Neger Ethiopia Issue 2
Neger Ethiopia Issue 2
Neger Ethiopia Issue 2
Create successful ePaper yourself
Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.
13የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2<br />
ነገረ-ኢትዮጵያ<br />
መመረጥ በሌላው ድክመት<br />
ሳይሆን በራስ ጥንካሬ<br />
ታምራት ታረቀኝ<br />
ፓርቲ የሚመሰረተው ለሀገር ይበጃሉ<br />
ተብሎ የታመነባቸው ፖለቲካዊ፣<br />
ኢኮኖሚዊና ማህበራዊ ዓላማዎች<br />
ተቀርጸውና እቅድ ተዘጋጅቶ<br />
የአፈጻጸም ስልትም ተነደፎ ነው፡፡<br />
አንድ ፓርቲ የሚኖሩት ሁለት ዋንኛ<br />
ሰነዶች ፕሮግራምና መተዳደሪያ<br />
ደንብም የሚያሳዩት ይህንኑ<br />
ነው፡፡ ፕሮግራሙ ዓላማውን<br />
መተዳደሪያ ደንቡ የአሰራር ሥልቱን<br />
ያመለክታሉ፡፡ ፓርቲው በፕሮግራሙ<br />
የሰፈረውን ዓላማውን ገቢራዊ<br />
ማድረግ የሚችለው የመንግሥትነት<br />
ሥልጣን ሲያገኝ ነው፡፡ ስለዚህም<br />
ነው የፖለቲካ ፓርቲ ዋንኛ ትግል<br />
የሥልጣን ጥያቄ የሚሆነው፡፡<br />
ለዓላማው ከግብ መድረስ<br />
የሚታገልበትን መንገድ ሠላማዊ<br />
ያደረገ ፓርቲ የሥልጣን ጥያቄውን<br />
ለማሳካት የሚጠቀምበት አንድና<br />
ብቸኛ መንገድ ደግሞ ምርጫ ነው፡<br />
፡ ነጻ ትክክለኛና ወቅታዊ ምርጫ፡<br />
፡ ይህ ዓይነቱ ምርጫ እውን<br />
ሊሆን የሚችለውም ዴሞክራሲያዊ<br />
ሥርዓት በአስተማማኝ መገንባት<br />
ሲቻል፣ አልያም በሥልጣን<br />
ላይ ያለው መንግስት አጠቃላይ<br />
ሁኔታዎችን ተገንዝቦ ራሱን<br />
በመለወጥ ወይንም በውስጥና<br />
በውጪ ተጽእኖ ተንበርክኮ ዓለም<br />
አቀፍ መስፈርቶችን የሚያሟላ<br />
ምርጫ ለማካሄድና ውጤቱንም<br />
በጸጋ ለመቀበል ሲዘጋጅ ነው፡፡<br />
ስለሆነም አንድ ፓርቲ ዓላማውን<br />
ተፈጻሚ ለማድረግ የሚያስፈልገውን<br />
ሥልጣን በትክክልና በአስተማማኝ<br />
ሁኔታ ለመጨበጥ በሀገሪቱ<br />
አስተማማኝ የዴሞክራሲያዊ<br />
ሥርዓት መሰረት እንዲጣል ይህ<br />
ካልሆነም ነጻና ፍትሀዊ ምርጫ<br />
ለማካሄድ የሚያሰችሉ ሁኔታዎች<br />
እንዲሟሉ መታገል ቀዳሚ ተግባሩ<br />
ይሆናል፡፡<br />
በምርጫው ማግሥት ውጤቱ<br />
በአሳዛኝ ሁኔታ ቢበላሽም ቅንጅት<br />
ከዚህ አንጻር በየታሪክ ወቅቶች<br />
የሚነሳ ተግባር አከናውኗል፡፡<br />
ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት አልነበረም፣<br />
