Neger Ethiopia Issue 2
Neger Ethiopia Issue 2
Neger Ethiopia Issue 2
Create successful ePaper yourself
Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.
15የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2<br />
ነገረ-ኢትዮጵያ<br />
እንደሀገር መግባባት ...<br />
ከ ገፅ 11 የዞረ<br />
የጸጥታ ሀይሉ ከህዝብ ተነጥሎ የኢህአዴግ<br />
የግል ንብረት እስኪመስል ድረስ ተለያይቷል፡<br />
፡<br />
ሌላው ደግሞ የፍትህ ተቋማት የምንላቸው<br />
ድርጅቶቻችን ናቸው፡፡ አብዛኛውን ጊዜ<br />
በሀገራችን የታዩ የፍርድ ሂደቶች የተመሩት<br />
በነጻ የዳኝነት ሂደት ሳይሆን በአለቃዎቻቸው<br />
በጎ ፈቃድ መሆኑ ጸሐይ የሞቀው ሀቅ ነው፡<br />
፡ ይህን መከራከሪያችን የሚያጠናክርልን<br />
የ1997 የቅንጅት አመራሮችና አባላት ላይ<br />
የተበየነው የእስር ፍርድ ነው፡፡ ጠቅላይ<br />
ሚንስትር መለስ ዜናዊ በፓርላማ ቀርበው<br />
እስከሞት ፍርድ ሊያስቀጣ የሚችል ወንጀል<br />
አግኝተንባቸዋል ብለው ተናግረው ነበር፡<br />
፡ ይህንን ተከትሎ ፍርድ ቤት መመላለሱ<br />
የሰለቻት ዳኛ ብርቱካን ሚዴቅሳ እንዲህ ስትል<br />
ተናግራ ነበር፡፡ “ለምን ታመላልሱናላችሁ፤<br />
መለስ ዜናዊ የሞት ፍርድ ፈርዶብን አይደል<br />
እንዴ!? ወስዳችሁ ግደሉን እንጂ፡፡” በቅርብ<br />
እነ እስክንድር ነጋን ጨምሮ በአንዱዓለም<br />
አራጌ፣ በሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ<br />
ኮሚቴወች ላይ የተወሰደው የጥፋተኝነት<br />
ውሳኔም ከቀድሞው የተለየ አይደለም፡<br />
፡ በዚህም ምክንያት በሀገራችን የፍትህ<br />
ተቋማት ላይ መግባባት ሆድና ጀርባ ሆኗል፡፡<br />
ማሳያ ሰባት፡- ዘውግ ተኮር ፌደራሊዝም<br />
የህገ መንግስቱ አንቀጽ 39 እንዲህ ይላል፤<br />
‹‹የራስን እድል በራስ መወሰን እስከ<br />
መገንጠል››፡፡ በዚህ አንቀጽ መሰረት ክልሎች<br />
እራሳቸውን በራሳቸው ያስተዳድራሉ፤<br />
ከፈለጉም መገንጠል መብታቸው ነው፡<br />
፡ በግሌ ‹እስከ መገንጠል› ብሎ መብት<br />
ምን እንደሆነ ባይገባኝም የፌደራል ስርዓት<br />
መኖሩን ግን አጥብቄ እፈልገዋለሁ፡፡ ‹እስከ<br />
መገንጠል› የሚለው ሀረግ መግባቱ ግን<br />
ላለመግባባታችን አንዱ ማሳያ ነው፡፡<br />
ማሳያ ስምንት፡- ምርጫና የምርጫ ቦርድ<br />
