይል<br />

ተጽዕኖ ውሳኔ የሚያስተላልፍ፣<br />

የአገሪቱን ጥቅም አሳልፎ የሚሰጥ<br />

ከሆነ የአገሪቱ ሉዓላዊነቷ ተደፍሯል፡<br />

፡ የኢትዮጵያን መሬት ለሱዳን አሳልፎ<br />

ለመስጠት እየተደራደረ ያለው ኢህአዴግ<br />

የአገርን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ፣ ለህዝብ<br />

ጥቅም በመቆም ከሚታወቅ ‹‹መንግስት››<br />

ከተባለ አካል ይልቅ በሚገዛት አገር<br />

ውስጥ ለሱዳን ጥቅም የቆመ መሆኑን<br />

አሳይቷል፡፡<br />

አንድ አገር ሉዓላዊ ነው የሚባለው<br />

የአገሪቱን ዜጎች ከውጭ ጥቃት<br />

የሚከላከል አካል (መንግስት) ካለ ብቻ<br />

ቢሆንም የሱዳን ኢትዮጵያ ድንበር<br />

ችግር ከተከሰተ በኋላ በመተማና<br />

አካባቢው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን<br />

ለሱዳን የደህንነት ኃይሎች ተላልፈው<br />

ተሰጥተዋል፡፡ ከስድስትና ሰባት አመት<br />

በፊት ደንብር አካባቢ የነበረው የኢትዮጵያ<br />

ሰራዊት ወደኋላ አፈግፍጎ አርሶ አደሮቹ<br />

ከሱዳን የጸጥታ ሀይሎች ጋር ፊት ለፊት<br />

እንዲጋፈጡ ተፈርዶባቸው እንደነበር<br />

በጊዜው ተዘግቧል፡፡ አሁንም ቢሆን<br />

የሱዳን እስር ቤት ውስጥ የሚማቅቁ፣<br />

ሀብትና ንብረታቸው የሚዘረፍና<br />

በርካታ ሰብዓዊ ጥሰት የሚፈጸምባቸው<br />

መኖራቸው እየተነገረ ነው፡፡ ይህን ሁሉ<br />

የሚያደርገው ከኢትዮጵያ መንግስት<br />

ይሁንታን ያገኘው የሱዳን የደህነነት<br />

ሀይል ነው፡፡ በዚህ ረገድ መንግስት<br />

የመጀመሪያውን ህዝብን ከውጭ ጥቃት<br />

የመከላከል የሉዓላዊነት መርህ አሳልፎ<br />

ሰጥቷል፡፡ የራሱ ህዝብ በውጭ ሃይል<br />

አደጋ እየደረሰበት ዝም ማለት ብቻ<br />

ሳይሆን ሱዳኖች ኢትዮጵያውያንን<br />

እንዲያስለቅቁ የፈቀደው መንግስት<br />

የመጀመሪያው የአገሪቱን ሉዓላዊነት<br />

አሳልፎ የሰጠ አካል ነው፡፡<br />

የዓለም አቀፍ ህግን የጣሰው<br />

ድብቅ ስምምነት<br />

የአንድ መንግስት ዋነኛው<br />

ተግባር አገር ውስጥ ህዝብን<br />

የሚያስተዳድርበትን፣ አገሪቱ ከውጭ<br />

አካላት ጋር የምትገናኝበትንና ጥቅሟን<br />

የምታስከብርበት ህግና አግባብ የአገሪቱን<br />

ጥቅም በሚያስከብር መንገድ መቅረጽ፣<br />

ማስከበርና መተግብር ነው፡፡ ዓለም<br />

አቀፍ ህግ ከእዚህ መካከል አንዱ ነው፡<br />

፡ ኢትዮጵያ ከፈረመቻቸው ዓለም<br />

አቀፍ የድንበር ስምምነቶች መካከል<br />

ደግሞ አብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገራት ነጻ<br />

ከወጡ በኋላ የተፈራረሙት ‹‹የካይሮ<br />

ስምምነት›› በአብነት ይጠቀሳል፡፡<br />

