06.03.2014 Views

Neger Ethiopia Issue 2

Neger Ethiopia Issue 2

Neger Ethiopia Issue 2

SHOW MORE
SHOW LESS

You also want an ePaper? Increase the reach of your titles

YUMPU automatically turns print PDFs into web optimized ePapers that Google loves.

ነገረ-ኢትዮጵያ ቅፅ 1 ቁጥር 2 የካቲት 7 ቀን 2006 ዓ.ም. 6<br />

ውህደት ወይስ ትብብር...<br />

ይችላሉ ማለት ነው፡፡ ትብብር አቃፊ<br />

ነው፡፡ የጎሳ ፓርቲውም ሆነ ህብረ-<br />

ብሄራዊው ፓርቲ በጋራ ጉዳዮች ላይ<br />

ተባብረው ከመስራት የሚያግዳቸው<br />

ነገር ሊኖር አይችልም፡፡<br />

በዚህ ረገድ ሰማያዊ ፓርቲ ከማናቸውም<br />

ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ጋር በትብብር<br />

ለመስራት ፍላጎቱ እንደሆነ ሲገልጽ<br />

ይደመጣል፡፡ ፓርቲው እንደሚለው፣<br />

ከውህደት በፊት የሚቀድሙ የቤት<br />

ስራዎችን መስራት ተገቢ ነው፤<br />

ለዚህም ትብብር ከውህደት ይቀድማል<br />

የሚል አቋም አለው፡፡<br />

በእርግጥም አሁን ላይ የፖለቲካ<br />

ፓርቲዎች ተቀራርበው በበለጠ<br />

በትብብር በመስራት ኃይላቸውን<br />

ማጠናከር ይገባቸዋል፡፡ ይህ አሁን ላይ<br />

በትብብር የሚጀምሩት ግንኙነትም<br />

ቀስ በቀስ ወደ ውህደት ሊያመራቸው<br />

ይችላል፤ ለውህደት የሚያደርሱ<br />

ስራዎችንም በዚያው ደረጃ በደረጃ<br />

እያከናወኑ መሄድ ይቻላል፡፡ በዚህ<br />

መልኩ የሚመጣ ውህደትም ዘላቂ<br />

እንደሚሆን መገመት ይቻላል፡፡ ያም<br />

ካልሆነ ደግሞ በትብብር መስራትን<br />

በመቀጠል አቅምን አጎልብቶ ወደ<br />

መሪነት መሸጋገር ትክክለኛ አካሄድ<br />

ይሆናል፡፡<br />

ከ ገፅ 3 የዞረ<br />

ከጅጋ ቋሪት ያለው የትራንፖርት ችግር<br />

ተገልጋዮችን ለስቃይ መዳረጉ ተገለፀ<br />

ጅጋ:- በምዕራብ ጎጃም ዞን ከጅጋ ከተማ<br />

እስከ ቋሪት ያለው የትራንስፖርት<br />

አገልግሎት ችግር ህዝቡን እያሰቃየ<br />

ነው ሲሉ ተሳፋሪዎች ገለጹ፡፡<br />

አራትና አምስት እጥፍ ክፍያ<br />

እንድንከፍል እንገደዳለን ያሉት<br />

ተሳፋሪዎች ‹በህገ-ወጥነት ተመዘበርን መንግስት<br />

ስርዓት ሊያስይዝልን ይገባል› የሚል ጥያቄ ስንጠይቅ<br />

ካልፈለጋችሁ አለመሳፈር ትችላላችሁ የሚል መልስ<br />

