06.03.2014 Views

Neger Ethiopia Issue 2

Neger Ethiopia Issue 2

Neger Ethiopia Issue 2

SHOW MORE
SHOW LESS

You also want an ePaper? Increase the reach of your titles

YUMPU automatically turns print PDFs into web optimized ePapers that Google loves.

3 የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2 ነገረ-ኢትዮጵያ<br />

ልብ አድርጉ<br />

ውህደት ወይስ ትብብር?<br />

በላይ ማናዬ<br />

ሀገር አቀፉ ምርጫ 2007 እየደረሰ ነው፤<br />

ምርጫን ተከትሎ የሚስተዋለው የፖለቲካ<br />

ግለትም በትንሹም ቢሆን ከወዲሁ ለብ<br />

ማለት የጀመረ ይመስላል፤ የት መሽገው<br />

እንደከረሙ ጠፍተውብን የነበሩ የፖለቲካ<br />

ፓርቲዎችም አንገታቸውን ብቅ ለማድረግ<br />

እየሞከሩ እንደሆነ መታዘብ ይቻላል፡፡<br />

በሀገራችን በፓርቲዎች የቁጥር ብዛት ረገድ<br />

ችግር የለም ማለት ይቻላል፡፡ ባለፈው<br />

ምርጫ 2002 እንኳ ወደ 90 የሚጠጉ<br />

ፓርቲዎች እንደነበሩ ይታወቃል፡፡<br />

በእርግጥም አሁን ላይ ኢትዮጵያ<br />

ውስጥ በቁጥር በጣም ብዙ የፖለቲካ<br />

ፓርቲዎች ተመዝግበው ይገኛሉ፤<br />

(በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚንቀሳቀሱትን<br />

ህብረ-ብሄር ፓርቲዎችም፣ ጎሳን ወይም<br />

አንድን ብሄረሰብ ማዕከል አድርገው<br />

የሚንቀሳቀሱትንም ማለቴ ነው)፡፡ ለአብነት<br />

በሁለተኛው ረድፍ ላይ ከሚመደቡት እንኳ<br />

ብናይ ለኦሮሞ ህዝብ እንታገላለን የሚሉት<br />

ከ10 በላይ፣ ጉራጌ 5፣ አርጎባ 3፣ ሀረሪ<br />

3 እና ሌሎችም በተመሳሳይ በርካቶች<br />

አሉ፡፡ በዚህም ከአጠቃላይ የፓርቲዎች<br />

ቁጥር አብላጫውን ሀገር አቀፍ ያልሆኑት<br />

ፓርቲዎች ይዘው ይገኛሉ፡፡ (የምዝገባ<br />

ፍቃዱን ወስዶ ዳናው የሚጠፋውም ጥቂት<br />

የሚባል አይደለም፡፡)<br />

ይህ ቁጥሩ የበዛ የፓርቲዎች እንቅስቃሴ<br />

ያለው ደግሞ በተቃውሞው ጎራ በኩል<br />

ነው፡፡ እንዲህ አይነቱ የፓርቲዎች አካሄድ<br />

ማንን እንደሚጠቅም ሳይታለም የተፈታ<br />

ነው፡፡ በምርጫ ወቅት የህዝብን ድምጽ<br />

በመከፋፈል የትኛውም ተቃዋሚ ፓርቲ<br />

አብላጫ ድምጽ በቀላሉ እንዳያገኝ በማድረግ<br />

ለገዥው ፓርቲ በተዘዋዋሪ ይጠቅመዋል፡<br />

፡ ስለሆነም እንዲህ ባለ ወቅት ተቃዋሚ<br />

