24.07.2013 Views

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

SHOW MORE
SHOW LESS

Create successful ePaper yourself

Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.

2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

ዋጋ 5:00<br />

“ቻይናውያን ሕገ-መንግሥታችሁንም<br />

የአዋጅ ሕጋችሁንም አናውቅም ብለዋል” 6<br />

አቶ ኩራባቸው ፍቅሩ ገ/ማርያም የዋልዳ ሆጀቶታ ዳንዲ ደራርቱ አርሲ<br />

“ከሲኦል ያመለጡ” ወጣቶች በግልፅ ይናገራሉ፡፡ ከእስር እንደተፈታ ሰው ነው ራሳቸውን<br />

የሚቆጥሩት፡፡ በየአደባባዩም “እንኳን ደስ ያለህ/ያለሽ!” ሲባባሉ ይሰማል፡፡ በተለይም<br />

በየወሩ ከደመወዛቸው የሚቆረጠው ገንዘብ፣የጋዜጣና የመፅሄት ክፍያ በአባላቱ ቋንቋ<br />

“የማይደርስ ዕቁብ” የሚሉት የድርጅቱ ክፍያ፣የልማት (....) መቶ ፕርሰንት መዋጮ እና . . .<br />

9<br />

አንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ም/ቤት መደበኛ<br />

ስብሰባውን አካሄደ<br />

የደብረብርሃን ከንቲባና<br />

ባለሥልጣናት በሙስና<br />

ተጠርጥረው<br />

መታሰራቸው ተገለፀ<br />

የዞኑ ደን ልማት ሽያጭ መነጋገሪያ ሆኖአል::<br />

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሰሜን<br />

ሸዋ ዞን ዋና ከተማ የሆነችው ደብረ ብርሃን<br />

ከተማ ከንቲባ የሆኑት “አቶ ስዩም ተፈራና<br />

በመሬት አስተዳደርና በልዩ ልዩ የሥራ ኃላፊነት<br />

ላይ የነበሩት የዞኑ ከፍተኛ ባለሥልጣናት<br />

ከሙስና ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው በእስር ላይ<br />

እንደሚገኙ...<br />

11<br />

ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ነፃ የሞያ<br />

ማህበራት ያስፈልጋሉ!<br />

የኢንዱስትሪ ሰላምን በሁለት ከፍሎ ማየት ይቻላል፡፡ ጊዜያዊ ሠላምና ዘላቂ ሠላም ናቸው፡፡ ጊዜያዊ<br />

የኢንዱስትሪ ሠላም የማስመሰያ /አሳሳች/ ሠላም ነው፡፡ የሠራተኛውን ልብ ያልገዛ /የሠራተኛውን ጥቅም<br />

ያልጠበቀ/፣አስተማማኝና ዘላቂ ልማትን የማያመጣ ሠላም ነው፡፡ የመፍጠር ችሎታን የማያበረታታና<br />

ምርታማነትን የማያሳድግ ሠላም ነው፡፡ ዘላቂ የኢንዱስትሪ ሠላም ግን የሠራተኛውን ጥቅምና መብትን<br />

የሚያስከብር፣በሠራተኛው ውስጥ በራስ መተማመንንና መረጋጋትን የሚፈጥር፣የሠራተኛውን የኃላፊነት<br />

ስሜት የሚያስከብር ነው፡፡ ሊኖር የሚገባው ጊዜያዊ ሳይሆን ዘላቂ የኢንዱስትሪ ሠላም ነው፡፡ በሀቅ ላይ<br />

የተመሠረተ ከሆነ የኢንዱስትሪ ሠላም ጥሩ ነው፡፡ ሠላም የሕይወትና የንብረት ዋስትና ይሰጣል፡፡ ሠላም<br />

ካለ ልማትና እድገት አለ፡፡ ሠላም ካለ ቤተሰብ በሰላም ወጥቶ ሠርቶ ይገባል፡፡ ሠላም ከሌለ ሁሉም<br />

የለም፡፡ ዛሬ ያለው ሰላም ግን ምን ዓይነት ሠላም ነው? መብትና ጥቅምን የገፈፈ ሠላም፤የታፈነ ሠላም፤<br />

በቁጭትና በዝምታ የታጀበ ሠላም፤ በፍርሃት የታጨቀ ሠላም፤አደጋን ያረገዘ ሠላም! እንዲህ ዓይነት ሠላም<br />

ውጤቱ የከፋ ስለሚሆን አደጋ ነው፡፡ ጊዜውን ጠብቆ የሚፈነዳ ሠላም አንሻም፡፡ ጥፋትን በውስጡ አምቆ<br />

የያዘ “ሠላም” አያሻንም...<br />

4<br />

በጂማ ከተማ የተቃጠለው ውሃ ልማትና ዐቃቤ<br />

ህግ ጽ/ቤት አነጋጋሪ መሆኑ ተገለፀ<br />

11<br />

15<br />

1<br />

የሠራተኞችን ደሞዝ<br />

ለመቀማት ሲል 3ሰው ገድሎ<br />

2 ሰው ያቆሰለው ፖሊስ<br />

በቁጥጥር ሥር ዋለ<br />

በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ሰሜን ሸዋ ዞን<br />

የምትገኝኘው የያያ ወረዳ አስተዳደር ሠራተኞች<br />

የጥቅምት ወር ደሞዝ ለመዝረፍ ሦስት ሰው<br />

ገሎ ሁለት ሰው ያቆሰለው የወረዳው ፖሊስ<br />

በቁጥጥር ሥር መዋሉን የዜና ምንጮቻችን<br />

በተለይ ለፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ገለጹ፡፡ እንደ<br />

ዜና ምንጮቻችን ገለጻ ከሆነ “ጥቅምት 20<br />

ቀን 2004 ዓ.ም አንድ ሚሊዮን ብር ይሆናል<br />

የሚባለውን የወረዳውን የመንግስት ሠራተኖች<br />

ደሞዝ ለማምጣት ከወረዳው ፍቼ ከተማ ንግድ<br />

ባንክ ይመጣሉ፡፡ ግንዘቡን ለማምጣት የመጡት<br />

ሦስት ሠራተኞች አንድ ፖሊስና አንድ ሹፌር<br />

በጠቅላላ አምስት ሰዎች ....<br />

11<br />

www.andinet.org.et


2<br />

www.andinet.org.et<br />

የሙስና መስፋፋት<br />

በአንድ አገር ውስጥ በጥቅም ላይ<br />

ሊውል የሚገባውን መዋዕለ-ንዋይ<br />

(Investment) ይሸረሽረዋል። የውጭ<br />

አገር ከበርቴዎችንም ቢሆን በዚያ አገር<br />

የመዋዕለ-ንዋይ (Foreign Investment)<br />

ተግባር እንዳይሳተፉ ተጽዕኖ ያሳድራል።<br />

በዚህ ጉዳይ ላይ ብዙ ጥናቶች ያደረጉ<br />

ተመራማሪዎች ሲገልጹ “አንዳንድ<br />

ባለሃብቶች ወደ አንዳንድ አገሮች፤<br />

በተለይም ወደ አፍሪካ አገሮች ውስጥ<br />

ከሚያስገቡት የውጭ ምንዛሬና መዋዕለ-<br />

ንዋይ ይልቅ ከነዚህ አገሮች ወደ ሀብታም<br />

አገሮች በስርቆት መልክ የሚወጣው<br />

የውጭ ምንዛሬ ይበልጣል” ይላሉ።<br />

(ለምሳሌ በቅርቡ የአለም ባንክ ያወጣው<br />

ጥናታዊ ጽሁፍ ከኢትዮጵያ ተመዝብሮ<br />

ወደ ውጭ ሀገር እንዲሸሽ የተደረገው<br />

ሀብት/ገንዘብ እስከ 11 ቢሊዮን ዶላር<br />

እንደሚደርስ አሳይቷል። የተባበሩት<br />

መንግሥታትም እንደጎርጎረሳውያን<br />

አቆጣጠር ከ1990 ዓ/ም ጀምሮ<br />

ከኢትዮጵያ ወደ ውጭ ሀገሮች ተዘርፎ<br />

የጎረፈው ሀብት ከ8.3 ቢሊልዮን ዶላር<br />

እንደማያንስ አሳይቷል።) አንዳንድ<br />

አበዳሪዎችም በተመሳሳይ ሁኔታ “ያገር<br />

መሪዎች የሃገራቸውን ሃብት ወደውጭ<br />

የሚያሸሹ ከሆነ እኛ ምን ቸግሮን ነው<br />

ወደነዚህ አገሮች መዋዕለ-ንዋያችንን<br />

የምናስገባው?” የሚል ጥያቄ ያነሳሉ።<br />

ለአብነት ለመጥቀስ ያህል በ1997<br />

ዓ/ም በኢትዮጵያ የተካሄደው ምርጫ<br />

በህወሓት/ኢሕአዴግ ከከሸፈ በኋላ<br />

ከኢትዮጵያ ወደ እንግሊዝ አገር የጎረፉት<br />

ሃብቶች በጣም በዝተው እንደነበር<br />

አንዳንድ የእንግሊዝ የዜና ማሰራጫዎች<br />

አጋልጠዋል። በዚያው ሰሞን ሰሚ ያጡ<br />

አቤቱታዎች ከተለያዩ አቅጣጫዎች<br />

መነሳታቸው አልቀረም። ለምሳሌ እ.ኤ.አ.<br />

በ1997 World Development Report<br />

በተባለው መጽሄት ታትሞ የወጣው<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

ጥናት ሲያመለክት እንደ ኢትዮጵያ<br />

በሙስና የተዘፈቁትና ሙስና ያላጠቃቸው<br />

አገሮች ሲወዳደሩ ሙስና ያጠቃቸው<br />

አገሮች በእድገት ወደ ኋላ መቅረታቸውን<br />

ዘግቧል፡፡ እንዲሁም በዚሁ አመት<br />

(National Bureau of Economic<br />

Research) ተብሎ በሚጠራው ጥናታዊ<br />

መጽሄት ያወጣው ጥናት እንደዘገበው<br />

ይህ ሁኔታ በሩቅ ምስራቅ የእስያ አገሮች<br />

እንደተከሰተ ዘግቧል።<br />

ሙስና እንደ ተጨማሪ<br />

ታክስም ስለሆነ የግል ተቋሞችና<br />

ኩባንያዎች እንዳያድጉ ያደርጋል።ሙስና<br />

በግል ተቋማትና በግለሰቦች መካከል<br />

መኖር የሚገባውን ጠቃሚ ውድድር<br />

ይቀንሳል፤ያጫጫል።<br />

ሙስና በጣት የሚቆጠሩ<br />

ሰዎች ብቻ ካለመጠን እንዲከብሩ<br />

ያደርግና በሃብታምና በድሆች መካከል<br />

ልዩነቶችና ቅራኔዎች ያስነሳል። ቅራኔው<br />

ሲገፋም ሀብታሞች ሕጋዊ ባልሆነ መልክ<br />

ያካበቷቸውን ሃብቶች ወደ ሌላ አገር<br />

እንዲያሸሹ ይገፋፋል። ይኸው ድርጊት<br />

በበኩሉ አገር ያራቁታል። ለምሳሌ የዛዬሩ/<br />

የኮንጎው ሞቡቱ ሴሴኮና የፊሊፒኑ<br />

ፈርድናንድ ማርቆስ በሥልጣን ላይ<br />

በነበሩበት ወቅት ያካበቷቸውና በውጭ<br />

አገር ባንኮች ያስቀመጧቸው ንብረቶች<br />

በብዙ ቢሊዮን ዶላር ይቆጠሩ ስለነበር<br />

ዛዬርም/ኮንጎም ሆነች ፊሊፒንስ ለብዙ<br />

ዓመታት የተከማቸባቸውን የውጭ<br />

ብድር በገዛ መሪዎቻቸው የተሰረቀው<br />

ገንዘብ ብድራቸውን ሁሉ ከፍሎ ከዕዳ ነጻ<br />

ሊያደርጋቸው እንደሚችል ተዘግቧል።<br />

ሙስና በአንዲት አገር ውስጥ<br />

የሚገኝን ሕጋዊና ትክክለኛ የንግድ ተግባር<br />

ያዛባል። የፍጆታ ዕቃዎች ትክክለኛ<br />

ዋጋ በተስተካከለ መልክ እንዳይተመን<br />

ያደርጋል። የሸቀጥ እቃዎች እንዲያንሱ<br />

ወይም እንዲጠፉ፤ ብሎም በጓዳ በር<br />

እንዲሸጡ መንገድ ይከፍታል። ዋጋቸው<br />

እንዲንር ያደርጋል፤ ቀስ በቀስም የፍጆታ<br />

ዕቃዎች ዋጋ በጣም ከፍ ይልና ህዝብን<br />

ያስቆጣል። በመንግስትና በነጋዴዎች<br />

መካከል አስፈላጊ ያልሆነ ጠብ እንዲፈጠር<br />

ያደርጋል። ባገራችንም ሆነ በሌሎች<br />

አገሮች እንደተከሰተው፤ መንግስት ነኝ ባዩ<br />

የራሱ መመሪያና ተግባር በፈጠረው ችግር<br />

ነጋዴዎች እንዲከሰሱና እንዲቀጡም<br />

ያደርጋል። በዚህ ምክንያት እንግልት፣<br />

እስርና ግድያ ሊከተል ይችላል። የፍጆታ<br />

ዕቃዎች ዋጋዎች ከፍ ሲሉ የፍጆታ<br />

ዕቃዎቹን ሊያገኙ የሚችሉ ሃብታሞችና<br />

ከነሱ ጋር ግንኙነት ያላቸው እንዲሁም<br />

ከሻጮች ጋር ዝምድና ያላቸው ብቻ<br />

ናቸው። ለዘመድና ለጓደኛ ብቻ መሸጥ<br />

ይመጣል። ሻጮች ዋጋ ከፍ አድርገው<br />

ለዘመዶቻቸውና ለጓደኞቻቸው ብቻ<br />

የመሸጣቸው ምክንያትም ለመንግስት<br />

አያጋልጡንም በሚል አስተሳሰብ<br />

ነው። ተራው ዜጋ በተለይም ድሀው<br />

የሕብረተሰብ ክፍል ግን ቁሳቁሶቹን<br />

እንዳያገኝ የገንዘብ አቅሙ የማይፈቅድለት<br />

በመሆኑ እንዲሁም ከሀብታሙም ሆነ<br />

ከሻጩ የሕብረተሰብ ከፍል ጋር የጠበቀ<br />

ግንኙነት ስለማይኖረው ሁሌም ተጎጂ<br />

ነው። እኒህን ዓይነት የሙስና ገጽታዎች<br />

በኢትዮጵያችን በጣም የተንሠራፉ<br />

ስለሆኑ ባንዳንድ ሰዎች አገላለጽ “በአገሪቱ<br />

ውስጥ ዛሬ የሚካሄደው ንግድ ከማፍያ<br />

ድርጊት የማይተናነስ ነው” ብለው<br />

እንደነ ሪፖርተር ያሉ ጋዜጦች ጭምር<br />

ያስገነዝባሉ። በማፍያ መልክ የሚሰራው<br />

ወንጀላዊ የንግድ አሠራር ከመብዛቱም<br />

የተነሣ በድብቅ መነገድና የጥቂቶች ብቻ<br />

መጠቃቀም ባህል ይሆናል፤ ኮንትሮባንድ<br />

ይስፋፋል፤ ዝርፊያ ይጧጧፋል፤<br />

ወንበዴዎች ይፈጠራሉ፤ ይባስ ብለውም<br />

ወንበዴዎች የራሣቸውን ኬላ ይፈጥራሉ፤<br />

እንዳሻቸው ይዘርፋሉ። የሚያሳዝነው ግን<br />

እነዚህን የመሰሉ ክስተቶች በአገራችን<br />

በሰፊው እየታዩ መሆናቸው ነው።<br />

ዳሰሳ<br />

2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />

የሙስና መስፋፋት በኢኮኖሚ፤በፖለቲካና በማህበራዊ ኑሮ<br />

ፕሮፌሰር ሰይድ ሐሰን<br />

መሪ ስቴት ዩኒቨርስቲ (አሜሪካ)<br />

ካለፈው የቀጠለ<br />

ዘርፍ የሚያስከትለው ችግር<br />

ሙስና ሰዎች በትጋት ሰርተው<br />

ሃብታቸውን እንዳያዳብሩ፤ ቤታቸውን<br />

እንዳያቀኑና አገራቸውን እንዳይገነቡ፤<br />

ባንፃሩ ግን ባቋራጭ የመክበር<br />

ፍላጎታቸው እንዲያድግ ያደርጋል። ዜጎች<br />

ለምርት ያላቸውን ዝግጁነት ይቀንሳል<br />

(It distorts incentives)። ይህ<br />

የሚሆንበት ምክንያቱ ብዙ ነው። ለምሳሌ<br />

በበርካታ አገሮች ውስጥ እንደታየውና<br />

እንደተከሰተው፤ ከሙስና ጋር የተሳሰሩ<br />

ድርጅቶችና የንግድ ተቋማት በመልካም<br />

መንገድ ሰርቶ መክበር አይችሉም።<br />

ሁሌም በሙስና መክበርን የሚመርጡ<br />

ናቸውና። ይህ ደግሞ ባኳያው በትክክልና<br />

በመልካም መንገድ ሥራቸውንና<br />

ሃብታቸውን ለማቃናት የሚጥሩትን ተስፋ<br />

ያስቆርጣል። ቀስ በቀስም በመልካም<br />

መንገድ የሚያካሂዱትን ሥራቸውን<br />

ለቀው ወደመጥፎ ጎዳና እንዲገፉ<br />

ይገደዳሉ፤ ብሎም እነሱም እንደሌሎቹ<br />

ጥቂት ገፋፊዎች በሙስናው እንዲሳተፉ<br />

ይገፋፋሉ። ይህ የስነ-ልቦና ለውጥ እያደር<br />

ለእንያንዳንዱ ዜጋ ይደርሰውና ቀስ በቀስ<br />

አገርና ዜጎች በሙስና ይጠመዳሉ።<br />

ቀደም ሲል ለመጠቆም<br />

እንደተሞከረው በታዳጊ አገሮች ብዙ<br />

መዋዕለ ንዋይ የለም፤ ይባስ ብሎ ያሉትም<br />

ሲዘረፉ ደግሞ አገሮቹ ለበለጠ ድህነት<br />

ይዳረጋሉ። ያገሮቹ ጥቂት ሃብቶች<br />

ወደተወስኑ ግለሰቦችና ድርጅቶች<br />

ወይም ቡድኖች ሲገቡ ደግሞ ያላግባብ<br />

በከበሩ ቡድኖችና በተራው ዜጋ መካከል<br />

መቃቃር ከመከተሉም በላይ የሀብቱ<br />

ልዩነት ይራራቅና ለግጭትና ለብጥብጥ<br />

ይዳርጋል። ይህ ሲሆን በሙስናና<br />

በብልጣብልጥነት የከበሩት አላግባብ<br />

መክበራቸውን ስለሚያውቁ አንደኛ<br />

ሃብታቸውን ሁለተኛ ራሳቸውንም<br />

ወደ ውጭ ማሸሽ ይከተላል። ይህ<br />

ተግባር በብዙ አገሮች ውስጥ የተከሰተና<br />

በኢትዮጵያችንም እያቆጠቆጠ ያለ አስፈሪ<br />

ክስተት ነው፤ መባባሱም አያጠራጥርም።<br />

በስልጣን የሚባልጉ<br />

ባለስልጣናትና የሙስና ተባባሪዎቻቸው<br />

ሃብት የሚያካብቱት ባቋራጭና በፍጥነት<br />

ስለሆነ፤ በፋሲካ የተዳረች ሁሌም ፋሲካ<br />

ይመስላታል ነውና፤ ሃብት ሁሉ በዚሁ<br />

መልክ የሚገኝና ምንጊዜም ሊተካ የሚችል<br />

አድርገው ስለሚቆጥሩ በፈጠነ መልክ<br />

ሃብታቸውን እንዲያባክኑ ይገፋፋሉ፤<br />

ይታለላሉ። ባጭር ጊዜ ውስጥ ያገር<br />

ሃብት የሚወድምበት አጋጣሚ ተፈጥሮም<br />

ሃገርና ዜጋ ያለረዳት ይቀራሉ።<br />

ብዙውን ጊዜ በሙስና<br />

የተበከሉ ሰዎች በሕገ-ወጥ መልክ<br />

ያካበቱትን ሀብት የሚያውሉት በድሎትና<br />

በቅምጥል (luxury) ዕቃዎች ላይ ነው።<br />

ከሚገዟቸው ቁሳቁሶች መካከልም፤<br />

ውድ የሆኑ መኪኖች፤ ጌጣጌጦች፤<br />

የቤት ማስጌጫዎች፤ መጠጥና ልብሶች<br />

ተጠቃሾች ናቸው። እንደነዚህ ያሉ<br />

እቃዎችም ባንድ በኩል አላቂና ግላዊ<br />

ስለሆኑ ላገር የሚያስገኙት ጥቅም እጅጉን<br />

ውሱን ነው። የቁሳቁሶቹ ዋጋ ከሌሎች<br />

ቁሳቁሶች ጋር ሲወዳደር ከፍ ስለሚልም<br />

የተገዙበት ንዋይ ተቀማጭ ወይም ታሳሪ


2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />

ዳሰሳ<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

እንጂ ተንቀሳቃሽ ወይም በሃገር ኢኮኖሚ<br />

ውስጥ ተዘዋውሮ ተነግዶበት ለትርፍ<br />

የሚያበቃ አይደለም። በሌላ በኩል ይህ<br />

የተወሰነው የሙስና ተሳታፊ የህብረተሰብ<br />

ከፍል ብዙውን ጊዜ በውድ ቁሳቁሶችና<br />

ጌጣጌጦች በማሸብረቅ ፉክክር ተጠምዶ<br />

ስለሚቀር ለአጓጉል ባህል መጸነስ <strong>ምንጭ</strong><br />

መሆንም ይንጸባረቅበታል።<br />

በርከት ያሉ ጥናቶች<br />

እንዳመለከቱትም ቀልጣፋ ያልሆኑትንና<br />

ውጤታማ ያልሆኑትን (inefficient)<br />

ድርጅቶችን፤ አምራቾችንና ግለሰቦችን<br />

የበላይነት እንዲኖራቸው በማድረግ አገር<br />

ወደ ኋላ እንድትጎተት ያደርጋል።<br />

ሙስና የሕብረተሰብን ንብረት<br />

ወስዶ ለግለሰቦች ያስረክባል። ይህንን<br />

በማድረግም ከሁሉም ይበልጥ የድሀውን<br />

የህብረተሰብ ክፍል በበለጠ ይጎዳል።<br />

ከመንግስት ባለስልጣኖች ጋር ግንኙነት<br />

ያላቸው በሙስና የተዘፈቁት ግለሰቦች<br />

የሕዝቡን ሀብት ለግላቸው ሲያውሉት<br />

የትምህርት ቤት ተቋማትን ለማቋቋም፤<br />

የጤና ጥበቃ ጣቢያዎችን ለመመስረት፤<br />

ለአዉራ ጎዳናና መንገድ ሥራው ሥራዎች፤<br />

ለዉሃ ልማቶች፤ ወ.ዘ.ተ. ሊዉል የሚገባው<br />

ሀብት እንዲባክን ያደርጋል።<br />

ሙስና ከዉጭ አገር<br />

የሚገኘውን እርዳታ ውጤተ-ቢስ<br />

እንዲሆንና እንዲባክን ያደርጋል። ምንም<br />

እንኳ እርዳታው የሚላከው ለድሆች<br />

እንዲደርስ ቢሆንም፤ እርዳታው ለድሆች<br />

እንዳይደርስ፤ በርዳታው ገንዘብ እንዲሰሩ<br />

የተፈለጉት ተቋሞች እንዳይሰሩ ወይም<br />

ብልሹ በሆነ መልክ እንዲሰሩ ያደርጋል።<br />

እኔ እራሴ እንደተገነዘብኩትም፤ በገባያ ላይ<br />

እንዳይሸጡ የተከለከሉ የርዳታ እቃዎች<br />

ሕገ-ወጥ በሆነ መልክ እንዲሸጡ ያደርጋል።<br />

ለዚህ ዋቢም ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ<br />

የሚላከውን የምግብ ዘይት መጥቀስ<br />

ይበቃል።<br />

ፖለቲካንና መንግስታዊ አስተዳደርን<br />

በሚመለከት (በከፊል)፤<br />

ሙስና እየገነነ ሲመጣ በሃገር<br />

ዕድገት መስክ ጉልህ ሚና የሌላቸው በጣም<br />

ጥቂቶች እየከበሩ ይመጡና የመንግስትና<br />

የሕዝብ መገልገያ በሆኑ መሥሪያ ቤቶች<br />

በመስራት ብዙ ልምድ ያካበቱና ታማኝ<br />

የሆኑ፤ እንዲሁም ብቃት ያላቸው<br />

የቢሮ ሰራቶኞችን ሥራቸውን ለቀው<br />

እንዲወጡና ቀስ በቀስ ብቃት የሌላቸው<br />

በቦታው እንዲተኩ በር ይከፍታል።<br />

ይህም በሕዝብ መሥሪያ ቤቶች ውስጥ<br />

መልካም ባህርይና ችሎታ ያላቸው መሪዎች<br />

እንዳይበቅሉ ያደርጋል፤ የሃገርን የብቁ ዜጋ<br />

ቋት ያራቁታል። መድረሻ የለንም የሚሉ<br />

ቢኖሩም፡፡<br />

ሙስና ላገራቸውና<br />

ለህዝባቸው ተግተው የሚሰሩ ዜጎችንና<br />

ከፍተኛ የሙያ ትምህርት የቀሰሙ<br />

ሊሂቃንን ለሀገራቸው የሚያደርጉትን<br />

የአገልግሎት ፍላጎት የሚቀንስ ነው።<br />

ሙስናው እየበረታ ሲሄድም የመንግስት<br />

ሥራን እየለቀቁ፤ ለትምህርታቸው<br />

የከፈለላችውን ህዝብ እንደማገልገል<br />

ፋንታ፤የግል ባለህብቶችን/ኩባንያዎችን<br />

ለማገልገል ወይም የራሳቸውን የግል ንግድ<br />

እንዲፈጥሩ ይገፋፋል፤ያስገዳዳልም።<br />

ብዙዎች ባልሰለጠኑበት ሙያ እንዲሰማሩ<br />

እንደሚያስገድድም በብዙ አገሮች ውስጥ<br />

ታይቷል። በኢትዮጵያም እንደዚሁ ባስከፊ<br />

ሁኔታ እየተከሰተ ነው። እያደር ተስፋቸው<br />

እየተሟጠጠ አገራቸውን ጥለው እንዲሄዱ/<br />

እንዲሸሹ የሚገፉ ብዙዎች ለመሆናቸውም<br />

ጥርጥር የለውም። ይህ እየበረከተ ሲሄድ<br />

ደግሞ አገር ምሁር አልባ፤ አዕምሮ አልባ<br />

ትሆናለች። ብዙ ሃብት ጠፍቶ የሰለጠኑ<br />

ምሁራን ለሀብታም አገሮች ሲሳይ (braindrain)<br />

ይሆናሉ። ድሃ አገሮች ደክመውና<br />

ከፍለው ያሰለጠኑት አዕምሮ እየሸሻቸው፤<br />

ያሳደጉትን መሳም ያልቻሉ ደካሞች ሆነው<br />

እንዲታዩም ምክንያት ይሆናል። በአፍሪካ<br />

አህጉር ኢትዮጵያና ጋና በዚህ ረገድ ቀዳሚ<br />

ተጠቃሽ ናቸው። ቀጥተኛ የሆነ የፖለቲካ<br />

ችግር ተጨምሮበት አገራችን ዛሬ ማቆሚያ<br />

በሌለው መልክ የሰለጠነ የአእምሮ ሃብቷ<br />

እየተራቆተ ነው።<br />

በሌላ በኩል በሙስና ምክንያት<br />

ችሎታና ብቃት ያላቸው ባለሙያዎች<br />

ከመንግስታዊ መዋቅሮች ሲለቁ ቦታው ብቁ<br />

ችሎታ በሌላቸው ሰዎች እንዲሞላ ግድ<br />

ይሆናል። ይህም እየቆየ የመንግስት መሥሪያ<br />

ቤቶች እንዲጠሉ ያደርግና ቀስ በቀስ<br />

የመንግስት ትእዛዞች እንዳይከብሩ፤ ብሎም<br />

መንግስት ራሱ እንዲጠላ የራሱን አሉታዊ<br />

ሚና ይጫወታል። በህዝብ የሚጠላ<br />

መንግስት ደግሞ ሕዝባዊ ችግሮችን ሊፈታ<br />

የሚችል አይሆንም።<br />

በሙስና ምክንያት ሌብነት<br />

በዝቶ ድህነት ሲስፋፋ እያደር ዴሞክራሲም<br />

ደብዛው ይጠፋል። ዴሞክራሲ ሲጠፋም<br />

በኤኮኖሚ የማደግ እድል ይቀንሳል፣<br />

በሌላ በኩል በሙስና ምክንያት ችሎታና ብቃት ያላቸው<br />

ባለሙያዎች ከመንግስታዊ መዋቅሮች ሲለቁ ቦታው ብቁ ችሎታ<br />

በሌላቸው ሰዎች እንዲሞላ ግድ ይሆናል። ይህም እየቆየ የመንግስት<br />

መሥሪያ ቤቶች እንዲጠሉ ያደርግና ቀስ በቀስ የመንግስት ትእዛዞች<br />

እንዳይከብሩ፤ ብሎም መንግስት ራሱ እንዲጠላ የራሱን አሉታዊ<br />

ሚና ይጫወታል። በህዝብ የሚጠላ መንግስት ደግሞ ሕዝባዊ<br />

ችግሮችን ሊፈታ የሚችል አይሆንም።<br />

ድህነትንም ያንሰራፋል። የሰብዓዊና<br />

ሌሎችም ዴሞክራሲዊ መብቶች መታጣት<br />

በበኩሉ ለእርስ በርስ ጥልና ንክሻ<br />

ምክንያት ይሆናል። ይህ የሚንጸባረቅበት<br />

ህብረተሰብ ችግርና መከራ እንደ አዙሪት<br />

እየተሽከረከሩበት (vicious circle)<br />

ለመኖር ይገደዳል። ካዙሪቱም መውጣት<br />

አስቸጋሪ ይሆናል።<br />

ሙስና ሲስፋፋ በሥልጣን<br />

ላይ ያሉ ግለሰቦች በሙስናው ይሰክሩና<br />

ያጋልጡናል ብለው የሚፈሯቸውን<br />

ለምሳሌ እንደ ነፃ ፕሬስና ሌሎችም<br />

የሕዝብ መገናኛ ዘዴዎች ባለሙያዎችን<br />

እንዲሁም ንቁ የህብረተሰብ ክፍሎችን<br />

ማፈንና ማሳደድን ስራዬ ብለው ይይዛሉ።<br />

አፋኝ የሆኑ አዳዲስ ሕጎችን እያወጡ ነጻ<br />

አሰራሮችን ያግዳሉ፤ ጋዜጠኞችን ያስራሉ፤<br />

ያሰቃያሉ፤ ያዋክባሉ። በዚህም የተነሳ ነጻው<br />

ፕሬስና የሕዝብ መገናኛው መድረክ ሁሉ<br />

እያደር እየተዳከመ የተልፈሰፈሰ ይሆናል።<br />

ተልፈስፋሽ እንዲሆንም ፍላጎታቸውም፤<br />

ተግባራቸውም ነው። ይኸው ድርጊት<br />

ጠቅላላው ሕብረተሰብ እንዳያውቅ<br />

እንዳይማርና እንዳይጠይቅ ሆኖ የሰጡትን<br />

ብቻ ተቀባይና መስማት የተሳነው እንዲሆን<br />

ያደርጋል። በኢትዮጵያችን ይህ እየሆነ ያለ<br />

ክስተት ይሁን እንጂ ህዝቡ ይባስ ብሎ<br />

ከመንግሥት ለሚተላለፉ መመሪያዎችም<br />

ሆነ ዜናዎች ጆሮ ዳባ ልበስ ካለ ዓመታት<br />

ተቆጥረዋል። ይልቁንም ዕውነትን<br />

ፍለጋ በውጭ መገናኛ ብዙሃን ዘርፎች<br />

ለመጠቀም ተገዷል። ሕዝቡ መንግሥት<br />

ተብዬው ለሚያወጣቸው መመሪያዎች<br />

ቁብ የለውም፤ እንዲለግም የተገደደበት<br />

ሁኔታ ነው የሚታየው። በዚህ ዓይነትም<br />

ፖሊሲዎች በወረቀት ላይ ብቻ ይሆናሉ።<br />

ሕዝብና መንግስትም ሆድና ጀርባ እንደሆኑ<br />

ይቀራሉ።<br />

ማህበረሰባዊ ኑሮን በሚመለከት<br />

(በከፊል)፤<br />

ተደጋግሞ እንደተገለጸው<br />

ሙስና እጅጉን ሲስፋፋ በመንግስት<br />

መዋቅሮች ውስጥ የሚሰሩ በተለይም<br />

በንቃት ሃገራቸውን ሊያገለግሉ የተዘጋጁና<br />

ለስልጠናቸው ብዙ የተደከመባቸው<br />

ወገኖች አእምሯቸው እንዲላሽቅ<br />

ይደረጋል።<br />

ሙስና በትምህርት፤ በሥራ<br />

ልምድና በታታሪነት ኑሮን ከማዳበር<br />

ይልቅ፤ በጓዳና ባቋራጭ መንገድ የመክበር<br />

ፍላጎትንና፡ ስግብግብነትን የሚያበረታታ<br />

ስለሆነ ተጎጂው ሁሌም ንቁና ሀገሩን ወዳዱ<br />

ክፍል ነው። ሙስና ሁሉም ሊከብርና<br />

ኑሮውን ሊያቃና የሚችልበት ሳይሆን<br />

ጥቂቶች ያላግባብ የሚበለጽጉበት በመሆኑ<br />

“እድሉ” ያላጋጠመው አብዛኛው ሁሌም<br />

ብስጭት ላይ ይወድቃል። ኑሮውን<br />

ያማርራል፤ ተስፋ የቆረጠ የህብረተሰብ<br />

አባልን ያበረክታል። ተስፋ በቆረጠ ዜጋ<br />

ሀገር ሊያድግ ከቶውንም አይችልም።<br />

ሙስና በተለይ ድሆችን ጎጂ<br />

ነው፤ ድሆች እንኳን ጉቦ የሚከፍሉት<br />

ሊኖራቸው ቀርቶ ለራሳቸውም የሚበቃ<br />

ሃብት የላቸውምና!<br />

በሃይማኖት በኩልም ቢሆን፤<br />

ሙስና ከኃጢዓት (መቅሰፍት) የሚቆጠር<br />

እንጂ የሚያበረታታ አይደለም። በጉቦ<br />

የተለከፈ ሕብረተሰብ ብርቱ ሞራልና<br />

የወደፊት የረጅም ጊዜ የኑሮ ዕቅድ<br />

የለውም፤የዛሬን የከብሮ ማደር ብቻ ቀዳሚ<br />

ዓላማው ነውና። በሙስና የተጠመዱ ሰዎች<br />

አእምሯቸው ሁሌም የተረበሸና በጥቅም<br />

የተበረዘ በመሆኑ ቀስ በቀስ እንደተላላፊ<br />

በሽታ ሌሎቹንም የሚበክሉ ናቸው።<br />

ለዚህም ነው ሙስና እኩይ ወጥመድ<br />

ነው የሚባለው። በሙስና የተለከፉ ዜጎች<br />

ርህራሄ የጎደላቸውና ከምንም በላይ<br />

ጥቅማቸውን የሚያስቀድሙ በመሆናቸው<br />

የጋራ ሃገር ዕድገት እንቅፋቶች ናቸው።<br />

በሙስና የተጠመዱ ሰዎች ሁሉንም<br />

ለማግበስበስ በሚያደርጉት ሩጫ በተለይ<br />

ድሃው የህበረተሰብ ክፍል በመንግስት<br />

የዕለት ተዕለት አገልግሎቶች እንኳ ሳይቀር<br />

ተጠቃሚ እንዳይሆን የሚያደርጉ ጨካኞች<br />

ናቸው። ሙስና ራሱ ሃጢዓተኛ ነው<br />

የሚባለውም ለዚህ ነው።<br />

ሙስና የህብረተሰብ የእድገት<br />

መስኮችን ሁሉ ገቺና ወደፊት የማያራምድ<br />

ማነቆ ነው። ዕድገትን ሳይሆን ዝቅጠትን<br />

የሚያስከትል አደገኛ የህዝብና የሃገር ነቀርሳ<br />

ነው።<br />

ሙስና ወንጀለኞችን<br />

ያበራክታል፤ ብዙ ጊዜም ድሃ ዜጎች<br />

በሕይወታቸው ደስተኝነትን በማጣት<br />

ሳቢያ ህይወታቸውን እንዲያጠፉ ጭምር<br />

የሚገፋፋ ነው።<br />

3<br />

ሙስና በሰፈነበት አገር<br />

የኢኮኖምም፤ የፖለቲካም የማህበራዊ<br />

ኑሮም አዳዲስ ግኝቶችና ሀሳቦች ማፍለቅ<br />

የሚበረታታበት መድረክ ጎልቶ አይታይም።<br />

ስለሆነም ሙስና የማህበረሰባዊ ዕድገት<br />

ጠንቅ ነው።<br />

ሐ) መደምደሚያና ማጠቃለያ፤<br />

ዉድ ወገኖች፤ ሙስና የአንዲት<br />

አገር ኤኮኖሚን አቆርቋዥ፤ ባህልንና<br />

ሕብረተሰባዊ ትብብርን አኮላሽ፤ መንገሥት<br />

ለሕዝብና ለሃገር ሊያደርግ የሚገባውን<br />

አገልግሎት ቀናሽ ሥለሆነ ሁላችንም<br />

ልንዋጋው ይገባል።<br />

ሙስናን የሚያራምዱ በባህላቸው<br />

የዘቀጡና የባህል ድህነት ያጠቃቸው፤<br />

በተንኮለኝነት አስተሣሰብ የተዘፈቁ፤<br />

በሌብነትና በቀማኛነት የተለከፉ፤ የጥሩ<br />

ሥነ-ምግባር ድሃ የሆኑ፤ የሕብረተሰብንና<br />

ያገር ንብረትን አባካኝ/አጥፊ የሆኑ፤ፀረ-<br />

ሕዝብ ግለሰቦች ናቸው። በሙስና ወረርሽኝ<br />

የተለከፉ ግለሰቦች ከሕብረተሰቡ ጋር<br />

ያላቸው ንክኪም በጣም የበረከተ ስለሆነ<br />

በሽታውን ለጠቅላላው ሕብረተሰብ<br />

የማስፋፋትና የማስለከፍ ችሎታቸው<br />

ከፍተኛ ስለሆነም ከሥልጣናቸው መወገድ<br />

አለባቸው።<br />

በሙስና የተዘፍቁ አግሮች በኢኮኖሚም<br />

ሆነ በባሕል ወደ ኋላ የቀሩ መሆናቸው<br />

በብዙ ጥናቶች የተረጋገጠ ስለሆነ ይህ<br />

ችግር በኢትዮጵያችን በሚያስፈራ መልክ<br />

እያንሠራራ ስለሆነ ይህንን የነቀርሳ<br />

በሽታ ለመዋጋትና መንግሎ ለማውጣት<br />

መተባብር ያስፈልገናል። ከብዙ አገሮች<br />

የተገኘው ልምድ እንደሚያመለክተው ሁሉ<br />

ሙስናን ለመዋጋት በሙስና የተለከፉትን<br />

ግለሰቦች ማጋለጥና መንግሥት ሙስናን<br />

ለመዋጋት የማይተባበር ከሆነም፤ በሕቡዕ<br />

በመደራጀትና በመተባበር መዋጋትን፤<br />

በሙስና የተዘፈቁትንም በምስጢራዊ<br />

ሰነድ አዘጋጅቶ እንደአስፈላጊነቱ ማጋለጥ።<br />

እንደዚህ ያለው አስተዋፅዖና መልካም<br />

ምግባር፤ ለሙስናው መሥፋፋት<br />

ምክንያት የሆነው የአስተዳደር ብልሹነት<br />

እንዲፍረከረክ ያደርገዋል። ተጎጅው<br />

ሕዝብንም እስትንፋስ ይሰጠዋል።<br />

እንደሚታወቀው ባገራችን በኢትዮጵያ<br />

(በየክፍለ ሃገሩ፤ በየከተማው፤ በየንመደሩ፤<br />

በልዩ ልዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች፤<br />

ዱሮ በመንግስት ሥር በነበሩት አሁን ግን<br />

“ለግል ባለ ሀብቶች” በርካሽ በተቸረቸሩት<br />

ተቋማት መካከል፤በግል ሀብቶች መስክ፤<br />

….ወዘተ) ከሙስና ጋር የተያያዘው ችግርና<br />

የሚደረገው ደባ ተዘርዝሮ አያልቅም።<br />

ሙስናው የወረርሽኝ በሽታ ስለሆነ<br />

ከዘራፊዎቹ በስተቀር ሁሉንም ሰው<br />

ይጎዳል። ስለዚህ “የኔ ጉዳይ አይደለም”<br />

ተብሎ የሚተው መሆን የለበትም።<br />

እስካሁን ድረስ በኢትዮጵያ ሕዝብና<br />

በሀገሪቷ ላይ አሁንም እየተፈፀሙ ያሉትን<br />

በደሎችን ብሔራዊ ወንጀሎችን በቀጣይነት<br />

መመዝገብና ማጋለጥ አለብን። የዜግነትና<br />

የሰው ልጅነት ግዴታችንን እንድንወጣ አላህ<br />

(እግዚአብሔር) እንዲረዳን እማፀናለሁ!<br />

በመጨረሻም ሙስና ከሰው ጋር<br />

ያልተፈጠረ ክስተት ስለሆነ ያለጥርጥር<br />

እናሸንፈዋለን! በሙስና የተበከሉ<br />

ግለሰቦች፤ ቡድኖችና የመንግሥት<br />

ባለስልጣኖች የድሃውን ወገናችንን ደም<br />

መጣጭ መዥገሮች ናቸውና መወገድ<br />

አለባቸው!የሁለተኛው የሙስና ክፍል፤<br />

ማለት፤ የመንግሥቱን የሥልጣን አውታር፤<br />

አስተዳደሩን፤ ህጎቹን፤ ወ.ዘ.ተ. በመማረክ<br />

የሚገለፁ የሙስና ጠባዮች (state<br />

capture) በሌላ ጊዜ እስከማቀርብ ድረስ፤<br />

እስከዚያው አላህ ቸር ይበለን።<br />

www.andinet.org.et


4<br />

ፍኖተ -ነፃነት ጋዜጣ ሐምሌ 2ዐዐ3 ዓ.ም<br />

ተመሠረተ፡፡ ፍኖተ ነፃነት በአንድነት ለዴሞክራሲና<br />

ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሥር የሚታተም<br />

በፖለቲካዊ፣ በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ፣ በወቅታዊ ጉዳዮችና<br />

