Neger Ethiopia Issue 2
Neger Ethiopia Issue 2
Neger Ethiopia Issue 2
You also want an ePaper? Increase the reach of your titles
YUMPU automatically turns print PDFs into web optimized ePapers that Google loves.
3 የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2 ነገረ-ኢትዮጵያ<br />
ልብ አድርጉ<br />
ውህደት ወይስ ትብብር?<br />
በላይ ማናዬ<br />
ሀገር አቀፉ ምርጫ 2007 እየደረሰ ነው፤<br />
ምርጫን ተከትሎ የሚስተዋለው የፖለቲካ<br />
ግለትም በትንሹም ቢሆን ከወዲሁ ለብ<br />
ማለት የጀመረ ይመስላል፤ የት መሽገው<br />
እንደከረሙ ጠፍተውብን የነበሩ የፖለቲካ<br />
ፓርቲዎችም አንገታቸውን ብቅ ለማድረግ<br />
እየሞከሩ እንደሆነ መታዘብ ይቻላል፡፡<br />
በሀገራችን በፓርቲዎች የቁጥር ብዛት ረገድ<br />
ችግር የለም ማለት ይቻላል፡፡ ባለፈው<br />
ምርጫ 2002 እንኳ ወደ 90 የሚጠጉ<br />
ፓርቲዎች እንደነበሩ ይታወቃል፡፡<br />
በእርግጥም አሁን ላይ ኢትዮጵያ<br />
ውስጥ በቁጥር በጣም ብዙ የፖለቲካ<br />
ፓርቲዎች ተመዝግበው ይገኛሉ፤<br />
(በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚንቀሳቀሱትን<br />
ህብረ-ብሄር ፓርቲዎችም፣ ጎሳን ወይም<br />
አንድን ብሄረሰብ ማዕከል አድርገው<br />
የሚንቀሳቀሱትንም ማለቴ ነው)፡፡ ለአብነት<br />
በሁለተኛው ረድፍ ላይ ከሚመደቡት እንኳ<br />
ብናይ ለኦሮሞ ህዝብ እንታገላለን የሚሉት<br />
ከ10 በላይ፣ ጉራጌ 5፣ አርጎባ 3፣ ሀረሪ<br />
3 እና ሌሎችም በተመሳሳይ በርካቶች<br />
አሉ፡፡ በዚህም ከአጠቃላይ የፓርቲዎች<br />
ቁጥር አብላጫውን ሀገር አቀፍ ያልሆኑት<br />
ፓርቲዎች ይዘው ይገኛሉ፡፡ (የምዝገባ<br />
ፍቃዱን ወስዶ ዳናው የሚጠፋውም ጥቂት<br />
የሚባል አይደለም፡፡)<br />
ይህ ቁጥሩ የበዛ የፓርቲዎች እንቅስቃሴ<br />
ያለው ደግሞ በተቃውሞው ጎራ በኩል<br />
ነው፡፡ እንዲህ አይነቱ የፓርቲዎች አካሄድ<br />
ማንን እንደሚጠቅም ሳይታለም የተፈታ<br />
ነው፡፡ በምርጫ ወቅት የህዝብን ድምጽ<br />
በመከፋፈል የትኛውም ተቃዋሚ ፓርቲ<br />
አብላጫ ድምጽ በቀላሉ እንዳያገኝ በማድረግ<br />
ለገዥው ፓርቲ በተዘዋዋሪ ይጠቅመዋል፡<br />
፡ ስለሆነም እንዲህ ባለ ወቅት ተቃዋሚ<br />
ፓርቲዎች በሁለት አማራጮች ላይ<br />