ፓርቲዎች በሁለት አማራጮች ላይ<br />

ይንጠለጠላሉ፤ አንድም በቁጥር የበዙትን<br />

ፓርቲዎች ወደ አንድ ኃይል ማምጣት<br />

ላይ፣ አሊያም በተናጠልም ቢሆን በሀገር<br />

አቀፍ ደረጃ ጎልቶ ለመውጣት የሚያስችልን<br />

አቅም ፈጥሮ ገዥው ፓርቲንም ሆነ<br />

ሌሎች ተወዳዳሪዎችን ተፎካክሮ ለማሸነፍ<br />

የሚያስችልን እንቅስቃሴ ማድረግ፡፡<br />

በተግባር እንቅስቃሴ ላይ ያሉትን የተለያዩ<br />

ፓርቲዎች ወደ አንድ ኃይል አምጥቶ<br />

ወደ ምርጫ መግባት በባለፉት የምርጫ<br />

ተሞክሮዎቻችን ላይ አይተናል፤ (ቅንጅትን<br />

በ97፣ መድረክን በ2002 መጥቀስ ይቻላል፡፡<br />

) ያለፉት ሂደቶችና ተሞክሮዎች የራሳቸው<br />

ጥንካሬና ድክመት እንደነበረባቸው መካድ<br />

አይቻልም፡፡ ያም ሆነ ይህ ግን አሁን<br />

ሌላ የታሪክ ምዕራፍ ላይ እንገኛለን፡<br />

፡ ቀደም ብዬ እንደጠቀስኩት ምርጫ<br />

2007 እየደረሰ ነው፡፡ ስለሆነም አሁን<br />

ፓርቲዎች የበለጠ ለስራ የሚነሱበት ጊዜ<br />

ነው፤ በተናጠልም፣ በትብብርም፡፡ ከዚህ<br />

ጋር ተያይዞ በዚህ ሰሞን ስለ ፓርቲዎች<br />

ውህደትም የሚያነሱት በዝተዋል፡፡ ይህን<br />

የውህደት ጉዳይ እንደሚከተለው ለማየት<br />

እንሞከራለን፡፡<br />

ውህደት እንዴት?<br />

በአጭሩ ውህደት አንድ መሆን ማለት<br />

ነው፡፡ ከውህደት በፊት ያለው የተናጠል<br />

ህጋዊ ህልውና አክትሞ አዲስ ፓርቲ<br />

በአንድ ላይ መመስረት ነው ውህደት፡<br />

፡ አንድ ለመሆን ደግሞ፣ አንድ ለመሆን<br />

የሚያስችሉ ሁኔታዎች መኖር አለባቸው፡<br />

፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለመዋህድ የፖለቲካ<br />

ፕሮግራማቸው መመሳሰልና መቀራረብ<br />

ይኖርበታል፡፡ ከዚህም በላይ ግን ፓርቲዎቹ<br />

ለመዋህድ ፍላጎት ማሳየት የግድ ነው፤<br />

በውህደቱ ሂደትና ከውህደት በኋላ<br />

ስለሚኖረው እንቅስቃሴም የተሻለ መስራት<br />

እንደሚችሉ ሊያምኑበት ይገባል፡፡ በዚህም<br />

ማን ከማን ጋር መዋህድ እንደሚችል<br />

ካላቸው የፖለቲካ ፕሮግራም፣ የውህደት<br />

ፍላጎትና በመዋህዳቸው ሊያመጡት<br />

የሚችሉትን ውጤት ገምግመው፣ ወይ<br />

ወደ ውህደት ይገባሉ አሊያም በራሳቸው<br />

መስመር ጠንክረው ለመስራት ውሳኔ<br />

ያስተላልፋሉ፡፡<br />

ከሰሞኑ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት<br />

ድርጅት (መኢአድ) እና አንድነት<br />

ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት)<br />

በአስቸኳይ ለመዋህድ እየሰሩ እንደሆነ<br />

ገልጸዋል፡፡ ፓርቲዎቹ ጥር 25 ቀን 2006<br />

ዓ.ም መአህድ/መኢአድ የተመሰረተበትን<br />

22ኛ አመት በዓል በጽ/ቤቱ ባከበረበት ወቅት<br />

እንደገለጹት፣ ሁለቱ ፓርቲዎች በፍጥነት<br />

ወደ ውህደት ለመምጣት መወሰናቸውን<br />

በይፋ በመሪዎቻቸው በኩል ግልጽ<br />

አድርገዋል፡፡ የመኢአድ ፓርቲ ፕሬዚዳንት<br />

አቶ አበባው መሐሪ ፓርቲያቸው መኢአድ<br />

ከአንድነት ፓርቲ ጋር መዋሃድ ፍላጎቱ<br />

መሆኑን ተናግረዋል፡፡<br />

በተመሳሳይ በቀድሞ ፓርቲያቸው 22ኛ<br />

አመት ክብረ በዓል ላይ የተገኙት የአንድነት<br />

ፓርቲ ፕሬዚዳንት ኢ/ር ግዛቸው ሺፈራው<br />

በበኩላቸው ፓርቲያቸው ከመኢአድ ጋር<br />

መዋሃድ ፍላጎቱ መሆኑን ገልጸው፣<br />

በ15 ቀናት ውስጥ ውህደቱ እውን ሊሆን<br />

እንደሚችልም ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡<br />

ፓርቲዎቹ ይህን ይበሉ እንጂ (በዕለቱ<br />

በነበረው የመድረክ ሞቅታ እንዳይሆን<br />

እሰጋለሁ) በዚህ ፍጥነት ሊዋሀዱ<br />

የሚችሉበት ሁኔታ ውስጥ እንዳልሆኑ<br />

ጠቋሚ ምልክቶች መኖራቸውን መካድ<br />

አይቻልም፡፡<br />

ውህደት መቼ?<br />

ውህደት ምርጫ ስለቀረበ የሚከናወን<br />

የይድረስ ይድረስ ስራ እንዳልሆነ እሙን<br />

ነው፡፡ በተቃራኒው ግን በሀገራችን የነበሩ፤<br />

ያሉ ፓርቲዎች ውህደት የሚታያቸው<br />

ምርጫ ሲቃረብ መሆኑ አለመታደል ነው፡፡<br />

አንዳንዶቹ ሂደቱን ቀድመው ቢጀምሩትም<br />

ሲያጓትቱ ሲያጓትቱ እስከ ምርጫ መቃረቢያ<br />

ድረስ ያደርሱታል፡፡ የመኢአድና የአንድነት<br />

ውህደት እውን ቢሆን የሚወድ ብዙ ነው፡<br />

፡ ዳሩ ግን ውህደቱ መሆን የነበረበት<br />

(በእውነት ኢ/ር ግዛቸው እንዳሉት በ15<br />

ቀናት ውስጥ የሚከናወን ከሆነ ወይም<br />

ቢሆን ኖሮ) እንዲህ በሩጫ አሁን ላይ<br />

አይደለም፤ (በ15 ቀናት ውስጥ የሚደረግ<br />

ውህደት የፖለቲካ ፓርቲዎች ሳይሆን….)፡<br />

፡ ይህ ውህደት ከምርጫ 2002 ማግስት<br />

ቢሆን በተገባ ነበር፡፡<br />

ውህደት በተናጠል በውጠ-ፓርቲ ትግል<br />

ፈተና ውስጥ የገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎች<br />

መሪዎች ከቀውስ ማምለጫ ወይም አጀንዳ<br />

ማስቀየሻ ሊሆን አይገባም፡፡ በተጨማሪም<br />