በመዝናኛ ላይ የሚያተኩር የፓርቲው ጋዜጣ ነው፡፡<br />

ጋዜጣችን እንደ ፓርቲ ልሳን ብቻ<br />

ሳይሆን እንደ አንድ ሚዛናዊ የግል<br />

ጋዜጣ ሆኖ ማገልገል ይፈልጋል<br />

የማንኛዉም ሰዉ ሀሳብና አመለካከት<br />

የሚስተናገድበትና የሚንሸራሸርበት<br />

እንዲሆን እንሻለን ሰፊ የሚዲያ<br />

ሽፋን ያለዉ ኢህአዴግም በዚህ ሚዲያ<br />

አቋሙንና ፖሊሲዉን ለማቅረብ ቢፈልግ<br />

ክፍት ነዉ<br />

ዋና አዘጋጅ፡-<br />

አንዳርጌ መሥፍን<br />

አድራሻ፡-<br />

የካ ክ/ከተማ ወረዳ 12<br />

የቤ.ቁ አዲስ<br />

አዘጋጆች፡-<br />

ብዙአየሁ ወንድሙ<br />

ብስራት ወ/ሚካኤል<br />

አምደኞች፡- ዶ/ር ኃይሉ አርዓያ<br />

ኢ/ር ዘለቀ ረዲ<br />

አንዱዓለም አራጌ<br />

ግርማ ሠይፉ<br />

ዳምጠው አለማየሁ<br />

ተስፋዬ ደጉ<br />

በላይ ፍቃደ<br />

ወንድሙ ኢብሳ<br />

ስለሞን ስዩም<br />

ኮምፒውተር ጽሑፍ፡-<br />

የሺ ሃብቴ<br />

ብርቱካን መንገሻ<br />

አከፋፋይ፡-<br />

ነብዩ ሞገስ<br />

አሣታሚው፡-<br />

አንድነት ለዴሞክሲና ለፍትህ ፓርቲ(አንድነት)<br />

አድራሻ፡- አራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 07 የቤ.ቁ አዲስ<br />

አታሚ፡- ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት<br />

አራዳ ክ/ከተማ ቀበሌ 07 የቤ.ቁ 984<br />

የዝግጅት ክፍሉ<br />

ስልክ +251 922 11 17 62<br />

+251 913 05 69 42<br />

+251 118-44 08 40<br />

+251 923 11 93 74<br />

ፖ.ሳ.ቁ፡ 4222<br />

ኢሜይል፡- udjparty@gmail.com<br />

andinet@andinet.org<br />

ፋክስ ቁጥር፡- +251-111226288<br />

www.andinet.org.et<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

ርዕሰ አንቀፅ<br />

ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ<br />

ነፃ የሞያ ማህበራት ያስፈልጋሉ!<br />

አገራችን የመድበለ ፓርቲ ሥርዓትን ተቀብላ በሕገ-መንግሥትዋ ካፀደቀች 17 ዓመት ሞላት፡፡ ተግባራዊነቱና<br />

ዕድገቱን ስንመለከት ግን የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት መጀመሩም አጠያያቂ ነው፡፡ ሕገ-መንግሥቱ በተለያየ<br />

ጊዜ በአዋጆች እየተሸረሸረ ነው፡፡ ከፍተኛ የሆነ የሰብአዊ መብት ጥሰት ይፈፀማል፡፡ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት<br />

መገንቢያ ተቋማት ከማስመሰያነት አልዘለሉም፡፡ ዛሬ በአገራችን ነፃ የሲቪክ ድርጅቶች እና ነፃ የሞያ ማህበራት<br />

አሉ ማለት አይቻልም፡፡<br />

በአገራችን ረጅም ታሪክ ያለው የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማሕበር ነበር፡፡ ዛሬ የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማሕበር<br />

ኮንፌዴሬሽንም አለ፡፡ ግን ጥርስ የሌለው አንበሳ ነው፡፡ ከዚህ በፊት ለረጅም ጊዜ የኢትዮጵያ መምህራን ማሕበር<br />

ነበር፡፡ ዛሬም ለስሙ የመምህራን ማሕበር አለ፡፡ ቀደም ሲል ከ30 ዓመት በፊት የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ማሕበር<br />

ነበር፡፡ ዛሬም በቁጥር መብዛት ከሄድን አምስት የጋዜጠኞች ማሕበራት አሉ፡፡ የወጣቶች፣የሴቶች፣የመንፈሳዊ<br />

ድርጅቶች፣የተማሪ ማሕበሮች፣የሰብአዊ መብት ድርጅቶች፣ወ.ዘ.ተ. ነበሩ፡፡ ዛሬም አሉ፡፡ በስም ብቻ መኖራቸው<br />

ግን ፋይዳ የለውም፡፡<br />

ወደ ኋላ መለስ ብለን የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማህበርን በጥቂቱ እናስታውሰው፡፡ በእነ አበራ ገሙ መሪነት<br />

የሠራተኛውን መብትና ጥቅም ለማስከበር ያደረገው እንቅስቃሴ ለዛሬው ኢሠማኮ መፈጠር መሠረት ነው፡፡<br />

የምድር ባቡር ሠራተኞች ማህበር የትግል ታሪክን መጥቀስ ይቻላል፡፡ የሠራተኛውን መብት ለማስከበር ታግለዋል፡<br />

፡ ከነበረው የፊውዳሉ ሥርዓት ጋር ሠላማዊ ትግል አድርገዋል፡፡ መደራጀት መብት መሆኑን አረጋግጠዋል፡<br />

፡ ደርግ ሥልጣን እንደያዘ አካባቢም ቢሆን ቀላል የማይባል መስዋዕትነት ከፍለዋል፡፡ ደርግ ይከተለው<br />

በነበረው ወታደራዊ አመራር የሠራተኛው ተወካዮችና ግንባር ቀደም ተሟጋቾች የቀይ ሽብር ሠለባ ሆነዋል፡፡<br />

መስዋትነታቸው ለሠራተኛው መብትና ጥቅም ሲሉ ቢሆንም ለዛሬው ለመደራጀትም አስተዋጽኦ አድርገዋል፡፡<br />

ደርግ ሥርዓቱን ከተቆጣጠረ በኋላ የሠራተኛ ማህበሩን እንደ አንድ የመንግስት ተቋም እንዲያገለግል<br />

አድርጐታል፡፡ ኢህአዴግ አገሪቱን ከተቆጣጠረ በኋላም ማህበሩን በአዲስ መልክ ለማደራጀት ጥረት ተደርጐ<br />

ነበር፡፡ በዚሁ መሠረት በዘጠኝ ፌዴሬሽኖች የተደራጀው ማህበር የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማህበር ኮንፌዴሬሽን /<br />

ኢሠማኮ/ መሠረተ፡፡ ኢሠማኮ እንደተመሠረተ አካባቢ የሠራተኛውን መብትና ጥቅም የሚያስጠብቁ ጥያቄዎችን<br />

ማንሳት ሲጀምር፡፡ ኢህአዴግ ነፃ ማህበራት እንዳይኖሩ ርምጃ ወሰደ፡፡<br />

እነዚህ ድርጅቶች እያንዳንዳቸው ያሉት እንደ አንድ ነፃ የሲቪክ ድርጅት ወይም እንደ አንድ ነፃ የሞያ ማሕበር<br />

ወይስ እንደ አንድ የመንግሥት ተቋም እያገለገሉ ነው? ብለን ብንጠይቅ መልሱ አጭርና ግልፅ ነው፡፡ እንደ<br />

አንድ መንግሥት ተቋም ሆነው እያገለገሉ ነው ብለን እናምናለን፡፡ ኢመማ ወይም ሌሎች የሞያ ማህበራትንም<br />

ብንመለከት መልሱ ተመሳሳይ ነው፡፡ ምክንያቱም የማሕበሩን አባላት መብትና ጥቅም የሚያስከብር፣በነፃ ምርጫ<br />

በማሕበሩ አባላት ተመርጠው ወደ አመራር በሚመጡ አመራሮች የሚመራ ሳይሆን በድርጅታዊ አሠራርና<br />

ተጽዕኖ ባለበት ምርጫ የሚቋቋሙ አመራሮች ያሉበት ተቋም ሆኖ ይገኛል፡፡ ሥራ አፈጻጸሙም የማሕበሩ አባላት<br />

የሚያነሱዋቸውን ጥያቄዎች በማፈን የሚቆጣጠር ዋና ኃይል ሆኖ የሚያገለግል ነው፡፡ አመራሮቹም ለሞያቸው<br />

ክብር የሚሰጡ፣ለወከሉት ሠራተኛ የቆሙ ሳይሆኑ በአፍቃሬ ኢህአዴግነት ለኢህአዴግ ታማኝ በመሆናቸው<br />

ክብር የሚሰማቸው ናቸው፡፡<br />

የሥርዓቱ ገዢዎች በተደጋጋሚ ሲናገሩ እንደምንሰማው የሠራተኛውን መብትና ጥቅም ለማፈን “ኢንዱስትሪ<br />

ሰላም ነው” ሲሉ ይደመጣሉ፡፡ የማሕበራት ተወካዮችም ይህንኑ ቃል በተደጋጋሚ ያስተጋባሉ፡፡ “የኢንዱስትሪ<br />

ሠላም” ምን ዓይነት ነው? የሠራተኛውን መብትና ጥቅም ወደ ጐን ትቶ የአሠሪውን ጥቅም ብቻ ያስከበረና<br />

የገዢውን የሥልጣን ጥቅም ለማስጠበቅ የታለመ ነው ወይንስ የሠራተኛውን መብትና ጥቅም የሚያስከብር?<br />

መልሱ ሠራተኛው የሥራ ዋስትና አጥቶ ሲበተን የህብረት ስምምነቱ እየተጣሰ መብቱና ጥቅሙ ሲነፈግ፤ ፍትህ<br />

አገኛለሁ ብሎ በየፍ/ቤቱ ሲጉላላ ማህበሩ ዝምታን መርጧል:: በመሆኑም የኢሕአዴግ የእድሜ ክር ቀጣይ እንጂ<br />

የሠራተኛውን መብትና ጥቅም የሚጠብቅ አይደለም፡፡ የይስሙላ “የኢንዱስትሪ ሰላም ነው”<br />

የኢንዱስትሪ ሰላምን በሁለት ከፍሎ ማየት ይቻላል፡፡ ጊዜያዊ ሠላምና ዘላቂ ሠላም ናቸው፡፡ ጊዜያዊ<br />

የኢንዱስትሪ ሠላም የማስመሰያ /አሳሳች/ ሠላም ነው፡፡ የሠራተኛውን ልብ ያልገዛ /የሠራተኛውን ጥቅም<br />

ያልጠበቀ/፣አስተማማኝና ዘላቂ ልማትን የማያመጣ ሠላም ነው፡፡ የመፍጠር ችሎታን የማያበረታታና<br />

ምርታማነትን የማያሳድግ ሠላም ነው፡፡ ዘላቂ የኢንዱስትሪ ሠላም ግን የሠራተኛውን ጥቅምና መብትን<br />

የሚያስከብር፣በሠራተኛው ውስጥ በራስ መተማመንንና መረጋጋትን የሚፈጥር፣የሠራተኛውን የኃላፊነት ስሜት<br />

የሚያስከብር ነው፡፡ ሊኖር የሚገባው ጊዜያዊ ሳይሆን ዘላቂ የኢንዱስትሪ ሠላም ነው፡፡ በሀቅ ላይ የተመሠረተ<br />

ከሆነ የኢንዱስትሪ ሠላም ጥሩ ነው፡፡ ሠላም የሕይወትና የንብረት ዋስትና ይሰጣል፡፡ ሠላም ካለ ልማትና እድገት<br />

አለ፡፡ ሠላም ካለ ቤተሰብ በሰላም ወጥቶ ሠርቶ ይገባል፡፡ ሠላም ከሌለ ሁሉም የለም፡፡ ዛሬ ያለው ሰላም ግን ምን<br />

ዓይነት ሠላም ነው? መብትና ጥቅምን የገፈፈ ሠላም፤የታፈነ ሠላም፤ በቁጭትና በዝምታ የታጀበ ሠላም፤ በፍርሃት<br />

የታጨቀ ሠላም፤አደጋን ያረገዘ ሠላም! እንዲህ ዓይነት ሠላም ውጤቱ የከፋ ስለሚሆን አደጋ ነው፡፡ ጊዜውን<br />

ጠብቆ የሚፈነዳ ሠላም አንሻም፡፡ ጥፋትን በውስጡ አምቆ የያዘ “ሠላም” አያሻንም!<br />

የሚያስፈልገን ሠላም ክፋትንና ጭንቀትን ያስወገደ፣ የዜጐችን መብትና ጥቅም ያስከበረ ሠላም ነው፡፡<br />

የሠራተኛውንና የባለሀብቱን መብትና ጥቅም ፍትሐዊ ያደረገ ሠላም እንሻለን፡፡ የሞያ ማሕበራት የመንግሥት<br />

ጣልቃ ገብነትና ተጽዕኖ የሌለባቸው፣የሥራ ብቻ ሣይሆን ነፃ የምርምር ተቋማት መሆን አለባቸው፡፡ ማህበራት<br />

በነጻነት መደራጀት መቻል አለባቸው፡፡ ይህ እስካልሆነና የማሕብራቱን አባላት መብት እስካላስጠበቀ ድረስ<br />

ኢህአዴግ የሚፈልገው የኢንዱስትሪ ሠላምና የሚመኘው ዕድገት ዘላቂነት አይኖረውም፡፡<br />

የተደራጁት ማሕበራት የአባሎቻቸውን መብት ማስከበር መቻል አለባቸው፡፡ መብታቸውንና ጥቅማቸውን<br />

በመጠየቃቸው አሠሪው ኃይልና መንግሥት በጋራ ሆነው ሠራተኛው ላይ የበቀል ጥቃት ማድረስ መቆም አለበት<br />

ብለን እናምናለን፡፡ ለዚህ ምሳሌ የሚሆነን በዋልዳ ሆጀቶታ ዳንዲ ደራርቱ አርሲ (W H D D A) የቻይና<br />

ሠራተኞች ማሕበር ሠራተኞችና የማሕበሩ አመራሮች ላይ የተወሰደውን ሠራተኞችን ማሰቃየትና የማኅበሩን<br />

የአመራር አባላት የሠራተኛውን መብት እንዳይጠይቁና እንዳያስከብሩ ከሥራቸው በማፈናቀል የተወሰደውን<br />

እርምጃ በጥብቅ እናወግዛለን፡፡ በሌላ በኩልም ጥቃቱም እንዲቆም እንጠይቃለን፡፡ ለደረሰባቸው ጥቃት ካሳ<br />

እንዲከፈላቸው፣ሕክምና እንዲያገኙና መብትና ጥቅማቸው እንዲከበር የሚመለከተው ሁሉ እንዲረባረብ<br />

ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡ እንዲሁም የመደራጀት ጥያቄ አቅርበው የተከለከሉ 120 ሺ መምህራን ጥያቄአቸው<br />

በአግባቡ ሊመለስላቸው ይገባል፡፡<br />

የኢህአዴግ መንግሥት እጁን ከማሕበራት ላይ ያንሳ፡፡ ማሕበራት የመጨቆኛና የማፈኛ ተቋማት መሆን<br />

የለባቸውም ብለን እናምናለን፡፡ በአገሪቱ አስተማማኝ የኢንዱስትሪ ሠላም ኢንዲመጣ ከተፈለገ ሞያ ማህበራት<br />

በነጻነት መደራጀት አለባቸው፡፡ ማህበራት የሠራተኛውን መብትና ጥቅም የማስጠበቅ አቅም ሊኖራቸው<br />

ይገባል፡፡ ጥቅማ ጥቅሞቻቸው መጠበቅ አለባቸው፡፡ የሠራተኛው ሞያዊ አቅምና ሥነልቦና መገንባት አለበት፡<br />

፡ ጠንካራ የሠራተኛ ተወካዮችን ከሥራ ገበታቸው ላይ ማፈናቀልና ለጥቃት መዳረግ የለባቸውም፡፡ ይህ አይነቱ<br />

ሠይጣናዊ ርምጃ በአስቸኳይ መቆም አለበት፡፡ ካልቻለ ግን እንደ አንድነት በአጅጉ ያሳስበናል፡፡ የሞያ ማህበራት<br />

የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ መሠረት ናቸው ብለን እናምናለን፡፡ የሞያ ማህበራት በአገሪቱ ፖለቲካዊ<br />

ኢኮኖሚያዊና ማሕበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል፡፡ የማሕበር አባሎቻቸውን መብትና ጥቅም<br />

አሳልፈው ሰጥተው የመጨቆኛ መሳሪያ፤ የሰብዓዊና የዴሞክራሲያዊ መብት ጥሰት ተባባሪ መሆን የለባቸውም፡<br />

፡ የተቋቋሙለትን ዓላማ በተቃራኒው መፈፀም ነው ብለን እናምናለን፡፡ በመጨረሻም ለመድበለ ፓርቲ ሥርዓትና<br />

ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ መጠናከር ነፃ የሞያ ማህበራት በእጅጉ ስለሚያስፈልጉ እነዚህ ማኅበራት<br />

ከኢሕአዴግ የተፅዕኖ ቀንበር ነፃ እንዲወጡ አብረን እንታገል፡፡<br />

ጋዜጣችን “ፍኖተ-ነፃነት” ብለናታል፡፡ “ፍኖት” ማለት መንገድ ማለት ሲሆን ከነፃነት ጋር<br />

ሲጣመር “የነፃነት መንገድ” ማለት ነው!!<br />

ነፃ አስተየት<br />

ታደሰ ፍስሐ<br />

ለማን አቤት<br />

እንበል?<br />

2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />

ኢትዮጵያውያን ብዙ ጮኽን ያዳመጠን ግን የለም፡<br />

፡ ለሰው ጩኽን፤ ለፈጣሪ ጩኽን፤ ለመሬትም ጮህን፤<br />

አንዳች ምላሽ በመሻት፤ ጩኽታችን ግን ለሠማይና<br />

ለምድርም ጮህን፤ ጩኸታችን ግን የቁራ ጩኽት ሆኖ ቀረ፡፡<br />

የተፈረደብን የመከራ ዘመን ከማለቅ ወይ ከመገባደድ ይልቅ<br />

እየጨመረ ሄደ፡፡<br />

በግልፅ የሚታየውን ችግራችንን፣ ከፊታችን ሳይቀር<br />

የሚነበበው ጉስቁልናችን፣ ሚሊዮኖችን ምርኮኝ ያደረገ<br />

ርሃባችን፣ ፀሐይ የሞቀው የርስበርስ ፍጅታችንን ደመናን<br />

ቀርቶ የጎጇችንን ጣሪያ ማለፍ የተሳነው ምህላና ፀሎታችን<br />

ብዙዎች በየቀኑ ሽቅብ የምንረጨው እንባችን፤ ሁሉም<br />

በማንም ዘንድ ተሰሚነት አላገኘም፡፡ አሁንም ለቅሶና<br />

ዋይታችን ተባብሶ እንደቀጠለ ነው፡፡<br />

ተንኮለኞች ያጠመዱትን ወጥመድ የደገሱልን መከራና<br />

የሰቆቃ ድግስ ከዘመናት በፊት በሴራ መክረው ያወጁብን<br />

የጥፋት ዘመን በብሄርና በጎሳ ከፋፍለው የኢትዮጵያን<br />

አንድነት ለመነጣጠል በመካከላችን የከተቱብን የተኩላ<br />

መንጋ ሁሉም እንዳሰቡት ሆኖ ትንቢታቸው ሲይዝላቸውና<br />

ምኞታቸው ሲሳካላቸው በስቃያችን ይደሰታሉ፡፡ በቁስላችን<br />

የጋለ ብረት እየሰደዱ ለቅሷችንን እንደ ጥጋብ፣ ጭንቀት<br />

ጥበታችንን እንደ ደስታ፣ ጦርነታችንን እንደ መዝናኛ፣<br />

መባዘናችንን እንደ በረከት፣ የርስ በርስ እልቂታችንን<br />

እንደሰላም በመቁጠር ያላግጡብናል፡፡ እውነቱን የማያውቁ<br />

ይመስል የላኳቸውን እንደራሴዎች የሚሰሩትን የማይረዱ<br />

ይመስል፡፡ የእኛን መከራና ችግር እንደማያውቁ ሆነው<br />

በመቆለል በጣት የሚቆጠሩ የተሻለ ኑሮ የሚኖሩ በገጠር<br />

በግብርና የሚተዳደሩትን ከተማ ያሉ ሃብታችን በመመልከት<br />

ብቻ ጥሩ ኑሮ ላይ ነን ይላሉ፡፡ እነዚያም ተቀብለው<br />

“ይኽ መቸ አነሳችሁ፤ ጥሩ ኑሮ እየኖራችሁ ነው” በማለት<br />

ይሳለቁብናል፡፡<br />

ጥቂት የምትባል የመናገር፣ የመፃፍ ግድብ (ዴሞክራሲ)<br />

መብት በማየት ብቻ ዴሞክራሲያችን እዚህ ደርሷል<br />

በማለት አዎንታዊ አብነት ወስደው ከእኛ አልፈው<br />

ለሌሎች አገሮች ማስተማሪያ ሊሆን እንደሚገባ ይሰብካሉ፡<br />

፡ ይህ ድርጊታቸው በዴሞክራሲ ላይ ብቻ ሳይሆን በሰው<br />

ልጆችም ላይ እንደማፌዝ የሚቆጠር ከመሆኑም በተጨማሪ<br />

ለይስሙላ ያህል በውሸት በሚያመልኩት በእግዚአብሄርም<br />

ዘንድ በእጅጉ አስነዋሪና ሃጢያት መሆኑን ሊገነዘቡት<br />

ይገባቸው ነበር፡፡ ፈጣሪ የሰውን ልጅ በቀለምና በዘር<br />

በስልጣኔና በመልካም ምድር ልዩነት እየፈጠራችሁ ተፋጁ<br />

(አፋጁ) አላለም፡፡ ከዚህ ነጥብ አኳያ ተምረዋል የተባሉት<br />

አማረዋል፡፡ እነዚህ ወገኖች እየሰሩት ያለው ግፍና በደል<br />

ሲጤን መሰልጠናቸው ሳይሆን መስይጤናቸውንና ፀረ<br />

ሰውም፣ ፀረ ፈጣሪም መሆናቸውን የሚያሳይ ነው፡፡<br />

ሀገራዊም ሆነ አለም አቀፋዊ ሁኔታዎች ለእኛ<br />

ለኢትዮጵያውያን የሚመቹ ባለመሆናቸው ተናግረን<br />

የምንደመጥበት፣ አኩርፈን የምንጠጋበት፣ ፍትህን<br />

የምናገኝበት አንድም አለኝታ የለንም፡፡ ሁሉም ነገር<br />

ያዘነበለው ወደ ገዢዎቻችን በመሆኑ የችግራችን መጠን<br />

ስፋትና ጥልቀት ተነግሮ አያልቅም፡፡ ፈጣሪ ጭምር አስጨናቂ<br />

ዘመን እንድንገፋ የፈረደብን ይመስላል፡፡ ከታሰርንበት<br />

የኑሮ ሰንሰለት ከገባንበት ምድራዊ ሲኦል ነበልባላዊ እቶን<br />

የሚታደገን ከቶ ማነው? ዳዊት በመዝሙሩ አቤቱ ጌታ ሆይ<br />

እስከመቼ ነው የምትተወኝ ያለው ወዶ አይደለም፡፡ እንደኛ<br />

ክፉኛ ቢጨንቀው እንጂ፡፡ በርግጥ መከራ ሲበዛ ያነሆልላል፤<br />

ስቃይ ሲበዛ መፈጠርን ያስረግማል፤ ግፍና በደል ከአንድ<br />

ሰው የመሸከም አቅም ሲያልፍ ራስን ብቻ ሳይሆን ፍጣሪን<br />

ድረስ ሊያስክድ ይደርሳል፡፡<br />

ምንም እንኳን “እረኛ ቢያኮርፍ ምሳው እራት ይሆነዋል”<br />

እንዲሉ አኩራፊ ቢያኮርፍ ከራሱ በላይ የሚጎዳው<br />

ባይኖርም የችግሩ ክረት ፈጣሪን እስከ መውቀስ ቢያደርሰው<br />

ቢያንስ ሊያስነውረው የሚገባ አይመስለኝም፡፡ በክርስቲያኑ<br />

ህይወት እንግልትና የቁም ስቅልን የሚያሳይ አሳር ሲገጥም<br />

በመፅናናት የሚጠቀስ አንድ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ምሳሌ ነው፡<br />

