Neger Ethiopia Issue 2
Neger Ethiopia Issue 2
Neger Ethiopia Issue 2
You also want an ePaper? Increase the reach of your titles
YUMPU automatically turns print PDFs into web optimized ePapers that Google loves.
5 የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2 ነገረ-ኢትዮጵያ<br />
ፖለቲካ<br />
‹‹መንግስት›› አሳልፎ የሰጠው<br />
ሉዓላዊነት<br />
ጌታቸው ሺፈራው<br />
ለአንድ አገር ሉዓላዊነት ቁልፍ<br />
ከሚባሉት ጉዳዮች መካከል<br />
ወሰን ዋነኛው መመዘኛ ነው፡፡<br />
የወሰን/የድንበር ጉዳይ ድንበር<br />
ብቻ ሳይሆን ከድንበሩ ጋር<br />
ያለውን ታሪካዊ ሂደትም ይጨምራል፡<br />
፡ ለአንድ መንግስትና ትውልድ የቀደሙ<br />
አባቶች ያኖሩትን ድንበር የመቆጣጠርና<br />
መጠበቅ ታሪካዊ ግዴታቸው ነው፡፡<br />
የውጭ አሊያም ሌላ ሀይል የኖረውን<br />
የአገሪቱን ድንበር የሚደፍር አሊያም<br />
የሚያስቀይር ከሆነ የአገሪቱ ሉዓላዊነት<br />
አደጋ ውስጥ ወድቋል ማለት ነው፡<br />
፡ የአንዲት አገርና ህዝቧ ያለ ድንበር/<br />
ወሰን ሊኖር አይችልም፡፡ አገሪቱ ብቻዋን<br />
መሆን እንደማትችል ሁሉ ክብሯን፣<br />
ታሪኳን፣ የዕለት ተዕለት እንቅስቀቃሴዋ፣<br />
ደህንነቷ ላይ ድንበር ከፍተኛ አስተዋጽኦ<br />
ይኖረዋል፡፡<br />
የወሰን አለመከበር ወይንም ሌላ ችግር<br />
እኒህን ሁሉ ጉዳዮች የሚያዛባ ይሆናል፡፡<br />
ለዚህም ነው ሌሎች አገራት ከሚሰጡት<br />
እውቅና ይልቅ ድንበር የአንድ አገር<br />
በተጨባጭ /የሚታይ/ ሉዓላዊነት<br />
መገለጫ ነው የሚባለው፡፡ ድንበር<br />
ዋነኛው የሉዓላዊነት አካል ስለመሆኑ<br />
የኢትዮጵያ ህዝብ ሲበድሉት የኖሩት<br />
አገዛዞች ‹‹አገርህ ተደፈረች›› ሲሉት<br />
ለጊዜውም ቢሆን ልዩነቱን ወደጎን ትቶ<br />
ዳር ድንበር ሊያስከበር ሲተም መኖሩ<br />
ትልቅ ማስረጃ ነው፡፡ በተቃራኒው<br />
መንግስታቱ ለሉዓላዊነት የህዝብን ያህል<br />
ቁርጠኛ ሆነው አልተገኙም፡፡ በዚህ በኩል<br />
ደግሞ ኢህአዴግ ሉዓላዊነትን አሳልፎ<br />
በመስጠት ወደር አልረገኘለትም፡፡<br />
አንድ አገር ሉዓላዊ የምትሆነው አሊያም<br />
ይህ ክብር የሚቀጥለው ድንበሯን፣<br />
ታሪኳንና የህዝብን ጥቅም አስጠብቆ<br />
የሚኖር አገር ወዳድ መንግስት ሲኖራት<br />
ብቻ ነው፡፡ በዚህ በኩል የአሁኗ<br />
ኢትዮጵያ አልታደለችም፡፡ የአገርን<br />
ጥቅም፣ በደምና በአጥንት የተገነባን<br />
ታሪክና ድንበር አሳልፎ የሚሰጥ አካል<br />
ባለበት የአገሪቱ ሉዓላዊነት አደጋ<br />
ውስጥ ይገባል፡፡ ሉዓላዊነት የአንዲት<br />
አገር ከሌሎች አገራት ጋር ሲነጻጸር<br />
ያላት እኩል ክብር፣ ህጋዊ ሰውነት<br />