አንድ ፓርቲ ከገጠመው የገንዘብ እጥረት<br />

አሊያም የቢሮ ኪራይ ችግር ለመውጣት<br />

ዘው ብሎ የሚገባበት ጉዳይ መሆን<br />

አይኖርበትም፡፡ በሩጫ የሚደረግ ውህደት<br />

ውጤቱ ምን ሊሆን እንደሚችል ለማንም<br />

የተሰወረ አይሆንም፡፡<br />

እናም ውህደት በቂ ጊዜ ወስዶ መጤን<br />

ያለበት ትልቅ የፖለቲካ ስራ ነው፡፡<br />

እርግጥ ነው ህዝቡ ፓርቲዎቹ እንዲዋህዱ<br />

ይፈልጋል፡፡ ከዚህ በላይ ግን አብዛኛው<br />

ህዝብ ፓርቲዎች ተዋህደው እንዲዘልቁና<br />

ለውጥ እንዲያመጡ እንደሚሻ ግልጽ ነው፡<br />

፡ ለዚህ ደግሞ ከጅምሩ የሰከነ የውህደት<br />

ሂደት መኖሩ ግድ ይላል፡፡<br />

የውህደት ፈተናዎች<br />

የፖለቲካ ፓርቲዎችን ወደ ውህደት<br />

ማምጣት፣ ከውህደት በኋላም ተስማምቶ<br />

መቀጠል ትልቅ ፈተና አለው፡፡ በተለይም<br />

እንዲህ በአጭር ጊዜ ውህደትን እናመጣለን<br />

ብለው ሰርጋቸውን ከሚያፋጥኑ ሰዎች<br />

ወደ ፊት የሚሆነውን በስጋት መመልከት<br />

ግርምትን የሚፈጥር ጉዳይ አይሆንም፡<br />

፡ በተዋሃጆቹም በኩል የእነቶሎ ቶሎ<br />

ቤት…እንዳይሆን መጠንቀቁ የሚበጅ ነው፡<br />

፡ ምርጫ ስለደረሰ ብቻ በፍጥነት ውህደትን<br />

ማከናወን ሊኖረው የሚችለውን ፈተና<br />

ሊያስረሳን አይገባም፡፡ ሰርገኛ መጣ በርበሬ<br />

ቀንጥስ እንዳይሆን መጠንቀቁ የብልሆች<br />

ምርጫ ነው፡፡<br />

በእርግጥም ውህደት የጥቂት ግለሰቦች<br />

ወይም የፖለቲካ ፓርቲዎች መሪዎች<br />

ፍላጎትና ተግባር ብቻ አይደለም፡፡ ከዚያ<br />

ይልቅ የሚዋሃዱት ፓርቲዎች አባላት<br />

(ጠቅላላ ጉባኤ በሚገባ ተወያይቶበት<br />

ውሳኔ ማሳለፍን ይጠይቃል፤) በየደረጃው<br />

ሰፊ ጊዜ ሰጥተው ጉዳዩን ሊወያዩበትና<br />

ሊያጤኑት ግድ ይላል፡፡ ይህን ለማድረግ<br />

የሚያስችላቸው ጊዜም ሊሰጣቸው<br />

እንደሚገባ እሙን ነው፡፡ በሌላ አነጋገር<br />

ውህደቱ ከጅምሩ እሰከ ፍጻሜው አባላትንም<br />

ማዕከል ያደረገ መሆን ይኖርበታል፡፡ ይህ<br />

ሳይሆን ቀርቶ ውህደቱ የጥቂቶች ስራ<br />

ከሆነ፣ አንድም ውህደቱ እውን አይሆንም፣<br />

እውን ከሆነም ዘላቂነቱ አጠራጣሪ ከመሆን<br />

አይድንም፡፡<br />

የውህድ ፓርቲው መሪ<br />

ሌላው ፈተና ውህደቱ ከተፈጸመ በኋላ<br />

የውህድ ፓርቲው (አዲሱ ፓርቲ) መሪ<br />

ማን ይሁን የሚለው ጉዳይ ነው፡፡ የዚህ<br />

ፈተና ምንጭ ውህደቱን ከመሰረቱት<br />

ፓርቲዎች ወገን ሁሉም የቀድሞ ፓርቲው<br />

መሪ፣ የአዲሱ ውህድ ፓርቲ መሪም<br />