ምርጫ ቦርድ አልተለወጠም፣<br />
የፖለቲካ ምህዳሩ ጠቧልና<br />
ከኢህአዴግ ጋር ካላተደራደርን ብሎ<br />
ልመናም ሆነ ምልጃ አላቀረበም፡፡<br />
በአጭር ግዜ እንቅስቃሴ መታመንን<br />
አተረፈና የሠላማዊ ትግሉ ዋንኛ<br />
ኃይል የሆነውን ሕዝብ በአንድ<br />
መንፈስ በቁርጠኝነት ለማሰለፍ<br />
ቻለ፣ እናም ያንን በዚህ ትውልድ<br />
ድጋሜ ስለመታየቱ ማንም ርግጠኛ<br />
ሆኖ ሊናገር የማይችለውን ዓለምን<br />
«….ኢህአዴግ መስተጋብሩን<br />
ጠብቆ በማያቋርጥ ሁኔታ እያሸነፈ<br />
መቀጠል ያለበት ድርጅት ነው፤<br />
መስተጋብሩን ጠብቆ በማያቋርጥ<br />
ሁኔታ የህዝቡን ልብ ይዞ፣ የህዝብ<br />
ልብ የሚያዘው በማያቋርጥ የልማት<br />
እንቅስቃሴ፣ በማያቋርጥ የህዝቡን<br />
ፍላጎት የማርካት እንቅስቃሴ፣<br />
በማያቋረጥ መልካም አስተዳደርን<br />
የመገንባት እንቅስቃሴዎች ነው፣<br />
ከዚህ ውጪ የሚመጣ አይደለም፣<br />
በታሪክ ማሸነፍ አይቻልም፣ ማሸነፍ<br />
የሚቻለው በተጨባጭ ተግባር ብቻ<br />
ነው፣ ምርጫን በታሪክ ማሸነፍ<br />
አይቻልም…» በማለት የተናገሩት<br />
የኢህአዴግ የእለት ተእለት<br />
እንቅስቃሴ ምርጫን መሰረት ያደረገ<br />
መሆኑን ያሳያል፡፡<br />
በአንጻሩ አብዛኛዎቹ ተቀዋሚዎች<br />
ለመመረጥ ኢህአዴግ ሕዛባዊ<br />
ተቀባይነት ስለሌለው ነጻ ምርጫ<br />
ከተካሄደ ሕዝቡ ተቀዋሚዎችን ነው<br />
የሚመርጠው በማለት የራሳቸውን<br />
ጥንካሬ ገንብተውና አስተማማኝ<br />
አማራጭ ሆነው በመቅረብ ሳይሆን<br />
በኢህአዴግ ድክመት እንመረጣለን<br />
ብለው የሚያስቡ በመሆናቸው<br />
ምርጫ የሚታሰባቸው ምርጫ ቦርድ<br />
የግዜ ሰሌዳ ሲያወጣ ነው፡፡ በዛች<br />
አጭር ግዜ በሚደረግ ዝግጅት ወደ<br />
ምርጫ መግባት ደግሞ ውጤት<br />
አያመጣም፡፡ የተሸነፍነው ምርጫው<br />
ተጭበርብሮ ነው ምርጫ ቦርድ<br />
ገለልተኛ ባለመሆኑ ነው በደል<br />
ተፈጽሞብን ነው ወዘተ የሚሉ<br />
ክሶችም ከባዶ ጩኸትነት ሊያልፉ<br />
አይችሉም፡፡ አንደ ፕ/ር መድሀኔ<br />
ታደሰ አባባል ምርጫ ሁለት<br />
ዓመትም ሲቀረው ይጨበረበራልና<br />
ስለ ምርጫ የሚሰራው የቀደመው<br />
ምርጫ በተካሄደ ማግስት ጀምሮ<br />
መሆን አለበት፡፡ ይህ ጉዳይ ሲነሳ<br />
ቅንጅት በስድስት ወር ግዜ አይደለም<br />
ወይ ለማሸነፍ የበቃው የሚል<br />
መከራከሪያ ለማቅረብ የሚዳዳቸው<br />
አሉ፡፡ ይህን የሚሉ ፖለቲከኞች፣<br />
1. ከላይ የጠቀስኳቸው አፈ<br />