ለአንድ ሀገር በዴሞክራሲ መበልጸግ<br />
የምርጫ ቦርድ ገለልተኛነት ወሳኝ ሚና<br />
አለው፡፡ የምርጫ ቦርድ ሃላፊነቱን በአግባቡ<br />
ከተወጣ አጭበርባሪዎችና ኮረጆ ገልባጮች<br />
ቦታ የላቸውም፡፡ ይህን አሰራር በሀገራችን<br />
ለማስፈን ጅምሩ እንኳን የለም ለማለት<br />
ያስደፍራል፡፡ የምርጫ ቦርድ አመራሮችም<br />
ሹመታቸው በቀጥታ ከመንግስት መሆኑ<br />
ለገዥው ተባባሪነታቸው መንገድ ከፋች ነው፡<br />
፡ ምርጫ ቦርድ የገዥውን ፓርቲ የሙቀት<br />
ልክ እየለካ የሚሰራ መሆኑ የታየ እውነት<br />
ነው፡፡ በዚህ የተባባሪነት አመሉ ገዥው<br />
ኮረጆ ሲገለብጥ ምርጫ ቦርድ የምርጫ<br />
ውጤት ተቀበሉ በሚል ተቃዋሚዎችን<br />
ያባብላል፤ ካልተሳካት ደግሞ ያስፈራራል፡፡<br />
ስለሆነም ምርጫ ቦርድ ሌላኛው እንደ ሀገር<br />
ያለመግባባታችን ምክንያት ሆኖ ሊጠቀስ<br />
ይችላል፡፡<br />
በአጠቃላይ ሀገሬ ኢትዮጵያ የዚህ ክፍለ<br />
ዘመን ዳግማዊ ባቢሎን እየሆነች ነው፡<br />
፡ ይህን በቋፍ ላይ ያለ አለመግባባት በጊዜ<br />
ካልፈታን እጣ ፋንታችን እንደ ባቢሎን ህንጻ<br />
መፈራረስ ከመሆን አያልፍም፡፡ አምላክ<br />
አያድርገው እላለሁ!<br />
እውነትና ህዝብ ያሸንፋል! ኢትዮጵያ<br />
ለዘላለም በክብር ትኑር!!!<br />
ኢህአዴግ ተሸንፏል...<br />
ከ ገፅ 16 የዞረ<br />
እንደተለመደው ወዲያውኑ ኢንተርኔትና<br />
ስልክ እንዲጠፋ ተደረገ፡፡<br />
አሁን ሰላማዊ ሰልፉ እየተቃረበ እንደመሆኑ<br />
የከተማውን አስተዳደር ይበልጡን ፈርቷል፡<br />
፡ ሰልፉ እንደማይቀር ከሰማያዊ ወጣቶች<br />
ድፍረትና ቆራጥነት ተረድተዋል፡፡<br />
በመሆኑም የከተማውን ነዋሪ በመሰብሰብ<br />
ማስፈራራት ነበረባቸው፡፡ ለዚህም ሰማያዊ<br />
ፓርቲን ስም እየለጠፉ ህዝቡን ለማራቅ<br />
ከመሞከር ባለፈ ‹‹ልጆቻችን ሰላማዊ ሰልፉ<br />
ላይ ቢሳተፉ በጥይት ይመታሉ!›› ብለው<br />
እስከማስፈራራት ደርሰዋል፡፡ የተሸናፊዎቹ<br />
አቅም ይህ ነው፡፡ ሰላማዊ ሰልፉ ሊደረግ<br />
10 ደቂቃ ሲቀረው ደግሞ በየ መግቢያው<br />
የተደረደሩት ፖሊሶች ህዝብን ወደ መስቀል<br />
አደባባይ እንዳይሄድ ሲያግዱ ተስተውለዋል፡<br />
፡ በሰላማዊ ሰልፉ ወቅትም የቀበሌ ካድሬዎች<br />
ከሰልፉ በኋላ በመሆን ህዝቡን በመቅረጽ<br />
ለማስፈራራት ሞክረዋል፡፡ በእርግጥ ከዚህ<br />
አልፈው ሰላማዊ ሰልፉ ከተጠናቀቀ በኋላ<br />
እርምጃ እየወሰዱ መሆናቸውም ተሰምቷል፡<br />
፡ ሰላማዊ ሰልፉ ካበቃ በኋላ በቅርብ<br />