ሆኖ እንዲዘልቅለትና ቡድናዊ ጥቅሙን<br />

እንዲያስከብርለት የመፈለጉ ጫና ነው፡፡<br />

በዚህም ሁሉም የየራሱን የቀደመ የትግል<br />

ታሪክና የአደረጃጀት ስፋት እያነሳ ስልጣኑ<br />

እንደሚገባው መሞገቱ ስለማይቀር ነው፡፡<br />

እንዲህ አይነቱ ጉዳይ ደግሞ ማን የተሻለ<br />

መምራት ይችላል ሳይሆን፣ ማን የውህድ<br />

ፓርቲው መሪነት ይገባዋል ወደሚል<br />

ሰንካላ ምክንያት ይገፋናል፡፡<br />

በተመሳሳይ ውህደቱ ከሚከናወንበት<br />

ወቅት አንስቶ፣ ውህደቱ ሊያመጣባቸው<br />

የሚችለውን ከጥቅማ ጥቅምና ስልጣን<br />

ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን ማጣት በማጤን<br />

ቅሬታ የሚሰማቸው ግለሰቦችም ሌላኛዎቹ<br />

ፈተናዎች መሆናቸው የማይቀር ነው፡<br />

፡ ከሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ<br />

ፓርቲዎች ወደ አንድ ሲመጡ፣ ቀድሞ<br />

በተናጠል የነበረውን የስራ አስፈጻሚ ያህል<br />

ቁጥር ሊያካትት አይችልም፡፡ በዚህ ጊዜ<br />

ተቀናሾች መኖራቸው ግድ ነው፤ እዚህ<br />

ጋር የሚነሳው ጉዳይ የመቀነሻ መስፈርቶቹ<br />

ናቸው፡፡ ያም ሆነ ይህ በአዲሱ ፓርቲ<br />

የሚደረገው የስልጣን ሽግሽግ በውህደት<br />

ወቅትና ከውህደት በኋላ ከሚገጥሙ<br />

ፈተናዎች መካከል መሆኑ የማይቀር ነው፡፡<br />

በሌላ በኩል ደግሞ ከውህደት በኋላም፣<br />

ከግል የስልጣን ጥማቸው ጋር በተገናኘ<br />

በስልጣን ተዋረድ ውስጥ ሁለተኛ ሰው<br />

ሆነው ለመስራት የማይፈልጉና ሁሌም ከኔ<br />

በላይ ላሳር ባዮች አይጠፉም፡፡ በዚህም፣<br />

እንዲህ አይነት ግለሰቦች አንዴ ከፖለቲካ<br />

ሲርቁ፣ ሌላ ጊዜ ያችኑ የመሪነት ቦታ<br />

ሲሰጣቸው ወደ መድረኩ ብቅ የሚሉ<br />

ናቸው፡፡ የእነዚህ ግለሰቦች የስልጣን ጥም<br />

የመሪነት ቦታ የነፈጋቸውን ፓርቲ ለቅቀው<br />

ወደ ሌላ ፓርቲ እስከመሄድ የሚያደርሳቸው<br />

ነው፡፡ ስለሆነም እነዚህን መሰል ግለሰቦች<br />

ዛሬ ስለውህደት አብዝተው ቢሰብኩም<br />

ያችኑ የመሪነት ቦታ የሚያሳጣቸው ጉዳይ<br />

ሲመጣ ሲያቀነቅኑት የነበረውን ዓላማ<br />

ረስተው የውህደቱ እንቅፋት ከመሆን<br />

ላይመለሱ ይችላሉ፡፡<br />

ደካማ የቀደመ የፖለቲካ ፓርቲዎች ውህደት<br />

ተሞክሮ ያለን ከመሆኑ ጋር ተያይዞ<br />

(በቅንጅቱ መፍረስ የተፈጠረ መንፈስን<br />

ማስታወስ ይበቃል፤) በህዝቡ ዘንድ ያለው<br />

ተስፋ የመቁረጥ ስሜትም እንደ አንድ ሌላ<br />