አንድ አይነት ቋንቋ የሚናገሩ የአፍሪካ<br />

ህዝቦች ለቅኝ ገዥዎች በሚመችና<br />

ዘፈቀደ ድንበር ተከፋፍለው ተገዝተዋል፡<br />

፡ አንዳንዶቹ ደግሞ ግልጽ ከሆነው<br />

ይልቅ በየጊዜው የሚቀየሩ የቅኝ ገዥ<br />

አስተዳዳሪዎች፣ እርስ በእርሳቸው<br />

በሚወዳደሩ የምዕራባዊያን አገራት<br />

እንዲሁም የአገር ውስጥ ወኪሎች<br />

(ባንዳዎች) ግራ የሚያጋባ ድንበር መሰረት<br />

ተከፋፋለው ኖረዋል፡፡ ለአብነት ያህል<br />

በሁለትና ሶስት የቅኝ ገዥዎች፣ እነዚህ<br />

አገራትን ወክለው፣ አሊያም ለእነዚህ<br />

አገራት ወኪል ሆነው ለየራሳቸው ጥቅም<br />

ከተሸነሸኑት በርካታ ወሰኖች መካከል<br />

አንዲት አገር በስተመጨረሻ ነጻ ስትወጣ<br />

የያዘችውን ይዛ እንድትቀጥል ነው<br />

የተደረገው፡፡ ይህ ግልጽነት የጎደለው<br />

ድንበር፣ የድንበር ክለላም ለግጭት<br />

መሰረት እንደሚሆን የታመነበት የአፍሪካ<br />

አገራት ነጻ ከመውጣታቸው አስቀድሞ<br />

ነው፡፡ በተለይም የተለያዩ አካላትና<br />

ግለሰቦች የየራሳቸውንና ለራሳቸው<br />

የሚጠቅመውን ድንበር የሚያቀርቡ<br />

መሆኑ ግጭቱን የባሰ እንደሚያደርገው<br />

ታምኖበታል፡፡ ይህም በመሆኑ የአፍሪካ<br />

ህብረት ቻርተር ከጸደቀ ከአመት በኋላ<br />

ይህን ችግር ለመቅረፍ የአፍሪካ አንድነት<br />

ድርጅት በካይሮ ተገኝቶ ቀኝ ገዥዎች<br />

ተክለውት የሄዱትን የድንበር ችግር<br />

ይፈታል ያለውን ስምምነት አጽድቋል፡፡<br />

የዚህ ስምምነት አላማ በቅኝ ግዛት ወቅት<br />

በቅኝ ገዥዎች፣ በግለሰቦች፣ በአገርም<br />

ሆነ በውጭ ቡድኖች አማካኝነት በዘፈቀደ<br />

የተከለሉ ድንበሮች የሚያመጡትን ችግር<br />

ለመቅረፍ የአፍሪካ አገራት ነጻ ሲወጡ<br />

የያዙትን ወሰን ይዘው እንዲቀጥሉ<br />

ማድረግ ነው፡፡ ሌሎች አገራትም<br />

የጎረቤቶቻቸውንም ሆነ የሌሎች ነጻ<br />

ሲወጡ የነበራቸውን ድንበር ማክበር<br />

እንዳለባቸው የሚያሳይ ነው፡፡ ይህ ህግ<br />

እ.ኤ.አ በ1963 በጸደቀው የአፍሪካ ህብረት<br />

ቻርተር ላይም በግልጽ ተቀምጧል፡<br />

፡ የ1963 ቻርተር እንዲሁም በሀምሌ<br />

1964 የተፈረመው ስምምነት “to respect<br />

the frontiers existing on their<br />

achievement of independence”<br />

ወይንም አገራት ነጻ ሲወጡ የነበራቸውን<br />

ወሰን/ድንበር የማክበር ግዴታን አጽንኦት<br />

ሰጥቶ አስቀምጧል፡፡ ይህ ችግር አሁንም<br />

ድረስ ባለመቀረፉ የአሁኑ አዲሱ<br />

የአፍሪካ ህብረት ቻርተርም በአንቀጽ<br />

4(b) ‹‹respect of borders existing<br />

on achievement of independence››<br />

