06.03.2014 Views

Neger Ethiopia Issue 2

Neger Ethiopia Issue 2

Neger Ethiopia Issue 2

SHOW MORE
SHOW LESS

Create successful ePaper yourself

Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.

13የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅፅ 1 ቁጥር 2<br />

ነገረ-ኢትዮጵያ<br />

መመረጥ በሌላው ድክመት<br />

ሳይሆን በራስ ጥንካሬ<br />

ታምራት ታረቀኝ<br />

ፓርቲ የሚመሰረተው ለሀገር ይበጃሉ<br />

ተብሎ የታመነባቸው ፖለቲካዊ፣<br />

ኢኮኖሚዊና ማህበራዊ ዓላማዎች<br />

ተቀርጸውና እቅድ ተዘጋጅቶ<br />

የአፈጻጸም ስልትም ተነደፎ ነው፡፡<br />

አንድ ፓርቲ የሚኖሩት ሁለት ዋንኛ<br />

ሰነዶች ፕሮግራምና መተዳደሪያ<br />

ደንብም የሚያሳዩት ይህንኑ<br />

ነው፡፡ ፕሮግራሙ ዓላማውን<br />

መተዳደሪያ ደንቡ የአሰራር ሥልቱን<br />

ያመለክታሉ፡፡ ፓርቲው በፕሮግራሙ<br />

የሰፈረውን ዓላማውን ገቢራዊ<br />

ማድረግ የሚችለው የመንግሥትነት<br />

ሥልጣን ሲያገኝ ነው፡፡ ስለዚህም<br />

ነው የፖለቲካ ፓርቲ ዋንኛ ትግል<br />

የሥልጣን ጥያቄ የሚሆነው፡፡<br />

ለዓላማው ከግብ መድረስ<br />

የሚታገልበትን መንገድ ሠላማዊ<br />

ያደረገ ፓርቲ የሥልጣን ጥያቄውን<br />

ለማሳካት የሚጠቀምበት አንድና<br />

ብቸኛ መንገድ ደግሞ ምርጫ ነው፡<br />

፡ ነጻ ትክክለኛና ወቅታዊ ምርጫ፡<br />

፡ ይህ ዓይነቱ ምርጫ እውን<br />

ሊሆን የሚችለውም ዴሞክራሲያዊ<br />

ሥርዓት በአስተማማኝ መገንባት<br />

ሲቻል፣ አልያም በሥልጣን<br />

ላይ ያለው መንግስት አጠቃላይ<br />

ሁኔታዎችን ተገንዝቦ ራሱን<br />

በመለወጥ ወይንም በውስጥና<br />

በውጪ ተጽእኖ ተንበርክኮ ዓለም<br />

አቀፍ መስፈርቶችን የሚያሟላ<br />

ምርጫ ለማካሄድና ውጤቱንም<br />

በጸጋ ለመቀበል ሲዘጋጅ ነው፡፡<br />

ስለሆነም አንድ ፓርቲ ዓላማውን<br />

ተፈጻሚ ለማድረግ የሚያስፈልገውን<br />

ሥልጣን በትክክልና በአስተማማኝ<br />

ሁኔታ ለመጨበጥ በሀገሪቱ<br />

አስተማማኝ የዴሞክራሲያዊ<br />

ሥርዓት መሰረት እንዲጣል ይህ<br />

ካልሆነም ነጻና ፍትሀዊ ምርጫ<br />

ለማካሄድ የሚያሰችሉ ሁኔታዎች<br />

እንዲሟሉ መታገል ቀዳሚ ተግባሩ<br />

ይሆናል፡፡<br />

በምርጫው ማግሥት ውጤቱ<br />

በአሳዛኝ ሁኔታ ቢበላሽም ቅንጅት<br />

ከዚህ አንጻር በየታሪክ ወቅቶች<br />

የሚነሳ ተግባር አከናውኗል፡፡<br />

ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት አልነበረም፣<br />

ምርጫ ቦርድ አልተለወጠም፣<br />

የፖለቲካ ምህዳሩ ጠቧልና<br />

ከኢህአዴግ ጋር ካላተደራደርን ብሎ<br />

ልመናም ሆነ ምልጃ አላቀረበም፡፡<br />

በአጭር ግዜ እንቅስቃሴ መታመንን<br />

አተረፈና የሠላማዊ ትግሉ ዋንኛ<br />

ኃይል የሆነውን ሕዝብ በአንድ<br />

መንፈስ በቁርጠኝነት ለማሰለፍ<br />

ቻለ፣ እናም ያንን በዚህ ትውልድ<br />

ድጋሜ ስለመታየቱ ማንም ርግጠኛ<br />

ሆኖ ሊናገር የማይችለውን ዓለምን<br />

«….ኢህአዴግ መስተጋብሩን<br />

ጠብቆ በማያቋርጥ ሁኔታ እያሸነፈ<br />

መቀጠል ያለበት ድርጅት ነው፤<br />

መስተጋብሩን ጠብቆ በማያቋርጥ<br />

ሁኔታ የህዝቡን ልብ ይዞ፣ የህዝብ<br />

ልብ የሚያዘው በማያቋርጥ የልማት<br />

እንቅስቃሴ፣ በማያቋርጥ የህዝቡን<br />

ፍላጎት የማርካት እንቅስቃሴ፣<br />

በማያቋረጥ መልካም አስተዳደርን<br />

የመገንባት እንቅስቃሴዎች ነው፣<br />

ከዚህ ውጪ የሚመጣ አይደለም፣<br />

በታሪክ ማሸነፍ አይቻልም፣ ማሸነፍ<br />

የሚቻለው በተጨባጭ ተግባር ብቻ<br />

ነው፣ ምርጫን በታሪክ ማሸነፍ<br />

አይቻልም…» በማለት የተናገሩት<br />

የኢህአዴግ የእለት ተእለት<br />

እንቅስቃሴ ምርጫን መሰረት ያደረገ<br />

መሆኑን ያሳያል፡፡<br />

በአንጻሩ አብዛኛዎቹ ተቀዋሚዎች<br />

ለመመረጥ ኢህአዴግ ሕዛባዊ<br />

ተቀባይነት ስለሌለው ነጻ ምርጫ<br />

ከተካሄደ ሕዝቡ ተቀዋሚዎችን ነው<br />

የሚመርጠው በማለት የራሳቸውን<br />

ጥንካሬ ገንብተውና አስተማማኝ<br />

አማራጭ ሆነው በመቅረብ ሳይሆን<br />

በኢህአዴግ ድክመት እንመረጣለን<br />

ብለው የሚያስቡ በመሆናቸው<br />

ምርጫ የሚታሰባቸው ምርጫ ቦርድ<br />

የግዜ ሰሌዳ ሲያወጣ ነው፡፡ በዛች<br />

አጭር ግዜ በሚደረግ ዝግጅት ወደ<br />

ምርጫ መግባት ደግሞ ውጤት<br />

አያመጣም፡፡ የተሸነፍነው ምርጫው<br />

ተጭበርብሮ ነው ምርጫ ቦርድ<br />

ገለልተኛ ባለመሆኑ ነው በደል<br />

ተፈጽሞብን ነው ወዘተ የሚሉ<br />

ክሶችም ከባዶ ጩኸትነት ሊያልፉ<br />

አይችሉም፡፡ አንደ ፕ/ር መድሀኔ<br />

ታደሰ አባባል ምርጫ ሁለት<br />

ዓመትም ሲቀረው ይጨበረበራልና<br />

ስለ ምርጫ የሚሰራው የቀደመው<br />

ምርጫ በተካሄደ ማግስት ጀምሮ<br />

መሆን አለበት፡፡ ይህ ጉዳይ ሲነሳ<br />

ቅንጅት በስድስት ወር ግዜ አይደለም<br />

ወይ ለማሸነፍ የበቃው የሚል<br />

መከራከሪያ ለማቅረብ የሚዳዳቸው<br />

አሉ፡፡ ይህን የሚሉ ፖለቲከኞች፣<br />

1. ከላይ የጠቀስኳቸው አፈ<br />

