ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless
ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless
ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless
Create successful ePaper yourself
Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.
2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />
ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />
2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />
ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />
ዋጋ 5:00<br />
“ቻይናውያን ሕገ-መንግሥታችሁንም<br />
የአዋጅ ሕጋችሁንም አናውቅም ብለዋል” 6<br />
አቶ ኩራባቸው ፍቅሩ ገ/ማርያም የዋልዳ ሆጀቶታ ዳንዲ ደራርቱ አርሲ<br />
“ከሲኦል ያመለጡ” ወጣቶች በግልፅ ይናገራሉ፡፡ ከእስር እንደተፈታ ሰው ነው ራሳቸውን<br />
የሚቆጥሩት፡፡ በየአደባባዩም “እንኳን ደስ ያለህ/ያለሽ!” ሲባባሉ ይሰማል፡፡ በተለይም<br />
በየወሩ ከደመወዛቸው የሚቆረጠው ገንዘብ፣የጋዜጣና የመፅሄት ክፍያ በአባላቱ ቋንቋ<br />
“የማይደርስ ዕቁብ” የሚሉት የድርጅቱ ክፍያ፣የልማት (....) መቶ ፕርሰንት መዋጮ እና . . .<br />
9<br />
አንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ም/ቤት መደበኛ<br />
ስብሰባውን አካሄደ<br />
የደብረብርሃን ከንቲባና<br />
ባለሥልጣናት በሙስና<br />
ተጠርጥረው<br />
መታሰራቸው ተገለፀ<br />
የዞኑ ደን ልማት ሽያጭ መነጋገሪያ ሆኖአል::<br />
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሰሜን<br />
ሸዋ ዞን ዋና ከተማ የሆነችው ደብረ ብርሃን<br />
ከተማ ከንቲባ የሆኑት “አቶ ስዩም ተፈራና<br />
በመሬት አስተዳደርና በልዩ ልዩ የሥራ ኃላፊነት<br />
ላይ የነበሩት የዞኑ ከፍተኛ ባለሥልጣናት<br />
ከሙስና ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው በእስር ላይ<br />
እንደሚገኙ...<br />
11<br />
ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ነፃ የሞያ<br />
ማህበራት ያስፈልጋሉ!<br />
የኢንዱስትሪ ሰላምን በሁለት ከፍሎ ማየት ይቻላል፡፡ ጊዜያዊ ሠላምና ዘላቂ ሠላም ናቸው፡፡ ጊዜያዊ<br />