ወይንም አገራት ነጻነት ሲያገኙ<br />

የነበራቸውን ድንበር ማክበርን የሚለውን<br />

መርህ በቀዳሚነት አስቀምጦታል፡፡<br />

የአፍሪካ ህብረት ሚኒስትሮች እ.ኤ.አ<br />

በየካቲት 25 2010 አዲስ አበባ ላይ<br />

‹‹DECLARATION ON THE AF-<br />

RICAN UNION BORDER PRO-<br />

GRAMME AND THE MODALI-<br />

TIES FOR THE PURSUIT AND<br />

ACCELERATION OF ITS IMPLE-<br />

MENTATION›› የሚል ሰነድ በህብረቱ<br />

ስም ተፈራርመዋል፡፡ ሰነዱ ግጭትን<br />

ለመከላከል፣ ህብረትን ለማጠናከር ያለመ<br />

ነው፡፡ ይህ ስምምነት መሰረቱ ያደረገው<br />

‹‹አገራት ነጻ ሲወጡ የያዙትን ድንበር<br />

ይዘው መቀጠል፣ የሌሎቹንም ማክበር<br />

ይኖርባቸዋል›› ከሚለው የካይሮው<br />

ስምምነትን የመነጨ ነው፡፡<br />

በአሁኑ ወቅት ለሱዳን ይሰጣል የተባለው<br />

መሬትን ስምምነት እ.ኤ.አ በ1902 እና<br />

በ1907 እንደተደረገ ታሪክ ያስረዳል፡<br />

፡ ሆኖም መንግስታቱ መካከል ይህ<br />

በእውን ሳይተገበር መቅረት ብቻ ሳይሆን<br />

ሻለቃ ጉይን የተባለው የእንግሊዝ አዛዥ<br />

መንግስታቱ ከተስማሙበትም ውጭ<br />

ብቻውን ያሰመረው መሆኑ ይታወቃል፡<br />

፡ ያም ሆኖ ሱዳን ነጻ ስትወጣ የያዘችው<br />

ድንበር የዚህን የሻለቃ ድንበር አይደለም፡<br />

፡ የአፍሪካ አንድነት ቻርተር፣ የካይሮ<br />

ስምምነት፣ የአፍሪካ ህብረት ቻርተርና<br />

እዚህን መርሆች መሰረት አድርገው<br />

በየጊዜው በድንበር ጉዳይ የሚወጡ ህጎች<br />

እያሉ በአሁኑ ወቅት እነዚህን ህጎች<br />

በሚጻረር መልኩ ሱዳን ነጻ ስትወጣ<br />

ከነበራት ድንበር ወደ ኢትዮጵያ እስከ<br />

40 ኪሎ ሜትር የሚገባ መሬት ሊሰጣት<br />

መሆኑ ይፋ ሆኗል፡፡<br />

የካይሮን ስምምነት፣ የአፍሪካ ህብረት<br />

ቻርተርና ሌሎችንም ከሁለቱ የሚመነጩ<br />

የድንበር ህጎች በሚጻረር መልኩ<br />

የሚተገበር ተግባር ይበልጡን አስገራሚ<br />

የአንድ መንግስት ዋነኛው ተግባር አገር ውስጥ ህዝብን የሚያስተዳድርበትን፣ አገሪቱ ከውጭ<br />

አካላት ጋር የምትገናኝበትንና ጥቅሟን የምታስከብርበት ህግና አግባብ የአገሪቱን ጥቅም<br />

በሚያስከብር መንገድ መቅረጽ፣ ማስከበርና መተግብር ነው፡፡ ዓለም አቀፍ ህግ ከእዚህ መካከል<br />

አንዱ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ከፈረመቻቸው ዓለም አቀፍ የድንበር ስምምነቶች መካከል ደግሞ<br />

አብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገራት ነጻ ከወጡ በኋላ የተፈራረሙት ‹‹የካይሮ ስምምነት›› በአብነት<br />