ከመንግስት አካላት ይሰጠናል ሲሉ ቅሬታቸውን<br />

ገልጸዋል፡፡<br />

24 ሰው የመጫን አቅም ያላቸው የአረጁና የወላለቁ<br />

መኪኖች እስከ 104 ሰው ድረስ ሲጭኑ ለህዝብ<br />

ህይወት በመቆርቆር እርምጃ የሚወስድ የመንግስት<br />

አካል አለመኖሩ እጅግ አሳዛኝ ነው ያሉት ተሳፋሪዎቹ፣<br />

የዚህን ህዝብ ሰቆቃና እንግልት ለማን አቤት እንደምንል<br />

አናውቅም ብለዋል፡፡<br />

መንግስት የመደባቸው ትራፊክ ፖሊሶች እንዲሁም<br />

የመንገድና ትራንስፖርት ሠራተኞች ተሳፋሪው<br />

ምንም አይነት መብት እንደሌለው ጫና ከማሳደርና<br />

የተሳፋሪውን ሰቆቃ ከማራዘም ውጭ በምንም ዓይነት<br />

ሁኔታ ግዴታቸውን ሲወጡ አናይም ብለዋል፡፡<br />

ጥቂት የወላለቁና ከጥቅም ውጭ የሆኑ መኪኖች<br />

የተመደቡለት ይህ መስመር መንግስት የዘነጋውና<br />

አመቱን ሙሉ ተሳፋሪ ህዝብ የሚንገላታበት ቦታ ሆኗል<br />

ሲሉ ያነጋገርናቸው ተሳፋሪዎች ጨምረው ገልፀዋል፡፡<br />

ፋሽስት ገዳይ ባየር...<br />

ታውቋል! ቀጥሏል! ቀጥሏል! ቀጥሏል! ወራሪው<br />

በማንአህሎኝነት መንፈስ ተረጋግቶ ተቀምጧል!<br />

ጀግናው ተሰማ እርገጤ አሁን ከወራሪው<br />

ኃይል ሰፈር በጣም ተጠግቷል! ብዙም ሳይቆይ<br />

ተኩስ ከፈተበት! ወራሪው ኃይል የሚይዘውና<br />

የሚጨብጠውን አጥቷል! ሆኖም ለጥቂት<br />

ደቂቃዎች ተታኩሷል! ወዲያው ግን ፈርጥጧል!<br />

ከጨለንቆ ደብረ ሲና ገብቷል! የጀግናው አርበኛ<br />

ተሰማ እርገጤ ድል አድራጊነት አሁንም<br />

ተረጋገጠ! ይህ በታሪካችን የጥንታዊት ኢትዮጵያ<br />

የጀግኖች አርበኞች የትግልና ድል ቀጥታ ድምጽ<br />

ነው! ከሸዋ ጠቅላይ ግዛት ጨለንቆ ከተባለ<br />

የውጊያ ሜዳ! መስከረም 19 ቀን 1929 ዓ.ም!<br />

ይህ ለዛሬው ወር ተረኛ ትውልድ የተላለፈ<br />

የጀግኖች አርበኞች ኢትዮጵያን የማዳን ተጋድሎ<br />

ታሪክ ቀጥታ ድምጽ ነው! ከአርበኝነት ገድላችን<br />

የተወሰደ!<br />

መስከረም አልቋል፡፡ ጥቅምትም አልፏል! አሁን<br />

በህዳር ወር ውስጥ መሆናችን ይመዝገብልን!<br />

ጀግናው አርበኛ ተሰማ እርገጤ አሁን ጉደ<br />

በረት ወረዳ የፋሽስት ወራሪ ኃይል የመሸገበትን<br />

ቦታ በመስክ መረጃ ለይቷል! ወራሪው ኃይል<br />

ከመሸገበት መንደር ደረሷል! አርበኞች ምድብ<br />

የውጊያ መስመራቸውን ይዘዋል! ከጥቂት<br />

ጊዜያት በኋላ እሳት ይዘንባል! አርበኞች ወደ<br />

ምሽጉ ተጠግተዋል! በጣም ቀርበዋል! ጊዜ<br />