እንደመሆኑ መንግስት የሚባለው አካል<br />
ወሰኗን ባልተገባ መንገድ ለሌሎች<br />
አሳልፎ የሚሰጥ ወይንም የሚወሰድበት<br />
ከሆነ ሉዓላዊነቷ ተደፍሯል ማለት ነው፡<br />
፡ ህወሓት የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት<br />
ማስደፈር የጀመረው ገና በርሃ በነበረበት<br />
ወቅት ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት ከማንም<br />
ቀድሞ በየጊዜው ሰራዊት ወደ ሶማሊያ<br />
የሚልከው ህወሓት ያኔ ገና በርሃ እያለ<br />
ተስፋፊውን የሶማሊያ መንግስት እስከ<br />
ድሬዳዋ ድረስ መንገድ መምራቱን<br />
እንደ አስግደ ያሉት የቀድሞው የቡድኑ<br />
አባላት እማኝነታቸውን በይቅርታ መልክ<br />
ገልጸዋል፡፡<br />
ህወሓት እንደ ፖለቲካ ቡድን<br />
ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ኤርትራ<br />
የኢትዮጵያ ቅኝ ግዛት እንደሆነችና ነጻ<br />
መውጣት እንዳለባት ሲሰብክ ኖራል፡፡<br />
ህወሓት ‹‹አሸባሪ›› በነበረበት በዛ ወቅት<br />
የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ<br />
መለስ ዜናዊ ስለ ኤርትራ ጉዳይ ሁለት<br />
መጽኃፍትን ጽፈዋል፡፡ ‹‹የኤርትራ<br />
ህዝብ ትግል ከየት ወደየት›› በተሰኘው<br />
መጽኃፋቸውም ኤርትራን ከኢትዮጵያ<br />
ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌላት<br />
ነጻ አገር መሆኗን አውጀዋል፡፡ አቶ<br />
መለስና ህወሓት ይህን በሚሉበት ወቅት<br />
በርካታ የኤርትራ ተወላጆች በአገሪቱ<br />
አሁን ህወሓት ለሌሎች የግንባሩ አባል<br />
ፓርቲዎች አሳልፎ የማይሰጣቸው ቁልፍ<br />
ስልጣን እንደነበራቸው አይዘነጋም፡፡<br />
ገና ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ኤርትራን<br />
ከኢትዮጵያ መነጠልን አላማው አድርጎ<br />
የተነሳው ህወሓት ደርግን አሸንፎ ቤተ-<br />
መንግስት ሲገባ የወሰደው እርምጃ<br />
የዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ ኤርትራን<br />
እውቅና እንዲሰጥ ማድረግ ነበር፡፡ ይህም<br />
ኢህአዴግን የዋናዋ አገር ገዥ ሆኖ<br />
የአገሪቱ ክፍልን በፈቃደኝነት ያስገነጠለ<br />
(ሉዓላዊነቷን አሳልፎ የሰጠ) ብቸኛው<br />
ፓርቲ ሳያደርገው አይቀርም፡፡ ኤርትራን<br />
በገዛ እጁ ያስገነጠለው ህወሓት/ኢህአዴግ<br />
ከሻዕቢያ ጋር የነበረው ፍቅር ሲያልቅ<br />
የአገሩ ሉዓላዊነት ተላልፎ የተሰጠበት<br />
የኢትዮጵያ ህዝብ በደሉን ለጊዜው ወደጎን<br />
ትቶ ዳር ድንበሩን ለማስከበር ሲነሳ አገዛዙ<br />
የማይጨነቅለትን ሉዓላዊነት ለማስከበር<br />
እንደማይደክመው አሳይቷል፡፡ ጦርነቱ<br />