ፈተና ሊወሰድ የሚችል ነው፡፡ ፈጥኖ ወደ<br />

ውህደት የመግባትን ያህል ከውህደት በኋላ<br />

ተስማምቶ የመቀጠሉ ፈተናም ከባድ ነው፡<br />

፡ ስለሆነም መዋሃዱ መልካም ሆኖ፣ ነገር<br />

ግን አሁንም ከውህደት በፊት መሰራት<br />

ያለባቸው የቤት ስራዎች በጊዜ ከተከናወኑ<br />

በኋላ ቢሆን የተሻለ ውጤት ይኖረዋል፡፡<br />

አሁን ላይ ውህደት ወይስ ትብብር?<br />

ቀደም ብሎ እንደተጠቀሰው ውህደትን<br />

ለማከናወን የተዋሃጅ ፓርቲዎች ፕሮግራም<br />

ተመሳሳይ ወይም ተቀራራቢ መሆን<br />

ይኖርበታል፡፡ በዚህም አንድ ፓርቲ ከሌላው<br />

ጋር ለመዋሃድ መሰሉን ወይም ቢጤውን<br />

መፈለግ ግድ ይለዋል፤ ይህም የሚሆነው<br />

የሌላኛው ፓርቲ ፍላጎት ሲጨመርበት<br />

ነው፡፡ እናም ውህደት አግላይ ጎንም<br />

እንዳለው መገንዘብ ይቻላል፡፡ ለአብነትም<br />

የመኢአድ ሊቀመንበር አቶ አበባው መሐሪ<br />

የፓርቲያቸውን አቋም በሚከተለው መልኩ<br />

ገልጸውታል፡፡<br />

‹‹መኢአድ በኢትዮጵያ አንድነት ላይ<br />

ከማያምኑ የብሄር (የጎሳ) የፖለቲካ<br />

ድርጅቶች፣ በኢትዮጵያ አንድነት ላይ<br />

አልደራደርም በማለት፣ በውህደት ደረጃ<br />

አብሮ ለመስራት እቸገራለሁ የሚለው በቂ<br />

ምክንያት ስላለው ነው፡፡›› (አንድነት ከአረና<br />

ትግራይ ጋር ለመዋሀድ ንግግር መጀመሩ<br />

የሚታወቅ ነው፡፡ ታዲያ መኢአድ በአንድነት<br />

በኩል የመጣውን አረና ትግራይን እንዴት<br />

ሊያደርገው ይሆን?) ያም ሆነ ይህ ጉዳዩ<br />

የሚያሳየን የውህደትን አግላይነት ነው፡፡<br />

ከመኢአድ አቋም ለመረዳት እንደሚቻለው<br />

ፓርቲው ለውህደት በሩን የሚከፍተው<br />

ጠንካራ ጥበቃዎችን ከፊት አቁሞ ነው፡<br />

፡ ስለሆነም ውህደት የራሱ ጠንካራ ጎኖች<br />

እንዳሉት ሆኖ፣ እንደ አሸን የፈሉትን<br />

የፖለቲካ ድርጅቶች በጋራ አስተባብሮ ወደ<br />

አንድ የማምጣቱ ነገር ውስን መሆኑን<br />

ነው፡፡<br />

በአብዛኛው የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች<br />

የጋራ የሆነ የሚታገሉት ኃይል አላቸው፤<br />

እሱም ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ ነው፡<br />

፡ እነዚህ ፓርቲዎች የየራሳቸው የተለያየ<br />

ዓላማን አንግበው የሚንቀሳቀሱ ቢሆኑም<br />

የወል ጉዳይ እስካላቸው ድረስ ግን መተባበር<br />

ወደ ገፅ 6 ይዞራል

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!