10.08.2015 Views

ሥነምግባር

Guest - Ethiopian Review

Guest - Ethiopian Review

SHOW MORE
SHOW LESS
  • No tags were found...

Create successful ePaper yourself

Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.

ቅጽ 9 ቁጥር 4 ሐምሌ 2002 ዓ.ምየአዘጋጁ መልዕክት --------------------------- 2መልዕክቶቻችሁ ------------------------------- 3ክራሞት ---------------------------------------- 4<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምቆይታ ------------------------------------------ 6ከዚህም ከዚያም ------------------------------ 10ትኩረት --------------------------------------- 12መልካም ዜጋ -------------------------------- 16ፋይል ---------------------------------------- 20“በመሬት ዘርፍ ሕገ ወጥነትን ለመከላከል ከፍተኛእንቅስቃሴ እያደረግን ነው”የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርዋና ሥራ አስኪያጅክቡር አቶ መኩሪያ ኃይሌክሽን --------------------------------------- 22ሳይቃጠል በቅጠል -------------------------- 24ከ<strong>ሥነምግባር</strong> አውታሮች ------------------- 27ኪነጥበብ ------------------------------------ 29በፌደራል የ<strong>ሥነምግባር</strong> እና የፀረ-ሙስናኮሚሽን በ<strong>ሥነምግባር</strong> ትምህርትና ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት በየሦስት ወሩየሚታተምስልክ 011 5529100ፖ.ሳ.ቁ 34798/9ፋክስ 011 5536987ኢሜይል feacedu@ethionet.etድረ ገጽ www.feac.gov.et“ከሙስና በፀዳ እና የቅንነትን መርህ ተከትሎበመሥራት በተሰማሩበት መስክ ውጤታማመሆን ይቻላል።”ዶ/ር መሰለ ኃይሌስምንተኛው መደበኛ ጉባዔ በአሶሳ ከተማ ሲካሄድ2


የአዘጋጁ መልዕክትለሙስናና ለብልሹ አሠራር ይበልጥ ተጋላጭ ከሆኑ ዘርፎች መካከል የመሬት አስተዳደርአንዱ መሆኑን የተለያዩ ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡ በመሆኑም የፌደራል የ<strong>ሥነምግባር</strong> እናየፀረ-ሙስና ኮሚሽን በዚሁ ዘርፍ ላይ ትኩረት በማድረግ ከፍተኛ እንቅስቃሴ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ እያደረገም ይገኛል፡፡ ኮሚሽኑ በተለይ ከአዲስ አበባ ከተማ የመሬት አሰጣጥና ይዞታጋር በተያያዘ ለሙስና በር የሚከፍቱ ቀዳዳዎችን ለመድፈን ያስችል ዘንድ የአሠራር ሥርዓትጥናት በማካሄድ የመፍትሄ ሀሳብ አቅርቧል፡፡ በሙስና ወንጀል በተጠረጠሩት ላይ ደግሞምርመራ እያካሄደ ለሕግ የማቅረብ ተግባር አከናውኗል፡፡ በወንጀሉ የተገኘ ከፍተኛ መጠንያለው መሬት እንዲታገድ ያደረገበት ሁኔታም አለ፡፡ከዚሁ ጋር ተያይዞ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርስ የከተማውን የመሬት አሰጣጥና ይዞታከህገ ወጥነት ለመከላከል የወሰዳቸው ርምጃዎች ምን ይመስላሉ የሚል ጥያቄሊነሳ ይችላል፡፡ መጽሔታችን ለዚህ እና ለሌሎችም ተያያዥ ጥያቄዎች ምላሽየሚሰጥ ቃለ ምልልስ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስኪያጅ ከክቡር አቶመኩሪያ ኃይሌ ጋር አካሂዳለች፡፡ ቃለ ምልልሱ ቆይታ በተሰኘው አምዳችን ተስተናግዷል፡፡ከዚሁ የመሬት ጉዳይ ሳንወጣ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የፌደራል የ<strong>ሥነምግባር</strong> እናየፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከሕገ ወጥ የመሬት ወረራ ጋር በተያያዘ ያከናወናቸውን የሕግ ማስከበርሥራዎች የሚዳስስ ፅሁፍ በትኩረት ዓምዳችን ይዘን ቀርበናል፡፡<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምመልካም ዜጋ በተሰኘው ዓምዳችን ደግሞ መልካም ተሞክሯቸውን ያካፍሉን ዘንድ በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሠማሩ አንድ ባለሙያ አወያይተናል፡፡እያዝናኑ ትምህርት ይሰጣሉ ያልናቸውን እንደ ክሽን፣ ከዚህም ከዚያምና ኪነጥበብ የመሳሰሉዓምዶችንም እንደተለመደው አካተናል፡፡ መልካም ንባብ፡፡3


መልዕክቶቻችሁህብረተሰቡ የበኩሉን ድጋፍ ቢያደርግ!ፍትህ ብትዘገይም ውጤቷ ጣፋጭ ነው!<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምበሃገራችን እየተካሄደ የሚገኘው የፀረ-ሙስና ትግልየታለመለትን ግብ እንዲመታ የተለያዩ ህጎችን እየወጡ ለተግባራዊነታቸውም የተለያዩ ጥረቶች በመደረግላይ መሆናቸው ግልጽ ነው፡፡በመሆኑም ሚያዝያ 2002 ዓ.ም ባወጣችሁትየ“<strong>ሥነምግባር</strong>” መጽሄት ቆይታ አምድ ላይ ከፌሥፀሙኮ የሕግ አገልግሎት ኃላፊ ጋር የጥረቱ አካልስለሆነው የሃብት ማሳወቅና ማስመዝገብ ስራ የተደረገው ሰፋ ያለ ቃለምልልስ በጉዳዩ ዙሪያ የነበረኝንግንዛቤ ከማሳደጉም ባሻገር ኮሚሽኑ እያደረገ በሚገኘው ዘርፈ ብዙ የፀረ-ሙስና እንቅስቃሴ ላይ የህብረተሰቡ ድጋፍና ትብብር ወሳኝ መሆኑንም ያመላከተነበር፡፡ ስለዚህ ህብረተሰቡም ለስራው መሳካት በባለቤትነት ስሜት የሚጠበቅበትን አስተዋጽኦ ቢያበረክትመልካም ነው እላለሁ፡፡ዳኜ አባተ - ከባህርዳርበ“<strong>ሥነምግባር</strong>” መጽሄት ባለፉት ሁለት እትሞችበተከታታይ በ ”ፋይል” አምድ ስር በቀረበው ጽሁፍየተላለፈው መልዕክት እጅግ አስተማሪ ሆኖ አግኝቼዋለሁ፡፡ በጽሁፉ የቀረበው ባለታሪክ ባለማወቅ የሙሰኞችና ህገወጦች መሣሪያ በመሆን ለከባድ እንግልትየተዳረገ መሆኑ ስንቶች በተመሳሳይ ድርጊትእየተንገላቱ እንደሚገኙ እንዳስብ አስገድዶኛል፡፡ሆኖም በህገወጥነት የተፈፀመን ድርጊት ለማረምየሚወሰድ እርምጃ ተጨማሪ ህገወጥ ድርጊትመሆን እንደማይገባውና ፍትህ ሊዘገይ ይችላል ነገርግን እውነትና ንጋት እያደር ይጠራል ነውና የሚባለው ጊዜው ሲደርስ የሚሰጠው ውጤትምን ያህል አስደሳች እንደሆነ ከጽሁፉ ተረድቻለሁ፡፡ሃሰን ቶፊቅ - ከድሬደዋየሙሰኞች የመጨረሻ ፍርድ ለህብረተሰቡ ይፋቢደረግ!የፌሥፀሙኮ በየሶስት ወሩ በሚያሳትመው “<strong>ሥነምግባር</strong>” መጽሄት ስለሙስና ወንጀሎች እና በሙሰኞቹም ላይ በፍርድ ቤት ስለተላለፉ የቅጣት እርምጃዎችየሚቀርቡት ጽሁፎች አስተማሪና በጉዳዩ ዙሪያ ግንዛቤን የሚያሳድጉ መሆናቸው አያጠራጥርም፡፡ ሆኖም ኮሚሽኑ በሙስና ወንጀል ተጠርጣሪ ስለሆኑ ግለሰቦች በብዙሃን መገናኛ በተለይ በቴሌቪዥንና በሬድዮየተጠርጣሪዎችን አድራሻ ለማወቅ የአፋልጉን ማስታወቂያ እንደሚያወጣ ሁሉ በግለሰቦቹ ላይ ፍርድ ቤትያስተላለፈውን ውሳኔ ህብረተሰቡ በስፋት የሚያገኝበትን መንገድ ቢያመቻች የሚኖረው አስተማሪነት የጎላ ነው እላለሁ፡፡አሸናፊ መልካሙ - ከአ.አ.ለጥናቱ ትኩረት ቢሰጥኮሚሽናችሁ በኢትዮጵያ ስኳር ልማት ኤጀንሲ የሀገር ውስጥ የስኳር ጨረታ ላይ ያካሄደውን ጥናትአስመልክቶ በ “<strong>ሥነምግባር</strong>” መጽሄት ቅፅ 9 ቁጥር 3 ሚያዝያ 2002 ዓ.ም “ሳይቃጠል በቅጠል” አምድ ላይ የቀረበው ጽሁፍ አሁን በሀገራችን እየተስተዋለ በሚገኘው የስኳር ገበያ ሁኔታ አንጻር ወቅታዊከመሆኑም ሌላ በተቋሙ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችንለማወገድ ከፍተኛ ጠቀሜታ የሚኖረው ይመስለኛል፡፡ኤጀንሲውም ሆነ የሚመለከታቸው አካላት በኮሚሽኑየቀረቡትን የመፍትሄ ሃሳቦች ከግምት ውስጥ በማገባት ለተግባራዊነታቸው እየተጉ እንደሆነ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡አለማየሁና መስከረም ከአራዳ ክ/ከተማ4


ክራሞትየ<strong>ሥነምግባር</strong> እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽኖችስምንተኛ መደበኛ ስብሰባ በአሶሳ ከተማ ተካሄደየፌደራል እና የክልል የ<strong>ሥነምግባር</strong> እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽኖች እና አግባብነት ያላቸው አካላትየጋራ ጉባዔ ስምንተኛ መደበኛ ስብሰባ ከሰኔ9-1ዐ ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአሶሳ ከተማ ተካሄደ፡፡በስብሰባው ላይ የጋራ ጉባዔውን 7ኛ መደበኛስብሰባ ውሳኔዎችን አፈፃፀም የተመለከተ ሪፖርት ቀርቦ የተደመጠ ከመሆኑም በላይ የ2ዐዐ2የመጀመሪያ ግማሽ በጀት ዓመት ሀገር አቀፍየፀረ-ሙስና እንቅስቃሴ ሪፖርትን መሠረትያደረገ ግምገማ እንደተካሄደ ታውቋል፡፡ በተመሳሳይም ‹‹በውጭ ዕርዳታ አጠቃቀም የፀረ-ሙስናተቋማት ሚና›› በሚል ርዕሰ-ጉዳይ ላይጉባዔው እንደተነጋገረም ለመረዳት ተችሏል፡፡በጉባዔው ላይ የትግራይ፣ የአፋር እና የሶማሌክልሎች በፍትሕና በፀጥታ አካላት የተወከሉሲሆን፣ የ<strong>ሥነምግባር</strong> እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽንያቋቋሙ የቀሪዎቹ ክልሎች ደግሞ በየኮሚሽኖቻቸው የሥራ ኃላፊዎች መወከላቸው ታውቋል፡፡ፍርድ ቤቱ በእምነት ማጉደል ወንጀልየተከሰሱ ግለሰቦች ላይ ውሳኔ አስተላለፈድሬዳዋ:- የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሚያዝያ 29, 2002 ዓ.ም በዋለው ችሎት በከባድ የእምነት ማጉደል የሙስና ወንጀል በተከሰሱ ሁለትግለሰቦች ላይ ከ 7-10 ዓመት በሚደርስ ፅኑእስራትና እያንዳንዳቸው የ 10,000 ብር የገንዘብቅጣት እንዲቀጡ ውሳኔ አስተላለፈ፡፡የፌደራል የ<strong>ሥነምግባር</strong> እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽንየድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አቃቤ ህግ በተከሳሾቹ ላይ የመሰረተው የክስ መዝገብ እንደሚያስረዳው አንደኛ ተከሳሽ መቶ አለቃ ተፈራ ሃይሉበሃገር መከላከያ ሚኒስቴር የደቡብ ምስራቅ ዕዝየ38ኛ ክፍለ ጦር ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ገንዘብ ያዥ ሆኖ በሚሰራበት ወቅት ተገቢ ያልሆነጥቅም ለራሱ እና ለሁለተኛ ተከሳሽ ለሆነው እናከሰራዊቱ በጡረታ ለተገለለው እውነተኛው ሎሌለማስገኘት በማሰብ የተጣለበትን ሃላፊነት ያለአግባብ ተጠቅሟል፡፡አንደኛ ተከሳሽ መቶ አለቃ ተፈራ ሃይሉ ሀረርከሚገኘው የደቡብ ምስራቅ ዕዝ ገንዘብ ማዘዣአካውንት ላይ ተቀንሶ ጅጅጋ ለሚገኘው የ38ኛክፍለ ጦር ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ለሠራዊቱ የነሀሴ ወር 2000 ዓ.ም. ደሞዝ እንዲከፈልበአደራ በስሙ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተረከበውን ብር 454,629.44 እና በሠራዊቱ ካዝና ውስጥየተረከበውን የአደራ ገንዘብ ብር 198,225.27በድምሩ ብር 652,855.01 ይዞ መሰወሩ በማስረጃ ተረጋግጦበታል፡፡ሁለተኛ ተከሳሽ እውነተኛው ሎሌም ለአንደኛተከሳሽ ሀሰተኛ የቀበሌ መታወቂያ በማውጣትከመንግስት የተመዘበረውን ገንዘብ በአዋሽ እናበንብ ኢንተርናሽናል ባንኮች አማካኝነት አንደኛ ተከሳሽ በራሱ ስም ገንዘቡን በማዛወር ለግልጥቅማቸው ማዋላቸውን የክስ መዝገቡ ያመለክታል፡፡በመሆኑም ተከሳሾቹ በኮሚሽኑ ዓቃቤ ህግ የቀረበባቸውን ከባድ የእምነት ማጉደል እና በሀሰተኛ ሰነድ የመገልገል የሙስና ወንጀል ክስ ለመከላከል ስላልቻሉ ፍርድ ቤቱ በአንደኛ ተከሳሽ መቶ አለቃ ተፈራ ኃይሉ ላይ የ 7 ዓመት ጽኑ እስራት እና የ 10,000 ብር ቅጣት በሁለተኛ ተከሳሽ እውነተኛው ሎሌ ላይ በሌለበት የ 10 ዓመትጽኑ እስራት እና የ 10,000 ብር የገንዘብ ቅጣትውሳኔ አስተላልፏል፡፡መንግስታዊ ሰነዶችን ወደ ሀሰት የመለወጥ የሙስና ወንጀል የፈፀመው ተፈረደበትየፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት 1ኛ ወንጀል ችሎትመንግስታዊ ሰነዶችን ወደ ሀሰት በመለወጥ ከ1.2ሚሊዮን ብር በላይ ለግል ጥቅሙ ያዋለው ብርሃኔ አብርሃ ሐጎስ በስምንት ዓመት ጽኑ እስራትእንዲቀጣ ወሰነ፡፡<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ም5


በፌደራል የ<strong>ሥነምግባር</strong> እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽንተከሶ ሚያዝያ 25 ቀን 2002 ዓ.ም የተፈረደበትይህ ግለሰብ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን በአዲስ አበባ ሪጅን ምዕራብ ዲስትሪክትከሐምሌ 1 ቀን 1997 እስከ ሰኔ 30ቀን 1998 ዓ.ም የዕቃ ግምጃ ቤት ፀሐፊ ሆኖበሚሠራበት ወቅት ለራሱ የማይገባ ጥቅምለማግኘት አስቦ የዲስትሪክቱ የዕቃ ግምጃቤት ይገለገልባቸው በነበሩት ኦሪጅናል የመጠየቂያ ሰነዶች ላይ ከፊትና ከኃላ ቁጥር በመጨመር እንዲሁም ቁጥሮችን በመሰረዝ እና በመደለዝ ግምታቸው ብር 1,216,213.82 (አንድሚሊዮን ሁለት መቶ አሥራ ስድስት ሺህሁለት መቶ አስራ ሦስት 82/100) የሚሆኑየኤሌክትሪክ ዕቃዎችን ለግል ጥቅሙ አውሏል፡፡ሁለቱም ተከሳሾች በፈጸሙት የወንጀል ድርጊትበመንግስት ድርጅት ላይ ግምቱ ከ207 ሺህ ብርያላነሰ ጉዳት ያደረሱ በመሆኑ በዋና ወንጀል አድራጊነት እና ተባባሪነት በፈጸሙት የቅጅና ተዛማች መብቶችን የማጣስ ወንጀል መከሰሳቸውን የክስ ቻርጁ ጨምሮ ያስረዳል፡፡በሙስና ወንጀል ሙከራ የተከሰሱ ግለሰቦችበእስራትና በገንዘብ ተቀጡድሬዳዋ:- የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግንቦት11 ቀን 2002 በዋለው ችሎት በግብረአበርነትበፈጸሙት የሙስና ወንጀል ሙከራ በተከሰሱሁለት ግለሰቦች ላይ ውሳኔ አስተላለፈ፡፡<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምበሙስና ወንጀል ተጠርጥረው የተያዙሁለት ጋዜጠኞች ክስ ተመሰረተባቸውየፌደራል የ<strong>ሥነምግባር</strong> እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽንበሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ሚያዚያ 13 እና14 ቀን 2002 ዓ.ም በቁጥጥር ሥር ውለው በነበሩት ጋዜጠኛ ኃይለየሱስ ወርቁ እና አብዱልሰመድ መሐመድ ላይ ግንቦት 12 ቀን 2002 ዓ.ምክስ መሰረተ፡፡ኮሚሽኑ የመሰረተው ክስ እንደሚያስረዳውጋዜጠኛ ኃይለየሱስ ወርቁ በኢትዮጵያ ሬድዮናቴሌቪዥን ድርጅት የዴሞክራሲና መልካምአስተዳደር ፕሮግራሞች ኤዲተር፣ አብዱልሰመድ መሐመድ ደግሞ የመዝናኛፕሮግራሞቸ ከፍተኛ ሪፖርተር ሆነው በመስራት ላይ እንዳሉ ተገቢ ያልሆነ ጥቅም ለማግኘት እና ለሌሎች ለማስገኘት በማሰብ ለሥራ ብለው ከድርጅቱ የተረከቧቸን 19 የተለያዩ የኦዲዮናየኦዲዮቪዡዋል መረጃዎችን ከድርጅቱ እውቅና እና ፍቃድ ውጭ እና የድርጅቱን የኦዲዮናኦዲዮቪዡዋል ላይብረሪዎች አጠቃቀም መመሪያና የኤዲቶሪያል ፖሊሲን በመጣስ በሳውዲአረቢያ አልኢቅራ ለተባለ የግል ቴሌቪዥንጣቢያ በወንጀል ግብረአበሮቻቻው አማካኝነትአሳልፈው በመስጠታቸው በፈፀሙት በስልጣንያለአግባብ የመገልገል የሙስና ወንጀል ተከሰዋል፡፡አንደኛ ተከሳሽ አህመድ ሙሜ እና ግብረአበሩከድር ጀማል በስራ ተግባር ላይ በፈጸሙት የመውሰድና የመሰወር የሙስና ወንጀል በፌደራልየ<strong>ሥነምግባር</strong> እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አቃቤ ህግ ክስተመስርቶባቸው በፍርድ ቤቱ ውሳኔ አግኝተዋል፡፡አህመድ ሙሜ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልኮርፖሬሽን ድሬዳዋ ዲዝል ኃይል ማመንጫጣቢያ ውስጥ “ስቶር ማን” ሆኖ በሚሰራበትወቅት ኮርፖሬሽኑ በጊዜው የነበረውን የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረት ለመቅረፍ ከናሽናል ኃይልኢትዮጵያ ከገዛው በተጎታች ቦቴ ውስጥ ከነበረ 8,702 ሊትር ናፍጣ ላይ ግምቱ 35,262.07ብር የሆነውን 5,281 ሊትር ናፍጣ መራገፍሲገባው ሁለተኛ ተከሳሽ ከሆነው እና በወቅቱ መኪናውን ሲያሽከረክር ከነበረው ከድር ጀማል ጋርበመመሳጠር የማይገባ ጥቅም ለራሳቸው ለማግኘት የመንግስትን ንብረት ከጣቢያው ሊያስወጡሲሞክሩ መያዛቸውን የክስ መዝገቡ ያስረዳል፡፡በዚህም ፍርድ ቤቱ ግለሰቦቹ በስራ ተግባርላይ በፈጸሙት የመንግስትን ንብረት የመውሰድእና የመሰወር ሙከራ የሙስና ወንጀል ጥፋተኛሆነው ስላገኛቸው እያንዳንዳቸውን በሁለትአመት ጽኑ እስራት እና በ2,000 ብር እንዲቀጡወስኗል፡፡6


ቆይታ“በመሬት ዘርፍ ሕገ ወጥነትን ለመከላከል ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረግን ነው”የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርዋና ሥራ አስኪያጅክቡር አቶ መኩሪያ ኃይሌ<strong>ሥነምግባር</strong> መፅሔታችን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርዋና ሥራ አስኪያጅ ከክቡር አቶ መኩሪያ ኃይሌ ጋር በከተማው መሬት አሰጣጥ፣ ይዞታና ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮችዙሪያ ቃለ ምልልስ አካሂዳለች፡፡ ከአቶ መኩሪያ ኃይሌጋር የተደረገውን ቃለ ምልልስ እነሆ፡፡<strong>ሥነምግባር</strong>፡- በአዲስ አበባ ከተማ ከ1997 ዓ.ም ወዲህሕገ ወጥ የመሬት አሰጣጥና ይዞታ በስፋት የታየበት ሁኔታ እንደነበር ይታወቃል፡፡ ለዚህ ሕገ ወጥ ድርጊት መበራከት ምክንያቱ ምንድን ነው ይላሉ?አቶ መኩሪያ፡- በጥያቄው ለተጠቀሰው ሕገ ወጥ ድርጊት መበራከት መሠረታዊ ምክንያት ነው ብሎ ማስቀመጥየሚቻለው ከአስተሳሰብ ጋር የተያያዘ ችግርን ነው፡፡ ይኸውም አግባብ ባልሆነና በአቋራጭ መንገድ መበልፀግ ይቻላል የሚል የተሳሳተ አስተሳሰብ የያዙ የህብረተሰብ ክፍሎች በተለይ በ1997 ዓ.ም በተካሄደው ሀገር አቀፍ ምርጫተቃዋሚዎች በከተማዋ ማሸነፋቸውን ተከትሎ ከመሬትአሰጣጥና ይዞታ ጋር በተያያዘ አሉታዊ ጫና የፈጠሩበት ሁኔታ ነበር፡፡ አሉታዊ ጫና ያሳደሩትምየተለያዩ አደረጃጀቶችንና ትስስሮችን ከመዋቅሮቻችን ጋርበመፍጠር ጭምር እንደነበር ይታወቃል፡፡ችግሩ በተለይ በሪል ስቴት መስክ ጎልቶ የታየ ሲሆን ከፍተኛ የመንግሥትና የህዝብ ንብረት የተመዘበረበት ሁኔታተፈጥሮ ነበር፡፡ በወቅቱ የተለያዩ ሕገ ወጥ የመኖሪያ ቤትየህብረት ሥራ ማህበራትን በማደራጀት እንዲሁም በኢንቨስትመንት ስም የመንግስትና የህዝብ መሬት ወደ ግለሰቦች በማዞርም ቀላል የማይባል የመንግስትና የህዝብ ሀብት ተመዝብሯል፡፡በአጠቃላይ ለነዚህ ሕገ ወጥ ድርጊቶች መበራከት መሠረታዊ እና የመጀመሪያ ምክንያቱ የአስተሳሰብ ችግር ሆኖበመቀጠልም የግልፅነትና የተጠያቂነት አሠራር መጓደልቀላል የማይባል ችግር እንደፈጠረም መገንዘብ ተችሏል፡፡እያንዳንዱ ጉዳይ እንዴት መፈፀም አለበት? ከባለጉዳይምን ይጠበቃል? የአሠራር ሥርዓት ሲጣስ የእርምትወይም የማስተካከያ እርምጃ የሚወሰደው እንዴት ነው?የሚሉና የመሳሰሉ ጥያቄዎችን የሚመልስ በግልፅ የተቀመጠ አሠራር ያለመኖር ችግር ነበር፡፡ መሬት እንደንብረት በአግባቡ የሚመዘገብበት፣ ወደ ህብረተሰቡ ሲተላለፍም ተመዝግቦ የሚያዝበት ሁኔታ በተሟላ መልኩ አልነበረም፡፡ የመሬት ልማት፣ ከተማ መልሶ የማደስ፣ በጨረታወይም በድርድር መሬት የማስተላለፍ፣ የግንባታ ፍቃድናየይዞታ አስተዳደር ሥራዎች በአንድ ተቋም ብቻ የተደራጁበት ሁኔታም የነበረ ሲሆን ይህም ግለሰቦች ሊሠሩት ከሚችሉትና ከሚገባቸው ወሰን በላይ ኃላፊነት እንዲይዙ አድርጓል፡፡ በሦስተኛ ደረጃ አደረጃጀቱም ግልፅነትና ተጠያቂነትን ለተላበሰ አሠራር ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር አልነበረም፡፡በአጠቃላይ ለሕገ ወጥ ድርጊቱ መበራከት ምክንያቱበመሠረታዊነት በሰው ኃይላችን ላይ የነበረው የአስተሳሰብችግር ከላይ ከጠቀስኳቸው የአሠራርና የአደረጃጀት እንከኖች ጋር ተዳምሮ በማስፈፀም አቅም ላይ ያስከተለውችግር ነው፡፡<strong>ሥነምግባር</strong>፡- መሬት የአዲስ አበባ ከተማንም ሆነ የነዋሪዎችን የልማትና ሌሎች ፍላጎቶች ለማሟላት ምን ድርሻ አለው?አቶ መኩሪያ፡- እንደሚታወቀው መሬት ለልማት አስፈላጊ ከሆኑ መሠረታዊ ግብአቶች አንዱ ነው፡፡ መሬት ከሌሎቹ ግብዓቶች ማለትም የሰው ኃይልና የቴክኖሎጂ አቅም ጋር ተዳምሮ ለልማት ቁልፍ መሣሪያ በመሆን ያገለግላል፡፡ ከዚህ አኳያ በከተማችን የትምህርት፣ የጤና፣ የመንገድ፣ የውሃ፣ የስልክ ወዘተ. መሠረተ ልማቶች እንዲስፋፉ መሬት በነፃ በማቅረብ እንዲሁም ለሰፊ የህብረተሰብክፍል የሥራ ዕድል እንዲፈጠር መሬትን ለኢንቨስትመንት፣ ለንግድ ወዘተ. በነፃ ወይም በአነስተኛ ወይም በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ህብረተሰቡ በመሬት ልማት ፍትሃዊ ተጠቃሚ እንዲሆን እየተደረገ ነው፡፡ ፍትሃዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ደግሞ ህበረተሰቡ በሠላምና ዴሞክራሲግንባታ የሚኖረው ተሳትፎ እንዲጎለበት ትልቅ ሚና ይጫወታል፡፡ ስለዚህም በአጠቃላይ የመንግሥትና የህዝብ ሀብት የሆነው መሬት በከተማዋ ለኢኮኖሚና ማህበራዊ አገልግሎቶች መስፋፋት ቀጥተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ ሲሆን ለሠላምና ለዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታችን መጠናከር ደግሞበተዘዋዋሪ የድርሻውን እያበረከተ ነው ለማለት ይቻላል፡፡<strong>ሥነምግባር</strong>፡- የከተማው አስተዳደር በአሁኑ ጊዜ ሕገወጥ የመሬት አሰጣጥና ይዞታን ለመከላከል ምን እርምጃዎችን እየወሰደ ይገኛል?አቶ መኩሪያ፡- በከተማው ሕገ ወጥ የመሬት አሰጣጥና7<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ም


<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምይዞታን ለመከላከል የአጭር ጊዜ እና የረጅም ጊዜ እቅዶችን አውጥተን በመንቀሳቀስ ላይ እንገኛለን፡፡ ከአጭርጊዜ አኳያ በእቅዳችን አስቀምጠን በመተግበር ላይ ያለነው በፍጥነት መስተካከል የሚችሉ አሠራሮችንና አደረጃጀቶችን የመቀየር ሥራ ነው፡፡ በተጨማሪም ሕገ ወጥነትየበላይነት እንዳያገኝ በአፋጣኝ የመቆጣጠርና አክሳሪመሆኑን በተጨባጭ ሊያሳይ የሚችል እንቅስቃሴ ማድረግንነው፡፡ በክቡር ከንቲባው የሚመራና እኔም ምክትል ሰብሳቢየሆንኩበት መዋቅሩ እስከ ቀበሌ የሚደርስ ግብረ ኃይልተቋቁሞ ሕገ ወጥነትን በመቆጣጠር፣ አሳፋሪ ሥራ መሆኑን በማስገንዘብና የከተማው አስተዳደር በዚህ ጉዳይ ላይድርድር የሌለው መሆንን በተግባር በማሳየት ረገድ ከአጭር ጊዜ አኳያ እቅድ ወጥቶ ባለፉት ሁለት ዓመታት ርብርብ ሲደረግ ቆይቷል፡፡ከረጅም ጊዜ አንጻር በመሠረታዊነት ትኩረታችንን ያደረግነው በቀጣይነት ሊሠራ የሚችል አሠራርና አደረጃጀትበመፍጠር ላይ ነው፡፡ ከአሠራር አንጻር የከተማችን መሬት አስተዳደር የአሠራር ሥርዓቱ ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀና ምርጥ የውጭ ተሞክሮዎችን ያካተተ ይሆን ዘንድበዓለም አቀፍ ደረጃ የተገኙትን ተሞክሮዎች አዲስ አበባላይ በመሞከር በሀገር አቀፍ ደረጃም እንዲያገለግልለማድረግ ትኩረት ሰጥተን እየተንቀሳቀስን እንገኛለን፡፡በዚሁ መሠረት የዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ግዥ ጨረታአውጥተን ከሁሉም የዓለማችን ክፍሎች አማካሪዎችከተወዳደሩ በኋላ ጀርመናዊያን አማካሪዎች አሸንፈውእና ውል ተዋውለው ወደ ሥራ ገብተዋል፡፡ ይህ ሥራአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ያለ መሬት በሙሉ በአውሮፕላን ፎቶ ተነስቶ፣ ወደ መስመር ማፕ ተቀይሮ፣እያንዳንዱ ይዞታ እና የማይንቀሳቀስ ንብረት በቴክኖሎጂተመዝግቦ፣ አገልግሎት ፈላጊዎች የተሟላ መረጃ የሚያገኙበት ሥርዓት ይፈጥራል ተብሎ ይታመንበታል፡፡ ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው አሠራር በማስፈን በተለይምስለ መሬት አቅርቦት ሁሉም ሰው በመረጃ መረብ እናበመገናኛ ብዙሃን ይፋ መረጃ የሚያገኝበትን ሁኔታ በመፍጠርም በዘርፉ ፍትሃዊነትን ለማረጋገጥ ያስችላል፡፡ በመሆኑም በዚህ ረገድ ልዩ ትኩረት ሰጥተን እየሰራን ነው፡፡በሰው ኃይል አስተሳሰብ ረገድ ለውጥ በማምጣትችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ርብርብ በማድረግላይ እንገኛለን፡፡ በመሆኑም በመሬት ላይ የሚፈፀመውንሕገ-ወጥነት መከላከል ይቻላል ብለን እናምናለን፡፡<strong>ሥነምግባር</strong>፡- የፌደራል የ<strong>ሥነምግባር</strong>ና የፀረ-ሙስናኮሚሽን ከአዲስ አበባ ከተማ የመሬት አስተዳደር ጋርበተያያዘ ለሙስናና ብልሹ አሠራር የሚያጋልጡአሠራሮችን በማጥናት የመፍትሄ ሃሳቦችን ማቅረቡይታወቃል። የከተማው አስተዳደር የመፍትሄ ሀሳቦቹን እንዴት ተመለከታቸው? ተግባራዊ ለማድረግስ ምንያህል ተንቀሳቅሷል? በተጨማሪም ኮሚሽኑ ከሕገ ወጥየመሬት አሰጣጥና ይዞታ ጋር በተያያዘ በርካታ ተጠርጣሪዎችን ለፍርድ ማቅረቡ፣ እንዲሁም ከፍተኛ ገንዘብየሚያወጣ የከተማ ቦታ እንዲታገድ ማድረጉ በዘርፉ ሕገወጥነት ለመከላከል ምን አስተዋጽኦ አበርክቷል ይላሉ?አቶ መኩሪያ፡- የፌደራል የ<strong>ሥነምግባር</strong>ና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከአዲስ አበባ ከተማ የመሬት አስተዳደርጋር በተያያዘ ከፍተኛ የሆነ አዎንታዊ ሚና ተጫውቷል፡፡ አሁንም ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ ከዚሁጉዳይ ጋር በተያያዘ ኮሚሽኑ ድጋፍ የመስጠት ሳይሆን የማይተካ ሚና ነበረው ለማለት እችላለሁ፡፡ ይህን የኮሚሽኑን ሚናም በሁለት መልኩ ከፍሎ ማየት ይቻላል፡፡አንደኛው ኮሚሽኑ የመንግስትንና የህዝብን ንብረት በጠራራ ፀሃይ መዝረፍ አይቻልም፤ የመንግስትንና የህዝብን ንብረት መዝረፍ አደጋ አለው፤ የኋላ ኋላም ተጠያቂነት ያስከትላል የሚል ግልጽ መልዕክት አስተላልፏል፡፡ይህም አንዳንድ መልካም ባህሪ ያላቸው ግለሰቦችንናመልካም አገልግሎት የሚሰጡ የሥራ ኃላፊዎችን በተወሰነ ደረጃ ያስደነገጠበት ሁኔታ ቢኖርም በዘርፉ ሕገወጥነትን ለማቆም ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጓል፡፡ በሕገወጥ መንገድ ተይዞ የነበረ ከፍተኛ መጠን ያለው መሬትለከተማው አስተዳደር መመለሱ እንዲሁም በፍርድ ቤትየታገደው መሬት መጠንም እጅግ ከፍተኛ መሆኑ በዘርፉሕገ ወጥነትን ለማስቆም ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጓል፡፡ከቴክኖሎጂ በተጨማሪ አስተሳሰቡ የተቀየረና እምነትየሚጣልበት የሰው ኃይል ለመፍጠር ዝርዝር ፕሮግራምአውጥተን ወደ ተግባር ገብተናል፡፡ የሰው ኃይላችንን አስተሳሰብ ለመቀየር ከእውቀት፣ ከሙያ፣ ከመንግሥት ፖሊሲናስትራቴጂ፣ ከደንቦችና መመሪያዎች አንፃር ሥልጠናዎችን የመስጠት እንዲሁም በተግባር በተገኙ ተሞክሮዎች ላይእርስ በእርስ እየተማማረና አሠራሮችን እየገመገመ የሚሄድበት ሥርዓትን የመዘርጋት ሥራዎች እየተከናወኑ ሲሆንይህም ቀጣይነት እንዲኖረው ለማድረግ ጥረቱ ይቀጥላል፡፡በሌላ በኩል ደግሞ ሦስት መሥሪያ ቤቶች ማለትም አንደኛ የመሬት ልማት፣ ባንክና ከተማ ማደስ፣ ሁለተኛ የመሬት አስተዳደርና ግንባታ ፍቃድ፣ ሦስተኛ የፕላንና የመሬት መረጃ ኢንስቲትዩት ሥልጣንና ተግባራቸው ተለይቶ ግልፅነትንና ተጠያቂነትን በሚያሰፍን መልኩ ተደራጅተዋል፡፡ ሥራዎችን ከፋፍለን በመሥጠታችን የአገልግሎትቅልጥፍና እና ውጤታማነት ከማምጣት አንጻር ጉልህለውጥ የማስመዝገብ ጅምር እየታየ ነው፡፡በአጠቃላይ የመሬትና መሬት ነክ ጉዳዮች የማስፈፀምአቅም ወደ ተሻለ ደረጃ እንዲደርስ የሚያስችሉ የአጭርናየረጅም ጊዜ ዕቅዶች አውጥተን በአሠራር፣ በአደረጃጀትና8ሁለተኛው የኮሚሽኑ ትልቅ አስተዋፅኦ ከከተማው የመሬት አስተዳደር ጋር በተያያዘ ለሙስናና ብልሹ አስተሳሰብናተግባር የሚያጋልጡ አሠራሮችን በማጥናት የመፍትሄሃሳቦችን ማቅረቡ ነው፡፡ የአሁኑ የከተማው አስተዳደርሥራ ሲጀምርም የጥናት ውጤቶቹን እንደ መጀመሪያግብዓት ተጠቅሞባቸዋል፡፡<strong>ሥነምግባር</strong>፡- በአሁኑ ጊዜ በሊዝ ቦታዎች ጨረታ አሰጣጥ፣ በይዞታ ማህደር፣ በግንባታ ፍቃድና በምትክ ቦታአሰጣጥ፣ በካሳ ክፍያ አፈፃፀም እንዲሁም በቦታ ማቅረብረገድ ያለው የግልጽነት፣ የፍትሃዊነትና የተጠያቂነት ሁኔታ ምን ይመስላል?አቶ መኩሪያ፡- በከተማዋ በሊዝ ቦታዎች ጨረታ አሰጣጥ፣ በይዞታ ማህደር፣ በግንባታ ፍቃድና በምትክ ቦታአሰጣጥ፣ በካሳ ክፍያ አፈፃፀም እንዲሁም በቦታ ማቅረብ ረገድ አሁን ያለው የግልጽነት፣ የፍትሃዊነትና የተጠያቂነት ሁኔታ ተስፋ ሰጪ ነው፡፡ በርካታ ለውጦች አሉ፡፡ቀደም ሲል ህብረተሰቡ የመሬት ጨረታ በሚወጣበት ጊዜየተሟላ መረጃ አግኝቶ የሚወዳደርበት ሁኔታ አልነበረም፡፡በዚህም ምክንያት የመሬት ዋጋ ከዓመት ዓመት እያሻቀበ