ጉባኤ አባዱላ ገመዳ እንዳሉት<br />

ምርጫን በተጨባጭ ተግባር እንጂ<br />

በታሪክ ማሸነፍ ማይቻል መሆኑን፣<br />

2. ቅንጅትን ለአሸናፊነት<br />

ያበቁትን መንገዶች ሁሉ ኢህአዴግ<br />

ከምርጫው ማግስት ጀምሮ<br />

የዘጋቸው መሆኑን፣<br />

3. በቅንጅት ምስረታና<br />

በምርጫ 97 መካከል የነበረው<br />

ግዜ ስድስት ወራት ብቻ ቢሆኑም<br />

ቅንጅትን የመሰረቱት በተለይ<br />

መኢአድና ኢዴፓ በረዥም ግዜ ሰፊ<br />

የምርጫ ስራ የሰሩና በቂ ዝግጅት<br />

ያደረጉ መሆኑን የዘነጉ ናቸው፡፡<br />

በምርጫ ውጤታማ ተወዳዳሪ<br />

ለመሆን የሚያስብ ፓርቲ በቅድሚያ<br />

በራሱ ጥንካሬ ለመመረጥ አልሞ<br />

የእለት ተእለት እንቀስቃሴው<br />

በመራጩ ልብ ውስጥ የሚገባና<br />

መታመንን የሚያስገኝለት እንዲሆን<br />

መስራት አለበት፡፡ ስለሆነም<br />

ሀገራዊና ዓለም ዓቀፋዊ ተጨባጭ<br />

ሁኔታዎችን ከፕሮግራሙ ጋር<br />

በማገናዘብ የአጭርና የረዥም ጊዜ<br />

እቅድ አዘጋጅቶ ለአፈጻጸሙም<br />

ግልጽ የሆነ የአሰራር ስልት ነድፎ<br />

የሚታይና የሚታመን እንቅሰቃሴ<br />

ማድረግ ይኖርበታል፡፡ በቢሮ<br />

ከትሞ፣ ከመግለጫ የዘለለ ተግባር<br />

ሳያሳዩ ከርሞ ሰዉ በኢህአዴግ<br />

አገዛዝ ተሰላችቷል ለውጥ ይፈልጋል<br />

በመሆኑም ተቀዋሚዎችን<br />

ይመርጣል በሚል እሳቤ ብቻ<br />

በምርጫ ሰሞን ብቅ በማለት ወንዝ<br />

በሌለበት ድልድይ አሰራለሁ አይነት<br />

ቅስቀሳ ማካሄድና ከእኔ በላይ ለሀገር<br />

አሳቢ ለህዝብ ሰሪ አይርኖም የሚል<br />

ፕሮፓጋንዳም እንበለው የምርጫ<br />

ቅሰቀሳ ማካሄድ ባዶ ጩኸት ነው<br />

የሚሆነው፡፡<br />

በየደረጃው የሚገኙት የፓርቲው<br />

መሪዎችና አባላት ማንነትና<br />

የተግባር እንዴትነት ብሎም<br />

በዕጩነት የሚያቀርባቸው<br />

ተወዳዳሪዎች ማንነት በምርጫው<br />

ውጤት ለማምጣት ወሳኝ ናቸው፡<br />

፡ እስከ መስዋዕትነት በሚጠይቀው<br />

ሠላማዊ ትግል ውስጥ የትወልድ<br />

ድርሻቸውን ሊያበረክቱ በበጎ<br />

ፈቃደኝነት የተሰለፉ አባላቱ የጠበቀ<br />

የዓላማ ትስሰርና የመንፈስ አንድነት<br />

አንዲሁም መተማመን ሲኖራቸው፣<br />

በመኖሪያ አካባቢያቸውም ሆነ<br />

በሥራ ቦታቸው በሥነ ምግባራቸው<br />

የተከበሩ በስራቸውም የተወደዱ<br />

ሲሆኑ የመራጩን ሕዝብ ቀልብ<br />

በመሳብ ፓርውን ለውጤት<br />

ያበቁታል፡፡ ይህ ሳይሆን ተቀዋሚ<br />

በመሆን ብቻ እንመረጣለን ብሎ<br />

ማሰብ ምርቻን በታሪክ ማሸነፍ<br />

እንደማይቻል ያለመገንዘብ ነውና<br />