ይንጠለጠላሉ፤ አንድም በቁጥር የበዙትን<br />
ፓርቲዎች ወደ አንድ ኃይል ማምጣት<br />
ላይ፣ አሊያም በተናጠልም ቢሆን በሀገር<br />
አቀፍ ደረጃ ጎልቶ ለመውጣት የሚያስችልን<br />
አቅም ፈጥሮ ገዥው ፓርቲንም ሆነ<br />
ሌሎች ተወዳዳሪዎችን ተፎካክሮ ለማሸነፍ<br />
የሚያስችልን እንቅስቃሴ ማድረግ፡፡<br />
በተግባር እንቅስቃሴ ላይ ያሉትን የተለያዩ<br />
ፓርቲዎች ወደ አንድ ኃይል አምጥቶ<br />
ወደ ምርጫ መግባት በባለፉት የምርጫ<br />
ተሞክሮዎቻችን ላይ አይተናል፤ (ቅንጅትን<br />
በ97፣ መድረክን በ2002 መጥቀስ ይቻላል፡፡<br />
) ያለፉት ሂደቶችና ተሞክሮዎች የራሳቸው<br />
ጥንካሬና ድክመት እንደነበረባቸው መካድ<br />
አይቻልም፡፡ ያም ሆነ ይህ ግን አሁን<br />
ሌላ የታሪክ ምዕራፍ ላይ እንገኛለን፡<br />
፡ ቀደም ብዬ እንደጠቀስኩት ምርጫ<br />
2007 እየደረሰ ነው፡፡ ስለሆነም አሁን<br />
ፓርቲዎች የበለጠ ለስራ የሚነሱበት ጊዜ<br />
ነው፤ በተናጠልም፣ በትብብርም፡፡ ከዚህ<br />
ጋር ተያይዞ በዚህ ሰሞን ስለ ፓርቲዎች<br />
ውህደትም የሚያነሱት በዝተዋል፡፡ ይህን<br />
የውህደት ጉዳይ እንደሚከተለው ለማየት<br />
እንሞከራለን፡፡<br />
ውህደት እንዴት?<br />
በአጭሩ ውህደት አንድ መሆን ማለት<br />
ነው፡፡ ከውህደት በፊት ያለው የተናጠል<br />
ህጋዊ ህልውና አክትሞ አዲስ ፓርቲ<br />
በአንድ ላይ መመስረት ነው ውህደት፡<br />
፡ አንድ ለመሆን ደግሞ፣ አንድ ለመሆን<br />
የሚያስችሉ ሁኔታዎች መኖር አለባቸው፡<br />
፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለመዋህድ የፖለቲካ<br />
ፕሮግራማቸው መመሳሰልና መቀራረብ<br />
ይኖርበታል፡፡ ከዚህም በላይ ግን ፓርቲዎቹ<br />
ለመዋህድ ፍላጎት ማሳየት የግድ ነው፤<br />
በውህደቱ ሂደትና ከውህደት በኋላ<br />
ስለሚኖረው እንቅስቃሴም የተሻለ መስራት<br />
እንደሚችሉ ሊያምኑበት ይገባል፡፡ በዚህም<br />
ማን ከማን ጋር መዋህድ እንደሚችል<br />
ካላቸው የፖለቲካ ፕሮግራም፣ የውህደት<br />
ፍላጎትና በመዋህዳቸው ሊያመጡት<br />
የሚችሉትን ውጤት ገምግመው፣ ወይ<br />
ወደ ውህደት ይገባሉ አሊያም በራሳቸው<br />
መስመር ጠንክረው ለመስራት ውሳኔ<br />
ያስተላልፋሉ፡፡<br />
ከሰሞኑ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት<br />
ድርጅት (መኢአድ) እና አንድነት<br />
ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት)<br />
በአስቸኳይ ለመዋህድ እየሰሩ እንደሆነ<br />
ገልጸዋል፡፡ ፓርቲዎቹ ጥር 25 ቀን 2006<br />
ዓ.ም መአህድ/መኢአድ የተመሰረተበትን<br />
22ኛ አመት በዓል በጽ/ቤቱ ባከበረበት ወቅት<br />
እንደገለጹት፣ ሁለቱ ፓርቲዎች በፍጥነት<br />
ወደ ውህደት ለመምጣት መወሰናቸውን<br />
በይፋ በመሪዎቻቸው በኩል ግልጽ<br />
አድርገዋል፡፡ የመኢአድ ፓርቲ ፕሬዚዳንት<br />
አቶ አበባው መሐሪ ፓርቲያቸው መኢአድ<br />
ከአንድነት ፓርቲ ጋር መዋሃድ ፍላጎቱ<br />
መሆኑን ተናግረዋል፡፡<br />
በተመሳሳይ በቀድሞ ፓርቲያቸው 22ኛ<br />
አመት ክብረ በዓል ላይ የተገኙት የአንድነት<br />
ፓርቲ ፕሬዚዳንት ኢ/ር ግዛቸው ሺፈራው<br />
በበኩላቸው ፓርቲያቸው ከመኢአድ ጋር<br />
መዋሃድ ፍላጎቱ መሆኑን ገልጸው፣<br />
በ15 ቀናት ውስጥ ውህደቱ እውን ሊሆን<br />
እንደሚችልም ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡<br />
ፓርቲዎቹ ይህን ይበሉ እንጂ (በዕለቱ<br />
በነበረው የመድረክ ሞቅታ እንዳይሆን<br />
እሰጋለሁ) በዚህ ፍጥነት ሊዋሀዱ<br />
የሚችሉበት ሁኔታ ውስጥ እንዳልሆኑ<br />
ጠቋሚ ምልክቶች መኖራቸውን መካድ<br />
አይቻልም፡፡<br />
ውህደት መቼ?<br />
ውህደት ምርጫ ስለቀረበ የሚከናወን<br />
የይድረስ ይድረስ ስራ እንዳልሆነ እሙን<br />
ነው፡፡ በተቃራኒው ግን በሀገራችን የነበሩ፤<br />
ያሉ ፓርቲዎች ውህደት የሚታያቸው<br />
ምርጫ ሲቃረብ መሆኑ አለመታደል ነው፡፡<br />
አንዳንዶቹ ሂደቱን ቀድመው ቢጀምሩትም<br />
ሲያጓትቱ ሲያጓትቱ እስከ ምርጫ መቃረቢያ<br />
ድረስ ያደርሱታል፡፡ የመኢአድና የአንድነት<br />
ውህደት እውን ቢሆን የሚወድ ብዙ ነው፡<br />
፡ ዳሩ ግን ውህደቱ መሆን የነበረበት<br />
(በእውነት ኢ/ር ግዛቸው እንዳሉት በ15<br />
ቀናት ውስጥ የሚከናወን ከሆነ ወይም<br />
ቢሆን ኖሮ) እንዲህ በሩጫ አሁን ላይ<br />
አይደለም፤ (በ15 ቀናት ውስጥ የሚደረግ<br />
ውህደት የፖለቲካ ፓርቲዎች ሳይሆን….)፡<br />
፡ ይህ ውህደት ከምርጫ 2002 ማግስት<br />
ቢሆን በተገባ ነበር፡፡<br />
ውህደት በተናጠል በውጠ-ፓርቲ ትግል<br />
ፈተና ውስጥ የገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎች<br />
መሪዎች ከቀውስ ማምለጫ ወይም አጀንዳ<br />
ማስቀየሻ ሊሆን አይገባም፡፡ በተጨማሪም<br />