የመጣበት ሁኔታ ነበር፡፡ በካሬ ሜትር እስከ 22 ሺህ ብርዋጋ የሚሰጥበት ሁኔታ እንደነበር ይታወሳል፡፡ሁኔታ ፈጥረናል፡፡ በዚህ ረገድ በተወሰነ ደረጃ የምንፈትሻቸው ጉዳዮች ቢኖሩም አሁን የተሻለ ሁኔታ ነው ያለው፡፡አሁን በቀየስነው ስትራቴጂ መሠረት የመሬት ጨረታበሚወጣበት ጊዜ በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን በተደጋጋሚስለሚገለፅ ህብረተሰቡ መረጃ ያገኛል፡፡ መሬት እየቀረበያለው በሚገመት ጊዜ ውስጥ (ለምሳሌ በወር ወይም በ15ቀን) ነው፡፡ ይህም በመሆኑ የመሬት ዋጋ በ4 ሺህና 5ሺህ ብር ገደማ ወርዷል፡፡ ከዚህም በታች ይወርዳል ብለንእንገምታለን፡፡ በእርግጥ ለእኛ ትልቁ ቁም ነገር የመሬትዋጋ መናር ወይም ማሻቀብ አይደለም፡፡ ዋናው ጉዳይ ባለሃብቱም ሆነ ነዋሪው መሬቱን ከያዘ በኋላ በፍጥነት ማልማቱላይ ነው፡፡ቀደም ሲል በነበረው አሠራር የመሬት ጨረታ ከወጣበኋላ በሦስትና በአራት ወራት እንኳ ውጤቱ አይታወቅምነበር፡፡ አሁን ባለው አሠራር ተጫራቹ ዋጋ በዕለቱ ያስገባል፡፡ የጨረታውን ውጤት ተጫራቹ እዛው አዳራሽ ውስጥእንዳለ በኮምፒዩተር ስክሪን እያየ የሚያውቅበትን አሠራርፈጥረናል፡፡ማንም ሰው እንደፈለገ መቀነስ፣ ማዛባትና መደለዝ የማይችልበት አሠራር ነው የፈጠርነው፡፡የይዞታ ማህደር ጉዳይ ብዙ ሰዎችን ሲያስለቅስ የቆየና‹‹ማህደሬ ጠፋ›› የሚል አቤቱታ ክቡር ከንቲባው ቢሮ ድረስ የሚቀርብበት ሁኔታ ነበር፡፡ በአሁኑ ወቅት ግን ማህደሩንፈልጎ የሚያጣ ሰው የለም፡፡ በአብዛኛው በቀበሌ፣ በተወሰነመልኩ ደግሞ በክፍለ ከተማ ደረጃ በደቂቃ ውስጥ ማህደርካሳ ክፍያን በተመለከተ በተወሰነ ደረጃ የካሳ መመሪያውን አሻሽለናል፡፡ ወጥ መመሪያ አጽድቀን ግን ወደ ሥራገና አልገባንም፡፡ በሙከራ ደረጃ የምናየውና የምናጠራውሁኔታ አለ፡፡ ያም ሆኖ በካሳ ክፍያ ረገድ ከቀድሞው በጣምየተሻለ ሁኔታ መኖሩ ግልጽ ነው፡፡እንደሚታወቀው የአሁኑ የከተማ አስተዳደር ሥልጣን በሚረከብበት ጊዜ ከ20 በላይ የመንገድ ፕሮጀክቶች የቆሙበትና አስተዳደሩ ለኮንትራክተሮችና ኮንሰልታንቶች ለባከነ ጊዜ ካሳ የሚከፍልበት ሁኔታ ነበር፡፡አሁን በወሰን ማስከበር የተነሳ የቆመ አንድምፕሮጀክት የለም፡፡ መንገዶች በፍጥነት እየተገነቡነው፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ የስልክ፣ የመብራትና የውሃ ወሰንማስከበር ችግር በማይፈጥርበት ደረጃ ላይ ነው ያለው፡፡ያለስጋት ለልማት መሬት የማቅረብ ሁኔታም ተመቻችቷል፡፡ ለጥቃቅንና አነስተኛና ለቤቶች ልማት ቦታ ማቅረብምበጣም ቀላል እየሆነ ነው፡፡ ለዩኒቨርሲቲዎችና ሆስፒታሎችም ያለ ችግር ቦታ ማቅረብ የሚቻልበት ደረጃ ላይ ነውየደረስነው፡፡ መሬትን ለመሠረተ ልማት፣ ለቤት ልማትና የሥራ እድልን ለመፍጠሪያ በነፃ በማቅረብ እንዲሁምበጨረታ ተደራሽ በማድረግ ፍትሃዊነትን የሚያረጋገጥመሠረት ተጥሏል፡፡<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምወጥቶ አገልግሎት የሚሰጥበት ሁኔታን ለመፍጠርተችሏል፡፡የግንባታ ፍቃድም በቀናት ውስጥ የሚሰጥበት ሁኔታ ተመቻችቷል፡፡ የምትክ ቦታ አሰጣጥን በተመለከተ የመሬቶቹ ቁጥር ተጠቅሶ በእጣ የሚሰጥበትንበአጠቃላይ ከምንጠብቀው አንጻር በተለይም ከረጅምጊዜ እቅዳችን አኳያ ብዙ ቢቀረንም በርካታና ከፍተኛ ሊባሉ የሚችሉ ተስፋ ሰጪ ሥራዎች ተሠርተዋል፡፡ በመሬት ዘርፍ ህገወጥነትን በመከላከል፣ መሬትን ግልጽ በሆነ አሠራር በማቅረብና በፍትሃዊነት በማገልገል ረገድ በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ የአሁኑ9


<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምየከተማ አስተዳደር ሥልጣን ከተረከበ ወዲህ በዘርፉያደረገው ለውጥ ቀደም ሲል ከነበረው ሁኔታ ጋር ሲነፃፀር በማንኛውም መለኪያ ከፍተኛ ሊባል የሚችል ነው፡፡<strong>ሥነምግባር</strong>፡- በከተማው መሬት አስተዳደር አማካይነትበሚታተሙ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታዎች ላይ ምን ያህልክትትልና ቁጥጥር ይደረጋል?አቶ መኩሪያ፡- አዲሱ የከተማ አስተዳደር ብዙ የይዞታማረጋገጫ ካርታ ያሳተመበት ሁኔታ አልነበረም፡፡ አብዛኛዎቹ ካርታዎቹ ቀድሞ የታተሙ ናቸው፡፡ ካርታዎችን በሚመለከት ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚጠይቀው ከማሳተሙ ጀምሮ ነው፡፡ ከታተሙ በኋላ ደግሞ በማዕከላዊ ደረጃ ተመዝግበው ስለ አወጣጣቸውና ምን ላይ እንደሚውሉ ክትትልአድርጎ ሥራ ላይ በማዋል ረገድ ትልቅ ክፍተት ነበር፡፡በአሁኑ ወቅት ግን በከተማው በተካሄደው የመሠረታዊአሠራር ሥርዓት ለውጥ ካርታን በሚመለከት የግልጽነትና የተጠያቂነት አሠራርን የሚያረጋግጥ መመሪያ ወጥቷል፡፡ ይህም ካርታ እንዴት መታተም እና መሰራጨትእንዳለበት በግልፅ የሚያሳይ በመሆኑ በአሁኑ ጊዜ ከይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ጋር በተያያዘ በተሻለ ደረጃ እየተሠራነው ብሎ በእርግጠኝነት ለመናገር ይቻላል፡፡ቀደም ሲል የወጡ ካርታዎችን ደግሞ ከፍተኛ ደረጃንበጠበቀ፣ ተአማኒነታቸውን ባረጋገጠና ከእንግዲህ በኋላችግር በማይፈጥር መልኩ ቀይሮ ለማስተካከል ቅድመዝግጅት እያደረግን ነው፡፡ የተለያዩ ሰነዶች ኖሯቸው የይዞታ ካርታ ለሌላቸው ቁጥራቸው 100 ሺህ ለሚጠጉ ሰዎች ካርታ ለመስጠትም ዝግጅት በማድረግ ላይ እንገኛለን፡፡<strong>ሥነምግባር</strong>፡- በከተማዋ የግንባታ ቦታ ወስደው ሥራበማይጀምሩ አልሚዎች ላይ ተገቢውን ክትትልና ቁጥጥር በማድረግ ወቅታዊ እርምጃ በመውሰድ ረገድ ችግርእንዳለ ይነገራል። በዚህ ላይ የእርስዎ ምላሽ ምንድን ነው?አቶ መኩሪያ፡-- በዋነኛነት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አሠራሩን ሲያስተካክል ከፍተኛ ጥንቃቄ በተሞላበትሁኔታ ነው፡፡ አስተዳደሩ ለሦስት ጉዳዮች ትኩረት በመስጠት ነው አሠራሩን እያስተካከለ ያለው፡፡አንደኛው ጉዳይ በሕገ ወጥ መንገድ ሀብት መፍጠር ኪሳራ እንደሚያስከትል በማሳየት ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነው፡፡ሁለተኛው ትኩረት የተደረገበት ጉዳይ ለልማታዊ ባለሀብቶችና ጉዳዩ ለሚመለከታቸው የህብረተሰብ ክፍሎች መሬት የማቅረብ ሥራ መሥራትና በዚህ ውስጥምየከተማው አስተዳደር ለልማታዊ ባለሀብቶች ያለበትንተጠያቂነት አጉልቶ ማሳየት ላይ ነው፡፡ ይህም በመሆኑመሬት ወስደው በወቅቱ ግንባታ የማይጀምሩትን ባለሀብቶች በተወሰነ ደረጃ የመታገስ በትዕግስትም ወደ ትክክለኛው መስመር የማስገባት መርህ ነው የተከተልነው፡፡ያጠፋውን ሁሉ መቅጣት ሳይሆን ጥፋቱ የደረሰው በእኛበቂ ድጋፍ አለማድረግ ሆኖ ሲገኝ በተወሰነ ደረጃ የታገስንበት ሁኔታ አለ፡፡ ይህም ሆኖ ከየካቲት 1997 በፊትየግንባታ ጊዜ ያለፈባቸው በመቶ የሚቆጠሩ ባለሃብቶችይዞታቸው ተሰርዞ መሬቱ ወደ ከተማው አስተዳደደር እንዲመለስ ተደርጓል፡፡ ከእነርሱ የተመለሰው መሬትም ለመኖሪያ ቤት ልማትና ለሌሎች የልማት እንቅስቃሴዎች እንዲውል እየተደረገ ነው፡፡ በከተማው ከየካቲት 1997 በኋላየግንባታ ጊዜ ባለፈባቸው ባለሃብቶች ይዞታ ላይ እርምጃእንደምንወስድ ማስጠንቀቂያ በመስጠትም ብዙዎቹ (ትልልቅ ባለሀብቶችን ጨምሮ) ወደ ልማት እንዲገቡ ተደርጓል፡፡ሦስተኛው ትኩረት ያደረግንበት ጉዳይ ከእንግዲህ በኋላመሬት በሚሰጥበት ጊዜ መሬቱ ለልማታዊ አገልግሎትብቻ መዋል የሚገባው መሆኑ ላይ ነው፡፡ በመሆኑምበእርግጥም ወደ ልማት ሊገባ ለሚችል፣ አቅም ላለውናቅድመ ዝግጅት ላጠናቀቀ ሰው ባወጣነው ግልፅ መመሪያመሠረት በጨረታም ሆነ በድርድር መሬት የመስጠትሁኔታን ነው የምንከተለው፡፡<strong>ሥነምግባር</strong>፡- በአዲስ አበባ ከተማ የመሬት አስተዳደርንና ይዞታን ከሙስናና ብልሹ አሠራር የጸዳ ለማድረግ የከተማው አስተዳደርና የፌደራል የ<strong>ሥነምግባር</strong>ና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምን ያህል ተቀራርበው እየሠሩ ይገኛሉ? በዚህ ረገድ ከህብረተሰቡስ ምን ይጠበቃል?አቶ መኩሪያ፡- ከላይ እንደገለፅኩት የፌደራል የ<strong>ሥነምግባር</strong>ና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከአዲስ አበባ ከተማ ሕገ ወጥየመሬት አሰጣጥና ይዞታ ጋር በተያያዘ ህገ-ወጥነትን ለመከላከል በርካታ ተጠርጣሪዎችን ለፍርድ በማቅረብ እንዲሁም ከከተማው የመሬት አስተዳደር ጋር በተያያዘ ለሙስናናብልሹ አሠራር የሚያጋልጡ አሠራሮችን በማጥናት የመፍትሄ ሃሳቦችን በማቅረብ ከፍተኛ እንቅስቃሴ አድርጓል፡፡በዚህ እንቅስቃሴ ውስጥ ሁሉ የከተማው አስተዳደር ከኮሚሽኑ ጋር ተግባብቶና ተቀራርቦ ሠርቷል፡፡ በመረጃ መለዋወጥ ረገድና የህዝብን ንቃተ ህሊና ከማጎልበት አንጻርምአብረን እንሠራለን ብለን እናስባለን፡፡ ይህ ተደጋግፎና ተቀራርቦ የመሥራት ሁኔታ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እምነታችን ነው፡፡በተለይም ከአሁን በኋላ የህብረተሰብን አስተሳሰብከመቅረፅ አንጻር የጎላ ሥራ ይሠራል ብዬ አምናለሁ፡፡በዚህ ረገድ ኮሚሽኑ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራዎቹን በማጠናከር ‹‹በሕገ ወጥና በአቋራጭ መንገድ መክበር ይቻላል›› የሚል የተሳሰተ አስተሳሰብን ተሸናፊ በማድረግ በኩልይበልጥ እንደሚያግዘን ተስፋ አለኝ፡፡የከተማውን የመሬት አስተዳደር ከሙስና የፀዳ በማድረግረገድ ከሕብረተሰቡ ምን ይጠበቃል ለሚለው በዚህ ረገድህብረተሰቡ የሚኖረው ድርሻ ከፍተኛ ነው ብዬ አስባለሁ፡፡ህብረተሰቡ አገልግሎት ለማግኘት ወደ ተለያዩ ተቋማትሲሄድ ህጋዊነትን ብቻ ተከትሎ መስተናገድ ይኖርበታል፡፡በምንም መልኩ የብልሹ አሠራርና የሙስና ተዋናይ ከመሆን መቆጠብ ይገባዋል፡፡ ህጋዊነትን ያልተከተለ ጥያቄሲቀርብለት በመጀመሪያ ጥያቄው ተገቢ አለመሆኑን በድፍረትና በግልጽ የመቃወም በመቀጠል ደግሞ ለሚመለከተው አካል ጥቆማ በማቅረብ የዜግነት ድርሻውን መወጣትይኖርበታል፡፡ ምክንያቱም በሙስና ጥቂቶች እንጂ ህብረተሰቡ ተጠቃሚ አይሆንምና፡፡ የከተማው አስተዳደር ከመሬት ጋር በተያያዘ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት ሥርዓት ለመዘርጋት እያደረገ ያለው ጥረት ከዳር እንዲደርስ የህብረተሰቡ ትብብር ተጠናክሮ መቀጠል ወሳኝ ነው፡፡ ግልጽነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት ሥርዓትን በማስፈን የመሬትአስተዳደርንና ይዞታን ከሙስና የጸዳ ማድረግ ደግሞ ሀገሪቱ ለተያያዘችው የልማት እንቅስቃሴ መጠናከርና ለዲሞክራሲያችን መጎልበት ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል የሚል እምነት አለኝ፡፡ አመሰግናለሁ፡፡10


ከዚህም ከዚያምፀረ-ሙስና በሥነጥበብበሁሉም መስኮች ላይ ሙስና በተንሰራፋበት ሀገር ሙስናን እንዴት መዋጋት ይቻላል? በሚል የፓኪስታኑ ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል ለየት ያለ ስልት ነድፏል፡፡ የፓኪስታኑ ፕሬዚደንት አሲፍ አሊ ዛርዳሪ በርካታ ሚሊዮንዶላሮችን በስዊዝ ባንክ አስቀምጠዋል በሚል የቀረበባቸውንየሙስና ወንጀል ክስ ተከትሎ የትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል የፀረ-ሙስና ትግል የተለየ አቅጣጫን ይዟል፡፡ይኸው ለየት ያለ ስልት በትምህርት ቤት ተማሪዎች ላይያተኮረ ነው፡፡ ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል ተማሪዎችየሥነጥበብ ችሎታቸውን በመጠቀም ሙስናን እንዲዋጉጥሪ ያቀረበ ሲሆን ሙስናን ለመከላከል ጥሩ ዘዴ መሆኑን አምኖበታል፡፡ በጥሪው መሠረት ተማሪዎቹ በርካታ ስዕሎችን ያቀረቡ ሲሆን ሥራዎቻቸው ከእድሜያቸው በላይየሙስናን አስከፊ ገጽታ ቀድመው መረዳታቸውን ያስረዳል፡፡ በቀረቡት ስዕሎች ሙስናን በአቦሸማኔ፣ በእሳት እናበጠንቋይ ገጽታ መስለውታል፡፡በተጨማሪም ስዕሎቹ ሙስና ትምህርት ቤቶችን፣ ፖሊስን፣ ዳኞችን እና ቤተሰብን የሚጎዳ አደገኛ ኃይል እንደሆነ ያሳዩ ነበሩ፡፡ በተማሪዎቹ ከቀረቡት ስብስቦች መካከልበአንደኛው ፖስተር ስር ‘‘በአሁኑ ወቅት ሰዎች ከብሔራዊ ባንዲራቸው ይልቅ ሙስናን ያከብራሉ’’ የሚል ጽሁፍ ይነበባል፡፡<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምየትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል የፓኪስታን ዋና ዳይሬክተር ሳአድ ራሺድ እንደገለጹት ሙስና ወጣቶች ረዳትየለሽ ስሜት እንዲኖራቸውና የድብርት በሽታ ተጠቂ እንዲሆኑ ያደርጋል፡፡ ተማሪዎች በብዙ ጥረት ተምረው ዲግሪያቸውን ከያዙ በኋላ ሥራ ለማግኘት ሲቸገሩ ለከፋ የሞራል ውድቀት ይዳረጋሉ፡፡ በተለይም ደግሞ ጓደኞቻቸውበጉቦ እና በዘመድ ሥራ ማግኘታቸውን ሲረዱ ለከፋ የስነልቦና ችግር ይዳረጋሉ በማለት አስረድተዋል፡፡ በመጨረሻምሁኔታው ሙስና ውስጥ ካልገቡ የትም እንደማይደርሱ እስከ መደምደም ድረስ ያደርሳቸዋል፡፡ በመሆኑም በሥነጥበብአማካይነት ወጣቶች ሙስናን አስመልክቶ የሚፈጠርባቸውን ስሜት አስተማሪ በሆነ መንገድ የሚገልጹበትን መንገድ ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል አመቻችቷል፡፡ዘ ፒክቸር ሾው ሜይ 26 2010በሩስያ የባለሥልጣናት ሕገወጥ ንብረትየሩስያ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር የሙሰኛ ባለሥልጣናትን ሕገወጥ ንብረት ለመውረስ እንዲቻል አስፈላጊ የሆኑየሕግ ማእቀፎች እንዲሻሻሉ ግፊት እያደረገ ነው፡፡ሚኒስቴሩ ወደዚህ እንቅስቃሴ ውስጥ የገባው የሀገሪቷፕሬዚዳንት ዲሚትሪ ሜድቬዴቭ ጉዳዩን አስመልክቶእርምጃ እንዲወሰድ ያስተላለፉትን ትእዛዝ ተከትሎ ነው፡፡ፕሬዚዳንት ዲሜትሪ ሜድቬዴቭየሀገሪቷ የአንዳንድ ባለሥልጣናት ንብረትና እና ገቢያቸው የማይመጣጠን መሆኑ በህዝቡ ዘንድ ቅሬታን እየፈጠረ መሆኑን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትርገልጸዋል፡፡ ሚኒስትሩ ጨምረው እንደተናገሩት የሩስያፕሬዚደንት የመንግሥት ባለሥልጣኖች ገቢያቸውንናንብረታቸውን እንዲያስመዘግቡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ተፈጻሚነቱን ለማረጋገጥ የሕግ ማሻሻያዎችን ማድረግና ንብረታቸውም የሚወረስበትን አሠራር መዘርጋት ያስፈልጋል፡፡የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትሩ የከፍተኛ ባለሥልጣናትን ገቢና ንብረት የያዘ ዝርዝር መረጃ አሳትሞ ይፋ ባደረገው መሠረት ከባለሥልጣናቱ መካከል ከፍተኛ ክፍያ እናንብረት ያስመዘገቡት የሴይንት ፒቲስበርጉ የፖሊስ አዛዥናቸው፡፡ የፖሊስ አዛዡ አጠቃላይ ገቢ በድምሩ 23 ነጥብ 8 ሚሊየን ሩብል ወይም 762 ሺህ ዶላር ሲሆን ንብረታቸው ደግሞ አንድ የመኖሪያ ቤት፣ አፓርታማ፣ በትርፍ ጊዜ መዝናኛ ቤት እና ሦስት መሬቶችን ያካተተ ነው፡፡በአሁኑ ወቅት የሕግ አስፈጻሚ አካላት የባለሥልጣናትትክክለኛ ገቢና ንብረታቸው አለመመጣጠኑን ሲረዱ አስፈላጊውን እርምጃ አይወስዱም፡፡ በመሆኑም እርምጃዎችን11


ለመውሰድ ይቻል ዘንድ የሕግ አውጪ አካላቱ በተያዘውየፈረንጆች አመት በሕጉ ላይ ማሻሻያዎችን በማድረግእንደሚያጸድቁ ይጠበቃል፡፡ በሚጸድቀው ሕግ መሠረት ምንጩ ያልታወቀ ንብረት ያካበቱ ባለሥልጣናት የንብረታቸውንአመጣጥ የማስረዳት ሸክም ወይም ግዴታ ይጣልባቸዋል፡፡ባለሥልጣናቱ ምንጩ ያልታወቀ ንብረት ከየት እንዳመጡ ሲጠየቁ ምናልባት የሴት አያታቸው የወርቅ ጥርስወይም ወንድ አያታቸው የቀበሩት ሀብት ትዝ ሊላቸውይችል ይሆናል፤ ያም ሆነ ይህ ግን ተጨባጭ የሆነ ማስረጃ ማቅረብ ግድ ይላቸዋል በማለት የሀገሪቷ አንድ ባለሥልጣን ገልጸዋል፡፡በሩስያ ሙስናን እና የፖሊሶች <strong>ሥነምግባር</strong>ን አስመልክቶየህዝቡ ቅሬታ እየጨመረ በመምጣቱ ፕሬዚዳንቱ ዲሜትሪ ሜድቬዴቭ በሀገሪቷ ከ50 አመታት ወዲህ ያልተከናወነና ትልቅ የተባለለትን የሕግ አፈጻጸም ግምገማ አከናውነዋል፡፡ በማስከተልም ፕሬዚደንቱ የሀገር ውስጥ ጉዳይሚኒስትር ሠራተኞች ቁጥር 20 በመቶ እንዲቀነስናበልዩ ሁኔታ የፓሊስ ኃይል በፌደራል ፋይናንስ ሥርእንዲካተት ትዕዛዝ አስተላልፈዋል፡፡ የሩስያ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ሰራተኞች ብዛት 1 ነጥብ 4 ሚሊዮንሲሆን ከሀገሪቱ የመከላከያ ሰራዊት ቁጥር ጋር ተመጣጣኝ መሆኑን የሀገሪቷ ጠቅላይ ሚኒስትር ቭላድሚር ፑቲንባለፈው የፈረንጆች አመት ገልጸዋል፡፡የሩስያ ሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር እንደገለጸው በሀገሪቱ ባለፈው የፈረንጆች አመት ብቻ በ13 ሺህ 141 የሙስና ጉዳዮች ላይ ምርመራ ተካሂዷል፡፡ቢዝነስ ዊክ ሜይ 26 2010ሪፖርቱ ሙስናው የተጠቀሱትን ዘርፎች በምንመልኩ እያሰጋ እንደሚገኝ ሲያብራራ እ.ኤ.አ በ 2004በምእራብ ኬንያ ገጠራማ አካባቢ በሚገኙ የመጀመሪያደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ የተደረገ ጥናት 20 በመቶየሚሆኑት መምህራን በስራ ገበታቸው ላይ እንደማይገኙያሳያል፡፡ በሌላ በኩል በዩጋንዳ የተካሄዱ ተመሳሳይ ጥናቶች እንደሚጠቁሙት የመምህራን በስራ ገበታቸው ላይያለመገኘት ችግር እ.ኤ.አ በ 2002, 27 በመቶ በ 2007ደግሞ 20 በመቶ እንደነበር ይገልጻሉ፡፡እንደ ሪፖርቱ የግብርናውን መስክ በሚመለከት በአምራቾችና በነጋዴዎች አካባቢ ባለው የላላ ቁጥጥር ምክንያት በ 1990 ዎቹ በምእራብ አፍሪካ ሃገራት አገልግሎት ላይ ከዋለው ማዳበሪያ 43 ከመቶው አስፈላጊ የሆነውን ንጥረ ነገር ያላሟላ ነው፡፡ በጤናው ዘርፍ ደግሞከስራ ገበታቸው አብዝተው የሚቀሩ የህክምና ባለሞያዎች ቁጥር ከፍተኛ እንደሆነ ያመላከተ ሲሆን መድሃኒቶችን በተመለከተ በ1990 ዎቹ በምእራብ አፍሪካዊቷሃገር ናይጄሪያ የሚገኙ መድሃኒት ቤቶች ከሸጧቸውመድሃኒቶች መካከል 50 በመቶው ተመሳስለው የተሰሩእንጂ ትክክለኛ መድሀኒት አለመሆናቸውን አረጋግጧል፡፡የ “ድምጽ አልባው” ሙስና ዋና ጎጂ ገጽታ በተጠቀሱትዘርፎች ላይ የረዥም ጊዜ ተጽእኖ ማሳደሩ መሆኑንከሪፖርቱ መረዳት ይቻላል፡፡ አዘውትረው ከስራ በሚቀሩመምህራን ምክንያት ተገቢውን ትምህርት የተነፈገ ልጅወይም ህፃን ለትምህርት የሚኖረው ፍላጎት ይቀንሳል፣ትምህርቱንም ለማቋረጥ ከመገደዱም ባሻገር ለወደፊትትምህርቱ መሰረት የሚሆነውን በቂ እውቀት ስለማያገኝራሱን፣ ቤተሰቡን ብሎም ሃገሩን በተገቢው መንገድ መጥቀም ሊሳነው ይችላል፡፡<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ም“ድምጽ አልባው” ሙስና አፍሪካንእያዳረሳት ነው:- የዓለም ባንክየዓለም ባንክ በቅርቡ ባወጣው አመታዊ የአፍሪካ ልማትጠቋሚ ሪፖርት ላይ “ድምጽ አልባው” ሙስና በአህጉሪቱእየተስፋፋ እንደሚገኝ ገልጧል፡፡ሪፖርቱ እንደሚያስረዳው“ድምጽ አልባው” ሙስና በአህጉሪቱ የሚገኙ የመንግስትሰራተኞች ለስራቸው ከሚከፈላቸው ደሞዝ ተመጣጣኝ የሆነ አገልግሎት ለህብረተሰቡ እንዳይሰጡ ምክንያት ሆኗል፡፡“ድምጽ አልባው” ሙስና የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓትላይ አሉታዊ ተጽእኖ በማሳደር ህብረተሰቡ ስርዓቱን እንዲንቅና እምነት እንዳይኖረው እያስገደደ ይገኛል፡፡ እንደ ሪፖርቱ ገለጻ ሁኔታው በተለይ በአህጉሪቱ የሙስና ችግርከጉቦና መደለያ ባለፈ በትምህርትና የአህጉሪቱ የጀርባ አጥንት በሆነው የግብርና መስክ ላይም ከፍተኛ ተጽእኖ እያሳደረ ይገኛል፡፡ ችግሩ በመላ አህጉሪቱ እየተስፋፋ በመሆኑህይወታቸው በመንግስት በኩል በሚሰጡ የተለያዩ አገልግሎቶች ላይ የተመሰረተውን የአፍሪካ ደሃ ህዝቦችና የሃገራቱን ልማት አደጋ ላይ እንደጣለው ሪፖርቱ ጠቁሟል፡፡በዓለም ባንክ የአፍሪካ ዋና የምጣኔ ሀብት ባለሞያ ሻንታዴቫራጃን እንዳብራሩት ምንም እንኳን እስካሁን “ድምጽአልባው” ሙስና ጎልቶ ያልወጣና በብዛት ያልተወራለትቢሆንም በህብረተሰቡ የእለት ተእለት ኑሮ ላይ አሉታዊተጽእኖ እያሳደረ ይገኛል፡፡ሪፖርቱ እንደገለጸው በጤናው ዘርፍ የመድሃኒትና የባለሞያ እጥረት፣ በወባና በሌሎች በሽታዎች ምክንያት የሚከሰተውን ሞት ያበራክተዋል፡፡ በሌላ በኩል ገበሬው ለምርትእድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ በሚያደርግና ጥራቱ በተጠበቀማዳበሪያ ምትክ ተገቢው ንጥረ ነገር የጎደለው ማዳበሪያሲቀርብለት ከነጭራሹ ማዳበሪያ መጠቀም ለማቆም ሊገደድ የሚችል ሲሆን ይህ ሁኔታ በሃገርና በአህጉር ደረጃለምርት መቀነስ ምክንያት መሆኑ አያጠራጥርም፡፡በተጨማሪም ሪፖርቱ የአፍሪካን የምጣኔ ሀብት ጠቋሚመረጃዎችንና “ድምጽ አልባው” ሙስና በምን መልኩ በአህጉሪቱ የአጭርና የረዥም ጊዜ የልማት እቅዶች መሳካትእንቅፋት እንደሆነ አብራርቷል፡፡ ምንም እንኳን “ድምጽአልባው” ሙስናን ለመዋጋት የፖሊሲና የተቋማት ቁርጠኝነት ጠቀሜታው የጎላ ቢሆንም በዋናነት ግን የህብረተሰቡን ተጠያቂነትና ተሳትፎ የሚሻ መሆኑን ዴቫራጃንጨምረው መግለጻቸው በሪፖርቱ ተካትቷል፡፡ቻታም ሀውስ የተባለ ለንደን የሚገኝ የምርምር ቡድን አባል የሆኑት ጆዌል ኪባዞን በበኩላቸው በዓለምባንክ በኩል ሪፖርቱ ይፋ መሆኑ ለችግሩ መፍትሄከመፈለግ አንጻር የመጀመሪያው እርምጃ መሆኑን ገልጸው ሌሎች አለም አቀፍ ድርጅቶችም የችግሩን አሳሳቢነት ለመጠቆም የበለጠ መስራትና በአፍሪካ መንግስታት ላይ ግፊት ማሳደር ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡ምንጭ:- የዓለም ባንክ እና ሌሎችም12