በኢትዮጵያ ህዝብ አሸናፊነት ከተጠናቀቀ<br />
በኋላም ቢሆን ህወሓት የለመደውን<br />
ሉዓላዊነት አሳልፎ የመስጠት ልክፍት<br />
ደግሞታል፡፡ ይህ አልበቃው ሲልም<br />
ህዝብ ከእሱ በላይ ለአገሪቱ ሉዓላዊነት<br />
እንደሚጨነቅ ጠንቅቆ ስለሚያውቅም<br />
‹‹ባድመን አግኝተናል!›› በሚል ህዝብን<br />
አሞኝቷል፡፡ ይህም ህወሓት/ኢህአዴግ<br />
ከሉዓላዊነት ጋር ያላውን ተቃርኖ<br />
በጉልህ የሚያሳይ ነው፡፡<br />
የኢህአዴግና የሉዓላዊነት ተቃርኖ<br />
አሁንም ቀጥሏል፡፡ ከስድስትና ሰባት<br />
አመታት ጀምሮ የኢትዮጵያን መሬት<br />
አሳልፎ ለሱዳን ለመስጠት በድብቅ<br />
እየተዋዋለ መሆኑ ሲነገር ቆይቷል፡<br />
፡ በቅርቡ ደግሞ ‹‹ሱዳን ትሪብዩን››<br />
የተባለው የሱዳን ጋዜጣ ‹‹ለም መሬታችን<br />
አገኘን!›› የሚል ዜና ማውጣቱን ተከትሎ<br />
ኢህአዴግ መሬቱን ለመስረከብ መቃረቡን<br />
አመላክቷል፡፡ የአንድ አገር መንግስት<br />
የአገሪቱን ድንበር ማስጠበቅና ማስከበር፣<br />
የዜጎቹን ጥቅም ማስከበር ሲኖርበት<br />
ለራሱ ግላዊ ጥቅም፣ ህጋዊ መሰረት<br />
በሌለው መንገድ የአገሩን ወሰንና ድንበር<br />
አሳልፎ የሚሰጥ ከሆነ በአገር ውስጥ<br />
የሌሎች ወኪል ሆኖ የአገርን ሉዓላዊነት<br />
እየደፈረ ከመሆን ውጭ ሌላ ሊባልለት<br />
አይችልም፡፡<br />
ይህ የ‹‹መንግስት›› ተግባር ልክ ቅኝ<br />
ገዥዎቹ የራሳቸው ታማኞች (ባንዳዎች)<br />
እንደነበሯቸው ማለት ነው፡፡ አንዲት<br />
በመንግስት ስር የምትገኝ አገር ሉዓላዊ<br />
የምትባለው ይህ መንግስት የአገሪቱን<br />
ወሰንና ሌሎች ጥቅሟን በህጋዊ መንገድ<br />
መቆጣጠርና ማስተዳደር ከቻለና<br />
በጥቅምም ይሁን በአቅም ማነስ ለውጭ<br />
ሀይል የአገሪቱን ጥቅም፣ ክብር፣ ወሰን<br />
አሳልፎ የማይሰጥ ከሆነ ብቻ ነው፡፡<br />
አገሪቱን ሁለመናው ነገር ተቆጣጥሮና<br />
እያስተዳደረም ቢሆን በውጭ ሀይል<br />
ተጽዕኖ ውሳኔ የሚያስተላልፍ፣<br />
የአገሪቱን ጥቅም አሳልፎ የሚሰጥ<br />
ከሆነ የአገሪቱ ሉዓላዊነቷ ተደፍሯል፡<br />
፡ የኢትዮጵያን መሬት ለሱዳን አሳልፎ<br />
ለመስጠት እየተደራደረ ያለው ኢህአዴግ<br />
የአገርን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ፣ ለህዝብ<br />
ጥቅም በመቆም ከሚታወቅ ‹‹መንግስት››<br />
ከተባለ አካል ይልቅ በሚገዛት አገር<br />
ውስጥ ለሱዳን ጥቅም የቆመ መሆኑን<br />
አሳይቷል፡፡<br />
አንድ አገር ሉዓላዊ ነው የሚባለው<br />
የአገሪቱን ዜጎች ከውጭ ጥቃት<br />
የሚከላከል አካል (መንግስት) ካለ ብቻ<br />
ቢሆንም የሱዳን ኢትዮጵያ ድንበር<br />
ችግር ከተከሰተ በኋላ በመተማና<br />
አካባቢው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን<br />
ለሱዳን የደህንነት ኃይሎች ተላልፈው<br />