አላጠፉም! የቅድሚያ ተነሳሽነት ወስደዋል!<br />

ወዲያው ጦርነቱ ተጋግሎ ቀጠለ! ጀግናው አርበኛ<br />

ተሰማ እርገጤ በርካታ የፋሽስት ኢጣሊያ ወራሪ<br />

ኢትዮጵያ ለምን ...<br />

ለማጣፈጥ ሲባል አዲስ ሰበካ ተጀምሯል። እኛ<br />

የምናካሂደው ትጥቅ ትግል የማንዴላ አይነት<br />

ትጥቅ ትግል ነው የሚል ማጭበርበሪያ። ጦርነት<br />

ጦርነት ነው። ይህን አባባል የሚያስተጋባው<br />

ቡድን በአንድ በኩል ተከታዮቹ መከተላቸውን<br />

እንዲቀጥሉ ለማድረግ ሲሆን በሌላ በኩል<br />

ደግሞ ሰላማዊ ትግል ካደረሰበት ትኩሳት<br />

ለጊዜው እረፍት ለማግኘት በሰላማዊ ትግል<br />

ንድፈ አሳብ ተማሪዎች እና ደጋፋዊዎች ላይ<br />

የከፈተው የማሸማቀቅ የስነ ልቦና ጦርነት ነው።<br />

መለስ ዜናዊ በምርጫ 97 የተቃሚው አሳብ<br />

የህዝብ ድጋፍ እያገኘ መሄዱን ሲያስተውል<br />

ደጋፊዎቹን ለማረጋጋት እና ተቃዋሚውን<br />

ለማሸማቀቅ ኢንተርሃምዌይ እስከማለት ደረሶ<br />

እንደነበር አስታውሳለሁ። አምባገነኖች ብዙ<br />

ከ ገፅ 8 የዞረ<br />

ኃይል ተዋጊዎችን በጥቂት ጊዜያት ከአፈር ጋር<br />

አዋህዷቸዋል! ታላቅ ጦርነት ሆነ! ከኢትዮጵያ<br />

ጀግኖች አስራ ሁለት አርበኞች በዚሁ ጦርነት<br />

ተሰውተዋል፡፡ በጀግንነት ወደ ታሪክ ወርደዋል!<br />

ጦርነቱ ቀኑን ሙሉ ቀጥሎ ውሏል! በዚህ<br />

ጦርነት ጀግናው ተሰማ እርገጤ በትከሻው ላይ<br />

በሁለት ጥይት ተመትቶ ቆስሏል፡፡ ብዙ ደምም<br />

ፈስሶታል! ጀግናው ተሰማ እርገጤ እስከ ጦርነቱ<br />

ፍጻሜ ዘጠኝ ጊዜ መቁሰሉ ታውቋል! የጉደ በረት<br />

ጦርነት እስከ ሌሊት ድረስ ቀጥሏል! በዚሁ<br />

ጦርነት ሰባ አምስት የፋሽስት ኢጣሊያ ወራሪ<br />

ኃይል መኮንኖችና ወታደሮች ተገድለዋል!<br />

ቆራጡ አርበኛ ተሰማ እርገጤ በአምስቱ<br />

የፋሽስት ኢጣሊያ ወረራ ዓመታት የተዋጋባቸው<br />

የጦር ሜዳዎች በጣም ብዙ ናቸው! በዚህም<br />

መሰረት ጥር ወር በ1929 ዓ.ም ባደረገው ውጊያ<br />

በርካታ የወራሪው ተዋጊዎችን በሞት ቀንሷል!<br />

እንዲሁም በየካቲት ወር 1929 ዓ.ም በሞፈር<br />

ውሃ ላይ በተደረገው ጦርነት ብዙ ፋስስቶችን<br />

ገድሏል! በዚህ ብቻም አላበቃም! በመጋቢት ወር<br />

1929 ዓ.ም ገዘት በተባለ ቦታ ጦርነት አድርጎ<br />

በርካታ የወራሪው ኃይል አባላትን ደምስሷል!<br />

አሁንም በመቀጠል በሚያዚያ ወር 1929<br />

ዓ.ም በመንዝ ውስጥ ወይራ ገበያ በተባለ ቦታ<br />

የተደራጀውን የወራሪውን ኃይል ተዋጊ ድባቅ<br />