፡ የኢዮብ ስቃይ ከእኛ ከኢትዮጵያውያን ስቃይ ማወዳደር<br />

የሚቻል አይመስለኝም፡፡ ለዘመንም ሆነ ከሌሎች መሰል<br />

ፖለቲካዊና ሃይማኖታዊ ችግሮች አንፃር የኢዮብን ከእኛ<br />

አስቸጋሪ ህይወት ላነፃፅር አልችልም፡፡<br />

የመከራ ዶፍ የወረደበት ኢዮብ በደረሰበት ስቃይ<br />

ሰማይ ምድሩ ተደፍቶበት ጭንቅ ውስጥ በነበረበት ወቅት<br />

ከተናገረው ጥቂት እናስታውስና እኛ ከተዘፈቅንበት የችግር<br />

ማጥ አኳያ ብሶት ምን ያህል እንደሚያናግር እንመልከት፡፡<br />

ከችግርና ከረሃብ ብዛት የተነሳ በለሊት ተነስተው ወደ<br />

በረሃ እየሄዱ<br />

ስራ ስሮችን ያኝኩ ነበር፡፡<br />

ጨው ጨው የሚል የበርሃ ቅጠላ ቅጠሎን ይለቅሙ<br />

ነበር፡፡<br />

ሰዎች ሌቦችን እየጮሁ እንደሚያባርሩ<br />

እነርሱም ከህብረተሰቡ መካከል ያባርሯቸው ነበር፡፡<br />

መኖሪያቸውም በየዋሻውና በየገደሉ ስር በተቆፈረ<br />

ጉድጓድ ውስጥ ነበር፡፡<br />

ወደ 10 ዞሯል


2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />

ፖለቲካ<br />

ግርማ ሞገስ<br />

(girmamoges1@gmail.com)<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

የዚህ ጽሑፍ ግብ የሰላም ትግል<br />

ለውጥ ማምጫ መንገዶች (Mechanisms<br />

of change) በኢትዮጵያ እንዴት ህዝብን<br />

የመንግስት ስልጣን ባለቤት ሊያደርጉ<br />

እንደሚችሉ በማጥናት በኢትዮጵያ የፖለቲካ<br />

ትግል እና የመንግስት ሽግግር ለማድረግ<br />

ሰላማዊ ትግል ማደረግ እንደሚቻል እና<br />

ተመራጩ የትግል ስልትም እሱ መሆኑን<br />

ማሳየት ነው።<br />

የሰላም ትግላችን ግብ ህዝብን የመንግስት<br />

ስልጣን ባለቤት ማድረግ ነው። ህዝብን<br />

የመንግስት ስልጣን ባለቤት ለማድረግ የሰላም<br />

ትግል በህዝብ እና በአምባገነን መንግስት<br />

መካከል የሚገኘውን የፖለቲካ ኃይል ሚዛን<br />

ግንኙነት ወደ ህዝብ እንዲያደላ ማድረግ<br />

አለበት። የሰላም ትግል ይኽን አስፈላጊ<br />

የሆነ የፖለቲካ ኃይል ሚዛን ግንኙነት<br />

ሽግሽግ (ለውጥ) ተፈጻሚ የሚያደርገው<br />

በአራት መንገዶች እንደሆነ ጅን ሻርፕ<br />

(Gene Sharp) አጥንቶ ለአለም የዲሞክራሲ<br />

ኃይሎች እና ተመራማሪዎች ካበረከተ<br />

ውሎ አድሯል። እነሱም፥ (1ኛ) የመቀየር/<br />

የመለወጥ (Peaceful conversion)፣ (2ኛ)<br />

የመቻቻል (accommodation)፣ (3ኛ)<br />

ሰላማዊ አስገዳጅነት (Peaceful coercion)<br />

እና (4ኛ) ሰላማዊ መፈረካከስ/መበታተን<br />

(Peaceful disintegration) የተባሉት<br />

ናቸው። እነዚህ ሰላማዊ ለውጥ ማምጫ<br />

መንገዶች ከሰላም ትግል መሳሪያዎች ጋር<br />

ዝምድና አላቸው። የሰላም ትግል መሳሪያዎች<br />

ሶስቱ አብይ ክፍሎች (1ኛ) ተቃውሞ እና<br />

ማግባባት (Protest and Persuasion)<br />

እስከዚኽ ድረስ እንዳየነው መቀየር/መለወጥ (Peaceful<br />

conversion) የተባለውን የለውጥ ማምጫ መንገድ ፕላን ቀይሰን<br />

በአግባብ እና በቀጣይነት ከተጠቀምንበት የዲሞክራሲ ትግልን በህብረተሰቡ ውስጥ<br />

ለማስፋፋት እና የህብረተሰቡን የሰላማዊ ትግል አቅምን ለመገንባት ይጠቅማል።<br />

ነገር ግን ይኽ ለውጥ የማምጫ ሰላማዊ መንገድ በአምባገነኖች የፖለቲካ ኃይል<br />

ምንጮች ላይ የሚያደርሰው ቀጥተኛ ጥቃት የለም። ጥቃቱ ተዘዋዋሪ ነው። ለጥቀን<br />

መቻቻል የተባለውን ለውጥ ማምጫ መንገድ እንመልከት።<br />

የሠላም ትግል ለውጥ ማምጫ አማራጭ<br />

መንገዶች በኢትዮጵያ<br />

፣ (2ኛ) ትብብር መንፈግ (noncooperation)<br />

፣ (3ኛ) ጣልቃ መግባት<br />

(intervention) እንደሆኑ እና ዝርዝራቸው<br />

ወደ 200 ግድም እንደሚደርስ በፍኖተ ነፃነት<br />

ቁጥር 13 “የሰላም ትግል መሳሪያዎች” በሚል<br />

ርዕስ ቀርቧል። እነዚኽ አራት ለውጥ ማምጫ<br />

መንገዶች ከሰላማዊ ትግል አቅም ግንባታ<br />

አንስቶ እስከ መንግስት ሽግግር ፍጻሜ ድረስ<br />

እንዴት አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉ ባጭር<br />

ባጭሩ እንመልከት።<br />

(1ኛ) መቀየር/መለወጥ (Peaceful<br />

conversion)<br />

የዲሞክራሲ ኃይሎች ያቀረቡትን የለውጥ<br />

አሳብ ወይንም የለውጥ ጥያቄ መንግስት<br />

ቢቀበል እሱም ተጠቃሚ ሊሆን እንደሚችል<br />

መንግስትን ማሳመን (መቀየር/መለወጥ)<br />

የሚቻልበት ሁኔታዎች (መንገዶች) ሊኖሩ<br />

ይችላሉ። ይኽን በማድረግ የዲሞክራሲ<br />

ኃይሎች ከሚያገኙዋቸው ፋይዳዎች ውስጥ<br />

ጥቂቱ፥ በህዝብ እና በመንግስት ዘንድ<br />

የተቃዋሚ መሪዎችን ህጋዊነት ከፍ ማድረግ፣<br />

ከመንግስት ጋር ሊደረጉ የሚችሉ ግጭቶችን<br />

መቀነስ፣ የሰላማዊ ትግልን የሰው እና የቁሳቁስ<br />

አቅም በረባ ባልረባው ሁሉ እንዳይባክን<br />

ማድረግ ናቸው።<br />

ርግጥ ይኽ መንገድ በመንግስት ላይ<br />

የሚያሳድረው ጫና (ክብደት) በጣም<br />

ዝቅተኛ በመሆኑ የሚያስገኘው ጠቀሜታ<br />

እዚህ ግባ የማይባል ሊሆን ይችላል።<br />

ያም ሆኖ ግን የተመረጠው የለውጥ ጥያቄ<br />

የአምባገነኖችን ስልጣን አደጋ ላይ የማይጥል<br />

እና የጥያቄው አቀራረብ ብልህ እስከሆነ<br />

ድረስ አልፎ አልፎም ቢሆን ጠቃሚ<br />

ውጤት አይገኝም ማለት ያስቸግራል።<br />

ለውጥ የተገኘበት ጊዜ አለ። ምሳሌ፥ እንደ<br />

አውሮፓ አቆጣጠር በ1962 ዓመተ ምህረት<br />

ቀድሞ የእንግሊዝ ቅኝ አገር በነበረችው<br />

በርማ ውስጥ በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን<br />

ላይ የወጣው ወታደራዊ አምባገነን ቡድን<br />

መጀመሪያ ከያዘው አቅዋም ከጊዜ በኋላ<br />

እንዴት እንደተለወጠ እንመልከት።<br />

ስልጣን እንደጨበጠ፣ የእንግሊዘኛ<br />

ቋንቋ ትምህርት በአንደኛ ደረጃ እንዳይሰጥ<br />

አደረገ። በዩንቨርስቲ ደረጃም የሚሰጥ<br />

የእንግሊዘኛ ቋንቋ ዝቅ እንዲል አደረገ።<br />

ወታደራዊው መንግስት ለህዝብ የሰጠው<br />

ሃሰተኛ ምክንያት “እንግሊዘኛ ቋንቋ የቅኝ<br />

ግዛት ዘመን ውርደታችን ማስታወሻ በመሆኑ<br />

መወገድ አለበት” የሚል ሲሆን ሃቀኛው<br />

ምክንያት ግን በመምህርነት ስራ የተሰማሩትን<br />

እና ኗሪ እንግሊዞችን ከአገር በማስወጣት<br />

የበርማን ህዝብ ከውጪው አለም ፖለቲካ<br />

ተጽእኖ ለማፈን (Censorship) ነበር። ይኽ<br />

ፖሊሲ የበርማ ተማሪዎችም ወደ ምዕራቡ<br />

አለም እንደቀድሞው እንደልብ እየወጡ<br />

ከፍተኛ ትምህርት ለመማር በቅድሚያ<br />

ማለፍ ያለባቸውን የእንግሊዘኛ ቋንቋ ፈተና<br />

ማለፍ እንዳይችሉ ማድረግ ጀመረ። በበርማ<br />

እንግሊዘኛ ቋንቋ መናገር የሚችሉ ተወላጅ<br />

የቢሮ አስተዳዳሪዎች ማግኘት አስቸጋሪ<br />

መሆን በመጀመሩ የውጭ አገር ኢንቨስተሮች<br />

ወደ በርማ መምጣት አቆሙ። የአገሪቱ<br />

ኢኮኖሚ ተንኮታኮተ። በዚኽ አይነት<br />

ለስልጣኑ መጠናከር ሲል ለ20 አመቶች<br />

ያህል አለም አቀፍ የቢዝነስ እና የንግድ<br />

ቋንቋ በበርማ እንዲዳከም ካደረገ በኋላ ይኽ<br />

ፖሊሲ በአገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ያስከተለው<br />

አሉታዊ ተጽእኖ ለአምባገነኖቹ ገዢዎች<br />

ወለል ብሎ ይታያቸው ጀመረ። የበርማ<br />

የንግዱ ማህበረሰብ እና የዲሞክራሲ ኃይሎች<br />

በእንግሊዘኛ ቋንቋ ትምህርት ላይ የተጣለው<br />

ገደብ እንዲነሳ ያቀርቡት የነበረውን የለውጥ<br />

ጥያቄ የበርማ አምባገነን መንግስት ተቀበለ።<br />

አምባገነኑ የበርማ መንግስት የለውጡን<br />

ጥያቄ የተቀበለው ለውጥ ቢያደርግ ተጠቃሚ<br />

መሆኑን በመገንዘቡ ነበር።<br />

የሰላም ትግል የመንግስት ባለስልጣኖችን<br />

ብቻ ሳይሆን ህዝብንም በመቀየር/በመለወጥ<br />

ለዲሞክራሲ ትግል መስፋፋት እና አቅም<br />

ግንባታ ጥቅም ይሰጣል። መንግስት በህዝብ<br />

ላይ የሚፈጽማቸው በደሎች፣ ዲሞክራሲ<br />

የሚሰጠው ጠቀሜታ እና ዛሬ በአለም ውስጥ<br />

እየተደረገ ስላለው የለውጥ እንቅስቃሴ<br />

እና ስለመሳሰሉት በሰፊው ማሰራጨት<br />

ህዝብ ለመለውጥ ያግዛል። በአለም ውስጥ<br />

ስለሚሆነው እና በአገር ስለሚፈጸም ሰላማዊ<br />

ሰልፎች፣ ተቃውሞዎች፣ ህዝባዊ ውይይቶች<br />

እና ተመሳሳይ የሰላማዊ ትግል ዜናዎች<br />

የህዝብን ዝንባሌ እንደሚቀይሩ እና ከፍራቻ<br />

ነፃ ለመውጣት እንደሚያግዙ መረሳት<br />

የለበትም። በዚህ ረገድ ድረ ገጾች፣ የህትምት<br />

እና የኤሌክትሮኒክ ሚዲያዎች ከፍተኛ<br />

ሚና አላቸው። ለዚህም ነው አምባገነኖች<br />

የሚያፍኗቸው።<br />

አምባገነኖች በሰላም ትግል ታጋዮች ላይ<br />

የሚፈጽሙት ግፍ እና የሰላም ትግል ታጋዮች<br />

የሚያሳዩት ጀግንነት ህዝብን በመለወጥ<br />

የዲሞክራሲ ትግሉን ያጠናክራል። በዚህ<br />

ረገድ በህዝብ ዘንድ ጀግንነት ተደርገው<br />

የሚወሰዱ ርምጃዎች ሌላውን የመለወጥ<br />

አቅም እንዳላቸውም መረሳት የለበትም።<br />

ምሳሌ፥ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር<br />

በ1950 ዎቹ እና 1960ዎቹ አፍሪካ<br />

አሜሪካውያን መንግስት በሚለቅባቸው<br />

ተናካሽ ውሻዎች መነከሳቸው፣ በእሳት አደጋ<br />

መኪናዎች በሚረጭ ውሃ መደብደባቸው፣<br />

ማታ ማታ በሰላም ትግል መሪዎች ቤቶች<br />

ላይ ይደርስ የነበረው ቃጠሎ፣ የሰላም<br />

ትግል ሰራዊት በሚሰበሰብባቸው ቤተ<br />

ክርስቲያኖች ላይ ይደርስ የነበረው ፈንጂ እና<br />

ቃጠሎ ሳይገታቸው በጀግንነት ለእኩለንት<br />

ያደረጉዋቸው ትግሎች ህዝባቸው ብቻ<br />

ሳይሆን ነጭ አሜሪካውያንን እና የቀረውን<br />

አለም ህዝብ በመለወጥ ከአፍሪካውያን<br />

አሜሪካውያን ጎን እንዲቆም አድርጓል።<br />

ሌላ ምሳሌ፥ ግብጾች መንግስት ሳያስፈቅዱ<br />

በነፃነት አደባባይ መስፈራቸው እና<br />

ነፃነታቸውን ማወጃቸው ብዙ ግብጻውያንን<br />

እንደለወጠ እና ሰላማዊ ትግሉን እንዲቀላቀሉ<br />

እንዳደረገ የምናውቀው ትኩስ ዜና ነው።<br />

እንዲሁም በድስፕሊን የታነጸ የሰላም<br />

ትግል ሰራዊት በአምባገነኖች እየተዋከበ፣<br />

ሳያስር እየታሰረ እና እየተገደለ፤ በጀግንነት<br />

ሰላማዊ ትግሉን በቀጣይነት ሲያኪያሂድ<br />

ሲያዩ የጨቋኙ መንግስት አባላት (የጦር<br />

መኮንኖች፣ ሚንስትሮች፣ ዲፕሎማቶች፣<br />

ወ.ዘ.ተ.) እንዲሁም የተባበሩት መንግስታት፣<br />

የምዕራቡ አለም መሪዎች፣ የመብት ተሟጋች<br />

ድርጅቶች ወ.ዘ.ተ. ሳይቀሩ እየተለወጡ<br />

ሰላማዊ ትግሉን ይቀላቀላሉ። ለምሳሌ<br />

የሊቢያው ጋዳፊ በሰላማዊ መንገድ አደባባይ<br />

ወጥቶ ነፃነቱን በጠየቀ ህዝብ ላይ አረመኒያዊ<br />

ጦርነት ሲያውጅ በጋዳፊ መንግስት ውስጥ<br />

በአገር ውስጥ የነበሩ ባለስልጣኖች እና<br />

ዲፕሎማቶች ሰላማዊ ትግሉን ተቀላቅለዋል።<br />

በየመንም አምባገነኑ የሳላህ መንግስት በሰንዓ<br />

(ለውጥ አደባባይ) እና በታኤዝ ከተሞች<br />

በሰፈረው ሰላማዊ ታጋይ ላይ ግድያ በፈጸመ<br />

ቁጥር ተመሳሳይ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል።<br />

እስከዚኽ ድረስ እንዳየነው መቀየር/<br />

መለወጥ (Peaceful conversion)<br />

የተባለውን የለውጥ ማምጫ መንገድ<br />

ፕላን ቀይሰን በአግባብ እና በቀጣይነት<br />

ከተጠቀምንበት የዲሞክራሲ ትግልን<br />

በህብረተሰቡ ውስጥ ለማስፋፋት እና<br />

የህብረተሰቡን የሰላማዊ ትግል አቅምን<br />

ለመገንባት ይጠቅማል። ነገር ግን ይኽ ለውጥ<br />

የማምጫ ሰላማዊ መንገድ በአምባገነኖች<br />

የፖለቲካ ኃይል ምንጮች ላይ የሚያደርሰው<br />

ቀጥተኛ ጥቃት የለም። ጥቃቱ ተዘዋዋሪ<br />

ነው። ለጥቀን መቻቻል የተባለውን ለውጥ<br />

ማምጫ መንገድ እንመልከት።<br />

(2ኛ) መቻቻል (Peaceful<br />

accommodation)<br />

አንዳንድ ጊዜ አምባገነናዊ መንግስቶች<br />

በዜጎች ዘንድ ላገር አሳቢ መስሎ ለመታየት፣<br />

በውጭ መንግስታት ዘንድ ተቀባይነት<br />

ለማግኘት ወይንም የገጠማቸውን የለውጥ<br />

ጥያቄ ውጥረት ለማርገብ ሲሉ የዲሞክራሲ<br />

ኃይሎችን ጥያቄዎች ይቀበላሉ። ይኽን<br />

የሚያደርጉት መብት አክባሪ እና ትሁት<br />

በመሆናቸው ሳይሆን ለተቃዋሚዎች የለውጥ<br />

ጥያቄ የመቻቻል መፍትሄ ብንሰጥ ስልጣናችን<br />

አይነጠቅም፣ አቅማችንም አይዳከምም ነገር<br />

ግን ከጭቅጭቅ እንድናለን ከሚል እምነት<br />

ነው። ይሁን እንጂ አንድ አምባገነን መንግስት<br />

መቻቻልን እንደመፍትሄ ከወሰደ በስልጣን<br />

ላይ የነበረው ፍጹም የሆነ ቁጥጥር ተቀንሷል<br />

ማለት ነው። በህዝብ እና በአምባገነኖች<br />

መካከል በነበረው የኃይል ሚዛን ግንኙነት<br />

ላይ የተወሰነ ሽግሽግ ተደርጓል ማለት ነው።<br />

ለምሳሌ የስራ ማቆም አድማዎችም ቆመው<br />

ሰራተኞች ወደ ስራ የሚመለሱት በአሰሪና<br />

በሰራተኞች መካከል በሚደረግ መቻቻል<br />

ነው።<br />

5<br />

በአገሮች መካከልም መቻቻል ይደረጋል።<br />

የቻይና መንግስት ጥቂት የፖለቲካ እስረኛ<br />

በመፍታት በምዕራቡ አለም የሚቀርብበትን<br />

የሰብዓዊ መብት ማሻሻል ጥያቄ ለማርገብ<br />

ሲሞክር እናያለን። ምዕራቡም ለጊዜው ዝም<br />

ይላል። በምዕራቡ እና በቻይና መንግስት<br />

መካከል መቻቻል ተደረገ ማለት ነው።<br />

የቻይና መንግስት ይኽን የሚያደርገው<br />

በምዕራቡ አለም ተገዶ (Coerced ሆኖ)<br />

ሳይሆን የቀረበው የመብት ጥያቄ ከምዕራቡ<br />

አለም ጋር ካለው የንግድ እና ሌሎች ጉዳዮች<br />

ጋር እየተወሳሰበ እንደልብ አላራምድ<br />

ስለሚለው ነው። ስለዚኽ ለምዕራቡ ጥያቄ<br />

የመቻቻል ምላሽ በመስጠት ንግዱን እና<br />

ሌሎች የሚጠቅሙትን ነገሮች ያደርጋል።<br />

ምርጫም መቻቻል ነው። በየአምስት<br />

ወይንም አራት አመቶች የሚደረግ ምርጫ<br />

ተቃዋሚ ፓርቲዎች ለሚያቀርቡት የፖለቲካ<br />

ለውጥ ጥያቄ አምባገነን መንግስቶች<br />

የሚሰጡት የመቻቻል መልስ ነው። ይሁን<br />

እንጂ ከተመክሮ ማነስ የተነሳ የተቃዋሚ<br />

ፓርቲ መሪዎች ምርጫው ነፃ እና ፍትሃዊ<br />

ይሆናል፣ ከምርጫው ጋር በተያያዘ<br />

መንግስት የሚፈጽመውን ወከባ ህዝቡ<br />

መቋቋም ይችላል ወይንም አለም አቀፍ<br />

ታዛቢዎች የምርጫውን ድምጽ ቆጠራ<br />

እንዳይሰረቅ ያደርጋሉ ብለው ይገምታሉ።<br />

ይኽ የዋህነት ነው። አምባገነኖች ነጻ ምርጫ<br />

ተደርጎ ስልጣናቸውን በፈቃዳቸው ይለቃሉ<br />

ብሎ መገመት ስህተት ነው። ሳይገደዱ<br />

በፈቃደኛነት ስልጣን ማስረከብ የአምባገነኖች<br />

ጸባይ አይደለም። አምባገነኖች ዲሞክራቶች<br />

አይደሉም። አምባገነኖች ስልጣን ላይ<br />

የሚወጡት በግድያ እና በሽብር ነው።<br />

በስልጣን ለመቆየትም መንግስታዊ ሽብር<br />

ይፈጽማሉ። ምርጫም ከሆነ የሚያግዳቸው<br />

ኃይል ከሌለ ድምጽ ይሰርቃሉ። እንደ<br />

አውሮፓ አቆጣጠር በ2000 ዓመተ ምህረት<br />

በሰርቢያ እና በ2002 ዓመተ ምህረት<br />

በዝንባቡዌ የተደረጉት ምርጫዎች በንፅፅር<br />

ማየት ይጠቅማል። ሁለቱም ምርጫዎች<br />

በስልጣን ላይ በነበሩት አምባገነኖች<br />

ተሰርቀው ነበር። ይሁን እንጂ በሰርቢያ<br />

የህዝብን ድምጽ ማስከበር ሲቻል በዝንባቡዌ<br />

ግን ያን ማድረግ ሳይቻል ቀርቷል። ስለዚኽ<br />

የሁለቱ ምርጫዎች የመጨረሻ ውጤት<br />

ሊለያይ ቻለ። እንመልከት።<br />

በሰርቢያ ተቃዋሚው በመላ አገሪቱ<br />

የምርጫ ታዛቢዎች አሰልጥኖ አሰማራ።<br />

ህዝቡ ንቅል ብሎ ወጥቶ ድምጹን እንዲሰጥ<br />

የሚያነሳሳ እና የሚቀሰቅስ የሰላማዊ የምርጫ<br />

ሰራዊት አሰልጥኖ በመላ አገሪቱ አዘመተ።<br />

መንግስት ድምጽ ቢሰርቅስ ብሎ ቀደም ብሎ<br />

በማሰብ ተቃዋሚው ድምጽ “ለማስከበር<br />

ፕላን ለ” (Plan B) አዘጋጅቶ ነበር። አንድ<br />

መንግስት የህዝብ ድምጽ አላከብርም ካለ<br />

ህዝቡም በበኩሉ ለመንግስት የለገሰውን<br />

የገዢነት ክብር እና ህጋዊነት የመንፈግ መብት<br />

አለው። ስለዚኽ “ፕላን ለ” (Plan B) ድምጽ<br />

ለማስከበር የሚደረግ የፖለቲካ እምቢታ፣<br />

ትብብር የመንፈግ እና የጣልቃ መግባት<br />

የሰላም ትግል መሳሪያዎችን የሚጠቀም<br />

ሰላማዊ ትግል ነው። በየምርጫ ጣቢያው<br />

የተመደቡ የተቃዋሚ ታዛቢዎች በድምጽ<br />

ቆጠራው ላይ በመሳተፍ ቆጠራው እንዳለቀ<br />

በዚያው ምሽት ውጤት በየጣቢያው ይፋ<br />

እንዲሆን አደረጉ። በመጨረሻ በሞሊሶቪች<br />

ይመራ የነበረው አምባገናንዊ መንግስት<br />

የምርጫው ውጤት እንደፈለገው ሳይሆን<br />

በመቅረቱ አይኑን በጨው አጥቦ አሸንፌያለሁ<br />

ቢልም በምርጫው እለት ምሽት በየምርጫ<br />

ጣቢያው ድምጽ ይፋ ተደርጎ ስለነበር ህዝቡ<br />

“ድምጽ ይከበር” አለው። ተቃዋሚው ቀደም<br />

ብሎ ያዘጋጀውን በሚሊዮኖች የሚቆጠር<br />

ወደ 13 ይዞሯል<br />

www.andinet.org.et


6<br />

www.andinet.org.et<br />

በማህበራችሁና በቻይና ኩባንያ በሚሰሩ ዜጐቻችን ላይ ከፍተኛ<br />

በደልና ግፍ እየተፈፀመ ነው ይባላል፡፡ እውነት ነው፡፡ ካለስ<br />

የሚፈፀመው በደል ምንድነው?<br />

- እውነት ነው፡፡ እጅግ አሰቃቂ ግፍ እየተፈጸመብን ነው፡፡<br />

ዋናው ጉዳይ ቻይናውያን በእኛ ሕግ ተዳደሩ ይሉናል፡፡ እኛ<br />

ደግሞ የለም፤ በአገራችን ሕገ-መንግሥትና በአዋጅ 377/96<br />

ሕግ መሠረት እንተዳደር እንላለን፡፡ ሕገ መንግሥቱ አንቀጽ<br />

55/ን/አ/3 የተሰጠን የዜግነት መብት ይከበርልን እንላለን፡<br />

፡ ቻይናውያን ሕገ-መንግሥታችሁንም የአዋጅ ሕጋችሁንም<br />

አናውቅም ብለው በገዛ አገራችን እንደ ዕቃ እየተጫወቱብን<br />

ነው፡፡ በጉልበታችን፤ በጊዜአችንና በሞራላችን ላይ ብቻ ሳይሆን<br />

የሰብአዊና የዴሞክራሲያዊ መብት ጥሰት፣የአካል ጉዳትና በሴት<br />

እህቶቻችን ላይ የፆታ ጥቃት እየተፈፀመ ነው፡፡<br />

የውል ስምምነት የላችሁም? ከሌላችሁስ እንዲኖራችሁ<br />

አልሞከራችሁም?<br />

- በአገራችን ካለው የሥራ እጦት መጀመሪያ ስንቀጠር ሠርተን<br />

እንብላ እያልን ተቀጠርን፡፡ መብታችን አልከበር ሲል፤ጥቃት<br />

ሲደርስብን፤በማህበር ተደራጅተን መብታችንን ለማስከበር<br />

ሞክረን፡፡ የሰራተኛው ብዛት 720 /ሰባት መቶ ሃያ/ ነው፡፡ 3 ጊዜ<br />

ማሕበሩን ለማፍረስ ተሞከረ፡፡ ሆኖም ግን አልቻሉም፡፡ ቀጥሎ<br />

እየነጣጠሉ ማጥቃት ጀመሩ፡፡<br />

የማሕበሩ አመራር በመሆኑ የደረሰ የተለየ የሚባል ጥቃት አለ?<br />

በማስረጃ ሊገልጹልኝ ይችላሉ?<br />

- አዎ፡፡ የማሕበራችን መስራች የሆነው አቶ አረጋኸኝ ተፈሪ<br />

የሚባል የ24 ዓመት ወጣት አለ፡፡ ማሕበሩን ለምን አቋቋምክ?<br />

ለምን አታፈርስም? ብለው ቢያዙት እንቢ በማለቱ የተወሰደበትን<br />

ጥቃት ልንገርህ፡፡ ሚስተር ማ የሚባል ቻይናዊ ከአንድ ሺ<br />

ኪ.ግ በላይ የሆነ የስሚንቶ ማቡኪያ በሃፍቼ ፔን ማሽን ብድግ<br />

ካደረገ በኋላ ከሥር ሆነህ ስሚንቶውን ፈቅፍቅልኝ አለው፡<br />

፡ ይህ ሠራተኛ በታዘዘው መሠረት ከሥር ገብቶ ስሚንቶውን<br />

መፈቅፈቅ ጀመረ፡፡ ማሽኑን አውርዶ አስቀመጠበት፡፡ አረጋኸኝ<br />

ከሥር ሆኖ በሲቃ ሲጮህ ለ49 ደቂቃ በላዩ ላይ አስቀመጠበት፡<br />

፡ አረጋኸኝ ከዚያ ሲወጣ ከሰውነቱ ሦስት አጥንት ወጥቷል፡፡<br />

ሽንቱን መቆጣጠር አልቻለም፡፡ ዛሬ አይነምድሩን እናቱ በጓንት<br />

ያፀዳዱለታል፡፡ የህክምና ፋይሉ ዮርዳኖስ ሆስፒታል ይገኛል፡<br />

፡ ዮርዳኖስ ሆስፒታል 15 ቀን ካስተኙት በኋላ አውጥተው<br />

እንዲሞት ተፈልጐ በአንድ ሆቴል ለ3 ቀን አስተኙት፡፡ ሆኖም<br />

ግን በቤተሰብ ጥረት ተረፈ፡፡ ማህበራችንን ከመሠረቱት ሰባት<br />

ሰዎች አንዱ ነው፡፡ በማህበሩ ውስጥ ንቁ ተሳትፎ ከሚያደርጉ<br />

መካከል አረጋኸኝ ተፈራ ግንባር ቀደም ነበር፡፡ ዛሬ አረጋኸኝ<br />

ሽንቱን መቆጣጠር አይችልም፡፡ የአልጋ ቁራኛ ሆኗል፡፡ ይህ<br />

የደረሰበት ሰው ነኝ፤ አገር አለኝ፤ መብቴን በሕገ-መንግሥቱና<br />

በአዋጁ መሠረት መብቴን አስከብራለሁ፤ መንግሥትም ከጐኔ<br />

ይቆምልኛል ብሎ በማመኑ ነበር፡፡ ነገር ግን አልሆነም፡፡<br />

ወንድሞቹን ያስተምር ነበር እናቱን የሚጦር እሱ ነው፡፡ በአሁኑ<br />

ጊዜ ከ6ቱ ወንድሞቹ አራቱ ትምህርታቸውን አቋርጠው ልመና<br />

ገብተዋል፡፡ ለአረጋኸኝ ምግብ ያስፈልገዋል፡፡ አረጋኸኝን<br />

ለሚያስታምሙ እናቱም ምግብ ያስፈልጋታቸዋል፡፡ የቀረነውን<br />

አመራሮች የሚያድን ኃይል ተመድቦብን ሕይወታችን አደጋ<br />

ውስጥ ወድቋል፡፡ በገዛ አገራችን መብታችንን በመጠየቃችን<br />

የሕይወት ዋስትና አጥተን ዛሬ የምንኖረው ተሸሽገን ነው፡<br />

፡ እኛ የጠየቅነው ሕገ መንግሥቱ ይከበር! ሕገ መንግሥስቱ<br />

የሰጠን መብት ይከበርልን ነው፡፡ ሕገ መንግሥቱን ቻይናውያን<br />

አንቀበልም ሲሉ የመንግሥት አካላትም በተገላቢጦሽ እኛን<br />

እንደወንጀለኛ አይተው እያሳደዱን ነው፡፡ እያሳደዱን ያሉት<br />

ሠራዊት ሕጋዊ ሠራዊት መሆኑን እየተጠራጠርን ነው፡፡ በማን<br />

መዋቅር የተደራጀ ሠራዊት በማን እንደሚታዘዝም አልገባንም፡<br />

፡ በዚህ አጋጣሚ የተደቀነብን የሕይወት አደጋ ለሚመለከተው<br />

ሁሉ አሳውቃችሁልን ሕይወታችንን አትርፍልን፡፡<br />

በሌላ አመራር ወይም አባል ላይ እንደዚህ ዓይነት የደረሰ ጉልህ<br />

በደል ይኖር ይሆን?<br />

- 17 አባሎቻችን ከፍተኛ የአካል ጉዳት ደርሶባቸው ለእንግልትና<br />

ለሥቃይ ተዳርገዋል፡፡ ህክምና አጥተው አካላቸው ተበላሽቶ<br />

በቁስል እየተሰቃዩ ናቸው፡፡ ለምን እንዴት ብሎ የሚጠይቅ<br />

ሠራተኛ ካለ በሎደር አፈር ይደፋበታል፡፡ በየዕለቱ በሴት<br />

እህቶቻችን ላይ አስገድዶ መድፈር ይፈፀምባቸዋል፡፡<br />

ለየትኛውም የመንግሥት አካል ብታመለክት መልስ አታገኝም፡፡<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

ቆይታ<br />

- “ቻይናውያን ሕገ-መንግሥታችሁንም የአዋጅ<br />

ሕጋችሁንም አናውቅም ብለዋል”<br />

አፍህን ሰብስበህ ሥራህን ሥራ እንባላለን፡፡ ለቻይና እስከሰራችሁ<br />

ድረስ፤ ቻይና ደሞዝ እስከፈለጋችሁ ድረስ፤ በቻይና ሕግ<br />

መተዳደር አለባችሁ ይሉናል፡፡ በቻይና ሕግ ማህበር ማቋቋም<br />

ክልክል ነው፡፡ በቻይና ሕግ ሐሳብን በነጻነት መናገር አይቻልም፡<br />

፡ መሰብሰብ ወንጀል ነው፡፡ ሐሳብን በነጻነት መናገር አይቻልም፡<br />

፡ ጋሻው ጣሰው የተባለ አንድ አባላችን ጥር 7 ቀን 2003 ዓ.ም<br />

በሰርግ ሚስት አገባ፡፡ ጥር 8 ቀን 2004 ዓ.ም አስጠርተው<br />

በሰርግህ ዕለት አንድ ቻይና የሚለብሰው ነጭ ተመሳሳይ ጃኬት<br />

ለምን ለበስክ ብለው ደብድበው የዘር ፍሬውን አበላሽተውታል፡<br />

፡ የዚህን ሠራተኛ የዘር ፍሬ ለማበላሸት የፈፀሙበት ስቃይ<br />

እነዚህ ሰዎች እንደ ሰው የሚያስቡ ናቸው የሚያስኝ ነው? ይህ<br />

ሰራተኛችን አሁንም በአካል አለ፡፡ ልታነጋግሩት ትችላላችሁ፡፡<br />

ከአካል ጉዳትና ከሴቶች መደፈር ሌላስ የሚጠቀስ ጥቃት<br />

ይኖራል?<br />

- እየተፈፀመ ያለው ጥቃት ተዘርዝሮ የሚያልቅ አይደለም፡፡<br />

የብሔራዊና የሃይማኖት በዓላትን እንዳናከብር ተከልክለናል፡፡<br />

በዚሁ ምክንያት 5 የክርስትና፣3 የእስልምና በዓላትን፣የአድዋና<br />

የሜዴይ በዓላትን እንዳናከብር ተከለከልን፡፡ የራሳችንን<br />

ብሔራዊ በዓላት ተከልክለን በአገራችን ተቀምጠን የቻይናን<br />

የጐማ በዓል ተገደን አንድናከብር እየተደረገ ነው፡፡<br />

ይህ ሁሉ በደል ሲፈፀም የት የት አመለከታችሁ? ምን መልስ<br />

ተሰጣችሁ?<br />

- መጀመሪያ አካባቢ የነበረን ግንዛቤ ቻይናውያን<br />

በኢትዮጵያውያን ላይ ለሚያደርሱብን ጥቃት አቤቱታ አቅርበን<br />

ከአንዳንድ የመንግሥት ባለሥልጣናት ፍትህ ስናጣ የመሰለን<br />

የባለሥልጣናት የሙስና ውጤት ነው፤እያልን እሱን ትተን<br />

ወደ ሚቀጥለው ባለሥልጣን እናመለክት ነበር፡፡ በመጨረሻ<br />

ላይ ግን እንደምናየው የመንግሥት አቋም ነው፡፡ መንግሥት<br />

ከቻይናውያን ጥቅም እስካገኘ ድረስ በዜጐች ላይ ምንም<br />

ጥቃት ቢደርስ የፈለገው ግፍ ቢፈጸም ማየትም መስማትም<br />

አለመፈለጋቸውን ነው የተረዳነው፡፡<br />

እንደዚህ ለማለት የሚያበቃችሁ ምንድነው? በቀጥታ ቀርባችሁ<br />

ለመጨረሻ ጊዜ ያነጋገራችሁት ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣን<br />

ማነው? ምንስ መልስ ሰጡዋችሁ?<br />

- ሌላውን ልተወውና ሁለት ቦታዎችን ብቻ ልግለጽልህ፡፡ ለህዝብ<br />

ተወካዮች ም/ቤት ሕግና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ<br />

አመለከትን፡፡ የፓርላማ አባል የሆኑት የተከበሩ አቶ ብርሃኑ<br />

2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />

አቶ ኩራባቸው ፍቅሩ ገ/ማርያም የዋልዳ ሆጀቶታ ዳንዲ ደራርቱ አርሲ (W H D D A) የቻይና ሠራተኞች ማህበር ሊቀመንበር ናቸው፡፡<br />

የቻይና ኩባንያዎች በማሕበራቸውና በዜጐቻችን ላይ እያደረሰ ነው በሚባለው ጉዳይ ላይ ባልደረባችን ብዙአየሁ ወንድሙ አነጋግሮአቸዋል፡፡<br />

አበበ ሥፍራው ድረስ ሄደው ተመልክተዋል፡፡ ሠራተኛው<br />

የደረሰበትን ነገር ሁሉ አስረድቷቸዋል፡፡ ተመልሰው ከሄዱ<br />

በኋላ ትልቅ መፍትሔ እናገኛለን ብለን ተስፋ አድርገን ነበር፡፡<br />

ምንም መልስ አላገኘንም፡፡ ለጠ/ሚኒስትሩ ጽ/ቤት አመልክትን፡<br />

፡ መፍትሄ ስንጠብቅ ያገኘነው ውጤት በተገኘንበት ቦታ ሁሉ<br />

እያሳደዱ እርምጃ መውሰድ ጀመሩ፡፡ ቀይ ሽብራዊ ግርፍ<br />

ተፈጽሞብናል፡፡ ታስረን ተገልብጠን ተገርፈናል፡፡ ሱሪንና<br />

ቡታንታን አስወልቀው እጅና እግርን አስረው ገልብጠው<br />

ሰቅለው መጫወቻ አደረጉን፡፡<br />

እንዲህ ተሰቅላችሁ የተገረፋችሁት የት ነው?<br />

በአርሲ ጮሌ ወረዳ ማኛ ላይ የፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ነው ይህንን የፈፀመብን፡<br />

፡ 51 አባሎቻችን ቀይ ሽብር ግርፍ ተፈጽሞብናል፡፡ በ7 አባሎቻችን ላይ<br />

ደግሞ ለምርመራ ተብለው ተወስደው በራሳቸው ላይ እንዲመሰክሩ<br />

አሰቃይተዋቸዋል፡፡ ኬሚካል ረጭተውባቸዋል፡፡ አእምሮአቸውን እንዲሰቱ<br />

አድርገዋቸዋል፡፡ ጥር 8 ቀን 2003 ዓ.ም ከፍተኛ ተኩስ ተከፍቶብን ሊፈጁን<br />

ሲሉ የሼክ አብዱራህማን ጉቺ የሚባል የእምነት ሥፍራ ያለ ህዝብ ወጥቶ<br />

ነው ያዳነን፡፡<br />

ይህ የተጋነነ ወይም ማስረጃ የሌለው ነገር ነው ማለት አይቻልም?<br />

- ይኸውልህ ከወረዳው መስተዳድር ደብዳቤ አጽፈን በእጃችን<br />

ይገኛል፡፡ ለተፈፀመብን ጥቃት በጠቅላላ የሲዲና የጽሑፍ<br />

ሰነዶቻችን ይኽውልህ፡፡ ሁሉንም አይተህ ማረጋገጥ ትችላለህ፡፡<br />

ሌሎች ሠራተኞችንም አነጋግር፡፡<br />

ቻይናዊያን ይህንን ግፍ ለምን የሚፈጽሙ ይመስልሃል?<br />

ቻይናዊያን እንደሚታወቀው በሰብአዊ መብት ጥሰት በዓለም ላይ የታወቁ<br />

ናቸው፡፡ በተለይ ኢትዮጵያ ከመጡ በኃላ ባለቤትና ከልካይ የሌለው ዜጋ<br />

አገኙ፡፡ እጅግ አድርገው ናቁን፡፡ የዜግንነትና ሉዓላዊ ክብር የሚነካ ስድብ<br />

ይሰድቡናል፡፡ ለመናገር የማይቻል ፀያፍ ስድብ ይሰድቡናል፡፡ በሥራ<br />

ምክንያት ለሚደርስ የአካል ጉዳት ህክምናና ካሳ አገልግሎት መክፈል የለብንም<br />

ብለው ያምናሉ፡፡ በሠራተኛ ማህበር ተደራጅቶ መብትን መጠየቅ ትልቅ<br />

ወንጀል አድርገው ያያሉ፡፡ በሴቶች ላይ የሚፈጽሙትን አስገድዶ መድፈር<br />

እንደመብታቸው ይቆጥሩታል፡፡ በኢትዮጵያ ህግ አንተዳደርም ብለው<br />

አምነዋል፡፡ ከመንግሥት ጋር ያላቸውን ውል አናውቅም፡፡ በአዋጅ 377/96<br />

ተከሰን ለአንድ ሠራተኛ አንድ ሺ ብር ከምንከፍል ለአንድ ባለሥልጣን አንድ<br />

ሚሊዮን ዶላር ሰጥተን ጉዳዩን ብንጨርስ ይሻላል ይላሉ፡፡ ምክንያቱን<br />

ሲገልጹ ለዘላቂ ጥቅም ለወደፊት ዓላማችን ይበጀናል ብለው ያምናሉ፡፡ እረፉ<br />

የሚላቸው ህግም ባለሥልጣንም ባለመኖሩ አጠናክረው ቀጥለዋል፡፡<br />

የኢትዮጵያ መንግስት በቻይናዊያንና በኢትዮጵያኖች መካከል<br />

የሚነሳ አለመግባባቶችን በህግ ለመዳኘት ችግሩ ምንድነው<br />

ይላሉ?<br />

ይህ መንግሥት ካለበት ውጫዊና ውስጣዊ ችግር ምክንያት ይመስለኛል፡፡<br />

መንግስት ከምዕራባዊያንና ከአሜሪካውያን ፊት ስላጣ ሙሉ በሙሉ በሚባል<br />

መልኩ ግንኙነቱን ወደ ቻይና አድርጓል፡፡ ቻይናን እንደ ከለላ መያዣ የፈለገ<br />

ይመስለኛል፡፡ ስለዚህ በምንም መልኩ የቻይናን ኩባንያ በአገሬ ላይ በዜጐች<br />

ላይ ይህንን አትፈጽሙ ለማለት ሞራል አላገኘም፡፡ እንዲያውም ከቻይና ጋር<br />

ግንኙነቱን ካረጋገጠና ካጠናከረ ጀምሮ ራሱ የእኛ መንግሥት በአገሪቱ ውስጥ<br />

ያለው የሰብአዊ መብት ጥሰት በእጅጉ ተጠናክሮ ቀጥሎአል፡፡ ልክ እንደቻይና<br />

ገዢው ፓርቲ ከሚያራምደው አመለካከትና ሐሳብ ውጪ አማራጭ<br />

ሐሳብን ማራመድ ከባድ ውንጀል እየሆነ ነው፡፡ ሚዲያውም የተለየ ሐሳብ<br />

እንዲያንሽራሽር አይፈልግም፡፡ በተጨማሪ ካለብን ድህነት ችግር በዜጐች<br />

ላይ የሚፈጸመውን ግፍና በደል አፍኖ እርዳታና ብድር ማግኘትን መርጧል፡<br />

፡ መንግስት ከዜጐች ይልቅ ገንዘብን የመረጠ ይመስላል፡፡ ምናልባትም የተለየ<br />

ውልና ስምምነትም ሊኖራቸው ይችላል፡፡<br />

በመጨረሻም ያልጠቀስኩት ነገር አለ ካሉ አጠር አድርገው<br />

መግለጽ የሚፈልጉት ሐሳብ ይኖራል?<br />

በመጀመሪያ አሁንም እንደትላንትናው ደግመን ደጋግመን የምንጠይቀው<br />

መንግስት ኃላፊነቱን ይወጣ ነው፡፡ የአገሪቱን ህገመንግስትና ያወጣቸውን<br />

አዋጆች ያስከብር፡፡ የዜጐችን በደልና ግፍ ያድምጥ፡፡ መፍትሄ ይሰጠን<br />

እንላለን፡፡ በሁለተኛ ደረጃ የሰብአዊ መብት ተከራካሪዎች ነን፤ የፆታ ጥቃትን<br />

እንታገላለን፤ የሚሉ ሁሉ ጩኽታችንን ሰምተው ከጐናችን እንዲቆሙ<br />

በሠራተኛው ስም ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡ በገዛ አገራችን እየተፈፀመብን ያለውን<br />

እጅግ ዘግናኝ ግፍና ሰቆቃ በገለልተኛ አካል ተጣርቶ እርምጃ እንዲወሰድ<br />

እንዲደረግልን፤ ህክምና ምግብ አጥተው በስቃይ ላይ ላሉ የጥቃት ሰለባዎች<br />

እርዳታ ድርጅቶችም ሆኑ የመርዳት አቅም ያላቸው ሁሉ እጃቸውን<br />

እንዲዘረጉልን፤ አሁንም በሠራተኛ ማሕበሩ ስም እማፀናለሁ፡፡ በመጨረሻም<br />

መላው ኢትዮጵያውያን ሁሉ በአገሩ ላይ እየተፈፀመ ያለውን ግፍ ይረዳልን<br />

ማለት እውዳለሁ፡፡<br />

እርማት<br />

በፍኖተ ነጻነት ጋዜጣ 2ኛ ዓመት ቅጽ 2 ቁጥር 14 ረቡዕ ጥቅምት 22 ቀን 2004ዓ.ም በወጣው እትም ዝግጅት ክፍላችን ከተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ ጋር ቆይታ ማድረጉ<br />

ይታወቃል፡፡ በገጽ 6 አራተኛው አንቀጽ በስምንተኛው ስንኝ ላይ በሰጡት መልስ “የኢሰፓ አባል ነበርኩ” የሚለው በመቅረፀ ድምጽ ጥራት የተፈጠረ ችግር ስለሆነ<br />

“የኢሠፓ አባል አልነበርኩም” ተብሎ እንዲታረም እየገለጽን ለተፈጠረው ስህተት አንባቢያችንንና የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉን ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡


2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />

በተስፋዬ ደጉ<br />

ወቅታዊ<br />

ሐሙስ ጥቅምት 2 ቀን 2004 ዓ.ም ከጠዋቱ አራት<br />

ሰዓት ላይ በመድረክ ጽ/ቤት ጋዜጣዊ መግለጫ<br />

እየተሰጠ ነው፡፡ በስድስት የተቃዋሚ የፖለቲካ<br />

ፓርቲዎች የተመሰረተው መድረክ፣ ከቅንጅትነት<br />

ወደ ግንባርነት መሸጋገሩን ለማብሰር፡፡ የየፓርቲዎቹ<br />

አመራሮች ጋዜጣዊ መግለጫውን ለመስጠት<br />

መድረኩን ይዘዋል፡፡ የአገር ውስጥም የውጭ አገርም<br />

በርካታ ጋዜጠኞች ሁኔታውን ለመዘገብ በቦታው<br />

ተገኝተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንም ካሜራዎቹን<br />

ደቅኖ ከአንድ ሰዓት በላይ የተካሄደውን ጋዜጣዊ<br />

መግለጫ እየቀረፀው ይታያል፡፡ መግለጫው ተነበበ፡<br />

፡ መድረኩ ለጋዜጠኞች ክፍት ተደረገ፣ ለአመራሮቹ<br />

ጥያቄ እንዲያቀርቡ፡፡<br />

የመጀመሪያዎቹ ሦስት ጥያቄዎች ከጋዜጠኞቹ<br />

ከተሰበሰቡ በኋላ፣ ለጥያቄዎቹ መልሶች መድረኩ ላይ<br />

ያሉት ዶ/ር መረራ ጉዲና መልስ መስጠት ጀምረዋል፡<br />

፡ ለመጀመሪያዎቹ ሁለት ጥያቄዎች በእርጋታ መልስ<br />

ሰጡ፡፡ ሦስተኛውን ጥያቄ ሲመልሱ ግን የተቆጡ<br />

መሰሉ፡፡ “እናንተ የኢሕአዴግ ካድሬዎች ግን<br />

መቼ ነው ፕሮፓጋዳችሁን መንዛት የምታቆሙት?<br />

መቼ ነው የምትተውን?” በማለት ጥያቄውን<br />

ወደ ጠየቃቸው ጋዜጠኛ እንደዋዛ እየተመለከቱ<br />

ጥያቄያቸውን ሰነዘሩ፡፡ ጋዜጠኛውም “ከኢሕአዴግ<br />

ቢሮ አልመጣሁም፡፡ የሬዲዮ ፋና ጋዜጠኛ ነኝ፡<br />

፡” ብሎ ጥያቄቸውን መለሰ፡፡ ዶ/ር መረራም<br />

ሃሳባቸውን ቀጠሉ፡፡ “ጋዜጠኛ ብትሆኑማ ጥሩ ነበር፡<br />

፡ የኢሕአዴግ ካድሬ እየሆናችሁ አስቸገራችሁን<br />

እንጂ፡፡” የሚል ምላሽ ከፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት<br />

ለመጣው ጋዜጠኛ ሰጡ፡፡<br />

ከፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት የመጣው ጋዜጠኛ<br />

የጠየቀው ጥያቄ ያጠነጠነው የመድረክ “ግንባርን”<br />

የፈጠሩት ስድስቱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያላቸውን<br />

የአይዲዮሎጂ ልዩነትን የተመለከተ ነው፡፡ ጋዜጠኛው<br />

ስድስቱ ፓርቲዎች ያላቸው ተቃራኒ ሊባል የሚችል<br />

የአይድዮሎጂ ልዩነት “ግንባር” ለመፍጠር<br />

እንደማያስችላቸው ጠቃቅሶ፣ በመካከላቸው ያለውን<br />

የአይዲዮሎጂ ልዩነት የት እንዳደረሱት የሚሞግት<br />

ዓይነት ነበር፡፡<br />

ከመለስተኛዋ መመላለስ በኋላ ዶ/ር መረራ ጉዲና<br />

ለተጠየቀው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በዚህም<br />

ምላሻቸውም አገራችን ኢትዮጵያ አሁን ባለችበት<br />

ዘርፈ ብዙ ችግሮች፤ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓቱ<br />

መገታቱ፣ የኢሕአዴግ አምባገነን ፓርቲ እየሆነ<br />

መሄድ፣ የዜጐች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች<br />

መታፈን፤ የገዢው ፓርቲ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና<br />

የመገናኛ ብዙሃንን ሙሉ በሙሉ በራሱ ቁጥጥር<br />

ሥር ማዋሉና አገራችን ያለችበት አጠቃላይ ቀውስ<br />

በተሰባሰቡት ወቅት በተቃዋሚዎች መካከል<br />

ያለውን የአዲዮሎጂ ልዩነትን በሁለተኛ ደረጃ ላይ<br />

እንዳስቀመጠው ገልፀዋል፡፡ አክለውም መድረክ<br />

በመለስተኛ ፕሮግራሙ ያስቀመጣቸው ነጥቦችም<br />

የጋራ መታገያቸው መሆናቸውን ገልፀው፤ የመድረክ<br />

ዓይነት ግንባር በመፍጠር በጋራ አገር መምራትም<br />

በሰለጠኑት አገራትም ጭምር የተለመደ አካሄድ<br />

መሆኑን የጀርመንና የእስራኤልን ተሞክሮን ዋቢ<br />

አድርገው አብራርተዋል፡፡<br />

ማታ በሁለት ሰዓቱ የአማርኛ ዜና ላይ የመድረክ<br />

ከቅንጅት ወደ ግንባር መሸጋገሩን ከደቂቃዎች<br />

በላይ ባልፈጀ ዜና የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተናገረ፡፡<br />

ሬዲዮ ፋናም በድረ ገጹ ላይ ባንድ መስመር ዜናውን<br />

አስፍሮት ተስተዋለ፡፡<br />

የመገናኛ ብዙሃንና ነፃነት<br />

በማንኛውም አገር ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን<br />

ለመመስረት መገናኛ ብዙሃን የሚያበረክቱት<br />

አስተዋፅኦ ከፍተኛ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ መገናኛ<br />

ብዙሃንም ሊያበረክቱት የሚችሉት አስተዋፅኦም<br />

ባላቸው የነፃነት መጠን ላይ ተንጠልጥሎ ይገኛል፡<br />

፡ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ስንልም የሃሣቦች ብዝሃነት<br />

(plurality of ideas) ዋነኛው አምድ መሆኑን<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

የመንግሥት መገናኛ ብዙሃን በሕገ-መንግሥቱ እውቅና የተሰጣቸውን ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብትንና የተለያዩ አስተሳሰቦችን ማስተናገድ ግዴታ እንዳለባቸው ተደንግጓል፡<br />

፡ ዴሞክራሲና መገናኛ ብዙሃን በጣም የተቆራኙ በመሆናቸው፤ አንዱን ከአንዱ ለይቶ ለማየት እስኪያስቸግር ድረስ ተደጋጋፊ ናቸው፡፡ የመንግሥት መገናኛ ብዙሃን ደግሞ<br />

ከየትኛውም የአገራችን የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት በበለጠ፤ ለሕዝብ ዓይንና ጆሮ በመሆን ሕገ-መንግሥቱ በተለያዩ ምክንያቶች ሲጣስ ለሕዝብ የማሳወቅ ግዴታ አለባቸው፡፡<br />

የሕዝብን ፍላጐት ግምት ውስጥ በማስገባት ምላሽ መሰጠት የሚችሉ ፕሮግራሞችን ማዘጋጀትም ሌላው ኃላፊነታቸው ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ላይ መጠነኛ የዳሰሳ<br />

ጥናት ያደረገው ተስፋዬ ደጉ ይሄን ለማድረግ እስካሁ ያልቻሉት “ከገዢው ፓርቲ በኩል የሚሰነዘር ጫና” በመኖሩ መሆኑን ሊያሳየን ተከታዩን ዘገባ አጠናቅሮልናል፡፡<br />