ጉባኤ አባዱላ ገመዳ እንዳሉት<br />
ምርጫን በተጨባጭ ተግባር እንጂ<br />
በታሪክ ማሸነፍ ማይቻል መሆኑን፣<br />
2. ቅንጅትን ለአሸናፊነት<br />
ያበቁትን መንገዶች ሁሉ ኢህአዴግ<br />
ከምርጫው ማግስት ጀምሮ<br />
የዘጋቸው መሆኑን፣<br />
3. በቅንጅት ምስረታና<br />
በምርጫ 97 መካከል የነበረው<br />
ግዜ ስድስት ወራት ብቻ ቢሆኑም<br />
ቅንጅትን የመሰረቱት በተለይ<br />
መኢአድና ኢዴፓ በረዥም ግዜ ሰፊ<br />
የምርጫ ስራ የሰሩና በቂ ዝግጅት<br />
ያደረጉ መሆኑን የዘነጉ ናቸው፡፡<br />
በምርጫ ውጤታማ ተወዳዳሪ<br />
ለመሆን የሚያስብ ፓርቲ በቅድሚያ<br />
በራሱ ጥንካሬ ለመመረጥ አልሞ<br />
የእለት ተእለት እንቀስቃሴው<br />
በመራጩ ልብ ውስጥ የሚገባና<br />
መታመንን የሚያስገኝለት እንዲሆን<br />
መስራት አለበት፡፡ ስለሆነም<br />
ሀገራዊና ዓለም ዓቀፋዊ ተጨባጭ<br />
ሁኔታዎችን ከፕሮግራሙ ጋር<br />
በማገናዘብ የአጭርና የረዥም ጊዜ<br />
እቅድ አዘጋጅቶ ለአፈጻጸሙም<br />
ግልጽ የሆነ የአሰራር ስልት ነድፎ<br />
የሚታይና የሚታመን እንቅሰቃሴ<br />
ማድረግ ይኖርበታል፡፡ በቢሮ<br />
ከትሞ፣ ከመግለጫ የዘለለ ተግባር<br />
ሳያሳዩ ከርሞ ሰዉ በኢህአዴግ<br />
አገዛዝ ተሰላችቷል ለውጥ ይፈልጋል<br />
በመሆኑም ተቀዋሚዎችን<br />
ይመርጣል በሚል እሳቤ ብቻ<br />
በምርጫ ሰሞን ብቅ በማለት ወንዝ<br />
በሌለበት ድልድይ አሰራለሁ አይነት<br />
ቅስቀሳ ማካሄድና ከእኔ በላይ ለሀገር<br />
አሳቢ ለህዝብ ሰሪ አይርኖም የሚል<br />
ፕሮፓጋንዳም እንበለው የምርጫ<br />
ቅሰቀሳ ማካሄድ ባዶ ጩኸት ነው<br />
የሚሆነው፡፡<br />
በየደረጃው የሚገኙት የፓርቲው<br />
መሪዎችና አባላት ማንነትና<br />
የተግባር እንዴትነት ብሎም<br />
በዕጩነት የሚያቀርባቸው<br />
ተወዳዳሪዎች ማንነት በምርጫው<br />
ውጤት ለማምጣት ወሳኝ ናቸው፡<br />
፡ እስከ መስዋዕትነት በሚጠይቀው<br />
ሠላማዊ ትግል ውስጥ የትወልድ<br />
ድርሻቸውን ሊያበረክቱ በበጎ<br />
ፈቃደኝነት የተሰለፉ አባላቱ የጠበቀ<br />
የዓላማ ትስሰርና የመንፈስ አንድነት<br />
አንዲሁም መተማመን ሲኖራቸው፣<br />
በመኖሪያ አካባቢያቸውም ሆነ<br />
በሥራ ቦታቸው በሥነ ምግባራቸው<br />
የተከበሩ በስራቸውም የተወደዱ<br />
ሲሆኑ የመራጩን ሕዝብ ቀልብ<br />
በመሳብ ፓርውን ለውጤት<br />
ያበቁታል፡፡ ይህ ሳይሆን ተቀዋሚ<br />
በመሆን ብቻ እንመረጣለን ብሎ<br />
ማሰብ ምርቻን በታሪክ ማሸነፍ<br />
እንደማይቻል ያለመገንዘብ ነውና<br />
