06.03.2014 Views

Neger Ethiopia Issue 2

Neger Ethiopia Issue 2

Neger Ethiopia Issue 2

SHOW MORE
SHOW LESS

Create successful ePaper yourself

Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.

15የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2<br />

ነገረ-ኢትዮጵያ<br />

እንደሀገር መግባባት ...<br />

ከ ገፅ 11 የዞረ<br />

የጸጥታ ሀይሉ ከህዝብ ተነጥሎ የኢህአዴግ<br />

የግል ንብረት እስኪመስል ድረስ ተለያይቷል፡<br />

፡<br />

ሌላው ደግሞ የፍትህ ተቋማት የምንላቸው<br />

ድርጅቶቻችን ናቸው፡፡ አብዛኛውን ጊዜ<br />

በሀገራችን የታዩ የፍርድ ሂደቶች የተመሩት<br />

በነጻ የዳኝነት ሂደት ሳይሆን በአለቃዎቻቸው<br />

በጎ ፈቃድ መሆኑ ጸሐይ የሞቀው ሀቅ ነው፡<br />

፡ ይህን መከራከሪያችን የሚያጠናክርልን<br />

የ1997 የቅንጅት አመራሮችና አባላት ላይ<br />

የተበየነው የእስር ፍርድ ነው፡፡ ጠቅላይ<br />

ሚንስትር መለስ ዜናዊ በፓርላማ ቀርበው<br />

እስከሞት ፍርድ ሊያስቀጣ የሚችል ወንጀል<br />

አግኝተንባቸዋል ብለው ተናግረው ነበር፡<br />

፡ ይህንን ተከትሎ ፍርድ ቤት መመላለሱ<br />

የሰለቻት ዳኛ ብርቱካን ሚዴቅሳ እንዲህ ስትል<br />

ተናግራ ነበር፡፡ “ለምን ታመላልሱናላችሁ፤<br />

መለስ ዜናዊ የሞት ፍርድ ፈርዶብን አይደል<br />

እንዴ!? ወስዳችሁ ግደሉን እንጂ፡፡” በቅርብ<br />

እነ እስክንድር ነጋን ጨምሮ በአንዱዓለም<br />

አራጌ፣ በሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ<br />

ኮሚቴወች ላይ የተወሰደው የጥፋተኝነት<br />

ውሳኔም ከቀድሞው የተለየ አይደለም፡<br />

፡ በዚህም ምክንያት በሀገራችን የፍትህ<br />

ተቋማት ላይ መግባባት ሆድና ጀርባ ሆኗል፡፡<br />

ማሳያ ሰባት፡- ዘውግ ተኮር ፌደራሊዝም<br />

የህገ መንግስቱ አንቀጽ 39 እንዲህ ይላል፤<br />

‹‹የራስን እድል በራስ መወሰን እስከ<br />

መገንጠል››፡፡ በዚህ አንቀጽ መሰረት ክልሎች<br />

እራሳቸውን በራሳቸው ያስተዳድራሉ፤<br />

ከፈለጉም መገንጠል መብታቸው ነው፡<br />

፡ በግሌ ‹እስከ መገንጠል› ብሎ መብት<br />

ምን እንደሆነ ባይገባኝም የፌደራል ስርዓት<br />

መኖሩን ግን አጥብቄ እፈልገዋለሁ፡፡ ‹እስከ<br />

መገንጠል› የሚለው ሀረግ መግባቱ ግን<br />

ላለመግባባታችን አንዱ ማሳያ ነው፡፡<br />

ማሳያ ስምንት፡- ምርጫና የምርጫ ቦርድ<br />

ለአንድ ሀገር በዴሞክራሲ መበልጸግ<br />

የምርጫ ቦርድ ገለልተኛነት ወሳኝ ሚና<br />

አለው፡፡ የምርጫ ቦርድ ሃላፊነቱን በአግባቡ<br />

ከተወጣ አጭበርባሪዎችና ኮረጆ ገልባጮች<br />

ቦታ የላቸውም፡፡ ይህን አሰራር በሀገራችን<br />

ለማስፈን ጅምሩ እንኳን የለም ለማለት<br />

ያስደፍራል፡፡ የምርጫ ቦርድ አመራሮችም<br />

ሹመታቸው በቀጥታ ከመንግስት መሆኑ<br />

ለገዥው ተባባሪነታቸው መንገድ ከፋች ነው፡<br />