የኢንዱስትሪ ሠላም የማስመሰያ /አሳሳች/ ሠላም ነው፡፡ የሠራተኛውን ልብ ያልገዛ /የሠራተኛውን ጥቅም<br />
ያልጠበቀ/፣አስተማማኝና ዘላቂ ልማትን የማያመጣ ሠላም ነው፡፡ የመፍጠር ችሎታን የማያበረታታና<br />
ምርታማነትን የማያሳድግ ሠላም ነው፡፡ ዘላቂ የኢንዱስትሪ ሠላም ግን የሠራተኛውን ጥቅምና መብትን<br />
የሚያስከብር፣በሠራተኛው ውስጥ በራስ መተማመንንና መረጋጋትን የሚፈጥር፣የሠራተኛውን የኃላፊነት<br />
ስሜት የሚያስከብር ነው፡፡ ሊኖር የሚገባው ጊዜያዊ ሳይሆን ዘላቂ የኢንዱስትሪ ሠላም ነው፡፡ በሀቅ ላይ<br />
የተመሠረተ ከሆነ የኢንዱስትሪ ሠላም ጥሩ ነው፡፡ ሠላም የሕይወትና የንብረት ዋስትና ይሰጣል፡፡ ሠላም<br />
ካለ ልማትና እድገት አለ፡፡ ሠላም ካለ ቤተሰብ በሰላም ወጥቶ ሠርቶ ይገባል፡፡ ሠላም ከሌለ ሁሉም<br />
የለም፡፡ ዛሬ ያለው ሰላም ግን ምን ዓይነት ሠላም ነው? መብትና ጥቅምን የገፈፈ ሠላም፤የታፈነ ሠላም፤<br />
በቁጭትና በዝምታ የታጀበ ሠላም፤ በፍርሃት የታጨቀ ሠላም፤አደጋን ያረገዘ ሠላም! እንዲህ ዓይነት ሠላም<br />
ውጤቱ የከፋ ስለሚሆን አደጋ ነው፡፡ ጊዜውን ጠብቆ የሚፈነዳ ሠላም አንሻም፡፡ ጥፋትን በውስጡ አምቆ<br />
የያዘ “ሠላም” አያሻንም...<br />
4<br />
በጂማ ከተማ የተቃጠለው ውሃ ልማትና ዐቃቤ<br />
ህግ ጽ/ቤት አነጋጋሪ መሆኑ ተገለፀ<br />
11<br />
15<br />
1<br />
የሠራተኞችን ደሞዝ<br />
ለመቀማት ሲል 3ሰው ገድሎ<br />
2 ሰው ያቆሰለው ፖሊስ<br />
በቁጥጥር ሥር ዋለ<br />
በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ሰሜን ሸዋ ዞን<br />
የምትገኝኘው የያያ ወረዳ አስተዳደር ሠራተኞች<br />
የጥቅምት ወር ደሞዝ ለመዝረፍ ሦስት ሰው<br />
ገሎ ሁለት ሰው ያቆሰለው የወረዳው ፖሊስ<br />
በቁጥጥር ሥር መዋሉን የዜና ምንጮቻችን<br />
በተለይ ለፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ገለጹ፡፡ እንደ<br />
ዜና ምንጮቻችን ገለጻ ከሆነ “ጥቅምት 20<br />
ቀን 2004 ዓ.ም አንድ ሚሊዮን ብር ይሆናል<br />
የሚባለውን የወረዳውን የመንግስት ሠራተኖች<br />
ደሞዝ ለማምጣት ከወረዳው ፍቼ ከተማ ንግድ<br />
ባንክ ይመጣሉ፡፡ ግንዘቡን ለማምጣት የመጡት<br />
ሦስት ሠራተኞች አንድ ፖሊስና አንድ ሹፌር<br />
በጠቅላላ አምስት ሰዎች ....<br />
11<br />
www.andinet.org.et
2<br />
www.andinet.org.et<br />
የሙስና መስፋፋት<br />
በአንድ አገር ውስጥ በጥቅም ላይ<br />
ሊውል የሚገባውን መዋዕለ-ንዋይ<br />
(Investment) ይሸረሽረዋል። የውጭ<br />
አገር ከበርቴዎችንም ቢሆን በዚያ አገር<br />