ኢሕአዴግና መገናኛ ብዙሃን<br />

ካሰብን ደግሞ ከኢ-ዴምራሲያዊ ጣልቃ ገብነትና<br />

ተፅዕኖ ነፃ በሆነ መልኩ መደራጀታቸውና ስራቸውን<br />

ማከናወናቸው፤ ዴሞክራሲያዊ ስርዓቱን በአጭር<br />

ጊዜ ለመመስረት የሚያስችል የማይተካ ሚና<br />

እንዳላቸው መረዳት ይቻላል፡፡<br />

መገናኛ ብዙሃን ላይ የተሰሩ በርካታ ጥናቶች<br />

እንደሚያሳዩት ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመመሥረት<br />

በመንገድ ላይ ያሉት በርካታ የአፍሪካ አገሮች<br />

ከመድበለ ፓርቲ ይልቅ ወደ አንድ ፓርቲ አገዛዝ<br />

እየሄዱ መሆኑን ያሳያል፡፡ በየአገራቱ መንግሥት<br />

የሚያስተዳድራቸው ብዙሃን መገናኛዎች በስልጣን<br />

ላይ ያለውን ገዢ ቡድን እንጂ የተለየ ድምፅ<br />

ለማሰማት በራቸውን ዘግተው ተቀምጠዋል፡<br />

፡ በመሆኑም በእነዚህ አገራት የዴሞክራሲያዊ<br />

ሥርዓት ግንባታ ሂደቱ ፈተና ላይ የወደቀው የአንድ<br />

ፓርቲ አገዛዝ ሥርዓት በመመስረቱ ብቻ ሳይሆን<br />

የመንግሥት መገናኛ ብዙሃን ከገዢው ፓርቲ ሃሳቦች<br />

በስተቀር ለሌሎቹ ወይም ለተቃዋሚዎቹ ዕድል<br />

አለመስጠታቸው ነው፡፡ ሲከፋም አሉታዊ ይዘት<br />

ያላቸውን ዘገባዎችን ማቅረብና “የስም ማጥፋት”<br />

ዘመቻዎችም ሲቀርብባቸው ይስተዋላል፡፡ እዚህ<br />

ጋ የዜናዎቹ /የዘገባዎቹ ሚዛናዊነት፣ ትክክለኛነት<br />

ወይም እውነተኛነት የመሳሰሉት የጋዜጠኝነት ስነ-<br />

ምግባር የሚጠይቃቸው እሴቶች አስታዋሽ ያላቸው<br />

አይመስሉም፡፡ እነዚህ ሆን ተብሎ የሚዘነጉ እሴቶች<br />

ደግሞ ለሃሳብ ብዝሃነት (plurality of ideas)<br />

ዋስትና፣ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ደግሞ<br />

መሠረት ናቸው፡፡<br />

ሮኒንግ ሄልግ “The Role of Media in Democracy”<br />

በተባለው መጽሐፍ እንዳስረዱት መገናኛ<br />

ብዙሃን ከመንግስት ወይም ከገዢ ፓርቲ ቀጥተኛ<br />

ጣልቃ ገብነት ነፃ ሆነው መደራጀታቸው በጣም<br />

አስፈላጊ የሚሆነው፤ መንግስት ስልጣኑን አላአግባብ<br />

እንዳይጠቀም ለመከላከል መሆኑን ያስረዳሉ፡፡<br />

ምናልባት የመንግሥትን ስልጣንን የያዙ ግለሰቦች<br />

ስልጣናቸውን ለራሳቸው ግላዊ ጥቅም ቢያውሉት<br />

የህዝብ ዓይንና ጆሮ ሆነው የሚያገለግሉት መገናኛ<br />

ብዙሃን “ስህተቱን” ለሕዝብ ያሳውቃሉ፡፡ መረጃው<br />

የደረሰው ሕዝብም፤ ያጠፉት ወኪሎቹን ማብራሪያ<br />

ከመጠየቅ ጀምሮ ውክልናውን እስከማንሳት የደረሰ<br />

እርምጃ ሊወሰድባቸው ይችላል፡፡ ይህ ሊሆን<br />

የሚችለው ግን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት በመሰረቱት<br />

እንደ አሜሪካና በምዕራብ አውሮፓ ባሉ አገራት<br />

ነው፡፡ በኢትዮጵያስ?<br />

ሁለቱ ወንበሮች<br />

ወንደስን አለሙ (ስሙ ለዚህ ፅሑፍ ተቀይሯል) እንደ<br />

ፖለቲካል ሳይንስ ተማሪነቱ የገዢው ፓርቲን ሁለት<br />

ወንበሮች ለመለየት እንደሚቸግረው ይናገራል፡፡<br />

እንደ ፓርቲ ስለየትኛውም ፖለቲካዊ ጉዳዮች የራሱን<br />

አቋም መያዝ መብቱ መሆኑን የሚቀበለው ቢሆንም፤<br />

የፓርቲውን አቋም ህገ-መንግሥቱን በመጣስ ጭምር<br />

በመንግሥታዊ ጉዳዮች ውስጥ ጣልቃ መግባቱን ግን<br />

አምርሮ እንደሚቃወመው ይናገራል፡፡<br />

የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራር የሆኑት ዶ/ር<br />

ኃይሉ አርአያ “መድበለ ፓርቲ በኢትዮጵያ የወደፊት<br />

ዕጣፋንታ” በሚለው ጥናታቸው ላይ እንደገለፁት<br />

“ከምርጫ 2002 በኋላ ኢሕአዴግ አምባገነናዊ<br />

አውራ ፓርቲ ሆኖ ወጥቷል፡፡ ወደዚህ የደረሰበት<br />

መንገድም ከምርጫ 97 በኋላ በወስዳቸው<br />

ኢ-ዴሞክራሲያዊ እርምጃዎች ነው፡፡” ይላሉ፡<br />

፡ ዝርዝራቸውን ለመቁጠር ወደ ጣቶቻቸው<br />

እየተመለከቱ፡፡ “የመጀመሪያው ነፃው ፕሬስን<br />

ለማዳከም የወጣው የሚዲያ አዋጅ፣ ሲቪክ<br />

ማህበራትን ተሳትፎ ለመቀነስ የወጣው አዋጅ፣<br />

የተቃዋሚ ፓርቲዎችን ደካማ ለማድረግ የወጣው<br />

አዋጅና የፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ” መሆናቸውን<br />

ይገልፃሉ፡፡<br />

ይሄው የዶ/ር ኃይሉ ተመሳሳይ ጥናት<br />

እንደሚያስረዳው ኢሕአዴግ አውራ ፓርቲ ሆኖ<br />

ለመውጣት የቻለው “ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን<br />

በማፈንና ነፃና ፍትሃዊ ባልነበረ ምርጫ በ2002<br />

በማሸነፉ” ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ኢሕአዴግ<br />

በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ “አምባገነናዊ አውራ<br />

ፓርቲ” እንጂ፣ “አውራ ፓርቲ” እንዳልሆነ<br />

ይደመድማሉ፡፡ ሃሳባቸውን በመቀጠልም<br />

“አምባገነናዊ አውራ ፓርቲዎች ባሉበት አገራት<br />

ገዢው ፓርቲንና መንግሥትን መለየት አለመቻል፣<br />

ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ መሰረት<br />

የሆኑ ነፃ የሚዲያ፣ የፍትህ፣ ሲቪክ ማኅበራትና<br />

የምርጫ አስፈፃሚ አካላት አለመኖር፤ ዋና ዋናዎቹ<br />

መገለጫዎቹ” መሆናቸውን አስታውሰው፤<br />

የአገራችን ነባራዊ እውነታም ይሄንኑ እንደሚያሳይ<br />

አስረድተዋል፡፡<br />

የገዢው ፓርቲ ይፋዊ ህትመቶች እንደሚያትቱት<br />

ደግሞ መንግሥት (ኢሕአዴግ ለማለት ነው) የግሉን<br />

የመገናኛ ብዙሃን ዘርፍ፤ “ሊቆጣጠረው” የሚገባው<br />

የአሁኑ ታዳጊ ዴሞክራሲያችን “እንዳይቀለበስ”<br />

ለመጠበቅ ነው፡፡ እነዚህ ይፋዊ ህትመቶችና አልፎ<br />

አልፎም የፓርቲው ሹማምንት እንደሚያስረዱት<br />

“ኢሕአዴግ የጀመረው የዴሞክራሲያዊ ስርዓት<br />

ግንባታ ሊቀለበስ በማይችልበት ደረጃ ላይ<br />

ገና አለመድረሱን ነው፡፡ ለዚህም ክርክራቸው<br />

የሚያቀርቡት ማስረጃም በምርጫ 97 ጊዜ ነፃው<br />

ፕሬስ ከተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጐን<br />

“መሰለፉ” የሚያሳየው ሐቅ ቢኖር፣ “ነፃው ፕሬስ”<br />

ከ “ኢ-ዴሞክራሲያዊ” ኃይሎች ጋር በማበር<br />

“ዴሞክራሲውን” አደጋ ላይ የመጣል አቅም<br />

እንዳለው ማሳየቱን የፓርቲው ህትመቶች ይገልፃሉ፡፡<br />

የዶ/ር ኃይሉ ጥናት የሚያሳየው ግን በሚድያ ህጉ<br />

እንደታየው የኢሕአዴግ ዓላማ ዴሞክራሲያዊ<br />

ስርዓቱን ለማፈን እንጂ ዴሞክራሲያዊ ስርዓቱን<br />

ለመጠበቅ የተሰራ አለመሆኑን ነው፡፡ የምሁሩ ጥናት<br />

እንዲማሳየው የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት በኢትዮጵያ<br />

ለወደፊት የሚኖረውን ዕጣ ፈንታን በተነተኑበት<br />

ፅሁፋቸው እንደደመደሙት ኢህአዴግ በሥልጣን<br />

ላይ እስካለ ድረስ የመነመነ ነው፡፡ እኚህ የአንድነት<br />

ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ከፍተኛ<br />

አመራር እዚህ መደምደሚያ ላይ ያደረሳቸውን<br />

ምክንያት ሲገልፁ ገዢው ፓርቲ ከምርጫ 97<br />

ያልጠበቀው ሽንፈት ወዲህ ያፀደቃቸውን አፋኝ<br />

አዋጆችን ነው፡፡ አዋጆቹም የመገናኛ ብዙሃን<br />

አዋጅ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ማቋቋሚያ አዋጅ፣<br />

የሲቪክ ማኅበራት አዋጅና የፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ<br />

መሆናቸውን ይናገራሉ፡፡ የምሁሩ ጥናታዊ ፅሁፍ<br />

እንደተነተነው እነዚህ አራት አዋጆች በአገራችን<br />

የዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ለማጐልበት እንዲረዱ<br />

በማሰብ ሳይሆን የፀደቁት፣ ይልቁንም ኢህአዴግ<br />

አምባገነናዊ አውራ ፓርቲ ሆኖ እንዲቀጥል፣<br />

ተቺዎቹንና ተቃዋሚዎቹን ከፖለቲካው ጨዋታ<br />

ውጭ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ያሰምሩበታል፡፡<br />

ዶ/ር ነጋሶና አንቀፅ 29<br />

ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ የአንድነት ለዴሞክራሲና<br />

ለፍትህ (አንድነት) ፓርቲ ሊቀመንበር ናቸው፡፡<br />

የኢትዮጵያ ህገ-መንግሥት ከያዛቸው ከመቶ በላይ<br />

አንቀፆች መካከል አንቀጥ 29ን የበለጠ የሚወዷት<br />

ያስመስልባቸዋል፡፡ ፓርቲያቸውን ወክለው<br />

በተገኙበት ቦታ ሁሉ፣ በጋዜጠኞች ቃለ-መጠይቅ<br />

ሲደረግላቸው….. ሁልጊዜም አንቀጽ 29 ሳያነሷት<br />

አያልፉም፡፡<br />

ዶ/ር ነጋሶ “ሃሰብን በነፃነት የመግለጽ መብት ” የህገ-<br />

መንግሥት አርቃቂ ኮሚሽን ውስጥ በነበሩበት ወቅት<br />

የፀደቀ አንቀጽ ነው፡፡ሕገ-መንግስቱም በ1987 ዓ.ም<br />

በርሳቸው የመጨረሻ ፊርማ ፀደቀ፡፡ ፕሬዚዳንት<br />

ስለነበሩ፡፡ ትዝታቸውንና ተስፋቸውን ወደኋላ<br />

ተመልሰው ሲያስታውሱ “ዜጐች የተቃውሞም<br />

ይሁን የድጋፍ ሃሳባቸውን በነፃነት እንዲገልፁ<br />

ዋስትና እንዲሆናቸውና፤ የመንግስት መገናኛ<br />

7<br />

ብዙሃንን ጭምር ተጠቅመው ለሕዝብ ማድረስ<br />

ዕድል ይሰጣቸዋል” በሚል እንደነበር ይናገራሉ፡፡<br />

ሕገ-መንግሥቱ ሥራ ላይ ከዋለ አስራ አምስትና<br />

አስራ ስድስት ዓመታት በኋላና ከኢሕአዴግ የፓርቲ<br />

አባልነት ራሳቸውን ካገለሉ አስር ዓመታት በኋላ<br />

ግን፤ ተስፋቸው አይናቸው እያየ እንደጉም መትነኑን<br />

ይናገራሉ፡፡ ገዢው ፓርቲ ወደለየለት አምባገነንነት<br />

የገባው በዋናነት ከ1993 ወዲህ ሲሆን፣ በተለይ<br />

ግን ከምርጫ 97 ወዲህ መሆኑን ያስምሩበታል፡፡<br />

ለዚህ መከራከሪያም የሚያቀርቡት ማስረጃም ህገ-<br />

መንግሥቱንና የፀረ-ሽብርተኝነት አዋጁን በማነፃፀር<br />

ነው፡፡ “የህገ-መንግሥቱ አንቀጽ 29 ሃሳብን በነፃነት<br />

መግለፅን የሚያበረታታ ሲሆን፣ የፀረ-ሽብርተኝነት<br />

አዋጁ ግን ወንጀል የሚያደርግ ነው፡፡” ይላሉ፡<br />

፡ በኢትዮጵያ ዴሞክራሲዊ ሥርዓት ለመመሥረት<br />

እነዚህ ሁለት ህጐች ሊያበረክቱት የሚችለውን<br />

አስተዋፅኦ ሲያነፃፅሩት ደግሞ “አንቀጽ 29<br />

የሚያበረታታና ገንቢ ነው፡፡ አዋጁ ግን የሚገታ ብቻ<br />

ሳይሆን ዜጐች በፍርሃት እንዲኖሩ የሚያስገድድ<br />

ነው፡፡” በማለት ተናገሩ ፡፡ “የሚያሳዝነው<br />

ደግሞ አዋጁን እየጠቀሱ፤ አንቀጽ 29ን ሲጥሱ<br />

መመልከታችን ነው፡፡ የአንዱዓለም አራጌና<br />

የጋዜጠኛ እስክንድር ነጋም እስር የዚህ ውጤት<br />

ነው፡፡ ሁላችሁም በነበራችሁበት፣ በዚሁ መድረክ<br />

ላይ ሁለቱም ያሉት በአዲሱ ዓመት በ2004 ዓ.ም<br />

በአገራችን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመመሥረት<br />

በሰላማዊና ህጋዊ መንገድ ለመታገል እንዘጋጅ<br />

ነው፡፡ ይህ በህገ-መንግሥቱ የተረጋገጠ መብት<br />

ነው፡፡ ወንጀል አይደለም፡፡ ወንጀል የሚደረገው<br />

በኢሕአዴግ ነው፡፡” በእጃቸው መድረኩን እያሳዩ<br />

ንግግራቸውን ጨረሱ፡፡<br />

እንደምን አመሻችሁ ዲሽ የሌላችሁ<br />

ከአራት ኪሎ ተነስተው ፒያሳ እንደገቡ ቀዝቀዝ<br />

ያለ አየር በሚነፍስበት ጥግ ቀዝቀዝ ያለ ገበያ<br />

ያላቸው ሁለት ሱቆች ይታያሉ። የመጀመሪያው<br />

ሱቅ ስም አልባ ቢሆንም በመስታወቱ ወደ ውስጥ<br />

ዘልቆ አተኩሮ ለተመለከተ የኤሌትሪክ ዕቃዎች<br />

መሸጫ መሆኑን መለየት ይቻላል። ሁለተኛው ሱቅ<br />

አጠገብ ያለው ደግሞ ለብዙ ዓመታት መስታወቱ<br />

ላይ በለጠፈውና የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ድርጅት<br />

ለሚሰጠው አገልግሎት ከደንበኞቹ ክፍያ መቀበያ<br />

መሆኑን የሚገልፀው ማስታወቂያ ያለበት ቢሮ ነው።<br />

ዛሬ ግን አዲስ የሚመስል ነጭ ባነር ላይ “የቴሌቪዥን<br />

ባለቤትነት ማረጋገጫና የቴሌቪዥን አገልግሎት<br />

ክፍያ መሰብሰቢያ” መሆኑን የሚገልፅ ፅሁፍ ሻተሩ<br />

ላይ እንደነገሩ ተንጠልጥሎ ይታያል። በሩ ክፍት<br />

ነው። ሰው ሲገባም ሆነ ሲወጣ አይታይም። ክፍሉ<br />

ውስጥ የሚታየው ደብዘዝ ያለ ብርሃን ክፍሉን<br />

ህይወት አልባና ፈዛዛ ድባብ አላብሶታል። ፒያሳ<br />

ውስጥ ያለ አይመስልም።<br />

በ1957 ዓ.ም የተመሠረተው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን<br />

ዛሬም ድረስ ብቸኛውና በመንግስት ቁጥጥር<br />

ስር ያለ ጣቢያ ነው። ኢሕአዴግ ወደ ስልጣን<br />

እንደመጣ ነፃ ፕሬስ እንዲቋቋም ቢፈቅድም<br />

የኤሌክትሮኒክስ ሚዲያውን ግን ለግል ባለሃብቶች<br />

እንደማይፈቅድ በተደጋጋሚ ሲገልፅ መሰንበቱ<br />

ይታወሳል። ፓርቲው እዚህ አቋም ላይ የደረሰበትን<br />

ምክንያት ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያዎች በባህሪያቸው<br />

ሰፋ ላለው የህብረተሰብ ክፍል በቀላሉ መድረስ<br />

የሚችሉ በመሆናቸው እነሱን ተጠቅሞ የሚደረግ<br />

“ቅስቀሳ” አገሪትዋን ወደ መተላለቅና ወደ መበታተን<br />

ሊያደርሳት መቻሉን ነው። ነፃው ፕሬስስ ? እሱማ<br />

በከተሞች አካባቢና በተማረው የህብረተሰብ<br />

ክፍል ብቻ ተደራሽ በመሆኑ ያን የሚያህል<br />

አቅም አይኖረውም ተብሎ በመታሰቡ ነው።<br />

ይህ የተጠቀሰው የፓርቲው መሠረታዊ ፍልስፍና<br />

ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የተቀየረው ከ1997ቱ<br />

ምርጫ በኋላ ይመስላል።<br />

ወደ 14 ይዞሯል<br />

www.andinet.org.et


8<br />

ከመ/ር ደረጀ መላኩ<br />

www.andinet.org.et<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

ኢትዮጵያውያን ሁሉ ኡኡ!<br />

ሪፖርተር ጋዜጣ ጥቅምት<br />

5, 2004 ቅፅ 16.ቁ.5/1197<br />

ግንባር ቀደም ዜናው ላይ<br />

ካራቱሪ የህንድ ገበሬዎችን ሊያሠፍር<br />

ነው በሚል ርእስ ስር ለኢትዮጵያ ህዝብ<br />

መርዶ አሰምቷል፡፡ አስደንጋጩ መርዶ<br />

የሚከተለውን ይመስላል፡፡<br />

ካራቱሬ አዲስ ባወጣው ህግ 20 ሺ<br />

ሄክታር መሬት ላይ የሕንድ ገበሬዎችን<br />

ለማሠራት ወስኗል፡፡ “ከገበሬዎቹ ቀና ምላሽ<br />

አግኝተናል፡፡ መሬቱን እውቀቱ ባላቸው<br />

ገበሬዎች እናለማለን” ሲሉ የኩባንያው ሃላፊ<br />

ገልፀዋል::<br />

“የገቢ ትርፋችን 65 በመቶ ለ35 በመቶ<br />

ሆኖ ከገበሬዎቹ ጋር ገቢውን እንጋራለን”<br />

ሲሉ ለህንዱ ቢዝነስ ስታንዳርድ ጋዜጣ<br />

ገልፀዋል፡፡ ገበሬዎችን ወደ ኢትዮጵያ<br />

የማምጣት ሂደት የሚቀጥል ሲሆን<br />

በሁለተኛው ዙር 50 ሺህ ሄክታር መሬት<br />

ላይ ተጨማሪ ገበሬዎችን እንደሚያስፍሩ<br />

ሀላፊው ተናግረዋል፡፡<br />

የኩባንያው እቅድ እንዳልገባቸው<br />

የጋምቤላ ምክትል ፕሬዜዳንት አቶ ጋነርየር<br />

ሲናገሩ “እኛ የምናውቀው ካራቱሪን<br />

እንጂ የሕንድ ገበሬዎችን አይደለም” ሲሉ<br />

አዲሱ እቅድ ግር እንዳሰኛቸው ገልፀዋል፡<br />

፡ በሌላ በኩል አገዛዙ በፌዴራል ግብርና<br />

ቢሮ ግብርና ኢንቨስትመንት ድጋፍ ሰጭ<br />

ዳይሮክቶሬት ዳይሪክተር በሚል ማዕረግ<br />

የሾማቸውን ግለሰብ ስማቸው አቶ ኢሳያስ<br />

ከበደ ይመስሉኛል አስተያየታቸውን<br />

ለማካተት የጋዜጣው ሪፖርተር ጥረት<br />

አድርጎ እንዳልተሣካለትም አስነብቦናል፡<br />

፡ ከቶ ለመሆኑ ይሄን ትልቅ ሀገራዊ ጉዳይ<br />

በተመለከተ የመአከላዊውን መንግስት አቋም<br />

የሚነግሩን ውጪ ሀገር ለስራ ጉዳይ የሄዱት<br />

ተሻóሚ ብቻ ናቸው? አይሠማም እየተባለ<br />

ነው? ግራም ነፈሰ ቀኝ በኢኮኖሚ ጉዳዮች<br />

ላይ የምታጠነጥ ነው ፎርቹን የእንግሊዝኞ<br />

ጋዜጣ ጥቅምት 5,2004 ዓ.ም እትሟ<br />

ላይ ስለዚሁ አሣሣቢ ጉዳይ ሰፊ ሽፋን<br />

ሰጥታ አስነብባናለች፡፡ አዎ የጋዜጠኞች<br />

ዋነኛ ሥራ እውነተኛ የዜና <strong>ምንጭ</strong> መሆን<br />

አይደል? በእውነቱ ለመናገር የሁለቱም<br />

ጋዜጦች አዘጋጆች አገራዊ ግዴታቸውን<br />

በመወጣታቸው ሊመሠገኑ ይገባል፡፡<br />

ይሄን ካልኩ ቀጥታ ወደ ተነሣሁበት ነጥብ<br />

ልውሰዳችሁ::<br />

እንደ ሥነ ህዝብ ጠበብት ከፍተኛ<br />

ስጋትና ጥናት ከሆነ ሀገሬ ኢትዮጵያ እጅግ<br />

በአጭር ግዜ ውስጥ ከ200 ሚሊዮን በላይ<br />

ህዝብ ይኖርባታል፡፡ አሁን 90 ሚሊዮን<br />

ደርሰናል፡፡ ዛሬ በወጣትነት እድሜ<br />

የሚገኙና ህፃናቶች ወደ እማይቀረው<br />

አለም ከመሄዳቸው በፊት ነው በኢትዮጵያ<br />

መሬት ላይ ከላይ የተጠቀሰው ህዝብ<br />

የሚኖርባት:: ለነገሩ የኢትዮጵያ መሬት<br />

ከተሠራበትና በሀገር ፍቅር ስሜት የነደደ<br />

እንዲሁም የተማረ እና በስልጣን ፍቅር<br />

ያለበደ መሪ ብታገኝ ከ40 ሚሊዮን በላይ<br />

ህዝብ እንደምት መግብ ብዙ ጠበብቶች<br />

የመሠከሩት ጉዳይ ይመስለኛል፡፡ ለዚህ<br />

አልታደልንም:: እና ዝንተ አለም ተመፅዋች<br />

ሆነን ቀርተናል፡፡ ያሳዝናል:: ሌላው ቀርቶ<br />

የሩቁን ትተን የቅርብ ጊዜውን ታሪካችንን<br />

ብንፈትሸው አንገት የሚያስደፋ ነው፡<br />

፡ ቀድሞ በየ አስርተ አመቱ (ከዚያ በላይ)<br />

እየመጣ የሚቀጣን ድርቅና ጠኔ ዛሬ<br />

“የዴሞክራሲ ስርዓት ጀማሪዎች ነን” እያሉ<br />

ሌት ተቀን በተቆጣጠሩት የኤሌክትሮኒክስ<br />

እና የህትመት መሣሪያዎቻቸው ዘወትር<br />

የሚወተውቱት ገዢዎቻችን ቃል እና ተግባር<br />

ያልተገናኙበት ጊዜና ሰዓት ላይ ደርሶናል፡፡<br />

እንደ አሰልቺ ዲስኩራቸው ቢሆን<br />

ኖሮ ሀገሬ ኢትዮጵያ ያልፍላት ነበር፡፡<br />

ከራሷ ልጆች አልፋ ለሌሎች ለተቸገሩ ቀን<br />

ለጨለመባቸው አለም ህዝቦች በደረሰች<br />

ማለት ይገባናል<br />

ነበር፡፡ ይህ ግን ከቶውንም ሲሆን አላየንም<br />

(አልሠማንም)፡፡<br />

በአንፃሩ ዜጎች “የዳቦ ያለህ” እያሉ<br />

ይጠይቃሉ፡፡ ወይንም ፈጣሪያቸውን<br />

ይማፀናሉ፡፡ “ምን አይነት ዘመን መጣን”<br />

በማለት በእውነቱ ለመናገር ካለፉት<br />

20 አመታት ጀምሮ እንደ ትሮይ ፈረስ<br />

የሚጋልቡን የደደቢት በርሃ ጨካኞችና<br />

ጋሻ ጃግሬዎቻቸው ለኢትዮጵያ ህዝብ<br />

ደረቅ ዳቦ እንኳን በስዓቱ ሊያቀርቡለት<br />

አልተቻላቸውም፡፡ ወይንም የስራ ጀግና<br />

የሆኑ ኢትዮጵያውያን በነፃነት ተንቀሳቅሰው<br />

ሊሰሩ የሚችሉበትን ሁኔታ ማመቻቸት<br />

አልቻሉም (አልፈለጉም)፡፡ ኢትዮጵያ እኮ<br />

የወላድ መካን አይደለችም፡፡ ብዙ ምርጥ<br />

ልጆች ሞልተዋታል፡፡<br />

በቅርቡ እንኳን ለአለም አዳጊ አገር<br />

ገበሬዎች መድህን የሆነ የአእምሮ ጭማቂ<br />

ከኢትዮጵያዊው ሣይንቲስት ፕሮፌሰር<br />

እጀታ ጋቢሳ እንደተገኘ አለም ሁሉ<br />

የሚያውቀው እውነት ይመስለኛል፡፡<br />

ኢትዮጵያ ግን ዛሬም ሊያልፍላት አልቻለም፡<br />

፡ ከቶ ለምን ይሆን? የፕሮፌሰሩ የትውልድ<br />

ቦታ ሣይቀር (ሆለታ) ሞልቶ የተረፈው<br />

አይደለም፡፡ መቀመጫቸውን ዴንማርክ<br />

ያደረጉት ፕሮፌሰር ማሞ ሙጬ በቅርቡ<br />

ስለ ኮምፒዮተር እና ኢንተርኔት አስፈላጊነት<br />

በጀርመን ድምፅ ተክሌ ይኋላ ጋር ቃለ<br />

ምልልስ አድርገዋል፡፡ ከቃለ ምልልሱ<br />

ለመረዳት እንደቻልኩት በ21ኛው ክፍለ<br />

ዘመን ያለ ኮምፒዩተር እና ኢንተርኔት<br />

እድገት ፈፅሞ አይታሰብም፡፡ ፕሮፌሰሩ<br />

ያላቸውን ጥልቅ እውቀት ለሀገራቸው<br />

እድገት ማዋል ባለመቻላቸው በሀዘን<br />

ሲናገሩም አድምጫለሁ፡፡ (የተጠቀሰውን<br />

ቴክኖሎጂ በኢትዮጵያ ለማስፋፋት<br />

ሁኔታው አመቺ ባለመሆኑ ለማት ነው)<br />

የደስታ እና አባ ሠንጋ በሽታ ክትባት ግኝት<br />

ባለቤት ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ የት ገቡ?<br />

ከ30 ሚሊዮን በላይ የቀንድ ከብት ከ50<br />

ሚሊዮን በላይ ዶሮዎች …. ወዘተ ባለቤት<br />

የነበረችው ኢትዮጵያ ዛሬ ያ ሀብቷ አለን?<br />

በቦረና በሌሎች አካባቢዎች በድርቅ<br />

ምክንያት በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ እንስሶች<br />

ወደ ትቢያነት ሲቀየሩ አልሰማንም?<br />

አፍንጫችን ሥር ያለችው ኬንያ ከኢትዮጵያ<br />

ጋር በእንሥሳት ብዛት መወዳደር ቀርቶ<br />

የምትደርስባት አይመስለኝም፡፡ ሆኖም ግን<br />

በአለም ገበያ ላይ ጥራት እና ከፍተኛ ክብደት<br />

ያለው ስጋ እና የሥጋ ውጤቶች (ከኢትዮጵያ<br />

በብዙ የሚልቅ ማለቴ ነው) በየጊዜው<br />

ትልካለች፡፡ ዛዲያ ለምን ለእማማ ኢትዮጵያ<br />

ቀኑ ጨለመባት? ያለ ሥሟ ያለ ምግባሯ<br />

የድሆች ደሀ ብለው ስም አወጡላት?<br />

እንደሚመስለኝ ፕሮፌሰር ጥላሁን እና ሌሎች<br />

ኢትዮጵያውያን ሀገር ቤት እውቀታቸውን<br />

በተግባር እንዳያውሉ በሩ ስለተዘገባቸው<br />

ነው፡፡ በአለምም ሆነ በአፍሪካ ደረጃ በንብ<br />

አንቢነት ከሚተወቁት ሀገራት ኢትዮጵያ<br />

ግንባር ቀደም ሀገር ነበረች፡፡ እውን ዛሬ<br />

ታዲያ ልጆቿ የማር ተጠቃሚዎች ሆነዋል?<br />

መልሱን ለአንባቢ ትቼዋለሁ፡፡ ኬንያ<br />

ከኢትዮጵያ በተሻለ ሁኔታ የተማሩ ዜጎቿን<br />

በማቅረቧ (በመያዟ) ከኢትዮጵያ የተሻለ<br />

እድገት አሣየች፡፡ እኛ ግን ዛሬም እየዳከርን<br />

እንገኛለን፡፡ ታሪክ እንደሚያስተምረን<br />

በንጉሱ ዘመን ብዙ የተማሩ ኢትዮጵያውያን<br />

ሀገራቸውን ለማግለገል ፍላጐት ነበራቸው፣<br />

በደርግ ዘመን ፖለቲካውን ሣይተቹ<br />

በሙያቸው የቀጠሉ መስራት የተከለከሉ<br />

አይመስለኝም፡፡ በእርግጥ የደርግን መጥፎ<br />

ድርጊት በመቃወም ስፍር ቁጥር የሌላቸው<br />

ልጆቿ እንደ ጨው ዘር በአለም ተበትነው<br />

ቀርተዋል፡፡ ዛሬ ደግሞ የጎሣ ፖለቲካ<br />

ተጨምሮበት ከዚህ በፊት ታይቶ ተሠምቶ<br />

በማይታወቅ ሁኔታ ብዙ ምኹራን ሀገር<br />

ለቀው ሄደዋል፡፡ ኢትዮጵያን ከምኹራን<br />

ፍልሰት ለመታደግ ዘላቂ መፍትሄ የተገኘ<br />

አይመስለኝም፡፡ እንዲያውም ጉዳዩን<br />

የሚያባብስ ድርጊት ተፈፅሟል፡፡ ከ1985ቱ<br />

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች አመፅ<br />

በኋላ ከ45 በላይ የዩኒቨርስቲው ነባር<br />

እና ምርጥ መምህራን መባረራቸውን ልብ<br />

ይሏል፡፡<br />

ዛሬ ከሰውነት ደረጃ ዝቅ ብለን እንደ<br />

እንስሳ ዝርያ እየፈለግን መቧደናችን<br />

አሣዛኝም አሣፋሪም ነው፡፡ ከ1983ቱ<br />

የደርግ ውድቀት ወዲህ በእያንዳንዳችን<br />

አእምሮ ውስጥ የተዘራው የጎሳ ፖለቲካ<br />

ውጤት እየታየ ነው፡፡ በወቅቱ 20 አመት<br />

እድሜ የነበረን ዛሬ 40 አመት ሞልቶናል፡<br />

፡ 40 እና ከዚያ በላይ እድሜ የነበራችሁ<br />

ኢትዮጵያውያን የእድሜ ባለ ጸጎች 60<br />

እና ከዚያ በላይ ሆኗችኋል፡፡ ከቶ ምን<br />

ይሰማችሁ ይሆን? ያቺ የወተት እና የማር<br />

ሀገር እንዲህ ስትራብ ስትጠማ? ፍሪምባ<br />

ከቁርጥ አማርጣችሁ የተመገባችሁ እናንተ<br />

ኢትዮጵያውያን፣ በ25 ሣንቲም ክትፎ<br />

የበላችሁ የሀገሩ ሰዎች በእውን ኢትዮጵያ<br />

እንዲህ ነበረች ብሎ ለሚጠይቃችሁ<br />

የአሁኑ ጨለማና አሣፋሪ ጊዜ ሣይሆን<br />

ያኔ ! ጥንት በጃንሜዳ በጥምቀት እለት<br />

የሚደረገው የአንድነትና የፍቅር ዜማ ትዝ<br />

ይላቹህ ይሆን? በደርግ ዘመን እንኳን<br />

የ1975 ዓ.ም አካባቢ ጃንሜዳ ኢዲዩ ቤት<br />

የሚባል ምግብ ቤት ነበር፡፡ ዛሬ ስለመኖሩ<br />

አላውቅም፡፡ ክትፎ ላይ የተጨመረው ቅቤ<br />

አነሰኝ ለሚል ደምበኛ ቅቤ በማንቆርቆሪያ<br />

እየዞረ የሚጨምር እንደነበር በአይኔ<br />

በብረቱ አይቻለሁ፡፡ ለዛውም ንፁህ የሸኖ<br />

ቅቤ፤ ዋጋው ቢበዛ 10 አሊያም ከ15 ብር<br />

አይበልጥም ነበር፡፡ ኢትዮጵያ ሀገራችን<br />

የባህር በሯን በማጣቷ የጂኦ ፖለቲካዊ<br />

ጠቀሜታዋ ከላይዋ ላይ ከተገፈፈ በኋላ<br />

የተፈጠራችሁ ደግሞ 20 አመት እድሜ ላይ<br />

የደረሳችሁ እናንት ሦታ ወጣቶች እኔ ማን<br />

ነኝ? የሚለውን ጥያቄ ለራሳችሁ አቅርባቹሁ<br />

ታውቁ ይሆን? አዎ እናንተ የባለ ታሪክ<br />

ኢትዮጵያ ልጆች መሆናችሁን ለአፍታም<br />

ቢሆን መዘንጋት የለባችሁም፡፡ የጎሳ ፖለቲካ<br />

ሊያጠምቃችሁ የሚፈልገውን እኔ ሰው<br />

ነኝ በማለት መከራከር ይገባችኋል፡፡ በጎስ<br />

ሥርዓት ውስጥ የተፈጠራችሁ በመሆናችሁ<br />

ጎሰኝነት ሊጣባችሁ ይችል ይሆናል፡፡ ግን<br />

ራሳችሁን በራሳችሁ ከቶባችሁ ከጎሳ በሽታ<br />

ተላቀቁ፡፡ የብሮዝ ቲቶ ሀገር የነበረችው<br />

ይጎዝላቪያና የብሬዥኔቭ ሦቬየት ህብረት<br />

እንዴት (ለምን) እንደተፈረካከሱ ታሪክን<br />

መመርመር ተገቢ ነው፡፡ (ታሪክን መርምሩ)<br />

ታላቁ የአፍሪካ ልጅ ኒልሰን ማንዴላ ለምን<br />

አለም አቀፍ እውቅና እና ክብር ተሰጣቸው<br />

ብላችሁ ጠይቁ፡፡<br />

ስማቸውን በወርቅ ቀለም ያፃፉት<br />

የሠላማዊ ትግል አስተማሪዎች የሆኑትን<br />

ማህተም ጋንዲና ማርቲን ሉተር ኪንግን<br />

የህይወት ታሪክ አንብቡ፡፡ እነ ወጣት<br />

አቢቹ፣ ደጃች በላይ ዘለቀ፣ ኮሎኔል አብዲሳ<br />

አጋ፣ ጄኔራል ተሾመ መተኪያ የሌላቸውን<br />

ወድ ህይወታቸውን ለምን ለኢትዮጵያ<br />

ሰውላት ብላችሁ ተመራመሩ፡፡ ጠይቁ?<br />

የትናቷ ኢትዮጵያ ማር ወተት ቅቤ ነበረች፤<br />

ጮማ ነበረች፤ ለዚች ቅዱስ ሀገር ነበር አፄ<br />

ቴዎድሮስ ሽጉጥ ጠጥተው ለክብሯ ሱሉ<br />

ሕይወታቸውን ያሳለፉላት፡፡ የሳቸውን<br />

ፈለግ ተከትለው ሌሎቹም የሚሰውላት<br />

በመሆኑም ይህ ትውልድም የሀገሩ ባለቤት<br />

ለመሆን ራሱን መጠየቅ አለበት፡፡ አለበለዚያ<br />

ጎሰኞች በጀመሩት ዕቅድ የሚገፉበት ከሆነ<br />

(ከመግፋትም አይመለሱም) ከጥቂት<br />

ዓመታት በኋላ የሕንድንና የቻይናን<br />

ቱጃር እያሰፈሩ አገር አልባ አድርገው<br />

እንደሚያስቀሩን ቅንጣት አትጠራጠሩ፡፡<br />

በመሆኑም ጎሳ ሳንለይ እጅ ለእጅ እንያያዝ፡፡<br />

ሰላማዊ ድምፃችንን በኡኡታ! እናሰማ፡፡<br />

የአደባባይ ምስጢሮች<br />

2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />

“ነፃ የሚያወጣኝ<br />

መድረክ ነው<br />

መሰለኝ”<br />

“ኦነግን ሳላውቅ የኦነግ አባል የሆንኩ መሰለኝ” የሚለውን<br />

ቃል የተናገሩት ከዛሬ ዘጠኝ ዓመት በፊት አንድ የዩኒቨርስቲ<br />

መምህር ናቸው፡፡ በ1994 ዓ.ም ክረምት ላይ ጠ/<br />

ሚኒስትር መለስ ዜናዊና አቶ ተፈራ ዋልዋ የከፍተኛ ትምህረት<br />

ተቋም መምህራንን ረዘም ላሉቀናት ያወያዩ ነበር፡፡ አንድ<br />

የዩኒቨርስቲ መምህር የኢህአዴግን የፍረጃ ፖሊሲ ለመግለጽ<br />

ሲሉ የተጠቀሙበት ቃል ነበር፡፡ “እኔ የማንም ድርጅት አባል<br />

አይደለሁም፡፡” አሉ መምህሩ ሲናገሩ “የማንም ድርጅት<br />

አባል ለመሆን እቅድም የለኝም፡፡ ሐሳቤን በነፃነት እሰጣለሁ፡፡<br />

የማላምንበት ነገር በነፃነት እከራከራለሁ፡፡ ኦሮምኛ ቋንቋ ተናጋሪ<br />

ብቻ በመሆኔ የኢህአዴግ አባላት “የኦነግ አባል የኦነግ አባል!<br />

እያሉ አሉኝ፡፡ ኦነግን እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ እንጂ በቅርብ<br />