፡ ምርጫ ቦርድ የገዥውን ፓርቲ የሙቀት<br />

ልክ እየለካ የሚሰራ መሆኑ የታየ እውነት<br />

ነው፡፡ በዚህ የተባባሪነት አመሉ ገዥው<br />

ኮረጆ ሲገለብጥ ምርጫ ቦርድ የምርጫ<br />

ውጤት ተቀበሉ በሚል ተቃዋሚዎችን<br />

ያባብላል፤ ካልተሳካት ደግሞ ያስፈራራል፡፡<br />

ስለሆነም ምርጫ ቦርድ ሌላኛው እንደ ሀገር<br />

ያለመግባባታችን ምክንያት ሆኖ ሊጠቀስ<br />

ይችላል፡፡<br />

በአጠቃላይ ሀገሬ ኢትዮጵያ የዚህ ክፍለ<br />

ዘመን ዳግማዊ ባቢሎን እየሆነች ነው፡<br />

፡ ይህን በቋፍ ላይ ያለ አለመግባባት በጊዜ<br />

ካልፈታን እጣ ፋንታችን እንደ ባቢሎን ህንጻ<br />

መፈራረስ ከመሆን አያልፍም፡፡ አምላክ<br />

አያድርገው እላለሁ!<br />

እውነትና ህዝብ ያሸንፋል! ኢትዮጵያ<br />

ለዘላለም በክብር ትኑር!!!<br />

ኢህአዴግ ተሸንፏል...<br />

ከ ገፅ 16 የዞረ<br />

እንደተለመደው ወዲያውኑ ኢንተርኔትና<br />

ስልክ እንዲጠፋ ተደረገ፡፡<br />

አሁን ሰላማዊ ሰልፉ እየተቃረበ እንደመሆኑ<br />

የከተማውን አስተዳደር ይበልጡን ፈርቷል፡<br />

፡ ሰልፉ እንደማይቀር ከሰማያዊ ወጣቶች<br />

ድፍረትና ቆራጥነት ተረድተዋል፡፡<br />

በመሆኑም የከተማውን ነዋሪ በመሰብሰብ<br />

ማስፈራራት ነበረባቸው፡፡ ለዚህም ሰማያዊ<br />

ፓርቲን ስም እየለጠፉ ህዝቡን ለማራቅ<br />

ከመሞከር ባለፈ ‹‹ልጆቻችን ሰላማዊ ሰልፉ<br />

ላይ ቢሳተፉ በጥይት ይመታሉ!›› ብለው<br />

እስከማስፈራራት ደርሰዋል፡፡ የተሸናፊዎቹ<br />

አቅም ይህ ነው፡፡ ሰላማዊ ሰልፉ ሊደረግ<br />

10 ደቂቃ ሲቀረው ደግሞ በየ መግቢያው<br />

የተደረደሩት ፖሊሶች ህዝብን ወደ መስቀል<br />

አደባባይ እንዳይሄድ ሲያግዱ ተስተውለዋል፡<br />

፡ በሰላማዊ ሰልፉ ወቅትም የቀበሌ ካድሬዎች<br />

ከሰልፉ በኋላ በመሆን ህዝቡን በመቅረጽ<br />

ለማስፈራራት ሞክረዋል፡፡ በእርግጥ ከዚህ<br />

አልፈው ሰላማዊ ሰልፉ ከተጠናቀቀ በኋላ<br />

እርምጃ እየወሰዱ መሆናቸውም ተሰምቷል፡<br />

፡ ሰላማዊ ሰልፉ ካበቃ በኋላ በቅርብ<br />

እርቀት ሲከታተሉ የነበሩት ካድሬዎች<br />

በሰልፉ ላይ የተሳተፉትን ወጣቶች የቀበሌ<br />

መታወቂያ ቀምተዋል፡፡ ወደ ቀበሌ ሄደው<br />

መታወቂያቸውን በተቀበሉበት ወቅትም<br />

ዳግመኛ ሰማያዊም ሆነ ሌሎች ፓርቲዎች<br />

በሚጠሩት ሰልፍ እንዳይሳተፉ ማስጠንቀቂያ<br />

ተሰጥቷቸዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ሰልፉን<br />

ያስተባበሩት የጎንደር የፓርቲው አባላትና<br />

ቤተሰቦቻቸው ላይ ደህንነቶች እየደወሉ<br />

ሲያስፈራሩዋቸው ሰንብተዋል፡፡<br />

ሰላማዊ ሰልፉ ተደርጎም ቢሆን ማዋከቡ እንደማይቆም ቀድመው የተገነዘቡት የፓርቲው<br />

አመራሮች ጎንደርን ቶሎ መልቀቅን እንዳለባቸው አምነዋል፡፡ እናም ሰላማዊ ሰልፉ<br />

ከተጠናቀቀ ከሁለት ሰዓት በኋላ ጉዞ ወደ አዲስ አበባ ተጀመረ፡፡ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች<br />