ትኩረትየመሬት ወረራው በሕግ ሲዳኝየፌደራል የ<strong>ሥነምግባር</strong> እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የተቋቋመው አግባብነት ካላቸው አካላት ጋር በመተባበር የ<strong>ሥነምግባር</strong>ና የፀረ-ሙስና ትምህርቶችን በማስፋፋት የነቃና ሙስናን ሊሸከም የማይችል ኅብረተሰብ ለመፍጠር፣የሙስና ወንጀልንና ብልሹ አሠራርን ለመከላከል እንዲሁም የሙስና ወንጀልንና ብልሹ አሠራርን ለማጋለጥ፣ለመመርመርና ለመክሰስ ነው፡፡ ከዚህ አንፃር ኮሚሽኑበአሁኑ ወቅት በርካታ አበረታች ተግባራትን አከናውኗል፡፡የ<strong>ሥነምግባር</strong>ና የፀረ-ሙስና ትምህርቶችን በማስፋፋት ረገድ እስከ 2002 ዓ.ም ድረስ ከ136,000 ለሚበልጡ የኅብረተሰብ ክፍሎች የግንዛቤ ማስጨበጪያ በፊት ለፊት ትምህርት አማካይነት ግንዛቤ ማስጨበጥ ተችሏል፡፡ ከዚህ ጎን ለጎን ኅብረተሰቡን እያዝናኑ በሚያስተምሩ አጫጭር የሬዲዮና የቴሌቪዥንስፖቶች፣ ድራማዎች፣ ቴሌ ኮንፈረንሶችና ቶክ ሾዎችእንዲሁም በሕትመት ውጤቶች አማካይነት በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ዜጎች የ<strong>ሥነምግባር</strong>ና የፀረ-ሙስና ትምህርት ተሰጥቷል፡፡ በመንግሥት መሥሪያ ቤቶችና የልማት ድርጅቶች ውስጥ የ<strong>ሥነምግባር</strong> መከታታያ ክፍሎችንበማቋቋም በተቋሞቹ ውስጥ ለሙስናና ብልሹ አሠራር በርየሚከፍቱ አሠራሮችን እያጠኑ ለሚመለከተው የመሥሪያቤቱ የበላይ አካል እያሳወቁና እንዲስተካከሉ እያደረጉይገኛሉ፡፡በተመሳሳይ ኮሚሽኑ ከ140 በላይ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶችና የልማት ድርጅቶች ውስጥ ለሙስናና ለብልሹ አሠራርበር የሚከፍቱ አሠራሮችን በማጥናት የመፍትሄ ሃሳቦችን በማቅረብ ተግባራዊነታቸውንም ክትትል በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ኮሚሽኑ ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ እስከ 2002 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ 14,400 የሙስና ወንጀል ጥቆማዎችንና አቤቱታዎችን ተቀብሎ የተለያዩ ውሳኔዎችንምአሳልፏል፡፡ በኮሚሽኑ ስልጣን ክልል ውስጥ የሚወድቁትንጥቆማዎችና አቤቱታዎች እንደየጉዳዩ ክብደት እና ቅደም ተከተል የምርመራ ሥራዎችን በማካሄድ አጥፊዎችን ለፍርድ የማቅረቡን ተግባር አከናውኗል፤ በማከናወንላይም ይገኛል፡፡ በዚህ ረገድ በተጠቀሰው ጊዜ 500በሚጠጉ የሙስና ወንጀል ፈፃሚዎች ላይ ከአንድ ዓመትእስከ 21 ዓመት የሚደርስ እስራት እንዲፈረድባቸውተደርጓል፡፡ በ1997 ዓ.ም ተካሂዶ የነበረውን ሀገርአቀፍ ምርጫ ምክንያት በማድረግ በተለይ በአዲስ አበባከተማ ውስጥ ከፍተኛ የመሬት ወረራ መፈፀሙይታወሳል፡፡ በመሆኑም ኮሚሽኑ እነዚህ ሕገወጥ የመሬት ወረራ እንዲፈፀም ሁኔታዎችን ያመቻቹት የመንግሥት ሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች፣ ደላሎችና ሌሎችተባባሪ ግለሰቦችን በጀመረው ምርመራ አማካይነት በቁጥጥር ሥር አውሏል። በወንጀሉም የተገኘውን መሬት እንዲታገድ አድርጓል፡፡ በምርመራ ውጤቱም መሠረት ኮሚሽኑ ክስአቅርቦ ሲከራከር ቆይቷል፤ አሁንም ክርክር እያደረገባቸውያሉ ጉዳዮች አሉ፡፡ በዚሁ መሠረት በ2002 በጀት ዓመትኮሚሽኑ ከመሬት ወረራ ጋር በተያያዘ የተሳትፉትን ክስመስርቶ ያስፈረደባቸውን መዝገቦችና የተሰጠውን የፍርድቤት ውሳኔ በዚህ ጽሁፍ ለመዳሰስ እንሞክራለን፡፡የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ ወንጀል ችሎትሚያዝያ 14 ቀን 2002 ዓ.ም ባዋለው ችሎት በአዲስአበባ ከተማ አስተዳደር ከ205 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ የመንግሥት መሬት በሕገ ወጥ መንገድ በመሸጥየሙስና ወንጀል የፈፀሙ ሰባት ግለሰቦች ከሁለት እስከ 15ዓመታት በሚደርስ እስራትና ከብር 500 እስከ 20,000በሚደርስ የገንዘብ ቅጣት እንዲቀጡ ውሳኔ አስተላልፎባቸዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ያስተላለፈባቸው እነዚህ ግለሰቦች በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ ክፍለ ከተሞች ከ1998-1999 ዓ.ም በመንግሥት ሥራ ላይ ተቀጥረውበሚሠሩበት ወቅት በፈፀሙት ወንጀል ነው፡፡ ግለሰቦቹ በሕገ ወጥ መንገድ የመኖሪያ ቤት የኅብረት ሥራ ማኅበራትንበማደራጀትና በሥራ አጋጣሚ ያገኙትን ምስጢር በመጠቀም የማይገባ ጥቅም ለራሳቸውና ለሌሎች ለማስገኘት አስበውበመንቀሳቀስ በመንግሥትና በሕዝብ ሃብት ላይ ጉዳትአድርሰዋል፡፡ኮሚሽኑ በመሠረተው ክስ መሠረት አንደኛ ተከሳሽበኃይሉ ለማ ድንቁ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቦታናየቤት አስተዳደር መምሪያ ቴክኒሽያን ሆኖ በሚሠራበትወቅት በሥራው አጋጣሚ በዕጁ የገባውን የአዲስ አበባከተማ ማስተር ፕላን ከኮምፒዩተር ወደ ሲዲ ገልብጦወስዷል፡፡ ይህን በሕገወጥ መንገድ በሲዲ ያወጣውንማስተር ፕላን መሠረት በማድረግና በኮምፒዩተር በመታገዝ በከተማው ያሉ ክፍት ቦታዎችን ለይቶ በማውጣትበወቅቱ ለማኅበራት ይፈቀድ የነበረውን የቤቶች ፕላንእያዘጋጀ ‹‹ሻላ›› እና ‹‹ቦጋለ›› የተባሉ ሁለት ሕገወጥየመኖሪያ ቤት የኅብረት ሥራ ማኅበራትን ከግብረ አበሮቹጋር አደራጅቷል፡፡ በእነዚህ የመኖሪያ ቤት የኅብረት ሥራማኅበራት የታቀፉ 468 አባላት ከ1981 ዓ.ም ጀምሮ በሕጋዊ መንገድ ተደራጅተው መሬት ያገኙ ለማስመሰል ሐሰተኛ ሰነዶችን፣ ደብዳቤዎችን፣ የመሥሪያ ቤቶችን ማኅተሞች እና ሳይት ፕላኖች መጠቀሙ በክሱ ላይ ተመልክቷል፡፡በተመሳሳይ በቅደም ተከተል ሁለተኛ እና ሦስተኛ ተከሳሾች ደሃብ ገብረሕይወት በየካ ክፍለ ከተማ የማኅበራት ቡድን መሪ እና አባይ ለገሰ ወልዴ በኮልፌ ቀራንዮክፍለ ከተማ ሊዝ አፈፃፀም ውል አጣሪ ሆነው በሚሠሩበት ወቅት በመንግሥት የተሰጣቸውን የሥራ ኃላፊነትያለ አግባብ በመገልገል ከአንደኛ ተከሳሽ ከኃይሉ ድንቁጋር በጥቅም በመመሳጠር የህገወጥ ማኅበራቱን ፋይሎች በ1998 እና በ1999 ዓ.ም ወደ ክፍለ ከተሞች መዝገብቤቶች እንዲገቡ አድርገዋል፡፡ እንዲሁም የማኅበራቱ አባላት እያንዳንዳቸው ለአንደኛ ተከሳሽ ብር 3000 እንዲከፍሉበማስደረግ በግብረ አበርነት ሙስና ወንጀል ፈጽመዋል፡፡13<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ም


በሌላ በኩል ተክለድንግል ገብረሚካኤል የተባለውስድስተኛ ተከሳሽ ደግሞ ከአንደኛ ተከሳሽ ጋር በመመሳጠር ‹‹ሻላ›› የተባለውን ሐሰተኛ የመኖሪያ ቤት የኅብረት ሥራ ማኅበር በመመሥረትና በሐሰተኛ መንገድየተዘጋጀውን የማኅበሩን ፋይል በ1998 ዓ.ም በሁለተኛ ተከሳሽ ደሃብ ገብረሕይወት አማካኝነት ወደ የካክፍለ ከተማ ማኅበራት ማደራጃ ጽሕፈት ቤት እንዲገባበማድረግ 248 ሰዎች በሕገወጥ መንገድ መሬት እንዲያገኙ አድርጓል፡፡ በዚህም ለራሱና ለማኅበሩቱ አባላትሕገወጥ ጥቅም በማስገኘት በመንግሥትና በሕዝብ ላይጉዳት ማድረሱን የኮሚሽኑ ዐቃቤ ሕግ ክስ ያስረዳል፡፡ሌሎች በቅደም ተከተል ሰባተኛ፣ ስምንተኛእና ዘጠነኛ ተከሳሾች መከተ ታደሰ፣ ዳንኤል በላይ እናሃብታሙ መኳንንት በበኩላቸው በ1999 ዓ.ም ከአንደኛተከሳሽ ጋር ተመሳጥረው በሕገወጥ መንገድ የጥቅሙ ተካፋይ መሆናቸውን የኮሚሽኑ የዐቃቤ ሕግ ክስአመልክቷል፡፡በአጠቃላይ ሁሉም ተከሳሾች በወንጀሉ ሥራ እና በተገኘው ውጤት ሙሉ ተካፋይ በመሆን የሊዝ ግምቱብር ከ205,540,000 /ሁለት መቶ አምስት ሚሊዮን አምስት መቶ አርባ ሺህ/ በላይ የሚያወጣ የመንግሥት መሬትለራሳቸውና በሕገወጥ መንገድ ላደራጇቸው የማኅበር አባላትአከፋፍለው ሰጥተዋል፡፡ ተከሳሾቹ በሙሉ ሃሳባቸውና አድራጎታቸው በግብረ አበርነት በፈፀሙት በሥልጣን አለአግባብመገልገል የሙስና ወንጀል ተከሰው ሊፈረድባቸው ችሏል፡፡የሥራ ኃላፊነትና ባለሙያነት ተመድበው ይሠሩ የነበሩትእነዚህ ተከሳሾች ለራሳቸው የማይገባ ጥቅም ለማግኘትናለሌሎች ለማስገኘት በማሰብ በሐሰተኛ ማኅበር ስም በሕገወጥ መንገድ ተደራጅተው የጋራ መኖሪያ ቤት /ኮንደሚኒየም/ መሥሪያ ቦታ እንዲሰጣቸው ለጠየቁ ነጋዴ ግለሰቦች እና ዘመዶቻቸውን ደግሞ በማኅበር አባልነት እንዲገቡ በማድረግ በሥልጣናቸው ያለአግባብ ተገልግለዋል፡፡እነዚህ በንግድ ሥራ ላይ የተሠማሩት ግለሰቦች ‹‹አግራው የመኖሪያ ቤቶች የኅብረት ሥራ ማኅበር›› የሚልሐሰተኛ ማኅበር በራሳቸው፣ በሚስቶቻቸው እና በዘመዶቻቸው ስም በመመሥረት እንዲሁም የማኅበሩ አመራርና ጉዳይ አስፈፃሚዎች በመሆን ተንቀሳቅሰዋል፡፡ በዚህየተነሳም በእነዚህ ነጋዴ ግለሰቦች፣ የመንግሥት የሥራኃላፊዎችና ባለሙያዎች አማካኝነት የሊዝ ግምቱ51,335,575.20 የሚሆን መሬት አለአግባብ ወስደዋል፡፡ተከሳሾቹም የቀረበባቸውን የሰውና የሰነድ ማስረጃመከላከል ባለመቻላቸው ፍርድ ቤቱ ከላይ በተጠቀሰው ቀንበዋለው ችሎት ወንድወሰን ዓለሙ በቀለ፣ ዮሴፍ ከበደመርኔ እና ገነት ማሞ ተምትሜ እያንዳንዳቸው በሰባትዓመት ጽኑ እስራትና በብር 2,000፣ አላዊ ሱሩርቡሴር፣ መሐመድ ሱሩር አብደላ እና ሙክታር ኑር ደግሞ እያንዳንዳቸው በሦስት ዓመት ጽኑ እስራትና በብር 2,000 ቅጣት እንዲሁም ሳምሶን በቀለ ቅጣው በሁለትዓመታት ጽኑ እስራትና በብር 500 እንዲቀጡ ወስኗል፡፡<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምበክሱ ሂደትም ኮሚሽኑ ያቀረበባቸውን የሰውና ሰነድ ማስረጃዎች መከላከል ባለመቻላቸው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ ወንጀል ችሎት ሚያዝያ 14 ቀን 2002ዓ.ም በዋለው ችሎት አንደኛ ተከሳሽ በኃይሉ ለማ ድንቁ በ11 ዓመት ጽኑ እስራትና ብር 20,000 እንዲቀጣሲወሰን በሁለተኛ ተከሳሽ ደሃብ ገብረሕይወት ላይ 15ዓመት ጽኑ እስራትና የብር 20,000 ቅጣት ወስኗል፡፡በተመሳሳይ በሦስተኛ ተከሳሽ አባይ ለገሰ ወልዴ እናበስድስተኛ ተከሳሽ ተክለድንግል ገብረሚካኤል እያንዳንዳቸው በአምስት ዓመት ጽኑ እስራትና በቅደም ተከተል 1000 እና የ1500 ብር ቅጣት አስተላልፎባቸዋል፡፡እንዲሁም ጉዳያቸው በሌሉበት የታየው በቅደም ተከተልሰባተኛ፣ ስምንተኛ እና ዘጠነኛ ተከሳሾች መከተ ታደሰ፣ዳንኤል በላይና ሃብታሙ መኳንንት እያንዳንዳቸው በሁለትዓመት ጽኑ እስራትና በብር 500 እንዲቀጡ ችሎቱ ወስኗል፡፡በተመሳሳይ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛወንጀል ችሎት ሚያዝያ 18 ቀን 2002 ዓ.ም በዋለውችሎት ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሕገወጥ ማኅበር ስም የከተማ ቦታ በመውሰድ የሙስና ወንጀልየፈፀሙ ሰባት ግለሰቦች ላይ እስራትና የገንዘብ ቅጣትወስኖባቸዋል፡፡ ኮሚሽኑ ክስ መስርቶባቸው ከተፈረደባቸው መካከል በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የመሬት ልማትጽሕፈት ቤት ውስጥ ሥራ አስኪያጅ የነበረው ወንድወሰንዓለሙ በቀለ፣ የመሬት ልማት አስተዳደር የቡድን መሪነበረው ዮሴፍ ከበደ መርኔ፣ የመሬት አስተዳደር የሊዝአፈፃፀም እና ክትትል ቡድን መሪ የነበረችው ገነት ማሞተምትሜ፣ የመሬት ልማት አስተዳደር የቅየሳ ሠራተኛሳምሶን በቀለ ቅጣው እንዲሁም በንግድ ሥራ የሚተዳደረው መሐመድ ሱሩር አብደላ እና ሙክታር ኑሪ ይገኙበታል፡፡ የኮሚሽኑ ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾቹ ላይ የመሠረተውየክስ መዝገብ እንደሚያስረዳው በተለያዩ የመንግሥት14በተመሳሳይ ኮሚሽኑ በገነት ማሞ ተምትሜ የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የሊዝ ክትትል ቡድን መሪ እና ዓለምይትባረክ ወ/ማርያም የክፍለ ከተማው የማኅበራት ማደራጃ ጽሕፈት ቤት ተወካይ ሆነው በሚሠሩበት ወቅትበሥልጣን አለአግባብ መገልገል ወንጀል በመሠረተው ክስበእስራትና በገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ የፌደራል ከፍተኛፍርድ ቤት አንደኛ ወንጀል ችሎት ወስኖባቸዋል፡፡ እነዚህ ተከሳሾች የማይገባ ጥቅም ለራሳችው ለማግኘትና ለሌሎች ለማስገኘት አስበው ‹‹እሸት ፍሬ ቁጥር 2›› ተብሎየሚጠራ ሕገወጥ የጋራ መኖሪያ ቤት ሕንፃ ኅብረትሥራ ማኅበር በማቋቋም በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማልዩ ስሙ ቤተል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የአዲስ አበባከተማ አስተዳደር ያወጣውን የጋራ መኖሪ ሕንፃ ኅብረትሥራ ማኅበር መመሪያን በመጣስ ስፋቱ 864 ካሬ ሜትርየሚሆን ቦታ ማንነታቸው በግልጽ ላልታወቁ ግለሰቦች በሊዝ መልክ በካርታ ቁጥር ሊዝ/ዕጣ/19188/00 አዘጋጅተውመስጠታቸው በሰውና በሰነድ ማስረጃ ተረጋግጦባቸዋል፡፡ተከሳሾቹም የቀረበባቸውን የሰውና የሰነድ ማስረጃ መከላከል ባለመቻላቸው ገነት ማሞ በ17 ዓመት ጽኑ እስራትና በብር 16,000 እና ዓለም ይትባረክ በሦስት ዓመትእስራትና በብር 1,000 እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ ወስኗል፡፡በሌላ በኩል ወ/ሮ አልማዝ ኪዳኔ ግደይ የቦሌ ክፍለ ከተማመሬት ልማት አስተዳደር መምሪያ ማኅደር አጣሪ፣ ወ/ሮማህሌት አምሳሉ ደርሰህ የክፍለ ከተማው የንድፍ ሠራተኛ፣ ገረመው ተስፋዬ መኩሪያ በቦሌ ክፍለ ከተማ የቀበሌ14/15 የነዋሪዎች አገልግሎት ኃላፊ ሆነው በሚሠሩበትወቅት በሥልጣናቸው አለአግባብ በመገልገል በግል ሥራከሚተዳደሩ አቶ ሃድራ ሃቢብ በክሪ እና የዓለምብርሃን ተስፋዬ አለሙ ጋር በመመሳጠር በሐሰት በተዘጋጀ ካርታ የመንግሥት መሬት በማስወሰድ ራሳቸውና ሌሎች እንዲጠቀሙ በማድረጋቸው በፈፀሙት የሙስና ወንጀል ተከሰዋል፡፡


ወ/ሮ አልማዝ ኪዳኔ የክፍለ ከተማው የመሬት ልማትአስተዳደር መምሪያ ማኅደር አጣሪ ሆና በምትሠራበትወቅት ለአቶ የዓለምብርሃን ተስፋዬ ሕገወጥ የስም ዝውውር በመፈፀም፣ ወ/ሮ ማህሌት አምሳሉ ደግሞ የተጭበረበረካርታን መሠረት በማድረግ የተሳሳተ የልኬት ሪፖርትበማቅረብ፣ አቶ ገረመው ተስፋዬ በበኩሉ አለአግባብ የነዋሪነት መታወቂያ በመስጠት እና ግለሰቡ በሕገወጥ መንገድበአቶ ሃድራ ሃቢብ እንዲወከል ሁኔታዎችን በማመቻቸትለወንጀሉ መፈፀም ተባባሪ ሆነዋል፡፡ አቶ የዓለምብርሃን ተስፋዬ ደግሞ በሐሰተኛ ሰነድ የተዘጋጀ ካርታ በተወካዩ ሃድራሃቢብ አማካኝነት ብር 40,000 በመሸጥ ሕገወጥ ተጠቃሚመሆናቸውን የኮሚሽኑ ዐቃቤ ሕግ ክስ ጨምሮ ያስረዳል፡፡በመሆኑም ተከሳሾቹ በኮሚሽኑ የቀረበባቸውን የሰውናየሰነድ ማስረጃ መከላከል ባለመቻላቸው ፍርድ ቤቱ መጋቢት 7 ቀን 2002 ዓ.ም በዋለው ችሎት የዓለምብርሃንተስፋዬ በአራት ዓመታት ጽኑ እስራትና በብር 6,000፣ አቶሃድራ ሃቢብ በሦስት ዓመታት ጽኑ እስራትና በብር 5,000፣ወ/ሮ መኅሌት አምሳሉ በሦስት ዓመታት ጽኑ እስራትናበብር 1,000፣ ወ/ሮ አልማዝ ኪዳኔ በአንድ ዓመት እስራትና በብር 500 እንዲሁም አቶ ገረመው ተስፋዬ በአንድ ዓመት እስራትና በብር 300 እንዲቀጡ ወስኗል፡፡በተመሳሳይ 208 ሚሊዮን ብር የሚገመት 120,000ካሬ ሜትር የከተማ ቦታ በመውሰድና በማስወሰድ ከተሳተፉ 13 ተከሳሾች መካከል ስምንቱ እንዲቀጡ ፍርድቤት ውሳኔ ሰጥቶባቸዋል፡፡ የኮሚሽኑ ዐቃቤ ሕግ ክስ እንደሚያስረዳው የመንግሥት ሠራተኛ ከነበሩት ተከሳሾች መካከል አንደኛ ተከሳሽ ሙለሜ ረሽድ ሲራጅ በአዲስ አበባከተማ መሬት አስተዳደር ባለሥልጣን የይዞታና መረጃመምሪያ ኃላፊ፣ ሁለተኛ ተከሳሽ ለማ ደግፌ አባይነህየኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ መሬት አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ፣ ሦስተኛ ተከሳሽ ደሃብ ገ/ሕይወት ብሩ በየካክፍለ ከተማ ማኅበራት ማስፋፊያ ቡድን መሪ፣ ስድስተኛተከሳሽ ሚፍታህ አብዱ ዩሱፍ በሥራና ከተማ ልማትሚኒስቴር የጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት ቡድን መሪ ሆነውበሚሠሩበት ወቅት የተሰጣቸውን የሥራ ኃላፊነት አለአግባብ በመገልገል የማይገባ ጥቅም ለራሳቸው ለማግኘትና ለሌሎች በንግድና በድለላ ሥራ ለተሰማሩትና በቅደምተከተል ዘጠነኛ፣ አስረኛ፣ 11ኛ እና 12ኛ ተከሳሾችለሆኑት ቆንጅት ደስታ መኩሪያ፣ መኮንን ወለላ ካሳ፣ዮሴፍ ጌትነት አበበ እና ሠለሞን ግርማ ማኅተሙ ተገቢያልሆነ ጥቅም ለማስገኘት ተንቀሳቅሰዋል፡፡ እንዲሁምበግል ሥራ የተሰማሩት የመንግሥትን ጥቅም ለመጉዳትናየማይገባ ጥቅም ለራሳቸው ለማግኘት አስበው በወንጀሉበሙሉ ፍላጎታቸው በመሳተፍ የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል፡፡በዚህ መሠረት ሙለሜ ረሽድ ሲራጅ፣ ለማ ደግፌ አባይነህ፣ ወ/ሮ ደሃብ ገ/ሕይወት ብሩ እና ሚፍታህ አብዱዩሱፍ በመንግሥት የተሰጣቸውን ኃላፊነት ወደ ጎን በመተው ‹‹ሆህተ ምሥራቅ››፣ ‹‹ታዳጊ ተክል››፣ ‹‹ገነት በር››እና ‹‹አዋሽ 85›› የሚባሉትን ነባር የመኖሪያ ቤት የኅብረትሥራ ማኅበራት ፋይሎችን አለአግባብ የተለያዩ ጥቅሞችንበመቀበል በግል ሥራ ለሚተዳደሩት ዮሴፍ ጌትነት እና ሠለሞን ግርማ አሳልፈው ሰጥተዋል፡፡ በተጨማሪም በማኅበራቱ ስም የተዘጋጁትን ሃሰተኛ ሰነዶች ተደራጅተው ወደክፍለ ከተማ መዝገብ ቤቶች እንዲመለሱና ሕጋዊ እንዲሆኑ እንዲሁም በሕጋዊ መንገድ እንዲስተናገዱ የተለያዩ ደብዳቤዎችን በመፃጻፍ ሕገወጥ የሆነ ሽፋንና እገዛ ሰጥተዋል፡፡ዮሴፍ ጌትነት እና ሰለሞን ግርማ ከ10ኛ ተከሳሽ መኮንን ወለላው ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ተቀብለው‹‹የአዋሽ 85›› እና ‹‹ገነት በር›› የመኖሪያ ቤት ኅብረትሥራ ማኅበራት ፋይሎችን የሸጡ ሲሆን መኮንን ወለላውደግሞ የእነዚህን ነባር ማኅበራት ፋይሎች አለአግባብ በማውጣት በማኅበራቱ ስም የተዘጋጁ ሃሰተኛ ሰነዶች ተደራጅተው ተመልሰው እንዲገቡና ወደ ሌላ ክፍለ ከተማ እንዲላኩለት አድርጓል፡፡ በዚህም ግለሰቡ በ‹‹አዋሽ 85›› ማኅበር ስም ብር 33,283,776 የሚገመት 19,200 ካሬ ሜትርእዲሁም በ‹‹ገነት›› ማኅበር ስም ብር 77,662,144 ግምትያለው 44,800 ካሬ ሜትር የመንግሥት መሬት በሕገወጥማኅበር ስም አለአግባብ በመያዝ ለግል ጥቅሙ አውሏል፡፡በተጨማሪም እነዚህ ግለሰቦች የመንግሥት ሠራተኛከነበሩት ተከሳሾች የተቀበሉትን የ‹‹ሆህተ ምሥራቅ››እና የ‹‹ታዳጊ ተክል›› ማኅበራት ፋይሎችን ለዘጠነኛተከሳሽ ቆንጅት ደስታ በከፍተኛ ገንዘብ ሸጠዋል፡፡ ቆንጅት ደስታም በዚህ መልክ ያገኘችውን ሰነድ የመንግሥት ሠራተኞችን በገንዘብ በመደለል ለሕገወጥ ማኅበራት ቦታ እንዲመቻችላት በማድረግ በ‹‹ሆህተ ምሥራቅ››ስም ብር 41,604,720 ግምት ያለው 32,000 ካሬሜትር፣ በ‹‹ታዳጊ ተክል›› ማኅበር ስም ብር 55,472,960ግምት ያለው 24,000 ካሬ ሜትር የመንግሥት መሬት አለአግባብ በመውሰድ ለግል ጥቅሟ አውላለች፡፡በመሆኑም ተከሳሾቹ የቀረበባቸውን ማስረጃ መከላከልባለመቻላቸው ፍርድ ቤቱ የካቲት 12 ቀን 2002 ዓ.ምበዋለው ችሎት ሙለሜ ረሽድ ሲራጅ በሰባት ዓመት ጽኑእስራትና በብር 5,000፣ ለማ ደግፌ አባይነህ እና ደሃብገ/ሕይወት እያንዳንዳቸው በስምንት ዓመታት ጽኑ እስራትና በብር 6,000፣ ሚፍታህ አብዱ ዩሱፍ በሰባት ዓመትጽኑ እስራትና በብር 3,000፣ ቆንጅት ደስታ በሁለት የተለያዩክሶች በስምንት ዓመት ጽኑ እስራትና በብር 20,000፣መኮንን ወለላው ካሳ በሁለት የተለያዩ ክሶች በዘጠኝ ዓመትጽኑ እስራትና በብር 15,000 እንዲሁም ዮሴፍ ጌትነት እናሰለሞን ግርማ እንዳንዳቸው በሁለት የተለያዩ ክሶች የ10ዓመት ጽኑ እስራትና በብር 6,000 እንዲቀጡ ወስኗል፡፡በተመሳሳይ አንደኛ ተከሳሽ ተሞገስ ወልደ መላክ በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የማኅበራት ማደራጃና ማስፋፊያቡድን መሪ ሆነው በሚሰሩበት ወቅት በግል ሥራ ከሚተዳደሩት ከነጋሽ ሰማን እና ከአንዋር ጀማል ጋር በመመሳጠር የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን የኅብረት ሥራማኅበራት አደረጃጀትና አፈፃፀም መመሪያ በሚቃረንመልኩ አንደኛው ተከሳሽ ‹‹ታሕቢብ ቁጥር 2/13›› በሚልስያሜ በሕገወጥ መንገድ በሁለት ግለሰቦች የተመሠረተው ማኅበር ለሕጋዊነት የሚያስፈልጉ መስፈርቶችን ያላሟላ መሆኑን እያወቀ የማኅበሩን የአባላት ዝርዝር የያዘ ቅጽአጽድቆ ከሌሎች ሕጋዊ ማኅበራት ጋር እንዲካተት አድርጓል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ተከሳሹ በሕገወጥ መንገድ የተደራጀውን ማኅበር ሕጋዊ እንደሆነ አድርጎ ለክፍለ ከተማው መሬት አስተዳደር የማረጋገጫ ደብዳቤ ጽፎ ሰጥቷል፡፡ከዚሁ ጋር በተያያዘ ነጋሽ ሰማን እና አንዋር ጀማል ሕገወጥጥቅም ለማግኘት አስበው የማኅበሩ ሊቀመንበር እና ምክትል ሊቀመንበር በመሆን ማኅበሩ በአግባቡ ለመደራጀት የሚያበቃውን መስፈርት ሳያሟሉ በሕገወጥ መንገድ በማደራጀት ስፋቱ 1135.68 ካሬ ሜትር የሆነውን የመንግሥት ቦታበቁጥር ሊዝ/ዕጣ/18829/00 በ2/13/97 ዓ.ም በተዘጋጀ የይዞታ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት አማካይነት ወስደዋል፡፡15<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ም