አላውቀውም፡፡ ኦነግ የእኔን ሐሳብ የሚያራምድ ድርጅት ነው?<br />

ብዬ እንዳስብ እድርጐኛል፡፡ ኦነግን ሳላውቀው የኦነግ አባል<br />

ሆንኩኝ እያልኩ አሰላስላለሁ” በማለት ጠ/ሚኒስትሩ ባሉበት<br />

መናገራቸውን አስታውሳለሁ፡፡<br />

ዛሬ ይህ ትዝ ያለኝ በተለያየ ጊዜ የተለያየ ስም እየተሰጣቸው<br />

ተከሰው በነፃ ስለሚወጡ ሰዎች ሳስብና እንዲሁም ጐንደር<br />

ላይ የገጠመኝ አንድ ገጠመኝ ትዝ ብሎኝ ነው፡፡ ኢህአዴግ<br />

ሥልጣን እንደያዘ አካባቢ አምርረው ኢህአዴግን የተቃወሙ<br />

ደርግ ኢሠፓ ቀይ ሽብር እየተባሉ ወህኒ ወረዱ፡፡ በአንድ ወቅት<br />

ደግሞ መአህድ ሌላ ጊዜ ሌላ ስም እየተሰጠ ይታሰራሉ፡፡ አልፎ<br />

አልፎ የህሊና ዳኛ ሲገጥማቸውም በነጻ ሲለቀቁ እሰማለሁ፡<br />

፡ ዛሬ ደግሞ ጊዜው መድረክ ሆኖአል፡፡ በአንድ ወቅት ደቡብ<br />

ጐንደር ደብረታቦር ከተማ የሰማሁትን ገጠመኝ ላካፍላችሁ፡፡<br />

ከአካባቢው ገጠራማ ቦታ የመጡ አንድ አርሶ አደር አግኝቼ<br />

ተግባባንና ጫወታ ጀመርን፡፡ ስለ ወቅቱ ዝናብ፣ ስለሰብሉ፣<br />

ስለማዳበሪያው ዋጋ ሌላው ሌላውንም አንስተን በመጨረሻው<br />

ወደ ፖለቲካው ገባን፡፡<br />

“ካድሬው አላስቀምጥ አላሰራ አለን፡፡ “አዲሱ እረኛ<br />

ከብትም አያስተኛ” እንደሚባለው አንዱን አውርደው አንዱ<br />

ሲሾም ጥዋት ማታ ሰብስባ ወሬ ጭቅጭቅ ነው፡፡ የተስፋ ወሬ<br />

ነው፡፡ የማዳበሪያው ዋጋ ሰማይ ወጣ ምንም የሚበጀን ነገር<br />

አላገኘንም፡፡ ቅንጅት ይመጣል ብለን ስንጠብቅ በዚያው ቀረ፡<br />

፡ ሰሞኑን ደግሞ መድረክ እየተባለ ነው፡፡ ምናልባት እንግዲህ<br />

መድረክ ነፃ ያወጣን እንደሆነ በተስፋ እየጠበቅን ነው፡፡<br />

አሉኝ እኔም ተገርሜ መድረክ እዚህ አለ እንዴ? አልኳቸው<br />

“ኽረ የለም” ሲሉ መለሱልኝ፡፡ ለእናንተ የሚበጅ ወይም<br />

የማይበጅ መሆኑን እንዴት አወቃችሁ አልኳቸው “ወያኔ ራሷ<br />

ትነግረናለች” አሉኝ፡፡ እንዴት አልኳቸው “ወያኔ ከመጣችበት<br />

ዘመን ጀምሮ የተረፈን ወሬዋ እና ውሸቷ ነው፡፡ የተረፈን፡፡<br />

ያገኘነው፡፡ ድህነትና ውርደት ነው፡፡ ሁሉም ነገር ተወደደ፤<br />

ገንዘብ አምጡ አምጡ ነው፡፡ ሰለቸን፤ የሚያሽንፋቸውና<br />

ለእኛ የሚበጀን ድርጅት ብቅ ሲል ሬዲዮኑም ካድሬውም<br />

ጥዋት ማታ ስም እየጠራ ይሳደባል፡፡ ተጠንቀቁ መጣባችሁ!<br />

ሊያጠፋችሁ ነው! እያለ እንደ ልጅ ሊያታልለን ይሞክራል<br />

ቅንጅት በነበረ ወቅት ቅንጅትን አውሬ አስመስሎ ሲነገረን ነበር፡<br />

፡ ኋላ ላይ ስንሰማ እንዲያ የጠሉት የእኛን ጥያቄ ስለሚያነሳ<br />

ነው አሉ፡፡ አሁን ደግሞ መድረክን እያሉን ነው፡፡ ታዲያ እኛም<br />

ሰማን ሰማንና ጐበዝ ይኽ መድረክ የሚሉት ደግሞ እኛን ነፃ<br />

የሚያወጣን ይሆናል ብለን አመንን፡፡ ለዚህ ነው መድረክ ጥሩ<br />

ነው ያልኩህ” ሲሉ አጫወቱኝ፡፡ “እነሱ ከጠሉት የእኛ ነው<br />

ማለት ነው፡፡” ሲሉ በለሆሳስ ነገሩኝ፡፡


2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />

ከአሸናፊ ደስታ ወንድም አገኘሁ<br />

ወቅታዊ<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

ሕወሓት ከደደቢት በረሀ መርሾ<br />

ማሃል አገር ገብቶ ዙፋን ላይ ከተቀመጠበት ጊዜ<br />

ጀምሮ በኢትዮጽያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ ብዙ<br />

ፍንዳታዎች ፈንድተው በብዙ ሚሊዮን ብር<br />

የሚገመት የኢትዮጵያ ሕዝብ ንብረት ወድሟል፡<br />

፡ በሰው ሕይወት ላይም እንዲሁ ብዙ ጉዳት<br />

ደርሷል፡፡<br />

ምንም እንኳን በዩኒበርሲቲው ላይ<br />

የሳት ቃጠሎ ባይደርስበትም፣ “የአገሩን ሠርዶ<br />

በአገሩ በሬ” በሚለው የአበው አባባል፣ባዕዳን<br />

መምህራንን ተክተው ሲያስተምሩ የነበሩ<br />

አንቱ የተባሉ አያሌ እውቅ ፕሮፌሰሮች ከሥራ<br />

ገበታቸው ተባረዋል፡፡ ይህም በራሱ በወቅቱ<br />

በትጉ መምህራን ሽብርና መቅሰፍት ነበር፡፡ በዚያን<br />

ወቅት በዩኒቨርስቲው ውስጥ የተወሰደው ርምጃ<br />

የመንፈስ ስብራት ዛሬም ድረስ ሊቃና አልቻለም፡፡<br />

ያወቅት በጣም አስጊ እና አደጋ<br />

የበዛበት ወቅት ስለነበር፣በወቅቱ የተባበሩት<br />

መንግሥታት ዋና ጸሐፊ የነበሩት የግብፅ ተወላጅ<br />

ቡትሮስ ቡትሮስ ጋሊን ለጉብኝት ወደ አዲስ አበባ<br />

መምጣት ተቃውሞው ሰላማዊ ሰለፍ በወጡ<br />

ተማሪዎች ላይ የጥይት በረዶ ተርከፍክሮባቸው<br />

ተገድለዋል፡፡ ተማሪዎቹ ሰላማዊ ሰልፍ የወጡበት<br />

ምክንያት ግልጽ ስለሆነ፣ከመናገር ተቆጥበን<br />

አልፈነዋል፡፡<br />

ወደ ተነሳሁበት ዋና ነገር ልመለስና<br />

የመጀመሪያው የአዲስ አበባ ነዋሪ ሕዝብ<br />

በሽብር ያናወጠው፣ማቄን ጨርቄን ሳይል<br />

ቤቱን ሳይዘጋ የሌሊት ልብሱን እንደለበሰ፣ቀበሮ<br />

እንደ ገባበት የበግ መንጋ ወደ እየአቅጣጫው<br />

ያስፈረጠጠው፣ከባድ፣እጅግ በጣም ከባድ ፈንዳታ<br />

ነፋስ ስልክ አካባቢ የፈነዳው ፍንዳታ ነበር፡፡<br />

በዚያ አደጋ በተጋለጠ ስፈራ ላይ ያ<br />

ፈንዳታ እንዲፈነዳ የተደረገው በዐፄ ኃ/ሥላሴ<br />

ዘመነ መንግሥት ተገንብቶ አገልግሎት በመስጠት<br />

ላይ የነበረን የሥንቅና ትጥቅ ዴፖ ለማውደም<br />

ሲሆን አጋጣሚ ሆኖ በዚያ አካባቢ ይኖሩ በነበሩ<br />

ነዋሪዎች ላይም በርካታ ቤቶች ተደርምሰዋል፡፡<br />

በቃጠሎ ወድመዋል፡፡ ይህ ነው የማይባል ንብረት<br />

ወድሟል፡፡ የሰው ሕይወት ሳይጠፋ አንዳልቀረም<br />

ተገምቷል፡፡<br />

ከላይ አንብበን እንደመጣነው<br />

ያ ወቅት በሳልና ጠሬውን ለመለየት ወይንም<br />

ማን ምን እንደሆነ ለይቶ ለማወቅ አስቸጋሪ<br />

የሆነበት ወቅት ስለነበር በፈንዳታው ፍንጣሪዎች<br />

ቤቶቻቸው የተደረመሱባቸው፣የተቃጠሉባቸውና<br />

ንብረቶቻቸው የወደሙባቸው አባወራዎችና<br />

እማወራዎች ዋይታ ሲያሰሙና ሲያነቡ<br />

የሚታዩበት ወቅት ነበር፡፡<br />

ስውር ደባ<br />

እነ አጅሬም ፍንዳታው በደረሰበትና<br />

በፍንዳታው በተደረመሱና በቃጠሎው<br />

በነደዱ ቤቶች ዙሪያ ወይም አካባቢ ቁምጣ<br />

ሱሪዎቻቸውን ታጥቀው፣ነጠላ ጫማዎቻቸውን<br />

ተጫምተው አንዳንዶቹ ፎጣቸውን ከአንገታቸው<br />

ላይ ጠምጥመው አንዳንዶቹ ደግሞ ፎጣቸውን<br />

ከራሳቸው ላይ ጠምጥመውና ጠብመንጃቻቸውን<br />

አንግበው፣የዚያን ከባድ ፍንዳታ ውጤት<br />

ለማየት ይርመሰመስ የነበረውን ሕዝብ “ወደዚያ<br />

ሂድ፣ወደዚህ አትጠጋ፣ወደዚህ አትቅረብ” እያሉ<br />

ይገረምሙ ነበር፡፡<br />

ከዚህበላይ ነግረን እንዳመጣነው፣ያ<br />

በከባድ ፈንዳታ የጋየ የሥንቅና ትጥቅ ዴፖ በዐፄ<br />

ኃ/ሥላሴ ዘመን መንግሥት የተገነባ፣ለሠራዊቱ<br />

ሥንቅ እንዲሆን ተዘጋጅተው የተቀመጡ ልዩ<br />

ልዩ የምግብ ዓይነቶች፣ልዩ ልዩ ጥይቶችና ልዩ ልዩ<br />

የጦር መሣሪያዎች የተከማቹበት<br />

ዴፖ ነበር፡፡ ይህም የዚች ሀገር ሀብት እንጂ<br />

የንጉሱ ወይንም የደርግ የግል ሀብት አልነበረም፡<br />

፡ ግን አጋጣሚውን ተጠቅሞ ሰርጎ የገባ<br />

ወይንም ከሕወሓት ጋር ተቀላቅሎ የመጣ ጠላት<br />

አቃጠለው፡፡ መጠነ ሰፊ የሕዝብ ንብረትም<br />

ወደመ፡፡ ይህም በዚያን ጊዜ የከፋና አስደንጋጭ<br />

ሽብር ነበር፡፡<br />

በኢትዮጵያዊነቱ ለሚያምንና<br />

የተከማቸን ብረትን ማውደም፣የአገር ቁርስን<br />

ማውደም መሆኑን ለሚያውቅና ለአገሩ<br />

ተቆርቋሪ ለሆነ ዜጋ፣የዚያ ሁሉ ንብረት<br />

መውደም፣ሳይቆጨውና ሳያንገበግበው<br />

እንደማይቀር ርግጠኛ ሆኖ መናገር ይቻላል፡<br />

፡ ይሁንና፣የፈሰሰ አልታፈሰ ነውና ከሚንቀለቀል<br />

እሣት ውስጥ እንደ ተጣለ ጅማት አሮ ተኮማትሮ<br />

ዝም ከማለት በስቀተር ሌላ መንም ለማድረግ<br />

ስለማይቻል እንደ ጅማቱ አረን ተቀብለነዋል፡፡ ዛሬ<br />

አገራችን ለኛ ባእድ እየሆነች ነው፡፡<br />

እንደሚታወቀው የነፋስ ስልክ አካባቢ<br />

ለአደጋ የተጋለጡ የነዳጅ ማደያዎች፣የእህል<br />

ጐተራዎች፣ከዕለት ጉርሳቸው በስተቀር ሌላ ቋሚ<br />

ንብረት የሌላቸው ባለብዙ ቤተሰብ አባውራዎች<br />

የሚኖሩበትና የኤሌክትሪክ መሥመር የተዘረጋበት<br />

በቀር ወረቀት አያሌ ሕፃናት የሚኖሩበት ት/<br />

ቤቶች ያሉበት በመሆኑ ለሽብር የተጋለጠ ነው፡፡<br />

ስለሆነም ነው የጦር መሣሪያ የተከማቸበት ዴፖ<br />

እንዲቃጠል የተደረገው፡፡<br />

ይህ ሁሉ ሆኖ አልፏል፡<br />

፡ የፈነዳ ፈንድቷል፤የወደመ ንብረትም<br />

ወድሟል፤የተቃጠለም ተቃጥሏል፡፡ የሞተ<br />

ሙቷል፣ግድ የለም፡፡ “በጊዜ ለኩሉ እንዳለው<br />

ቅዱስ ዳዊት” ለሁሉም ጊዜ ስላለው ጊዜው ሲደርስ<br />

የሚጠየቀው አጥፊ ይጠየቃል፡፡ ቢያንስ በታሪክ<br />

እንዲቀመጥ ይደረጋል፡፡ ደባውን ትውልድ<br />

እንዲያውቀው ተጽፎ ይቀመጣል፡፡<br />

ሁለተኛው ከባድ ፍንዳታ በሽሮሜዳ<br />

አካባቢ በአንድ የልዩ ልዩ ቁሣቁሦች ማከማቻ<br />

የፈነዳው ፍንዳታ ነበር፡፡ ምክንያቱ ከመጋዘኑ<br />

ውስጥ የነበሩ ልዩ ልዩ ፈንጂዎችና ሌሎች ልዩ ልዩ<br />

መሣሪያዎች ፈንድተው የአያሌ ሰዎች ሕይወትና<br />

ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሶ አልፏል፡፡<br />

ይህም በዚያን ወቅት የከፋ ሽብር ነበር፡፡<br />

ሦስተኛው ፍንደታ በለደታ<br />

ቤተክርስቲያን ማዶ ከባለወልድ ቤተክርስቲያን<br />

ዝቅ ብሎ ባሉት ቤቶች ውስጥ ከዐፄ ኃ/ሥላሴ<br />

ዘመነ መንግሥት ጀምሮ ጥይት ይከማችባቸው<br />

ስለነበር ያ ሁሉ ጥይት እንዲፈነዳና በአካባቢው<br />

ነዋሪ ሕዝብ ላይ ጉዳት እንዲያደርስ ሆነ ተብሎ<br />

እሳት በመለኮሱና በጥይቶቹና ሌሎች ፈንጂዎችም<br />

በመፈንዳታቸው የጥይቶቹ አረሮችና የሌሉች<br />

ፈንጀዎች ፈንጣሪዎች በሰው ሕይወትና በንብረት<br />

ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል፡፡ ይህም አሳፋሪ<br />

ሽብር ነበር፡፡<br />

ሌላውና አራተኛው ፍንዳታ የደረሰው<br />

ፒያሣ አካባቢ መብራት ኃይል መሥሪያ ቤት በስተ<br />

ጀርባ ትግራይ ሆቴል እየተባለ ይጠራ በነበረውና<br />

የትግሬዎች ዋና መናሐሪያ በነበረው ሆቴል<br />

ውስጥ የፈነዳ ቦመብ ሲሆን፣ሆቴሉ ከምድር<br />

ቤቱ አንስቶ ፎቆ ድረስ በቃጠሎ ወድሟል፡<br />

፡ በዚያ ወቅትም በሆቴሉ ውስጥ ይዝናኑ የነበሩ<br />

በርካታ ዜጎች ሞተዋል፤እንዲሁም ከፎቁ ላይ<br />

ተኝተው በነበረው ከምድር ቤቱ ውስጥ ሲጠጡ<br />

በነበሩትና በአሰላፊዎቹ ላይ ቃጠሎና የሞት<br />

አደጋ ደርሶባቸዋል፡፡ ቤቱም በጣም ወድሞ<br />

ስለነበር፣አሁን ከቦታው ላይ ሌላ ትልቅ ፎቅ<br />

ተሠርቶ ከሆቴል ቤትነት ወደ ሌላ ሸቀጣሸቀጥ<br />

ንግድ ቤትነት ተለውጦ በመሥራት ላይ ይገኛል፡፡<br />

በጣም የሚያስገርምና በጣም<br />

የሚያሳዝነው በዚያ ግዙፍ ሆቴል ላይ ያ ሁሉ<br />

ቃጠሎ ሲደርስ፣ያ ሁሉ ንብረት ሲወድምና በሰው<br />

ሕይወት ላይ የሞት አደጋ ሲደርስ ምክንያቱ ምን<br />

እንደሆነ አይታወቅም፡፡ አለመታወቁ ብቻ ሣይሆን<br />

ለማወቅም ጠረት አለመደረጉ አስገራሚ ድራማ<br />

ነው፡፡ ምኒልክ ዐደባባይ የሚገኘው በእሳት አደጋ<br />

ጣቢያ በወቅቱ ደርሶ ቃጠሎውን ለማጥፋትና<br />

የሰው ሕይወትና ንብረት ለማዳን፣አልሞከረም፡<br />

፡ ከጥፋቶቹ ብርቱ ክንድ ከበስተ ጀርባ እንዳለ<br />

በቂ ማሣያ ነው፡፡ አጥፊው አለመታወቁም በራሱ<br />

ሽብር ነው፡፡<br />

9<br />

ሌላው በጣም አሳዛኝ ወይም ሳይወሳ መታለፍ<br />

የሌለበት አንገብጋቢ ጉዳይ ትምህርቷን ጨርሳ<br />

የመመረቂያ ጊዜዋ ደርሶ ወላጆቿን ጠይቃ<br />

ለመመለስ ወደ ቦሌ በመጓዝ ላይ እንዳለች ውጭ<br />

ጉዳይ ሚኒስቴር ዝቅ ብሎ ቤተ መንግሥት አካባቢ<br />

ስትደርስ ከሚኒባሱ ውስጥ ተጠምዶ የነበረ ቦምብ<br />

ፈንድቶ ካሉት ተሳፋሪዎች ጋር አብራ የተቀሰፈችው<br />

ልጃ ገረድ ናት፡፡ ሌሎችንም፣አሷንም፣ልዑል<br />

እገዚአብሔር ነፍሳቸውን ይማር እንላለን፡፡ ይኸም<br />

በወቅቱ አሣፋሪ ሽብር ነበር፡፡ ብቻ ኢህአዴግ<br />

በሥልጣን ላይ ከወጣ ጀምሮ ከጥፋትና ከሽብር<br />

ወጥተን አናውቅም፡፡ መሸም ነጋም ሽብር ነው፡፡<br />

ዛሬም ከሽብር አልወጣንም፡፡ ነገር፣ኪነጋ ወዲያም<br />

አንወጣም፡፡<br />

ሌላው ሳይወሳ ተዘሎ መታለፍ<br />

የሌለበት ታሪካዊ ጉዳይ በሰማይ ነፈሳቸውን<br />

ይማረውና የመላው አማራ ድርጅት የተባለ<br />

የፖለቲካ ፓርቲ አቋቁመው ባያተርፉት ኖሮ<br />

የብሔርን ትርጉም ጠንቅቀው የማያውቁ ጐሰኞች<br />

የቀበሌ መታወቂያ ላይ “ብሔር አማራ” የሚል<br />

ቅጽል የተሰጠው የኢትዮጵያ ዜጋ መጨረሻው ምን<br />

ይሆን ነበር? የሚል ጥያቄ ማስከተሉ አይቀርም፡፡<br />

በ1984 ዓ.ም የተባለው ድርጅት<br />

ተቋቁሞ የብዙ ንጹሐን ዜጐች ሕይወት<br />

እስከታደገበት ጊዜ ድረስ አያሌ ንጹሐን ዜጐች<br />

ተገድለዋል፤ወደ ገደል ተጥለዋል፤አሰቦት የተባለ<br />

ገዳም ተቃጥሏል፤ገዳሙን ሲያገለግሉ የነበሩ<br />

መነኮሳትም ተገድለዋል፡፡ ይህም በታሪክ ልንረሳው<br />

የማንችለው ክፉ የዘር ሽብር ነበር፡፡ በአማራ<br />

ሕዝብ ላይ የተፈፀመ ሁለገብ ዘመቻ ትውልድ<br />

በክፋቱ ሲያወሳው የሚኖር ከሽብሮች ሁሉ<br />

የከፋው ሽብር ነበር፡፡<br />

በመሠረቱ ሕወሓት አዲስ አበባን<br />

ከረገጠበት ወቅት አንስቶ የተለያዩ ሽብሮች<br />

ተካሒደዋል፡፡ ለነዚያ አያሌ የሰው ሕይወትና<br />

የንብረት ውድመት ለደረሱት ሽብሮች ኃላፊነትን<br />

የወሰደ ግለሰብ፣ቡድን ወይም ድርጅት ግን<br />

እስካሁን ድረስ አልተገኘም፡፡<br />

ስለዚህ ክቡር የሰው ሕይወትና ንብረት እንደ<br />

ወደመ ታፍኖ ይቅር የሚል ሕግ ስለሌለ የሕግ<br />

ልዕልና የሚያከብርና ሐቅን የሚከተል አካል እስከ<br />

ሚገኝ ድረስ ወይም በሌላ አነጋገር ኢህአዴግ<br />

በሥልጣን ላይ እስካለ ድረስ ታፍኖ ይቆያል፡፡<br />

እስከዚያው ግን ከሽብር ማጥ ውስጥ መውጣት<br />

አንችልም፡፡ በመሆኑም ልዑል እግዚአብሔር<br />

እንዲገላግለን እሱን መማፀን ተገቢ ነው፡፡<br />

ከሲኦል ያመለጡ የኢህአዴግ አባላት<br />

ከመ/ር ቀለሙ ሁነኛው<br />

በአንድ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ<br />

ዜናዊ “የኢህአዴግ ስልጣን ዛፍ ላይ ወጥቶ እንደ<br />

ማንቀላፋት ነው ይሉና ፍሬውን ለቅመው ይወርዳሉ”<br />

ሲሉ በተሻDሚዎቻችው ላይ አፊዘው እንደነበር<br />

ሰምቻለሁ፡፡ መዳፈር አይሁንብኝና በራሳቸውም ላይ<br />

ያፌዙ ይመስለኛል፡፡ ፍሬውን የለቀሙት ግን እነማን<br />

ናቸው? በአርግጥም የዛፍ አናት ላይ ቁጢጥ ያሉት<br />

ለበሰለው ፍሬ እጅግ የቀረቡ በመሆናቸው እንዳሻቸው<br />

እጃቸውን እየዘረጉ ለቅመዋል፤እየለቀሙም ነው፡<br />

፡ ከታች ያሉት ተሻሚዎች ደግሞ ከጌቶቻቸው<br />

የተራረፈውን ለመቃረምም ይሁን ከቅንነት በመነጨ<br />

አመለካከት የኢህአዴግን ልማታዊ መንግሥትነት<br />

ለመደስኮር እንደ ክልፍልፍ ውሻ ነጋ ጠባ በየመንደሩ<br />

ሲዘሩ ያተረፉት ቢኖር “ዘመናዊ ቆራሊዮ”የሚል<br />

ስያሜ ነው፡፡ አሁንማ በየወረዳው የተሾሙ<br />

ካቢኔዎችና ግንባር ቀደም ካድሬዎች ውሎአቸው<br />

በየመንደሩ መሆኑ ክፉኛ አማሯቸዋል፡፡ ከዚህ<br />

አንፃር በግምገማም ይሁን በተገኘው ቀዳዳ ሾልከው<br />

መውጣትን ይሻሉ፡፡ በብዛትም እየወጡ ናቸው፡፡<br />

በቅርቡ ከአመራርም ሆነ ከአባልነት የተሰናበቱና<br />

ወደ ቀድሞ ሥራቸው የተመለሱ “ከሲኦል ያመለጡ”<br />

ወጣቶች በግልፅ ይናገራሉ፡፡ ከእስር እንደተፈታ ሰው<br />

ነው ራሳቸውን የሚቆጥሩት፡፡ በየአደባባዩም “እንኳን<br />

ደስ ያለህ/ያለሽ!” ሲባባሉ ይሰማል፡፡ በተለይም በየወሩ<br />

ከደመወዛቸው የሚቆረጠው ገንዘብ፣የጋዜጣና<br />

የመፅሄት ክፍያ በአባላቱ ቋንቋ” የማይደርስ ዕቁብ”<br />

የሚሉት የድርጅቱ ክፍያ፣የሕዳሴው ግድብ መቶ<br />

ፕርሰንት መዋጮ . . . /የሕዳሴው ግድብ መዋጮ<br />

ከኛም ደመወዝ በግዴታ መወሰዱ ሳይዘነጋ/<br />

ኑሮአቸውን ከማቃወሱ ባሻገር በገንዘባቸው ላይ<br />

ማዘዝ የማይችሉ እንደነበረ በምሬት ይገልፃሉ፡<br />

፡ ይበልጥ ደግሞ ፋታ የማይሰጠው የኢህአዴግ<br />

ግምገማ ከሰውነት ተራ አውጥቷቸዋል፡፡ የወጣትነት<br />

ሞራላቸውን ያላሸቀ ግምገማ እጅግ አድርጎ<br />

ከርፍቷቸዋል፡፡ በራስ የመተማመን ስሜታቸውን<br />

ክፉኛ ጎድቶታል፡፡ የዚህ አስተያየት ፀሐፊ እነዚህ<br />

ወጣቶች የስነ ልቡና ሀኪም እንደሚያስፈልጋቸው<br />

ያምናል፡፡<br />

ከሲኦል ካመለጡ ወጣቶች አንዳንዶቹ ካወጉልኝ<br />

ገጠመኞቻቸው መሀከል ባንድ ወቅት የኢህአዴግን<br />

የፖለቲካ መስመር ለመስበክ በየመንደሩ እየዞሩ<br />

በር ሲያንኳኩ አንዲት እማወራ “ኽረ ውሾቹ<br />

እንዳይነክሷቸው” ሲሉ አባወራው ቀበል አድርገው<br />

“ምንነካሽ?! ውሾቹ ከእኛ ይልቅ የሚያውቁት እነሱን<br />

አይአለም እንዴ?!” ያሏቸው ከልብ አስደንቆኛል፡፡<br />

በ2002 ምርጫ ወቅት ጠቅላይ ሚንስትሩ<br />

ሳይቀሩ የኢህአዴግ አባላት ቁጥር ሰባት ሚሊዮን<br />

እንደሚደርስ በኩራት ሲናገሩ ነበር፡፡ “ውስጡን<br />

ለቄስ” እንዲሉ፡፡ አሁን አሁን ግን ይህንን አሀዝ<br />

በእርግጠኝነት ደፍሮ የሚናገር የለም፡፡ የድርጅቱ<br />

ገመና በራሱ የድርጅቱ አባላት ገሀድ እየወጣ ነው፡<br />

፡ በራሱም ጊዜ መፈራረስ ጀምሯል፡፡ “እከሊትን ያየ<br />

በእሳት አይጫወትም” እንዲሉ ከሲኦል ያመለጡትን<br />

የኢህአዴግ አባላት የሞራል ድቀትና ምሬት ያስተዋለ<br />

እንኳን አባልና ደጋፊ ሊሆን አይፈልግም፡፡<br />

የዚህ አስተያየት ፀሀፊ ለዚህ አንድ መረጃ አለው፡<br />

፡ በዚህ ወር እንኳን ከየወረዳው በተባረሩ አመራሮች<br />

መትክ ተረኛ ተዋራጆችን ለመመደብ ድርጅቱ<br />

ያደረገው ጥረት ከንቱ ልፋት ሆኗል፡፡ በየመስሪያ ቤቱ<br />

የሚገኙ አባላቱ በተደጋጋሚ ቢለመኑም አሻፈረን<br />

ብለዋል፡፡<br />

ኢህአዴግ መቼም “አልሞት ባይ ተጋዳይ” ነው፤<br />

አንድ ቀን ጥርስ የሌለው አንበሳ መሆኑ ባይቀርም<br />

/አባባሉ ጋዳፊንም ያስተውሏል/፡፡ ጥቅምት 18<br />

ቀን 2004 ዓ.ም በመዲናችን አዲስ አበባ በሚገኙ<br />

ፕላዝማ ቴሌቪዥን በተዘረጋባቸው ት/ቤቶች<br />

በየወረዳው የሚገኙ አባላትን ለመሰብሰብ ተሞክሮ<br />

ነበር፡፡ የምክትል ከንቲባውና የሌሎች የአዲስ አበባ<br />

መስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ከሥልጣናቸው<br />

መባረር በመጠኑም ቢሆን ኢህአዴግን ያሳስበዋል፡፡<br />

የእያንዳንዳቸው የግንኙነት ሰንሰለት እስከ ወረዳዎች<br />

ወርዶ ተራ አባላትንም ስለሚያካትት የአኩራፊዎቹ<br />

ቁጥር ማሻቀቡ አይቀርም፡፡<br />

በጣም የሚያስገርመው ግን ከመስከረም<br />

15/2004 ጀምሮ የትምህርት ሥርጭት ይጀምራል<br />

የተባለው የፕላዝማ ቴሌቪዥን አስታዋሽና ባለቤት<br />

አጥቶ እስከ ጠቅምት 18/2004 ባልጀመረበት<br />

ሁኔታና የቴክኒክ ችግር እንዳጋጠመ ሲነገር እንዳልቆየ<br />

የኢህአዴግን አባላት ለማወያየት ግን መፍትሄ<br />

ተገኘለት፡፡ በሰበቡም የፕላዝማው ትምህርት<br />

ተጀመረ፡፡ የትምህርት ጥራት ይሏችኋል ይሄ ነው፡፡<br />

ሀሳቤን የምቋጨው በስብከት ነው፡፡ ስብከቱ<br />

ግን ቤተ እምነቶችን አይመለከትም፡፡ በሲኦል ያሉ<br />

ቤተ-ኢህአዴጎችን አይመለከትም-በሲኦል ያሉ<br />

ቤተ-ኢህአዴጎችን እንጂ ሰባኪው እንዲህ ይላል፡፡<br />

“የመዳን ቀን አሁን ነው! በሕይወት ሳሉ እንጂ ከሞት<br />

በኋላ ከሲኦል ማምለጥ አይቻልም፡፡ ቢጤዎቻችሁ<br />

በኢህአዴግ የግምገማ መድረኮች ለራሳቸው የደረጃ<br />

ውጤት “ር” እየሰጡ ከሲኦል አምልጠው ከኢትዮጵያ<br />

ሕዝብ ጋር በንሰሐ እንደተቀላቀሉ ሁሉ መንታ<br />

መንገድ ላይ የቆማችሁ የድርጅቱ አባላትም ጊዜ<br />

አተባክኑ! ፍጠኑ! መዳን ይሆንላችሁ ዘንድ አትፍሩ!<br />

አትፍሩ! “ር” ውጤት ማስመዝገብ የሚያሳፍረው<br />

ለዩኒቨርሲቲ ትምህርት ነው፡፡ በኢህአዴግ ግምገማ<br />

“ር” ማስመዝገብ ግን ጀግንነት ነው፤ “F” ማስመዝገብ<br />

ደግሞ ከጀግንነትም በላይ ጀግንነት ነው!!<br />

ፈጣሪ አምላክ ኢትዮጵያን ይባርክ!<br />

www.andinet.org.et


10<br />

ከብሩክ ከበደ<br />

www.andinet.org.et<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

“ ነጋ-እንዴና የግብሩ አብዮት”<br />

ከላይ የተቀመጠውን ርዕስ የተጠቀምኩት<br />

ለቀጣይ ፅሁፌ አንድም ሁለትም<br />

ትርጉም እንዲሰጥልኝ በማሰብ ነው፡<br />

፡ አንደኛው መጠይቂያዊ ወይም ቃል<br />

አጋኖአዊ ትርጓሜ የያዘው የቃላቱ<br />

ዘርፍ ሌሊቱ አልፏአል፣ ነግቷል፣ ፀሐይ ወታለች የሚል<br />

ጥያቄ አዝሎ በመንጋቱ የሚቆጭም፣ የሚደነግጥም፣<br />

የሚደሰትም ሲመስል፤ በሌላ በኩል ደግሞ ነግቷል<br />

ፈጥኜ ለሥራ ጀንበሯን ልቀላቀል የሚል መልህክት<br />

ይይዛል፡፡<br />

ሌላውና ዋነኛው ከዚህ ጋር የተያያዘው<br />

ደግሞ በላቡና ጥረቱ ብቻ ለማደግ የሚጣጣረው<br />

የነጋዴ ክፍል ንጋትን በናፍቆት እንደሚጠብቃት<br />

የታወቀ በመሆኑ አዲስ የሽያጭ ዕቃ ለማስገባት፣<br />

አዲስ ትርፍ ለማግኘት፣ አዲስ ዘርፍ ለመክፈት ካለው<br />

ጉጉት በመነሣት የንጋት ጥያቄና ነጋዴ የሚነጣጠሉ<br />

አይደሉም፡፡ ለዚህም ነው ሳድሶችን በማስወገድ ራሱን<br />

የቻለ ትርጉም የሚሰጥ “ነጋዴ” የሚለውን ሥርወ /ቃል<br />

እንዲያነግስ ያመቻቸሁት፡፡<br />

ይህስ ሆነ ቃሉን ግን እንዲህ ለመሰነጣጠቅ<br />

መልሶም ለማዛመድ ያበቃህ ምንድነው? የሚል ጥያቄ<br />

ሊነሣ ይችላል፡፡ ቢነሣም ተገቢ ነው፡፡ ምክንያቱም<br />

የሰኔ ሰማይ ማጉረምረም ሲጀምር ሁለቱ የቴሌቮዥን<br />

መስመሮች፣ ዋናውን ሬዲዮ ጨምሮ የተለያዩ ኤፍ<br />

ኤም ጣቢያዎች፣ በመንግስት የሥራና በውጭ ቋንቋ<br />

የሚታተሙ የህትመት ውጤቶች፣ በያደባባዩ፣ በተለያዩ<br />

ህዝባዊና መንግስታዊ ተቋማት ደጃፍ የሚሰቀሉ<br />

መፈክሮችና ጥቅሶች ወዘተ ግብር መክፈል ግዴታ<br />

ብቻ ሳይሆን የዜግነት ድርሻ እንደሆነ በሚያስገነዝቡና<br />

በሚያስተምሩ ጽሁፎች ይጥለቀለቃሉ፡፡<br />

በተለይ ዘንድሮ ከመቼውም በተለየ መልኩ<br />

ግብር፣ ክፍያውንና ሂደቱን በተመለከተ ከከፍተኛ<br />

የስራ አላፊዎች እስከመምሪያና ክፍል አለቆች ተራ<br />

ሠራተኞች እስከ አንዳንድ የከተማ ነዋሪዎች ተብለው<br />

እስከሚጠቀሱት ድረስ በየመገናኛ ብዙኃኑ እየቀረቡ<br />

በተቀነባበሩ ቃለምልልሶችና የውይይት መድረኮች<br />

የተነገራቸውን በሰፊው ለማስረዳት ሲጨነቁና<br />

ሲውተረተሩ መመልከት የዘወትር ጸሎት ያህል<br />

የሚደጋገም ነበር፡፡<br />

ግማሹ የመንግስት ተቀጣሪ ሠራተኛ<br />

በአንዳንዱ ነጋዴ ላይ በተጣለው (በተወረወረው)<br />

ከፍተኛ ግብር ባያምንበትም ስራው ደሞዝ<br />

የሚያገኝበት ብቻ በመሆኑ ለከፋዩ ያንያህል ግብር<br />

ለምን እንደተጣለበት ለማሳወቅ በቂ ግንዛቤ ይሁን<br />

በቂ ማብራሪያ መስጠት የተሳነውና እየተውለፈለፈ<br />

ለማን አቤት እንበል...<br />

በየጫካው እየዞሩ እንደዱር አውሬ ይጮሁ ነበር::<br />

በየቁጥቋጦው ስር ተጠግተው ይኖሩ ነበር፡፡<br />

አሁን ግን ልጆቻቸው እየሰደቡኝ ይዘባበቱብኛል::<br />

ተፀይፈውኝ ከእኔ ይርቃሉ<br />

ማምለጫና ኡፎይ የምታሰኘውን “የመንግስት መመሪያ<br />

ነው” የምትለውን ቃል በመሰንዘር የዜጎችን መብትና<br />

ግዴታ እንደግዴታ ብቻ ቆጥሮ “አበቃሁ ጨርሻለሁ”<br />

የሚል ሲቪልሰርቫንት (የመንግስት ተቀጣሪ )<br />

መመልከት ሆነ ሊያጋጥም የሚችለው ይኽችው ሰኔ<br />

ስትመጣ ነው፡፡<br />

ጉዳዩ ይመለከተናል፣ ያገባናል የሚሉት<br />

ተቋማትና ግለሰቦች የሚናገሩትን፣ በማስታወቂያና<br />

ማስጠንቀቂያ ብዛት የሚያጨናንቁትን የግብር<br />

ክፍያ ከተወሰነው በቀር ቁብ ሰቶት የሚከታተላቸው<br />

እምብዛም ነው፡፡ ለምን ቢባል ስር የሰደደው<br />

አንዳንዴም ያልተጠናው እና ያልታሰበበት መልሶም<br />

የሚዘነጋው ጨርሶም ትቼዋለሁ ሊባል የሚችለው ክፍያ<br />

ቀድሞ ግዴታውን የተወጣውን ሲጐዳ እንጂ ሲጠቅም<br />

አለመመልከቱ በህይወት ልምድና ኑሮ ሲያልፍበት<br />

የቆየውነው፡፡ ለዚህም በ1997 ዓ.ም ተፈጥሮ የነበረውን<br />

እና መልሶ የከሰመውን የግብር አብዮት ግብረኛው<br />

በሚገባ የሚያውቀው ብቻ ሳይሆን የተቀጣበትም<br />

ነውና፡፡<br />

ከዚህ ከደነደነ የግብር አከፋፈል ትከሻው<br />

ልምዱ በመነሳት “ደግሞ ይሔ ግብር መጣ !” እያለ<br />

ከመዘባበትና ጊዜው ሳያልቅ ክፈሉ የሚለውን<br />

ማስጠንቀቂያ ችላ በማለት የተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ<br />

ሊያልቅ ሁለት አልያም አንድ ቀን ሲቀረው ከሚደርሰው<br />

መጨናነቅ የዘለለ አዲስ ነገር አይጠበቅም፡፡ ዘንድሮ<br />

ግን ይህን አካሄድ በመጠኑ የሚገለባብጠው አስጨናቂ<br />

ጉዳይ ተፈጥሮ ግብረኛው ማማረር ብቻ ሳይሆን ከፈለጉ<br />

ያሸጉት ሲልም በንግድ ቤቱ ላይ የፈረደበት ይመስላል፡፡<br />

ግብር አስከፋዩን በየጊዜው ገማቾች<br />

የገመቱት ነው በሚለውና አንዳንዴም የተጠና<br />

የማይመስለውን ግብር በከፋዩ ላይ ሲከምረው ከፋዩ<br />

እንዴት እንዲህ ሊሆን ይችላል አስረዱኝ? በሚልበት<br />

ጊዜም መጀመሪያ የተጣለብህን ግማሹን ክፈልና<br />

አቤቱታህን ማቅረብ ትችላለህ የሚል አገር ያለህዝብ<br />

ባዶ መሆኗን ያልቃኘ ምላሽ ይቀርብለታል፡፡ ይህንንም<br />

የሚጠናክርሎት ምላሽ ገንዘብንና ገንዘብን ብቻ ያማከለ<br />

አሰራር እንዲሰሩ የተዋቀሩት የየክፍለ ከተማው ገቢዎች<br />

ሰራተኞች በሚገባዎት ቋንቋ ያስረዳዎታል፡፡ እነዚሁ<br />

በአንዳንድ ክፍለ ከተማ በአንድ ወንበር ላይ ሁለትና<br />

ሦስት ሠራተኞች ሆነው ተደራርበው ሲተረማመሱ<br />

ለሚመለከት ታዛቢ ግብር አስከፋዩ ገንዘብን ብቻ<br />

መሰብሰብ የሚል መመሪያ የሚከተልና ከሰው በፊት<br />

ገንዘብ እንዲቀድም የሚፈልግ ይህንኑም በትጋት<br />

የሚሰብክ ቢመስለው አይፈረድበትም፡፡<br />

እነኚህ በየክፍ ከተማው ያሉ የፋይናንሱ<br />

የስራ ኃላፊዎችና ተራ ሠራተኞች በርካታ ሚሊዮኖችን<br />

ሰብስበው በከፍተኛ የሥራ አለቆቻቸው ለመመስገን<br />

ከገፅ 4 የዞረ<br />

ያለ አንዳች ፍርሃት እፊቴ ምራቃቸውን ይተፋሉ<br />

እግዚአብሄር ሃይሌን አድክሞ ስላዋረደኝ እነርሱም<br />

ልጓሙ እንደወቀለት ፈረስ በላዬ ይፈነጩብኛል፡፡<br />

የኛ ሲቃይም ከላይ ከተጠቀሰው ከኢዮብ<br />

የሰመጉ ጥሪ<br />

ብሎም ዋንጫና የምስክር ወረቀት ከግብር ከፋዩ<br />

በሚሰበሰበው ገንዘብ ድል ያለ ድግስ ደግሰው<br />

ለመቀበልና ለመሸላለም በሚያደርጉት ነፍስ ውጪ ነፍስ<br />

ግቢ አካሄድ ግብር ከፋዩን ህብረተሰብ እስከ ማማረር<br />

የሚደርስ ነው፡፡ በተጨማሪም በተመሣሣይ ስራና ሙያ<br />

ላይ ያለው የግብር አከፋፈል እና አወሳሰን አንዱ ክፍለ<br />

ከተማ ከአንዱ የሚለያይበት አጋጣሚ ስለሚፈጠርም<br />

እርስ በእርሱ የሚነጋገረው ነጋዴ በልዩነቱ ላይ አጥብቆ<br />

ሲማረር ይደመጣል፡፡<br />

ግብርን በወቅቱ ሰብስበን ለመሠረተ ልማት፣<br />

ለዳንድበር ጥበቃ፣ ለደን ልማት ወዘተ እያለ ግብር<br />

አስከፋዩ ተቋም በየጊዜው ቢወተውትም ግብር ከፋዩ<br />

ሕዝብ ግን የሚከፍለው ግብር ለአላስፈላጊ የመንግስት<br />

ተቋማት ልዩ ልዩ ወጪዎች እየዋለ ነው የሚለው<br />

ምክንያት እልባት እስካልተገኘለት ወይም እስካልተሻሻለ<br />

ድረስ ግብርን በትጋት ለመክፈል የሚያበረታታ<br />

አይመስልም፡፡ ይህን አባባል በምሣሌ ለማስረዳት<br />

ካስፈለገም አንድ የገጠር የውስጥ ለውስጥ ጥርጊያ<br />

መንገድን አሊያም ንፁህ የመጠጥ ውሃን ወይንም<br />

አንደኛ ደረጃ ት/ቤትን ለመመረቅ የሚጠሩ እንግዶች<br />

በተናጥል እያግተለተሉ ይዘዋቸው የሚነግዱትን<br />

በሚሊዮኖች የሚቆጠር ግንዘብ የፈሰሰባቸውን<br />

ተሽከርካሪዎች መመልከት ይበቃል፡፡ ጭርሱንማ አሁን<br />

አሁን ያአንዳንድ መስሪያ ቤት ሹመኞች V-8(ቪ-ኤይት)<br />

የተባለውንና ከ3 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣውን<br />

ተሽከርካሪ ካልተገዛልን እያሉ ነው የሚል ጭምጭምታ<br />

እየተሰማ ነው፡፡ ከነሱ የቀደሙትና በእጃቸው ያስገቡት<br />

ግን በከተማችን ውስጥ ሲፈሱበት እየተመለከትናቸው<br />

ነው፡፡<br />

ከዚህ ውጪ ለአዲስ እና ለተጀመሩ<br />

ፕሮጀክቶች ማስፈጽሚያ፣ ለዕቃ ግዢ ወዘተ. እየተባለ<br />

የሚባክነው እና የሚወድመው አንሶ የ----------- መ/<br />

ቤት የስራ ኃላፊ፣ ገንዘብ ያዥ፣ ዕቃ ግዥ----------<br />

ሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ይዞ ተሰወረ፡፡ የ--------<br />

ክፍለ ከተማ የመሬት አስተዳደር ባለሥልጣን ከሁለት<br />

ሚሊዮን ብር በላይ መዘበሩ፡፡ ወዘተ የሚሉና የመሳሰሉ<br />

ዜናዎች መደጋገሙ አገር ብቻ ሳይሆን ግለሰቦችም<br />

የሚለሙት ባንተ ኪስ ነው እየተባለ በተዘዋዋሪ<br />

የሚነገረው ግብር ከፋይ በተለይ ደግሞ ታታሪውና<br />

ሀቀኛው ነጋዴ “ገንዘቤ የበላተኛ ሲሳይ ሆኗአል” እያለ<br />

ዘወትር ቢቆጭና ስለግብር የምሰማበት ጆሮ የለኝም ቢል<br />

ማን ይፈርድበታል?፡፡<br />

ከዚህ ውጪ ሕዝብ ግብር በመክፈሉ፣<br />

ግዴታውን በመወጣቱ የሚደረግለት ተመጣጣኝ<br />

ነገር ባለመኖሩም ቀበሌ ሆነ እስታዲዮም፣ ሆስፒታል<br />

ሆነ አውቶብስ ተራ የሚያጋጥመውን ሰልፍ፣ ጡጫና<br />

ልምጭ፤ በየፖሊስ ጣቢያው፣ ፈርድ ቤት ሕክምና<br />

ወደ 13 ዞሯል<br />

ሲቃይና መከራ ቢበልጥ እንጂ አያንስም ችግራችን<br />

በዝቷል፤ ሸክማችን ከብዷል፤ እንዲቀልልን ለማን<br />

አቤት እንበል?<br />

የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ሰመጉ) በቀድሞው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉበኤ /<br />