መሬቱን ለማስመለስ የተደረገውን ግፊት ቢያደንቁም ሰማያዊ በመመለሱ ከመጠን በላይ<br />

የሚቆራረጠው የስልክና የኢንተርኔት አገልግሎት ጋብ እንደሚል በግልጽ ይናገሩ ነበር፡<br />

፡ ሰላማዊ ሰልፉ በሰላም መካሄዱ ያናደደው የሚመስለው ገዥው ፓርቲ ግን ከጎንደርም<br />

ውጭም እየተከተለ መተንኮሱን አላቆመም፡፡ አዲስ አበባ ለመድረስ ጥቂት ኪሎ ሜትሮች<br />

ሲቀሩንም ቢሆን ‹‹ከበላይ አካል›› ትዕዛዝ የተላለፈላቸው የሚመስሉት የትራፊክ<br />

ፖሊሶች ደብረ ጽጌ ላይ በመሳሪያ አስቆሙን፣ አስጸያፊ ስድብምና ማስፈራራትም<br />

ተጨመረበት፡፡<br />

ሆኖም በሰልፉ የተገኙት ወጣቶችም ይህን<br />

የአካባቢው ቅርንጫፍ በደረሰባቸው ወከባ<br />

አለመደናገጣቸውን ደውለው ነግረውኛል፡፡<br />

ለሰላማዊ ሰልፉ በሄድንበት ወቅት ጎንደር<br />

ውስጥ ካገኘኋቸው የኢህአዴግ አባላት<br />

መካከል አብዛኛዎቹ መሬቱ ለባዕድ ተላልፎ<br />

መሰጠቱን ከመቃወም አልፈው በጉዳዩ<br />

ከተቃዋሚዎች ጋር አብረው ለመስራት<br />

ፍላጎት እንዳላቸው ተረድቻለሁ፡፡ ደብድቡ<br />

ተብለው የተላኩት ፖሊሶችና የከተማው<br />

አስተዳደርም እንደ ፌደራል መንግስቱ<br />

ግትር አቋም አለመውሰዱ የሽንፈቱ አንድ<br />

አካል ነው ማለት ይቻላል፡፡<br />

ወደ አዲስ አበባ<br />

ጉዞ<br />

ሰላማዊ ሰልፉ ተደርጎም ቢሆን ማዋከቡ<br />

እንደማይቆም ቀድመው የተገነዘቡት<br />

የፓርቲው አመራሮች ጎንደርን ቶሎ<br />

መልቀቅን እንዳለባቸው አምነዋል፡፡ እናም<br />

ሰላማዊ ሰልፉ ከተጠናቀቀ ከሁለት ሰዓት<br />

በኋላ ጉዞ ወደ አዲስ አበባ ተጀመረ፡<br />

፡ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች መሬቱን<br />

ለማስመለስ የተደረገውን ግፊት ቢያደንቁም<br />

ሰማያዊ በመመለሱ ከመጠን በላይ<br />

የሚቆራረጠው የስልክና የኢንተርኔት<br />

አገልግሎት ጋብ እንደሚል በግልጽ ይናገሩ<br />

ነበር፡፡ ሰላማዊ ሰልፉ በሰላም መካሄዱ<br />

ያናደደው የሚመስለው ገዥው ፓርቲ ግን<br />

ከጎንደርም ውጭም እየተከተለ መተንኮሱን<br />

አላቆመም፡፡ አዲስ አበባ ለመድረስ ጥቂት<br />

ኪሎ ሜትሮች ሲቀሩንም ቢሆን ‹‹ከበላይ<br />

አካል›› ትዕዛዝ የተላለፈላቸው የሚመስሉት<br />

የትራፊክ ፖሊሶች ደብረ ጽጌ ላይ<br />