በዚህም ሁሉም ተከሳሾች መንግሥት በወቅቱ በነበረውየሊዝ መሸጫ ዋጋ ከቦታው ማግኘት የሚገባውን ብር1,835,258.88 እንዲያጣ እና መንግሥት ላይ ከፍ ያለጉዳት ከማድረሳቸውም በላይ በመላ ሃሳባቸውና አድራጎታቸውም በሚያስከትለው ውጤት ተስማምተው አውቀውናፈቅደው በግብረአበርነት የፈፀሙት የሙስና ወንጀል ጥፋተኝነታቸው በሰውና በሰነድ ማስረጃ ተረጋግጦባቸዋል፡፡ በመሆኑም የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ ወንጀል ችሎት የካቲት 12 ቀን 2002 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተሞገስ ወልደመላክ በስምንት ዓመታት ጽኑ እስራትና በብር 50,000፣ነጋሽ ሰማን እና አንዋር ጀማልን ደግሞ እያንዳንዳቸው በሰባት ዓመት ጽኑ እስራትና በብር 4,000 እንዲቀጡ ወስኗል፡፡እንዲሁም በዚሁ ክፍለ ከተማ የመሬት አስተዳደር ውስጥ በተለያዩ የስራ ኃላፊነቶች ላይ ይሠሩ የነበሩ ተከሳሾች 1ኛ ወንደሰን ዓለሙ፣ 2ኛ ገነት ማሞ፣ 3ኛዮሴፍ ከበደ፣ 4ኛ ሳምሶን በቀለ፣ 5ኛ ብርቱካን ማሩበሕገወጥ መንገድ ጥቅም ለማግኘትና ለማስገኘት በማሰብበግል ሥራ ከሚተዳደሩትና በቅደም ተከተል ከ6ኛ - 8ኛከሆኑት ተማም ላለምዶ፣ ኑረዲን ሲን እና ሴፉ ከማልጋር በመመሳጣር መሬት በመምራትና በመስጠት በመንግሥት ላይ ከ2,000,000 ብር በላይ ጉዳት አድርሰዋል፡፡የሚሰራው ስራ ግልጽትንና ተጠያቂነትን ተላብሶ እንዲተገበርእገዛ ያደርጋል ፤ ለሚታዩ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠትከማስቻሉም በላይ ባለሙያዎች ከግል ስሜታቸውና አድሏዊአሰራር ነጻ ሆነው እንዲሰሩ የሚያሰችል መሆኑን ጥናቱያመለክታል::በአጠቃላይ በድሬዳዋ መሬት ልማትና አስተዳደር ባለሥልጣንእየተካሄደ ያለው የመሠረታዊ የአሠራር ሂደት ለውጥ አሠራሩን ቀልጣፋና ግልፅ በማድረግ ተገልጋዩን ለማርካት ከማስቻሉባሻገር ሙስናና ብልሹ አሠራርን ከመከላከል አንፃርም አስተዋጽኦ እንደሚኖረው የሚታመን ሲሆን በተለይም በመሬት አስተዳደር ሥርዓቱ ውስጥ የታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ ግልጽነትንናተጠያቂነትን ለማስፈን የሚያስችሉ ሁኔታዎችን ከማጠናከርአንፃር በባለሥልጣኑ፡-1. በአስተዳደሩ ያለውን የመሬት ይዞታና አጠቃቀም በዝርዝርመዝግቦ መያዝና ይህን መሠረት ያደረገ አጠቃቀም መዘርጋትናለዚህም የመሬት አጠቃቀም ስርአቱ በዘመናዊ የመረጃ ቴክኖሎጂእንዲታገዝ ማድረግና የመረጃ ስርአቱን ማጠናከር፣2. አሠራሩን ለመምራት የወጡ ህጎችን ጠንቅቆ በመረዳት ለተፈፃሚነታቸው ተገቢውን ትኩረት መስጠት፣3. የሚከናወኑ ጥሩ ሥራዎችን ከማበረታታት ባሻገር ለሚፈጠሩየህግ ጥሰቶችና ጥፋቶች ተጠያቂነትን በግልጽ ማመላከት፣<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምተከሳሾቹም በኮሚሽኑ የቀረበባቸውን የሰውና ሰነድማስረጃ መከላከል ባለመቻላቸው 1ኛ እና 2ኛ ተከሳሾች እያንዳንዳቸው በ15 ዓመት ጽኑ እስራትናበብር 15,000፣ 3ኛ ተከሳሽ በ11 ዓመት ጽኑእስራትና በብር 14,000፣ 4ኛ ተከሳሽ በአራት ዓመትጽኑ እስራትና በብር 4,000፣ 5ኛ ተከሳሽ በሦስት ዓመት ጽኑ እስራትና በብር 3,000 እንዲሁም ከ6ኛ - 8ኛያሉ ተከሳሾች እያንዳንዳቸው በሌሉበት በአራት ዓመት ጽኑ እስራትና በብር 4,000 እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱጥር 25 ቀን 2002 ዓ.ም በዋለው ችሎት ወስኖባቸዋል፡፡በአጠቃላይ ኮሚሽኑ የሙስና ወንጀል የሚፈጽሙትንተጠርጣሪዎች ከኅብረተሰቡ በሚደርሰው ጥቆማ እና በራሱተነሳሽነት ተከታትሎ ለፍርድ የማቅረቡን ሥራ አጠናክሮቀጥሏል፡፡ በተጠናቀቀው በጀት ዓመትም በተለይ በሕገወጥመንገድ የመሬት ወረራ እንዲፈፀም ሁኔታዎችን በማመቻቸት የተሳተፉትንና ወረራውን የፈፀሙት ላይ ፍርድ ቤቱለሌሎች አስተማሪ ይሆናል ያለውን ውሳኔ አስተላልፏል፡፡ምንም እኳን ወንጀል ፈጽሞ ለጊዜው መሰወር ቢቻልም ከሕዝብና ከመንግሥት መሠወር አይቻልም፡፡ ስለሆነም በሌሉበት ፍርድ የተላለፈባቸውን ወንጀለኞች ኅብረተሰቡ ጥቆማበማቅረብ አጋልጦ እንዲሰጥ ኮሚሽኑ ጥሪውን ያቀርባል፡፡ውስን ... ከገጽ 26 የዞረነገር ግን በስራው ላይ የተሰማሩ ፈጻሚ አካላት በቂ ግንዛቤእንዲኖራቸው ስልጠና ስለማይሰጣቸው በሚሰጧቸው አገልግሎቶች ለይ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ወጥ ባልሆነና ተጠያቂነትንና ግልፅነትን ባልተከተለ መንገድ ስራቸውን ስለሚያከናውኑ አሰራሩን ለሙስናና ብልሹ አሰራር የተጋለጠ አድርጎታል፡፡4. የተገልጋዮችን ቅሬታ ለማስተናገድ የሚቻልበት አመቺ ስርአት መዘርጋትና ተግባራዊ ማድረግ፣5. የክትትልና ቁጥጥር ሥራዎችን በተቀናጀ መልኩ ማከናወን፣6. የመሬት አስተዳዳደሩን ሥራዎች በየጊዜው በመገምገምና የክዋኔ ኦዲት በማካሄድ በሚታዩ ክፍተቶች ላይ ተገቢውን የእርምት እርምጃ መውሰድ፣7 በመሬት አስተዳደሩ ውስጥ ሊፈጠር የሚችል ሙስናን ለመከላከል የበላይ አመራሩን ቁርጠኝነት የበለጠ ማጎልበትና ህግንማዕከል አድርጎ መንቀሳቀስ፣8. ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር ያለውን የቅንጅትሥራ የበለጠ ማጠናከር፣9. የህብረተሰቡን ተሳትፎ ማሳደግና በሚወጡ ህጎች ላይ የተገልጋዩንም ሆነ በስራው ላይ የተሰማራውን ባለ ሙያ ግንዛቤ በማሳደግ አቅሙን ለማጎልበት አስፈላጊ መሆኑን የጥናቱ ሪፖርት በማጠቃለያው አመልክቷል ፡፡እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ ኮሚሽኑ ለከተማው አስተዳደሩ በሰጠው አስተያየት መሰረት በዱከም ከተማ ዘመናዊ የመሬት አስተዳደር ላይ የልምድ ልውውጥ አድርጓል፡፡ በመሆኑም በድሬዳዋከተማ አስተዳደር ከመሬት ጋር ተያይዞ የታዩት ችግሮች በሀገሪቱ በሚገኙ በሌሎችም ከተሞች የታዩ በመሆናቸው ችግሩንለማስወገድ የሁሉንም ርብርብ የሚጠይቅ ነው፡፡ ውስን የሆነውንመሬት ለመኖሪያም ሆነ የተለያዩ ልማቶችን ለማከናወን የሚፈልጉ ዜጎችና ልማታዊ ባለሀብቶች መመሪያና ደንቡን መሰረት ባደረገ፣ ግልጽና ፍትሀዊ መንገድ ሊያገኙ ይገባል፡፡የአሠራር ሥርዓት ክፍተቱን ለመድፈን የመሬት ልማትና አስተዳደርን በተመለከተ የወጡ አዋጆች፣ ደንቦችና መመሪያዎችንመሠረት ያደረገ አፈፃፀም ተግባራዊ ለማድረግ ለስራ ኃላፊዎችናለሰራተኞች ስልጠና በመስጠት በቂ ግንዛቤ በማሰጨበጥ በአፈጻጸሙ ለሚከሰቱ ችግሮች ወቅታዊ የእርምት እርምጃ በመውሰድግልጽትንና ተጠያቂነትን በማስፈን መስራት ያስፈልጋል ፡፡በሚወጡ አዋጆች፣ ደንቦችና መመሪያዎች ላይ ግንዛቤ መያዝ16


መልካም ዜጋ“ከሙስና በፀዳ እና የቅንነትን መርህ ተከትሎበመሥራት በተሰማሩበት መስክ ውጤታማመሆን ይቻላል።”ዶ/ር መሰለ ኃይሌዶ/ር መሰለ ኃይሌ ይባላሉ በግንባታው ዘርፍ የተሰማሩባለሙያ ናቸው፡፡ የሳቸው ተሞክሮ በግንባታ እና በኢንቨስትመንት ዘርፍ ለተሰማሩት ብቻ ሳይሆን <strong>ሥነምግባር</strong>ንበተከተለ መንገድ ሠርተው ስኬታማ ለመሆን ለሚጥሩዜጎች ሁሉ አርአያ ሊሆኑ እንደሚችሉ እናምናለን፡፡ ቃለምልልሱን እነሆ፡፡<strong>ሥነምግባር</strong>፡- በመጀመሪያ ስለ ተወለዱበት አካባቢ፣ አስተዳደግዎ፣ የቤተሰብዎ እና ፡ በልጅነትዎ የነበረዎትን የ<strong>ሥነምግባር</strong> ሁኔታ ቢገልጹልን?ዶ/ር መሰለ፡- የተወለድኩት በወለጋ ነቀምት ከተማ ነው፡፡አባቴ በጥብቅና ሞያ ነበር የሚተዳደሩት እናቴ ደግሞ የቤት እመቤት ናት፡፡ አባቴ በተለይ ልጅን በመቅጣት፣ በማስተካከል በዲሲፕሊን በጣም የሚያምን ስለነበር በጣም በከፍተኛ ቁጥጥር ነበር ያሳደገኝ፡፡ የእኔን <strong>ሥነምግባር</strong> በተመለከተ እንደ እድሜዬ የሚለያይ ይመስለኛል። የተወሰኑ ጊዜዎች በጣም ወላጅን፣ አካባቢን፣ ሁሉን አክባሪ የነበርኩበትጊዜ ነበር፡፡ የተወሰነ ጊዜ ደግሞ ወደ 14 ወደ 15 ዓመት አካባቢ የጉርምስና ወቅት በመሆኑ በእኛ ጊዜ የተለመደው ወደፖለቲካ መግባት ስለነበር በዛ ውስጥ የመሳተፍ ሁኔታ ነበር፡፡በአጠቃላይ በልጅነቴ ወይም በወጣትነት ዘመኔ መጥፎየማይባል <strong>ሥነምግባር</strong> ነበረኝ ማለት እችላለሁ፡፡ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ የአካባቢያችን ህብረተሰብ በልጆች አስተዳደግና <strong>ሥነምግባር</strong> ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ነበረው፡፡ ህብረተሰቡ ሁሉ ልጆችን አሳዳጊ፣ አስተማሪ እናቀጪ ነው፡፡ ስለዚህ ልጅ ሆነን በምናጠፋበት ጊዜ ከወላጅቢሰወር ጎረቤት ዝም ብሎ አያልፍም ነበር፡፡ ኳስ ስንጫወትትልቅ ሰው በስፍራው ካለ ጨዋታችንን አቁመን ሰውካለፈ በኋላ ነበር የምንቀጥለው፡፡ ምክንያቱም ሰው በኳስብንመታ ጥሩ <strong>ሥነምግባር</strong> አይደለም ብለን ስለምናስብ ነበር፡፡ ሌላው የማስታውሰው እኔ ባደግኩበት ሰፈር የፖሊስማሰልጠኛ ነበር፡፡ በማሰልጠኛው የነበሩ የፖሊስ አሰልጣኞች እግርኳስ፣ ሩጫ፣ ቅርጫት ኳስ፣ ቮሊቦል፣ ቦክስያለማምዱንና በራሳቸው ገንዘብ ደግሞ ሽልማት ገዝተውይሰጡን ነበር፡፡ የሰፈሩን ልጅ በማሳደግ ኃላፊ ነን ብለውጊዜያቸውንና ገንዘባቸውን ሰውተው ትርፍ ጊዜያችንን በስፖርት እንድናሳልፍ ያሰለጥኑን ነበር፡፡ ሌላው ደግሞ ወደጊንቢ/ቡና የሚመረትበት አካባቢ/ እንኳንስ ሊሰራረቅ ሰውገንዘብ ሲለዋወጥ ሳይቆጥር ነበር የሚረካከበው፡፡ ሀያ ሺህሰላሳ ሺህ ብር ዝም ብሎ ነበር የሚቀባበለው፡፡ በህብረተሰቡ መሀል በመተማመን እና ቃልን በመጠበቅ ላይየተመሰረተ ጠንካራ እሴት ነበረ፡፡ ይህ ታዲያ ለአካባቢው ልጆችመልካም <strong>ሥነምግባር</strong> እንዲኖረን የራሱ አስተዋጽኦ ነበረው፡፡<strong>ሥነምግባር</strong>፡- የአንደኛ፣ የሁለተኛ ደረጃ እንዲሁም የከፍተኛ ትምህርትዎን የት ተከታተሉ? ዝንባሌዎና አጠቃላይ የትምህርት ሁኔታዎን ቢያጫውቱን?ዶ/ር መሰለ፡- አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቴን የተማርኩት ነቀምቴ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትየሚባል ነው፡፡ በዛን ጊዜ በመጀመሪያ የነበረኝ ዝንባሌ የህብረተሰብ ሳይንስ ማጥናት ነበር፡፡ ሆኖም በዚያን ጊዜ ኢህአፓ መኢሶን ተብሎ ተከፋፍሎ በነበረው የፖለቲካ ቀውስወደ ምህንድስና ብሄድ ይሻለኛል ብዬ የህብረተሰብ ሳይንስየማጥናት ሀሳቤን የቀየርኩት 12ኛ ክፍል ከደረስኩ በኋላነው እንጂ እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ ኢኮኖሚክስ እማራለሁብዬ አስብ ነበር፡፡ በምህንድስና ቢ.ኤስ.ሲ. እና የመጀመሪያውን ኤም.ኤስ.ሲ. የሰራሁት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ነው፡፡ ሁለተኛውን ኤም.ኤስ.ሲ. እና ዶክትሬት ዲግሪ የሰራሁት ደግሞ በጃፓን አገር ቶክዮ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ ነው፡፡ለትምህርት ከፍተኛ ትኩረት እሰጥ ስለነበር ጥናቴን በፕሮግራም አጠና ነበር፡፡ ስለዚህ ከ1ኛ ክፍል ጀምሮ የማዕረግ ተማሪ ነበርኩ ማለት እችላለሁ፡፡ የከፍተኛ ትምህርት በተከታተልኩበት ወቅትም እንደዚሁ በማዕረግ ነበር የተመረቅኩት፡፡ለዚህ ውጤት ምክንያቱ ደግሞ የተለየ ችሎታ ሳይሆን በ<strong>ሥነምግባር</strong> በመታነጽ ጠንክሮ ከመስራት ጋር የተያያዘ ነው፡፡<strong>ሥነምግባር</strong>፡- ትምህርት እንዳጠናቀቁ በምን ሥራተሰማርተው ነበር? አሁን የተሰማሩበት የሥራ ዘርፍ ምንእንደሆነ ቢገልጹልን?17<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ም


ዶ/ር መሰለ፡- ትምህርት እንደጨረስኩኝ አዲስ አበባዩኒቨርሲቲ በመምህርነት ማገልገል ጀመርኩ፡፡ በትርፍጊዜዬ ደግሞ የግንባታ ዲዛይን ሥራ እሰራ ነበር፡፡ በመቀጠል ከጃፓን ትምህርቴን አጠናቅቄ ከተመለስኩ ጀምሮ እስከ አሁን አዲስ አበባ የዩኒቨርሲቲ የማስተማር ስራዬን በመቀጠል በሌላ በኩል ደግሞ በማማከር ሥራ እናበሪል ስቴት ዴቨሎፕመንት ስራ ላይ በማገልገል ላይእገኛለሁ፡፡ ዋናው ሥራዬ ዩኒቨርሲቲ ማስተማር ሲሆንከዛ ውጪ ግን ኤም.ኤች. ኢንጂነሪንግ የሚባል የአማካሪድርጅት እና ካንትሪ ክለብ የሚባል ድርጅት ሥራ በመሥራት ላይ እገኛለሁ፡፡ የኤም.ኤች. ኢንጂነሪንግ ባለቤትእና ሥራ አስኪያጅ ነኝ፡፡ ድርጅቱ አርክቴክቶችንና ኢንጂነሮችን ጨምሮ ወደ 300 የሚደርሱ ሠራተኞች ያሉትሲሆን አንደኛ ደረጃ አማካሪ ድርጅት ነው፡፡ ከአንድ ሌላግለሰብ ጋር በጋራ ባቋቋምነው ካንትሪ ክለብ በሚባለውሪል ስቴትም በሥራ አስኪያጅነት እየሰራሁ እገኛለሁ፡፡<strong>ሥነምግባር</strong>፡- በድርጅትዎ ውስጥ የሙስና ድርጊቶችእንዳይፈጸሙ እና የሚሰጡት አገልግሎት <strong>ሥነምግባር</strong>ንየተከተለ እንዲሆን ምን ጥረት ይደረጋል?ከተከተለ ከሥራ እስከ ማባረር የሚደርስ አፋጣኝ ርምጃ እንወስዳለን፡፡ በርካሽ የመግዛት፣ መጥፎ እቃ የመግዛት፣ ጥራቱንያልጠበቀ ስራ የመስራት ነገር ሲኖር እርምጃ እንወስዳለን፡፡<strong>ሥነምግባር</strong>፡- ከናንተ ልምድ በመነሳት ሙስናን ለመዋጋት የኃይማኖት ተቋማትን ሚና እንዴት ያዩታል?ዶ/ር መሰለ፡- ከዚህ ጋር ተያይዞ እኛ ሙስናን በመዋጋት በአንድ ድርጅት ብቻ ሳይሆን በዛ ቤተክርስቲያንአባላት የሆኑ ሰዎች ሁሉ ሙስና ውስጥ መግባትየለባቸውም በሚል የ<strong>ሥነምግባር</strong> ቻርተር አዘጋጅተንየ<strong>ሥነምግባር</strong> ደንቡን ሁሉም የቤተክርስቲያን አባል እንዲፈርም አድርገናል፡፡ በአጠቃላይ በተለያዩ የኃይማኖትተቋማት ውስጥ ወይም የእምነት ቦታዎች ሁሉም ሰውየ<strong>ሥነምግባር</strong> ደንቦች በማውጣት እንዲሳተፍና እንዲፈርምቢደረግ ሙስናን በመዋጋት በኩል ትልቅ አስተዋጽኦይኖረዋል የሚል እምነት አለኝ፡፡ እያንዳንዱ ሰው ሲፈርም በሚኖረኝ ወይም በምሰራበት ድርጅት ያለ ምንምሙስና ሥራዬን አካሂዳለሁ ብሎ ይፈርማል ማለት ነው፡፡አስገዳጅ ሳይሆን የሞራል ግዴታን የሚጥል ይሆናል፡፡<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምዶ/ር መሰለ፡- በድርጅቶቻችን ውስጥ ጠንካራ የሆነእና በተግባርም እያረጋገጥነው ያለ መመሪያ አለን፡፡ ይህምሥራችን ሙሉ በሙሉ ከሙስና እንዲፀዳ በሚል ‘‘zerotolerance to corruption’’ የሚል መርህ ያለው ነው፡፡ መመሪያው መሠረቱ በቤተክርስቲያን ደረጃ ያወጣነው ምንምአይነት ጉቦ አለመክፈል ወይም አለመቀበል የሚል ነው፡፡ እኔ በምሳተፍበት ቤተክርስቲያን የ<strong>ሥነምግባር</strong> ቻርተርብለን የፈረምነው መመሪያ ማለት ነው፡፡ ሁሉም የቤተክርስቲያኗ አባል በተሰማራበት የሥራ ዘርፍ ሁሉ ከሙስናበፀዳ ሁኔታ ሥራውን እንደሚያከናውን ቃል መግባቱንበፊርማ አረጋግጧል፡፡ ይህንን መመሪያ ከቤተክርስቲያንበመውሰድ በነዚህ በሁለት ድርጅቶች ውስጥ ተግባራዊበማድረግ ላይ እንገኛለን፡፡ ይህ የ<strong>ሥነምግባር</strong> መመሪያ በድርጅቶቹ ራዕይና ዓላማ ውስጥም ተካትቶ ይገኛል፡፡ በድርጅታችን ውስጥ ከሙስና ጋር ተያይዞ የተፈጸመ ድርጊት ከተገኘ ወዲያውኑ በፈጸመው ሰራተኛ ላይ እርምጃ ይወሰዳል፡፡የድርጅታችን ደንበኛ ግለሰብም ይሁን መንግሥት ክፍያን ለፈጸመበት ተገቢውን አገልግሎት ማግኘቱን ማረጋገጥየመጀመሪያው ሙስናን የምንዋጋበት መንገድ ነው ብለን እናምናለን፡፡ አቅማችንና ችሎታችን እስከፈቀደ ተገቢውን አገልግሎት ለመስጠት እንሰራለን፡፡ ሁለተኛው ደግሞከሙስና የጸዳ አሠራር እንዲኖር የግልጽነትን መርህ ተግባራዊ እናደርጋለን፡፡ የግንባታ ዘርፍ ለሙስና በጣም የተጋለጠ መስክ በመሆኑ ይህንን ለመከላከል ከፍተኛ ጥረትእናደርጋለን፡፡ በግንባታ ዘርፍ በተለይ አማካሪ ድርጅትሙስናን በማስፋፋትም ሆነ ሙስናን በመዋጋት ጉልህሚና ሊጫወት የሚችል በመሆኑ ትኩረት ሰጥተን ሥራችንን እናከናውናለን፡፡ በመሆኑም ይህንን ስራ በቅንነት/Integrity/እና በከፍተኛ የሥራ አፈጻጸም/Excellence/ መስራትበሚል መርህ ሙስናን የምንዋጋበት አሠራር ዘርግተናል፡፡በተጨማሪም በኤም.ኤች. ኢንጂነሪንግ የአማካሪ ድርጅትባለፈው አመት ብቻ ቫት ሳይጨምር ወደ አምስት ሚሊየንብር የገቢ ግብር ከፍለናል፡፡ ካንትሪ ክለብ በሚባለው ድርጅታችን በኩልም በጉምሩክና በቫት፣ በሊዝ ክፍያ በመሳሰሉት 150 ሚሊየን ብር በላይ ለመንግሥት ገቢ አድርገናል፡፡ማንም በድርጅቴ ውስጥ ያለ ሰው የስርቆትን መንገድ<strong>ሥነምግባር</strong>፡- አሁን እየሠሩት ባለው ሥራ <strong>ሥነምግባር</strong>ንበተከተለ እና ከሙስና በፀዳ ሁኔታ እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙ ገልጸውልናል፡፡ ድርጅትዎ ምን ያህል ትርፋማ ነው?አሁን ለደረሱበት ስኬት ምክንያት ምንድነው ብለው ያስባሉ?ዶ/ር መሰለ፡- ለምሳሌ ኤም.ኤች. ኢንጂነሪንግ የተቋቋመው የዛሬ አስር አመት ነው፡፡ ይህ ድርጅት ትልቁ አማካሪ ድርጅት ነው ብለን እናስባለን፡፡ የድርጅቱ ዕድገት በፐርሰንት ሳይሆን በመቶ እጥፍ ነው ያደገው፡፡ ለምሳሌ ሥራውን ስንጀምር የድርጅቱ ሰራተኞች ሶስት ነበርን፡፡ አሁንከሶስት መቶ በላይ ሰራተኞች አሉን፡፡ የወር ደሞዝ ወጪሲጀመር ከነበረው 3000 ብር ተነስቶ በአሁን ጊዜ ወደ 1.44ሚሊየን ብር አድጓል፡፡ ድርጅቱ ሥራውን ሲጀመር ከነበረው 230000 ብር አመታዊ አጠቃላይ ገቢ ተነስቶ በአሁኑወቅት ከ30 እስከ 40 ሚሊየን ብር የሚጠጋ አመታዊ ገቢላይ ደርሷል፡፡ ይህም ከሙስና በፀዳ እና የቅንነትን መርህተከትሎ በመሥራት ውጤታማ መሆን የሚቻል እንደሆነ በተጨባጭ የሚያሳይ ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ ካንትሪ ክለብ ሪል ስቴት የሚባለው ድርጅት በመኖሪያ ቤቶች ግንባታላይ የተሰማራ ሲሆን በአሁኑ ወቅት በሀገሪቷ ውስጥ ከሚገኙት ትልልቅ ሪል ስቴቶች አንዱ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት2 ቢሊዮን ብር በሚጠጋ ገንዘብ 500 ቤቶችን እየሰራን እንገኛለን፡፡ በዚህ ድርጅትም ያለምንም ሙስና ሰርቶ ካሰቡትግብ መድረስ እንደሚቻል በተግባር አይተናል፡፡ በተጨማሪአሁን ለደረስኩበት ስኬት ምክንያቱ ጠንክሮ መስራት ነው፡፡<strong>ሥነምግባር</strong>፡- አንዳንድ ሰዎች በሙስና ወይም በአቋራጭ ካልሆነ በስተቀር ውጤታማ መሆን ወይም ገንዘብማግኘት አይቻልም ብለው ያስባሉ፡፡ ይህንን በተመለከተየእርስዎ አስተያየት ምንድነው?ዶ/ር መሰለ፡- እኔ ይሄንን እንደ አእምሮ በሽታ ነውየማየው፡፡ አንድ ሰው ሰርቶ መኖር ሲችል ሰርቄ እኖራለሁሰርቄ ደግሞ እንጀራ እበላለሁ፣ መርቸዲስ እገዛለሁ፣ ትልቅ ፎቅ እሰራለሁ ሲል መቼም ይሄ የአእምሮ በሽታ ነውብዬ ነው የምወስደው፡፡ ከጤነኛ ሰው አእምሮ ሊሆን የሚችል ነው ብዬ አላስብም፡፡ ለዚህ ደግሞ ሙስናን የመዋጋትአስተሳሰባችን እና ባህላችን በዝቅተኛ ደረጃ ላይ በመገኘቱ18


እንዲሁም ለሙስና ምቹ የሆኑ አንዳንድ አሰራሮች መኖራቸው ይመስለኛል፡፡ ስለዚህ ይሄ ሠርቶ ማደግ አይቻልምየሚባለው እውነትነት የሌለው ነው፡፡ እኔ በብዛት እንዳስተዋልኩት በግንባታው ዘርፍ በሙስና የተሰማሩ ኮንትራክተር፣ ኮንሰልታንት ወይም በመንግሥት በኩል አሰሪ የሆኑት ለጊዜው የተጠቀሙ መስለው ይታዩ እንጂ ወደ ኪሳራናውድቀት ያመራሉ፡፡ ምክንያቱም ስርቆቱ ላይ ስለሚተማመኑ ስራቸውን በአግባቡ አይከታተሉም፡፡ በመሆኑም የሰረቁትን ያህል እነሱም ስለሚሰረቁ ሥራቸውም እየወደቀ ይሄዳል፡፡ ስለዚህ ይሄንን ያህል አትራፊ ናቸው ብዬ አላስብም፡፡ሰርቶ ግን በልፋት ላይ ከተመሰረተ ጥሩ ትርፍም ማግኘትይቻላል እድገቱም ቀጣይነት ይኖረዋል፡፡ ጠንክሮ በመስራት እና የመንግስትን ታክስ በመክፈል ትርፍ ማግኘት ይቻላል፡፡ የእኛ ድርጅቶች በትርፋማነት፣ ለሀገር በማገልገል፣በእድገትም ጥሩ ደረጃ ላይ የሚገኙ በመሆናቸው ያለሙስና መስራት እንደሚቻል ምሳሌ ይሆናሉ ብዬ አስባለሁ፡፡<strong>ሥነምግባር</strong>፡- ከእርስዎ የሕይወት ተሞክሮ ለሌሎችይጠቅማል ብለው የሚያስቡት ምክር ምንድነው? <strong>ሥነምግባር</strong>ን በተከተለ ሁኔታ ሥራዎትን በሚያከናውኑበት ጊዜየገጠመዎት ችግር አለ ወይ? ችግሩንስ እንዴት ፈቱት?ዶ/ር መሰለ፡ የስራው ፀባይ ከትልልቅ ባለሥልጣናት፣ከሚኒስትሮች፣ ከምክትል ሚኒስትር ጋር ያገናኘናል፡፡በዚህ ደረጃ ካሉ ባለሥልጣናት ከሙስና አንፃር የሚያስብወይም ያንን ሀሳብ የሚሰጥ ሰው አላጋጠመኝም፡፡ በእኔበኩል ሥለ ሥራው መሰራት እንጂ ስለሙስና ሲያነሱአልሰማሁም፡፡ በታችኛው የሥልጣን እርከን ላይ ያሉ አንዳንድ ሰዎች ግን ሙስና ለመፈጸም ሙከራዎችን ሲያደርጉአያለሁ፤ ፊትለፊት አውጥቶ ገንዘብ ስጡን ብሎ የሚጠይቀን ባያጋጥመንም፡፡ “አንዳንድ ነገር ብትሉን እኛኮ እንረዳችሁ ነበር” የሚል ነገር አለ፡፡ ሁሌ ደግሞ “የእናንተ ድርጅትእኮ ምንም አይረዳንም ምንም አያደርግልንም” የሚልወቀሳ ይገጥመናል፡፡ እንደዚህ በሚሆን ጊዜ በተቻለ መጠንሰዎቹን ለመምከር እሞክራለሁ ፡፡ በጣም ግን አስቸጋሪ ከሆነያንን ሥራ እተወዋለሁ፡፡ ወደ ላይ ሄጄ ለመክሰስ ማስረጃስለሌለው ሙስና አለበት በምለው አካባቢ ጨረታም አልገባም፣ ወደ ስራም አልገባም፣ እዛ ቢሮም ሁለተኛ ተመልሼ አልሄድም፡፡ እኔ ለይቼ የምሰራው ከሙስና የፀዱ ናቸው ብዬ ካመንኩባቸው ጋር ብቻ ነው፡፡ ማስረጃም ባይኖረኝየሙስና አዝማሚያ ካስተዋልኩ ጨረታም አልወዳደርምመስራትም አቆማለሁ በዚህ አይነት ድርጊቱን አስወግዳለሁ፡፡<strong>ሥነምግባር</strong>፡- በተለያዩ ዘርፎች አንዳንድ ሙያተኞችለሙያ ሥነምግባራቸው ተገዢ የማይሆኑበት ሁኔታያጋጥማል፡፡ በግንባታው ዘርፍ ስለሚፈጸመው ሙስናአስመልክቶ የእርስዎ አስተያየት ምን ይመስላል?ዶ/ር መሰለ፡- በግንባታ ዘርፍ ሙስና መኖሩ የሚደበቅነገር አይደለም፡፡ ለዚህም ዋናው ምክንያት በአጭርጊዜ ሳይሰሩ ገንዘብ የማግኘት ፍላጎት ነው፡፡ ኮንስትራክሽንሴክተር ብዙ ገንዘብ የሚንቀሳቀስበት ዘርፍ በመሆኑ በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ የሚንቀሳቀስበት ሥራ ጨረታይወጣል፡፡ አንዱ ፕሮጀክት ብቻ በሚሊዮን ወይም በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ስለሚያንቀሳቅስ ለሙስና በጣምየተጋለጠ ነው፡፡ ብዙ ጊዜ በመንግሥት አካባቢ ጨረታን በተመለከተ ፕሮሲጀሩ ልክ መሆኑን ነው የሚከታተሉት፡፡ ለምሳሌ የግዢ መመሪያው አርባ አምስት ቀን አየርላይ ቆይቷል ወይ? የመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ትኩረትይደረጋል፡፡ ይኼ ብቻ ሙስናን አያስቀርም፡፡ መንግስትመስሪያ ቤት ሰባ ወይም ሰማንያ ፐርሰንት ለቴክኒካልግምገማ /technical evaluation/ እና ሀያ ወይም ሰላሳፐርሰንት ለፋይናንሽያል ግምገማ/financial evaluation/ብሎ ያወጣል፡፡ ያንን ቴክኒካል የሚያርመው ሰው ሲጀመር ማሳለፍ ለፈለገው ቴክኒካል ግምገማ ላይ ከፍተኛ ነጥብ ይሰጠውና ሌላውን ደግሞ አነስተኛ ነጥብ ቢሰጠው ሰብጀክቲቭ የሆነ ነገር አለ፡፡ መንግሥት ይህ ሕገወጥ ድርጊት መፈጸሙን ሊያውቀው አይችልም፡፡ በመሆኑም ገና ሥራውን በመገምገም ደረጃ ላይ ሙስናው ሊጀመር ይችላልማለት ነው፡፡ ሌላው ደግሞ መጥቀም ለፈለገው ተጫራች የሚመቸውን መመዘኛ በማውጣት ሊፈፀም ይችላል፡፡በመሆኑም አማካሪውን ድርጅት ወይም ኮንትራክተርንበመምረጥ ሥራውን የሚሰጠው የመንግሥት አካል በተለይደግሞ ገምጋሚው ቡድን ይሄንን ክፍተት በመጠቀምሙስና የሚፈጽሙበት ሁኔታ እንዳለ ይሰማኛል፡፡ በግንባታው ዘርፍ የሚፈጸመው ሙስና የሚጀምረው እዛጋነው፡፡ ቀጥሎ ደግሞ በሙስና አማካሪው ጨረታውን አሸንፎ ያንን ስራ ከወሰደ በኋላ ለኮንትራክተሩ ሥራ ሲሰጥሌላ ሙስና የሚፈጸምበት ሁኔታ ሊኖር ይችላል፡፡ ሥራውውስጥ በዝቅተኛም ገንዘብ ተወዳድሮ ሊገባ ይችላል፡፡ በዝቅተኛ ገንዘብ ገብቶ ከኮንትራክተሩ ያልተገባ ጥቅም ሊያገኝይችላል፡፡ ሌላው ሥራ ሲሰጥ በአማካሪውና በኮንትራክተሩመካከል እረዳሀለሁ አልረዳህም በሚል መደራደር ለሙስና በር የሚከፍትበት ሁኔታ አለ፡፡ ስለዚህ ሥራው ከመጀመሩ በፊት አማካሪው ስራውን በማግኘት፣ በመቀጠልምደግሞ አማካሪው ሥራውን ለኮንትራክተሩ በመስጠት(ጨረታውን የሚያካሂደውን የመንግሥት አካልን ጨምሮምሆነ ሳይጨምርም) ሙስና ሊካሄድ ይችላል፡፡ በእኔ ግምትእነዚህ አካባቢዎች ሙስና ይፈጸማል የሚል እምነት አለኝ፡፡ከዚህ ቀጥሎ ሶስተኛው ደረጃ ደግሞ ሥራው ሲሰራ የሚፈጸመው ነው፡፡ አማካሪው የኮንትራክተሩን ሥራ ሊቀበለውም ላይቀበለው ብዙ መብት ስላለው ሙስና መስራትከፈለገ የማያስኬድ መመዘኛ እያመጣ በማስቸገር(ወይምኮንትራክተሩም ድክመት ሊኖረው ይችላል) ሊሰርቅወይም በመተባበር ሊሰርቁ ይችላሉ፡፡ ሌላው ደግሞለምሳሌ የሚሰራው ትልቅ መንገድ ነው እንበልና፤ አንድመሰረት ላይ የ300‚000 ብር አፈር ቁፋሮ ቢኖር የ400‚000ብር ቢያደርገው ሊደረስበት ስለማይቻል 100‚000ብሩ በሕገወጥ መንገድ ሊወሰድ ይችላል፡፡ ስለዚህ የግንባታው ዘርፍ ከሙስና የፀዳ እንዲሆን እነዚህን አሰራሮች አይቶ ክፍተቶችን መዝጋት ይጠይቃል፡፡ የመንግሥት መስሪያቤቶች ፕሮሲጀሩን ተከትሎ የጨረታ ጊዜአየር ላይ የቆየበት ጊዜ የሚሉት ላይ ያተኩራሉ ነገርግን ሙስና የሚፈጸመው ከስራ መስጠት ጀምሮአማካሪ ሲመረጥ፣ አማካሪው ወይም አስፈጻሚው አካልኮንትራክተር ሲመርጥ በኋላ ደግሞ ስራው ሲለካና የስራውን ጥራት በመከታተል ላይ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል፡፡ሙስና ስለመፈጸሙም በግልጽ የሚታይበት ሁኔታምይኖራል፡፡ ለምሳሌ አንድ ሥራ ሲሰራ በጣም በዝቅተኛዋጋ ነው የተሰራው ቫሪየሽኑም ደግሞ ከአንድ ፐርሰንትበታች ነው እንበል፡፡ በሌሎች ፕሮጀክቶች ተመሳሳይሥራ በምን ያህል ዋጋ ነው የሚሰራው? ምን ያህል ቫሪየሽን አለ? ብሎ በቀላሉ ማግኘት ይቻላል፡፡ ብዙ ተመሳሳይ የሆኑ ህንፃዎችን ማወዳደር ይቻላል፡፡ ስለዚህ ይህንንበትኩረት መከታተል ያስፈልጋል፡፡ እንደ እኔ አስተሳሰብበግንባታው ዘርፍ ያለውን ሙስና ማስቆም ካልተቻለከሙስና በፀዳ ሁኔታ መስራት የሚፈልገው ከሥራ ውጪ19<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ም