እርቀት ሲከታተሉ የነበሩት ካድሬዎች<br />
በሰልፉ ላይ የተሳተፉትን ወጣቶች የቀበሌ<br />
መታወቂያ ቀምተዋል፡፡ ወደ ቀበሌ ሄደው<br />
መታወቂያቸውን በተቀበሉበት ወቅትም<br />
ዳግመኛ ሰማያዊም ሆነ ሌሎች ፓርቲዎች<br />
በሚጠሩት ሰልፍ እንዳይሳተፉ ማስጠንቀቂያ<br />
ተሰጥቷቸዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ሰልፉን<br />
ያስተባበሩት የጎንደር የፓርቲው አባላትና<br />
ቤተሰቦቻቸው ላይ ደህንነቶች እየደወሉ<br />
ሲያስፈራሩዋቸው ሰንብተዋል፡፡<br />
ሰላማዊ ሰልፉ ተደርጎም ቢሆን ማዋከቡ እንደማይቆም ቀድመው የተገነዘቡት የፓርቲው<br />
አመራሮች ጎንደርን ቶሎ መልቀቅን እንዳለባቸው አምነዋል፡፡ እናም ሰላማዊ ሰልፉ<br />
ከተጠናቀቀ ከሁለት ሰዓት በኋላ ጉዞ ወደ አዲስ አበባ ተጀመረ፡፡ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች<br />
መሬቱን ለማስመለስ የተደረገውን ግፊት ቢያደንቁም ሰማያዊ በመመለሱ ከመጠን በላይ<br />
የሚቆራረጠው የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎት ጋብ እንደሚል በግልጽ ይናገሩ ነበር፡<br />
፡ ሰላማዊ ሰልፉ በሰላም መካሄዱ ያናደደው የሚመስለው ገዥው ፓርቲ ግን ከጎንደርም<br />
ውጭም እየተከተለ መተንኮሱን አላቆመም፡፡ አዲስ አበባ ለመድረስ ጥቂት ኪሎ ሜትሮች<br />
ሲቀሩንም ቢሆን ‹‹ከበላይ አካል›› ትዕዛዝ የተላለፈላቸው የሚመስሉት የትራፊክ<br />
ፖሊሶች ደብረ ጽጌ ላይ በመሳሪያ አስቆሙን፣ አስጸያፊ ስድብምና ማስፈራራትም<br />
ተጨመረበት፡፡<br />
ሆኖም በሰልፉ የተገኙት ወጣቶችም ይህን<br />
የአካባቢው ቅርንጫፍ በደረሰባቸው ወከባ<br />
አለመደናገጣቸውን ደውለው ነግረውኛል፡፡<br />
ለሰላማዊ ሰልፉ በሄድንበት ወቅት ጎንደር<br />
ውስጥ ካገኘኋቸው የኢህአዴግ አባላት<br />
መካከል አብዛኛዎቹ መሬቱ ለባዕድ ተላልፎ<br />
መሰጠቱን ከመቃወም አልፈው በጉዳዩ<br />
ከተቃዋሚዎች ጋር አብረው ለመስራት<br />
ፍላጎት እንዳላቸው ተረድቻለሁ፡፡ ደብድቡ<br />
ተብለው የተላኩት ፖሊሶችና የከተማው<br />
አስተዳደርም እንደ ፌደራል መንግስቱ<br />
ግትር አቋም አለመውሰዱ የሽንፈቱ አንድ<br />
አካል ነው ማለት ይቻላል፡፡<br />
ወደ አዲስ አበባ<br />
ጉዞ<br />
ሰላማዊ ሰልፉ ተደርጎም ቢሆን ማዋከቡ<br />
እንደማይቆም ቀድመው የተገነዘቡት<br />
የፓርቲው አመራሮች ጎንደርን ቶሎ<br />
መልቀቅን እንዳለባቸው አምነዋል፡፡ እናም<br />