ምርጫ 2007 እንደ ምርጫ 2007<br />
እንዳይሆን ያሰጋል፡፡<br />
ፓርቲዎች በየግል ተጠናክረው<br />
በጋራ ተማምነው በስፋት መክረውን<br />
በረዥሙ አቅደው ሳይሆን ተባብረን<br />
ከታየን ሕዝቡ ይመርጠናል በሚል<br />
ብቻ በምርጫ ሰሞን የሚካሄድ<br />
የመተባበር ሆይ ሆይታም ጥንካሬ<br />
ፈጥሮ አስተማማኝ አማራጭ<br />
ሆኖ ከመቅረብ የሚነሳ ባለመሆኑ<br />
ለውጤት አያበቃም፡፡ እንደምንም<br />
ተደጋግፈን ከፊት ለፊታችን ያለውን<br />
ግዙፍ ተራራ መናድ የሚለው<br />
የኋላ መሰረት የዛሬ ጥንካሬ የፊት<br />
ራዕይ የሌለው ሥልጣንን ብቻ<br />
አስቦ የሚነሳ መደጋገፍ ፈጥረው<br />
ለምርጫ ቢቀርቡም የሚፈጥሩት<br />
መጎነታተል(በቅንጅትም<br />
በመድረክም የታየ ነው) ደካማ<br />
አቅማቸውን ይበልጥ ያዳክመውና<br />
ለኢህአዴግ አሸናፊነት ምቹ ሁኔታ<br />
ይፈጥሩለታል፡፡<br />
ዛሬ ትናንት አይደለም ነገሮች ተለዋውጠዋል፣ ጠንክሮ በመገኘት<br />
እንጂ በሌላው ድክመት ለመመረጥ ማለም ግዜ አልፎበታል፡<br />
፡ ኢህአዴግን ደካማ አድርጎ ማሰብም በራሱ ትልቅ ድክመት<br />
ይመስለኛል፡፡ በደቂቃ ውስጥ መረጃ ለሚሊዮኖች በሚደርስበት<br />
ዘመን በተግባር ሆኖ ሳይሆን በፕሮፓጋንዳ መስሎ በመቅረብ<br />
ለውጤት መብቃት የሚቻል አይደለም፡፡<br />
በየግላቸው ድርጅታዊ ብቃት<br />
ሳይፈጥሩ በጋራም በቅጡ<br />
መክረው የጋራ እቅድ ሳይነድፉና<br />
ሆነው ሳይሆን መስለው ለምርጫ<br />
በመቅረብ በጥረታቸው ሳይሆን<br />
በሕዝቡ ለውጥ ፈላጊነትና ታሪክ<br />
ሰሪነት ለአሸናፊነት ቢበቁ ውጤቱን<br />
አሰጠብቀው በስምምነት የሥልጣን<br />
ክፍፍል አድርገው በምርጫ ያገኙትን<br />
ውጤት ወደ ተግባር በመለወጥ<br />
ሕዝቡ በድምጹ የሰጣቸውን ኃላፊነት<br />
መወጣት መቻላቸው ያጠራጥራል፡<br />
፡ ምክንያቱም ወደ ምርጫ የገቡት<br />
ጥንካሬ ፈጥረው የህዝብን አመኔታ<br />
አትርፈው ሳይሆን በመተባበር ሽፋን<br />
በመሆኑ ነው፡፡<br />
አንድነቱ የጠነከረ፣ በሚያራምደው<br />
ዓላማ በእኩል ደረጃ እምነት<br />
ያለው፣ በፓርቲ ዲስፕሊንና በንጹህ<br />
ሰብአዊ ፍቅር የተሳሰረ፣ እሰከ<br />
መስዋእትነት አብሮ ለመዝለቅ<br />
የተማመነ ከአባለቱም ሆነ ከመራጩ<br />
ሕዝብ አመኔታን ያተረፈ አመራር<br />
እንዲሁም በዓላማው የጸና ሞራሉ<br />
የተገነባና በመንፈስ የጠነከረ አባል<br />
መኖር ለአንድ ፓርቲ ዓላማ<br />
መሳካትም ሆነ ተባብሮ በምርጫ<br />
ለመሰለፍ በእጅጉ ወሳኝ ናቸው፡<br />