በመሳሪያ አስቆሙን፣ አስጸያፊ ስድብምና<br />

ማስፈራራትም ተጨመረበት፡፡<br />

ይህ ሁሉ ወከባ ግን ልዑካኑን አላስደነገጠም፡<br />

፡ ወደ ጎንደር ጉዞ ከጀመሩበት ወቅት አንስቶ<br />

ወጣቶቹ በድፍረት ከተሸናፊው መንግስት<br />

ጋር ፊት ለፊት ተጋፍጠዋል፡፡ ደብረ ጽጌ<br />

ላይም ያደረጉት ተመሳሳይ ነው፡፡ ትራፊክ<br />

ፖሊሶች መኪናውን ወደ ጣቢያ እንዲወስድ<br />

ሲወተውቱት የሰነበተውና ከልዑካኑ ጋር<br />

ሁለቱንም ቀን የታሰረው ሾፌር ደብረ ጽጌ<br />

ላይም ልክ እንደ ሰማያዊ ወጣቶች መብቱን<br />

አሳልፎ ላለመስጠት ያለውን ቁርጠኝነት<br />

አሳየ፡፡ የልዑካኑ አባላት መሳሪያ አውጥቶ<br />

‹‹እበትንሃለሁ!›› ላለው ፖሊስ ደረታቸውን<br />

ሰጡ፤ አጸያፊ ስድብ የተሳደበውን<br />

አፋጠጡት! አሁን ልዑካኑን ለማስቆም<br />

የጣሩት ፖሊሶች እንደገና መደናገጥ<br />

ጀምረዋል፡፡ የከተማው ህዝብ ወጣቶቹና<br />

የትራፊክ ፖሊስ የሚያደርጉትን ክርክር<br />

እየተመለከተ ተስብስቧል፡፡<br />

የሰማያዊ ወጣቶች ዋናው ሰላማዊ ሰልፍ<br />

ከመደረጉ በፊት መስቀል አደባባይና አዘዞ<br />

ላይ ፖሊስ ሲያስቆማቸው ሲይዛቸው<br />

በመዘመር፣ ህጉን በማስረዳት ህዝብን<br />

ሰብስበዋል፡፡ በጽናታቸውና በድፍረታቸው<br />

ፖሊሶቹን ሳይቀር አስገርመዋል፡፡ ደብረ<br />

ጽጌ ላይ በመሳሪያ ለማስቆም ሲጥርም<br />

ሌላ ሰላማዊ ሰልፍ አድርገዋል፣ ህዝብን<br />

ሰብስበው ስለመብቱ አስተምረዋል፡<br />

፡ ከፖሊስ ጋር እየተከራከሩ፣ ህዝብን<br />

ሰብስበው እያስተማሩም ለቀሪው ህዝብ<br />

በስልክና በማህበራዊ ድህረ ገጾች ትዕይንቱን<br />

ማካፈላቸውን ቀጥለዋል፡፡ በተለይ በፌስ<br />

ቡክ ዜናው በስፋት መዳረስ ጀምሯል፡፡<br />

ይህን ሁሉ ያልጠበቁት ትራፊክ ፖሊሶችን<br />

የላኩት የበላይ አካላትም ይሁኑ የከተማው<br />

ካድሬዎች ወጣቶቹን ለመልቀቅ ተገድደዋል፡<br />

፡ ለኢህአዴግ ሌላ ሽንፈት! ለሰማያዊ<br />

ወጣቶች ሌላ ድል! ከድል በኋላም የድል<br />

መዝሙር!<br />

ተከብረሽ የኖርሽው በአባቶቻችን ደም፣<br />

በአባቶቻችን ደም፣<br />

እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውደም<br />

ያስደፈረሽ ይውደም፣<br />

……….<br />