ይሆናል፡፡ በሙስና የሚጠቀመው ብቻ ሥራ እያገኘየሚቀጥልበት ሁኔታ ከተፈጠረ ደግሞ በመጨረሻሀገሪቱ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል፡፡ በመሆኑምትልቅ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባው በግንባታው ዘርፍ የሚታየውን ሙስና ለመከላከል ተገቢውን ትኩረትመስጠት ይኖርብናል፡፡ሙስና ካለ ህዝብም ሆነ መንግስት የሚጎዳው አግባብያልሆነ ከፍተኛ ወጪ በማውጣት ብቻ ሳይሆን ጥራት ያለውን ሥራ ባለማግኘትም ጭምር ነው፡፡ አንድአማካሪ ካንድ ኮንትራክተር ጋር በሙስና ከተጣመረበአግባቡ ሥራውን አይቆጣጠረውም፡፡ በመሆኑምሊታረሙ የሚገባቸውን ችግሮች እንዲታረሙ ከማድረግ ይልቅ ስህተቱን ይሸፍንለታል፡፡<strong>ሥነምግባር</strong>፡- በህብረተሰቡ ውስጥ የ<strong>ሥነምግባር</strong>ለማጠናከርና ሙስናን ለመቀነስ ምን ጥረት መደረግአለበት ብለው ያስባሉ?<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምዶ/ር መሰለ፡ ሙስናን መዋጋት የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት ነው ብዬ አስባለሁ፡፡ ሙስና ውስጥ አለመግባት የሚበረታታ ቢሆንም ሙስናንም መዋጋት ደግሞሌላው ነገር ነው፡፡ ብዙዎቻችን የምናስበው ራሳችን ሙስና ውስጥ ካልገባን ሌላው እንደፈለገ ያድርግብለን ነው የምንቀመጠው፡፡ ለዚህ አንደኛው ምክንያትበቂ ማስረጃ ስለማይገኝ ሊሆን ይችላል፡፡ ሁለተኛከሰው ጋር ምን አጣላኝ ይሄ ሙስና የት ድረስ ነውየሚሄደው ብለን በመስጋትም ሊሆን ይችላል፡፡ እኔ ራሴንየምወቅሰው በዚህ ነው፡፡ በምንም ዓይነት በግሌም ሆነ በድርጅቴ ሙስና እንዳይኖር እጥራለሁ፡፡ ሆኖም ሙስና በሌላ በኩል ለመዋጋትም ብዙ ጥረት አላደርግም፡፡ ሁላችንምግን ተባብረን ወደ መዋጋት አብረን ብናመራ ሙስናን በቀላሉ ማጥፋትና ከሙስና የፀዳ ሥራ ለመስራት የሚያስችል ደረጃ ላይ ለመድረስ ይቻላል ብዬ አስባለሁ፡፡ ነገር ግንየሰው የራሱ የ<strong>ሥነምግባር</strong> እሴት እና የእምነት እሴት ካልተጨመረበት በቁጥጥር ብቻ አስፈላጊው ደረጃ ላይ ይደረሳል ብዬ አላስብም፡፡ ለእኔ ለምሳሌ ሙስና ውስጥ አለመግባት የእምነትና የሕይወትም ጉዳይ ነው፡፡ ምክንያቱም ሰውባይጠይቀኝ እግዚአብሔር ይጠይቀኛል ብዬ ስለማምን በምንም መንገድ አላስበውም፡፡ ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት ስለዚህመልካም <strong>ሥነምግባር</strong>ን ሁሉም ከየእምነቱ ጋር ቢያያይዘውከሕጉም በላይ ትልቅ ለውጥ ያመጣል የሚል ሀሳብ አለኝ፡፡ሌላው ወጣቱ ላይ መስራት ነው፡፡ በአሁኑ ወቅትከአንደኛ ደረጃ አንስቶ የሚሰጥ የሲቪክስ ትምህርትአለ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የሞራል ትምህርት ቢጨመርእና የ<strong>ሥነምግባር</strong> ትምህርቱ ተጠናክሮ በሰፊው ቢሰጥመልካም ነው እላለሁ፡፡ ከትምህርቱ ጎን ለጎንም የፍትህሥርዓቱ በሚገባ መጠናከርና አጥፊዎች ከተጠያቂነትየሚያመልጡበትን ቀዳዳ እጅጉን የጠበበ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ስለዚህ በአጭሩ ለማጠቃለል በትምህርት ቤትለወጣቶች እና ለልጆች፤ ለአዋቂዎች ደግሞ በእምነትቦታዎች በማስተማር እንዲሁም የፍትህ ሥርዓቱን በማጠናከርና አጥፊዎች ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ በማድረግሙስናን መከላከል ይቻላል፡፡ ለዚህ ሁሉ ስኬት ግን በተጠቀሱት ዘርፎች ጠንክሮ መስራት በጣም አስፈላጊ ነው፡፡<strong>ሥነምግባር</strong>፡- የቤተሰብዎ ሁኔታ ምን ይመስላል? ትዳር መስርተዋል? ስንት ልጆችን አፍርተዋል ? ልጆችዎመልካም <strong>ሥነምግባር</strong>፣ ትጋትና ሥራ አክባሪ እንዲሆኑያደረጉት ጥረት ምን ይመስላል? ያገኙትስ ውጤት?ዶ/ር መሰለ፡- ትዳር መስርቻለሁ፡፡ ሶስት ወንዶች ልጆች አሉኝ፡፡ አሁን ደግሞ 12 ዓመት የሆናት አንድ ሴትልጅ በቅርቡ የቤተሰባችን አባል ሆናለች፡፡ ሶስቱ ወንዶችልጆቼ ወደ ኮሌጅ የደረሱ እና 12ኛ ክፍል አሁን የጨረሱናቸው፡፡ ሴቷ ገና 3ኛ ክፍል ነች፡፡ እኔ ለማድረግየሞከርኩት የልጆቼ የራሳቸው ምርጫ የተጠበቀ ሆኖበመሠረታዊ ጉዳዮች ላይ በመወያየት ከስምምነት የምንደርስበት መንፈስ በቤተሰቤ ውስጥ ማስረጽ ችያለሁ፡፡ ለምሳሌ ጠንክሮ ስለመስራት፣ ከሙስና ስለመራቅ፣ እንዲሁም የሀገር ፍቅር የተመለከቱ እሴቶችን እንዲያዳብሩ ሁልጊዜ እንነጋገራለን፡፡ በተለይ ስለነዚህ ጉዳዮች ከልብየምንወያይበት እሁድ ማታ የቤተሰብ ጊዜ አለን፡፡ ጊዜያችንን እንዴት እንዳሳለፍን እንወያያለን፤ በፀሎት ነውየምንዘጋው፡፡ ዞሮ ዞሮ በትክክል እና በእውነት እንዲሰሩ በመነጋገር ሁል ጊዜ ደግሞ የእኔን ጥሩ ህይወትአይተው ከእኔም ጥሩ ነገር እንዲወስዱ በተሻለ ራሳቸውም ጨምረውበት ጥሩ ህይወት እንዲመሩ ነው የምመክራቸው፡፡ እስከ አሁን ድረስ የከፋ የስነምግባር ችግርልጆቼ ላይ አይቼ አላውቅም፡፡ በሙያ ረገድ ሦስቱምወንዶች እስከ አሁን የእኔን ሙያ መስክ ነው የተከተሉት፡፡20


አተርፍ ባይ አጉዳይ!በህዝብ እና በመንግስት የተሰጠን ኃላፊነት በአግባቡከመወጣትና በሀቀኝነት ከመስራት ይልቅ ከስግብግብነትእና ከልክ ባለፈ ራስ ወዳድነት በመነጨ አስተሳሰብ የሃገርሃብትን መመዝበርና ለራስ ጥቅም ማዋል ከአንድ ዜጋየሚጠበቅ ተግባር አለመሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ሆኖም አንዳንድ ግለሰቦች ይህንን ሀቅ ወደጎን በመተው የተሰጣቸውን ኃላፊነት አላግባብ በመጠቀምከባድ የሙስና ወንጀል ሲፈጽሙ ይስተዋላል፡፡የፌደራል የ<strong>ሥነምግባር</strong>ና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የተቋቋመበትን ዓላማና በአዋጅ የተሰጠውን ስልጣን መሰረትበማድረግ ይህንን ዓይነት ለሃገር ልማት ብሎምለመልካም አስተዳደር እንቅፋት የሆነ የሙስና ወንጀል ለመታገል ዘርፈ ብዙ ጥረቶችን እያደረገ ይገኛል፡፡ባሳለፍነው ወርሃ ግንቦት የኮሚሽኑ አቃቤ ህግ ላለፉትሁለት አመታት በፍርድ ቤት ሲከራከርበት በቆየው ከባድየአታላይነት እና በመንግስት የተሰጠን ኃላፊነት ለግልብልጽግና የማዋል ተደራራቢ ወንጀል ላይ የፌዴራልከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ ወንጀል ችሎት አንድ ውሳኔአስተላልፏል፡፡ በዚህ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የመንግስት ገንዘብ በመመዝበር ከባድ የሙስና ወንጀል በመፈጸምበተከሰሱ ሶስት ግለሰቦች ላይ ፍርድ ቤቱ የቅጣትውሳኔ አስተላልፏል፡፡ ፍርድ ቤቱ ግለሰቦቹ ከ 5-21አመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እና ከ 5,000-20,000በሚደርስ ብር እንዲቀጡ ወስኗል፡፡በወንጀሉ አንደኛ ተከሳሽ የሆነው የ39 ዓመቱ ጎልማሳ ጎሹ አንዱአለም ነው፡፡ ግለሰቡ በ ህዳር ወር 1997ዓ.ም. በ 760 ብር የወር ደሞዝ በእቃ ግዥ ሰራተኝነት ከሚሰራበት የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድቤት ወደ ፌዴራል ፍርድ ቤቶች የፍርድ አፈጻጸም መምሪያ በሂሳብ ሰራተኝነት እንዲዛወር ደብዳቤ ይደርሰዋል፡፡ይህ ከሆነ ብዙም ሳይቆይ ነበር ግለሰቡ የተሰጠውንኃላፊነት በአግባቡ ከመወጣትና በሀቀኝነት ከማገልገልይልቅ ያላግባብ ለመበልጸግ በመመኘት ለወንጀል የተነሳሳው፡፡ የግለሰቡን ለሙስና ወንጀል በከፍተኛ ሁኔታ የተነሳሳ አእምሮ ያልተገነዘበው መስሪያ ቤት በቅንነት በፍቃድ ምክንያት ያልነበሩትን የሂሳብ ክፍል ሃላፊን ወክሎእንዲሰራ ተጨማሪ ኃላፊነትን በ16/12/97 ይሰጠዋል፡፡ታዲያ ባልለፋበት ገንዘብ ለመበልጸግ የተነሳሳ አእምሮየያዘው ግለሰብ ይህን ቦታ ሲያገኝ የወንጀል ጥሙንለማርካት ጊዜ አልወሰደበትም፡፡የመጀመሪያ የሙስና ወንጀሉ ዒላማ ያደረገውም በፍርድ ቤት በፍርድ ባለመብትናበፍርድ ባለዕዳ በሆኑ ሁለት ወገኖች መካካል የተፈጸመንክፍያ ነበር፡፡ ጉዳዩ እንዲህ ነው ጎሹ አንዱአለም የሚሰራበት የፍርድ አፈጻጸም መምሪያ በፍርድ ቤት ትእዛዝመሰረት የባለዕዳ ንብረት በሃራጅ እንደተሸጠ ለመምሪያውበተከፈተ የባንክ አካውንት በገንዘብ ያዡ በኩል እንዲገባይደረጋል፡፡ የፍርድ ባለመብቱም ገንዘቡ እንዲከፈላቸውባመለከቱት መሰረት በህጋዊ መንገድ ሁሉንምአከናውነው የተዘጋጀላቸውን የባንክ ቼክ ይወስዳሉ፡፡ይህ በእንዲህ እንዳለ ግለሰቡ ወንጀሉን ለመፈጸም አቅዶ በርሄ ገብረሚካኤል በሚል ሀሰተኛ ስም ባዘጋጀውየመታወቂያ ደብተር ከዳሸን ባንክ ባወጣው የሂሳብ ቁጥርብር 268,601.14 (ሁለት መቶ ስልሳ ስምንት ሺህ ስድስትመቶ አንድ ብር ከአስራ አራት ሳንቲም) ከፍርድአፈጻጸም መምሪያው ሂሳብ ላይ እንዲከፈል በተጭበረበረመንገድ ደብዳቤና ቼክ ያዘጋጃል፡፡በመቀጠልም የመምሪያውን ሃላፊ በማሳሳት በቼኩ ላይ አንዲፈርሙበት በማድረግ ይህንኑ ሀሰተኛ ሰነድ ለብሄራዊ ባንክ ካቀረበ በኋላቀደም ሲል ለወንጀሉ ማስፈጸሚያ ይሆን ዘንድ ባዘጋጀውሀሰተኛ ስም በመፈረም ቼኩን ዳሸን ባንክ ልደታ ቅርንጫፍ በመውሰድ በሃሰተኛ ስም ባወጣው የሂሳብ ቁጥርበ01/13/97 ገቢ ያደርጋል፡፡ ባንክ ካስቀመጠው ገንዘብላይም ብር 250,000 (ሁለት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር)በ05/13/97 ወጪ በማድረግ ለግል ጥቅሙ ያውለዋል፡፡የስግብግብነትና ያላግባብ የመበልጸግ አመለካከት የተጠናወተው ጎሹ አንዱአለም በዚህ በቃኝ አላለም፡፡ በመሆኑም የመጀመሪያውን ወንጀል በፈጸመ አንድ ወር ባልሞላጊዜ ውስጥ ዳግም ለሌላ ወንጀል ተነሳሳ፡፡ ሁኔታው እንዲህ ነበር በፍርድ ባለመብት በሆኑ በአንድ ግለሰብና የፍርድ ባለዕዳ በሆነ አንድ ድርጅት መካከል በነበረው የፍርድ አፈጻጸም ክርክር ጉዳይ መነሻነት ለፍርድ ባለመብትብር 756,666.66 (ሰባት መቶ ሃምሳ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ ስልሳ ስድስት ብር ከስልሳ ስድስት ሳንቲም)እንዲከፈላቸው በፍርድ ቤት በተወሰነው መሰረት ለፍርድባለመብቱ በፍርድ አፈጻጸም መምሪያው በተዘጋጁት ሶስት ቼኮች መሰረት ከላይ የተጠቀሰውገንዘብ በብሄራዊ ባንክ አማካኝነት ይከፈላቸዋል፡፡ጎሹ አንዱአለም ይህ ክፍያ የተፈጸመበት መዝገብ ደብዛው እንዲጠፋ በማድረግ ባለመብቱ ገንዘቡን አልወሰድኩም የሚል አቤቱታ በደብዳቤ እንዳቀረቡ በማስመሰልናበ10/1/1998 ዓ.ም. የተጻፈ ደብዳቤ ለኢትዮጵያ ብሄራዊባንክ በማዘጋጀት የፍርድ አፈጻጸም መምሪያ ሃላፊውን<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ም21


<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምዳግም አሳስቶ ፊርማቸውን እንዲያስቀምጡበት በማድረግ ከላይ የተጠቀሰውን የብር መጠን የያዘ ቼክ ለፍርድባለመብት የሚከፈል በማስመሰል ያዘጋጃል፡፡ ሀሰተኛውንቼክ በመጠቀም ከፍርድ አፈጻጸም መምሪያው የሂሳብቁጥር ላይ ወጪ እንዲደረግ በማዘጋጀት በበርሄ ገብረሚካኤል ስም ለራሱ ባወጣው የባንክ ሂሳብ በፍርድ ባለመብቱ ስም ፊርማቸውን አስመስሎ በመፈረም በ12/01/98ዓ.ም ገቢ ያደርጋል፡፡ ከእዚሁ ባንክም በ20/01/98ዓ.ም. የተጠቀሰውን ገንዘብ ወጪ በማድረግ ይወስዳል፡፡ግለሰቡ በተለያየ ጊዜ የመንግስትን ሰነድ አስመስሎ በማዘጋጀት የመዘበረውን ገንዘብ ሰውሮ ለማቆየት የተለያዩንብረቶችን በመግዛት ህጋዊ ለማድረግ ሞክሯል፡፡ ለዚህም ተባባሪ ካደረጋቸው ግለሰቦች ውስጥ ከግለሰቡ ጋርበትዳር ተሳስራ የምትኖረውና የባለቤትዋን ወርሃዊ ደመወዝ አሳምራ የምታውቀው ሆኖም አመጣጡ ህጋዊ ያልሆነን ገንዘብ አሜን ብላ በደስታ የተቀበለችው አስቴር አዘዘግንባር ቀደሙን ስፍራ ትይዛለች፡፡ ወንጀለኛውበራሱ ስም ከአንድ ግለሰብ 20/7/98 ዓ.ም. የሰሌዳ ቁጥሩ 2-64901 አ.አ. የሆነውን “አቶዝ” አውቶሞቢል በብር68,500 (ስልሳ ስምንት ሺህ አምስት መቶ) ገዝቷል፡፡በተጨማሪም እ.ኤ.አ. በ20/06/05 ደግሞ ከናሽናል ሞተርስ ኮርፖሬሽን በብር 486,000 የሰሌዳ ቁጥሩ 3-33093አ.አ. የሆነ ሞዴል FSR 33 አይሱዙ የህዝብ ማመላለሻ ተሸከርካሪ በባለቤቱ በሁለተኛ ተከሳሽ ወ/ሮ አስቴርስም ገዝተው ለግል ጥቅማቸው ሲገለገሉበት ቆይተዋል፡፡ከዚህም ሌላ ዳግመኛ በወ/ሮ አስቴር ስም ጉለሌ ክፍለከተማ ውስጥ የመኖርያ ቤትም መግዛታቸውን የኮሚሽኑአቃቤ ህግ ያሰባሰበው መረጃ ይጠቁማል፡፡ ግለሰቡ ከላይየተጠቀሰውን ገንዘብ በተጭበረበረ ቼክ ወደራሱ የባንክሂሳብ ገቢ ካደረገ በኋላ ከቤተሰብ ውርስ አግኝቻለሁበሚል ሰበብ ስራውን በፈቃዱ ይለቅቃል፡፡ይህ በእንዲህ እንዳለ ነበር ጎሹ አንዱአለም ቀደም ሲልያገለግልበት ከነበረው ከፌዴራል ፍርድ ቤቶች የፍርድአፈጻጸም መምሪያ በ8/8/2000 ዓ.ም. ለፌዴራል<strong>ሥነምግባር</strong>ና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ጉዳዩን በተመለከተጥቆማ የቀረበው፡፡ ይህንን ጥቆማ በመያዝም የኮሚሽኑመርማሪዎች ምርመራ ሲያካሂዱ ቆይተው ተገቢውን መረጃ ካሰባሰቡ በኋላ ጉዳዩን ለአቃቤ ህግ አስተላልፈው የክስሂደቱ በ20/10/00 ተጀመረ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ በኮሚሽኑ አቃቤ ህግና በተከሳሹ መካከል የፍርድ ቤት ክርክርሲካሄድ ቆይቷል፡፡በ14/08/02 ዓ.ም. ግለሰቡ በፈጸመው የሙስና ወንጀል በቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ ባለቤቱና ሶስተኛ ተከሳሽበአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የፖሊስ ሰራዊት ባልደረባ የሆነው ምክትል ኢንስፔክተር አብርሃም አያሌውበሙስና የተገኘውን ንብረት ደብዛውን ለማጥፋት መረባረብ ጀመሩ፡፡ ይህንንም ለመፈጸም የተጠቀሙበት ዘዴየጎሹ አንዱአለም የአጎት ልጅ የሆነው ሶስተኛ ተከሳሽየህዝብ ማመላለሻ አውቶብሱን በሃሰተኛ የሽያጭ ውልበ350,000 (ሶስት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር) እንዲገዛማድረግ ነበር፡፡መኪናውን ገዛ የተባለው ኗሪነቱ ደብረማርቆስ የሆነው ኢንስፔክተር አብርሃም አያሌው በመንግስትመስሪያ ቤት የሚሰራ ሌላ ዘመዱን በማታለልና22የመኪናውን የሰሌዳ ቁጥር በመቀየር መኪናው በምስራቅ ጎጃም አካባቢ ሲሰራ እንዲቆይ በማድረግ ወንጀሉየበለጠ ዱካው እንዲጠፋ አድርጓል፡፡በዚህ የወንጀል ድርጊት የኮሚሽኑ አቃቤ ህግ ያቀረባቸው በ ጎሹ አንዱአለም የተዘጋጁ የተለያዩ ሀሰተኛ መረጃዎች ሲኖሩ ከእነዚህም መካከል አንደኛ ተከሳሽና የትዳር ጓደኛው በ10/02/94 ዓ.ም. ተዋድደውና በመፈቃቀድየመሰረቱት ለሁለት ወንዶችና ለአንዲት ሴት ልጅ መገኘትምክንያት የሆነውን ትዳር በሙስና የተገኘውን ንብረትደብዛ ለማጥፋት በ24/06/00 ዓ.ም ፍቺ የፈጸሙለማስመሰል የተጠቀሙበት የፍርድ ቤት የሃሰት ማስረጃ አንዱ ነው፡፡ሶስተኛ ተከሳሽ ኢንስፔክተር አብርሃም በመንግስትመስሪያ ቤት ከተቀጠረበት ከ15/2/80 እስከ 30/1/00ዓ.ም ድረስ ከወር ደመወዝ 150 ብር ተነስቶ 1450.00ብር ይከፈለው የነበረና መኪናውን ለመግዛት 350,000ብር ከየትም ሊያመጣ እንደማይችል የአቃቤ ህግ ለፍርድ ቤት ያቀረባቸው ማስረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ይኸው ግለሰብህዝብና መንግስት የጣሉበትን ኃላፊነት ከመወጣት እናለህዝብ ደህንነት በሀቀኝነት ከመቆም ይልቅ ያላግባብብልጽግና ለማግኝት በማሰብ የሙስና ወንጀሉ ተባባሪ ሆኖተገኝቷል፡፡ምንም እንኳን ይህንን ከፍተኛ የሆነ የማጭበርበር የሙስና ወንጀል ለመሸፋፈንና ነጻ ሆኖ ለመታየት ተከሳሾቹየተለያዩ ጥረቶችን ቢያደርጉም እውነት ትመነምናለችእንጂ አትጠፋም እንዲሉ በፍርድ ሂደቱ ወቅት ኮሚሽኑያቀረበባቸውን የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን መከላከልባለመቻላቸው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛወንጀል ችሎት ግንቦት 6 ቀን 2002 ዓ.ም. በዋለው ችሎትበአንደኛ ተከሳሽ ጎሹ አንዱአለም ላይ በተለያየ መዝገብ የ21 አመት ፅኑ እስራትና የብር 35,000.00 (ሰላሳአምስት ሺህ ብር) ቅጣት እንዲሁም በሁለተኛ ተከሳሽአስቴር አዘዘ ላይ የአምስት ዓመት ጽኑ እስራትና የብር5,000 (አምስት ሺህ ብር) ቅጣት እንዲሁም በሶስተኛተከሳሽ በምክትል ኢንስፔክተር አብርሃም አያሌው ላይየሰባት አመት ጽኑ እስራትና የብር 10,000 (አስርሺህ ብር) ቅጣት ውሳኔ አስተላልፏል፡፡የተሰጣቸውን ኃላፊነት በመጠቀም ያለአግባብ ለመበልጸግ በማሰብ በተፈጸመው ወንጀል የመንግስት እና የህዝብገንዘብ ከመመዝበሩም ባሻገር ሶስት የነገ ሀገር ተረካቢዜጎች በወላጆች ስግብግብነትና አልጠግብ ባይነት ምክንያት የወላጆቻቸውን ፍቅር አጥተው እንዲያድጉ እና የሰቀቀን ህይወት እንዲገፉ ተገደዋል፡፡ በመሆኑም ግለሰቦቹይህንን ሃገርንና ወገንን ብሎም ራሳቸውን የሚጎዳ እኩይ ተግባር ከመፈጸማቸው በፊት ቆም ብለው ሊያስቡይገባ ነበር እንላለን፡፡


ክሽንሄላ - ኢ-ፍትሃዊው የምርምር ዓለም ክስተትእ.ኤ.አ በ1951 በአንድ ወቅት ሄነሪታ ላክስ የተባለች የ31ዓመት ጥቁር አሜሪካዊትሴት ባልቲሞር ሜሪላንድወደሚገኘው ጆን ሆፕኪንስ ሆስፒታል ለህክምናእርዳታ ትመጣለች። በሆስፒታሉ የተደረገላት ህክምና የማህጸን ካንሰር በሽተኛ እንደሆነችና በማህጸኗ ውስጥ እጢ እንደሚገኝ ያሳያል።ሄነሪታ በሆስፒታሉውስጥ ህክምና እየተደረገላት ሳለ ዶክተሮቹ የሷንፍቃድ ሳይጠይቁ በማታውቀው ሁኔታ ከማህጸኗከወጣው እጢ ላይ ናሙናበመውሰድ ለበለጠ ሳይንሳዊ ምርምር ወደ ላብራቶሪይልኩታል፡፡ ይህ በሆነ በጥቂት ወራት ውስጥ ከማህጸኗ የወጣው ናሙና ለሳይንሱ ዓለም ብሎም ለሰውልጅ ጤና ያበረከተውን አስተዋጽኦ ለማየት እንኳንሳትታደል ሄነሪታ ይህቺን ዓለም ትሰናበታለች።ሆኖምከሰውነቷ የተወሰደው ናሙና እሷ ከሞተች በኋላምህይወት እንዳለው የቆየና የህክምናውን ዓለም ሰዎች አጀብ ያሰኘ የመጀመሪያው የሰው ልጅ ህዋስ ነው፡፡ ናሙናውሳይንሳዊ ምርምር ከተደረገበት በኋላ በመጀመሪያ በአንድላብራቶሪ በመቀጠል በመቶዎችና በሺዎች እየተባዛ ለኤድስህሙማን እድሜ ማራዘሚያ መድሃኒት እና ለፖሊዮ በሽታክትባት ከማስገኘቱም በላይ ኒኩሊየር የሚያስከትለውን የጉዳት መጠን ለማሳወቅ የሚያስችል ምርምር ተካሂዶበታል።ከሄነሪታ የተወሰደውና በሳይንሳዊ አጠራር ሄላ በመባልየሚጠራው ናሙና ለምርምር ወደ ጠፈርም መላኩንናለዘመናዊ ሳይንስ መሰረት በመሆን የዘረ-መል ማባዛት፣ቫይረሶች እንዴት እንደሚራቡና ካንሰር በሰውነት ውስጥያለው የእድገት ሁኔታንም ለማወቅ በር ከፋች መሆኑንዘገባዎች ይጠቁማሉ።ሄነሪታ ላክስ ለህክምናው የምርምር ዓለም ባጠቃላይለሰው ልጆች ያበረከተችው አስተዋጽኦ ይህ ሆኖ ሳለያብራኳ ክፋዮችና ሌሎች የቤተሰቡ አባላት ግን የኢኮኖሚአቅማቸው ደካማ ስለነበር ከእናታቸው ሴል ከተሰሩት እናበሌሎች መድሃኒቶች እጦት ምክንያት ሲሰቃዩ ኖረዋል፡፡ይሁን እንጂ በጋዜጠኛ ርብቃ ስክሉት የተጻፈና “ህያዉየሄነሪታ ላክስ ህይወት” (The Immortal Life of HeneritaLacks) የተባለ በሴትየዋ ህይወትና አስተዋጽኦ ዙሪያየሚያጠነጥን መጽሀፍ እውነታውን ይዞ ወጥቷል።መጽሀፉ ናሙናው እንዴት ከባለቤቱ እውቅና ውጪ ለምርምር እንደዋለ ብሎም በላብራቶሪ እየተባዛ ወደተለያየ የዓለም ክፍል እንደተሰራጨና በሚሊዮኖች በሚቆጠር ገንዘብ እየተሸጠ እንደሚገኝም ለዓለም ህዝብ ይፋ አድርጓል።በተጨማሪም መጽሀፉ በኢኮኖሚ አቅሙ ደካማ ስለሆነው እና በህይወት ለመኖር በጣም አስፈላጊ የሆነውን የህክምና አገልግሎት ሽፋን በዘረኝነት ምክንያትስለተነፈገው የሄነሪታን ቤተሰብ አሳዛኝ ታሪክ ይዞ ወጥቷል። ከዚህም ሌላ በርብቃ ስክሉት የተጻፈው መጽሀፍ በአሜሪካ የህክምና ሳይንስ ምርምር ዙሪያ የተፈጸሙ ተመሳሳይ ኢ-ፍትሃዊ ድርጊቶችንም አካትቷል።ታይም መጽሄት የካቲት 2010 እና ሌሎችምለስኳር በሽታ መፍትሄ የሆኑ 12 የምግብአይነቶችበአለማችን በአሁኑ ጊዜ 285 ሚሊዮን ሰዎች የስኳርህሙማን ናቸው። ከነዚህም ውስጥ 80 በመቶው ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ባላቸው ሃገራት ይገኛሉ። በቂየሆነ ምርመራና ህክምና እጦት እንዲሁም የተዛባ የአመጋገብ ባህርይ ለቁጥሩ መጨመር ከፍተኛ አስተዋጸኦእንዳለው የዓለም የጤና ድርጅት አስታውቋል። ድርጅቱተገቢው የመፍትሄ እርምጃ ካልተወሰደ በ2030በዓለማችን የስኳር ህሙማን ቁጥር ወደ 438 ሚሊዮንእንደሚያሻቅብና በተለይ ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ባላቸውሃገራት በሚቀጥሉት አስር አመታት በበሽታው ሳቢያየሚከሰተው ሞት በ17 በመቶ እንደሚጨምር ይገልጻል፡፡ሜንስ ሄልዝ የተባለው መጽሄት ሰሞኑን ያሰራጨው ዘገባ ግን ለስኳር ህሙማን ታላቅ የምስራችን ይዞ ቀርቧል።እንደ ዘገባው አንዳንድ ምግቦች በደም ውስጥ የሚገኘውን የስኳር መጠን ለማረጋጋት ከመቻላቸውም በላይ ልብንና የዓይን ብርሃን ላይ በስኳር በሽታ ምክንያት ከሚከሰትየጤና መቃወስን ለመቋቋም እንደሚረዱ መጽሄቱ ከተለያዩ የምርምር ተቋማት ያገኘውን መረጃ በመጥቀስ ዘግቧል፡፡ምግቦቹ ፖም፣ቀረፋ፣ ፍራፍሬዎች (ብርቱካን፣ ሎሚ፣መንደሪን…ወዘተ)፣ በቀዝቃዛ የውሃ አካላት ውስጥ የሚገኙ የዓሳ ዝርያዎች ለምሳሌ ሰርዲን፣ በፋይበር የበለጸጉምግቦች፣ ጥራጥሬዎች (ሽምብራ፣ ባቄላ፣ አተር፣ ምስር)፣አረንጓዴ ሻይ፣ የለውዝ ዝርያዎች፣ ዝኩኒን የመሳሰሉአረንጓዴ ተክሎች፣ ጠቆር ያለ ቸኮሌት፣ ስጋንና ኮምጣጤን ያጠቃልላሉ፡፡ፖምበፊንላንድ የተካሄደው ጥናት እንደሚጠቁመው አዘውትረው ፖም የሚመገቡ ሰዎች በስኳርና በልብ በሽታ የመሞት እድላቸው ከማይበሉት ጋር ሲነጻጸር በ 20 በመቶቀንሶ ተገኝቷል፡፡ቀረፋበአሜሪካ የተካሄደው ጥናት እንደሚያሳየው በቀን ግማሽ ማንኪያ ቀረፋ መጠቀም የህዋሳቶቻችንን (ሴሎቻችንን) በደም ውስጥ የሚገኘውን ስኳር ወደ ኃይልየመለወጥ ብቃት ከፍ ያደርገዋል፡፡23<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ም


ፍራፍሬዎች (ብርቱካን፣ሎሚ፣መንደሪን)አንዳንድ የምርምር ውጤቶች እንደሚያሳዩት የስኳርህሙማን በሰውነታቸውውስጥ የሚገኘው የቫይታሚን ሲ መጠን ዝቅተኛስለሆነ ብርቱካን፣ሎሚ፣መንደሪን የመሳሰሉትንበቫይታሚን ሲ የበለጸጉፍራፍሬዎች ቢመገቡመልካም ነው፡፡የዓሳ ዝርያዎች ለምሳሌ ሰርዲንየልብ በሽታ ከጤነኞች ይልቅ የስኳር ህሙማንን በበለጠ ስለሚያጠቃ እንደሰርዲን ያሉትንየዓሳ ዝርያዎች መመገብ የደምቧንቧዎች መዘጋትን ከመቀነሱም በላይ ለሰውነት ጠቃሚየሆነውን የኮሌስትሮል (HDL)መጠንም የተመጣጠነ ያደርጋል፡፡የለውዝ ዝርያዎችምንም እንኳን ለውዝን የመሳሰሉምግቦች በካሎሪ እጅግ የበለጸጉ ቢሆንም ቢያንስ ሁለት የሻይ ማንኪያ በቀን ከተለያየ ምግብ ጋር ቀላቅሎ መጠቀም ለልብ ህመም ተጋላጭነትን ይቀንሳል (የስኳር ህሙማን ከሌሎች ሰዎች በበለጠ ለልብበሽታዎች የተጋለጡ ናቸው)፡፡ዝኩኒና ሌሎች አረንጓዴ ተክሎችዝኩኒን የመሳሰሉ አረንጓዴ ተክሎች ለአይን ጤንነትጠቃሚ የሆነውን ካሮቴኖይድ የተባለ ንጥረ ነገር በውስጣቸው የያዙስለሆነ የስኳር ህሙማን ላይሊደርስ የሚችለውን የአይን ችግርበመከላከል ረገድ ጉልህ ሚና ይኖራቸዋል፡፡ጠቆር ያለ ቸኮሌት<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምበፋይበር የበለጸጉ ምግቦችከቴክሳስ ዩንቨርሲቲ የተገኘው የጥናት ውጤት እንደሚያሳየው በፋይበር የበለጸጉ ምግቦች (ምሳሌ ቆስጣ እናጥቅል ጎመን የመሳሰሉ አትክልቶች) በደም ውስጥ በሚገኘውየስኳር መጠን ላይ ከፍተኛመሻሻል እንዲኖር ስለሚረዱበቀን ከ 24-50 ግራም በፋይበር የበለጸጉምግቦች መመገብለጤና ጠቃሚእንደሆነ ይገልጻል፡፡ጥራጥሬዎች (ሽምብራ፣ባቄላ፣አተር፣ምስር)እነዚህ ጥራጥሬዎች የካሎሪ መጠናቸው ዝቅተኛ የሆነና ከፍተኛ ፕሮቲን ስላላቸው የስኳርና የልብ በሽታዎችን ለመቀነስ አስተማማኝ መፍትሄ ናቸው፡፡አረንጓዴ ሻይአረንጓዴ ሻይ መጠጣት ለሰኳር ህመም መፍትሄ እንደሆነ የተለያዩ ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡ተፍት ዩኒቨርሲቲ የሚገኙ ተመራማሪዎች በቅርቡ ይፋያደረጉት የምርምር ውጤትእንደሚያሳየው በመጠኑ የሚወሰድጠቆር ያለ ቸኮሌት የኢንሱሊንን ደምየማጣራት ተግባር በማፋጠን ለስኳር ህመም መፍትሄ ከመሆኑም በተጨማሪ የደም ግፊትንም በመቀነስረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው፡፡ስጋከገንቢ ንጥረ ነገሮችና ከቫይታሚን ሲ በተጨማሪ በስጋ ውስጥደም ውስጥ የሚገኘውን የስኳርዝውውር የሚያስተካክል ንጥረነገር ይገኛል፡፡ኮምጣጤከምግብ በፊት የሚወሰድ ሁለትየሻይ ማንኪያ ኮምጣጤ በደም ውስጥየሚገኘውን የስኳር መጠን ይቀንሰዋል፡፡ማሳሰቢያሜንስ ሄልዝ እና የዓለም የጤና ድርጅትየስኳር በሽታን ለመቆጣጠር ከተለያዩ ምንጮች ያገኘናቸውን መረጃዎች እንድታገኙ ያቀረብነው ይህ መጣጥፍየሀኪም የቅርብ ክትትል እና ምክር እጅግ አስፈላጊመሆኑን የሚያስቀር አለመሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን፡፡24