ሰላማዊ ሰልፉ ከተጠናቀቀ ከሁለት ሰዓት<br />
በኋላ ጉዞ ወደ አዲስ አበባ ተጀመረ፡<br />
፡ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች መሬቱን<br />
ለማስመለስ የተደረገውን ግፊት ቢያደንቁም<br />
ሰማያዊ በመመለሱ ከመጠን በላይ<br />
የሚቆራረጠው የስልክና የኢንተርኔት<br />
አገልግሎት ጋብ እንደሚል በግልጽ ይናገሩ<br />
ነበር፡፡ ሰላማዊ ሰልፉ በሰላም መካሄዱ<br />
ያናደደው የሚመስለው ገዥው ፓርቲ ግን<br />
ከጎንደርም ውጭም እየተከተለ መተንኮሱን<br />
አላቆመም፡፡ አዲስ አበባ ለመድረስ ጥቂት<br />
ኪሎ ሜትሮች ሲቀሩንም ቢሆን ‹‹ከበላይ<br />
አካል›› ትዕዛዝ የተላለፈላቸው የሚመስሉት<br />
የትራፊክ ፖሊሶች ደብረ ጽጌ ላይ<br />
በመሳሪያ አስቆሙን፣ አስጸያፊ ስድብምና<br />
ማስፈራራትም ተጨመረበት፡፡<br />
ይህ ሁሉ ወከባ ግን ልዑካኑን አላስደነገጠም፡<br />
፡ ወደ ጎንደር ጉዞ ከጀመሩበት ወቅት አንስቶ<br />
ወጣቶቹ በድፍረት ከተሸናፊው መንግስት<br />
ጋር ፊት ለፊት ተጋፍጠዋል፡፡ ደብረ ጽጌ<br />
ላይም ያደረጉት ተመሳሳይ ነው፡፡ ትራፊክ<br />
ፖሊሶች መኪናውን ወደ ጣቢያ እንዲወስድ<br />
ሲወተውቱት የሰነበተውና ከልዑካኑ ጋር<br />
ሁለቱንም ቀን የታሰረው ሾፌር ደብረ ጽጌ<br />
ላይም ልክ እንደ ሰማያዊ ወጣቶች መብቱን<br />
አሳልፎ ላለመስጠት ያለውን ቁርጠኝነት<br />
አሳየ፡፡ የልዑካኑ አባላት መሳሪያ አውጥቶ<br />
‹‹እበትንሃለሁ!›› ላለው ፖሊስ ደረታቸውን<br />
ሰጡ፤ አጸያፊ ስድብ የተሳደበውን<br />
አፋጠጡት! አሁን ልዑካኑን ለማስቆም<br />
የጣሩት ፖሊሶች እንደገና መደናገጥ<br />
ጀምረዋል፡፡ የከተማው ህዝብ ወጣቶቹና<br />
የትራፊክ ፖሊስ የሚያደርጉትን ክርክር<br />
እየተመለከተ ተስብስቧል፡፡<br />
የሰማያዊ ወጣቶች ዋናው ሰላማዊ ሰልፍ<br />
ከመደረጉ በፊት መስቀል አደባባይና አዘዞ<br />
ላይ ፖሊስ ሲያስቆማቸው ሲይዛቸው<br />
በመዘመር፣ ህጉን በማስረዳት ህዝብን<br />
ሰብስበዋል፡፡ በጽናታቸውና በድፍረታቸው<br />
ፖሊሶቹን ሳይቀር አስገርመዋል፡፡ ደብረ<br />
ጽጌ ላይ በመሳሪያ ለማስቆም ሲጥርም<br />
ሌላ ሰላማዊ ሰልፍ አድርገዋል፣ ህዝብን<br />
ሰብስበው ስለመብቱ አስተምረዋል፡<br />
፡ ከፖሊስ ጋር እየተከራከሩ፣ ህዝብን<br />
ሰብስበው እያስተማሩም ለቀሪው ህዝብ<br />
በስልክና በማህበራዊ ድህረ ገጾች ትዕይንቱን<br />
ማካፈላቸውን ቀጥለዋል፡፡ በተለይ በፌስ<br />
ቡክ ዜናው በስፋት መዳረስ ጀምሯል፡፡<br />