ኢሰመጉ/ የቆመው ለህግ ልዕልና፣ ለዲሞክራሲና ለሰብአዊ መብቶች መከበር ነው፡፡ የሰመጉ<br />

አባል ይሁኑ፡፡ ዓላማውን ለማስፈጽም ይችል ዘንድ በገንዘብ ይደግፉ፡፡<br />

ስልክ 011 551-44089/011 551-77-04<br />

አድራሻ ሣህለ ሥላሴ ሕንፃ 8ኛ ፎቅ ከአዲስ አበባ ስታዲየም ፊት ለፊት<br />

2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />

የሰመጉ ይግባኝ በፌዴራል<br />

ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ችሎት<br />

ሊታይ ነው<br />

በቀድሞ አጠራር የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ<br />

(ኢሰመጉ) በአሁኑ የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ሰመጉ)<br />

በበጐ አድራጐት ድርጅቶችና ማህበራት ያለአግባብ<br />

የባንክ አካውንቴ ታግዶአል በማለት ከፍቶት የነበረው<br />

ክስ በፌደራል በከፍተኛ ፍ/ቤት ውድቅ በመደረጉ<br />

ለፌደራሉ ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ችሎት ይግባኝ ጠይቋል፡<br />

፡ ጉዳዩ “በይግባኝ ያሳቀርባል ወይስ አያስቀርብም<br />

በማለት የተመለከተው ሠበር ችሎት ያስቀርባል ወይስ<br />

አያስቀርብም በማለት የተመለከተው ሠበር ችሎት<br />

ያስቀርባል ተብሎ ብይን መስጠቱን” ከሰመጉ ያገኘነው<br />

መረጃ ይገልጻል፡፡<br />

በዚሁ መሠረት በከፍተኛ ፍ/ቤት የተፈጠረውን የህግ<br />

ጥሰት በማንሳት በሰበር ችሎት ለመከራከር ሰመጉ ዝግጅት<br />

እያደረገ መሆኑን” ገልጸዋል፡፡ ከሠመጉ ባገኘነው መረጃ<br />

መሠረት “የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ(ሰመጉ)፣ በቀድሞ<br />

አጠራር የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ)<br />

መንግስታዊ ያልሆነ፤ ከየትኛውም ፖለቲካ ድርጅት<br />

ጋር ያልወገነ ነፃ ድርጅት ነው፡፡ ጉባኤው የቆመው<br />

ለሕግ ልዕልና፤ ለዴሞክራሲ እና ሰብአዊ መብቶች<br />

መከበር ነው፡፡ በቅርቡ ባጋጠመው ችግር ምክንያት<br />

ሥራ እንቅስቃሴው በመድከሙ ጨርሶ ሥራውን ያቆመ<br />

የመሰላቸው በርካታ ሰዎች እንዳሉ ተገንዘበናል፡፡ ሆኖም<br />

ለአላማው ፅኑ እምነት ባላቸው አባላቱ እና ጥቂት<br />

ሠራተኞቹ እየታገዘ አሁንም በመንቀሳቀስ ላይ እንደሆነ<br />

ለደጋፊዎቹ ሁሉ ለማሳወቅ እንፈልጋለን፡፡<br />

ቀደም ሲል ጉባኤው በአብዛኛው ድጋፍ ያገኝ የነበረው<br />

ከውጭ አገር ለጋሾች እንደነበር ይታወሳል፡፡ ሆኖም<br />

አዋጅ 621/2001 በሰብአዊ መብቶች ማስከበር<br />

አኳያ የሚንቀሳቀሱ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች<br />

ከአመታዊ ገቢያቸው ዘጠና በመቶ ማግኘት ያለባቸው<br />

ከአገር ውስጥ ምንጮች መሆን እንዳለበት በመደንገጉ<br />

ገቢው በእጅጉ ቀንሷል፡፡ ከአባላት ሊሰበሰብ የቻለው<br />

ገቢ አነስተኛ ከመሆኑም ሌላ ጉባኤው ለመቋቋሚያ<br />

ብሎ አሥራ ስምንት ዓመታት ሙሉ በማጠራቀም<br />

በባንክ ያስቀመጠው ገንዘብ በበጎ አድራጎት ድርጅቶች<br />

እና ማህበራት ኤጀንሲ ታግዶበት ለማስለቀቅ በክስ ላይ<br />

ይገኛል፡፡<br />

`ሰመጉ` ላለፉት 20 ዓመታት በ12 ቅርንጫፎች እና<br />

ለሰብዓዊ መብት ዴሞክራሲ እና የህግ የበላይነት<br />

መስፈን ፅኑ ፍላጎት ባላቸው ሠራተኞቹ የሰብአዊ<br />

መብት ተጠቂዎች ለጉዳታቸው ድምፅ እንዲያገኙ እና<br />

አጥፊዎቹም እንዲታረሙ በሰፊው ተንቀሳቅሷል፡፡ ከላይ<br />

የተጠቀሰው አዋጅ እስከወጣበት ጊዜም `ሰመጉ` 58<br />

ሠራተመፐች 3 የሥራ ሂደቶች እና 8 ንዑስ የሥራ ሂደቶች<br />

የነበሩት ሲሆን በ2001 ብቻ በ16 የሰብአዊ መብት ጥሰት<br />

መርማሪዎች እና በ12 ቅርንጫፎቹ በመንቀሳቀስ 1723<br />

የሰብአዊ መብት ምርመራዎችን አድርጓል፤ 3 መደበኛ<br />

ሪፖርቶችን እና 6 ልዩ መግለጫዎችን አሳትሟል፡፡<br />

አዋጅ 621/2001 ከወጣ ጊዜ ጀምሮም በተከተለው<br />

አሉታዊ ተጽዕኖ ምክንያት አቅሙ በመዳከሙ ዘጠኝ<br />

ቅርንጫፎቹን ለመዝጋት የተገደደ ሲሆን 85%<br />

ሠራተኞቹንም አጥቷል፡፡ ይህም `ሰመጉ`በመላው<br />

ኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ተጎጂዎችን ጩኽት<br />

በማሰማት እና ከጎናቸው በመቆም ሲያደርግ የነበረውን<br />

የማይተካ ሚና ያስተጓጎለበት ከመሆኑም በተጨማሪ<br />

በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግሥት ማንኛውም ሰው<br />

ለማንኛውም ዓላማ ማህበር የማደራጀት መብት አለው<br />

የሚለው ድንጋጌ ከማጠናከር ይልቅ ውጤት አልባ<br />

የሚያደርግ ነው፡፡ በተለይም የኢትዮጵያ ህዝብ ድምፁን<br />

ከማጠናከር ይልቅ ውጤት አልባ የሚያደርግ ነው፡<br />

፡ በተለይም የኢትዮጵያ ህዝብ ድምፁን ሲያሰማበት<br />

የነበረውን `ሰመጉ`ን በማዳከም ዋናው የህጉ ተጎጅ<br />

`ሰመጉ` ሳይሆን ሲያገለግለው እና ድምፁን ሲያሰማለት<br />

የነበረው ህዝቡ ነው፡፡ ምንም እንኳን ይህ ሁኔታ<br />

ከፍተኛ ጫና ያሣደረብን ቢሆንም ሰመጉ በሰብአዊ<br />

መብት፣ ዲሞክራሲ እና በህግ የበላይነት ፅኑ እምነት<br />

ባላቸው ኢትዮጵያውያን በመታገዝ ሥራዎቹን ቀጥሏል<br />

ለወደፊትም ይቀጥላል፡፡ አሁንም ባሉት ሠራተኞ<br />

በመታገዝ 5 ልዩ መግለጫዎችን እና 1 መደበኛ ሪፖርት<br />

አውጥቷል፡፡<br />

ጉባኤያችን እስካአሁን ሲታገል የቆየው ለህዝብ መብቶች<br />

መከበር እንደመሆኑ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ሊደግፉት<br />

ይገባል የሚል እምነት አለን ስለሆነም ገቢ ለመሰብሰብ<br />

በምናደርገው ጥረት ሁሉ ተካፋይ እንድትሆኑ ከአደራ<br />

ጭምር እናሳስባለን፡፡” ብለዋል፡፡


2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />

ዜና<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

የሠራተኞችን ደሞዝ ለመቀማት ሲል 3ሰው ገድሎ<br />

2 ሰው ያቆሰለው ፖሊስ በቁጥጥር ሥር ዋለ<br />

በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ሰሜን ሸዋ ዞን<br />

የምትገኝኘው የያያ ወረዳ አስተዳደር ሠራተኞች<br />

የጥቅምት ወር ደሞዝ ለመዝረፍ ሦስት ሰው ገሎ<br />

ሁለት ሰው ያቆሰለው የወረዳው ፖሊስ በቁጥጥር<br />

ሥር መዋሉን የዜና ምንጮቻችን በተለይ ለፍኖተ<br />

ነፃነት ጋዜጣ ገለጹ፡፡ እንደ ዜና ምንጮቻችን<br />

ገለጻ ከሆነ “ጥቅምት 20 ቀን 2004 ዓ.ም አንድ<br />

ሚሊዮን ብር ይሆናል የሚባለውን የወረዳውን<br />

የመንግስት ሠራተኖች ደሞዝ ለማምጣት ከወረዳው<br />

ፍቼ ከተማ ንግድ ባንክ ይመጣሉ፡፡ ግንዘቡን<br />

ለማምጣት የመጡት ሦስት ሠራተኞች አንድ<br />

ፖሊስና አንድ ሹፌር በጠቅላላ አምስት ሰዎች<br />

ነበሩ፡፡ ከነዚህ ውስጥ አንዷ ሠራተኛ ነፍሰጡር<br />

ነበረች፡፡ ለጊዜው በባንክ ያለው 12ሺ ብር ብቻ ነው<br />

ባንክ ውስጥ ያለው ተብለው ያንን እንደተሰጣቸው”<br />

ምንጮቻችን ገልፀዋል፡፡<br />

በመቀጠልም የዜና ምንጮቻችን እንደሚሉት<br />

“የተሰጣቸውን ብር 12ሺ ይዘው ወደ ወረዳቸው<br />

ሊንቀሳቀሱ ሲሉ አንድ ሌላ የወረዳው ፖሊስ<br />

ይዛችሁኝ ሂዱ ብሎ ትብብር ይጠይቃቸዋል፡፡<br />

እነሱም እሺ ብለው አሳፈሩት ጉዞ ጀምረው ገጠር<br />

ሲደርሱ ያ በልመና የተሳፈረው ፖሊስ “ሽንት<br />

ሰለያዘኝ አንዴ ሽንቴን ልሽና” ብሎ ጠየቃቸው፡<br />

፡ አሁንም እሺ ብለው መኪና አቆሙለት፡<br />

፡ ከወረደ በኃላ መሣሪያውን አውቶማቲክ ላይ<br />

አድርጐ በቅድሚያ ፖሊሱን ከመታው በኋላ ከዚያ<br />

በተሳፈሩት ላይ በጠቅላላ ጥይት አርከፈከፈባቸው፡<br />

፡ ሁለት ወዲያውኑ ሲሞቱ ሌሎቹ ቆሰሉ፡፡ ገንዘቡን<br />

አንስቶ ለማምለጥ ሞከረ፡፡ ጥይት ጨርሶ ስለነበር<br />

የአካባቢው አርሶ አደሮች ከበው በዱላ ቀጥቅጠው<br />

ከያዙት በኋላ ወዲያውኑ ለፖሊስ አስረክበውታል፡፡<br />

የቆሰሉት ሦስቱ አዲስ አበባ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል<br />

እንደደረሱ ፖሊሱ በጠና ተጐድቶ ስለነበር<br />

ወዲያውኑ ሲሞት፤ አንዱ ተሽሎት ከሆስፒታል<br />

ሲወጣ ነፍሰጡሯ እስከ አሁን ሆስፒታል በከፍተኛ<br />

ጉዳት ላይ ትገናለች፡፡” ብለዋል፡፡ ስለጉዳዩ መረጃ<br />

እንዲሰጡን የፍቼ ከተማ ዞን ፖሊስ ጠይቀን<br />

ስማቸውን ለመጥቀስ ያልፈለጉ ሰው “የተሟላ መረጃ<br />

ሊነግሩአችሁ የሚችሉት ህዝብ ግንኙነቶች ናቸው፡<br />

፡ እነሱ በአሁኑ ጊዜ የሉም፡፡ ለጊዜው ልሰጣችሁ<br />

ይምችለው መረጃው ተጠናቅሮ ለኦሮሚያ ፖሊስ<br />

ተላልፏል” በማለት መልስ ሰጥተውናል፡፡ በተያያዘ<br />

ዜና በዚህ ዕለት ማለትም ጥቅምት 20 ቀን 2004<br />

ዓ.ም በዚሁ በፍቼ ቆላማው አካባቢ ልዩ ቦታው<br />

ግራር አዲስ ጌ ቀበሌ ገ/ማህበር ውስጥ “አንድ<br />

ታጣቂ ህዝቡን ሰብሰባ ውጡ እያለ በየቤቱ እየዞረ<br />

በዱላ ሲደባደብ በጥይት ተገድሏል” ሲሉ የዜና<br />

ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡ እንደ ዜና ምንጮቻችን<br />

ገለጻ “በግድያ ተጠርጣሪው ነው የተባለው ግለሰብ<br />

ከሦስት ቀን በኋላ ለመንግስት እጁን ሰጥቷል”<br />

ብለዋል፡፡ በዚህም ጉዳይ ያነጋገርናቸው የዞኑ ፖሊስ<br />

“ግጭቱ የተፈጠረው በሁለት ታጣቂዎች መካከል<br />

ነው፡፡ በአካባቢው ማህበራዊ ፍ/ቤት ተካሰው ነበር፡<br />

፡ ተይዞ እንዲቀርብ የተወሰነበት ታጣቂ ቤቱን ዘግቶ<br />

እንቢተኛ በመሆኑ ለማስወጣት ሲሞክሩ ከቤት<br />

ውስጥ በተተኮሰ ጥይት አንድ ታጣቂ ሞቷል፡፡ ቤት<br />

ውስጥ የነበረው ታጣቂ ለጊዜው የተሰወረ ቢሆንም<br />

በህዝብ ትብብርና በፖሊስ ጥረት ተጠርጣሪው<br />

በቁጥጥር ሥር ውሎአል፡፡ ጉዳዩ በምርመራ ላይ<br />

ነው” በማለት መልስ ሰጥተውናል፡፡<br />

የደብረብርሃን ከንቲባና ባለሥልጣናት በሙስና ተጠርጥረው መታሰራቸው ተገለፀ<br />

የዞኑ ደን ልማት ሽያጭ መነጋገሪያ ሆኖአል<br />

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሰሜን ሸዋ<br />

ዞን ዋና ከተማ የሆነችው ደብረ ብርሃን ከተማ ከንቲባ<br />

የሆኑት “አቶ ስዩም ተፈራና በመሬት አስተዳደርና<br />

በልዩ ልዩ የሥራ ኃላፊነት ላይ የነበሩት የዞኑ ከፍተኛ<br />

ባለሥልጣናት ከሙስና ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው<br />

በእስር ላይ እንደሚገኙ” የዜና ምንጮቻችን<br />

በተለይ ለፍኖተ ነጻነት ጋዜጣ ገለጹ፡፡ እንደ መረጃ<br />

ምንጮቻችን ገለጻ ከሆነ “የዞኑ ነዋሪዎች በተለያየ<br />

ጊዜ በመልካም አስተዳደር እጦት ለተለያዩ አካላት<br />

አቤቱታ ቢቀርብም ፍትህ ማግኘት አይቻልም ነበር፡፡<br />

በጂማ ከተማ የተቃጠለው ውሃ ልማትና ዐቃቤ ህግ ጽ/ቤት<br />

አነጋጋሪ መሆኑ ተገለፀ<br />

በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ጂማ ዞን ዋና ከተማ<br />

በሆነችው ጂማ ከተማ ውስጥ ልዩ ቦታው “ውሃ<br />

ልማት” በሚባል አካባቢ ኖክ ማደያ ፊት ለፊትና<br />

ከፍ/ቤት ጐን የሚገኙት የውሃ ልማትና የዐቃቢ<br />

ህግ ጽ/ቤቶች ሰሞኑን ሙሉ በሙሉ በእሳት ቃጠሎ<br />

መውደማቸው በከተማው አነጋጋሪ ጉዳይ መሆኑን<br />

የዜና ምንጮቻችን ገለጹ፡፡ እንደ ዜና ምንጮቻችን<br />

ገለጻ በ2003 ዓ.ም ለምዕራብ ኦሮሚያ (ጂማ፣ ምዕራብ<br />

ወለጋ፣ ምስራቅ ወለጋና፣ ኢሊባቦር ዞኖች…) በገጠራማ<br />

ሥፍራዎች ለውሃ ቁፋሮ ከፌዴራል መንግስት<br />

ህጋዊ የሆኑ ይዞታዎችን እየነጠቁ ለሚፈልጉት እየሰጡ<br />

ዜጐችን ሲያንከራትቱ፣ ምሪት ቦታዎችን እንዳሻቸው<br />

ለፈለጉት ሲሰጡ ከልካይ አልነበራቸውም፡፡ፍትህ<br />

ሲያዛቡ ጠያቂም አልነበራቸውም፡፡ የአካባቢው<br />

ህዝብ አድማጭ አልነበረውም፡፡ የሚቃወማቸውንና<br />

ልክ አይደለችሁም የሚላቸውን ተለጣፊ ስም እየሰጡ<br />

እያሳሰሩና ከኑሮው እያፈናቀሉ ቆይተዋል፡፡ ዛሬ<br />

ለገዢዎች ባልተመቿቸው ወቅት ጠብቀው ማሰራቸው<br />

የዘገየ እርምጃ ነው” ሲሉ በቁጭትና በሐዘን ገልፀዋል፡፡<br />

በተያያዘ ዜና “ከጣርማ በር መዘዞ ባሽ የሚገኘው<br />

ከተመደበው በጀት ውስጥ 13 ሚሊዮን ብር ጉድለት<br />

በማሳየቱ በባለሥልጣኖች ላይ ክስ ተከፍቶ ጉዳዩን<br />

የፌዴራል ዋናው ኦዲተር መ/ቤት ካሸገው በኋላ ክሱን<br />

የከፈተው የዐቃቢ ህግ ጽ/ቤት ኦዲት ሊደረግ የነበረው<br />

የውሃ ልማት ጽ/ቤት በአንድ ቀንና ሰዓት መቃጠላቸው<br />

እያነጋገር ነው” ሲሉ አብራርተዋል፡፡<br />

የመረጃ ምንጫችን እንደሚሉት “የእሳት<br />

ቃጠሎው ርብርብ አድርጐ ንብረትን፣ ገንዘብንና<br />

ሰነዶችን ማትረፍ ሲቻል ተቃጥሎ እንዲወድም<br />

የተፈለገበት ምክንያት ግልጽ አይደለም፡፡ ካሉ በኋላ<br />

ሰፊ የባህር ዛፍና የጥድ ደን ግልጽነት በጐደለው<br />

ሽያጭ ተሸጦ እየተጨፈጨፈ ነው” ሲሉ አንዳንድ<br />

የአካባቢው ነዋሪዎች ለዝግጅት ክፍላችን ገለጹ፡፡ እንደ<br />

ነዋሪዎቹ ገለጻ “ከጣርማ በር መዘዞ ከመዘዞ መካከል<br />

ባሽ የሚገኘው የሌባ መስቀያ የሚባለው ደን ብቻውን<br />

በእግር ሁለት ሰዓት ያስኬዳል፡፡ ከጣርማ በር እስከ ባሽ<br />

ድረስ በመኪና የአንድ ሰዓት መንገድ ነው፡፡ ይህንን<br />

በ10 ሚሊዮኖች የሚቆጠረውን ደን እንደ ተራ እቃ<br />

በስውር መሸጥ እና ጭፍጨፋ መጀመር አነጋጋሪ ነው”<br />

ሲሉ ያብራራሉ፡፡<br />

ምናልባት ከፍተኛ የመንግስት ባለሥልጣን እጅ<br />

ሳይኖርበት አይቀርም” በማለት ጥርጣሬአቸውን<br />

ገልፀዋል፡፡<br />

በጉዳዩ ላይ አስተያየት እንዲሰጡን የጂማ ከተማ<br />

ፖሊስ ደውለን ነበር፡፡ ስማቸውን ለመጥቀስ ያልፈለጉ<br />

አንድ ግለሰብ ጥያቄያችንን ካዳመጡ በኋላ “ጉዳዩ<br />

በምርመራ ላይ ያለ በመሆኑ አስተያየት ልንሰጣችሁ<br />

አንችልም” በማለታቸው ዜናውን ሚዛናዊ ማድረግ<br />

አልቻልንም፡፡<br />

አርቲስት ደበበ እሸቱ ተጨማሪ ቀነ<br />

ቀጠሮ ተጠየቀበት<br />

በ ”ሽብር” ተጠርጥሮ ማዕከላዊ እስር ቤት የሚገኘው አርቲስት ደበበ እሸቱ ጥቅምት<br />

24 ቀን 2004 ዓ.ም አራዳ ምድብ ችሎት ተቀጥሮ እንደነበር ይታወሳል፡፡<br />

አርቲስት ደበበ በቀጠሮው ቀን ከማዕከላዊ እስር ቤት ወደ ችሎት ቀርቧል፡፡<br />

ችሎቱን ለመከታተልም የተጠርጣሪው ቤተሰብም ሆነ ጋዜጠኞች እንዳይገቡ የተከለከለ<br />

ሲሆን ተጨማሪ የ28 ቀን ቀነ ቀጠሮ ተጠይቆበታል ሲሉ ጠበቃው በተለይም ለዝግጅት<br />

ክፍላችን ገልፀዋል፡፡<br />

ተጠርጣሪውም ጥቅምት 24 ቀን 2004 ዓ.ም ችሎት እስከቀረቡበት ጊዜ<br />

ድረስ በማዕከለዊ እስር ቤት ከጠበቃቸው ጋር እንዲገናኙ ባለመፈቀዱ ጠበቃው ችሎት<br />

ፊት ከደንበኛቸው ጋር እንዲመክሩ በጠየቁት መሠረት ተፈቅዶላቸዋል ሲሉ ምንጮቻችን<br />

ጠቁመዋል፡፡ በዚህም ክቡር ፍ/ቤቱ ተጠርጣሪው ከጠበቃቸው ጋር የመገናኘት ሕገ<br />

መራግሥታዊ መብታቸው መሆኑንና ሊከለከሉ እንደማይገባ ለመርማሪው ፖሊስ<br />

በማሳሰባቸው ጠበቃቸውም ተግባራዊ መሆኑን ለማረጋገጥ ዛሬ ወይም ነገ ማዕከላዊ<br />

እስር ቤት ሄደው ደንበኛቸው አርቲስት ደበበ እሸቱን ለማነጋገር መወሰናቸውን በተለይም<br />

ለዝግጅት ክፍላችን ገልፀዋል፡፡<br />

11<br />

በናይጄሪያ 150 ሰዎች<br />

በአጥፍቶ ጠፊዎች<br />

መገደላቸው ተገለፀ<br />

በሰሜን ናይጄሪያ ደማቱሩ ከተማ 150 ሰዎች<br />

በአጥፍቶ ጠፊዎች ቦምብና በጠብመንጃ በተፈጠረው<br />

ተኩስ ጥቃት ያለፈው ቅዳሜ መገደላቸው ተገለፀ፡፡ ለጥቃቱ<br />

“ይሄነስ” የተባለው እስላማዊ ቡድን እጅ አለበት ብለዋል”<br />

ሲሉ የሀገሪቱን ባለሥልጣናትን ጠቅሶ ቢቢሲ ዘግቧል፡፡<br />

ይህንንም አስመልክቶ የፕሬዘዳንት ጉድላክ<br />

ጆናታን ቃል አቀባይ ሩበን አባቲ ጥቃቱ የተፈፀመው<br />

ከ5 በማያንሱ አጥፋቶ ጠፊዎች እንደሆነና ጉዳዩንም<br />

የሚመለከተው አካል እያጣራ እንዳለ አስታውቀዋል፡<br />

፡ ቃል አቀባዩ አያይዘውም አሁን በአካባቢው ምንም<br />

የፀጥታ ችግር እንደሌለና ጥቃቱን አስተባብረዋል ተብለው<br />

የተጠረጠሩትም በእስር ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል<br />

ሲሉ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙኋን ዘግበዋል፡፡<br />

በኬንያ ቱሪስት መዳረሻ<br />

ኬንያዊ ሾፌር ሲገደል<br />

ስዊዘርላንዳዊ ጐብኚ መቁሰሏ ተገለፀ<br />

በኬንያ ምስራቃዊ ክፍል “ጌም ፓርክ” በተባለው የቱሪስት<br />

መዳረሻ ስዊዘርላንዳዊ ጐብኚዎችን ይዞ የነበረው ኬንያዊ<br />

ሾፌር ባልታወቁ ታጣቂዎች ሲገደል አንድ ስዊዘርላንዳዊት<br />

ጐብኝ መቁሰሏን የፈረንሳይዩ የዜና ወኪል ኤ ኤፍ ፒ<br />

ዘግቧል፡፡<br />

ባለፈው አርብ በተፈፀመ ጥቃት በከፍተኛ ደረጃ የቆሰለችው<br />

ስዊዘርላንዳዊት ቱሪስት ወደ አቅራቢያ ሆስፒታል ሄዳ<br />

የሕክምና እርዳታ እየተደረገላት እንደሆነና አብሯት<br />

የነበረው ስዊዘርላንዳዊ የመቁሰል አደጋ እንዳልገጠመው<br />

የኬንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ስቴፈን ቮን<br />

ቢሎው አስታውቀዋል፡፡<br />

ኬንያ በቱሪዝም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የምታገኝ<br />

ሀገር ስትሆን ከዚህ በፊት በመስከረም ወር እንግሊዛዊ<br />

ጐብኚ ሲገደል ባለቤቱ ታግታ አንደነበር ይታወሳል፡<br />

፡ በተመሳሳይም በጥቅምት ወር አንድ ፈረንሳያዊት እና<br />

ሁለት ስፔይናዊ ዜጐች ጥቃት እንደደረሰባቸው ተዘግቧል፡<br />

፡ ይህንንም አስመልክቶ ኬንያ ከቱሪስት የምታገኛቸው<br />

ገቢዎች እንዳይቀንስ ስጋት የፈጠረ ሲሆን የሀገሪቱ<br />

መንግሥት በበኩሉ ድርጊቱን የሚፈፅሙ ያልታወቁ<br />

ታጣቂዎችን በቅርቡ በቁጥጥር ሥር እንደሚያውል<br />

ገልጿል፡፡<br />

ዓለም አቀፉ የገንዘብ<br />

ድርጅት ለኮትዲቯር<br />

616 ሚሊዮን ዶላር ብድር አፀደቀ<br />

ኮትዲቯር ካለፈው ዓመት ምርጫ ውጤት ጋር<br />

በተያያዘ በተፈጠረ ችግር ከፍተኛ የምጣኔ ሃብት<br />

ውድቀት ተከስቶ እንደነበር ይታወቃል፡፡ ይህ ምጣኔ<br />

ሃብት እንዲያንሰራራ ፕሬዘዳንት ኦታራ ዓለም አቀፍ<br />

አበዳሪ ተቋማትን የተማፀኑ ሲሆን በዚህም መሠረት<br />

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት 616 ሚሊዮን ዶላር ብድር<br />

ያለፈው አርብ ዕለት ማፅደቁ ተጠቁሟል፡፡<br />

በተያያዘ ዜና ባለፈው የኮትዲቯር ምርጫ ተሸንፈው<br />

የነበሩት ሎረንት ባግቦ “ስልጣን አልለቅም” በሚል<br />

በተፈጠረው አለመግባባት 3ሺህ ሰዎች መገደላቸውን<br />

አስመልክቶ በወቅቱ ጥቂት የሀገሪቱ አመራሮች ላይ<br />

የኦታራ መንግስት ክስ መስርቷል፡፡<br />

ከተከሳሾችም መካከል የቀድሞ ፕሬዘዳንት ሎረንት<br />

ባግቦ፣ 24 ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ባለሥልጣናት<br />

እና 57 የሀገሪቱ ወታደራዊ አመራሮች ይገኙበታል ሲል<br />

የፈረንሣዩ የዜና ወኪል ዘግቧል፡፡<br />

www.andinet.org.et


12<br />

ከዳምጠው አለማየሁ<br />

www.andinet.org.et<br />

“ወይ ቶሎ ግደለኝ ወይ እድሌን ባርከው”<br />

“ሊቀደድ ነው ሆዴ ሲርበኝ የማከው”<br />

ድምፃዊ ባሕሩ ቃኘው<br />

“ድህነት ባጭሩ ሲተረጎም የሚበሉትን<br />

ማጣት ወይም መታረዝ ወይም መጠለያ<br />

ማጣት ብቻ ሊመስል ይችላል፡፡ ድህነት<br />

ከሁሉም ይበልጥ ተስፋ ማጣት ነው፣ ክብር<br />

ማጣት ነው፣ በሰዎች መካከል እየተመላለሱ<br />

አለመታየትና መረሳት ነው፡፡ ድህነት<br />

በእያንዳንዱ ቀን ነገን እየፈሩ መኖር ነው፡፡<br />

የኢትዮጵያ ሕዝብ በኢህአዴግ ልማታዊ<br />

መንግስትነት ከላይ በተገለፀው ሁኔታ<br />

ውስጥ የማይኖር ከሆነ ፍርዱ የራሱ ነው፡<br />

፡ ስለሆነም በእኛ ግንዛቤ ዛሬ በኢትዮጵያ<br />

ኢትዮጵያውያንን የሚጠቅም ሰባዊ ልማት<br />

የለም፡፡ ኢኮኖሚው አስርና አስራ አንድ<br />

በመቶ አደገ አላደገ ለሕዝቡ ግን “ያው በገሌ”<br />

እንደተባለው መሆኑን ልብ ይላል፡፡ ይህን<br />

ህዝብ ይፍረድ!!” ከብርሀን ፓርቲ የምርጫ<br />

ቅስቀሳ ሰነድ የተወሰደ፡፡<br />

ሰሞኑን “ድርቅ እንጂ ርሀብ<br />

የለም” በማለት ጠቅላይ ሚኒሰትሩና<br />

ሹማምንቶቻቸው እየተቀባበሉና እየደጋገሙ<br />

ሲናገሩ የምንሰማው እውን በዚህ ሀገር ያለ<br />

ሀቅ ነው?<br />

እንደ እውነቱ ከሆነ ኮሚኒስቶች<br />

ብዙ ጊዜ መፈክሮቻቸውም ሆነ<br />

ዕቅዶቻቸው፤ ህልሞቻቸውም ሆነ የድርጊት<br />

ፕሮግራሞቻቸው ግልፅነት የጎደላቸው<br />

ስለሆኑ ተደናግረው ማደናገር ይወዳሉ፡፡<br />

ረሀብ ትርጉሙ ካልጠፋን በስተቀር<br />

የሚላስ የሚቀመስ ማጣት ብቻ ሳይሆን<br />

በየለቱ በሚቀመሰው ምግብ ውስጥ አማካኝ<br />

የካሎሪ መጠን ማጣት ጭምር መሆኑ<br />

መዘንጋት የለበትም፡፡<br />

ሕወሓት በሽፍትነት ዘመኑ የተከሰተው<br />

ዐይነት ርሀብና የሙት እናቱን ጡት<br />

እየጠባ እነደታየው ህፃን ሰቆቃ፣ “ዋይ ዋይ<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