ውስን ሀብት በሆነው መሬት ላይየሚፈጸም ሙስና ጉዳቱ የከፋ ነውየፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን በተለያዩየመንግስት መስሪያ ቤቶችና የልማት ድርጅቶች ውስጥየሚታዩ የአሰራር ክፍተቶችን ለመዝጋት የችግሮቹን መንስኤዎች በጥናት በመለየት ለሚመለከተው ተቋም የመፍትሄሃሳብ ማቅረብና ተግባራዊነቱን ማረጋገጥ ሙስናና ብልሹአሰራርን ለመከላከል ከሚጠቀምባቸው ስልቶች አንዱ ነው፡፡የዚህ ጽሁፍ ዋና መነሻ ኮሚሽኑ በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የቦታ ግንባታ ፈቃድ አሰጣጥና ይዞታ አስተዳደር የሥራሂደት እና የመሬት ልማት፣ የነዋሪዎች ዳግም ማስፈርናየከተማ ፕላን ዝግጅት የሥራ ሂደት ላይ በቀረቡ ቅሬታዎችመነሻነት በኮሚሽኑ የተካሄደ ጥናት ላይ የሚያተኩር ይሆናል፡፡በድሬዳዋ ከተማ አሰተዳደር በመሬት ልማትና አስተዳደር ባለሥልጣን የቦታ፣ ግንባታ ፈቃድ አሰጣጥና ይዞታ አስተዳደርእና የመሬት ልማት፣ የነዋሪዎችን ማስፈርና የከተማ ፕላንዝግጅት አብይ የሥራ ሂደቶች በሚሰጧቸው አገልግሎቶች ላይእና የሪል ስቴት ግንባታ በተሰጠባቸውና በቀበሌ አስተዳደር ላይየሚሰጠውን አገልግሎት በተመለከተ ምልከታም ተከናውኗል፡፡በጥናቱ በሁለቱም የስራ ሂደቶች የአሰራር ክፍተቶች የሚታዩባቸውና ፍትሃዊ ያልሆነ አሰራር እንዲሰፍን የሚጋብዙ በመሆናቸው የታዩትን ችግሮች ለመቅረፍ የመፍትሄ ሀሳቦች ቀርበዋል፡፡በዚሁ መሰረት የተጠናከረ የመሬት የመረጃ አያያዝ እና አጠቃቀም ሥርዓት አለመኖር የጥናት ቡድኑ ከለያቸው ችግሮችየመጀመሪያው ነው፡፡ የመረጃ አያያዝ እና አጠቃቀምን በተመለከተ ቦታዎች እንደመሬቱ ተፈላጊነትና አስፈላጊ የሆነውንየኢንቨስትመንት ወይም የንግድ ዘርፍ፣ በሪል ስቴት፣ለከተማግብርና፣ ኢንቨስትመንትና ለልዩ ልዩ ማህበራዊ ጉዳዮች ሊውሉ የሚገባቸው ቦታዎች አስቀድሞ ባለመለየታቸውና ባለመያዛቸው ውስን የሆነውን መሬት ለብክነት ከመዳረጉም ባሻገርፍትሀዊነት ለጎደለው የቦታ አሰጣጥና አሰራር በር ከፍቷል::ይህን ችግር ለመፍታት በከተማ አስተዳደሩ ያለውን የመሬትሃብት በአግባቡ በመያዝ በአካባቢው ካሉ የክልል መስተዳድሮችእና ገበሬዎች ጋር በመደራደር “Land -Sharing System” በመጠቀም የመሬት ባንክ /Land-stock/ እንዲጨምር ማድረግ ወሳኝ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ መረጃዎችን ለማሰባሰብ የመሬት ቆጠራማካሄድንና በከተማዋ ያለውን የመሬት ሁኔታን ዘመናዊ ለማድረግ በቂ ማሰባሰብ ያለውን የመሬት ሀብት በቁጠባ ለመጠቀምየሚያስችል መሆኑ በጥናት ቡድኑ በመፍትሔነት ተጠቁሟል፡፡አሰራራቸውን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እንዲደገፍ ካደረጉ የከተማ አስተዳደሮች ልምድ በመቅሰም ተግባራዊ ማድረግ የበለጠ ጠቃሚ በመሆኑ አስተዳደሩ በቂ ትኩረት በመስጠት በአግባቡ ሊከታተለውና ወቅታዊ ምላሽ ሊሰጠው የሚገባ ነው::የመሬት ልማትና አስተዳደርን ለመምራት የወጡ አዋጆች፣ደንቦችና መመሪያዎች በአግባቡ አለመፈጸም በጥናቱ በሁለተኛ ደረጃ የተቀመጠ ነበር፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር በቻርተርአዋጅ ቁጥር 416/97 ከተቋቋመበት ጀምሮ የመሬት ልማትናአስተዳደርን በተመለከተ ለማስፈፀሚያ በርካታ አዋጆችን፣ደንቦችንና መመሪያዎችን አውጥቷል፡፡ ነገር ግን የመሬትልማትና አስተዳደር ባለሥልጣን በሚሰጣቸው አገልግሎቶችዙሪያ የወጡትን አዋጆች፣ደንቦችና መመሪያዎች መሠረት በማድረግ ሥራውን በአግባቡ አለመከናወኑን ጥናቱ ያመለክታል፡፡ባለሥልጣኑ የመሬት ልማትና አስተዳደርን በተመለከተየወጡ አዋጆች፣ ደንቦችና መመሪያዎችን የመሠረታዊየአሰራር ሥርአት ሂደት ለውጥ መሠረት አድርጎ ከአዲሱአደረጃጀትና አሰራር ጋር በሚጣጣም መልኩ የሚሻሻሉ የህግማዕቀፎችን በማሻሻል ተግባራዊ በማድረግ አፈጻጸማቸው በየጊዜው እየተገመገመና ኦዲት እየተደረገ ለሚከሰቱ ችግሮችወቅታዊ እርምጃ በመውሰድ ግልጽነትንና ተጠያቂነትን ማስፈንእንዲሁም በወጡና በሚወጡ ሕጎችና መመሪያዎች ዙሪያግንዛቤ የማስጨበጥና የማዳበር ሥራ ቀጣይነት ባለው መልኩማከናወን ችግሩን ሊፈቱ የሚችሉ መሆኑን ጥናቱ ያመለክታል፡፡በአስተዳደሩ የሊዝ ደንብ መሠረት የተቋቋመው የሊዝ ቦርድተግባርና ኃላፊነቱን በአግባቡ አለመወጣት የጥናት ቡድኑየተመለከተው ሶስተኛው ችግር ነው፡፡ በድሬዳዋ አስተዳደር በሊዝየሚሰጡ ቦታዎችን በተመለከተ አግባብ ያለው ተጠያቂነትናግልፅነትን የተከተለ አገልግሎት ለመስጠት ያስችል ዘንድ የሊዝቦርድ ተቋቁሟል፡፡ የሊዝ ቦርዱ በመሬት ልማትና አስተዳደርአማካኝነት የሚቀርብለትን የውሳኔ ሃሳብ በመመርመርና የመጨረሻ ውሳኔ በመስጠት ረገድ የተሰጠውን ኃላፊነትና ተግባር በአግባቡ ባለመወጣቱ የሊዝ ቦታ አሰጣጥ ስርአቱ በተመለከተ ወጥነትየጎደለው መሆኑ፣ መሬት ለልማታዊ ባለሀብቶች ከመስጠትይልቅ ለማልማት አቅም ለሌላቸውና መሬት ለሚሸጡ ግለሰቦችመስጠት፣ ምትክ ቦታ ሲጠየቅ ባለሥልጣኑ ማዘጋጀት ሲገባውጠቁሙ ማለትና የተጠቆመውንም ቦታ ጥያቄውን ላላቀረበ ባለሀብት አሳልፎ መስጠት፣መሬትን በሊዝ በድርድር ምንም ቅድመሁኔታ ላላሟሉ በዝምድና መስጠት፣የሊዝ ዋጋ ግምት በጣምዝቅተኛ እንዲሆን ማድረግ፣ በአንድ አካባቢ በአንድ ደረጃ ላይለሚገኙ ቦታዎች የተለያየ የሊዝ ዋጋ ማውጣት፣ አቅም እያላቸው መሬት ያላገኙ ልማታዊ ባለሀብቶች ያሉባቸውን ችግሮችለመፍታት ጥረት አለማድረግ ከታዩት ችግሮች ውስጥ ይጠቀሳሉ ፡፡እነዚህን ችግሮች ለመፍታት በሊዝ የሚሰጡ ቦታዎች የጨረታ አሠጣጥና የመነሻ ዋጋ አፈፃፀም መመሪያን መሠረት በማድረግ ቦርዱ የተሰጠውን ተግባርና ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት፣ባለሀብቱንና ህዝቡን በማወያየት ለሚታዩ ችግሮች አፋጣኝ ምላሽመስጠት እንዲሁም የሥነ ምግባር ጉድለት በሚታይባቸውሠራተኞች ላይ ትምህርት ሰጪ የሆነ ርምጃ መውሰድ አስፈላጊመሆኑን የጥናት ቡድኑ ጠቁሟል፡፡ ይህ አሰራር የሥራ ኃላፊዎችን የሥራ መደራረብና ተጨማሪ ጊዜ የሚጠይቅ ቢሆንም የኃላፊዎችን ጣልቃ ገብነት ከመከላከሉም በላይ ግለጽነትንና ተጠያቂነትንየተላበሰ የአሰራር ስርአት ተከትሎ እንዲተገበር እገዛ ያደርጋል ::የጥናት ቡድኑ በአራተኛ ደረጃ ያስቀመጠው የአሰራርችግር በአስተዳደሩ በሊዝ የሚሰጡ ቦታዎችን ለመሸጥየግልፅ ጨረታ ዘዴን አለመጠቀም ነው፡፡ የከተማ ቦታ በሊዝእንዲያዝ የሚፈቀደው በጨረታ መሆኑንና ለጨረታ የሚቀርቡ ቦታዎችን የተመለከተ ዝርዝር ጉዳዮችን የአፈጻጸም መመሪያው ይገልፃል፡፡ ነገር ግን በከተማዋ በሊዝ የሚሰጡ ቦታዎች የመንግስትንና የህዝብን ተጠቃሚነት የማያረጋግጡና በአብዛኛው የግልፅ ጨረታ ዘዴን መሰረት ያደረጉ አይደሉም ፡፡ለአብነት ያህል በግልፅ ጨረታ መሰጠት የሚገባውን ለንግድስራ የሚሆን “Commercial Area” አንደኛ ደረጃ ቦታ ካለጨረታ ከሊዝ ነፃ ተጨማሪ ካሬ ሜትር በማካተት መስጠት፣ ለአንድ ግለሰብ በቀጥታ በሊዝ የአቅም ማሳያ ሳይኖርና የሊዝ ቦርድውሳኔ ሳይሰጥ፣ የሊዝ ቦርድ ሰብሳቢ በሌሉበትና ውክልናም ባልተሰጠበት ሁኔታ በሜትር ካሬ በብር 184 ሂሳብ እስከ 11‚433ካሬ ሜትር መሬት መስጠት የመሳሰሉት ችግሮች ተስተውለዋል፡፡25<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ም


<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምይህ አሰራር ከመሬት ሽያጭ ሊገኝ የሚገባውን ጥቅም ከማሳጣቱም ባሻገር ወጥነት ለጎደለውና በጥቅም ላይ ለተመሰረተ ግንኙነት ሊዳርግ ይችላል፡፡ ይህን ችግር ለመፍታትበከተማው ያሉ በሊዝ ሽያጭ የሚውሉ ቦታዎች የሚገኙባቸውን አካባቢዎች መሠረት በማድረግ ደረጃ በማውጣትበአንደኛ ደረጃ ላይ ያሉ ቦታዎችን በግልጽ ጨረታ ዘዴ ብቻበመጠቀም የመንግስትንና የህዝብን ጥቅም ፍላጎት ሊያስጠብቅየሚችል አሰራር መዘርጋት ፣በሊዝ ሽያጭ ሊውሉ የሚችሉቦታዎችን ለተለያዩ አገልግሎቶች እንዲውሉ በሚያስችልመንገድ ለንግድ፣ ለማህበራዊ አገልግሎቶችና ለሌሎች የልማትዘርፎች ሊውሉ አስቀድሞ በመለየት በድርድር ወይም በውስንጨረታ ዘዴ ለሽያጭ ማቅረብ በጥናቱ በመፍትሄነት ተጠቁሟል::በዚህ አሰራር የጨረታ ሂደቱ ተጨማሪ ጊዜና ወጪ የሚጠይቅ ቢሆንም የሊዝ አፈጻጸም ከመሬት ዝግጅት እስከ ሽያጭናርክክብ ድረስ ያለው የስራ ሂደት በእቅድና በፕሮግራም እንዲከናወን ለክትትልና ቁጥጥር የተመቻቸ ይሆናል፡፡ በተጨማሪ የሊዝቦታ ሽያጭ አፈጻጸምን ህግና መመሪያ መከተሉ ግልጽነትንናተጠያቂነትን የተላበሰ አሰራር ስርአት እንዲዘረጋ እና አልሚውቦታውን ለወሰደው ዓላማ በአግባቡ እንዲጠቀምበት ስለሚያደርግሊፈጸሙ የሚችሉ የሙስና ወንጀሎችን ለመከላከል ያስችላል ፡፡በሊዝ መሬት ለሚጠይቁ አልሚዎች ቅድመ ሁኔታ ሳያሟሉ መስጠት ጥናቱ ያመለከተው ስድስተኛው ችግር ነው፡፡ ከመሬት ልማትናአስተዳደር ባለሥልጣን በሊዝ መሬት የሚወስዱ ባለሀብቶች በተጫራቾች መመሪያ መሰረት እንደ ሽያጭ ውሉ ሊለያይ ቢችልም ቢያንስ የሚከተሉትን ቅድመ ሁኔታዎችን ማሟላት ይጠበቅባቸዋል ፡፡ትክክለኛና ልማታዊ የሆኑ ባለሀብቶች ፕሮፖዛል አቅርበውና ቅድመ ሁኔታዎችን አሟልተው መሬት የማያገኙበት ሁኔታ ሲኖር በሌላ በኩል ደግሞ የውል ስምምነት አስፈጻሚ ባለሙያዎች ቅድመ ሁኔታ አለመሟላቱን እያሣወቁም በሚፈጠር ጫና አንዳንዶች መሬት ያለአግባብ እንዲያገኙሲደረግ ይታያል፡፡ በሊዝ ቦርድ መወሰን የሚገባው ጉዳይሳይወሰን ተወስኗል ብሎ ለውል መላክና የውል ስምምነትሠነድ መፈረም፣ ባለ ንብረት ላይ በተሰጠው ውክልና ያለ ኢንቨስትመንት ፈቃድ መሬት መስጠት ሁኔታዎች ተከስተዋል፡፡የጥናት ቡድኑ ካሰባሰባቸው መረጃዎች ለመገንዘብ እንደተቻለውአስተዳደሩ መሬት ከሰጣቸው ከ552 አልሚዎች መካከል 91(16%)ብቻ ቅድመ ሁኔታውን አሟልተው የሊዝ መሬት የተረከቡሲሆን 84% ያህሉ ቅድመ ሁኔታን ያላሟሉ ሆነው ተገኝተዋል፡፡ከዚህ አንፃር በሊዝ የመሬት አሰጣጥ ሥርዓቱ ፍትሃዊነት የጎደለውና ለሙስናና ብልሹ አሠራር የተጋለጠ ነበር ለማለት ይቻላል፡፡ማንኛውም መሬት ይሰጠኝ ባይ ባለሃብት ቦታውን በትክክል ማልማት የሚችል መሆኑን ለማወቅ የሚረዱና በግልጽ የተቀመጡ ቅድመ ሁኔታዎች መሟላታቸውን በማረጋገጥ ቦታ መስጠት፣ የተከናወኑ ስራዎችን በየጊዜው በመገምገምና ችግሮችን በመለየት ወቅታዊ የማስተካከያ እርምጃመውሰድ ያስፈልጋል:: በጥናቱ እንደተመለከተው ይህ አሰራር የከተማዋን ቦታ አሰጣጥ ግልጽነትንና ተጠያቂነትን የተላበሰ እንዲሆን በማድረግ ልማታዊ ባለሀብቶችን የሚያበረታታናየከተማዋን እድገት በማፋጠን ረገድ ጉልህ ሚና ይኖረዋል::ከዚሁ ጋር ተያይዞ የተጭበረበሩ ማስረጃዎች ሊቀርቡየሚችሉበትን ሁኔታ እና በሌሎች አካላት የሚሰጡ ማስረጃዎችም ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመፍታት በአግባቡእንዲቀርቡ ለማድረግ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ትኩረትሰጥቶ በቅንጅት መስራት ችግሩን ለመፍታት አስፈላጊ ነው፡፡በጥናቱ የተመለከተው ስድስተኛው ችግር በየጊዜው የተመደቡአንዳንድ ኃላፊዎች ሥልጣናቸውን አለአግባብ መገልገል ነው፡፡በአስተዳደሩም መሬትን በተመለከተ እና አጠቃላይ የከተማውንዕድገት ለማፋጠንና ልማትን ለማምጣት የሚያስችሉ ሥርዓቶችተዘርግተዋል፡፡ ነገር ግን በተለያየ ወቅት በከተማ አስተዳደሩ በኃላፊነት ላይ የተመደቡ ኃላፊዎች የተቀመጡ ግልጽ አሠራሮችንተከትለው በመስራት የመንግስትንና የሕዝብን ጥቅም ከማስጠበቅ26ይልቅ ስልጣናቸውን ያለገደብ በመጠቀም ህገወጥ ተግባሮችንመፈጸማቸውን የጥናት ቡድኑ ለመገንዘብ ችሏል፡፡ለአብነት ነዋሪዎችን ህገወጥ ናችሁ በማለት እንዲነሱ ማድረግናመሬት ለራስ በመያዝ የመኖሪያ ቤት መገንባት፣ የሰዎችን ፍላጎት መሠረት ያደረገ የመንገድ ቅየሳና የማስተር ፕላን ክለሳ ማካሄድ፣ በሪል ስቴት ስም ፕሮጀክት ፕሮፖዛል የሌላቸውና የጊዜ ገደቡ ያለፈ የመከነ ካርታ በኃላፊዎች ትዕዛዝ እንዲቀጥል ማድረግየተስተዋሉ ችግሮች ናቸው፡፡ በተጨማሪም የከተማውን የቀለበትመንገድ ግንባታ 32 ኪሎ ሜትር ፕሮጀክት ማሻሻያ በ74 ሚሊዮን ብር የተዘጋጀውን አንድ የሥራ ኃላፊ የአንድ ባለሀብት የእርሻ ቦታ ይነካል በማለት መቀየር፣ በሊዝ ቦርድ የተወሰኑ ውሳኔዎችን በመሻር የመንግስትን ጥቅም መጉዳት፣ የሊዝ ቦርድ የሰጠውን ካሬ ሜትር በማስበለጥ ከሊዝ ነፃ እንዲሰጥ ማድረግ (ለ1ሺካሬ ሜትር 4ሚሊዮን ያቀረበ አልሚ እያለ ካርታው እንዲመክን በማድረግ ቀጥታ የሊዝ ቦርዱ ከወሰነለት በተጨማሪ 43ዐ ካሬ ሜትር ቦታ በማካተት በአጠቃላይ 143ዐ ካሬ ሜትር አቅምማሳያ 5ዐዐ ብር አስይዞ መንገድ ዳር አንደኛ ደረጃ ቦታ በ184ብር በካሬ ሜትር መስጠት) የመሳሰሉት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡እነዚህን ችግሮች ለመፍታት ቀደም ሲል በከተማ አስተዳደሩ ያሉ የሥራ ኃላፊዎች ሥራቸውን በተሰጣቸው ስልጣንናኃላፊነት መሠረት ብቻ ደንብና መመሪያ ተከትለው መሥራት፣ አለአግባብ የተወሰዱ እርምጃዎች እንዲስተካከሉ ማድረግ፣የሚሰጡ ውሳኔዎችን በየጊዜው መገምገምና ሪፖርት እንዲቀርብ ማድረግ፣ ኃላፊነትንና ተጠያቂነትን ማመላከት እንዲሁም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በተፈጸመ ህገ ወጥ ተግባር ላይአስተማሪ የሆነ አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰድ አስፈላጊ ነው፡፡የተነሺዎች የካሳ ክፍያ አፈጻጸም ደንብንና መመሪያን የተከተለ አለመሆን በጥናቱ በሰባተኛ ደረጃ የተቀመጠ ችግር ነው፡፡ለህዝብ ጥቅም እና ለልማት ተግባር ሲባል የመሬት ይዞታእንዲለቀቅ ሲደረግ ለባለ ይዞታው ካሣ የሚከፈልበት ሥርዓትአለ፡፡ ይህ አሠራር ሲተገበር የካሣ ክፍያው የሚያካትታቸውየግንባታ ባለቤቶች (የግል ባለይዞታዎች፣ የመኖሪያ ቤት ግንባታ፣የቀበሌ ቤት፣ የኪራይ ቤቶች አስተዳደር ድርጅት ቤቶች) እናየቤት ካሣ ክፍያው ሲፈፀም ሊሟሉ የሚገባቸው የንብረት ማረጋገጫና ዝርዝር ቅድመ ሁኔታዎች መሟላታቸውን ማረጋገጥይኖርበታል፡፡ ነገር ግን እነዚህ ሁኔታዎች በአግባቡ ክትትል ስለማይደረግባቸው የካሣ ክፍያ በቀበሌና በኪራይ ቤቶች ለግለሰቡ/ለነዋሪው/ለተከራዩ መክፈል፣ በተነሺዎች ላይ ያልነበረ ሰው በማካተት የካሣ ክፍያ እንዲሰጠው ማድረግ፣ለተነሺዎች ተመሳሳይቦታ መስጠትና የካሣ ክፍያ መፈፀም፣ የባለንብረቱ/ባለቤቱ ማስረጃ ሳይጣራና ሳይለይ ለግለሰብ ክፍያ መፈፀም፣ የካሣ ክፍያ ሳይከፍል አንደኛ ደረጃ የንግድ ቦታን መስጠት እንዲሁም የንብረት ግምት በሚሠራበት ወቅት አግባብ ያለው ማጣራት አለማድረግና የጥቅም ግንኙነት ላይ በመመስረት የተጋነነ ዋጋ ማስላትንየመሳሰሉት ችግሮች መኖራቸውን በጥናት ቡድኑ ተመልክቷል፡፡ስለሆነም ከላይ የተጠቀሱትና ሌሎች መሰል የ<strong>ሥነምግባር</strong>ግድፈቶች አንዳንድ ግለሰቦች ከአንዳንድ የመሬት ልማትና አስተዳደር ባለሥልጣን የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ጋር በሚፈጥሩት ልዩ የጥቅም ግንኙነት አላግባብ ተጠቃሚ እንዲሆኑእንዳስቻላቸው በጥናቱ ወቅት የታዩ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡በአስተዳደሩ የካሣ ክፍያና የምትክ ቦታ አሰጣጥ የአፈፃፀምመመሪያና ከሌሎች አካላት ጋር የተፈጸሙ የጋራ መግባቢያስምምነቶችን መሠረት በማድረግ ለልማት ከሚፈለገው ቦታለሚነሱ ተነሺዎች ለሚፈፀም የካሣ ክፍያ የሚወሰድ መረጃ በቅድሚያ ሁኔታዎችና ዝርዝር መሠረት(መረጃ አሰባሳቢው አካልየሚሰበስባቸውን መረጃዎች ከተነሺዎች ነባራዊ ሁኔታ ጋር የተጣጣመና እውነተኛ እንዲሆን በማድረግ ፣ በዚህም ተጠያቂነትና ኃላፊነት እንዲወስድ ማድረግ ፣ በመንገድ ልማት ምክንያትየሚነሱ ሲሆን ከመንገዶች ባለስልጣን ጋር በመተባበር መስራትናበተጨማሪ ያለውን የአፈጻጸም መመሪያ በማሻሻል) የተሻለስርአት እንዲኖር የተሟላና የተረጋገጠ መሆኑን በማጣራት የካሣክፍያ መፈጸም ያስፈልጋል፡፡ ከዚሁ ጋር ቀደም ሲል በተሳሳተ መረጃ የተፈፀሙ የካሳ ክፍያዎችን በማጣራት የማስተካከያ


እርምጃ መውሰድም ጠቃሚ መሆኑን የጥናቱ ውጤት ያመለክታል፡፡ይህ አሰራር ተጨማሪ ጊዜና አስተዳደራዊ ወጪ የሚያስከትልቢሆንም ግልጽነትንና ተጠያቂነትን የተላበሰ የአሰራር ስርአትተከትሎ እንዲተገበር እገዛ ያደርጋል፤ ለሚታዩ ችግሮች ዘላቂመፍትሄ ከመስጠቱ ባሻገር የተመደቡ ኃላፊዎችና ባለሙያዎችከግል ስሜታቸውና አድሏዊ አሰራር ነጻ ሆነው እንዲሰሩ ያስችላል ፡፡ጥናቱ ያመለከተው ስምንተኛው የአሰራር ችግር ለኢንቨስትመንትበሚሰጡ መሬቶች ላይ ያለው ክትትል፣ ቁጥጥርና ድጋፍ ደካማመሆን ነው፡፡ በአስተዳደሩ ኢንቨስትመንት ላይ በተለያዩ ዘርፎችበማምረቻ ኢንዱስትሪ፣ በአገልግሎት እና በከተማ ግብርና የኢንቨስትመንት መስክ ሥራ ለመሥራት መሬት የወሰዱ የግል ባለሀብቶችን በተመለከተ ሊደረግ የሚገባው አግባብ ያለው ክትትል፣ቁጥጥርና ድጋፍ ስለማይከናወን በኢንቨስትመንት ስም መሬትለመውሰድና ለማልማት በተደጋጋሚ የ}ወሰኑ ባለሀብቶች መሬትወስደው በመሸጥ የሚበለጽጉበት አሠራር ይታያል፡፡ ይህ አሰራርልማታዊ ባለሀብቶችን ማዕከል ያደረገና የከተማዋን ኢንቨስትመንት የሚያሳድግ ሳይሆን የጥቅም ግንኙነትን መሰረት ላደረገ አሰራር በመጋበዝ ሙስናና ብልሹ አሰራር እንዲስፋፋ በር ይከፍታል፡፡እንደ ጥናቱ መሬት ለማልማት የሚወስድ ባለሀብት በመጀመሪያ የግንባታ አቅም ማሳያ ገንዘብ ያለው፣ የኢንቨስትመንትፈቃድ ያወጣ፣ ሌሎችን ቅድመ ሁኔታዎችን ያሟላ እንዲሆን በማድረግ እና የአቅም ማሳያውን ገንዘብ ከሚያሳየው የግንባታ እንቅስቃሴ አንፃር ግምገማ እየተደረገበት የሚለቀቅበትን አሠራር መዘርጋት ያስፈልጋል፡፡ አልሚዎች ቦታዎችንሲወስዱ ግንባታውን ለመጀመርና ለማጠናቀቅ በተቀመጠው የጊዜገደብ መሠረትና በገቡት የውል ስምምነት ሠነድ አማካኝነትተገቢው ክትትል፣ቁጥጥርና ድጋፍ እንዲደረግላቸው በማድረግመሥራት ችግሩን ሊቀርፈው እንደሚችል በጥናቱተመልክቷል፡፡ ይህ አሰራር የከተማዋን ቦታ አሰጣጥ ግልጽነትንናተጠያቂነትን የተላበሰ አሰራር እንዲተገበር ስለሚያደርግ ልማታዊባለሀብትን በማበረታታት የከተማዋን እድገት ለማፋጠን ያስችላል፡፡ጥናቱ በዘጠነኛ ደረጃ ያመለከተው ችግር የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ አሰጣጥ ተጠያቂነትንና ግልፅነትን የተከተለ አለመሆን ነው፡፡ የመሬት ልማትና አስተዳደር ባለሥልጣን ከሚሰጣቸውዋና ዋና ተግባራት አንዱ የቦታና ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ አሰጣጥ ነው፡፡ ይህን ሥራ በተገቢው ሁኔታ ለመወጣት ተጠያቂነትና ግልጽነትን የተከተለ ባለመሆኑ በማህበር ተደራጅተው መሬት ለመውሰድ ጥያቄ ላቀረቡ ተገልጋዮች በአንድ ሰው ስም ካርታበመስጠት ህገ ወጥ ተግባር መፈፀም፣ በአንድ ቦታ ላይ ለሁለት ሰዎች ካርታ መስጠት፣ መሀንዲሶች ሲለኩ ባዶ ቦታ መተውና በህገወጥ መንገድ እንዲያዝ አድርጎ ካርታ በገንዘብ ማሰራት፣በካርታ ላይ ካርታ በመስራት፣ ተገልጋዮችን ለአላስፈላጊ ሁኔታመዳረግና ፍትህን ማዛባት፣ የመንግስትን ቤት ተከራይተው ለሚኖሩ ግለሰቦች ማስፋፊያ አግባብ በሌለው መንገድ መስጠት፣ የቀበሌ ቤት በግል ይዞታ ማዞር ለዚህም የግል ማህደር ማጥፋትናበግለሰብ እንዲቀየር ማድረግ፣ Open and green areas ቦታዎችን ለግለሰቦች በመስጠት የይዞታ ማረጋገጫ እንዲኖራቸው ማድረግ፣ ለአንድ ግለሰብ ከአራት ቦታ በላይ ለመኖሪያ ቦታ መስጠት፣በውጭ ድርጅቶች ለቆሻሻ ማስወገጃ የተሠራውን ቦታ በጥቅማጥቅም ለግለሰብ መስጠትና በአካባቢው ነዋሪ ላይ የጤናና ማህበራዊ ችግሮችን ማስከተል የሚጠቀሱ ችግሮች ማሳያዎች ናቸው፡፡ስለሆነም ትክክለኛ የሆነ የቦታና ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ አሰጣጥ ሊያሰፍን በሚችል መልኩ ደንብና መመሪያን መሠረት አድርጎ የሚከናወን ባለመሆኑ ከዚህ ጋር ተያይዘው ለሚከሰቱ ሙስናና ብልሹ አሰራር የተጋለጠ ነው፡፡በመሆኑም ይህን ክፍተት ለመሙላት ተገልጋዩን ፍትሃዊናበአግባቡ ለማስተናገድ ለመከላከል እንዲቻል ደንብና መመሪያን መሠረት ያደረገ የቦታ ይዞታና ካርታ ማረጋገጫ አሰጣጥእንዲተገበር ማድረግ፣ ቀደም ሲል አላአግባብ የተሰጡ የይዞታማረጋገጫ ካርታዎችን በማጣራት አግባብ ያለው እርምጃ መውሰድ፣ ተፈጻሚነቱን በየጊዜው በመከታተልና በመገምገም ለሚፈጠሩ ችግሮች ወቅታዊ እርምጃ መውሰድና በአገልግሎቱ ዙሪያ የህብረተሰቡን ግንዛቤ ማሳደግ ተገቢ መሆኑን ጥናቱ አመላክቷል::በከተማው ያሉትን ህገወጥና ሠነድ አልባ ይዞታዎች ምዝገባና ይዞታ ማስረጃ የመስጠት ሥራና አዘገጃጀት ትክክለኛመረጃዎችን መሠረት ያደረገ አለመሆን ጥናቱ የተመለከተውአስረኛ ችግር ነው፡፡ በከተማው በተለያየ ጊዜያት ህገ-ወጥ እናሠነድ አልባ ይዞታዎች በሬጉላራይዜሽን ፕላን መሠረት በቀበሌደረጃ በአጥኚ ድርጅት በተዘጋጀው አማካኝነት አስተዳደሩ የሚያጸድቀው ህገወጥ አሰፋፈሩን ሥርዓት የሚያስይዝበት ፕላንአለው:: ይሁን እንጂ አተገባበሩ ትክክለኛና እውነተኛ መረጃንመሠረት ያደረገ ባለመሆኑ ሰነድ አልባና ህገወጥ ቤቶች ተሰርተው የቆዩ በማስመሰል ካርታ በገንዘብ እንዲዘጋጅላቸው ማድረግ፣ የሠነድ አልባ ቤቶችን በተመለከተ የመንደር ኮሚቴ ስልጣናቸውን በጥቅማጥቅም አለአግባብ መጠቀም፣ ለሀሰተኛ ሰነድየተጋለጠ መሆን፣ የሀሰተኛ ሠነድ ባለጉዳዩ እንዲያዘጋጅ የተመቻቸ ሁኔታ መኖር፣ በቀበሌ በአግባቡ የማረጋገጥ ሥራ አለማከናወን፣ ፍ/ቤት የባለቤትነት ማረጋገጫ ሲጠይቅ አንዳንድ ቀበሌና የመሬት አስተዳደር ባለሥልጣናት ሀሰተኛ መረጃ በመስጠትናውሳኔዎችን በማዛባት ካርታ እንዲያገኙ ማድረግ፣ የተጭበረበረሠነድ ማዘጋጀትና ህግን የማስከበር አቅም ደካማ መሆን በአሠራሩ ውስጥ ይታያል፡፡ ይህም በከተማዋ የልማት እንቅስቃሴ ላይከሚያሳድረው አሉታዊ ተጽእኖ ባሻገር ግልጽነት የጎደለውና በህገ ወጥ ጥቅም ላይ የተመሰረተ ግንኙነት እንዲሰፍን ያደርጋል፡፡የአሠራር ሥርዓት ክፍተቱን ለመዝጋት በከተማዋ በተለያዩጊዜያት የተገነቡ ህገ-ወጥና ሠነድ አልባ ቤቶችን ህጋዊ ለማድረግ ትክክለኛና እውነተኛ መረጃን መሠረት ያደረገ አሠራርመዘርጋት ያስፈልጋል፡፡ እንዲሁም ባለጉዳዩ ከመሬት አስተዳደርናቀበሌ ፎርሙን ወሰዶ በመንደር ኮሚቴ እንዲያስሞላ የሚያደርገውን አሠራር ማስቀረትና ሁሉንም ህገወጥና ሠነድ አልባቤቶችን አንድ ጊዜ ጥናት በማካሄድ ትክክለኛ መረጃ ግብር የተገበረበትን፣ ውሃ፣ የመብራትና ስልክ የገባባቸውን ሰነዶች በማሰባሰብ ማጣራት ተገቢ ነው፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘም ቦታውየመኖሪያ ቤት መሆኑን በ GIS በማስተር ፕላኑ በማረጋገጥየካዲስተር ማረም ስራ በአግባቡ በመስራት በቀበሌና በመሬትልማትና አስተዳደር ባለሥልጣን ደረጃ መረጃ እንዲያዝ በማድረግትክክለኛ የማረጋገጥ ሥራ ማከናወን ይገባል፡፡ ከዚህም በተጨማሪየመረጃ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ አሰራር መከተል ያስፈልጋል::በመፍትሄነት የተቀመጠው አሰራር በየደረጃው ያሉ ሰራተኞችና ኃላፊዎች የሚሰሩትን ስራ ተጠያቂነት እንዳለው ጠንቅቀው በማወቅ እንዲሰሩና የስነምግባር ጉድለት ባለባቸው ሰራተኞችና ኃላፊዎች ላይ የሚወሰድ አስተዳደራዊ እርምጃ ለሌሎች አስተማሪ ስለሚሆን ህገ ወጥነትን ለመከላከል ያስችላል፡፡በጥናቱ በአስራ አንደኛ ደረጃ የተመለከተው ችግር አግባብያለው የቅሬታ አቀራረብና አፈታት ስርአት አለመዘርጋት ነወ።በመሬት አስተዳደር ላይ ተገልጋዩ ቅሬታውን የሚያቀርብበትናየሚፈታበት ስርአት በአግባቡ ስላልተዘረጋለት ለእንግልት እናለአላስፈላጊ ወጪ መዳረግና ማግኘት የሚገባውን አገልግሎት ህገወጥ በሆነ መንገድ ጥቅም ለማግኘት በር ይከፍታል፡፡ተገልጋዩ ቅሬታውን የሚያቀርብበትና የሚፈታበት ስርአት በአግባቡ እንዲዘረጋለት በማድረግ አግባብ ያለው የቅሬታ አቀራረብና አፈታት ስርአት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑን ጥናቱ ይጠቁማል:: ይህ አሰራር የሚታዩ ችግሮችን ወቅታዊ መፍትሄ ለመስጠት፣ አግባብ ያለው የቅሬታ አቀራረብና አፈታት ስርአት አድሏዊአሰራርን ለማስቀረት፣ አገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋ በማድረግግልጽነትንና ተጠያቂነትን የተላበሰ አሰራር እንዲተገበር ያደርጋል፡፡የመሬት ልማትና አስተዳደርን ለመምራት የወጡ አዋጆች፣ደንቦችና መመሪያዎችን በአግባቡ ለፈጻሚ አካላት አለማሳወቅጥናቱ የተመለከተው አስራ ሁለተኛው የአሰራር ክፍተት ነው፡፡የመሬት ልማትና አስተዳደርን በተመለከተ በርካታ አዋጅ፣ ደንብናመመሪያዎች ወጥተዋል፡፡ የመሬት ልማትና አስተዳደር ባለሥልጣን በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ዙሪያ የወጡትን አዋጆች፣ደንቦችናመመሪያዎች መሠረት በማድረግ ሥራውን በአግባቡ ለማከናወንፈጻሚ አካላት በቂ ግንዛቤ በማግኘት ማከናወን ይጠበቅባቸዋል ፡፡ወደ ገጽ 15 የዞረ27<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ም