ይህን ሁሉ ያልጠበቁት ትራፊክ ፖሊሶችን<br />
የላኩት የበላይ አካላትም ይሁኑ የከተማው<br />
ካድሬዎች ወጣቶቹን ለመልቀቅ ተገድደዋል፡<br />
፡ ለኢህአዴግ ሌላ ሽንፈት! ለሰማያዊ<br />
ወጣቶች ሌላ ድል! ከድል በኋላም የድል<br />
መዝሙር!<br />
ተከብረሽ የኖርሽው በአባቶቻችን ደም፣<br />
በአባቶቻችን ደም፣<br />
እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውደም<br />
ያስደፈረሽ ይውደም፣<br />
……….<br />
‹‹የትግል ጉዞ ታሪካዊ፣<br />
ዓላማው ፍጹም ህዝባዊ፣<br />
ራዕያችንም ኢትዮጵያዊ…››<br />
መሬት ያስቆረሱት...<br />
ከ ገፅ 7 የዞረ<br />
የሚያስረዱ መረጃዎች ሊሆኑ አይችሉምን?<br />
ድብቅነት በኢትዮጵያ በመግዛት ላይ ላለው<br />
ገዥው አካል ዋና መለያ ባህሪው ነው፡፡ ነገሮችን<br />
ደብቆ በመያዝ እያንዳንዱን በማሞኘት ላይ<br />
ይገኛሉ፡፡ አቶ መለስ በህይወት በነበሩበት ጊዜ<br />
እና በአሁኑ ጊዜ ያሉት ሎሌዎቻቸው ደግሞ<br />
የቅብብሎሽ ዱላውን ከጌታቸው ራዕይ በመቀበል<br />
በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እያሳዩ ያሉት ንቀት<br />
የህዝቡን ምንነት ሳይገመግሙ እና ሳይረዱ<br />
በራቁት ገላው ላይ ሱፍ እየጎተቱ መሆኑን<br />
በውል ሊያጤኑት ይገባል፡፡ አቶ መለስ እና<br />
ጋሻጃግሬዎቻቸው አሰብን እና ባድመን በቤሣ<br />
ቁርጥራጮች ካስረከቡ በኋላ ዝምታ ብቻ<br />
መልስ ስላገኙ ከዚያ ነገር አንድ ቁም ነገር<br />
ተምረዋል፡፡ ይኸውም ኢትዮጵያውያንን እና<br />
የኢትዮጵያን ግዛት የእነርሱ የግል እንደፈለጉ<br />
የሚለውጧት፣ የሚሸጧት የህግ ተጠያቂነት<br />
የሌለበት የግል ንብረታቸው መሆኗን አረጋገጡ፡<br />
፡በመለስ/ኃይለማርያም ከምዕራብ ኢትዮጵያ<br />
የግዛት አንድነት መሬት በመቁረስ ለሱዳን<br />
ለመስጠት የሚደረግ ማንኛውም “ስምምነት”<br />
ህገመንግስታዊ አይደለም፡፡ እ.ኤ.አ. ወደ 2008<br />
መለስ ብለን ስናይ አቶ መለስ የኢትዮጵያን<br />
መሬት ቆርሰው ለሱዳን ወይም ደግሞ ለማንም<br />
ቢሆን ለመስጠት ህጋዊ ስልጣን የላቸውም ብዬ<br />
ተከራክሬ ነበር፡፡<br />
ዛሬም ቢሆን አቶ ኃይለማርያም የኢትዮጵያን<br />
መሬት ቆርሰው ለሱዳን የመስጠት ህጋዊ<br />
መብትም ሆነ ስልጣን የላቸውም፡፡ ይህንን ካልኩ<br />
ዘንድ አቶ መለስ “ከአማራ ክልል ግዙፍ የሆነ<br />
መሬት” ቆርሰው ለሱዳን ለመስጠት “ስምምነት”<br />