መትቷል! የጦር መሳሪያም ማርኳል! ጀግናው<br />

አርበኛ ተሰማ እርገጤ አሁንም በጽኑ የውጊያ<br />

ስነ-ልቦና ይስተዋላል! ቀጥሏል! ግንባሩን ሳያጥፍ<br />

ቀን ከሌት ይዋጋል! በዚህ ሂደት ሐምሌ 18<br />

ከ ገፅ 9 የዞረ<br />

ይላሉ። የሚሉት ሁሉ ግን ከአጭር ጊዜ<br />

መፍትሄነት ባሻገር አይረዳቸውም። ይሄም ያን<br />

አይነት የስነ ልቦና ጦርነት ነው። የአለም ህዝብ<br />

ለማንዴላ ክብር የለገሰው ጠበንጃ በማንሳቱ<br />

አይደለም። በሃውልቱም ላይ የሚጻፈው ጦረኛ<br />

መሆኑ አይደለም።<br />

ቤተሰቡም እስከ ልጅ ልጆቹ ድረስ በአደባባይ<br />

ስለማንዴላ የሚሰብኩት ሰላማዊነቱን እና<br />

በሰላማዊ መንገድ አፓርታይድን እንዳፈረሰ<br />

ነው። አፓርታይድ የፈረሰው በትጥቅ ትግል<br />

አይደለም። የደቡብ አፍሪካ የመጀመሪያው<br />

ጥቁር ፕሬዘዳንት ሊሆን የቻለው በትጥቅ<br />

ትግል አይደለም። ጥቁር እና ነጭ ደቡብ<br />

አፍሪካውያን በህብረት ያደረጉት ሰላማዊ<br />

ትግል መዘንጋት የለበትም። ታዋቂ ጥቁር እና<br />

እና 22 ቀን 1929 ዓ.ም ግንደ በረት ላይ ክልቤ<br />

በተባለ ቦታ ተዋግቶ ድል ማድረጉን የአርበኝነት<br />

ታሪኩ ያመለክታል፡፡ በመቀጠልም ሺኖ በተባለ<br />

ቦታ ተዋግቶ አኩሪ ውጤት አስመዝግቧል!<br />

ቆፍጣናው አርበኛ ተሰማ እርገጤ በመቀጠልም<br />

በሰላሌ አውራጃ ውስጥ ኩዩ ጊዮርጊስ በተባለ<br />

ቦታ ከወራሪው ኃይል ጋር ተዋግቶ ድል<br />

አስመዝግቧል! ለሁለት ቀናት በተካሄደው በዚሁ<br />

ጦርነት በርካታ የወራሪው ኃይል ተዋጊዎቹን<br />

መግደሉ ታውቋል! እንዲሁም መስከረም 12<br />

ቀን 1930 ዓ.ም ተዋግቶ ወራሪው ኃይል<br />

እንዲፈረጥጥ አድርጓል! በተመሳሳይ መልኩ<br />

መስከረም 15 ቀን 1930 ዓ.ም ተዋግቶ ድል<br />

ተቀዳጅቷል!<br />

ጅግናው አርበኛ ተሰማ እርገጤ እስከ ጦርነቱ<br />

ፍጻሜ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ውስጥ በወራሜ<br />

በላሎ ምድር በአይት በተጉለት ወረዳ አምባ<br />

ሞሻ፣ በከሴ ቆላ አቦ ጉር ህዳባይ፣ በላሎ<br />

ምድር ኪደር በምሐይና በአንጉቦላ ቀበሌዎች<br />

እየተዘዋወረ ከፍተኛ ጀብዱ ፈጽመዋል!<br />

የታወቀው ጀግና ተሰማ እርገጤ ከድል በኋላ<br />

የአምስት ዓመት የአርበኝነት ኒሻን ባለአምስት<br />

ዘንባባ ተሸልሟል! እንዲሁም የድል ኮከብ<br />

ሜዳይ አግኝቷል! በተመሳሳይ መልኩ የቅዱስ<br />