ከ<strong>ሥነምግባር</strong> አውታሮችየፌዴራልና የክልል የ<strong>ሥነምግባር</strong> እና የፀረ-ሙሰና ኮሚሽኖች እናአግባብነት ያላቸው አካላት 8ኛ መደበኛ ጉባኤሰኔ 9-10 2002 ዓ.ምየፌዴራልና የክልል የ<strong>ሥነምግባር</strong>ና የፀረ-ሙሰና ኮሚሽኖች እና አግባብነት ያላቸው አካላት የጋራ ጉባኤ 8ኛ መደበኛ ስብሰባ ከሰኔ 9-10 2002 ዓ.ም በቤኒሻንጉል ጉሙዝብሔራዊ ክልል አስተናጋጅነት በአሶሳ ከተማተከናውኗል፡፡የህብረተሰብ ክፍል የተውጣጡ ሰዎችን በስልጠና፣አውደ ጥናትና ሌሎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች አማካኝነት መድረስ ተችሏል፡፡ የኤሌክትሮኒክስናየህትመት ሚዲያውን በመጠቀምም ከዚህ የሚበልጡ ዜጎችን መድረስና ስለኮሚሽኖቹ አላማዎች፣ ተልዕኮ፣ ሙስናን ከመከላከልና ከመዋጋት አንፃር ስለተከናወኑ ተግባራትና የተገኙ ውጤቶች ማሳወቅ ተችሏል፡፡ኮሚሽኖቹ ባዋቀሯቸው የሙስና መከላከል የስራ ክፍሎች አማካኝነትም በተለያዩ የመንግሥት መ/ቤቶችና የልማት ድርጅቶች ውስጥ በተመረጡ 51 አሠራሮች ላይ እንዲሁም በ3 መ/ቤቶች የአጠቃላይ አሰራርላይ ጥናት ተካሂዷል፡፡ በተጨማሪም 33 መ/ቤቶችበራስ ተነሳሽነት ለጀመሯቸው የአሰራር ሥርዓትጥናቶች ድጋፍ ተደርጓል፡፡ እነዚህ ሙስናን ከመከላከልአንፃር ቁልፍ ተልዕኮ ባላቸው ተቋማትና ተግባራት ላይየተደረጉ ጥናቶች ትግበራም ክትትል ተደርጎባቸዋል፡፡<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምበክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አህመድ ናስር የመክፈቻ ንግግር የተጀመረው ጉባኤ በበርካታ ጉዳዮች ላይ የመከረ ሲሆን ሀገር አቀፍ የፀረ-ሙስናትግሉ በአበረታች ርምጃ ላይ መሆኑን የሚያመላክቱውይይቶችና የልምድ ልውውጦች ተደርገውበታል፡፡ጉባኤው መደበኛ ውይይቱን የጀመረው ከጥር06 - ጥር 07 2002 ዓ.ም በጋምቤላ ከተማ በተደረገው 7ኛ መደበኛ ስብሰባ ወቅት የተላለፉ ውሳኔዎችን አፈፃፀም ሪፖርት በማድመጥ ነው፡፡ በቀረበውሪፖርት ኮሚሽኖቹና አግባብነት ያላቸው አካላት የትኩረት አቅጣጫን በመምረጥና ቅደም ተከተል በማበጀት የውሳኔ ሀሳቦቹን ለማስፈጸም ከፍተኛ ጥረትማድረጋቸውና ውጤትም ማስመዝገባቸው ተጠቁሟል፡፡በ2002 ሁለተኛ ግማሽ የበጀት አመት ኮሚሽኖቹናአግባብነት ያላቸው አካላት ያከናወኗቸውን ተግባራትየተመለከተ ሪፖርትም ቀርቧል፡፡ በዚህ የሪፖርትጊዜ ኮሚሽኖቹ የ<strong>ሥነምግባር</strong> ትምህርት ከማስፋፋት፣ከባለድርሻ አካላት ጋር የተመሰረቱ የተለያዩ መድረኮችንከማጠናከር፣ ሙስና ከመከላከል እንዲሁም የሙስናወንጀሎችን ከመመርመር እና ተጠርጣሪዎችን ለፍርድከማቅረብ አንፃር ያከናወኗቸው ተግባራት ተዳሰዋል፡፡በዚህ የሪፖርት ጊዜ 59,407 የሚሆኑና ከተለያየ28አቶ አህመድ ናስር የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰመስተዳድርበምርመራና የክስ የስራ ሂደቶችም በዚህ ግማሽዓመት የፌዴራሉና የክልል ኮሚሽኖች ከህብረተሰቡበርካታ ጥቆማና መረጃዎችን መቀበላቸው ተጠቅሷል፡፡ከነዚህ መረጃዎች መካከል 67 ከመቶው በኮሚሽኖቹየስልጣንን ክልል ውስጥ የሚወድቁ እንደነበሩ ተመልክቶ በመረጃዎቹ ላይ የተሰጡ ውሳኔዎች በዝርዝርተመልክተዋል፡፡ ከነዚሁ መረጃዎች መካከል በበርካታዎቹላይ ምርመራ ተጠናቅሮ ተጠርጣሪዎች ለፍርድ እንዲቀርቡ የተደረገ ሲሆን በዚህ ሂደትም 85 ከመቶ የሚሆኑት ተጠርጣሪዎች እንዲከላከሉ ተበይኖባቸዋል፡፡ እንዲከላከሉ ከተወሰነባቸው ተጠርጣሪዎች መካከልም 74ከመቶ የሚሆኑት ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው ከ1እስከ 20 አመት የሚደርስ እስራትና የተለያየ መጠን ያለው የገንዘብ ቅጣት ተጥሎባቸዋል፡፡ በክስናበምርመራ ሂደቱም በተጠርጣሪዎቹ ስም የተመዘገበንብረትና ጥሬ ገንዘብ የታገደና በኤግዚቢትነት የተያዘሲሆን ከክስ ሂደቱ መጠናቀቅ በኋላም በወንጀል ድርጊቱያፈሩት ሀብትና ንብረት እንዲወረስና ለመንግስት ገቢእንዲሆን ተደርጓል፡፡ በሪፖርቱ እንደተመለከተው በሂደት ላይ ያሉ ክሶች በመልካም ሁኔታ እየሄዱ ነው፡፡ እነዚህ ክሶች ውሳኔ ሲያገኙ የኮሚሽኖቹን በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው የተከሰሱ ግለሰቦችን ጥፋተኛ የማስባልና የማስቀጣት አሀዝ ከፍ እንደሚያደርገው ይጠበቃል፡፡በፀረ-ሙስና ትግሉ የባለድርሻ አካላትን ድርሻናአስተዋጽኦ ለማሳደግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራትምበሪፖርቱ አንድ ክፍል ተዳሷል፡፡ በተለያየ ደረጃከተመሰረቱ ጥምረቶችና የጋራ መድረኮች ጋር እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት አበረታች ውጤት እያስመዘገቡይገኛሉ፡፡ የክልል ኮሚሽኖች ተግባርና ሀላፊነቶቻቸውን በብቃት መወጣት ይችሉ ዘንድ ከፌሥፀሙኮ


ስምንተኛው መደበኛ ጉባዔ በአሶሳ ከተማ ሲካሄድበገንዘብ እና በሌሎች የአቅም ግንባታ መስኮች እየተደረገላቸው ያለው ድጋፍና እገዛም በሪፖርቱ ተጠቁሟል፡፡በዚሁ 8ኛ መደበኛ ጉባኤ ከለጋሾች በሚገኝ እርዳታና ድጋፍ አጠቃቀም የፀረ-ሙስና ተቋማት ሊኖራቸውየሚገባ ሚና ላይ አጭር የመነሻ ጽሁፍ ቀርቦ ሰፊውይይትም ተደርጓል፡፡ የዚህ ጉባኤ የመጨረሻ አጀንዳ የፌዴራል የ<strong>ሥነምግባር</strong> እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽኖችለክልል ኮሚሽኖች የሚሰጠውን ድጋፍና ከክልሎችጋር ስላለው ግንኙነት የተደረገ ውይይት ነበር፡፡ በውይይቱ ይህ እገዛና ድጋፍ ሀገር አቀፍ የፀረ-ሙስና ትግሉንበሚገባ እያገዘ መሆኑ ተጠቁሞ ወደፊት ትብብርና ድጋፍ የሚያስፈልግባቸው መስኮች ተለይተው ተቀምጠዋልየጋራ ጉባኤው በ6 ወር ሪፖርቱ እና በሌሎች አጀንዳዎች ላይም በተወያየበት ወቅት ኮሚሽኖቹ ተግባራቸውን በሚያከናውኑበት ወቅት ያጋጠሟቸውን ችግሮችምለይቶ በማውጣት የመፍትሄ ሀሳብ አስቀምጧል፡፡ የጋራጉባኤው በቀጣይ 6 ወራት ትኩረት አድርጎ ሊንቀሳቀስባቸው የሚገባ መስኮችም በሰብሳቢው በምክትል ኮሚሽነር አዲሱ መንግስቱ የቀረቡ ሲሆን በነዚህ የጋራ ነጥቦችላይም የጋራ መግባባት ተደርሷል፡፡ የትኩረት ነጥቦቹ፡-• በጋምቤላ ክልል አስተናጋጅነት በተካሄደውየፀረ-ሙስና ኮሚሽኖችና አግባብነት ያላቸው አካላትየጋራ ጉባኤ 7ኛ መደበኛ ስብሰባ በተወሰነው መሰረት በክልሎች የፀረ-ሙስና ጥምረት መመስረት፡፡የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ አዋጅ እና የምስክሮችጥበቃ አዋጅ ለማውጣት መንቀሳቀስ፡፡ የመረጃ ቴክኖሎጂን ለሙስና መከላከል ተግባር መጠቀምና ክልሎች በዘርፉ ልምድ መለዋወጥን አጠናክሮ መቀጠል፡፡እርዳታዎችና ድጋፎች በትክክል ለታለመላቸውተግባር መዋላቸውን ለማረጋገጥ ተግቶ መስራት፡፡• ሀገር አቀፍ የፀረ-ሙስና ትግሉን ወጥነትና ገላጭ በሆነመልኩ መቃኘት እንዲቻል በአዲስ መልክ የተዘጋጀውንየሪፖርት ማቅረቢያ ቅጽ ሙሉ በሙሉ ተግባር ላይ ማዋል፡፡• ክልሎች እርስ በእርስ የሚያደርጉት የመደጋገፍና የልምድ ልውውጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል፡፡ ከክልል ኮሚሽኖች አንፃር በተሻለ ደረጃ ላይ የሚገኘው የፌዴራል የ<strong>ሥነምግባር</strong>ና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የክልል ኮሚሽኖችን አቅም የመገንባትና ሌሎች ድጋፎች አጠናክሮ እንዲቀጥል፡፡የሚሉ ሲሆኑ እነዚህን ውሳኔዎች በብቃትና በውጤታማነት ለማስፈጸም ከፍተኛ ጥረት እንደሚያደርጉ የኮሚሽኖቹናአግባብነት ያላቸው አካላት የስራ ኃላፊዎች ቃል ገብተዋል፡፡በየስድስት ወሩ የሚካሄደው ይህ የፌዴራልና የክልልየ<strong>ሥነምግባር</strong>ና የፀረ-ሙሰና ኮሚሽኖች እና አግባብነትያላቸው አካላት የጋራ ጉባኤ በዋነኛ የስብሰባ አጀንዳዎች ከመወያየትና የጋራ ስምምነት ከመድረስ ባሻገርየሌሎች ብሄራዊ ፋይዳቸው የጎላ ክንውኖች ባለቤትእየሆነ መጥቷል፡፡ በክልሎች የልማትና መልካም አስተዳደር ጉዳዮች ላይ የልምድ ልውውጥ ማድረግ፣ የወንድማማችነትና የህትማማችነት ስሜት የሚያጎለብቱመድረኮችን መፍጠር እና የክልሎቹን ባህላዊና ታሪካዊእሴቶች በመጎብኘት የርስ በርስ ትውውቁ ጥልቀት እንዲኖረው ማድረግ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ በዚህ 8ኛ መደበኛጉባኤም ይህ ክንውን እየተጠናከረ መምጣቱን የሚያሳዩመርሀ ግብሮች ተካተዋል፡፡<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ም• በ5 አመቱ የስትራቴጂክ ዘመን በመሬት አስተዳደር፣በፍትህ አካላት፣ በትላልቅ የመንግስት ግዢዎችና ሽያጭ፣በሀብትና ንብረት ማሳወቅና ምዝገባ እንዲሁም በመንግስት ግብርና ገቢ አሰባሰብ ላይ ትኩረት አድርጎ መንቀሳቀስ፡፡• ከለጋሽ ሀገሮችና ዓለም አቀፍ ተቋማት የሚገኙ29


ኪነጥበብ<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምፀረ-ሙስና ኮሚሽን ‘‘ሙስና የዕድገት ፀር ነው’’ ‘‘ሙስናንእንፀየፍ’’ እና የመሳሰሉትን አይነት ፖስተሮች በየመሥሪያቤቱ እና በየአደባባዩ በምስል አስደግፎ ማቅረቡን ሳልፍ ሳገድም ተመልክቼአለሁ፡፡ የዛሬው ፀረ-ሙስና እንቅስቃሴ የኋሊት ወስዶ በትዝታ ባህር ቢያሰጥመኝ ማን ሊፈርድብኝ? ማንስለምን ብሎ ሊጠይቀኝ ሊሞግተኝ ይቻለዋል? ስል አሰብኩኝ፡፡በዘመነ ቀዳማዊ ኃይለስላሴ በአንድ መሥርያ ቤት ውስጥይሰሩ የነበሩ ሥራ ኃላፊ አንድን ሾፌር የ50 ብር ቤንዚን በማጭበርበሩ ይቀጡታል፡፡ የተቀጣው ሾፌር ለካስ በዘመኑ የአንድ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ሹም የሆኑ ባለሥልጣንን ዘመድነበርና ሄዶ አቤት በማለቱ የእሱ ሌብነት እንደ ዝና ተቆጥሮየቀጡትን የሥራ ኃላፊ ጨምሮ ሌሎች አራት አምስት የሚሆኑ ሰዎች እያንዳንዳቸው ከደሞዛቸው መቶ መቶ ብር እንዲቀጡ ያስደርጋል፡፡ ‘‘ጌታዋን የተማመነች በግ ላቷን ውጪታሳድራለች’’ ይሏል ይኸው አይደለም? ከትልቁ የሌባው ዘመድጋር መላተም ከተራራ ጋር እንደ መጋጨት የቆጠሩት ብዙዎቹ ካለአግባብ የተጫነባቸውን ቅጣት እያቃራቸውም ቢሆንአጣጥመው ለመዋጥ ዝም ማለትን ይመርጣሉ፡፡ ‘‘ጭራሽሌባ ይዤ በቀጣሁ የመቶ ብር ቅጣት ለምን ይጣልብኛል?’’ያሉትና የሾፌሩ የቅርብ አለቃ የሆኑት ሰው ግን ነገሩ ‘‘የሌባአይነደረቅ መልሶ ልብ ያደርቅ’’ ሆኖባቸው ባለሥልጣኑንበጃንሆይ ችሎት ከሰው ለመሞገት ይወስናሉ፡፡ እናም የድሮትምህርት ቤት ጓደኛቸውን ይፈልጉና ያገኙታል፡፡ የጓደኛቸውአባት በቤተመንግስት የንጉሱ እልፍኝ አሳላፊ ናቸውና ጓደኛቸው ጃንሆይ ፊት ቀርቦ የሚያስረዳበት ዕድል ያገኛሉ፡፡ በዘመኑእንግሊዞች በታዛቢነት ይገኙበታል በሚባለው ችሎት ባለሥልጣኑ እና ዘመዳቸውን በመቅጣቱ ተቆጥተው የቀጡት ሰውሙግት ይገጥማሉ፡፡ ከብዙ ክርክርና ውርደት በኋላ ባለሥልጣኑበቀዳማዊ ኃይለስላሴ ሃይለኛ ቁጣ ተዘልፈው ተገስፀው በክርክሩይረታሉ፡፡ አሸናፊውና ለእውነት የቆሙት የሥራ ኃላፊ ካለአግባብ የተጣለባቸውን ቅጣት እስከ ኪሳራው እንዲቀበሉ ይደረጋል፡፡ ይህ በሆነ ማግስት ባለሥልጣኑ ያሸነፏቸውንና ዙፋንድረስ ወጥተው በችሎት ሙግት የረቷቸውን የሥራ ኃላፊ በመኪና አስገጭተው ለመግደል ሙከራ ያደርጋሉ፡፡ ነገር ግን እኚህሃቀኛ ሰው ሲጓዙባት የነበረችው ቮልስ ዋገን መኪና ብትጨረማመትም ሰውዬው ግን ምንም አደጋ ሳይደርስባቸው ተርፈዋል፡፡ እኚህ ሰው ከዚያም በኋላ በተለያዩ መስሪያ ቤቶች ኃላፊነት ሲያገለግሉ የቆዩት ጉቦኝነትን እንደጠሉ ጉበኞችን እንዳጋለጡ እንደመከሩ በጓዳ እንዳስተማሩ ነው፡፡ ‘‘ወይ አይበላ ወይአያስበላ’’ እየተባሉ ጡረታ የወጡት አዛውንት ታሪካቸው መስጦኝ የዚህ ፅሁፍ ክፍል ሳደርገው የ85 ዓመት ዕድሜ ባለፀጋየ10 ልጆች አባት የ22 የልጅ ልጆች አያት ለመሆን በቅተዋልብለው ያጫወቱኝ በቅርብ የሚያውቋቸው ግለሰብ ናቸው፡፡ ሌሎች ሰዎችም ሰውዬውን በፀረ-ጉቦ አቋማቸው ሲያደንቋቸው ሰምቼአለሁ ቁጥራቸው አይብዛ እንጂ መቼም ቢሆን መልካም ሰዎች በእንደዚህ አይነቱ ሁኔታ እንኳ መገኘታቸውን ልብ ይሏል፡፡በዘመነ ደርግ ጉቦ የእድገት ነቀርሳ ነው ከመባል አልፎአንድ ሰሞን ዘመቻ ተከፍቶበት እንደነበር ትውስ ይለኛል‘‘የወር ደሞዙ 500(አምስት መቶ) የቀን ወጪው 200(ሁለት መቶ) ሎተሪ አልደረሰው ውርስ የለው ይህን ሰው ማንእንበለው?’’የሚል መልዕክት ያዘለ ነበር በስዕል የተደገፈውየያኔው ፖስተር፡፡ ቀልደኛው ሕዝብ በባዶ ቦታዎች ላይ30እኛ እና ሙስና /ወግ/የወቅቱን ከፍተኛ ባለሥልጣናት ሙሉ ስም ገጠገጠበት፡፡ ኋላምፖስተሩ ከተለጠፈበት በአፋጣኝ ተነሳ፡፡ ለምን? ተብሎሲጠየቅ ሕዝቡ መልሱን ስለሞላ ፈተናው ሊታረም ይሆናልእየተባለ ሁሉም ተዘባበተበት፡፡ በዚያ ሰሞን ሙሰኞች በጋዜጣ ይወጣሉ በቴሌቭዥን ይታያሉ በሬድዮ ይደመጣሉ፡፡የገዙት ቤት መኪና መወረሱን ብቻ ሳይሆን መሸታ ቤትገብተው አሸሼ ገዳሜ ሲሉ በአዝማሪ ግምባር ላይ የለጠፉትባውንድ ሳይቀር መታወቁ እና ተመላሽ መሆኑ ለሕዝብይፋ ሲደረግ አይቼ ሰምቼ ጉድ ጉድ ብዬ እንደነበር አልረሳሁትም፡፡ ዘመቻን ዘመቻ እየወለደው የቀደመው እስኪረሳ ድረስ፡፡ጎበዝ ሙስና አደራረግ አከዋወኑ እንደ ሥልጣኔ እና ዘመኑእየተዥጎረጎረ ይኸው ዛሬ ላይ ገጭ አድርጎናል፡፡ የበግ የፍየልሙክት ከውስኪ ከአረቄ ጋር ተሸክሞ እንደድሮው ክርፍፍ ፈራተባ እያለ የየቢሮክራቱን እና በየደረጃው ያለውን ባለሥልጣንደጅ የሚጠና ባለጉዳይ ዛሬ ዛሬ ላናይ መቻላችን እውነት ነው፡፡ለነገሩ የመኪና ኮፈን ካስፈለገ ለበግና ለአረቄ መች ይጠብና?ዛሬ የኪስ የጠረጴዛ ስልኩ፣ ፋክሱ፣ ኢሜል፣ ኢንተርኔቱ የሃዋላ አገልግሎቱ እና ሌላው ሁሉ ሙስናን አዘምነው አቀላጥፈውታል፡፡ እሳት የላሱ የአደባባይ ደላሎችም ሰልጥነውበታል፡፡ጠዋት ጠብ ጠብ እያለ እና እየተጀነነ ወደ ሥራው አርፍዶ የሚገባው ሠራተኛ በዘር በሃይማኖት በቋንቋ በወንዝልጅ በአምቻ ጋብቻ ወይም በምልጃና እጅ መንሻ ካልሆነጉዳይ የፈጸመ የማይመስለው አደራ በላ ሁሉ ሲታሰብ ስለዕድገትም ሆነ ስለልማት ከማሰባችን በፊት ሙስናን አስቀድመን በማይንሰራራበት ሁኔታ አንገት ማስደፋት ይኖርብናል፡፡በየትኛውም መሥሪያ ቤት ሠራተኛ ሲወጣ ግር ብሎ መውጣቱንና ሲገባ አንድ አንድ እያለ እንደሚዘልቅ ብቻ ሳይሆንከሰዓት ቀድሞ በመውጣት ጉዳይ የመሳሰለውን ነገር ሁሉታዝባችሁ ታውቃላችሁ? ለሥራ የተሰጣቸውን ብዕርና ወረቀትለልጆቻቸው መማሪያ የበጀቱ አባወራዎች ወይም እማወራዎች ቢኖሩ ሰራተኛ ከወጣ በኋላ በመሥሪያ ቤቱ ቅጽር ግቢያደገውን ሳር አጭዶ ከምሮ የሚወጣ የጥበቃ ሠራተኛ በመንግስት መኪና እቃ እያጓጓዘ ሽቀላ የጀመረ ዐይን አውጣ ሾፌር ቢያጋጥማችሁ ሙስናው በሚሊዮን ብር ካልተሰየመ በቀርእነዚኛዎቹ ከመልከስከስ አልፈው አልሞሰኑም ትሉኝ ይሆን?የሚያውቀውን ሰው ሲያገኝ በፈገግታ ተጥለቅልቆ ሞቅ ያለሰላምታ ሰጥቶ ሳይፈተሽ ወደ መሥሪያ ቤቱ ቅጽር ግቢ የሚያስገባው ዘበኛ ድኻ እንደ አቅሙ በሥልጣኑ አለአግባብ አይጠቀምም? አይባልግም እንዴ! ማለቱ ይሆን? ሊያሰኘን ይችላል፡፡የሙስና ጉዳይ አሁን በደረስንበት ዘመንና ወደ ዕድገትበምናደርገው እንቅስቃሴ ላይ የተደቀነ ትልቅ ጋሬጣ መሆኑየጎላ ነው፡፡ ‘‘የብዙዎችን ጥቅም በጥቂቶች ከመለወጥ የበለጠምን ወንጀል አለ?’’ ያለው ማን ነበር? ሃሣቡ ሳይጠፋኝ ተናጋሪው ተሰወረብኝ፡፡ አዎ ብዙዎችን ለሥራ አጥነት ለሴተኛአዳሪነትና ለመሳሰሉት ሌሎች ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ እናኢኮኖሚያዊ ቀውሶች የሚዳርገው ሙስና በተለይ ዛሬምየድኻ አገራት ነቀርሣ እንደሆነ አለ፡፡ እንዲህ የሆነው እንደዚህ ስለሆነ ነው እያልን በምንሰጣቸው በርካታ ምክንያቶችሣቢያ ሙስና ከመቀነስ ብሎም ከመጥፋት ይልቅ ፋፍቶ እያማረበት እንዲሄድ መፍቀድ የለብንም፡፡ በታሪኬ ቀዳሚ ክፍልእንዳስነበብኳችሁ እምቢ ማለት የምንችል ይመስለኛል፡፡ እኛበትንሹ አቅማችን የምናደርገው እኮ ሲጠራቀም ትልቅ