ተሰጥተዋል፡፡ ከስድስትና ሰባት አመት<br />
በፊት ደንብር አካባቢ የነበረው የኢትዮጵያ<br />
ሰራዊት ወደኋላ አፈግፍጎ አርሶ አደሮቹ<br />
ከሱዳን የጸጥታ ሀይሎች ጋር ፊት ለፊት<br />
እንዲጋፈጡ ተፈርዶባቸው እንደነበር<br />
በጊዜው ተዘግቧል፡፡ አሁንም ቢሆን<br />
የሱዳን እስር ቤት ውስጥ የሚማቅቁ፣<br />
ሀብትና ንብረታቸው የሚዘረፍና<br />
በርካታ ሰብዓዊ ጥሰት የሚፈጸምባቸው<br />
መኖራቸው እየተነገረ ነው፡፡ ይህን ሁሉ<br />
የሚያደርገው ከኢትዮጵያ መንግስት<br />
ይሁንታን ያገኘው የሱዳን የደህነነት<br />
ሀይል ነው፡፡ በዚህ ረገድ መንግስት<br />
የመጀመሪያውን ህዝብን ከውጭ ጥቃት<br />
የመከላከል የሉዓላዊነት መርህ አሳልፎ<br />
ሰጥቷል፡፡ የራሱ ህዝብ በውጭ ሃይል<br />
አደጋ እየደረሰበት ዝም ማለት ብቻ<br />
ሳይሆን ሱዳኖች ኢትዮጵያውያንን<br />
እንዲያስለቅቁ የፈቀደው መንግስት<br />
የመጀመሪያው የአገሪቱን ሉዓላዊነት<br />
አሳልፎ የሰጠ አካል ነው፡፡<br />
የዓለም አቀፍ ህግን የጣሰው<br />
ድብቅ ስምምነት<br />
የአንድ መንግስት ዋነኛው<br />
ተግባር አገር ውስጥ ህዝብን<br />
የሚያስተዳድርበትን፣ አገሪቱ ከውጭ<br />
አካላት ጋር የምትገናኝበትንና ጥቅሟን<br />
የምታስከብርበት ህግና አግባብ የአገሪቱን<br />
ጥቅም በሚያስከብር መንገድ መቅረጽ፣<br />
ማስከበርና መተግብር ነው፡፡ ዓለም<br />
አቀፍ ህግ ከእዚህ መካከል አንዱ ነው፡<br />
፡ ኢትዮጵያ ከፈረመቻቸው ዓለም<br />
አቀፍ የድንበር ስምምነቶች መካከል<br />
ደግሞ አብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገራት ነጻ<br />
ከወጡ በኋላ የተፈራረሙት ‹‹የካይሮ<br />
ስምምነት›› በአብነት ይጠቀሳል፡፡<br />
አንድ አይነት ቋንቋ የሚናገሩ የአፍሪካ<br />
ህዝቦች ለቅኝ ገዥዎች በሚመችና<br />
ዘፈቀደ ድንበር ተከፋፍለው ተገዝተዋል፡<br />
፡ አንዳንዶቹ ደግሞ ግልጽ ከሆነው<br />
ይልቅ በየጊዜው የሚቀየሩ የቅኝ ገዥ<br />
አስተዳዳሪዎች፣ እርስ በእርሳቸው<br />
በሚወዳደሩ የምዕራባዊያን አገራት<br />
እንዲሁም የአገር ውስጥ ወኪሎች<br />
(ባንዳዎች) ግራ የሚያጋባ ድንበር መሰረት<br />
ተከፋፋለው ኖረዋል፡፡ ለአብነት ያህል<br />
በሁለትና ሶስት የቅኝ ገዥዎች፣ እነዚህ<br />
አገራትን ወክለው፣ አሊያም ለእነዚህ<br />
አገራት ወኪል ሆነው ለየራሳቸው ጥቅም<br />
ከተሸነሸኑት በርካታ ወሰኖች መካከል<br />
አንዲት አገር በስተመጨረሻ ነጻ ስትወጣ<br />
የያዘችውን ይዛ እንድትቀጥል ነው<br />
የተደረገው፡፡ ይህ ግልጽነት የጎደለው<br />
ድንበር፣ የድንበር ክለላም ለግጭት<br />
መሰረት እንደሚሆን የታመነበት የአፍሪካ<br />
አገራት ነጻ ከመውጣታቸው አስቀድሞ<br />
ነው፡፡ በተለይም የተለያዩ አካላትና<br />