‹‹የትግል ጉዞ ታሪካዊ፣<br />

ዓላማው ፍጹም ህዝባዊ፣<br />

ራዕያችንም ኢትዮጵያዊ…››<br />

መሬት ያስቆረሱት...<br />

ከ ገፅ 7 የዞረ<br />

የሚያስረዱ መረጃዎች ሊሆኑ አይችሉምን?<br />

ድብቅነት በኢትዮጵያ በመግዛት ላይ ላለው<br />

ገዥው አካል ዋና መለያ ባህሪው ነው፡፡ ነገሮችን<br />

ደብቆ በመያዝ እያንዳንዱን በማሞኘት ላይ<br />

ይገኛሉ፡፡ አቶ መለስ በህይወት በነበሩበት ጊዜ<br />

እና በአሁኑ ጊዜ ያሉት ሎሌዎቻቸው ደግሞ<br />

የቅብብሎሽ ዱላውን ከጌታቸው ራዕይ በመቀበል<br />

በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እያሳዩ ያሉት ንቀት<br />

የህዝቡን ምንነት ሳይገመግሙ እና ሳይረዱ<br />

በራቁት ገላው ላይ ሱፍ እየጎተቱ መሆኑን<br />

በውል ሊያጤኑት ይገባል፡፡ አቶ መለስ እና<br />

ጋሻጃግሬዎቻቸው አሰብን እና ባድመን በቤሣ<br />

ቁርጥራጮች ካስረከቡ በኋላ ዝምታ ብቻ<br />

መልስ ስላገኙ ከዚያ ነገር አንድ ቁም ነገር<br />

ተምረዋል፡፡ ይኸውም ኢትዮጵያውያንን እና<br />

የኢትዮጵያን ግዛት የእነርሱ የግል እንደፈለጉ<br />

የሚለውጧት፣ የሚሸጧት የህግ ተጠያቂነት<br />

የሌለበት የግል ንብረታቸው መሆኗን አረጋገጡ፡<br />

፡በመለስ/ኃይለማርያም ከምዕራብ ኢትዮጵያ<br />

የግዛት አንድነት መሬት በመቁረስ ለሱዳን<br />

ለመስጠት የሚደረግ ማንኛውም “ስምምነት”<br />

ህገመንግስታዊ አይደለም፡፡ እ.ኤ.አ. ወደ 2008<br />

መለስ ብለን ስናይ አቶ መለስ የኢትዮጵያን<br />

መሬት ቆርሰው ለሱዳን ወይም ደግሞ ለማንም<br />

ቢሆን ለመስጠት ህጋዊ ስልጣን የላቸውም ብዬ<br />

ተከራክሬ ነበር፡፡<br />

ዛሬም ቢሆን አቶ ኃይለማርያም የኢትዮጵያን<br />

መሬት ቆርሰው ለሱዳን የመስጠት ህጋዊ<br />

መብትም ሆነ ስልጣን የላቸውም፡፡ ይህንን ካልኩ<br />

ዘንድ አቶ መለስ “ከአማራ ክልል ግዙፍ የሆነ<br />

መሬት” ቆርሰው ለሱዳን ለመስጠት “ስምምነት”<br />

እንደተፈራረሙ አጠያያቂ ነገር አይደለም፡<br />

፡ አቶ ኃይለማርያም እና ጌቶቻቸው ይህን<br />

ህገወጥ የመሬት ዕደላ ዕኩይ ተግባራቸውን<br />

“የስልታዊ/ስትራቴጂክ ስምምነት ማዕቀፍ”<br />

በማለት የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ በመክፈት ጣፋጭ<br />