አንድ ፓርቲ ከገጠመው የገንዘብ እጥረት<br />
አሊያም የቢሮ ኪራይ ችግር ለመውጣት<br />
ዘው ብሎ የሚገባበት ጉዳይ መሆን<br />
አይኖርበትም፡፡ በሩጫ የሚደረግ ውህደት<br />
ውጤቱ ምን ሊሆን እንደሚችል ለማንም<br />
የተሰወረ አይሆንም፡፡<br />
እናም ውህደት በቂ ጊዜ ወስዶ መጤን<br />
ያለበት ትልቅ የፖለቲካ ስራ ነው፡፡<br />
እርግጥ ነው ህዝቡ ፓርቲዎቹ እንዲዋህዱ<br />
ይፈልጋል፡፡ ከዚህ በላይ ግን አብዛኛው<br />
ህዝብ ፓርቲዎች ተዋህደው እንዲዘልቁና<br />
ለውጥ እንዲያመጡ እንደሚሻ ግልጽ ነው፡<br />
፡ ለዚህ ደግሞ ከጅምሩ የሰከነ የውህደት<br />
ሂደት መኖሩ ግድ ይላል፡፡<br />
የውህደት ፈተናዎች<br />
የፖለቲካ ፓርቲዎችን ወደ ውህደት<br />
ማምጣት፣ ከውህደት በኋላም ተስማምቶ<br />
መቀጠል ትልቅ ፈተና አለው፡፡ በተለይም<br />
እንዲህ በአጭር ጊዜ ውህደትን እናመጣለን<br />
ብለው ሰርጋቸውን ከሚያፋጥኑ ሰዎች<br />
ወደ ፊት የሚሆነውን በስጋት መመልከት<br />
ግርምትን የሚፈጥር ጉዳይ አይሆንም፡<br />
፡ በተዋሃጆቹም በኩል የእነቶሎ ቶሎ<br />
ቤት…እንዳይሆን መጠንቀቁ የሚበጅ ነው፡<br />
፡ ምርጫ ስለደረሰ ብቻ በፍጥነት ውህደትን<br />
ማከናወን ሊኖረው የሚችለውን ፈተና<br />
ሊያስረሳን አይገባም፡፡ ሰርገኛ መጣ በርበሬ<br />
ቀንጥስ እንዳይሆን መጠንቀቁ የብልሆች<br />
ምርጫ ነው፡፡<br />
በእርግጥም ውህደት የጥቂት ግለሰቦች<br />
ወይም የፖለቲካ ፓርቲዎች መሪዎች<br />
ፍላጎትና ተግባር ብቻ አይደለም፡፡ ከዚያ<br />
ይልቅ የሚዋሃዱት ፓርቲዎች አባላት<br />
(ጠቅላላ ጉባኤ በሚገባ ተወያይቶበት<br />
ውሳኔ ማሳለፍን ይጠይቃል፤) በየደረጃው<br />
ሰፊ ጊዜ ሰጥተው ጉዳዩን ሊወያዩበትና<br />
ሊያጤኑት ግድ ይላል፡፡ ይህን ለማድረግ<br />
የሚያስችላቸው ጊዜም ሊሰጣቸው<br />
እንደሚገባ እሙን ነው፡፡ በሌላ አነጋገር<br />
ውህደቱ ከጅምሩ እሰከ ፍጻሜው አባላትንም<br />
ማዕከል ያደረገ መሆን ይኖርበታል፡፡ ይህ<br />
ሳይሆን ቀርቶ ውህደቱ የጥቂቶች ስራ<br />
ከሆነ፣ አንድም ውህደቱ እውን አይሆንም፣<br />
እውን ከሆነም ዘላቂነቱ አጠራጣሪ ከመሆን<br />
አይድንም፡፡<br />
የውህድ ፓርቲው መሪ<br />
ሌላው ፈተና ውህደቱ ከተፈጸመ በኋላ<br />
የውህድ ፓርቲው (አዲሱ ፓርቲ) መሪ<br />
ማን ይሁን የሚለው ጉዳይ ነው፡፡ የዚህ<br />
ፈተና ምንጭ ውህደቱን ከመሰረቱት<br />
ፓርቲዎች ወገን ሁሉም የቀድሞ ፓርቲው<br />