እንደተፈራረሙ አጠያያቂ ነገር አይደለም፡<br />
፡ አቶ ኃይለማርያም እና ጌቶቻቸው ይህን<br />
ህገወጥ የመሬት ዕደላ ዕኩይ ተግባራቸውን<br />
“የስልታዊ/ስትራቴጂክ ስምምነት ማዕቀፍ”<br />
በማለት የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ በመክፈት ጣፋጭ<br />
በማስመሰል በማር የተለወሰ መርዛቸውን<br />
ሊግቱን ይፈልጋሉ፡፡ እውነታው ግን በአሁኑ<br />
ጊዜ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ያለው ገዥ አካል<br />
ምንም ዓይነት የኢትዮጵያን መሬት ለሱዳንም<br />
ሆነ ለማንም ሌላ አገር አሳልፎ የመስጠት ህገ<br />
መንግስታዊም ሆነ ዓለም አቀፋዊ መብትም<br />
ስልጣንም የለዉም፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ<br />
ሊታይ የሚችለው ይህ የተካሄደው የድብቅ<br />
ስምምነት የኢትዮጵያን ህገ መንግስት አንቀጽ<br />
12 የሚጻረር ስለሆነ የህገ መንግስት ጥያቄን<br />
ያስነሳል፡፡ አቶ መለስ በህይወት በነበሩበት ጊዜ<br />
እና እርሳቸውን ተክተው በመስራት ላይ ያሉት<br />
የአሁኖቹ ገዥዎቻችን ከኢትዮጵያ ህዝብ እና<br />
ከተወካዮች ምክር ቤት በሸፍጥ ደብቀው ከኦማር<br />
አልባሽር ጋር ያደረጉትን የሚስጥር “ስምምነት”<br />
እየተባለ የሚጠራውን ተግባራዊ ለማድረግ<br />
ይፍጨረጨራሉ፡፡ በኢትዮጵያ ህገ መንግስት<br />
አንቀጽ 12 ስር (“የመንግስት የስራ ድርሻ<br />
እና ተጠያቂነት“) እንዲህ ይላል፣ “መንግስት<br />
ተጣያቂነት እና ለህዝብ ግልጽነት ባለበት ሁኔታ<br />
ስራውን ይሰራል… ማንም የህዝብ ባለስልጣን<br />
ወይም ተመራጭ በህግ የተሰጠውን ስልጣን<br />
በህግ አግባብ ካልተጠቀመ ተጠያቂ ይሆናል፡<br />
፡” አቶ መለስ እና ተኪዎቻቸው “የህዝብ<br />
ባለስልጣን” እንደመሆናቸው መጠን ግልጽነት<br />
እና ተጠያቂነት ባለበት ሁኔታ ስራቸውን<br />
ለማከናወን ህገ መንግስታዊ ግዴታ አለባቸው፡<br />
፡ ለህዝብ ሳይቀርብ እና የስምምነቱ ሁኔታም<br />
በዝርዝር ምን እንደሆነ ሳይታወቅ እንዲሁም<br />
ህጋዊ ስልጣን የተሰጠው የተወካዮች ምክር<br />
ቤት ሳያጸድቀው የአገርን የግዛት አንድነት<br />
በመጣስ መሬት ቆርሶ ለሌላ አገር ለመስጠት<br />
በእራስ ፈቃድ የሚደረግ የሚስጥር ስምምነት<br />
የህገመንግስቱን አንቀጽ 12 ይጻረራል፣ ሙሉ<br />
በሙሉም ህገ መንግስቱን ይደፈጥጣል፡፡<br />
ኢትዮጵያ ለዘላለም በክብር ትኑር!<br />
(ሳምንት ይቀጥላል…)