ምርጫ 2007 እንደ ምርጫ 2007<br />

እንዳይሆን ያሰጋል፡፡<br />

ፓርቲዎች በየግል ተጠናክረው<br />

በጋራ ተማምነው በስፋት መክረውን<br />

በረዥሙ አቅደው ሳይሆን ተባብረን<br />

ከታየን ሕዝቡ ይመርጠናል በሚል<br />

ብቻ በምርጫ ሰሞን የሚካሄድ<br />

የመተባበር ሆይ ሆይታም ጥንካሬ<br />

ፈጥሮ አስተማማኝ አማራጭ<br />

ሆኖ ከመቅረብ የሚነሳ ባለመሆኑ<br />

ለውጤት አያበቃም፡፡ እንደምንም<br />

ተደጋግፈን ከፊት ለፊታችን ያለውን<br />

ግዙፍ ተራራ መናድ የሚለው<br />

የኋላ መሰረት የዛሬ ጥንካሬ የፊት<br />

ራዕይ የሌለው ሥልጣንን ብቻ<br />

አስቦ የሚነሳ መደጋገፍ ፈጥረው<br />

ለምርጫ ቢቀርቡም የሚፈጥሩት<br />

መጎነታተል(በቅንጅትም<br />

በመድረክም የታየ ነው) ደካማ<br />

አቅማቸውን ይበልጥ ያዳክመውና<br />

ለኢህአዴግ አሸናፊነት ምቹ ሁኔታ<br />

ይፈጥሩለታል፡፡<br />

ዛሬ ትናንት አይደለም ነገሮች ተለዋውጠዋል፣ ጠንክሮ በመገኘት<br />

እንጂ በሌላው ድክመት ለመመረጥ ማለም ግዜ አልፎበታል፡<br />

፡ ኢህአዴግን ደካማ አድርጎ ማሰብም በራሱ ትልቅ ድክመት<br />

ይመስለኛል፡፡ በደቂቃ ውስጥ መረጃ ለሚሊዮኖች በሚደርስበት<br />

ዘመን በተግባር ሆኖ ሳይሆን በፕሮፓጋንዳ መስሎ በመቅረብ<br />

ለውጤት መብቃት የሚቻል አይደለም፡፡<br />

በየግላቸው ድርጅታዊ ብቃት<br />

ሳይፈጥሩ በጋራም በቅጡ<br />

መክረው የጋራ እቅድ ሳይነድፉና<br />

ሆነው ሳይሆን መስለው ለምርጫ<br />

በመቅረብ በጥረታቸው ሳይሆን<br />

በሕዝቡ ለውጥ ፈላጊነትና ታሪክ<br />

ሰሪነት ለአሸናፊነት ቢበቁ ውጤቱን<br />

አሰጠብቀው በስምምነት የሥልጣን<br />

ክፍፍል አድርገው በምርጫ ያገኙትን<br />

ውጤት ወደ ተግባር በመለወጥ<br />

ሕዝቡ በድምጹ የሰጣቸውን ኃላፊነት<br />

መወጣት መቻላቸው ያጠራጥራል፡<br />

፡ ምክንያቱም ወደ ምርጫ የገቡት<br />

ጥንካሬ ፈጥረው የህዝብን አመኔታ<br />

አትርፈው ሳይሆን በመተባበር ሽፋን<br />

በመሆኑ ነው፡፡<br />

አንድነቱ የጠነከረ፣ በሚያራምደው<br />

ዓላማ በእኩል ደረጃ እምነት<br />

ያለው፣ በፓርቲ ዲስፕሊንና በንጹህ<br />

ሰብአዊ ፍቅር የተሳሰረ፣ እሰከ<br />

መስዋእትነት አብሮ ለመዝለቅ<br />

የተማመነ ከአባለቱም ሆነ ከመራጩ<br />

ሕዝብ አመኔታን ያተረፈ አመራር<br />

እንዲሁም በዓላማው የጸና ሞራሉ<br />

የተገነባና በመንፈስ የጠነከረ አባል<br />

መኖር ለአንድ ፓርቲ ዓላማ<br />

መሳካትም ሆነ ተባብሮ በምርጫ<br />

ለመሰለፍ በእጅጉ ወሳኝ ናቸው፡<br />

፡ ይህ በምርጫ ለማሸነፍ ወሳኝ<br />