መሪ፣ የአዲሱ ውህድ ፓርቲ መሪም<br />
ሆኖ እንዲዘልቅለትና ቡድናዊ ጥቅሙን<br />
እንዲያስከብርለት የመፈለጉ ጫና ነው፡፡<br />
በዚህም ሁሉም የየራሱን የቀደመ የትግል<br />
ታሪክና የአደረጃጀት ስፋት እያነሳ ስልጣኑ<br />
እንደሚገባው መሞገቱ ስለማይቀር ነው፡፡<br />
እንዲህ አይነቱ ጉዳይ ደግሞ ማን የተሻለ<br />
መምራት ይችላል ሳይሆን፣ ማን የውህድ<br />
ፓርቲው መሪነት ይገባዋል ወደሚል<br />
ሰንካላ ምክንያት ይገፋናል፡፡<br />
በተመሳሳይ ውህደቱ ከሚከናወንበት<br />
ወቅት አንስቶ፣ ውህደቱ ሊያመጣባቸው<br />
የሚችለውን ከጥቅማ ጥቅምና ስልጣን<br />
ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን ማጣት በማጤን<br />
ቅሬታ የሚሰማቸው ግለሰቦችም ሌላኛዎቹ<br />
ፈተናዎች መሆናቸው የማይቀር ነው፡<br />
፡ ከሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ<br />
ፓርቲዎች ወደ አንድ ሲመጡ፣ ቀድሞ<br />
በተናጠል የነበረውን የስራ አስፈጻሚ ያህል<br />
ቁጥር ሊያካትት አይችልም፡፡ በዚህ ጊዜ<br />
ተቀናሾች መኖራቸው ግድ ነው፤ እዚህ<br />
ጋር የሚነሳው ጉዳይ የመቀነሻ መስፈርቶቹ<br />
ናቸው፡፡ ያም ሆነ ይህ በአዲሱ ፓርቲ<br />
የሚደረገው የስልጣን ሽግሽግ በውህደት<br />
ወቅትና ከውህደት በኋላ ከሚገጥሙ<br />
ፈተናዎች መካከል መሆኑ የማይቀር ነው፡፡<br />
በሌላ በኩል ደግሞ ከውህደት በኋላም፣<br />
ከግል የስልጣን ጥማቸው ጋር በተገናኘ<br />
በስልጣን ተዋረድ ውስጥ ሁለተኛ ሰው<br />
ሆነው ለመስራት የማይፈልጉና ሁሌም ከኔ<br />
በላይ ላሳር ባዮች አይጠፉም፡፡ በዚህም፣<br />
እንዲህ አይነት ግለሰቦች አንዴ ከፖለቲካ<br />
ሲርቁ፣ ሌላ ጊዜ ያችኑ የመሪነት ቦታ<br />
ሲሰጣቸው ወደ መድረኩ ብቅ የሚሉ<br />
ናቸው፡፡ የእነዚህ ግለሰቦች የስልጣን ጥም<br />
የመሪነት ቦታ የነፈጋቸውን ፓርቲ ለቅቀው<br />
ወደ ሌላ ፓርቲ እስከመሄድ የሚያደርሳቸው<br />
ነው፡፡ ስለሆነም እነዚህን መሰል ግለሰቦች<br />
ዛሬ ስለውህደት አብዝተው ቢሰብኩም<br />
ያችኑ የመሪነት ቦታ የሚያሳጣቸው ጉዳይ<br />
ሲመጣ ሲያቀነቅኑት የነበረውን ዓላማ<br />
ረስተው የውህደቱ እንቅፋት ከመሆን<br />
ላይመለሱ ይችላሉ፡፡<br />
ደካማ የቀደመ የፖለቲካ ፓርቲዎች ውህደት<br />
ተሞክሮ ያለን ከመሆኑ ጋር ተያይዞ<br />
(በቅንጅቱ መፍረስ የተፈጠረ መንፈስን<br />
ማስታወስ ይበቃል፤) በህዝቡ ዘንድ ያለው<br />