፡ ይህ በምርጫ ለማሸነፍ ወሳኝ<br />
የሆነ የፓርቲ ጥንካሬ ማሳያ በአንድ<br />
ሰሞን የሚገነባ አለመሆኑ ምርጫን<br />
የረዥም ግዜ ስራ ከሚያደርጉት<br />
ምክንያቶች አንዱ ይሆናል፡፡<br />
በተለይ የፓርቲው አመራር በአደባባይ<br />
ስለ ፍቅር እየሰበከ በፓርቲው<br />
ውስጥ ጥላቻን የሚያነግስ ከሆነ፣<br />
ስለ አንድነት እያዜመ ተለያይቶ<br />
የሚቆም ከሆነ፣ ሥልጣን ላይ ካለው<br />
ፓርቲ ጋር መነጋገር እሻለሁ እያለ<br />
በሀሳብ ከሚለዩ የአመራር አባላትም<br />
ሆነ ጥያቄ ከሚያነሱ አባላት ጋር<br />
ለመነጋገር የማይደፍር ከሆነ፣<br />
ዘመናት ላስቆጠረው የሀገራችን<br />
ችግር ዋናው መፍትሄ ብሔራዊ<br />
እርቅ ነው ብሎ በፕሮግራሙ አስፍሮ<br />
ይህንኑ በአደባባይ እየተናገረና<br />
ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር<br />
የሚያስችል ጉባኤ አሰፈላጊነትን<br />
እየጠየቀ፣ በፓርቲው ውስጥ<br />
የሚፈጠሩ ጥቃቅን ልዩነቶችን<br />
በውይይት መፍታትና በእርቅ<br />
ማድረቅ የማይችል ከሆነ ወ.ዘ.ተ<br />
እንኳን በመራጩ ሕዝብ ዘንድ<br />
በአባላቱም መታመንና መከበርን<br />
ሊያተርፍ አይችልም፡፡ አመራሩ<br />
ካልታመነ ደግሞ ፓርቲው ሊታመን<br />
አይችልም፡፡ የማይታመን ደግሞ<br />
አይመረጥም፡፡<br />
ዛሬ ትናንት አይደለም ነገሮች<br />
ተለዋውጠዋል፣ ጠንክሮ በመገኘት<br />
እንጂ በሌላው ድክመት ለመመረጥ<br />
ማለም ግዜ አልፎበታል፡፡<br />
ኢህአዴግን ደካማ አድርጎ ማሰብም<br />
በራሱ ትልቅ ድክመት ይመስለኛል፡<br />
፡ በደቂቃ ውስጥ መረጃ ለሚሊዮኖች<br />
በሚደርስበት ዘመን በተግባር ሆኖ<br />
ሳይሆን በፕሮፓጋንዳ መስሎ<br />
በመቅረብ ለውጤት መብቃት<br />
የሚቻል አይደለም፡፡<br />
ፖለቲከኞቹ ከደረሰባቸውም<br />
ካደረሱትም መማር ባይችሉም<br />
ሕዝቡ ከሁሉም አቅጣጫ ከደረሰበትና<br />
ከሚደርስበት ችግር፣ በየጊዜውም<br />
ከሚያይና ከሚሰማው እንዲሁም<br />
21 ዓመታት ለውጥ ካላመጣውና<br />
መስዋዕትነቱ ግን ካልተቋረጠው<br />
ትግል ብዙ ተምሯል፡፡ ተፎካካሪ<br />
ፓርቲዎች ትግላቸው ለውጤት<br />
ባያበቃውም ዳፋቸው እያዳፋው ብዙ<br />
መከራ አይቷል፣ ስለሆነም ምንም<br />
ማድረግ ባይችል በሚታወቅበት<br />
ዝምታው ይሸኛል፡፡<br />
በመሆኑም ሕዝብን የሠላማዊ<br />
ትግሉ ተሳታፊ ብቻ ሳይሆን<br />
ባለቤት ለማድረግና በምርጫ 2007<br />
ለውጥ ለማምጣት ራስን አጥርቶና<br />
ወደ ገፅ 15 ይዞራል