ጊዮርጊስ ሜዳይ ባለሁለት ዘንባባ ተሸልሟል፡፡<br />

ጀግናው የኢትዮጵያ ልጅ ተሰማ እርገጤ ከአባቱ<br />

ከባሻ እርገጤ ሀብተ-ገብርኤልና ከእናቱ ወይዘሮ<br />

ወለተ አረጋይ ጨድድ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት<br />

በይፋት ውስጥ ሐር አምባ በተባለ ቀበሌ በ1888<br />

ነጭ ደቡብ አፍሪካውያን አርቲስቶች የአለምን<br />

ህዝብ በአፓርታይድ ላይ ለማስተባበር<br />

ያደረጉት ቀጣይነት ያለው አለም አቀፍ<br />

ሰላማዊ ዘመቻቸው መዘንጋት የለበትም።<br />

ማንዴላን ለማስፈታት እና አፓርታይድን<br />

ለማስፈታት የአለም ህዝብ ያደረገው ሰላማዊ<br />

ትግል መዘንጋት የለበትም። በማንዴላ<br />

ሃውልት ላይ የሚጻፈው የጦር አበጋዝነቱ እና<br />

የገደለው ሰው ቁጥር ሳይሆን ማንዴላ ከእስር<br />

ቤት ከወጣ በኋላ የፈጸመው ነው።<br />

በመጨረሻ ወደ ኢትዮጵያ ልመለስ እና<br />

ጽሁፌን ልደምድም። ሰላማዊ ትግል ሰላማዊ<br />

ሰልፍ ማድረግ ብቻ አይደለም። ሰላማዊ<br />

ትግል በምርጫ መሳተፍ ብቻ አይደለም።<br />

ሰላማዊ ትግል በአደባባይ ወጥቶ መቃወም<br />

ዓ.ም ተወለደ፡፡ በልጅነቱ አማርኛ ተምሯል፡<br />

፡ ማይጨው ዘምቷል! ግዳጁን ተወጥቷል!<br />

ከማይጨው መልስ የይፋትን ህዝብ ለጦርነት<br />

አስተባብሯል! ቆፍጣናው ጀግና ተሰማ እርገጤ<br />

ሰኔ 23 ቀን 1964 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት<br />

ተለይቷል፡፡ ጀግናው ተሰማ እርገጤ በህይወት<br />

ዘመኑ ሰባት ልጆችን አፍርቷል፡፡ ጀግናው<br />

አርበኛ ተሰማ እርገጤ ከዚህ ዓለም በሞት ሲለይ<br />

ባህላዊ ወታደራዊ ማዕረጉ ደጃዝማች እንደነበር<br />

ታውቋል!<br />

ውድ የኢትዮጵያ ወጣት ሆይ በቀደምት<br />

የኢትዮጵያ ጀግኖች መስዋዕትነት ታፍራና<br />

ተከብራ የኖረችው ሀገራችን ተዋርዳለች! ሀገር<br />

ለመሸጥ ደላላ ኮሚሽን ተቋቁሟል! ስለዚህ<br />

ወጣቱ ትውልድ የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ<br />

ጠንቅቆ በማወቅ ህሊናዊ ሁኔታዎችን ለማሳደግ<br />

ሊነሳ ይገባል! እርግጥ ነው ሀገርን ጠብቆ<br />

በክብር ለመጪው ትውልድ ማስረከብ የዜጎች<br />

ሁሉ ግዴታ ይሆናል፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያን<br />

ከጠቅላላ ውድቀት ለማዳን በቁርጠኝነትና በዓላማ<br />

ጽናት በተግባር እንነሳ! ክብር ለቆራጡ አርበኛ<br />