የመዋዕለ-ንዋይ (Foreign Investment)<br />
ተግባር እንዳይሳተፉ ተጽዕኖ ያሳድራል።<br />
በዚህ ጉዳይ ላይ ብዙ ጥናቶች ያደረጉ<br />
ተመራማሪዎች ሲገልጹ “አንዳንድ<br />
ባለሃብቶች ወደ አንዳንድ አገሮች፤<br />
በተለይም ወደ አፍሪካ አገሮች ውስጥ<br />
ከሚያስገቡት የውጭ ምንዛሬና መዋዕለ-<br />
ንዋይ ይልቅ ከነዚህ አገሮች ወደ ሀብታም<br />
አገሮች በስርቆት መልክ የሚወጣው<br />
የውጭ ምንዛሬ ይበልጣል” ይላሉ።<br />
(ለምሳሌ በቅርቡ የአለም ባንክ ያወጣው<br />
ጥናታዊ ጽሁፍ ከኢትዮጵያ ተመዝብሮ<br />
ወደ ውጭ ሀገር እንዲሸሽ የተደረገው<br />
ሀብት/ገንዘብ እስከ 11 ቢሊዮን ዶላር<br />
እንደሚደርስ አሳይቷል። የተባበሩት<br />
መንግሥታትም እንደጎርጎረሳውያን<br />
አቆጣጠር ከ1990 ዓ/ም ጀምሮ<br />
ከኢትዮጵያ ወደ ውጭ ሀገሮች ተዘርፎ<br />
የጎረፈው ሀብት ከ8.3 ቢሊልዮን ዶላር<br />
እንደማያንስ አሳይቷል።) አንዳንድ<br />
አበዳሪዎችም በተመሳሳይ ሁኔታ “ያገር<br />
መሪዎች የሃገራቸውን ሃብት ወደውጭ<br />
የሚያሸሹ ከሆነ እኛ ምን ቸግሮን ነው<br />
ወደነዚህ አገሮች መዋዕለ-ንዋያችንን<br />
የምናስገባው?” የሚል ጥያቄ ያነሳሉ።<br />
ለአብነት ለመጥቀስ ያህል በ1997<br />
ዓ/ም በኢትዮጵያ የተካሄደው ምርጫ<br />
በህወሓት/ኢሕአዴግ ከከሸፈ በኋላ<br />
ከኢትዮጵያ ወደ እንግሊዝ አገር የጎረፉት<br />
ሃብቶች በጣም በዝተው እንደነበር<br />
አንዳንድ የእንግሊዝ የዜና ማሰራጫዎች<br />
አጋልጠዋል። በዚያው ሰሞን ሰሚ ያጡ<br />
አቤቱታዎች ከተለያዩ አቅጣጫዎች<br />
መነሳታቸው አልቀረም። ለምሳሌ እ.ኤ.አ.<br />
በ1997 World Development Report<br />
በተባለው መጽሄት ታትሞ የወጣው<br />
ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />
ጥናት ሲያመለክት እንደ ኢትዮጵያ<br />
በሙስና የተዘፈቁትና ሙስና ያላጠቃቸው<br />
አገሮች ሲወዳደሩ ሙስና ያጠቃቸው<br />
አገሮች በእድገት ወደ ኋላ መቅረታቸውን<br />
ዘግቧል፡፡ እንዲሁም በዚሁ አመት<br />
(National Bureau of Economic<br />
Research) ተብሎ በሚጠራው ጥናታዊ<br />
መጽሄት ያወጣው ጥናት እንደዘገበው<br />
ይህ ሁኔታ በሩቅ ምስራቅ የእስያ አገሮች<br />
እንደተከሰተ ዘግቧል።<br />
ሙስና እንደ ተጨማሪ<br />
ታክስም ስለሆነ የግል ተቋሞችና<br />
ኩባንያዎች እንዳያድጉ ያደርጋል።ሙስና<br />
በግል ተቋማትና በግለሰቦች መካከል<br />
መኖር የሚገባውን ጠቃሚ ውድድር<br />
ይቀንሳል፤ያጫጫል።<br />