ይጠቀሳል፡፡<br />

የሚሆነው ሌሎቹ ቅኝ ግዛት ስር<br />

በነበሩበት ወቅት የራሷ ወሰን የነበራት<br />

የህብረቱ መስራችና መቀመጫ ኢትዮጵያ<br />

ላይ መሆኑ ነው፡፡ ህግጋቱን ጥሶ<br />

የአገሪቱን መሬት ከድሮው እንደለመደው<br />

መሬትን ብቻ ሳይሆን ‹‹ሉዓላዊነትን››<br />

ለሌሎች በገጸ በረከትነት የሚያስረክበው<br />

ደግሞ ኢትዮጵያን እወክላለሁ በሚለው<br />

‹‹መንግስት›› መሆኑ ኢህአዴግ<br />

ከሉዓላዊነት ጋር ምን ያህል እንደተጣላ<br />

የሚያሳይ ነው፡፡<br />

ሱዳኖችን ጨምሮ መሬቱ ለሱዳን<br />

መሰጠት እንዳለበት ለሚያምነው<br />

ኢህአዴግ ዋነኛው መከራከሪያ<br />

ብሪታኒያና አጼ ምኒልክ በድንበሩ ጉዳይ<br />

ቢዋዋሉም መሬቱ በኢትዮጵያ ቁጥጥር<br />

ስር መቆየቱን ነው የሚያነሱት፡፡ በጉዳዩ<br />

ጥናት ካደረጉት አምስት ኢትዮጵያውያን<br />

መካከል በህይወት የሚገኙት ፕ/ር<br />

መስፍን ወ/ማሪያም ጥር 17/ 2006<br />

ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ ተገኝተው<br />

እንዳስረዱት፤ አሁን በኢትዮጵያና ሱዳን<br />

መካከል አጨቃጫቂ ነው የሚባለውን<br />

ድንበር የከለለው ሻለቃ ጉይን የተባለው<br />

የእንግሊዝ አዛዥ ብቻውን ሆኖ ነበር፡፡<br />

በወቅቱ ኢትዮጵያ ወኪል አልነበራትምና<br />

ስምምነቱ አይገዛትም ማለት ነው፡<br />

፡ ሻለቃው እንዳፈተተው በሚከልልበት<br />

ወቅትም ቢሆን የድንበር ለውጥ<br />

በመደረጉ ድንበሩ ወደ ሱዳን ገባ<br />

ብሎ እንደሚከለል ደብዳቤ ደርሶታል፡<br />

፡ ሆኖም ሻለቃው ከብሪታኒያ ክልል<br />

ካለችው ውጭ ወደ ኢትዮጵያ መሬት<br />

ገብቶ የራሱን ዘፈቀደ ድንበር አስቀምጦ<br />

አልፏል፡፡ ይህ ሆኖ እያለ ኢትዮጵያን<br />

ወክያለሁ የሚለው ኢህአዴግ በዚህ<br />

በተዛባ ህግ፣ አንድ የቅኝ ገዥ መኮነን<br />

ያሰመረውን የተሳሳተና ያልተገባ ድንበር<br />

የሚቀበል ከሆነ ምን አልባትም ለራሱ<br />

ጥቅም ሲል ብቻ ተጠቀመበት እንጂ<br />

ለስልጣን የማይጠቅመው ቢሆን የአባይን<br />

ስምምነትንም መቀበሉ የማይቀር<br />

እንደነበር ነው የሚያሳየው፡፡<br />

አሁን ለሱዳን ይሰጣል የተባለው መሬት<br />

የኢትዮጵያ አካል በነበረበት ወቅት<br />

ሱዳን ገና ነጻ አልወጣችም፡፡ በመሆኑም<br />

ከአፍሪካ አንድነት ቻርተር ጀምሮ፣<br />

በካይሮ ስምምነት፣ በአዲሱ የአፍሪካ<br />

ህብረት ቻርተርና በየጊዜው ድንበርን<br />

በተመለከተ በሚወጡት ህጎች መሰረት<br />

ድንበሩ የኢትዮጵያ እንጂ የሱዳን ሊሆን<br />

አይችልም፡፡ ከመቶ አመት በፊት በአንድ<br />

የቅኝ ገዥ መኮነን የተደረገን የመከለል<br />

ሙከራ እውነት አድርጎ ለሌላኛው አገር<br />

አሳልፎ መስጠት ከአንድ አገር መንግስት<br />

የሚጠበቅ አይደለም፡፡ ኢህአዴግ<br />

ኢትዮጵያ ውስጥ ስልጣን የያዘበት<br />

ጊዜ ዓለም ከጦርነት ይልቅ ወደ ሰላም<br />

የመጣችበትና በህግ የምትመራበት ነው፡<br />

፡ በዚህ ዘመን የአንድ አገርን ሉዓላዊነት<br />

ለማስጠበቅ ፈተናዎች የማይበዙበት<br />

ዘመን ነው፡፡ ከዚህ ይልቅ በርካታ<br />

የኢትዮጵያ መንግስታት የአገሪቱን<br />

ሉዓላዊነት የሚፈታተኑ አጋጣሚዎችን<br />

በጽናት አልፈዋል፡፡<br />

ኢህአዴግ በጣሊያን ወረራም ሆነ በሌሎች<br />

የአገሪቱ ሉዓላዊነት ጥያቄ ውስጥ<br />

በገባበት ወቅት ገዥ ቢሆን ኖሮ ራሱ<br />

ምንዳ እስካገኘ ድረስ ሙሉ በሙሉም<br />

ይሁን የውጭ ሀይሎች በሚፈልጉት<br />

መልኩ አገሪቱን አሳልፎ ይሰጥ እንደነበር<br />

ለመገመት አይከብድም፡፡ በእርግጥ<br />

አሁንም ቢሆን ሉዓላዊነትን አሳልፎ<br />

መስጠቱ ለሱዳን በሚሰጠው መሬት<br />

ይቆማል ተብሎ የሚገመት አይደለም፡<br />

፡ ፕ/ር መስፍን ውይይቱን በመሩበት<br />

ወቅት ለህዝብ መልሰው የጠየቁት<br />

ጥያቄም ‹‹ኢህአዴግ በቀጣይነት አሳልፎ<br />

የሚሰጠው የትኛውን መሬት ይሆን?››<br />

የሚል ነበር፡፡ ከተሳታፊዎችም ‹‹አዲስ<br />

አበባንስ መቼ ያስከልሏት ይሆን?››<br />

የሚል ጥያቄ ተነስቷል፡፡ ይህ እንግዲህ<br />

ኢህአዴግ ምን ያህል ለሉዓላዊነት<br />

የማይጨነቅ መሆኑና በጉዳዩ ታማኝነቱን<br />

ማጣቱን በግልጽ የሚያሳይ ሀቅ ነው፡፡

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!