<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምይሆንና ሚዛኑ ወደ እውነት፣ እምነትና ሀቀኛነት ያዘነብላል፡፡ይህም ለኔ እንዲሁ ነው የሚሰማኝ በሉ እባካችሁ እንበርታ!በቅርቡ ወደ ድሮ ሰፈሬ እናቴን ለመጠየቅ ብቅ ብዬ ነበር፡፡አብሮኝ ያደገ አንድ የማውቀው በመንግስት ሥራ የሚተዳደርሰው ነበር እና ስለጤንነቱ የሚቀርቡትን ጠየኩኝ፡፡ ‘‘ኸረ እሱዛሬ ብትጠራው አይሰማም’’ ተባልኩኝ፡፡ እንዴት? … በሚባልሰፈር ባለ 3 ፎቅ ቤት፣ 2 የጭነት መኪና፣ 1 የቤት መኪናገዝቶ ወደ ብልጽግና ጎራ ከተቀላቀለ እኮ ቆየ ተባልኩ፡፡ ያ ሰውዲፕሎማ ብቻ ያለው ሠራተኛ ነበር፡፡ ኋላም አጋጥሞኝ መኪናይዞ አገኘሁት የአካባቢው ሰዎች ካሉኝ ከፊሉን አረጋገጥኩኝ፡፡የወር ደሞዙ አልብቃቃ ብሎት ቅርብ ሩቅ አበዳሪዎችን ከወርወር ከዓመት ዓመት ሲማፀን የነበረ ሁሉ በሙስና ጀት ተመንጥቆ ባለቪላ ባለ ውድ ዋጋ አውቶሞቢል ችግር ኮሽ የማይልበት የተትረፈረፈ ኑሮ ባለቤት ሲሆን ሚስት ባሏን ባል ሚስቱን ከየት አመጣሽው ከየት አመጣኸው? አይባባሉም እንዴ?ብሎ የሚጠይቅ የዋህ ቢጤ የዚህ ዘመን ሰው ቢኖር ዕድሉን ያላገኘ ለመዝረፍ ተመኝቶ አጋጣሚው እንደሰማይ የራቀበት ተደርጎ የሚቆጠርበት ጊዜ ላይ ነው ያለነው፡፡ ማን ማንንይቆጣል? ይመክራል? ይገስፃል? ድሮ ቀሩ ተብለው የተዘነጉትክፉውን ነገር እየተፀየፉ ከመልካም ነገር ጋር የመተባበር <strong>ሥነምግባር</strong>ና ሞራል ከህብረተሰባችን ወዴት ተወሰዱ? ብሎ ማሰብናመጠየቅ ጊዜው ዛሬ ቢሆንስ? ጉቦ እኮ ቢዝነስ የተባለበት ዘመንነው፡፡ ዛሬ ዛሬ አለቃ እና የበታች ሰራተኛ የሥራ ሰዓት ሰርቀው ባለጉዳይና የሥራ ውዝፍ እያንቃቁ አፍ ለአፍ እያወሩጫት የሚቅሙባቸው የከተማችን አደባባዮችና ሥርቻዎች በርካቶች ናቸው፡፡ የችሎታ የዕውቀት የደሞዝ ማነስ ለሙስና በርከፋቾች ናቸው ቢባሉና ቢሻሻሉም እንኳ ባለው የማይረካ ሰርቼያገኘሁት ብቻ ይበቃኛል የማይለው የሰው ልጅ ስጋ ከሙስና እንደዋዛ መፋታት የሚቻለው አይመስልም፡፡ አካሄድና ሁኔታው፡፡ቤተሰብ፣ ትምህርት ቤት፣ የሃይማኖት ተቋማት በተቀናጀ እና ሆን ተብሎ በዕቅድ ወደሚተገበር እንቅስቃሴውስጥ ገብተው የ<strong>ሥነምግባር</strong>ና የሥነ ዜጋ ትምህርትማቀጣጠል ካልቻሉ ዕድሮችና የዕቁብ ማማዎች የበኩላቸውንካላስተዋሉ እና አለን ካላሉ ያልበላው በበላው እየቀና ምራቁን የሚውጥ ከመሰለ ዛሬ የሚታየው የሙስና ሰደድ ኢትዮጵያን እጅጉን ከማዳከም የሚያግደው አንዳች ነገር አይኖርም፡፡ ‘‘ያዳቆነ ሰይጣን ሳያቀስስ አይለቅም’’ ይሆናል እንጂ፡፡የምኖረው በተቀራረበ መንደር ነው፡፡ አንደ ቡና ባህላችን እንደ ሰርግ፣ ልደት፣ ክርስትና፣ በዓላት በመሳሰሉት ማህበራዊግንኙነቶች ዙሪያ አብዝተን እንሳተፋለን፡፡ ግን ለምንድነውግንኙነታችን መልካም ለመስራት አጥፊን ለማረም የማይሆነው? በጉቦ በወጣ መንጃ ፈቃድ የምንሞተውም የምንገድለውም እኛው ነን፡፡ ለምን? በታክሲ ተሳፍረን ስንጓዝ ትርፍመጫኑን የምናወግዝ ስንቶቻችን ነን? ወይም የሚያወግዙትን የምንደግፍ የምንተባበርስ ምን ያህል እንሆናለን? ማህበራዊ ምንቸገረኝነቱ በብዙ ሁኔታዎች የሚገለጽ ቢሆንም እንደከተማዋ ጽዳት ያሳበቀብን ግን የለም፡፡ አንዱ ቆሻሻ አምጥቶአደባባይ ሲደፋ ጽዳት ተቆጣጣሪ ወይም ፖሊስ ካልሆንን ስንቶቻችን ይመለከተናል ብለን ድርጊቱን ለመቃወም እንቆማለን?ለታክሲው ትርፍ መጫንና ከታሪፍ በላይ ማስከፈል ይከላከሉልናል ብለን የምናስባቸው ትራፊክ አሊያም መንገድ ትራንስፖርትን እንጂ ቀዳሚዎቹ እኛው ተጠቃሚዎቹ መሆናችን ማንሊያስረዳን ይገባ ይሆን? ብሎ መጠየቅ ጤናማነት ይሆናል፡፡ግን በፍጹም አይቼም ሰምቼም አላውቅም እና ነገረ አካሄዳቸው ‘‘የትም ፍጭው ዱቄቱን አምጭው’’ ይሉትን ብሂልሥራ ላይ እያዋሉት ነው ለማለት ቢዳዳኝ ያስፈርድብኝ ይሆን?እከሌ ግትር ነው፣ ጨቅጫቃ ተመሳስሎ ማደር የማይሆንለት ነገር ከያዘ የማይለቅ አጉል ሃቀኛ እንዲሁ ሲንገታገትከጓደኞቹ በታች ሆኖ ቀረ … ከተባለ ያ ሰው ጉቦ እምቢ!የሚሆንበት ሁኔታ ገጥሞኛል፡፡ በሙስና ቪላ የገነቡ በውድና ቄንጠኛ አውቶ ሞቢሎች የሚምነሸነሹ ገንዘብ የሚረጩትጎንበስ ቀና ሲባልላቸው ከላቤ ውጪ አልበላም በፊቴ ወዝ ቃሉእንዳዘዘኝ ሰርቼ እኖራለሁ ያሉት ግን ከቤታቸው ጀምሮየተናቁበትና የተገፉበት ሁኔታ ጎልቶ መታየቱን ስንቶቻችሁታዝባችሁ ይሆን? ጉቦ የማይበላ የማያስበላ ዕውቀት ጎደለው ለራሱ እና ለቤተሰቡ የማይጠቅም የማያሳልፍ የማያልፍለት መናኛ ፍጡር ተደርጎ መቆጠሩ በየመንደሩ የገዘፈ ትርኢት ሆኖአል፡፡ እርግጥ ነው ማናችንስ ብንሆን ሙስናን በመፀየፋቸው በአደባባይ በቴሌቭዥን፣ በሬድዮ፣ በጋዜጣ ቀርበውየተሞገሱ ተመስግነው የተሸለሙ ስንት ሰዎችን እናውቃለን?ከጠቅላላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አንጻር ሲታይ ጥቂቶች ሞሰኑ፡፡መዘንጋት የሌለብን ግን ጥቂት እርሾ ሊጡን ታቦካዋለችናእነዚህ ጥቂቶች ብዙዎቹን ለጎስቋላ ኑሮ እና ፍትሀዊ ያልሆነ የሃብት ክፍፍል መዳረጋቸው የማይቀር ነው፡፡ በጉዳዩ ላይከአሁኑ በጥብቅ ካልታሰበና መፍትሄ ካልተበጀ፡፡ ከጥቂትወራት በፊት ለአንድ ዶክመንተሪ ፊልም ሥራ አንዲት አምባሻሸጣ ሁለት ልጆቿን የምታሳድግ ምስኪን እናት ‘‘አሁን ይሄየምትኖሪበት ሠፈር ምን ተብሎ ይጠራል’’ ተብላ ስትጠየቅ‘‘ሙስና ሰፈር’’ ስትል በእርግጠኝነት መመለሷ ትዝ አለኝ፡፡ይህ ትልቅ የማንቅያ ደወል ይመስላቸዋል፡፡ ይህች ሴት ያለችውን ሌሎችም ብዙዎች የሚሉት ነው፡፡ ነገር ግን ራሳችንን የመፍትሄው አካል አድርገን የምናየው ስንቶቻችን ነን? የማይገባቸውን አግኝተዋል፣ መሆን የማይገባቸውን ሆነዋል፣ ማድረግየማይገባቸውን ፈጽመዋል የምንላቸውን የመንግስት ባለሥልጣኖች፣ ነጋዴዎች፣ የማህበረሰብ መሪዎች አሳልፎ ለመስጠት ከኛየቀረበ ከቶ ማን ሊኖር ይችላል? ምክንያቱስ? ብትሉኝ አብረንእየሰራን አገልግሎታቸውን በመሻት ቢሯቸው እንሄዳለን ወዘተ.የሕግ የበላይነት፣ መልካም አስተዳደር፣ ልማት ኢንቨስትመንትን እና ሌሎች አንኳር አንኳር አገራዊ ጉዳዮች መሃልሁሉ እንደ ጆከር ሆና እየገባች አጫዋች የሆነችውን ሙስናን ማሸነፍ ይገባናል፡፡ ‘‘ዕውቀት የአእምሮ ዓይን ነው’’የሚሉት እንግሊዞች ናቸው፡፡ ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በየደረጃውህብረተሰቡን ለማስተማር እንዴት እየሰራ ይሆን? በዚያ ሰሞንበወርቅ ስም ብሔራዊ ባንክ ተሞሽሮ የተገኘውን ባሌስትራሚስጥር ፀረ ሙስና ኮሚሽን እንደምን ደረሰበት ምንስ ርምጃወሰደ? የከተማ ቦታን በወረራ በሕገወጥነት የሰጡ ያሰጡ የተቀበሉና ያቀባበሉትን ግለሰቦች ጉዳይስ የኮሚሽኑን ተግባራትበቅርበት መከታተል መልስ ሊሰጠን ስለሚችል እስቲ ቀረብብለን ኮሚሽኑን ምን ሰራህ ምንስ ውጤት ተገኘ? ብለን እንጠይቀው ምላሹ ምስጋና የሚገባው ከሆነ ምስጋና በጎደለውለመሙላት ደግሞ ምክራችንን ለመለገስ መልካም አጋጣሚይፈጥርልናል፡፡ ስለ ሙስና ስንቱ ተነስቶ ስንቱ ይጣላል? ጊዜ፣ወረቀት፣ ቀለሙስ በዋዛ ይበቃል? እስቲ አገርን ቁልቁል ከሚጎትተው ከሙስና ሃሳብና ተግባር ይሰውረን በቸር እንክረም፡፡<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምእንደየ እምነታችን ሰርተን ካገኘነው አሥር ከመቶ አስራት አንድ ከመቶ መባ ወይም ዘካ … ለቤተ እምነት እንሰጣለን፡፡ የእምነት አባቶች አንድ ሰው በላቡ ሰርቶ ያገኘውካልሆነ በሙስና ካግበሰበሰው የራሱ ካልሆነ ገቢ ለእግዚአብሔር ቤት ሥራ አስራት መክፈሉ መባ መጣሉንና ዘካማውጣቱን ተቃውመው ሠላማዊ ሰልፍ መውጣታቸውን31


Volume 9 Number 4 July 2010content<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምEditor’s note ......... 32News ................ 33Focus ................. 34Ethics July 2010Guest ................ 37“We have been executing wide-ranging activitiesto curb illegal activities in the land administrationsector”His Excellency Ato Mekuria Haile,General manager, Addis Ababa City Administration.Quarterly Published by the EthicsEducation and Communication Affairs Directorate of The FederalEthics and Anti-Corruption CommissionTel. - 011-5529100P.O.Box - 34798/99Fax - 011-5536987E-mail - feacedu@ethoinet.etWeb site - www.feac.gov.etAddis AbabaEthiopia32


Editor’s NoteEthics July 2010This issue (Vo.9 No.4) of Ethics is the last one for this Ethiopian budget year. The teamin charge of producing this quarterly magazine as usual tried its best to collect and presentnews and articles on the national combat against corruption.Corruption in the land administration sector especially here in the capital Addis and itsoutskirts has been the talk of the town for long. We hear people involved in the illegalprovision and ownership of land brought to the court, found guilty and received variousterms of imprisonment and fines. The Federal Ethics and Anti-Corruption Commission accomplishedvarious preventive and corrective measures. However, much is expected fromthe City Administration. In this issue we have invited His Excellency Ato Mekuria Haile,General manager of the Addis Ababa City Administration, to tell us about the extent of theproblem, measures being taken by the Administration, the improvements observed and onother related issues where the administration working jointly with the FEACC.Our other column “Focus” is also devoted to this similar issue. We have also selected themajor accomplishments of the Commission and made them available in the News Section.Don’t forget to visit our website www.feac.com for detailed information on this selected newsitems and other accomplishments of FEACC.<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምWe hope you enjoy your reading and send us feed backs and suggestions that add a lotto the improvement of our quarterly Ethics.33


NEWS<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምCommissions hold 8th Regular JointConferenceThe 8th Regular Joint Conference of the Federaland Regional Ethics and Anti-Corruption Commissionsand other judicial organs held in Assosatown, capital of the Beneshangul-GumuzRegion from June 16-17, 2010.Opening the conference, Deputy Commissionerof the Federal Ethics and Anti-Corruption Commissionof Ethiopia (FEACC), H.E. Ato AddisuMengistu said utmost efforts should be exertedto make sure that corruption and unethical conductsdo not impede the country’s developmentendeavor. He said the fight against corruptionshould also be harmonized with the ongoingspeedy and all rounded development of the nation.He also expressed the Commission’s readinessto share its experience in the designing ofthe five-year strategic plan to Regional Ethicsand Anti-Corruption Commissions in a bid toenable the Commissions be successful in theirfight against corruption.The conference heard the report about theimplementation of the decisions passed duringthe 7th Regular Joint Conference. It has alsoevaluated the national anti-corruption activitieshalf budget year (2009) report.The conference also deliberated on the supportbeing provided by the FEACC to Regional Ethicsand Anti-Corruption Commissions and itsrelationship with them, it was learned.The conference participants discussed andadopted a five points resolution. The participantsreached on consensus about the establishmentof Anti-Corruption Coalition in Regional States,making efforts for the enactment of the proclamationsproviding for the registration of assetsand properties of public officials and protectionof whistleblowers.They have also agreed to share experience in thearea of utilizing information technology in theanti-corruption struggle and launch activitieswith a view to making sure that the donationsprovided by donors is used for the intended purpose.110 corruptors receive jail terms in threemonths timeIn the last three months alone (February to April,2010), Courts handed out jail terms to a total of110 corrupt personswho had been charged by theFederal Ethics and Anti-corruption Commissionof Ethiopia (FEACC) for committing corruptioncrimes in various periods of time.The jail terms given range between 1 and 21years and the fines handed out to them fluctuatebetween 3,000 and 50, 000 Birr.The offenders were held culpable for abuse ofpower, forgery, traffic in official influence, maladministration,acceptance of undue advantages,bribery, and breach of trust.Chief among the culprits were the former GeneralManager of the Land Development Officewith the Kolfe Keranio Sub-City , Wond WosenAlemu Bekele, and the former Finance Officerwith the Judgement Execution Department of theCont’d on page 40Ethics July 201034


Ethics July 2010DEVELOPMENT, INFRASTRUCTURE ANDTHE NEED TO CURRBING CORRUPTIONThe Construction Sector assumes a central positionin any nation’s development endeavors. The sectorcomprises of construction activities in the Housing(private and public), Non-residential buildings forthe health and education sectors, industrial and commercialconstruction, transportation (both land andair), energy, water supply etc. Development in thisvast and diverse sector is the major expressions of acountry’s status in the global economic order whileat the same time the basis for further developmentendeavors. Due to this central role, infrastructure developmentis the world’s leading sector in its capitalflow, the number and kind of employment created, therapidly developed methods, techniques and technologytransfer.When we come to the present and shared concern ofthe global community we will find this sector evenmore important. It is underdevelopment, inequalityand poverty which have remained in the agenda ofthe global community in general and leaders in particular.After a series of conferences and summitsheld for decades, in September 2002, world leadersadopted a significant document “The United NationsMillennium Declaration” expected to bridge the hugegap between the poor and rich nations of our globe.It is the most valuable document ever produced andtrusted to bring an end for the suffering of the world’spoor as far as its practical implementation is carriedout as stated and with in the specified time. The declarationusually termed as, the Millennium DevelopmentGoals (MDGs), is a set of eight globally agreeddevelopment goals expected to be fulfilled in 2015.These goals include: Eradicating extreme poverty,Achieve Universal Primary Education, Reduce ChildMortality, Improve Maternal Health, Combat HIV/AIDS, Malaria and other diseases and other closelyrelated issues to poverty.These eight MDGs are very much intertwined andtheir attainment demands a concerted effort. In addition,one very important factor serves as a centralrole player, the construction sector. To achieve eachone of the MDGs, it requires recognizing the role ofinfrastructure development and it has to be made partof the plan. In one hand it is the means to reach thesegoals and in the other it is a goal by itself. Betteraccess to infrastructure services means improvingchildren and maternal health. Roads facilitate bettertransport services which make access to health,education and other services easier. With these conditionsat hand, staffing and smooth operations of theinstitutions will be more feasible. To achieve universalprimary education bringing the service nearerto children is badly demanded. When this MDG isachieved, besides maximizing the literacy rate, manyof the health problems responsible for child mortality,maternal health and other serious health problems getpart of their remedy. The logic here is many of thehealth problems that lead to death are preventable andfor these educated and aware citizens are seriouslyneeded. For all these the construction of roads, healthstations, schools, administrative and other multipurposebuildings has to be planned and properly implemented.Development in the infrastructure sector necessitatesthe fair and increased flow of capital to every cornerof the country and the employment of a large numberof people, most of whom are expected to be locals.Increase in the income of citizens, training in variousvocations of the construction sector and eventuallyhaving a trained and a decently paid work force willcome out of this effort. In this way we can say a lotabout the relation between the MDGs and their closeattachment to the infrastructure development.The World Bank and other global institutions, importantallies of this global partnership to reduceextreme poverty has clearly understood this factorand accomplish a major adjustment on their fundingpolicy. The World Bank especially underpinned thecrucial position infrastructure plays in bringing incomegrowth and human development. So, it is in theBank’s convention that poor people in the developingnations should have access to basic services that camethrough infrastructure development.Due to all these, infrastructure development remainsto be a global challenge. Especially in the developingpart of the world where these things are still underdeveloped,higher commitment and expendingis expected. Besides the urge to fulfill the MDGs, adramatic increase in urbanization, economic and pop-<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ም35


<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምulation growth as well as increasing trade relationsbetween nations, demands hugely expanding infrastructuredevelopment. An estimate from the OECDsuggests that annual investment requirements just onthe 5 sectors: telecommunications, road, rail, electricityand water requires around an average of 2.5% ofworld gross domestic product (OECD Policy Brief,2008). When we add the problem of more than 1 billionpeople (this number expected to rise to 2 billionin 2030) currently living in slums and inner cities, theportion of the global GDP the sector demands willbe very high. According to studies by internationallyreputed organizations, the demand attributed to thisdemographic and underdevelopment factors requiresan annual investment of over US$ 2 trillion each yearover the next 20 years.The huge capital involved in the sector and contractslarge in number and complex in nature givento construction firms make the sector a bit demandingto manage and control. As a result, the sector iscategorized among the most vulnerable economicactivities both in the developed and developing nations.So corruption and related malpractices are themajor concerns of the construction sector. Defectiveprojects, unnecessary delays, theft and subsequent increasein cost are threats the sector is facing. A 2006study by the American Society of Civil Engineersestimated that 10% or US$400 billion spent on constructionworldwide is lost to corruption. The OECDreport confirms that corruption in public constructioncontracts was widespread, and the cost even exceeds20% of the Contract value. (CoST News letter).This corrupt practice manifests in all phases of theconstruction process: during project planning, projectdesign, tendering and project implementation. As thebribes are paid for some thing in return for the contractorsthat maximize their interests, a lot of damageis inflicted in the construction projects that exceed theamount paid in bribes. The use of construction inputsbelow the required amount as well as quality is themajor problem that could be sighted here. Buildingsthat collapse and roads that break up before their duetime; the delivery of pure water, health and educationservices fallen short of their target to some extent attributedto corruption and other improprieties in thesector.The global community has taken this problem veryseriously and a lot of practical actions have beenstarted to overcome this grate problem. The WorldBank-IMF report that warns some countries mayfall short of the Millennium Development Goals isadditional drive to pursue proper majors to counter36corruption in the infrastructure development. The majordevelopment in this regard is the UN ConventionAgainst Corruption (UNCAC) which come to forcein 2005. This convention is exceptional in many instanceswhen compared to other international instrumentsof fighting corruption. It has the most extensiveprovisions on the ways, means and standards for preventingcorruption in the public and private sectors. Italso criminalizes a wide range of offences. The otherand most interesting aspect of the UNCAC is its provisionsof assets recovery that works globally.The OECD Convention on Combating Bribery ofForeign Officials in International Business Transactionswhich come to force in 1999 is another developmentin this regard. This Convention imposes criminalsanctions on international business organizationsconvicted of bribing officials to win contracts. Thisgreatly prevents corruption at all phases of the constructionprocess and avoids damages that encounterdue to improperly handled contracts. There are alsoother regional conventions that assist efforts to fightcorruption in the sector.Construction Sector Transparency initiative (CoST)is a specialized international initiative introduced toincrease transparency and accountability in the constructionsector. CoST, is an initiative supported byThe UK Department for International Development(DFID) and the World Bank. According to the objectiveput forward, the initiatives aims to enhance theaccountability of procuring bodies and constructioncompanies for the cost and quality of public sectorconstruction projects. In short it is a proper responsein terms of fulfilling the millennium demand for theinfrastructure development, effectively combatingcorruption in the sector and make sure all the resourcesallocated effectively serve this purpose. A lot ofcountries and donors are joining this very importantinitiative.The other key component in combating corruptionin the construction sector comes from the conceptof National Integrity System (NIS) developed andintroduced by Transparency International (TI). TI isa non governmental organization fighting corruptionworld wide. NIS is based on the notion that the societybecomes resistant to corruption when the relevantinstitutions are present and properly functioning inthe country. These institutions constitute the parliament;the executive; independent judiciary; the civilservice; the law enforcement agencies; the civil society;the private sector and the media.Ethics July 2010


Ethics July 2010All these initiatives need member states dedicated forthe cause and work hard to see their practical implementation.At this stage there are a lot of positive signalsand progresses. The number of countries signingthe conventions or becoming party to one or more ofthese initiatives is increasing each year. We are nowvery much used to forums and international conferencescalled to discuss on corruption, its effects andthe need for international cooperation to prevent it.Ethiopia is among countries expected to exert a lotof efforts for infrastructure development. The pastfew years exhibited such efforts in the developmentof road networks, telecommunication, water and irrigationprojects, power generation and other infrastructuredevelopments. As official reports reveal thecapital allocated for the sector is ascending every yearand even citizens who used to be remote to such servicebegan to reap the fruits of this development.As the case in other countries, huge capital allocationhas to be followed by proper control mechanism. Thegovernment of the Federal Democratic Republic ofEthiopia has identified corruption among the majorthreats to the democratization and development programsof the country. Various mechanisms of curbingcorruption in the infrastructure and other sectors vitalto our development endeavors has been developedand put in to practice. The first and important stepis the establishment of a federal agency, The FederalEthics and Anti-Corruption Commission, to deal withcorruption and related mal practices. The country’spenal code has also been amended and made to includenew provisions on corruption. Other relevantlegal instruments of fighting corruption are also madeavailable now.corruption laws are practical responses to this globalconcern. The government and its institutions workingfor this cause have interred agreements and createclose and cooperative relations with internationalorganizations like Transparency International (TI),Constructions Sector Transparency Initiative (CoST),the United Nations Development Program (UNDP).The support from these international organizationshas been valuable to implement the programs andpolicies designed.The UNDP through its Democratic Institutions program(DIP) is closely working with the Federal Ethicsand Anti-corruption Commission. Many of the publicawareness raising programs, the media campaigning,and the cooperative and consultative forums FEACCcreated with many and relevant stakeholders are financiallyand technically supported by the DIP. Acurrently started cooperation with CoST is expectedto create an opportunity for a much needed technicalassistant to prevent corruption before it becomesan impediment to the development in the sector. Theinitiative has already opened its liaison office with inFEACC’s premises and started its operations. As stated,Supporting Economy Growth and Poverty reductionby Increasing Transparency and Accountabilityin Government Funded Construction Projects is theobjective of CoST. The massive construction projectstaking place through out the country will not beeffective with out putting in place this governanceprinciple stated in the objective of CoST. So, it is possibleto say that this cooperation is timely and expectedto assist our endeavor in the area to a great extent.<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምBesides, Key organizations in the development of theinfrastructure sector has been made to evaluate theirprevious practices, identify their shortcomings andespecially to pin point loopholes conducive to corruptionand come up with a new and much improvedwork procedures. Together with the program to enhancethe capacity of the oversight bodies which hasgot proper attention these days, the infrastructure sectorwill be in a position to guarantee the success welonged to see.In terms of international cooperation, Ethiopia isa signatory to the UNCAC. Through the adoptionof this international instrument to curbing corruptionand others like the AU Convention to Preventingand Combating Corruption, we are party to theinternational initiative and contribute our share. Theinstitutions built, the policies, strategies and the anti37


Guest“We have been executing wide-ranging activities tocurb illegal activities in the land administration sector”His Excellency Ato Mekuria Haile,Geneal manager, Addis Ababa City Administration.In this issue of Ethics we interviewed GeneralManager of the Addis Ababa City Administration,Ato Mekuria Haile on the illegal land provision,ownership and related issues in the city.<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምEthics:- It has been observed that, after 2005 there hasbeen an extensive illegal land provision and ownershipin Addis Ababa. What is the reason behind this?Ato Mekuria:- following the result of the 2005 nationalelection where the majority of seats won by theopposition political coalition, some people tried touse this moment for their own benefit through imposingunjust and negative impact on the land administrationsector. These people did that by establishingvarious networks with persons in the Administration.The problem was especially visible in the real estatesector. At that time a huge amount of government andpublic property was embezzled by illegal housing constructionassociations and land was illegally transferredto individuals using investment as a disguise. In general,in addition to the attitude of the people involvedin the act, lack of transparency and accountability areresponsible for the problem observed in the sector. Therewas no working procedure which clearly provides answersto questions related to service delivery such as,how should the administration execute every affair?What is expected from customers? How proper measuresshould be taken during transgression of workingprocedures? There was also no working procedure thatallows land to be registered as any other property. Landdevelopment, city reconstruction, land transfer to individualsthrough auction, construction permits and ownershipadministration activities have been executed byone institute. This made some people to get authoritybeyond their duties and responsibilities. In addition, theorganizational structure did not create favorable conditionfor transparent and accountable working procedure.The problems in the working procedure and organizationalsetup together with the mentality of the employeesof the city administration led to inefficient executive capacityin the disposal of services and eventually contributeda lot to the spread of this illegal practice in the sector.Ethics:- How do you evaluate the role of land in addressingthe developmental and other needs of the city and itsdwellers?Ato Mekuria:- As we all know, land is one of the basicinput for development. When combined with manpower and technology, land serves as a key instrumentfor the realization of development endeavors. Cognizantof this fact, the Administration has been striving for theexpansion of various infrastructural facilities includingeducation, health, road, water and telecommunication byproviding land free of charge and with fair price. TheAdministration has been doing this out of its strong convictionthat such projects create a lot of jobs, introduceproductive transactions and facilitate equity in the distributionof benefits to citizens that come out of this communalproperty.Land has been providing a direct contribution for theexpansion of economic and social services in the city.It also has an indirect contribution to the enhancementof the ongoing peace and democratization process.Ethics: - What are the measures being taken by the Administrationto prevent the illegal land provision andownership?Ato Mekuria:- We have launched various activities aimingat preventing the illegal land provision and unlawfulownership by designing short and long-term plans.Regarding the short-term plans, we have been focusing onchanging working procedures and organizational structures,which can be easily corrected within a short periodof time. A taskforce led by the Mayor of the City Administrationis established. This taskforce has a structurestretched to the lowest echelon ‘the kebeles’ and aimedat controlling the illegal activity by raising public awarenessthrough emphasizing the seriousness of the issue.Ethics July 201038


Ethics July 2010Under the long-term plans we have attached due attentionto creating a working procedure and organizationalstructure that would bring sustainable improvement in theland administration sector. The Administration has alsolaunched efforts to make the working procedures of thecity’s land administration up to standard by implementingbest practices drawn from other countries in the sector.We have also plans to expand it to the national level.The Administration has organized an auction to purchasethe latest technologies that would facilitate theland administration activities. Accordingly, a Germanconsultant won the bid and has already started operation.The technology is expected to create fair, transparentand accountable working system that would enablecustomers to get full information via Web Pages and media.In addition to that, we have launched activities todevelop and strengthen the administration’s man power.In this regard, we have been providing training in theareas of skill, professional competence, governmentpolicies and strategies and rules and regulation. The Administrationhas also been striving to enable employeesto draw lessons from best practices thereby evaluatingthe overall working procedure. Concerted efforts arebeing made to make the above activities sustainable.In another development, the three public offices: LandDevelopment, Bank and Town Reconstruction; LandAdministration and Construction Permit: and the thirdone Planning and Land Information Authorities werereorganized in manners that clearly state their powerand duties. Due to this clear division in duties and responsibilities,encouraging signs are being observedin ensuring efficient and effective service delivery.In general, we have been striving to improve the executioncapacity of land and land related affairs in a sustainablemanner by designing and implementing the shortand long-term plans. We believe that it is possible tocurb illegal activities in the land administration sector.Ethics:- The Federal Ethics and Anti-Corruption Commission(FEACC) has forwarded possible solutions tostop the fraudulent activities and corruption in the landadministration sector by conducting studies on the CityAdministration’s working procedures. What was the responseof the Administration concerning the solutionsforwarded by the Commission? What are the actionsso far taken by the Administration for their implementation?The Commission has been bringing people involvedin the illegal land provision and ownership tojustice and restrain land worth lots of money throughcourt order. How do you evaluate this contribution ofthe Commission to curb illegal activities in the sector?Ato Mekuria:- The FEACC has been playing an irreplaceablerole in the effort to curb the illegal activitiesin the land administration sector. We can put the role ofthe Commission in two ways. The first vital contributionis that the Commission through its practical measureshas communicated clear messages about the illegalityof embezzling government and public propertyand its consequences. Even though it surprised faithfuland ethical employees and officials, this contributeda lot towards preventing illegal actions in the sector.The second important contribution of the FEACC isthat it has forwarded solutions by conducting studieson working procedures that are susceptible to corruptionand other related malpractices. The incumbentCity Administration has utilized the outcome of thestudy as an input when it commenced its office term.Ethics:- Would you tell us about the current situationregarding transparency and accountability in theprovision of lease land through auction, land ownershiprecord, construction permit, land replacement,compensation payment execution and related issues?Ato Mekuria:- Currently the transparency and accountabilityin these areas are encouraging. Many changeshave been made to improve the working procedures inthe above areas. Previously, the bidders could not get fullinformation when they enter in to an auction. As a result,the price of land had been increasing from year to year. Itis to be recalled that one square meters of urban land wassold up to 22,000 Birr. But in the new working procedure,when a land auction is conducted we make sure that thepublic is well-informed by advertising it through variousmedia. Land is being provided to the public within a specificperiod of time (15 to 30 days), this made the price ofland to go down and we expect it to continue decreasing.What matters most for us is not the fluctuation in the pricebut the speedy development of the land by the owners.We have also set up a transparent working procedurethat enables bidders to follow the whole procedureand know the result of the auction on the spot throughcomputer screen, unlike the previous practice wherebidders were made to wait for months to know the results.There is also a significant improvement regardingdocumentation of ownership records, which previouslyhad many complaints. It is also possible to putinto practice a working procedure that would enablecustomers to get their ownership records at kebele andsub-city level within a very short period of time. A waythrough which construction permits would be givenwithin few days has already been facilitated. We havealso improved our service delivery regarding provisionof replacement land and compensation payment.It is becoming easy to provide land for different developmentpurposes including for micro and small-scaleenterprises, education and health facilities. A workingprocedure that would facilitate land provision for infra-<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ም39


structural development and job creation free of chargeand through auction has been set up. Even though alot remains to be done to fully execute our long-termplans, we have accomplished encouraging activitiesto prevent illegal practices, ensure transparent andfair working procedure. When compared to the previousCity Administration the incumbent Administrationhas scored significant achievements in the sector.Ethics: - How does the Administration follow up and inspectthe land ownership maps issued by the Administration?<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ምAto Mekuria:- Most of the land ownership maps wereprepared pervious to the coming to office of the presentAdministration. A serious precaution should be takenstarting from the publishing of the maps. In this regardthere was a gap in following up the proper provision ofownership maps. But the Administration has prepared aguideline with a view to ensuring a transparent and accountableworking procedure after it conducted BusinessProcess Reengineering (BPR). As the guidelinehas clearly stated how the maps should be publishedand provided to customers, now it is possible to say thatthe activities related with land ownership maps havebeen improved. Preparation is also well underway toprovide the ownership maps to close to 100,000 dwellersof the city, who previously have no formal maps.Ethics:- It is constantly mentioned that there is a problemregarding the follow up and inspection on land developersand take measures on those who fail to accomplish ontime as per the agreement. What is your response to this?Ato Mekuria:- The Addis Ababa City Administration washighly careful when it started to improve its working procedures,in so doing, it has attached due attention to threeissues.The primary focus is on raising awareness on illegalland provision and ownership by clearly stating its consequences.The second is providing land to investorsand concerned segments of the society. We have beentrying to bring those investors who previously failed tolaunch construction on time to the right track. Insteadof hurrying to punish them, we have tried to asses thesituation and reconsider if the problem is caused dueto lack of assistance from the Administration. But theAdministration took away the land provided to hundredsof investors whose construction period passed before1997 E.C. The land is now being utilized to housingdevelopment and for other development purposes.The third focus area is to make sure that land providedby the Administration is utilized for development purposesonly. A clear regulation has already been issuedthat facilitates provision of land only for investors readyand capable of developing it.Ethics:- How do you evaluate the cooperation betweenthe Administration and FEACC to curb corruption andmalpractices with regard to, the land sector? What doyou think is expected from the public in this regard?Ato Mekuria:- As I have tried to mention above, the FE-ACC has executed wide-ranging activities to curb illegalactions in land provision and ownership sector in the metropolis.The Commission has brought several suspects tojustice. It has also forwarded solutions by conducting studieson the Administration’s working procedures that arebelieved to be susceptible to corruption and related malpractices.The Administration has been working closelywith the Commission for the same cause. We believe thatwe will continue working closely in exchanging informationand raising the awareness of the public. We are alsoof the opinion that this concordant collaboration betweenthe Administration and the Commission will sustain.It is my belief that a lot of activities would be executed inshaping the attitude of the public. To this end, I hope theCommission would support us by enhancing the awarenesscreation activities.The public has also a vital role in the ongoing effortto curb corruption in the land administration sector.The public should refrain from being part of the corruptpractice and stick to formal lines when going topublic offices for various services. The public shouldalso boldly say no to illegal actions; if the action cannot be stopped the public should discharge its responsibilityby giving tip-offs to concerned bodies. Thecooperation of the public is crucial for the success ofthe efforts being made by the Administration to put inplace transparent and accountable working procedure.I believe that freeing the land administration sectorfrom corruption by putting in place transparent andaccountable working procedure has a vital role towardsstrengthening the ongoing development anddemocratization process in the country. Thank you.Ethics July 201040


Some 110 ....... Cont’d from page 33Federal High Courts, Goshu Andualem Limenih.Each of them received 21 years of rigorousimprisonment in connection with illegal landgrab in the Metropolis and acceptance of undueadvantages respectively.Meanwhile the First Instance Bench of theFederal High Court sentenced Berhane Abraha,former employee of the Ethiopian Electric PowerCorporation, on 3 May 2010 to eight years ofrigorous imprisonment for forging governmentdocuments to steal public property worth 1, 216,213.82 Birr.Furthermore, Wondwosen Alemu Bekele hasbeen charged with committing other corruptioncrimes and is awaiting verdict on those additionaloffenses, it was learned.While working as Secretary of Store at the Corporationfrom 8 July 2005 to 7 July 2006, he forgedoriginal government documents in order to steal(which he managed to do) various electric appliancesworth 1, 216, 213.82 BirrEthics July 2010Corruptors receive imprisonment, fineThe First Criminal Bench of the Federal HighCourt on May 14, 2010 sentenced three corruptorsto 5-21 years of imprisonment and orderedthem to pay 5,000-35,000 Birr in fine.According to the file charged by the ProsecutionDepartment of the Federal Ethics and Anti-CorruptionCommission, Goshu Andualem who wasformer finance officer at the Federal judgmentExecution Department with the Federal Courts,embezzled more than one million Birr throughforging documents and cheques.The convict forged two bank cheques by puttingan imitated signature and deposited the embezzled1,025,267.81 Birr in a bank account openedwith a forged Identity Card he prepared for himselfwith a fabricated name.Aster Azeze, who is the wife of Goshu Andualemand Deputy Inspector, Abrham Ayalew, collaboratedin the crime by hiding the property obtainedthrough corruption.Since all the convicts failed to refute the corruptioncharges brought against them by the Commission,the Court gave Goshu Andualem 21years of rigorous imprisonment and fined him35,000 Birr.A five year prison terms and 5,000 Birr fine weregiven to Aster Azeze, while Deputy Inspector,Abrham Ayalew received 7 years of imprisonmentand 10,000 Birr fine.Court sends corruptors to prisonThe Federal High Court on May 7, 2010 sentencedtwo convicts of corruption offences toprison terms ranging from 7-10 years. It alsoimposed a 10,000 Birr fine on each.The court passed the verdict on, Lieutenant TeferaHailu, who was a teller at the 38th Brigade TrainingSchool of the Ministry of Defense, and EwnetegnawLole, a former member of the defense force.According to the charge, Lieutenant Tefera Hailuembezzled 454,629.44 Birr, which was thedefense force’s July, 2007 salary and additional198,255.27 Birr. The second convict, EwnetegnawLole collaborated in the corrupt practiceby preparing a false Identity Card for LieutenantTefera Hailu, which helps the latter to transferthe embezzled money to his own account.Since the convicts had failed to refute theevidences corroborated against them, the courtgave Lieutenant Tefera Hailu 7 years of rigorousimprisonment and 10,000 Birr in fine.Ewnetegnaw Lole received 10 years of rigorousimprisonment and 10,000 Birr in fine inabsentia.The court passed the verdict in favor of the ProsecutionDepartment of the Diredawa BranchOffice of the FEACC.<strong>ሥነምግባር</strong> ሐምሌ 2002 ዓ.ም41

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!