ተስፋ የመቁረጥ ስሜትም እንደ አንድ ሌላ<br />
ፈተና ሊወሰድ የሚችል ነው፡፡ ፈጥኖ ወደ<br />
ውህደት የመግባትን ያህል ከውህደት በኋላ<br />
ተስማምቶ የመቀጠሉ ፈተናም ከባድ ነው፡<br />
፡ ስለሆነም መዋሃዱ መልካም ሆኖ፣ ነገር<br />
ግን አሁንም ከውህደት በፊት መሰራት<br />
ያለባቸው የቤት ስራዎች በጊዜ ከተከናወኑ<br />
በኋላ ቢሆን የተሻለ ውጤት ይኖረዋል፡፡<br />
አሁን ላይ ውህደት ወይስ ትብብር?<br />
ቀደም ብሎ እንደተጠቀሰው ውህደትን<br />
ለማከናወን የተዋሃጅ ፓርቲዎች ፕሮግራም<br />
ተመሳሳይ ወይም ተቀራራቢ መሆን<br />
ይኖርበታል፡፡ በዚህም አንድ ፓርቲ ከሌላው<br />
ጋር ለመዋሃድ መሰሉን ወይም ቢጤውን<br />
መፈለግ ግድ ይለዋል፤ ይህም የሚሆነው<br />
የሌላኛው ፓርቲ ፍላጎት ሲጨመርበት<br />
ነው፡፡ እናም ውህደት አግላይ ጎንም<br />
እንዳለው መገንዘብ ይቻላል፡፡ ለአብነትም<br />
የመኢአድ ሊቀመንበር አቶ አበባው መሐሪ<br />
የፓርቲያቸውን አቋም በሚከተለው መልኩ<br />
ገልጸውታል፡፡<br />
‹‹መኢአድ በኢትዮጵያ አንድነት ላይ<br />
ከማያምኑ የብሄር (የጎሳ) የፖለቲካ<br />
ድርጅቶች፣ በኢትዮጵያ አንድነት ላይ<br />
አልደራደርም በማለት፣ በውህደት ደረጃ<br />
አብሮ ለመስራት እቸገራለሁ የሚለው በቂ<br />
ምክንያት ስላለው ነው፡፡›› (አንድነት ከአረና<br />
ትግራይ ጋር ለመዋሀድ ንግግር መጀመሩ<br />
የሚታወቅ ነው፡፡ ታዲያ መኢአድ በአንድነት<br />
በኩል የመጣውን አረና ትግራይን እንዴት<br />
ሊያደርገው ይሆን?) ያም ሆነ ይህ ጉዳዩ<br />
የሚያሳየን የውህደትን አግላይነት ነው፡፡<br />
ከመኢአድ አቋም ለመረዳት እንደሚቻለው<br />
ፓርቲው ለውህደት በሩን የሚከፍተው<br />
ጠንካራ ጥበቃዎችን ከፊት አቁሞ ነው፡<br />
፡ ስለሆነም ውህደት የራሱ ጠንካራ ጎኖች<br />
እንዳሉት ሆኖ፣ እንደ አሸን የፈሉትን<br />
የፖለቲካ ድርጅቶች በጋራ አስተባብሮ ወደ<br />
አንድ የማምጣቱ ነገር ውስን መሆኑን<br />
ነው፡፡<br />
በአብዛኛው የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች<br />
የጋራ የሆነ የሚታገሉት ኃይል አላቸው፤<br />
እሱም ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ ነው፡<br />
፡ እነዚህ ፓርቲዎች የየራሳቸው የተለያየ<br />
ዓላማን አንግበው የሚንቀሳቀሱ ቢሆኑም<br />
የወል ጉዳይ እስካላቸው ድረስ ግን መተባበር<br />
ወደ ገፅ 6 ይዞራል