የሆነ የፓርቲ ጥንካሬ ማሳያ በአንድ<br />

ሰሞን የሚገነባ አለመሆኑ ምርጫን<br />

የረዥም ግዜ ስራ ከሚያደርጉት<br />

ምክንያቶች አንዱ ይሆናል፡፡<br />

በተለይ የፓርቲው አመራር በአደባባይ<br />

ስለ ፍቅር እየሰበከ በፓርቲው<br />

ውስጥ ጥላቻን የሚያነግስ ከሆነ፣<br />

ስለ አንድነት እያዜመ ተለያይቶ<br />

የሚቆም ከሆነ፣ ሥልጣን ላይ ካለው<br />

ፓርቲ ጋር መነጋገር እሻለሁ እያለ<br />

በሀሳብ ከሚለዩ የአመራር አባላትም<br />

ሆነ ጥያቄ ከሚያነሱ አባላት ጋር<br />

ለመነጋገር የማይደፍር ከሆነ፣<br />

ዘመናት ላስቆጠረው የሀገራችን<br />

ችግር ዋናው መፍትሄ ብሔራዊ<br />

እርቅ ነው ብሎ በፕሮግራሙ አስፍሮ<br />

ይህንኑ በአደባባይ እየተናገረና<br />

ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር<br />

የሚያስችል ጉባኤ አሰፈላጊነትን<br />

እየጠየቀ፣ በፓርቲው ውስጥ<br />

የሚፈጠሩ ጥቃቅን ልዩነቶችን<br />

በውይይት መፍታትና በእርቅ<br />

ማድረቅ የማይችል ከሆነ ወ.ዘ.ተ<br />

እንኳን በመራጩ ሕዝብ ዘንድ<br />

በአባላቱም መታመንና መከበርን<br />

ሊያተርፍ አይችልም፡፡ አመራሩ<br />

ካልታመነ ደግሞ ፓርቲው ሊታመን<br />

አይችልም፡፡ የማይታመን ደግሞ<br />

አይመረጥም፡፡<br />

ዛሬ ትናንት አይደለም ነገሮች<br />

ተለዋውጠዋል፣ ጠንክሮ በመገኘት<br />

እንጂ በሌላው ድክመት ለመመረጥ<br />

ማለም ግዜ አልፎበታል፡፡<br />

ኢህአዴግን ደካማ አድርጎ ማሰብም<br />

በራሱ ትልቅ ድክመት ይመስለኛል፡<br />

፡ በደቂቃ ውስጥ መረጃ ለሚሊዮኖች<br />

በሚደርስበት ዘመን በተግባር ሆኖ<br />

ሳይሆን በፕሮፓጋንዳ መስሎ<br />

በመቅረብ ለውጤት መብቃት<br />

የሚቻል አይደለም፡፡<br />

ፖለቲከኞቹ ከደረሰባቸውም<br />

ካደረሱትም መማር ባይችሉም<br />

ሕዝቡ ከሁሉም አቅጣጫ ከደረሰበትና<br />

ከሚደርስበት ችግር፣ በየጊዜውም<br />

ከሚያይና ከሚሰማው እንዲሁም<br />

21 ዓመታት ለውጥ ካላመጣውና<br />

መስዋዕትነቱ ግን ካልተቋረጠው<br />

ትግል ብዙ ተምሯል፡፡ ተፎካካሪ<br />

ፓርቲዎች ትግላቸው ለውጤት<br />

ባያበቃውም ዳፋቸው እያዳፋው ብዙ<br />

መከራ አይቷል፣ ስለሆነም ምንም<br />

ማድረግ ባይችል በሚታወቅበት<br />

ዝምታው ይሸኛል፡፡<br />

በመሆኑም ሕዝብን የሠላማዊ<br />

ትግሉ ተሳታፊ ብቻ ሳይሆን<br />

ባለቤት ለማድረግና በምርጫ 2007<br />

ለውጥ ለማምጣት ራስን አጥርቶና<br />

ወደ ገፅ 15 ይዞራል

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!