ሙስና በጣት የሚቆጠሩ<br />
ሰዎች ብቻ ካለመጠን እንዲከብሩ<br />
ያደርግና በሃብታምና በድሆች መካከል<br />
ልዩነቶችና ቅራኔዎች ያስነሳል። ቅራኔው<br />
ሲገፋም ሀብታሞች ሕጋዊ ባልሆነ መልክ<br />
ያካበቷቸውን ሃብቶች ወደ ሌላ አገር<br />
እንዲያሸሹ ይገፋፋል። ይኸው ድርጊት<br />
በበኩሉ አገር ያራቁታል። ለምሳሌ የዛዬሩ/<br />
የኮንጎው ሞቡቱ ሴሴኮና የፊሊፒኑ<br />
ፈርድናንድ ማርቆስ በሥልጣን ላይ<br />
በነበሩበት ወቅት ያካበቷቸውና በውጭ<br />
አገር ባንኮች ያስቀመጧቸው ንብረቶች<br />
በብዙ ቢሊዮን ዶላር ይቆጠሩ ስለነበር<br />
ዛዬርም/ኮንጎም ሆነች ፊሊፒንስ ለብዙ<br />
ዓመታት የተከማቸባቸውን የውጭ<br />
ብድር በገዛ መሪዎቻቸው የተሰረቀው<br />
ገንዘብ ብድራቸውን ሁሉ ከፍሎ ከዕዳ ነጻ<br />
ሊያደርጋቸው እንደሚችል ተዘግቧል።<br />
ሙስና በአንዲት አገር ውስጥ<br />
የሚገኝን ሕጋዊና ትክክለኛ የንግድ ተግባር<br />
ያዛባል። የፍጆታ ዕቃዎች ትክክለኛ<br />
ዋጋ በተስተካከለ መልክ እንዳይተመን<br />
ያደርጋል። የሸቀጥ እቃዎች እንዲያንሱ<br />
ወይም እንዲጠፉ፤ ብሎም በጓዳ በር<br />
እንዲሸጡ መንገድ ይከፍታል። ዋጋቸው<br />
እንዲንር ያደርጋል፤ ቀስ በቀስም የፍጆታ<br />
ዕቃዎች ዋጋ በጣም ከፍ ይልና ህዝብን<br />
ያስቆጣል። በመንግስትና በነጋዴዎች<br />
መካከል አስፈላጊ ያልሆነ ጠብ እንዲፈጠር<br />
ያደርጋል። ባገራችንም ሆነ በሌሎች<br />
አገሮች እንደተከሰተው፤ መንግስት ነኝ ባዩ<br />
የራሱ መመሪያና ተግባር በፈጠረው ችግር<br />
ነጋዴዎች እንዲከሰሱና እንዲቀጡም<br />
ያደርጋል። በዚህ ምክንያት እንግልት፣<br />
እስርና ግድያ ሊከተል ይችላል። የፍጆታ<br />
ዕቃዎች ዋጋዎች ከፍ ሲሉ የፍጆታ<br />
ዕቃዎቹን ሊያገኙ የሚችሉ ሃብታሞችና<br />
ከነሱ ጋር ግንኙነት ያላቸው እንዲሁም<br />
ከሻጮች ጋር ዝምድና ያላቸው ብቻ<br />
ናቸው። ለዘመድና ለጓደኛ ብቻ መሸጥ<br />
ይመጣል። ሻጮች ዋጋ ከፍ አድርገው<br />
ለዘመዶቻቸውና ለጓደኞቻቸው ብቻ<br />
የመሸጣቸው ምክንያትም ለመንግስት<br />
አያጋልጡንም በሚል አስተሳሰብ<br />
ነው። ተራው ዜጋ በተለይም ድሀው<br />
የሕብረተሰብ ክፍል ግን ቁሳቁሶቹን<br />
እንዳያገኝ የገንዘብ አቅሙ የማይፈቅድለት<br />
በመሆኑ እንዲሁም ከሀብታሙም ሆነ<br />
ከሻጩ የሕብረተሰብ ከፍል ጋር የጠበቀ<br />
ግንኙነት ስለማይኖረው ሁሌም ተጎጂ<br />
ነው። እኒህን ዓይነት የሙስና ገጽታዎች<br />
በኢትዮጵያችን በጣም የተንሠራፉ<br />
ስለሆኑ ባንዳንድ ሰዎች አገላለጽ “በአገሪቱ<br />
ውስጥ ዛሬ የሚካሄደው ንግድ ከማፍያ<br />