ግለሰቦች የየራሳቸውንና ለራሳቸው<br />
የሚጠቅመውን ድንበር የሚያቀርቡ<br />
መሆኑ ግጭቱን የባሰ እንደሚያደርገው<br />
ታምኖበታል፡፡ ይህም በመሆኑ የአፍሪካ<br />
ህብረት ቻርተር ከጸደቀ ከአመት በኋላ<br />
ይህን ችግር ለመቅረፍ የአፍሪካ አንድነት<br />
ድርጅት በካይሮ ተገኝቶ ቀኝ ገዥዎች<br />
ተክለውት የሄዱትን የድንበር ችግር<br />
ይፈታል ያለውን ስምምነት አጽድቋል፡፡<br />
የዚህ ስምምነት አላማ በቅኝ ግዛት ወቅት<br />
በቅኝ ገዥዎች፣ በግለሰቦች፣ በአገርም<br />
ሆነ በውጭ ቡድኖች አማካኝነት በዘፈቀደ<br />
የተከለሉ ድንበሮች የሚያመጡትን ችግር<br />
ለመቅረፍ የአፍሪካ አገራት ነጻ ሲወጡ<br />
የያዙትን ወሰን ይዘው እንዲቀጥሉ<br />
ማድረግ ነው፡፡ ሌሎች አገራትም<br />
የጎረቤቶቻቸውንም ሆነ የሌሎች ነጻ<br />
ሲወጡ የነበራቸውን ድንበር ማክበር<br />
እንዳለባቸው የሚያሳይ ነው፡፡ ይህ ህግ<br />
እ.ኤ.አ በ1963 በጸደቀው የአፍሪካ ህብረት<br />
ቻርተር ላይም በግልጽ ተቀምጧል፡<br />
፡ የ1963 ቻርተር እንዲሁም በሀምሌ<br />
1964 የተፈረመው ስምምነት “to respect<br />
the frontiers existing on their<br />
achievement of independence”<br />
ወይንም አገራት ነጻ ሲወጡ የነበራቸውን<br />
ወሰን/ድንበር የማክበር ግዴታን አጽንኦት<br />
ሰጥቶ አስቀምጧል፡፡ ይህ ችግር አሁንም<br />
ድረስ ባለመቀረፉ የአሁኑ አዲሱ<br />
የአፍሪካ ህብረት ቻርተርም በአንቀጽ<br />
4(b) ‹‹respect of borders existing<br />
on achievement of independence››<br />
ወይንም አገራት ነጻነት ሲያገኙ<br />
የነበራቸውን ድንበር ማክበርን የሚለውን<br />
መርህ በቀዳሚነት አስቀምጦታል፡፡<br />
የአፍሪካ ህብረት ሚኒስትሮች እ.ኤ.አ<br />
በየካቲት 25 2010 አዲስ አበባ ላይ<br />
‹‹DECLARATION ON THE AF-<br />
RICAN UNION BORDER PRO-<br />
GRAMME AND THE MODALI-<br />
TIES FOR THE PURSUIT AND<br />
ACCELERATION OF ITS IMPLE-<br />
MENTATION›› የሚል ሰነድ በህብረቱ<br />
ስም ተፈራርመዋል፡፡ ሰነዱ ግጭትን<br />
ለመከላከል፣ ህብረትን ለማጠናከር ያለመ<br />
ነው፡፡ ይህ ስምምነት መሰረቱ ያደረገው<br />
‹‹አገራት ነጻ ሲወጡ የያዙትን ድንበር<br />
ይዘው መቀጠል፣ የሌሎቹንም ማክበር<br />
ይኖርባቸዋል›› ከሚለው የካይሮው<br />
ስምምነትን የመነጨ ነው፡፡<br />
በአሁኑ ወቅት ለሱዳን ይሰጣል የተባለው<br />
መሬትን ስምምነት እ.ኤ.አ በ1902 እና<br />
በ1907 እንደተደረገ ታሪክ ያስረዳል፡<br />
፡ ሆኖም መንግስታቱ መካከል ይህ<br />
በእውን ሳይተገበር መቅረት ብቻ ሳይሆን<br />
ሻለቃ ጉይን የተባለው የእንግሊዝ አዛዥ<br />