ለደጃዝማች ተሰማ እርገጤ! ክብር በአምስቱ<br />

የፋሽስት ኢጣሊያ ወረራ ዓመታት በዱር<br />

በገደሉ ለወደቁ ጀግኖች! ክብር ዛሬም ከዕለታዊ<br />

ጥቅምና ጊዜያዊ ተድላ ርቀው ለኢትዮጵያ ነጻነት<br />

በመታገል ላይ ለሚገኙ ቆራጦች! ኢትዮጵያዊ<br />

ብሄርተኝነት ያሸንፋል!<br />

ብቻ አይደለም። ሰላማዊ ትግል እነዚህን ሁሉ<br />

ማድረግ ነው። በተጨማሪ ሰላማዊ ትግል<br />

ህዝብን የራሱ ነፃ አውጭ በማድረግ (1)<br />

በስልጣን ላይ የሚገኝን አምባገነን መንግስት<br />

አስወግዶ ህዝብን የመንግስት ስልጣን ባለቤት<br />

ማድረግን፣ (2) መፈንቅለ መንግስት ቢነሳ<br />

ትብብር መንፈግ፣ (3) እንደ ህውሃት/<br />

ኢህአዴግ ከጫካ ወይንም ከጎረቤት አገር<br />

(ኤርትራን ጨምሮ) ተነስቶ ልውረርህ የሚል<br />

ቡድን ቢመጣ ህዝባዊ መከላከል (Civil Resistance)<br />

ማድረግን ያካትታል። ሰላማዊ<br />

ትግልን በሚመለከት ግንዝቤያችን ሰፋ ያለ<br />

መሆን አለበት። የቀድሞው የመንግስት<br />

ሽግግር ባህላችን ደደብ ነው። ብልህ ሰዎች<br />

አይከተሉትም።<br />

እንዲሆን በማሰብ ፓርቲው ቀኑን መዘከር አስፈላጊ<br />

መሆኑን ያምናል ብለዋል፡፡ በዕለቱ በሁለቱም<br />

ፕሮግራሞች ላይ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ እንዲሳተፍ<br />

አቶ ብርሃኑ ጥሪ አቅርበዋል፡፡<br />

ሰማያዊ ፓርቲ በ2005 ዓ.ም ጣሊያኖች በወገኖቻችን<br />

ላይ ከፍተኛ በደል የፈጸመውን ሮዶልፍ ግራዚያኒ<br />

በትውልድ ከተማው ‹የጀግና› ሐውልት በማቆም<br />

ዕውቅና መስጠታቸውን በመቃወም ሰላማዊ የተቃውሞ<br />

ሰልፍ በአዲስ አበባ መጥራቱን ተከትሎ በቦታው የተገኙ<br />

አባላቱ ለእስር መዳረጋቸው የሚታወስ ነው፡፡<br />

በጎንደር በተካሄደው...<br />

ከ ገፅ 1 የዞረ<br />

ያስተባበሩት የአካባቢው የፓርቲው መዋቅር አካላት<br />

ደህንነቶች ለቤተሰቦቻቸው ደውለው እያስፈራሩዋቸው<br />

መሆኑን የፓርቲው የዞን ሰብሳቢ አቶ አግባው ሰጠኝ<br />

ለዝግጅት ክፍላችን ገልጸዋል፡፡<br />

ፓርቲው ጥር 25 በጎንደር ከተማ መስቀል አደባባይ<br />

በጠራው ሰልፍ፣ የኢትዮ-ሱዳን የድንበር ማካለል<br />

ሂደትን በተመለከተ መንግስት ለህዝብ ጉዳዩን ግልጽ<br />

እንዲያደርግና ሉዓላዊነትን እንዲያከብርና እንዲያስከብፈር<br />

መጠየቁ ይታወሳል፡፡

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!