በማስመሰል በማር የተለወሰ መርዛቸውን<br />

ሊግቱን ይፈልጋሉ፡፡ እውነታው ግን በአሁኑ<br />

ጊዜ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ያለው ገዥ አካል<br />

ምንም ዓይነት የኢትዮጵያን መሬት ለሱዳንም<br />

ሆነ ለማንም ሌላ አገር አሳልፎ የመስጠት ህገ<br />

መንግስታዊም ሆነ ዓለም አቀፋዊ መብትም<br />

ስልጣንም የለዉም፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ<br />

ሊታይ የሚችለው ይህ የተካሄደው የድብቅ<br />

ስምምነት የኢትዮጵያን ህገ መንግስት አንቀጽ<br />

12 የሚጻረር ስለሆነ የህገ መንግስት ጥያቄን<br />

ያስነሳል፡፡ አቶ መለስ በህይወት በነበሩበት ጊዜ<br />

እና እርሳቸውን ተክተው በመስራት ላይ ያሉት<br />

የአሁኖቹ ገዥዎቻችን ከኢትዮጵያ ህዝብ እና<br />

ከተወካዮች ምክር ቤት በሸፍጥ ደብቀው ከኦማር<br />

አልባሽር ጋር ያደረጉትን የሚስጥር “ስምምነት”<br />

እየተባለ የሚጠራውን ተግባራዊ ለማድረግ<br />

ይፍጨረጨራሉ፡፡ በኢትዮጵያ ህገ መንግስት<br />

አንቀጽ 12 ስር (“የመንግስት የስራ ድርሻ<br />

እና ተጠያቂነት“) እንዲህ ይላል፣ “መንግስት<br />

ተጣያቂነት እና ለህዝብ ግልጽነት ባለበት ሁኔታ<br />

ስራውን ይሰራል… ማንም የህዝብ ባለስልጣን<br />

ወይም ተመራጭ በህግ የተሰጠውን ስልጣን<br />

በህግ አግባብ ካልተጠቀመ ተጠያቂ ይሆናል፡<br />

፡” አቶ መለስ እና ተኪዎቻቸው “የህዝብ<br />

ባለስልጣን” እንደመሆናቸው መጠን ግልጽነት<br />

እና ተጠያቂነት ባለበት ሁኔታ ስራቸውን<br />

ለማከናወን ህገ መንግስታዊ ግዴታ አለባቸው፡<br />

፡ ለህዝብ ሳይቀርብ እና የስምምነቱ ሁኔታም<br />

በዝርዝር ምን እንደሆነ ሳይታወቅ እንዲሁም<br />

ህጋዊ ስልጣን የተሰጠው የተወካዮች ምክር<br />

ቤት ሳያጸድቀው የአገርን የግዛት አንድነት<br />

በመጣስ መሬት ቆርሶ ለሌላ አገር ለመስጠት<br />

በእራስ ፈቃድ የሚደረግ የሚስጥር ስምምነት<br />

የህገመንግስቱን አንቀጽ 12 ይጻረራል፣ ሙሉ<br />

በሙሉም ህገ መንግስቱን ይደፈጥጣል፡፡<br />

ኢትዮጵያ ለዘላለም በክብር ትኑር!<br />

(ሳምንት ይቀጥላል…)

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!