ሲሉ” የሚደመጥ የልጆች እሮሮ ዛሬም ከ<br />

አርባ አመታት በኋላም የምንጠብቅ ከሆነ<br />

የተዋቀርንበት ስርዓት ሰብዓዊ ስርአት መሆኑ<br />

ይቀርና በደመ-ነፍስ የተሰባሰቡ የዓራዊት<br />

ዱለታ ያስመስለዋል፡፡<br />

የሀገራችን ድርቅ እያሰለሰና አብዛኛውን<br />

ጊዜ በየአስር አመቱ የሚመላለስ ክስተት መሆኑ<br />

ባይካድም ረሀብና መራብ ግን የአብዛኛው<br />

ህዝብ የእለት በእለት ኑሮና ቋሚ ህይወት<br />

ነው፡፡ በአስከፊ ድህነት ውስጥ ከሚኖረው<br />

የአብዛኛውን ገበሬ ህይወት እንለፈውና<br />

በመካከለኛ ደረጃ ውስጥ የሚኖረውን ገበሬ<br />

ህይወት እንመርምር፡፡ እንደሚታወቀው<br />

የሀገራችን ገበሬ ተበልቶ ባለቀና በተበጣጠሰ<br />

አነስተኛ ማሳ የሚያመርታት ምርት እጅግ<br />

አነስተኛ ከመሆኑም በላይ በአማካኝ ከአምስት<br />

እስከ ሰባት የሚደርሱ ቤተሰቦቹን ከመመገብ<br />

ጀምሮ ካመረታት ምርት ውስጥ ግማሽ ያህሉን<br />

ይሸጥና…………<br />

1. ግብር ይከፍልበታል<br />

2. የማዳበርያ እዳ ይከፍልበታል<br />

3. ለራሱ ለልጆቹና ለቤተሰቡ<br />

የዓመት ልብስና መጫሚያ እነደአቅሙ<br />

ይገዛል<br />

4. ለልማት መዋጮ እና ለገዢው<br />

ፓርቲ ማጠናከሪያ የግድ ይከፍላል<br />

5. የሚታደሱና ያለቁ የእርሻ<br />

መሳሪያዎችን ይገዛል ለምግብ ማጣፈጫ<br />

ጨው፣በርበሬ፣ዘይት፣ሽሮ፣ስኳር፣ቡና……<br />

ወዘተ ይገዛበታል<br />

6. ማገዶና ሳሙና ወዘተ<br />

የሚያሟላው ከዚሁ ገንዘብ ነው፡፡<br />

በዚህ ሁኔታ በግድ መሟላት<br />

የሚገባቸውን ሸቀጦች ለመግዛት ሲል ወደ<br />

ጎተራው ከገባችው ሰብል የተረፈችው<br />

ምን ያህል ወራት መመገብ እንደምትችል<br />

መገመት አያዳግትም፡፡ በዚህም ምክንያት<br />

የተረፈችው ሰብል ያለጥርጥር ከስድስት<br />

ወራት በላይ ሊመገቧት አይቻላቸውም፡፡<br />

በዚህ አይነት የድህነት አዙሪት ቀለበት ውስጥ<br />

የሚኖረው አብዛኛው የሀገራችን ገበሬ በቂ<br />

ዝናብ ባለባቸው ወቅቶችም እንኳን ከስድስት<br />

ወራት በላይ ሊመግበው የሚያስችለው<br />

ምርት ከቶም ሊያመርት አይችልም፡<br />

፡ ቀሪዎቹ ስድስት ወራት የረሀብ ወራት<br />

ናቸው፡፡ ምክንያቱም እጅግ ኋላ ቀር በሆነ<br />

የአስተራረስ ዘዴ እና ምርታማነቱ ተሟጦ<br />

ባለቀ የተበጣጠሰ አነስተኛ ማሳ ግማሽ ዓመት<br />

የሚመግበው ሰብል ማምረት የሚችል ገበሬ<br />

እጅግ አነስተኛ ሊሆን ይችላል፡፡ በመሆኑም<br />

ረሃብ በአገራችን በማናቸውም ጊዜ በየዓመቱ<br />

ህዝብ እንዲሰደድና እንዲፈናቀል እንዲሁም<br />

ከተሞችን በስራ አጦች ከማጨናነቅ ለማዳን<br />

አልተቻለም፡፡<br />

እንግዲህ ይህ ተጨባጭ የሀገራችን<br />

ሀቅ ረሀብ፣ስደት፣መፈናቀልና ሞት እጣ<br />

ፈንታችን ሆኖ አብሮን የኖረ ነው፡፡ በቅርቡ<br />

በመካከለኛው ምስራቅ ከሊብያ ወደ<br />

አውሮፓ እንዲሁም ከመቋዲሾ ወደ የመን፤<br />

በሶማሌ ላንድ የታገቱና ሞትን ንቀው በስደት<br />

የሚንገላቱ የኢትዮጵያውያን ህይወት ዘግናኝና<br />

አሳዛኝ ነው፡፡ በይበልጥ የሚያሳዝነው ከነዚህ<br />

ውስጥ ከፊሎቹ በጀልባ ሲያቋርጡ የባህር<br />

አውሬ ቀለብ የሆኑ ወገኖቻችን ኢትዮጵያ<br />

ምን ያህል ከሞትም በታች እንደሆነች<br />

የሚያመለክት ነው፡፡<br />

በሌላ በኩል ደግሞ አንድ አለምአቀፍ<br />

የጥናት ማእከል በቅርቡ ይፋ ባደረገው መረጃ<br />

መሰረት ከኢትዮጵያ ህጻናት ግማሽ ያህሉ<br />

በምግብ እጥረት ምክንያት አካላዊ መቀጨጭ<br />

የደረሰባቸው ናቸው፡፡ ይህ ሁኔታ የአእምሮ<br />

መቀጨጭንም ስለሚያስከትል ለማህበራዊ<br />

ልማት ዋና ጉዳይ የሆነው ትምህርትን<br />

የመቀበል አቅማቸውን ከማዳከሙም በላይ<br />

ትውልድ ገዳይ ከሆነው ስርዓተ-ትምህርት<br />

ጋር ተደምረው የኢትዮጵያን ሰብዓዊ ልማት<br />

መካን ያደርገዋል፡፡<br />

በ 1996 ዓ.ም መ.ኢ.አ.ድ. ስለህዝብ<br />

አደረጃጀት ጉዳይ በጎጃም፣ በጎንደርና<br />

በወሎ ታላቅ ፖለቲካዊ ጉዞ መድረጉን<br />

አስታውሳለሁ፡፡ እንዳጋጣሚ ሆኖ ከአዲስ<br />

አበባ የተጓዝን በመሆናችን የገጠሩን<br />

ህዝባችንን ብስቁልና ስንመለከት ሁላችንም<br />

መረበሻችን ትዝ ይለኛል፡፡ በዚያን ግዜ<br />

በደብረታቦር ከተማ ለሚደረገው ታላቅ<br />

ህዝባዊ ስብሰባ ቅድመ ዝግጅት ሲባል<br />

ከተመረጡ አረጋውያንና የአካባቢው<br />

ፖለቲከኞች ጋር የዋዜማው ዕለት አመሻሽ<br />

ላይ በተደረገ ውይይት የመክፈቻ ንግግር<br />

እንዲያደርጉ የተጋበዙት ኢንጂነር ኃይሉ<br />

ሻውል ነበሩ፡፡ ኢንጂነሩም ንግግራቸውን<br />

ከመጀመራቸው ሳግ እየተናነቃቸውና<br />

ንግግራቸውንም እያደናቃቀፈባቸው ያነቡት<br />

እንባ በብርበራ ሰበብ ፊልሙ ካልተዘረፈ<br />

በስተቀር በቪዲዮ ካሜራ የተቀዳ መሆኑ<br />

አይረሳም፡፡ በማግስቱ የዞኑ ህዝብና ከፊል<br />

ፈረሰኛ በቴዎድሮስ አደባባይ ወደሚካሄደው<br />

ህዝባዊ ስብሰባ ከመታደማችን በፊት የዚህ<br />

ጽሁፍ አቅራቢ በማለዳ በመነሳትና በመኝታ<br />

ቤታቸው በመገኘት ትላንትና ማታ ለምን<br />

እንዳለቀሱ ጠየኳቸው፡፡ እርሳቸውም<br />

እስከዛሬ የማይረሳኝንና ጥልቅ ስሜታቸውን<br />

የተገነዘብኩበትን ሃሳባቸውን ገለጹልኝ<br />

እንዲህ በማለት “የወልድያ ወረታ መንገድ<br />

የቻይና ኩባንያ በሚሰራበት ዘመን እኔ<br />

የአውራ ጎዳና ስራአስኪያጅ ነበርኩና መንገዱ<br />

በተሰጠው ንድፍና ደረጃ እየተሰራ መሆኑን<br />

ለመቆጣጠር በተደጋጋሚ እመላለስበት<br />

ነበር፡፡ በዚያን ግዜም በደብረታቦር የነበረ<br />

የሰው ዘር ቁመናው ያማረ፣ ሸበላና መለሎ<br />

ትውልድ አልቆ ትቢያ የመሰለ የደቀቀና<br />

ድውይ ህዝብ ተሰብስቦ ስመለከት ራሴን<br />

መቆጣጠር ተሳነኝ፡፡ ይህንን የተራቆተ መሬት<br />

መልሰን እንዲያገግም ማድረግ እንችላለን፡<br />

፡ ነገር ግን ያለቀውን ዝርያችንንና ወገናችንን<br />

ከየት እናገኘዋለን?” ካሉ በኋላ በመቀጠልም<br />

’’የሰሜን ሸዋን ህዝብ ቢቀጠቅጡት ምኒልክን<br />

የተበቀሉ መስሎአቸው ነው፡፡ የደብረታቦር<br />

ህዝብ ግን ምን አደረጋቸው’’?ማለታቸው<br />

የሚረሳ አይደለም፡፡<br />

ለነገሩማ በአፄ ቴዎድሮስ<br />

“አንድ ሀገር አንድ ንጉሰ ነገስት” የተባለው<br />

የዘመናዊው የኢትዮጵያ አንድነት ታሪክ<br />

ጠንካራ አምድ የተተከለው፤ በፀረ-<br />

ኢምፒሪያሊዝምና በፀረ-ቅኝ አገዛዝ የታነፁና<br />

የአድዋን ጦርነት አይቀሬነት ቀድሞ የተገነዘቡ<br />

ጠንካራዋ የአለማችን የመጀመሪያዋ ሴት<br />

እቴጌ ጣይቱ የተገኙበትና እንዲሁም<br />

በኢትዮጵያ እንደ ቀዳሚ ኢንዱስትሪ አባዮት<br />

የተቆጠረውና ያልዘለቀው ጋፋት የጦር<br />

መሳሪያ ፋብሪካ ማዕከላት ደብረታቦር እና<br />

ጎንደር መሆኑ መቼ ሚረሳ ሆነና ብዬ በልቤ<br />

አሰብኩ፡፡ ደብረታቦርም በፀረ-ኢትዮጵያ<br />

ኃይሎች ኢላማ ውስጥ መግባቱ እንደምን<br />

ያጠራጥራል?<br />

አዲሱ የከተማ ውስጥ ርሃብ!<br />

ድርቅ፣ አስከፊ ድህነትና ኋላ ቀር<br />

ያስተራረስ ዘዴ ያስከትል የነበረው ርሃብና<br />

ሞት በገጠሪቱ ኢትዮጵያ እንደነበረ<br />

አይዘነጋም፡፡ ይሁንና ዛሬዛሬ ርሃብ ባጠቃላይ<br />

2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />

ዕውን በኢትዮጵያ ውስጥ “ድርቅ እንጂ<br />

በዚህ ረገድ እጅግ የሚያሳዝኑ ህፃናት አሉ፡፡ አንዳንዶቹ<br />

ህፃናት ትምህርት ቤት መሄድ እድል ቢያጋጥማቸውም<br />

ምሳ ለመቋጠር ያልታደሉ ወላጆች ስላሉዋቸው ባንዳንድ<br />

የመንግስት ትምህርት ቤቶች ጠኔ የሚጥላቸው ልጆች<br />

መታየት አዲስ ክስተት ነው፡፡ ይህ አስጨናቂ ሀላፊነት<br />

የወደቀው ደግሞ በመምህራንና በየትምህርት ቤቱ<br />

ማህበረሰብ ትከሻ ላይ ነው፡፡ በመሆኑም በአንዳንድ<br />

ትምህርት ቤቶች ጊዜያዊ የመመገቢያ ስፍራዎች<br />

እየተደራጁ ነው፡፡ ቀድሞውኑም ቢሆን ጥቂት የማይባሉ<br />

ህፃናት ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ፣ አልባሳትና<br />

ጥሬ የምግብ ሰብሎች የሚሰጡዋቸው ግብረ ሰናይ<br />

ድርጅቶች አሉ፡፡ በመረጃ አቀራረብ ረገድ መተላለፊያው<br />

ጠባብ ባይሆን ኖሮ በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ እርዳታ<br />

ፈላጊዎች እንደሚኖሩ መገመት አያዳግትም፡፡ በዚህ<br />

አይነት ሰቆቃ በእያንዳንዱ ድሃ ጎጆ ተደፍተው ሚያድሩ<br />

ረሃብተኛ ህፃናት አንጀት የሚበሉ ናቸው፡፡ የዚህ ሀገር<br />

መሪ መሆን እንደመርግ የሚከብድ አበሳ ለመሸከም<br />

ዝግጁ መሆንን እንጂ በመሬት ላይ ካለው ሃቅ ሸሽቶ<br />

’’ድርቅ እንጂ ርሃብ የለም’’ ማለት ይገባል??<br />

ርሃብ የለም ?”<br />

ኢኮኖሚ<br />

በኢትዮጵያ ከተሞችና በተለይ ደግሞ በአዲስ<br />

አበባ ከተማ አዲስ ማህበራዊ ቀውስና<br />

ክስተት ሆንዋል፡፡ የጦር ቁስለኞች፣የኤድስ<br />

ህሙማን፣ጧሪ የሌላቸው አረጋውያን፣<br />

ወላጅ አልባ ህጻናት፣ ቤት አልባና ጎዳና<br />

ተዳዳሪዎች፣ በልመና የሚተዳደሩ ድሆች፣<br />

ስራአጥ ወጣቶች ከግብርናና ከኢንዱስትሪ<br />

ስራ የተገለሉ በርካታ ዜጎች ………ወዘተ<br />

ከተማይቱን በማጨናነቅ ላይ ያሉ ርሃብተኞች<br />

ናቸው፡፡ እነዚህ ሁሉ የአዲሱ የከተማ ውስጥ<br />

ርሃብ ሰለባዎች ናቸው፡፡<br />

በዚህ ረገድ እጅግ የሚያሳዝኑ ህፃናት<br />

አሉ፡፡ አንዳንዶቹ ህፃናት ትምህርት ቤት<br />

መሄድ እድል ቢያጋጥማቸውም ምሳ<br />

ለመቋጠር ያልታደሉ ወላጆች ስላሉዋቸው<br />

ባንዳንድ የመንግስት ትምህርት ቤቶች ጠኔ<br />

የሚጥላቸው ልጆች መታየት አዲስ ክስተት<br />

ነው፡፡ ይህ አስጨናቂ ሀላፊነት የወደቀው<br />

ደግሞ በመምህራንና በየትምህርት ቤቱ<br />

ማህበረሰብ ትከሻ ላይ ነው፡፡ በመሆኑም<br />

በአንዳንድ ትምህርት ቤቶች ጊዜያዊ<br />

የመመገቢያ ስፍራዎች እየተደራጁ ነው፡፡<br />

ቀድሞውኑም ቢሆን ጥቂት የማይባሉ ህፃናት<br />

ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ፣ አልባሳትና<br />

ጥሬ የምግብ ሰብሎች የሚሰጡዋቸው ግብረ<br />

ሰናይ ድርጅቶች አሉ፡፡ በመረጃ አቀራረብ<br />

ረገድ መተላለፊያው ጠባብ ባይሆን ኖሮ<br />

በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ እርዳታ ፈላጊዎች<br />

እንደሚኖሩ መገመት አያዳግትም፡፡ በዚህ<br />

አይነት ሰቆቃ በእያንዳንዱ ድሃ ጎጆ ተደፍተው<br />

ሚያድሩ ረሃብተኛ ህፃናት አንጀት የሚበሉ<br />

ናቸው፡፡ የዚህ ሀገር መሪ መሆን እንደመርግ<br />

የሚከብድ አበሳ ለመሸከም ዝግጁ መሆንን<br />

እንጂ በመሬት ላይ ካለው ሃቅ ሸሽቶ ’’ድርቅ<br />

እንጂ ርሃብ የለም’’ ማለት ይገባል??<br />

ውድ አንባቢያን!<br />

ኢትዮጵያ ያላት ዋና ሀብት መሬት፣ውሃና<br />

ታታሪ ህዝቧ ነው፡፡ ይህንን አቀናጅቶ<br />

በመስራት ሀገራችን ከወደቀችበት አረንቋ<br />

መንጭቆ በማውጣት ድህነትና ርሃብን<br />

መሰናበት ይቻላል፡፡ ተደጋግሞ እንደሚነገረው<br />

በውሃ ሊለማ የሚችል ድንግል መሬት አለን፡<br />

፡ በተለይ በሰባቱ ታላለቅ ተፋሰሶቻችን<br />

ውስጥ ያለው በሚሊዮን ሄክታር የሚቆጠር<br />

ለም መሬት ለማረስና ለማልማት የሚያስችል<br />

በቂ የገንዘብ አቅም እንዳለ ይታወቃል፡<br />

፡ የኢህአዴግ መንግስት በያአመቱ ከአራት<br />

ቢሊዮን ዶላር በላይ በይፋ እርዳታ የሚያገኝ<br />

ከመሆኑም በላይ ይፋ ባልሆነ መንገድ<br />

የዚህን ሶስት እጥፍ እንደሚያገኝ የኢኮኖሚ<br />

ሊቃውንት ይናገራሉ፡፡ ይህ ሁሉ ለልማት<br />

የተትረፍረፈ ሀብት እያለ የሀገሩን ህዝብ<br />

ጩኸት እና ዋይታ ከማዳመጥ ይልቅ ላለም<br />

አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ጆሮ መስጠት<br />

ቀዳሚ አጀንዳ ሆኖዋል ይልቁንም ገንዘብ<br />

ካለን ሸምተን እንበላለን ማለት ይቀናቸዋል፡<br />

፡ በዛሬው አለም የምግብ እህል ዋጋ<br />

መናር አያስጨንቀንም፡፡ እንደ እውነቱ<br />

ከሆነ ኢትዮጵያ ያላትን ለም መሬትና ውሃ<br />

ተጠቅማ ብታርስ የአለምን የምግብ ዋጋ<br />

መናር በማረጋጋት እረገድ የራስዋን ድርሻ<br />

ልታዋጣ ከመቻልዋም በላይ በመቶ ሺህዎች<br />

የሚቆጠሩ የእርሻ ሰራተኞችን በማሰማራት<br />

ይልቁንም ርሃብና ድህነትን ከማስወገድ<br />

ጀምሮ ወደ ብልፅግና በመረማመድ የሀገሪቱን<br />

ገፅታ መለወጥ ይቻላል፡፡ የህንድ ገበሬዎችን<br />

ለማስፈር የመሬት ቅርምትን ከማስፋፋት<br />

ይልቅ የሀገራችንን ህዝብ ችግር እንፍታ፡<br />

፡ በባዶ ፕሮፖጋንዳ የሀገር ገፅታ ግንባታ<br />

አይኖርም!፡፡


2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

“ ነጋ-እንዴና የግብሩ ...<br />

መስጫ ተቋማት የሚጠየቀውን ጉቦ የሚያስጥለው<br />

ባለመኖሩ ስለ ግብር አከፋፈል ዝቅተኛ እውቀት<br />

ብቻ ሳይሆን ጭርሱንም ላለመክፈል የሚያደርገውን<br />

ድብብቆሽ የሚያባብስበት እንጂ የሚመልስለት<br />

እንደማይሆን እሙን ነው፡፡<br />

ግብር ከፋዩ ዛሬ ግብሩን ከፍሎ ነገ ወደ<br />

አንድ ሕክምና መስጫ ማዕከል ጐራ ቢል ከጎንት<br />

(ግላቭ) ጨምሮ የተለያዩ የህክምና መድኃኒቶችን<br />

በጓሮ በር እያወጡ ለሚቸረችሩ ጥቅመኞች ቀድመው<br />

የተጋለጡ በመሆናቸው ሚስቱ ወይም ልጁ<br />

በግላቭ ወይም ጓንት እጦት ህይወታቸው ሲያልፍ<br />

እየተመለከተና እያዳመጠ ግብር ጠቀሜታው ላንተነው<br />

የሚለውን ፕሮፓጋንዳ እንዴት ሊያዳምጥ ይችላል?<br />

እንዲያዳምጥስ ይጠበቃልን ?፡፡<br />

ታታሪው ግብረኛ አመታዊውን ዜግናታዊ<br />

ግዴታ ተወቶና እፎይ ግብሬን ከፈልኩ ብሎ ለሌላ<br />

ጉዳይ ወደ ሌላ ቢሮ ሲገባ ለመሀንዲስ ትራንሰፖርት<br />

አቅርብ፣ ለልዩ ልዩ ጉዳዮች ማስፈጸሚያ ለምሣሌ እንደ<br />

የሰላም ትግል...<br />

ሰላማዊ የምርጫ ሰራዊት አንቀሳቀሰ። ይኽ ሰላማዊ<br />

ሰልፈኛ “ድምጽ ይከበር” በማለት ፓርላማውን<br />

ያዘ። ወታደሩ እና የፖሊስ ኃይል በምርጫ ፖለቲካ<br />

እንዳይገባ ተቃዋሚው ቀደም ብሎ ህጋዊ ስራ<br />

በመሰራቱ ጣልቃ ከመግባት ተቆጠቡ። የመንግስት<br />

ስልጣን ወደ አሸናፊ ፓርቲዎች ግንባር ተላለፈ።<br />

ይኽ ግንባር በውስጡ 16 ያህል ተቃዋሚ ፓርቲዎች<br />

ነበሩበት። እስቲ የዝንባቡዌን ሁኔታ እንመልከት።<br />

በዝንባቡዌ ተቃዋሚው ፓርቲ ደጋፊዎቹ<br />

በብዛት ወጥተው እንዲመርጡ በማድረግ እንዲሁም<br />

ምርጫው ነፃ እና ፍትሃዊ እንዲሆን አለም አቀፍ<br />

ህብረተሰብ በሙጋቤ አምባገነን መንግስት ላይ ጫና<br />

እንዲያሳርፍ በማድረግ ረገድ ጥሩ ዝግጅት አድርጎ<br />

ነበር። ምርጫውን ከሙጋቤ መንግስት ስርቆት<br />

የሚያድን “ፕላን ለ” (Plan B) ግን ቸል ተብሉ ነበር።<br />

የሙጋቤ መንግስት በምርጫ ሽንፈት ቢደርስበት<br />

ስልጣን እንደማይለቅ የሚጠቁሙ ምልክቶች ቀደም<br />

ብለው ይታዩ ነበር። በምረጡኝ ዘመቻ ወቅት<br />

በተቃዋሚ ፓርቲ ደጋፊዎች እና ፓርቲ ሰራተኞች<br />

ላይ ወከባዎች፣ ድብደባዎች፣ ግድያ፣ ማሳደድ<br />

እና እስር ቤት የማጎር ተግባራት ይፈጸሙ ነበር።<br />

በምርጫው ቀን ሳይቀር አለም አቀፍ ታዛቢዮች<br />

እየተመለከቱ ድምጽ ለመስጠት የተሰለፉ ዜጎች<br />

ይደበደቡ ነበር። ፖሊስ፣ ደህንነት፣ የጦር ኃይል፣<br />

ካድሬ፣ ሚሊሺያ፣ እና በገንዘብ የተገዙ ቦዘኔዎች<br />

ሳይቀሩ በተቃዋሚ ፓርቲ ደጋፊዎች ላይ አረመኔያዊ<br />

ተግባሮች ፈጸሙ። ተቃዋሚ ፓርቲ የመረጡ ብዙ<br />

ዜጎች ለህይወታቸው በመፍራት መኖሪያቸውን ለቀው<br />

ተሰደዱ። አገር ለቀው ወደ ደቡብ አፍሪካ የጎረፉት<br />

ጥቂት አልነበሩም። ምርጫ ለመታዘብ ከአውሮፓ<br />

ተጋብዘው ከመጡት ውስጥ ምርጫው ሳያልቅ አገር<br />

ለቀው እንዲወጡ የተደረጉ ነበሩ። ባጭሩ ምርጫው<br />

ተሰረቀ። የዝምባቡዌው ሙጋቤ እንደሰርቢያው<br />

ሞሊሶቪች አይኑን በጨው አጥቦ በምርጫው አሸናፊ<br />

መሆኑን አወጀ። የሞሊሶቪች አዋጅ ተቀባይ እንዳጣ<br />

አይተናል። የሙጋቤ አዋጅ ግን ተቀባይ አላጣም።<br />

ምክንያቱም ተቃዋሚው ፓርቲ ምርጫውን ከሙጋቤ<br />

ስርቆት ማዳን ባለመቻሉ። ተቃዋሚው ድምጽ<br />

ለማስከበር የሚያስችል ዝርዝር ፕላን እና የሰላም<br />

ትግል አቅም ስላልነበረው “ምርጫው ነፃ አይደለም፣<br />

ድምጽ ይጣራ፣ ሌላ ምርጫ ይደረግ” የሚሉ ፋይዳ<br />

ቢስ ጩኸቶች ከማሰማት፣ የሙጋቤን መንግስት<br />

በጎ ፈቃደኛነት ከመጠየቅ እና የምዕራቡን አለም<br />

ከመማጸን ባሻገር ምንም ማድረግ ሳይችል ቀረ።<br />

የዝንባቡዌው ተቃዋሚ ፓርቲ እንደ ሰርቢያ “ፕላን<br />

ለ” (Plan B) ያስፈልገው ነበር !!<br />

በምርጫ ሽንፈትን መቀበል ማለት ለገዢው ፓርቲ<br />

በአገር ውስጥ እና በአለም አቀፍ ደረጃ ህጋዊነትን<br />

ማጣት ስለሚሆን በስልጣን ላይ ያሉ አምባገነን<br />

መንግስቶች ሽንፈትን ለመቀበል ዝግጁ አይደሉም።<br />

ተቃዋሚ የዲሞክራሲ ኃይሎችም በምርጫ ያገኙትን<br />

አሸናፊነት ማስከበር ካልቻሉ በአገር ውስጥ እና<br />

በአለም አቀፍ ደረጃ የገዢነት እውቅናን እና ህጋዊነትን<br />

ማግኘት አይችሉም ! ህዝብን የመንግስት ስልጣን<br />

ባለቤት ማድረግ ዋዛ አይደለም።<br />

መታወቂያ ለመሳሰለው ይሄን ያህል ክፈል እየተባለ<br />

በሚጠየቅበት እና በሚከፍለው ግብር ልክ እንኳን<br />

ባይሆን እጅግ አናሳ አገልግሎቶች እንዲያጣ እየተደረገ<br />

ከዓመታት በኃላ ታገኛቸዋለህ ሲለሚባለው ትልልቅ<br />

ፕሮጀክቶች እንዲያስብ ለማድረግ መሞከር በእጅጉ<br />

አስቸጋሪ ነው የሚሆነው፡፡<br />

ከሁሉ በላይ ደግሞ ግብር የሚከፍለውም ሆነ<br />

ማይከፍለው፣ ህገውጡና ወንጀለኛው ነጋዴ ከንፁህና<br />

ታታሪው ነጋዴ ጋር ተደበላልቆ ለትንሹም ለትልቁም<br />

ጉዳይ እኩል ከተጉላላና አንዳንዴም ቅድሚያው<br />

ለህገወጡ ለወንጀለኛው ነጋዴ ሲሰጠው ከታየ ግብር<br />

በመክፈል የሚመጣውን ለውጥና ልዩነት መለፈፉ<br />

ነገሩን ከፈረሱ ጋሪውን ማስቀደም ያስመስላል፡፡<br />

ባለፈው ክረምት ውስጥ የከተማችን ከንቲባ<br />

በቴሌቪዥን መስኮት ብቅ ብለው ግንባራቸውን እንደዛ<br />

ከስክሰው ስለግብር ሲያስረዱ ለተመለከተ ግብር<br />

በዜጐች ቀና አመለካከትና ፈቃደኝነት ፍፁም ለአገርና<br />

ሕዝብ እድገት ተገዢ በመሆን የሚከፈል የንፁህ ነፍስ<br />

ከገፅ 5 የዞረ<br />

የሆነው ሆኖ መቀየር/መለወጥ (Peaceful<br />

conversion) እና መቻቻል (Peaceful<br />

accommodation) የተባሉት ለውጥ ማምጫ<br />

መንገዶች ለገዢው ቡድን ከተቃዋሚዎች የቀረበለትን<br />

ጥያቄ የመቀበል እና ያለመቀበል ምርጫ ይሰጣሉ።<br />

ገዢውን ቡድን ማስገደድ አይችሉም። ሰላማዊ<br />

ማስገደድ (Peaceful coercion) የተባለው ለውጥ<br />

ማምጫ መንገድ ግን ገዢው ቡድን የቀረበለትን<br />

የለውጥ ጥያቄ እንዲቀበል ማስገደድ ይችላል።<br />

እንመልከት።<br />

(3ኛ) ሰላማዊ ማስገደድ (Peaceful coercion)<br />

ሰላማዊው ትግል ማስገደድን ተፈጻሚ ማድረግ<br />

ከሚችልበት ደረጃ ከደረሰ በስልጣን ላይ ያለው<br />

አምባገነናዊ መንግስት አቅም እጅግ ዝቅ ብሏል ማለት<br />

ነው። በአንጻሩ የዲሞክራሲ ኃይሎች የፖለቲካ ኃይል<br />

ከፍ ብሏል ማለት ነው። ጉልህ የፖለቲካ ኃይል ሚዛን<br />

ግንኙነት ሽግሽግ ተደርጓል ማለት ነው። የሆነው ሆኖ<br />

የገዢውን ቡድን ህልውና ላይ ስጋት የሚያሳድሩ<br />

አስገዳጅ ጥያቄዎች ከመቅረባቸው በፊት ግን<br />

ተቃዋሚው ጥንቃቄ የተሞላበት ፕላን መቀየስ እና<br />

ሰፊ የአቅም ዝግጅት ማድረግ ይኖርበታል። ተፈጻሚ<br />

ሊሆኑ የማይችሉ አስገዳጅ ጥያቄዎች ማቅረብ በህዝብ<br />

ዘንድ ተዓማኒነት ያሳጣል። የፕላን አለመጠናቀቅ<br />

ወይንም የትግል አቅም ማነስ ካለ አስገዳጅ ጥያቄዎችን<br />

ከማቅረብ መቆጠብ ወይንም አኪያሄድን ማስተካከል<br />

ይመረጣል። በስልጣን ላይ ያለው አምባገነን መንግስት<br />

የቀረበለትን አስገዳጅ የለውጥ ጥያቄ ፈቃደኛ ሳይሆን<br />

ተገዶ ከተቀበለ ማስገደድ ተሳካ ሊባል ይችላል።<br />

የሰርቢያን እና የዝምባቡዌን ሁኔታዎች እንመልከት።<br />

(4ኛ) (Peaceful disintegration)<br />

ከፍ ብለን እንዳየነው ተቃዋሚው በስልጣን<br />

ላይ ያለውን መንግስት ማስገደድ ከቻለ በገዢው<br />

ቡድንና በህዝብ መካከክል ተጨባጭ የሆነ የስልጣን<br />

ሽግሽግ ተደርጓል ማለት ነው። የፖለቲካ ኃይል ሚዛን<br />

ግንኙነት ወደ ተቃዋሚ ማድላቱ በእርግጠኛነት<br />

ከታወቀ የፖለቲካ እምቢተኛነት (Political defiance)<br />

ትብብር መንፈግ (Non-cooperation) እና ጣልቃ<br />

መግባት (Intervention) የተባሉትን የሰላም ትግል<br />

መሳሪያዎች በመጠቀም ስርዓቱን በበርካታ ግንባሮች<br />

ማጥቃት ይቻላል። ይኽ ጥቃት ቀጣይነት ካለው<br />

የፖለቲካ ኃይል ምንጮች እንደሚደርቁ እና መንግስት<br />

ተርቦ እንደሚፈረካከስ መገመት አያዳግትም።<br />

በመጨረሻ በኢትዮጵያ ሰላማዊ ትግል ህዝብን<br />

የመንግስት ስልጣን ባለቤት ማድረግ እንደሚችል<br />

በመተንተን ጥናታችንን እንፈጽማለን። በኢትዮጵያ<br />

ህዝብን የመንግስት ስልጣን ባለቤት ማድረግ<br />

የሚችልባቸው ሁለት አማራጭ ቀዳዳዎች አሉ ማለት<br />

ይቻላል። እነሱም፡-<br />

(1) አንደኛው አማራጭ በሰሜን አፍሪካ እና<br />

በመካከለኛው ምስራቅ የአረቡ ህዝብ የመረጠው<br />

መንገድ ነው። ህዝብ ለመንግስት የሰጠውን የገዢነት<br />

መብት እና ክብር በመንፈግ ህጋዊነቱን ገፍፎ ከስልጣን<br />

ማውረድ ይችላል። ህዝብ በፈለገው ጊዜ የመንግስት<br />

ለውጥ የማድረግ መብት እንዳለው የታወቀ ነው።<br />

የግብጹ ፕሬዘዳንት ሙባረክ የተመረጠበትን የአራት<br />

ከገፅ 10 የዞረ<br />

ስርዓት መገለጫ ሳይሆን ክተት የተዋጀበት ጦርነት<br />

አስመስለው ማቅረባቸው አሁንም ግብርን በተመለከተ<br />

ገዢው ፓርቲ ለራሱ በራሱ ያልገባው ስነልቦናዊ<br />

አመለካከት እንዳለ አስረጂ ነው፡፡ ይህንንም ስል ግብር<br />

መብትም ግዴታም እንደሆነ በሙሉ ልቤ ስለማምንበት<br />

ብቻ ሳይሆን እንደ ሃይማኖታዊ ትዕዛዝ የተቀበልኩት<br />

መሆኔንም ጭምር ለማሳወቅ ነው፡፡<br />

አለመታደል ሆኖ እንጂ ለጉዳይ በምንሄድባቸው<br />

የተለያዩ ህዝባዊ ሆነ መንግሥታዊ ተቋማት፣ ለምርጫ<br />

በቀረብንባቸው የምርጫ ጣቢያዎች፣ ፓርላማ፣<br />

ሆስፒታል ወዘተ ልባችን ሞልተን፣ ደረታችን ነፍተን<br />

እኔእኮ ግብር ከፋይ ነኝ! ያንተን ደሞዝ የምከፍልህ<br />

እኔነኝ ለማለት ቅንጣት ፍርሀትና የዛኛው ወገን አሉታዊ<br />

ምላሽ የምንፈራ ባልሆን ነበር፡፡ ይህን ግን አልሆነም<br />

ለዚህም አልታደልንም ግብር እንዲህ በትንሹ ነገርግን<br />

ትልልቅ ጉዳዮችን ተሸክሞ ባልጠራበት ሁኔታ እየተጓዘ<br />

ገዢው ፓርቲ የኢህአዴግ ደጋፊ ነጋዴዎች ፎረም<br />

የሚል ስያሜ ነጋዴው ላይ በመለጠፍ ነጋዴው እርስ<br />

ወይንም የአምስት አመት የስልጣን ዘመኑን ሳይጨርስ<br />

ከስልጣን እንደተወገደ እናስታውሳለን። ባጭሩ ህዝብ<br />

እምቢ አልገዛም ካለ መንግስት ሊኖር አይችልም።<br />

የኢትዮጵያ ህዝብ ይኽን አማራጭ ከመረጠ የትግሉ<br />

ባለቤት እራሱ ህዝቡ ነው የሚሆነው። የተቃዋሚ<br />

ፓርቲዎች ሚና ከህዝብ ጎን መቆም ነው የሚሆነው።<br />

(2) ሁለተኛው አማራጭ “ለድምጽ ስርቆት<br />

የማይች ምርጫ ማድረግ” ወይንም በአጭሩ<br />

“የማይሰረቅ ምርጫ” ብለን የምንጠራው ነው።<br />

የኢትዮጵያ ህገ መንግስት በምርጫ ሰላማዊ የመንግስት<br />

ሽግግርን ይፈቅዳል። ይኽ ህገ መንግስታዊ ድንጋጌ<br />

ቢያንስ በወረቀት ላይ ለመንግስት ለውጥ ጥያቄ<br />

ያመቻቻል መልስ ይሰጣል። ነገር ግን በኢትዮጵያ<br />

በስልጣን ላይ ያለው መንግስት በፈጠራቸው የምርጫ<br />

ቦርድ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ ካድሬዎች እና<br />

ሲያስፈልግ ፖሊስ በመጠቀም ምርጫ ስለሚሰርቅ<br />

የኢትዮጵያን ህዝብ የመንግስት ስልጣን ባለቤት<br />

እንዳይሆን ያደርጋል። ይኽን ምርጫ የመስረቅ<br />

ችግር መቋቋም ከተቻለ በህገ መንግስት የተደነገገው<br />

ይመቻቻል መፍትሄው የከፈተውን ቀዳዳ መጠቀም<br />

እንደሚቻል ግልጽ ነው። የመንግስትን ምርጫ<br />

መስረቅ ለመከላከል “ነፃ አውጭ” የተባለ ተቃዋሚ<br />

ቡድን ጫካ ገብቶ የእርስ በርስ ጦርነት መጀመር<br />

የለበትም። ከዚኽ በኋላ የኢትዮጵያ ህዝብ የአዞ እንባ<br />

ረጪ ነፃ አውጪዎች አያስፈልጉትም። ህዝቡ ራሱን<br />

ነፃ ማውጣት አለበት። አብረውት እየኖሩ የሚታገሉ<br />

የሰላማዊ ትግል መሪዎች በሚለግሱት እገዛ ብቻ ራሱ<br />

ህዝቡ የሚያስፈልገውን መስዋዕት በመክፈል ድምጹን<br />

ከስርቆት ተከላክሎ የመንግስት ስልጣን ባለቤት<br />

መሆን ይችላል። ዛሬ ዲሞክራሲ በሆኑ አብዛኛዎቹ<br />

አገሮች ህዝቡ ነው እራሱን በሰላማዊ ትግል ነፃ<br />

ያወጣው። ለዲሞክራሲ ሽግግር አስተማማኙ<br />

መንገድም ይኸው ህዝቡ የተሳተፈበት ሰላማዊው<br />

መንገድ ነው። የኢህአዴግ መንግስት የኢትዮጵያን<br />

ህዝብ ድምጽ አላከብርም ካለ የኢትዮጵያም<br />

ህዝብ በበኩሉ አልገዛልህም ማለት አለበት። ህዝብ<br />

የኢትዮጵያ ህዝብ ድምጹ እንዳይሰረቅ የመጠበቅ<br />

መብትም አለው። ድምጽህን እኛ እንጠብቅልሃለን<br />

የሚሉ የአዞ እንባ ረጪ ካድሬዎችንም ያለማመን እና<br />

በድምጽ አሰጣጥ እና በድምጽ ቆጠራ ላይ በተወካዮቹ<br />

አማካኝነት የመሳተፍ መብትም አለው።<br />

የሆነው ሆኖ የኢትዮጵያ ህዝብ በህገ መንግስቱ<br />

ውስጥ የተጠቀሰውን የምርጫ (መቻቻል) ድንጋጌ<br />

ከ“ፕላን ለ” ጋር አዳቅሎ መጠቀምን ከመረጠ ከህዝቡ<br />

ጋር አብረው የሚኖሩ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ብዙ<br />

ስራ ይጠበቅባቸዋል። በኢትዮጵያ የምርጫ ቦርድ<br />

እና የምርጫ አስፈጻሚዎች ገለልተኛ እንዲሆኑ እና<br />

አለም አቀፍ ምርጫ ታዛቢዎች በብዛት እንዲሰማሩ<br />

ከመደራደር አንስቶ ህዝቡ ድምጹን ከስርቆት<br />

እንዲጠብቅ የማዘጋጀት ኃላፊነት አለባቸው። የሰላም<br />

ትግል ሰራዊት መገንባት ይኖርባቸዋል።<br />

ከፍ ብለው የተመለከቱት ሁለቱም አማራጮች<br />

የሰላም ትግል ሰራዊት ይሻሉ። ለመሆኑ የሰላም ትግል<br />

ሰራዊት ማን ነው? ኢንጅነሮች፣ መምህራን፣ የህግ<br />

ባለሙያዎች፣ የህክምና ባለሙያዎች፣ ተማሪዎች፣<br />

13<br />

በርስ የጎሪጥ እንዲተያይ በአሜት እንዲበላላ መንገድ<br />

ከፍቶለት ይገኛል፡፡<br />

አመታዊውን የሕዝብ ምንዳቸውን በተገቢው መልክ<br />

የሚከፍሉ ሕዝቤና አገሬ አድገው አያቸዋለሁ የሚሉ<br />

እንዳሉ ሁሉ ከባለሥልጣን ጋር በመሞዳሞድ፣ በዘር፣<br />

በቋንቋ፣ በቡድን፣ በኃይማኖት በመጠላላለፍ እና<br />

በመሳሳብ ከሕገወጡ ከኮንትሮባንድ ንግድ ጀምሮ<br />

ሰነድ እስከመደለዝና ማዘጋጀት አልፎ የሕዝብ ንብረት<br />

የሆኑ እንደ መሬት ማምረቻና ማከፋፈያ ተቋማትን<br />

ወደ እራሳቸውን ግብረ አበሮቻቸው የሚያዘዋውሩ<br />

ጥቂት አይደሉም፡፡ የሚያሳዝነው ደግሞ ይህን አደገኛ<br />

አካሄድ የሚቀላቀሉ ግለሰቦች ቁጥር ከእለት ወደ እለት<br />

በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ መምጣቱ ሌላው አደገኛ እና<br />

አሳሳቢ ሁኔታ ነው፡፡ አሁንም የዘንድሮ የግብር ዓመቱ<br />

ጥቅምት 30/2004 ዓ.ም እንደሚገባደድ የታወቀ ነው፡፡<br />

ቢሆንም ግን ምን ያህሉ ከጨዋታ ውጪ እንደሚሆንና<br />

ምን ያህሉም ተፍገምግሞ ምን ያህሉም ተዝናንቶ<br />

እንደሚቀጥል ይለይለታል፡፡<br />

ኢኮኖሚስቶች፣ የባንክ ሰራተኞች፣ የቴሌ፣ የመብራት<br />

ኃይልና የውሃ ሀብት ሠራተኞች አርቲስቶች፣ ታክሲ<br />

ነጂዎች፣ ግንበኞች፣ ሱቅ ነጋዴዎች፣ እናቶች፣<br />

አባቶች፣ የከተማ እና የገጠር ኗሪ ባጠቃላይ የሀገሪቱ<br />

ለውጥ ፈላጊ ዜጎች ሁሉ ሰላማዊ የዲሞክራሲ ኃይል<br />

ናቸው። የሰላም ትግል ሰራዊት አባላት ስራቸውን<br />

ሲጨርሱ ወደ መደበኛ ስራቸው የሚመለሱ ዜጎች<br />

ናቸው። አምባገነን መንግስትን ከስልጣን ለማስወገድ<br />

የሚደረግ ቀጣይነት ያለው የትጥቅ ትግል የሰለጠነና<br />

የተደራጀ መደበኛ የጦር ኃይል ሊኖረው እንደሚገባ<br />

ሁሉ የህዝብ ድምጽ እንዳይሰረቅ ለማድረግም ሆነ<br />

የህዝብ ድምጽ አላከብርም ያለ አምባገነን መንግስትን<br />

በሰላማዊ ትግል ከስልጣን ለማስወገድ የሚደረግ<br />

የሰላም ትግልም የሰለጠነ፣ የተደራጀ እና በድስፕሊን<br />

የታነጸ የሰላም ትግል ሰራዊት ያስፈልገዋል። የሰላም<br />

ትግል ሰራዊት ራሱን ከመንግስት ወሬ አቀባዮች<br />

(in<strong>for</strong>mers) እና ከመንግስት መልክተኛ ቆስቋሾች<br />

በመጠበቅ ረገድም የሰለጠነ ነው። በመኪና ነዳጅ<br />

ውስጥ ውሃ መቀላቀል የመኪና ነዳጅን እንደሚበክል<br />

ሁሉ የሰላም ትግል በካዮችም እንዳሉ የሚያውቅ እና<br />

በጥንቃቄ የሚጓዝ ኃይል ነው። የሰላም ትግል ሰራዊት<br />

ከገዢው ፓርቲ ደጋፊዎች ጋር ግጭት ቀርቶ ክፉ ቃል<br />

መቀያየር እንደማያስፈልግ ያውቃል። የሰላም ትግል<br />

ሰራዊት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የሰለጠኑ አባሎች<br />

ስለሚያሳትፍ የተወሰኑ መሪዎች ቢታሰሩም ትግሉ<br />

ይቀጥላል። አምባገነኖች የአገሪቱን ህዝብ በሙሉ<br />

የሚያስሩበት እስር ቤት የላቸውም።<br />

በፍኖተ ነፃነት ቁጥር 4 በአክሱም ዘመን የነበረው<br />

የመንግስት ሽግግር ባህላችን አስከፊ እንደነበር<br />

ተመልክቷል። ከዘመነ አክሱም ወዲህ ኢህአዴግ<br />

ስልጣን እስከጨበጠበት ድረስም ቢሆን የመንግስት<br />

ሽግግር ታሪካችን ይበልጥ አስከፊ እየሆነ እና ኋላቀር<br />

እያደረገን እንጂ ወደፊት እንድንራመድ አንዲት<br />

ጋት አልረዳንም። በእርስ በርስ ጦርነት የሚደረግ<br />

የመንግስት ሽግግር ቢትዮጵያ ላይ ያደረሰው ኪሳራ<br />

በፍኖተ ነፃነት ቁጥር 12 ቀርቧል። በእርስ በርስ<br />

መገዳደል የሚፈጸም የመንግስት ስልጣን ሽግግር<br />

በኢትዮጵያ መቆም አለበት። ኢትዮጵያ ህዝብ<br />

የመንግስት ስልጣን ባለቤት የሚሆንበት ዘመናዊ<br />

የመንግስት ሽግግር ባህልን ተቀብላ በዘመናዊ<br />

መንግስት መመራት መጀመር አለባት። ለዚህ<br />

አስተማማኙ የፖለቲካ ትግል መንገድ ሰላማዊ ትግል<br />

ነው። ከፍ ብለን ያየናቸው ሁለት አማራጮች የሰላም<br />

ትግል መንገዶች ናቸው። ለዲሞክራሲ የሚደረግ<br />

ትግል በየትም አገር ቢሆን ቀላል ሆኖ አያውቅም።<br />

ይሁን እንጂ ከገዢ አምባገነኖች አቅም ጨቁነው<br />

የሚገዙት ህዝብ አቅም ሚሊዮን ጊዜ እንደሚበልጥ<br />

ላፍታ መዘንጋት የለብንም። ስለዚኽ በረጅሙ<br />

አስፈላጊው ጥናት እና ዝግጅት ከተደረገ፣ አቅም<br />

ከተገነባ፣ ስትራተጂዎች እና ፕላኖች በጥንቃቄ ከተሰሉ<br />

በኢትዮጵያ የሰላም ትግል መስራት ብቻ ሳይሆን<br />

ለኢትዮጵያ ተመራጩ የፖለቲካ እና የመንግስት<br />

ሽግግር ባህል እሱ ብቻ ነው በማለት ጥናታችንን<br />

እንደመድማለን።<br />

www.andinet.org.et


14<br />

ኢሕአዴግና መገናኛ ...<br />

www.andinet.org.et<br />

የግሉን ሚዲያ በተመለከተ ምርጫ 97 ለኢትዮጵያ<br />

ያመጣው መልካምም መጥፎ ነገሮችም አሉ።<br />

የኢትዮጵያ ሚዲያ ላይ ከፍተኛ ጥናት ያደረጉና<br />

ስማቸው እንዳይገለፅ የጠየቁ ምሁር እንደሚሉት<br />

“መልካም ነገር የምለው በአገር ውስጥና በዓለም<br />

ዓቀፍ ጫናዎች ምክንያት ኢሕአዴግ በጭራሽ<br />

ፍቃድ ሊሰጠው የማይፈልገው የነበረውን የሬዲዮ<br />

ፍቃድ መስጠቱ ነው። በእርግጥ ፍቃድ አሰጣጡ<br />

ጥንቃቄ ያልተለየው መሆኑ የሚያስታውቀው፣<br />

የኤፍ.ኤም ሬዲዮ መስመሮች መሆናቸውና ለሦስት<br />

ድርጅቶች ብቻ መፈቀዱ ነው።” ይላሉ። እነዚህ<br />

ሶስት በስራ ላይ ያሉት የኤፍ.ኤም ሬዲዮ ጣቢያዎች<br />

ዛሚ FM 90.7፣ ፋና FM 98.1 እና ሸገር FM 102.1<br />

ናቸው።<br />

በ1999 ዓ.ም የፀደቀው ስለብሮድካስት አገልግሎት<br />

የወጣው አዋጅ በአንቀጽ 23(3) ላይ “የፖለቲካ<br />

ድርጅት ወይም የፖለቲካ ደርጅት ባለአክስዮን<br />

የሆነበት ወይም የፖለቲካ ድረጅት የበላይ አመራር<br />

አባል ባለአክስዮን ወይም በማንኛውም ደረጃ<br />

የአመራር አባል የሆነበት ድርጅት” የብሮድካስት<br />

ፍቃድ እንደማይሰጠው ያውጃል፡፡በኢትዮጵያ<br />

የመገናኛ ብዙሃን ላይ እንደሚያሳየው ዛሬ<br />

በኢትዮጵያ አንድ ሙሉ በሙሉ በመንግሥት<br />

ቁጥጥር ስር ያሉ የቴሌቪዥን ጣቢያና አስር የሬዲዮ<br />

ጣቢያዎች እንዳሉ ይገልፃል፡፡ ይህ ጥናት በግልፅ<br />

እንዳስቀመጠው ስምንቱ ክልላዊ ሽፋን (FM)<br />

ሲኖራቸው፤ ሁለቱ ደግሞ በክልል ደረጃም በአገር<br />

አቀፍ ደረጃም ስርጭት ያስተላልፋሉ፡፡<br />

ምሁሩ ድህረ 97 የተጋረጠ ከባድ ፈተና የሚሉት<br />

ዸግሞ በአጠቃላይ የሚዲያ ተቋማትን የተመለከተ<br />

ቢሆንም፤ እጅግ የከበደው ፈተና ግን ወደ ነፃው<br />

ፕሬስ ማድላቱን ያሰምሩበታል። “ኢሕአዴግ<br />

ከምርጫ 97 በፊት የነፃው ፕሬስ ተፅዕኖ ከቁጥጥሩ<br />

እንደማይወጣ የነበረው እምነት ስህተት መሆኑን<br />

የተረዳው በምርጫው ጊዜ ነበር። ስልጣኑን<br />

ጭምር ሊያሳጡት የሚያስችል አቅማቸውን<br />

በማየቱ ከምርጫው በኋላ በወሰዳቸውና አሁንም<br />

ከሚወስዳቸው እርምጃዎች በቀላሉ ለመረዳት<br />

ይቻላል።” ይላሉ። ለዚህ አባባላቸውም ማስረጃ<br />

አድርገው የሚያቀርቧቸው ዋና ዋናዎቹ የገዢው<br />

ፓርቲ እርምጃዎች በ2001 ዓ.ም የወጣው<br />

የማያላውሰው የሚዲያ ህግንና የአዲስ ነገር ጋዜጣን<br />

እጣ ፈንታ ነው።<br />

የ42 ዓመቱ ሸምሱ ኢቲቪ 3 አልጠራ ብሎት<br />

የቴሌቪዥኑን የውስጥ አንቴና አንዴ ቴሌቪዥኑ<br />

ላይ ይሰካዋል፣ አንዴ ግድግዳው ላይ ይሰካዋል፣<br />

አንዴ ገመድ ቀጥሎበት ከቤቱ ውጭ አጣና አቁሞ<br />

ቢሰቀለውም፤ ጥርት ያለ ምስልና ድምፅ ማግኘት<br />

አልቻለም። ይህን ሁሉ ድካም የሚያይበት ምክንያት<br />

“ኢቴቪ አንድና ሁለት ልዩነት ስለሌላቸው፣ ኢቴቪ<br />

ሦስት የተለየ ነገር ይኖረዋል።” በሚል ተስፋ<br />

መሆኑን ይናገራል። የመስሪያም የመኖሪያም<br />

ስፍራው በሆነችው ትንሿ “ሻይ ቤት” ውስጥ ቀኑን<br />

ሙሉ ተከፍቶ የሚውለው ቴሌቪዥኑ፤ ከኢትዮጵያ<br />

ቴሌቪዥን በስተቀር የሳተላይት ቴሌቪዥን<br />

ፕሮግራሞችን ለመሳብ የሚያስችል መቀበያ ሳህን<br />

ስለሌለው መሆኑን ያስረዳል።<br />

ትንሿ ሻይ ቤቱ በደንበኞች የምትጨናነቀው<br />

በምሳ ሰዓትና በእራት ሰዓታት ነው። በመጠነኛ<br />

ዋጋ የሚሸጣቸው ከሻይ ጀምሮ ያሉት ሌሎች<br />

ምግቦቹን ከኢቴቪ በሚተላለፉት የሰባት ሰዓትና<br />

የምሽት ሁለት ሰዓት ዜናዎች አጅቦ ያቀርባቸዋል።<br />

አብዛኛዎቹ ደንበኞቹ መገናኛ አካባቢ የህንፃ መሳሪያ<br />

በሚሸጥባቸው መደዳ ሱቆች ውስጥ የጉልበት ስራ<br />

የሚሰሩ ሰራተኞች ናቸው። ሲሚንቶና የአርማታ<br />

ብረት የመሳሰሉትን ከመኪና ወደ ሱቆቹ፣ ከሱቆቹ<br />

ወደ መኪና ይጭናሉ፣ ያወርዳሉ። ደንበኞቹን<br />

በከፍተኛ ክብካቤ የሚያስተናግደው ሸምሱ፣<br />

ደንበኞቹ በሁለት ነገሮች ቀልድ እንደማውቁ<br />

ይናገራል። በምግባቸውና በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን።<br />

“አድካሚ የጉልበት ሥራ ስለሚሰሩ፣ ምግባቸውን<br />

በጥራት ብቻ ሳይሆን በፍጥነትም ማቅረብ አለብህ”<br />

ይላል። ከተቀመጠበት እንደነገሩ ወደ ተቀመጠው<br />

ቴሌቪዥን እያማተረ። በምሳና በእራት ሰዓታት<br />

ደምበኞቹ ከምግባቸው ጋር እንዲቀርብላቸው<br />

የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንን የቀትር የሰባት ሰዓትንና<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