መንግስታቱ ከተስማሙበትም ውጭ<br />
ብቻውን ያሰመረው መሆኑ ይታወቃል፡<br />
፡ ያም ሆኖ ሱዳን ነጻ ስትወጣ የያዘችው<br />
ድንበር የዚህን የሻለቃ ድንበር አይደለም፡<br />
፡ የአፍሪካ አንድነት ቻርተር፣ የካይሮ<br />
ስምምነት፣ የአፍሪካ ህብረት ቻርተርና<br />
እዚህን መርሆች መሰረት አድርገው<br />
በየጊዜው በድንበር ጉዳይ የሚወጡ ህጎች<br />
እያሉ በአሁኑ ወቅት እነዚህን ህጎች<br />
በሚጻረር መልኩ ሱዳን ነጻ ስትወጣ<br />
ከነበራት ድንበር ወደ ኢትዮጵያ እስከ<br />
40 ኪሎ ሜትር የሚገባ መሬት ሊሰጣት<br />
መሆኑ ይፋ ሆኗል፡፡<br />
የካይሮን ስምምነት፣ የአፍሪካ ህብረት<br />
ቻርተርና ሌሎችንም ከሁለቱ የሚመነጩ<br />
የድንበር ህጎች በሚጻረር መልኩ<br />
የሚተገበር ተግባር ይበልጡን አስገራሚ<br />
የአንድ መንግስት ዋነኛው ተግባር አገር ውስጥ ህዝብን የሚያስተዳድርበትን፣ አገሪቱ ከውጭ<br />
አካላት ጋር የምትገናኝበትንና ጥቅሟን የምታስከብርበት ህግና አግባብ የአገሪቱን ጥቅም<br />
በሚያስከብር መንገድ መቅረጽ፣ ማስከበርና መተግብር ነው፡፡ ዓለም አቀፍ ህግ ከእዚህ መካከል<br />
አንዱ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ከፈረመቻቸው ዓለም አቀፍ የድንበር ስምምነቶች መካከል ደግሞ<br />
አብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገራት ነጻ ከወጡ በኋላ የተፈራረሙት ‹‹የካይሮ ስምምነት›› በአብነት<br />
ይጠቀሳል፡፡<br />
የሚሆነው ሌሎቹ ቅኝ ግዛት ስር<br />
በነበሩበት ወቅት የራሷ ወሰን የነበራት<br />
የህብረቱ መስራችና መቀመጫ ኢትዮጵያ<br />
ላይ መሆኑ ነው፡፡ ህግጋቱን ጥሶ<br />
የአገሪቱን መሬት ከድሮው እንደለመደው<br />
መሬትን ብቻ ሳይሆን ‹‹ሉዓላዊነትን››<br />
ለሌሎች በገጸ በረከትነት የሚያስረክበው<br />
ደግሞ ኢትዮጵያን እወክላለሁ በሚለው<br />
‹‹መንግስት›› መሆኑ ኢህአዴግ<br />
ከሉዓላዊነት ጋር ምን ያህል እንደተጣላ<br />
የሚያሳይ ነው፡፡<br />
ሱዳኖችን ጨምሮ መሬቱ ለሱዳን<br />
መሰጠት እንዳለበት ለሚያምነው<br />
ኢህአዴግ ዋነኛው መከራከሪያ<br />
ብሪታኒያና አጼ ምኒልክ በድንበሩ ጉዳይ<br />
ቢዋዋሉም መሬቱ በኢትዮጵያ ቁጥጥር<br />
ስር መቆየቱን ነው የሚያነሱት፡፡ በጉዳዩ<br />
ጥናት ካደረጉት አምስት ኢትዮጵያውያን<br />
መካከል በህይወት የሚገኙት ፕ/ር<br />
መስፍን ወ/ማሪያም ጥር 17/ 2006<br />
ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ ተገኝተው<br />
እንዳስረዱት፤ አሁን በኢትዮጵያና ሱዳን<br />
መካከል አጨቃጫቂ ነው የሚባለውን<br />
ድንበር የከለለው ሻለቃ ጉይን የተባለው<br />
የእንግሊዝ አዛዥ ብቻውን ሆኖ ነበር፡፡<br />
በወቅቱ ኢትዮጵያ ወኪል አልነበራትምና<br />