ከገፅ 7 የዞረ<br />

የምሽት ሁለት ሰዓት ዜናን ነው። ከዜናውም<br />

የስፖርት ዜናውን። የምግብ ቤቷ ደንበኞች፤ የስራ<br />

ልብሳቸውን እንኳን ሳይቀይሩ፣ ሲሚንቶ የጠጣውን<br />

ፀጉራቸውን ሳያራግፉ ቶሎ ምሳቸውን በልተው ወደ<br />

ሥራቸው ለመመለስ ሲጣደፉ ይታያሉ። አንዳንዶቹ<br />

ከላይ ካደረጉት ካኪ ቱታ ሥር የአርሰናል፣ የቼልሲና<br />

የማንቸስተር ዩናይትድ እግር ኳስ ቡድኖች<br />

ማሊያዎችን /ቲ-ሸርቶች/ ማድረጋቸው ይታያል።<br />

ሰባት ሰዓት ሞልቶ የኢቴቪ የዕለቱ ዜና መቅረብ<br />

ቢጀምርም፤ ተመጋቢዎቹ ግድ የሰጣቸው<br />

አይመስልም። ፕሬዝዳንት ግርማ ለሁለቱ ምክር<br />

ቤቶች “በአሜሪካ የተከሰተውን የኢኮኖሚ …..”<br />

ቢልም ዜና አንባቢው ግድ የሰጣቸው አይመስልም።<br />

በየከበቡት ጠረጴዛና እጃቸውን በየሚሰዱበት<br />

ትሪ ላይ አፍጥጠው፣ አልፎ አልፎ ገልመጥ እያሉ<br />

የተከፈተውን ቴሌቪዥን እየቃኙ የራሳቸው<br />

“ወግ” ይጠርቃሉ። ዜና አቅራቢው “አሁን ለሰዓቱ<br />

ወደያዝናቸው የስፖርት …….” የጀመረውን ዓረፍተ<br />

ነገር ከመጨረሱ በፊት “ስፖርት” የሚለውን ቃል<br />

ሲጠራው፤ ከየጠረጴዛው “ዝም በሉ እስፖርት<br />

እንስማ” የሚሉ ድምፆች መውጣት ጀመሩ።<br />

የቴሌቪዥኑ ድምፅ ከፍ እንዲል ተጠየቀ። ታዛዡ<br />

ሸምሱ ድምፁን ጨመረ።<br />

የአገር ውስጥ የስፖርት ክንውኖች ቀረቡ። የውጭ<br />

አገር ስፖርታዊ ክንውኖች በተለይም እ.ኤ.አ የ2012<br />

የአውሮፓ ዋንጫ ማጣሪያ ግጥሚያዎች በምስል<br />

ተደግፈው በጥሩ ትንታኔ በቴሌቪዥኑ መስኮት<br />

ታዩ። የስፖርት ዜናው አብቅቶ ወደ ዋና ዋና ዜናዎች<br />

መመለሱን ዜና አቅራቢው ከመናገሩ በጫጫታ<br />

ተሞላች። “ፈረንሳይ አለፈች፣ የናስሪን ፔናሊቲ<br />

አመታት አየኸው?”፣ “የክርስቲያኖ ሮናልዶን ጐል<br />

ተመለከትህ?”፣ “ፓርቹጋል መሸነፏ ያሳዝናል።”<br />

ሌላም ሌላም የኳስ ትንታኔም አስተያየትም<br />

እየተሰጣጡ ሻይ ቤቷን ጥለው ወጡ። ምሳቸውን<br />

ከኢቴቪ የስፖርት ዜና ጋር አጣጥመው፣ ለራታቸው<br />

የሚሆን ገንዘብ ለማግኘት ወደ ሥራቸው ተመለሱ።<br />

ሸምሱንና ቴሌቪዥኑን ለብቻቸው ትተው።<br />

ሸምሱም አንዴ የቴሌቪዥኑን የርቀት መቆጣጠሪያ፤<br />

አንዴ ውጭ አጣና ላይ የሰቀለውን አንቴናን<br />

መነካካት ይጀምራል። የኢቴቪ ሦስትን የጠራ<br />

ድምፅና ምስል ለማግኘት። ፍለጋውን ይቀጥላል<br />

እስኪሳካለት ድረስ። ወይም ደምበኞቹ ሁለት ሰዓት<br />

መሙላቱን እስኪነግሩት ድረስ።<br />

ኢሣት ያመጣው ጣጣ<br />

ሰለሞን ቻላቸው በህይወቱ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንን<br />

እንደመመልከት የሚጠላው ነገር ያለ አይመስልም፡<br />

፡ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ሲባል መንገሽገሽ<br />

ይጀምራል፡፡ ቤተሰቡ ውስጥ በአማርኛ ዜና<br />

መመልከት የሚፈልግ ሰው በመኖሩ ግን ዘወትር<br />

ማታ ቴሌቪዥኑ ፊት ማፍጠጥ ግድ ሆኖበታል፡<br />

፡ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ሁለትም ሆነ ሦስት<br />

ወይም አራት ግድ እንደሌለው ይናገራል፡፡ በፊት<br />

በፊት የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን እንዳይከፈት ነበር<br />

ከቤተሰቡ ጋር ሲከራከር የከረመው፡፡ ቀድሞ የሱን<br />

ሃሳብ ደጋፊ የነበረችው ታናሽ እህቱ በእሱ አገላለፅ<br />

“ሌላውን ዓይነት ኢቴቪ” ካልተመለከትኩ እያለች<br />

ታስቸግረዋለች፡፡<br />

ሰለሞን እንደሚለው EBS የተባለውን በዲሽ<br />

የሚተላለፈውን ጣቢያ የኮሌጅ ተማሪ የሆነችው<br />

እህቱ ካላየን ብላ ታስቸግረዋለች፡፡ እንደ ዕምነቱ<br />

EBS የተከፈተው ESAT ጣቢያን ለማስቀየስ ነው፡<br />

፡ በፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ንቁ ተሣታፊ መሆኑን<br />

የሚገልፀው ሰለሞን “መንግሥት በፈጠራት በዚች<br />

ትንሽ መሸወጃ” እህቱን ጨምሮ ብዙ ሰዎች ሲሸወዱ<br />

መመልከቱ እንደሚያናድደው እጁን እያወናጨፈ<br />

ይናገራል፡፡አማራጭ ሲያጣ ሸገር ኤፍ ኤምን<br />

ለመስማት መኝታ ቤቱ መደበቅ ብቸኛ መፍትሄው<br />

መሆኑን ያስረዳል ፡፡<br />

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲና ብቸኛው<br />

የተቃዋሚ ፓርቲ የምክር ቤት አባል የሆኑት<br />

የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ ደግሞ የተለየ ሃሳብ<br />

አላቸው፡፡ “ኢቴቪን ለማየት ምንም የሚያጓጓ<br />

ነገር የለውም፡፡ እንደ ህዝብ ተወካይነታቸው ግን<br />

የመንግሥትን ወቅታዊ አቋሞችና ሃሳቦችን ለማወቅ<br />

ብቻ የሚከታተሉት መሆኑን ገልፀዋል፡፡” አቶ<br />

ግርማ ከዚያ ይልቅ በጣም የሚገርማቸው ጠቅላይ<br />

ሚንስተሩን ጭምር ጠይቀው መልስ ያላገኙለት<br />

ጥያቄ ኢቴቪ አንድ ሆኖ በብቃት መስራት ሳይችል<br />

ሁለትና ሶስት የመሆኑ ሚስጥር ነው፡፡<br />

የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ሚዛናዊነት<br />

አቶ ሰለሞን ኃይለ ማርያም “Trans<strong>for</strong>ming State<br />

Broadcasting in to Public Service Broadcasting<br />

in <strong>Ethiopia</strong>” በሚለው ከ1997 ዓ.ም በፊት<br />

በተሰራው ጥናታቸው እንዳሳዩት የኢትዮጵያ ሬዲዮ<br />

ድርጅት አየር ላይ ካዋላቸው የሁለት ሰዓት ዜናዎች<br />

ውስጥ 74.8% የሚሆኑት ይሰሩ የነበሩት በጣቢያው<br />

ጋዜጠኞች ሳይሆን በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት<br />

እንደነበር ያስረዳሉ፡፡ ጣቢያው በሁለት ሰዓቱ<br />

የማታ የዜና ክፍለ ጊዜው ያሰራጫቸውን ዜናዎች<br />

በመውሰድ የተደረገው ይህ ጥናት እንደሚያሳየው<br />

የዜናው አንባቢዎች ብቻ ሳይሆኑ፤ የዜና አራሚዎቹ<br />

ጭምር የዜናውን ሚዛናዊነት፣ ትክክለኛነትና ነፃ<br />

መሆን ማረጋገጥ እንደማይችሉ ይገልፃል፡፡<br />

ይኸው ተመሳሳይ ጥናት የደረሰበት ድምዳሜ<br />

እንደሚያሳየው ባለስልጣናት በቃል በሚሰጡት<br />

ትዕዛዝ ምክንያት፣ የጣቢያው ጋዜጠኞች<br />

የተዛባ፣ ትክክል ያልሆነና ሚዛናዊ ያልሆኑ<br />

ዘገባዎችን እንዲያስተላልፉ እንደሚገደዱ ፅፏል፡<br />

፡ በተጨማሪም ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸው፣<br />

በመንግሥት ላይ ሂስ የሚሰነዝሩ ዜናዎች በጣቢያው<br />

ጋዜጠኞች ቢዘጋጁም፤ ብዙ ጊዜ ዕጣ ፈንታቸው<br />

ውድቅ መደረግና ከኢዜአ ወይም ከዋልታ በመጡ<br />

ሌሎች ዜናዎች መተካት እንደነበር አስፍርውታል፡፡<br />

ሌላው የአቶ ሰለሞን ጥናት የደረሰበት ድምዳሜ<br />

እንደሚያሳየው ለአንድ ወር ገደማ የሰበሰባቸውና<br />

የተነተናቸው የኢትዮጵያ ሬዲዮ ዜናዎች<br />

በማጠቃለያቸው ውስጥ እንዳስቀመጡት የተቃዋሚ<br />

የፖለቲካ ፓርቲዎችን በተመለከተ የተሰሩት ዜናዎች<br />

በሙሉ አሉታዊና ሚዛናዊ ያልሆኑ ሲሆኑ ገዢውን<br />

ፓርቲ የተመለከቱት ደግሞ አዎንታዊ ነበሩ፡፡<br />

በመሆኑም አቶ ሰለሞን ሲደመድሙም የተጠቀሰው<br />

ግኝት የሚያደርሰን መደምደሚያ ገዢው ፓርቲ<br />

በቁጥጥሩ ሥር ያሉትን የመንግሥት መገናኛ<br />

ብዙሃንን ፣ሕገ-መንግሥቱን፣ ሌሎች ድንጋጌዎችንና<br />

የዴሞክራሲን መሠረታዊ መርህ በሚጥስ መልክ<br />

እየተጠቀመበት መሆኑን ነው፡፡ መሠረታዊ መርህ<br />

ብለው የጠቀሱትም የተለያዩ ሃሳቦችን ማስተናገድ<br />

(plurality of opinion) መሆኑን ነው፡፡<br />

አቶ ሰለሞን ኃይለማርያም የጥናታቸው ግኝትን<br />

መሠረት በማድረግ የመፍትሄ ሃሳቦችን በመጠቆም<br />

ጥናታቸውን አጠናቀዋል፡፡ ካስቀመጧቸው<br />

የመፍትሄ ሃሳቦችም መካከልም የህገ-መንግሥቱን<br />

አንቀፅ 29(2) መንፈስ የያዘ አዲስ ህግ በፓርላማው<br />

ማውጣት የመንግሥት መገናኛ ብዙሃንን<br />

ወደ Public service Broadcasting ማዞር ፤<br />

የመንግስት መገናኛ ብዙሃን የቦርድ አባላትን ግልፅ<br />

በሆነ መንገድ መሾም፤የመንግሥትን ጣልቃ ገብነት<br />

በህግ መገደብ፤ሚዲያውን ለህዝብ ክፍት ማድረግና<br />

ሙያዊ ጣልቃ ገብነትን ማስወገድ ጋዜጠኞቹ ሙያዊ<br />

ነፃነት እንዲኖራቸው ማድረግ የሚሉ አሉበት፡፡<br />

ኢሕአዴግ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የግንባሩን<br />

አቋም በሚያንፀባርቁት ይፋዊ ህትመቶቹ ውስጥ<br />

በግልፅ እንዳስቀመጠው፣ መገናኛ ብዙሃን<br />

ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ሊያበረክቱት<br />

የሚችሉትን ሚና ከፍተኛ መሆኑን እውቅና<br />

ይሰጣሉ፡፡ ይህ እውቅና ግን “ለማጥፋትም” ትልቅ<br />

አቅም እንዳላቸው ከመግለፅም ባለፈ መልኩ<br />

መንግሥት ሊቆጣጠራቸው እንደሚገባ አፅንኦት<br />

ይሰጣል፡፡ ለዚህም መከራከሪያው በተደጋጋሚ<br />

የሚያነሳው ምሳሌም በምርጫ 97 ወቅት “ነፃው<br />

ፕሬስ” ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር “በመወገን”<br />

በመንግስት፣ በሕዝብና በአገር አንድነትና ፀጥታ ላይ<br />

ሊያደርሱት የነበሩትን “አደጋዎችን” ነው፡፡ ለዚህም<br />

ምክንያቱን ሲገልፅ “የዴሞክራሲያችን ታዳጊነትና<br />

ውስንነት” መሆኑን ይገልፃል፡፡ ይፋዊ ህትመቶቹም<br />

መፍትሄ ብለው የሚሰነዝሩት፣ አሁን በአገራችን<br />

የሌለው የነቃ ሊብራል መካከለኛ መደብ የመገናኛ<br />

ብዙሃን አካሄድን መስመር ማስያዝ የሚችለው<br />

እስኪፈጠር ድረስ በአንድ በኩል የመንግሥት<br />

ቁጥጥር ተገቢ መሆኑን ያሰምርበታል፡፡ በሌላ በኩል<br />

“ታዳጊ ዴሞክራሲያችን” እንዲጐለብት መንግሥት<br />

2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />

የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታው ሂደት ላይ<br />

ርብርብ ማድረግ ለመቀጠል ቁርጠኛ መሆኑን<br />

ይገልፃል፡፡<br />

ሸክሙ የማነው ?<br />

ምርጫ 97 ውጤትን ተከትሎ በኢሕአዴግና<br />

በቅንጅት መካከል ተፈጥሮ በነበረው ውዝግብ<br />

እንደታየው፣ ሁለቱም ፓርቲዎች የተለያዩ የመገናኛ<br />

ብዙሃንን በመጠቀም ከህዝብ ጋር ይገናኙ እንደነበር<br />

ይታወሳል፡፡ ሂዩማን ራይትስ ዎች አውጥቶት<br />

የነበረው አንድ ዘገባ እንደሚያሳየው፤ በምርጫ 97<br />

ሰሞን በኢትዮጵያ ታይቶ የነበረው የነፃው ፕሬስ<br />

በነፃነት ያሰራውን ከባቢ መፈጠሩ በኢትዮጵያ ታሪክ<br />

ተከስቶ እንደማያውቅ ነው፡፡ ይኸው ተመሳሳይ ዘገባ<br />

እንደሚያትተው ከድህረ-ምርጫ 97 በመንግሥት<br />

የተወሰዱ እንደ ጋዜጠኞችን ማሰርና ብዙም<br />

የማያላውስ አዲስ የሚዲያ ሕግ ማውጣት ፕሬሱን<br />

መቀመቅ እንደከተተው ይደመድማል፡፡<br />

ፖለቲካ ፓርቲዎች ውጤት ለማምጣት የመገናኛ<br />

ብዙሃንን እድሎችን አሟጦ መጠቀም፣ ከየፓርቲዎቹ<br />

የቀን ተቀን ስራ እኩል (ምናልባትም የበለጠ?)<br />

ትኩረት እንደሚያስፈልገው ከኢሕአዴግና<br />

ከቀድሞው ቅንጅት በስተቀር በደንብ የተረዳው<br />

ያለ አይመስልም፡፡ የቀድሞው ቅንጅት ምክር ቤት<br />

ለመግባት ወይም ላለመግባት ረጅምና ተከታታይ<br />

ስብሰባዎች አድርጐ፣ በመጨረሻ ላይ የደረሰበት<br />

ውሳኔ የማመቻቸት (Compromise) ነበር፡<br />

፡ ፓርቲው ምርጫ 97 ነፃና ፍትሃዊ ያልነበረ<br />

መሆኑን ቢያምን፣ ለኢሕአዴግ “ስምንት ነጥቦችን”<br />

አቅርቦ ገዢው ፓርቲ ከተቀበለው ምክር ቤት<br />

ሊገባ እንደሚችል መግለጹ ይታወሳል፡፡ ከስምንቱ<br />

ጥያቄዎች ውስጥም የመንግሥት መገናኛ ብዙሃን<br />

ከገዢው ፓርቲ ቁጥጥር ተላቀው፣ ራሳቸውን ችለው<br />

ነፃ ሆነው እንዲቋቋሙ የሚጠይቀው አንዱ ነው፡፡<br />

በሌላ በኩል ኢሕአዴግ በመንግሥት ቁጥጥር<br />

ሥር ያሉትን መገናኛ ብዙሃንን ለሚቃሙ ወገኖች<br />

ለማጋራት ፍቃደኛ አይመስልም፡፡ ይህ ብቻ<br />

አይደለም፡፡ ለተቃዋሚ ፓርቲዎች “በራቸው<br />

ክፍት ነው” ተብለው የሚገመቱ የመገናኛ ብዙሃንን<br />

ከማዳከምም የሚመለስ አይመስልም፡፡ ነፃውን<br />

ፕሬስ ጠንከር ባለ አዋጅ፤ ኢሳትን፣ የአሜሪካንና<br />

የጀርመን ድምፅን በማፈን ይህንን አቁዋሙን<br />

አሳይቱአል፡፡<br />

በምርጫ 2002 ሰሞን እንዳስተዋልነው፤ የአሜሪካን<br />

ድምፅ ሬዲዮን ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳይሰማ<br />

ለማድረግ መንግሥታቸው እንደሚያፍነው<br />

ጠቅላይ ሚንስትር መለስ በግልፅ መናገራቸው<br />

አንድ ማሳያ ተደርጐ ሊወሰድ ይችላል፡፡ በእርግጥ<br />

ኢሳት (ESAT) የተባለውን ከኢትዮጵያ ውጭ<br />

የሚሰራጨውን የሳተላይት ቴሌቪዥንን ኢትዮጵያ<br />

ውስጥ እንዳይደርስ የተደረገው የመንግሥታቸው<br />

እጅ ስለገባበት እንደሆነ ተጠይቀው፤ በጉዳዩ ላይ<br />

አስተያየት መስጠት እንደማይፈልጉ በመግለጽ ፣<br />

ጥያቄውን አለመመለሳቸው ይታወቃል፡፡ የዚህ<br />

ዓይነት መልስ ግን የቴሌቪዥን ፕሮግራሞቻቸው<br />

ኢትዮጵያ ውስጥ ሊታዩ ያልቻሉት ኢሕአዴግ<br />

ስርጭታቸው ላይ እየፈጠረ ባለው ማስተጓጐል<br />

ምክንያት መሆኑን ለሚከሱት የኢሳት ጣቢያ<br />

ኃላፊዎች፣ በቂ መልስ መስጠት የቻለ አይመስልም፡<br />

፡አሁንም ክሳቸውን ቀጥለዋልና ፡፡<br />

አጠቃላዩ የአገራችን የመገናኛ ብዙሃን ነባራዊ<br />

እውነታ፣ በፍፁማዊ የበላይነት በሚያስብል<br />

ደረጃ ኢሕአዴግ ለብቻው ተቆጣጥሮት ባለበት<br />

ሁኔታ ሌሎች ድምፆች የመስተናገዳቸው ዕድል<br />

በጣም ጠባብ ይመስላል፡፡ መድረክ ወደ “ግንባር”<br />

መሸጋገሩን ለማብሰር መድረክ ላይ የወጡት ዶ/ር<br />

መረራም፣ ኢቲቪ አንድና ሁለት ሰልችተውት ኢቲቪ<br />

ሦስትን ሲፈልግ የሚውለው ሸምሱም፣ ኢሳትን<br />

ለመከታተል ያልቻለውና ኢቲቪን ሸሽቶ ማምለጥ<br />

ያቃተው ሰለሞንም የልባቸው በቅርቡ የሚደርስ<br />

አይመስልም፡፡ የምርጫ 97 ውጤት የሆነው<br />

የሸገር ኤፍ.ኤም ሬዲዮ አይነት የቴሌቪዥን ጣቢያ<br />

እንዲመጣ መመኘታቸው አልቀረም፡፡ ምኞታቸው<br />

መቼ እውን እንደሚሆን ግን መገመት እንኳን<br />

አልቻሉም፡፡


2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />

መግለጫ ተያት<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

ትግሉ መራራ ቢሆንም በፅናት ለድል እንበቃለን!<br />

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ<br />

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ የተነሳለትን ዓላማ<br />

ለማሳካት የአምባገነኖችን አፈና እየተቋቋመ አባላቱ የህይወትና የንብረት መስዋዕትነት እየከፈሉ<br />

እስከዛሬ ቀን ደርሰዋል፡፡ ዛሬም ገዢው ፓርቲ በአዋጅ በመደገፍ በአካሄደው መንግስታዊ<br />

የጥቃት ዘመቻ ከፍተኛ የፓርቲው አመራሮች፡- (1ኛ) ምክትል ሊቀመንበርና የሕዝብ ግንኙነት<br />

አላፊ አቶ አንዱዓለም አራጌ፣ (2ኛ) የብሔራዊ ምክር ቤት አባል አቶ ናትናኤል መኮንን፣ (3ኛ)<br />

የብሔራዊ ምክር ቤት አባል አቶ ብርሃኑ አሳምነው የማያባራው የግፍ ጥቃት ሰለባ ሆነዋል፡፡<br />

በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስተር መለስ ዜናዊ ባደረጉት ንግግር በተቃዋሚው ጎራ በተለይ<br />

በአንድነት ፓርቲ ላይ የሚደረገው አፈና ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡ ከጥቃት ዘመቻው<br />

በተጨማሪም የፍርድ ቤቱን በትር በህግ ሽፋን እንደሚጠቀሙ በአደባባይ ያለምንም ይሉኝታ<br />

አረጋግጠውልናል፡፡ መንግስት አንድነትን በህግ ሽፋን ስም በጉልበት ለማዳከም መዘጋጀቱን<br />

ያለጥርጥር አረጋግጠውልናል፡፡<br />

ይህ አደገኛ መንግስታዊ ሽብር በፓርቲያችን ላይ እየተፈፀመ ባለበት በአሁኑ ወቅት<br />

የፓርቲያችን ከፍተኛ የስልጣን አካል የሆነው ብሔራዊ ምክር ቤታችን ከጥቅምት 25-<br />

26/2004 ዓ.ም. የአንደኛውን ዙር የመጨረሻ የሥራ ዘመኑን ስብሰባ በታላቅ ቁጭትና ወኔ<br />

ታጅቦ ጉባኤውን አከናውንዋል፡፡<br />

ጉባኤው መንግስት ሕገ-መንግቱን በመጣስ በአባሎቻችን ላይ እየፈፀመ ያለውን የእብሪት<br />

እርምጃ አውግዝዋል፡፡ እንዲሉ በሽብርተኝነት ስም በግፍ<br />

አፍኖ ከማንም ጋር እንዳይገናኙ ሸብቦ ያስራቸው አባሎቶቻችን በአስቸካይ እንዲፈቱ ምክር<br />

ቤቱ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡<br />

ምክር ቤቱ በቀረበለት አጀንዳ ላይ ለሁለት ቀናት ሰፊና ጥልቀት ያለው ውይይት በማድረግ<br />

የኢትዮጵያ ሕዝብ ለነጻነትና ለዴሞክራሲ የሚያደረገውን ሰላማዊ ትግል ወደ ፊት ለማራመድ<br />

የሚያስችሉ ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን አስተላፏል፡፡ በተለይም የፓርቲውን የ2003 ዓ.ም. የሥራ<br />

አፈፃፀምን በተመለከተ ሰፊ ሪፖርት ቀርቦ ደካማና ጠንካራ ጎኖች ተገምግመዋል፡፡<br />

ምክር ቤቱ ከአምስት ወር በፊት ያቋቋመው የጠቅላላ ጉባኤ ጠሪ ኮሚቴ ከአንድ<br />

ወር በኋላ የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ተጠርቶ የስራ ዘመኑን የጨረሰውን ይህን ምክር ቤት<br />

በክብር ያሰናብተዋል፡፡ የሁለተኛው ዙር አዲስ ምክር ቤት በጠቅላላ ጉባኤው በሚደረግ ነፃና<br />

ዴሞክራሳያዊ ምርጫ አዲስ ብሔራዊ ምክር ቤት በመምረጥና የስልጣን ርክክብ ለማድረግ<br />

አንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ም/ቤት መደበኛ ስብሰባውን አካሄደ<br />

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ /አንድነት/<br />

ብሔራዊ ም/ቤት የመጀመሪያ ዙር የመጨረሻውን የሥራ<br />

ዘመን ጥቅምት 25 እና 26 ቀን 2004 ዓ.ም በጽ/ቤቱ<br />

አዳራሽ መደበኛ ስብሰባውን አካሄደ፡፡<br />

በስብሰባውም በዋነኛነት አራት አጀንዳዎች<br />

ለውይይት የቀረቡ ሲሆን እነኝህም 1ኛ የብሔራዊ ሥራ<br />

አስፈፃሚ ኮሚቴ የሥራ ሪፖርት ማዳመጥ 2ኛ የጠቅላላ<br />

ጉባዔ ጠሪ ኮሚቴ የሥራ ሪፖርት ማዳመጥ 3ኛ የአምስት<br />

ዓመት እቅድና ስትራቴጂ መሠረት በማድረግ የ2004<br />

ዓ.ም በጀት ዕቅድን ማጽደቅ እና 4ኛ ያለፉትን ስብሰባዎች<br />

ቃለ ጉባዔ ማፅደቅ በሚሉ አጀንዳዎች ዙሪያ ነበር፡፡<br />

ብሔራዊ ምክር ቤቱ በአጀንዳዎቹ ላይ<br />

ሰፊ ውይይት በማድረግ አጀንዳዎችን ያፀደቀ ሲሆን<br />

በተለይም በብሔራዊ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የሥራ<br />

ሪፖርት በፓርቲው ሊቀመንበር በዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ<br />

ቀርቧል፡፡<br />

በሪፖርቱ ላይ በእቅዱ መሠረት የተሰሩና<br />

ያልተሰሩ ሥራዎችን መለየት ተችሏል ሲሉ አባላቱ<br />

ገልፀዋል፡፡ በእቅዱ መሠረት ከተሰሩት ውስጥ የፓርቲው<br />

ልሳን “ፍኖተ ነፃነት” ጋዜጣ በየሳምንቱ አሳትሞ<br />

የፓርቲውን እንቅስቃሴ ወቅታዊ የሆኑ ሀገር አቀፍና ዓለም<br />

አቀፍ መረጃዎችን ለሕዝቡ ማድረስ፣በሀገራዊ ወቅታዊ<br />

ጉዳይ ላይ የተለያዩ ምሁራንን ከውጭና ከሀገር ውስጥ<br />

በመጋበዝ ውይይት ማድረግ፣የፓርቲው መመሪያና ደንብ<br />

በሚፈቅደው መሠረት ከመድረክ አቻ ፓርቲዎች ጋር<br />

ሰፊና ጥልቅ ውይይት በማድረግ መድረክን ከቅንጅት<br />

ወደ ግንባር የማሸጋገር ሂደት፣ከብርሃን ለአንድነትና<br />

ለዴሞክራሲ ፓርቲ ጋር ውህደት የመፍጠር ሂደት<br />

ከተሳኩ ተግባራቶች መካከል ጥቂቶቹ ናቸው ተብሏል፡፡<br />

ሌላው ፓርቲው መዋቅሩን በመላው<br />

ሀገሪቱ የማስፋፋትና አሰራሩንም እስከ ወረዳ ድረስ<br />

በመዘርጋት የፓርቲው አባላት በአቅራቢያቸው<br />

እንዲደራጁ ተደርጓል፡፡ ይሁን እንጂ ይህንና ሌላሎች<br />

እቅዶች ሙሉ በሙሉ ተፈፃሚ እንዳይሆኑ የተለያዩ<br />

እንቅፋቶች ተፈጥረው ነበር፡፡ ከችግሮቹም መካከል<br />

ኢህአዴግ የፖለቲካ ምህዳሩን ማጥበብ፣የፓርቲ አባላትን<br />

ማስፈራራት፣ማሰርና መግደል ዋነኞቹ ችግሮች እንደሆኑ<br />

በም/ቤቱ ተጠቁሟል፡፡<br />

በተጨማሪም ፓርቲው በሰው<br />

ኃይል፣በአቅምና በገንዘብ ማነስ ምክንያት በእቅዱ መሠረት<br />

የሚጠበቅበትን አልሰራም ሲሉ ያለፈው ዓመት ስራ<br />

አፈፃፀም ሪፖርትን ም/ቤቱ ገምግሟል ሲል የፓርቲው<br />

ጽ/ቤት ገልጿል፡፡<br />

ለእቅዱ መሳካት ሌሎች ችግሮችም<br />

ተነስተዋል፡፡ እንደ ችግር ከተነሱት መካከል በቂ የገንዘብ<br />

የታሰበውን ያህል ያለማግኘት፣በቂ የሰው ኃይል ያለመኖር<br />

ተጠቅሰዋል፡፡<br />

ከላይ የተጠቀሱትን ችግሮችን ለመቅረፍ<br />

በ2004 ዓ.ም የተለያዩ የመፍትሄ አቅጣጫዎች የተነሱ<br />

ሲሆን ከነዚህም መካከል በዕውቀትና በቁርጠኝነት<br />

ላይ የተመሰረተ የሰው ኃይል ወደ ፓርቲው እንዲመጣ<br />

መጋበዝ፣ደጋፊዎች ከእውቀትና ከጉልበት በተጨማሪ<br />

በገንዘብም ድጋፍ ማድረግ እንዲችሉ ሕጋዊ የሆኑ<br />

የተለያዩ ስልቶችን መቀየስና ለሕዝቡ ይፋ ማድረግ፣<br />

የሚመጣውም አዲሱ ም/ቤት አባላት በዕውቀትና<br />

በቁርጠኝነት ላይ መሠረት ማድረግ እንዳለበትም ም/ቤቱ<br />

ጠቁሟል፡፡<br />

አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ<br />

አካባቢ ያሉ ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙ የፓርቲው<br />

አባላትንና ሌሎች የፖለቲካና የሕሊና እስረኞችን ጉዳይ<br />

የሚከታተል ልዩ ግብረ ኃይል እንደተቋቋመና ሥራውን<br />

እያከናወነ እንዳለም በሪፖርቱ ገልጿል፡፡<br />

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከ13 ቀናት በፊት<br />

የፓርቲው አባል አቶ ገዛኸኝ ምትኩ በሽብር ተጠርጥሮ<br />

ከሚኖርበት ቂርቆስ ክ/ከተማ በመውሰድ ማዕከላዊ እስር<br />

ቤት እንደሚገኝ ተጠቁሟል፡፡ ባለፈው መስከረም 4 ቀን<br />

2004 ዓ.ም ተጠርጥረው ከታሰሩት መካከል የአንድነት<br />

ፓርቲ ም/ሊቀመንበርና የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ<br />

አንዱዓለም አራጌ ታመው ሆስፒታል ሄደው የሕክምና<br />

እርዳታ እንደተደረገላቸው በሪፖርቱ ላይ የፓርቲው<br />

ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ገልፀዋል፡፡<br />

በስብሰባው ላይ በቀረቡት አጀንዳዎች ዙሪያ ሰፊ<br />

ውይይት ካደረገ በኋላ በአባላቱ ፀድቆ የመጨረሻው<br />

የሥራ ዘመን ጥቅምት 26 ቀን 2004 ዓ.ም ተጠናቋል<br />

ሲል የአንድት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ /አንድነት/<br />

ብሔራዊ ም/ቤት በተለይም ለዝግጅት ክፍላችን ገልጿል፡<br />

፡ይህ በእንዲህ እንዳለ የጉበኤ ጠሪ ኮሚቴ የተሻሻለ<br />

ፕሮግራምና ደንብ ለምክር ቤቱ አቅርቧል፡፡ በአንድነት<br />

15<br />

ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ለምክር ቤቱ አብስሮዋል፡፡ ብሔራዊ ምክር ቤቱ የአንድነት ጠቅላላ<br />

ጉባኤ ህዳር 30 እና ታህሳስ 1/2004 እንዲካሄድ ወስኗል፡፡<br />

ይህንን ተከትሎ ለጠቅላላ ጉባኤ ቀርበው የሚፀድቁትን ልዩ ልዩ የፓርቲው የመታገያ<br />

ሠነዶች ለምክር ቤቱ ቀርበው ከተመረመሩ በኋላ ጠቅላላ ጉባኤው መርምሮ እንዲያፀድቃቸው<br />

ወስኗል፡፡ የፓርቲያችን አዲሱ ሊቀመንበር ከሁሉም አባላት በውድድር በዕጩነት ቀርበው<br />

በጠቅላላ ጉባኤው ፊት አባላት ቀጥተኛ የድምፅ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት እንዲመረጡ<br />

ወስኗዋል፡፡<br />

አንድነት በአለፉት ሦስት ዓመታት ከአጋጠሙት መሰናክሎች ትምህርት ወስዶ የራሱን<br />

የትግል ስትራቴጂና የአምስት አመት እቅድ ነድፎ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ የተቀየሰውን<br />

ስትራቴጂ ለመተግበር የሚያስችል አቅም ለመፍጠር ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ነው፡፡<br />

በአዲሱ ዓመት ዜጎች ያለፍርሃት፣ ሳይሸማቀቁ በነፃነት የሚኖሩባት፣ በግል ጥረታቸው<br />

ያፈሩትን ሃብትና ንብረት በግፍ የማይነጠቁባት፤ የዴሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብቶች<br />

የተከበረባት ኢትዮጵያን ለመፍጠር በሚደረገው ትግል ኢትዮጵያዊያን ሁሉ እጅ ለእጅ<br />

ተያይዘን በፅናት እንድንታገል ብሔራዊ ምክር ቤታችን ጥሪውን ያቀርባል፡፡<br />

መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሕገወጦችን አውግዞና፣ ጊዜው የለውጥ መሆኑን ተገንዝቦ<br />

ፓርቲያችን የሰነቀውን ሀገራዊ ራዕይ ደግፎ በዕውቀት ላይ የተመሠረተና የሰለጠነ የመቻቻል<br />

የፖለቲካ መርሆችን ተከትሎ ለነፃነቱ የበኩሉን አስተዋፅኦ እንዲያበረክት የአንድነት ፓርቲ<br />

ብሔራዊ ምክር ቤት ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡<br />

የፖለቲካና የህሊና እስረኞች በአስቸኳያ ይፈቱ!!<br />

ሠላማዊ ትግል ያሸንፋል!!<br />

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት<br />

ጥቅምት 26/2004 ዓ.ም.<br />

አዲስ አበባ<br />

የስብሰባው ተካፋዮች በከፊል<br />

ፕሮግራም ውስጥ እንዲካተቱ ከተደረጉ ጉዳዮች<br />

መካከል አሸባሪነትን በተመለከተና የመሬት ወረራ<br />

ጉዳይን ያካትታል፡፡ ምክር ቤቱ የፓርቲው ፕሮግራም<br />

ውስጥ እንደ አዲስ የተካተቱትን ጉዳዮች በጥልቀት<br />

ተወያይቶበቷል ሲል ምክር ቤቱ ጠቁሟል፡፡<br />

የተሻሻለው የፓርቲው ህገ-ደንብ እንደሚያስረዳው<br />

የፓርቲው ሊቀመንበር በጠቅላላ ጉባኤ የሚመረጥ ሲሆን፣<br />

ሊቀመንበሩ ሌሎች የስራ አስፈፃሚ አባላትን መልምሎ<br />

በዕጩነት ለብሔራዊ ምክር ቤት አቅርቦ ያፀድቃል፡<br />

፡ የፓርቲው መሪ መሆን የሚፈልጉና የተቀመጠውን<br />

መስፈርት የሚያሟሉ አባላት የጠቅላላ ጉባኤ አባላትን<br />

ድጋፍ እንዲያደርጉ በመቀስቀስ መወዳደር እንደሚችሉ<br />

ተገልጿል፡፡ በተመሳሳይም የስራ አስፈፃሚ አባለት ቁጥር<br />

ከ18 ወደ 11 እንዲወርድ ተደርጓል፡፡<br />

ብሔራዊ ምክር ቤቱም የፓርቲውን ጠቅላላ ጉባኤ<br />

በህዳር 30 እና ታህሳስ 01 ቀን 2004 ዓ.ም. እንዲካሄድ<br />

መወሰኑን ምክር ቤቱ በተለይም ለዝግጅት ክፍሉ<br />

ገልጿል፡፡<br />

www.andinet.org.et


16<br />

www.andinet.org.et<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

E-mail: udjparty@gmail.com<br />

andinet@andinet.org<br />

2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!