ስምምነቱ አይገዛትም ማለት ነው፡<br />
፡ ሻለቃው እንዳፈተተው በሚከልልበት<br />
ወቅትም ቢሆን የድንበር ለውጥ<br />
በመደረጉ ድንበሩ ወደ ሱዳን ገባ<br />
ብሎ እንደሚከለል ደብዳቤ ደርሶታል፡<br />
፡ ሆኖም ሻለቃው ከብሪታኒያ ክልል<br />
ካለችው ውጭ ወደ ኢትዮጵያ መሬት<br />
ገብቶ የራሱን ዘፈቀደ ድንበር አስቀምጦ<br />
አልፏል፡፡ ይህ ሆኖ እያለ ኢትዮጵያን<br />
ወክያለሁ የሚለው ኢህአዴግ በዚህ<br />
በተዛባ ህግ፣ አንድ የቅኝ ገዥ መኮነን<br />
ያሰመረውን የተሳሳተና ያልተገባ ድንበር<br />
የሚቀበል ከሆነ ምን አልባትም ለራሱ<br />
ጥቅም ሲል ብቻ ተጠቀመበት እንጂ<br />
ለስልጣን የማይጠቅመው ቢሆን የአባይን<br />
ስምምነትንም መቀበሉ የማይቀር<br />
እንደነበር ነው የሚያሳየው፡፡<br />
አሁን ለሱዳን ይሰጣል የተባለው መሬት<br />
የኢትዮጵያ አካል በነበረበት ወቅት<br />
ሱዳን ገና ነጻ አልወጣችም፡፡ በመሆኑም<br />
ከአፍሪካ አንድነት ቻርተር ጀምሮ፣<br />
በካይሮ ስምምነት፣ በአዲሱ የአፍሪካ<br />
ህብረት ቻርተርና በየጊዜው ድንበርን<br />
በተመለከተ በሚወጡት ህጎች መሰረት<br />
ድንበሩ የኢትዮጵያ እንጂ የሱዳን ሊሆን<br />
አይችልም፡፡ ከመቶ አመት በፊት በአንድ<br />
የቅኝ ገዥ መኮነን የተደረገን የመከለል<br />
ሙከራ እውነት አድርጎ ለሌላኛው አገር<br />
አሳልፎ መስጠት ከአንድ አገር መንግስት<br />
የሚጠበቅ አይደለም፡፡ ኢህአዴግ<br />
ኢትዮጵያ ውስጥ ስልጣን የያዘበት<br />
ጊዜ ዓለም ከጦርነት ይልቅ ወደ ሰላም<br />
የመጣችበትና በህግ የምትመራበት ነው፡<br />
፡ በዚህ ዘመን የአንድ አገርን ሉዓላዊነት<br />
ለማስጠበቅ ፈተናዎች የማይበዙበት<br />
ዘመን ነው፡፡ ከዚህ ይልቅ በርካታ<br />
የኢትዮጵያ መንግስታት የአገሪቱን<br />
ሉዓላዊነት የሚፈታተኑ አጋጣሚዎችን<br />
በጽናት አልፈዋል፡፡<br />
ኢህአዴግ በጣሊያን ወረራም ሆነ በሌሎች<br />
የአገሪቱ ሉዓላዊነት ጥያቄ ውስጥ<br />
በገባበት ወቅት ገዥ ቢሆን ኖሮ ራሱ<br />
ምንዳ እስካገኘ ድረስ ሙሉ በሙሉም<br />
ይሁን የውጭ ሀይሎች በሚፈልጉት<br />
መልኩ አገሪቱን አሳልፎ ይሰጥ እንደነበር<br />
ለመገመት አይከብድም፡፡ በእርግጥ<br />
አሁንም ቢሆን ሉዓላዊነትን አሳልፎ<br />
መስጠቱ ለሱዳን በሚሰጠው መሬት<br />
ይቆማል ተብሎ የሚገመት አይደለም፡<br />
፡ ፕ/ር መስፍን ውይይቱን በመሩበት<br />
ወቅት ለህዝብ መልሰው የጠየቁት<br />
ጥያቄም ‹‹ኢህአዴግ በቀጣይነት አሳልፎ<br />
የሚሰጠው የትኛውን መሬት ይሆን?››<br />
የሚል ነበር፡፡ ከተሳታፊዎችም ‹‹አዲስ<br />
አበባንስ መቼ ያስከልሏት ይሆን?››<br />
የሚል ጥያቄ ተነስቷል፡፡ ይህ እንግዲህ<br />
ኢህአዴግ ምን ያህል ለሉዓላዊነት<br />
የማይጨነቅ መሆኑና በጉዳዩ ታማኝነቱን<br />
ማጣቱን በግልጽ የሚያሳይ ሀቅ ነው፡፡