ድርጊት የማይተናነስ ነው” ብለው<br />
እንደነ ሪፖርተር ያሉ ጋዜጦች ጭምር<br />
ያስገነዝባሉ። በማፍያ መልክ የሚሰራው<br />
ወንጀላዊ የንግድ አሠራር ከመብዛቱም<br />
የተነሣ በድብቅ መነገድና የጥቂቶች ብቻ<br />
መጠቃቀም ባህል ይሆናል፤ ኮንትሮባንድ<br />
ይስፋፋል፤ ዝርፊያ ይጧጧፋል፤<br />
ወንበዴዎች ይፈጠራሉ፤ ይባስ ብለውም<br />
ወንበዴዎች የራሣቸውን ኬላ ይፈጥራሉ፤<br />
እንዳሻቸው ይዘርፋሉ። የሚያሳዝነው ግን<br />
እነዚህን የመሰሉ ክስተቶች በአገራችን<br />
በሰፊው እየታዩ መሆናቸው ነው።<br />
ዳሰሳ<br />
2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />
የሙስና መስፋፋት በኢኮኖሚ፤በፖለቲካና በማህበራዊ ኑሮ<br />
ፕሮፌሰር ሰይድ ሐሰን<br />
መሪ ስቴት ዩኒቨርስቲ (አሜሪካ)<br />
ካለፈው የቀጠለ<br />
ዘርፍ የሚያስከትለው ችግር<br />
ሙስና ሰዎች በትጋት ሰርተው<br />
ሃብታቸውን እንዳያዳብሩ፤ ቤታቸውን<br />
እንዳያቀኑና አገራቸውን እንዳይገነቡ፤<br />
ባንፃሩ ግን ባቋራጭ የመክበር<br />
ፍላጎታቸው እንዲያድግ ያደርጋል። ዜጎች<br />
ለምርት ያላቸውን ዝግጁነት ይቀንሳል<br />
(It distorts incentives)። ይህ<br />
የሚሆንበት ምክንያቱ ብዙ ነው። ለምሳሌ<br />
በበርካታ አገሮች ውስጥ እንደታየውና<br />
እንደተከሰተው፤ ከሙስና ጋር የተሳሰሩ<br />
ድርጅቶችና የንግድ ተቋማት በመልካም<br />
መንገድ ሰርቶ መክበር አይችሉም።<br />
ሁሌም በሙስና መክበርን የሚመርጡ<br />
ናቸውና። ይህ ደግሞ ባኳያው በትክክልና<br />
በመልካም መንገድ ሥራቸውንና<br />
ሃብታቸውን ለማቃናት የሚጥሩትን ተስፋ<br />
ያስቆርጣል። ቀስ በቀስም በመልካም<br />
መንገድ የሚያካሂዱትን ሥራቸውን<br />
ለቀው ወደመጥፎ ጎዳና እንዲገፉ<br />
ይገደዳሉ፤ ብሎም እነሱም እንደሌሎቹ<br />
ጥቂት ገፋፊዎች በሙስናው እንዲሳተፉ<br />
ይገፋፋሉ። ይህ የስነ-ልቦና ለውጥ እያደር<br />
ለእንያንዳንዱ ዜጋ ይደርሰውና ቀስ በቀስ<br />
አገርና ዜጎች በሙስና ይጠመዳሉ።<br />
ቀደም ሲል ለመጠቆም<br />
እንደተሞከረው በታዳጊ አገሮች ብዙ<br />
መዋዕለ ንዋይ የለም፤ ይባስ ብሎ ያሉትም<br />
ሲዘረፉ ደግሞ አገሮቹ ለበለጠ ድህነት<br />
ይዳረጋሉ። ያገሮቹ ጥቂት ሃብቶች<br />
ወደተወስኑ ግለሰቦችና ድርጅቶች<br />
ወይም ቡድኖች ሲገቡ ደግሞ ያላግባብ<br />
በከበሩ ቡድኖችና በተራው ዜጋ መካከል<br />
መቃቃር ከመከተሉም በላይ የሀብቱ<br />
ልዩነት ይራራቅና ለግጭትና ለብጥብጥ<br />
ይዳርጋል። ይህ ሲሆን በሙስናና<br />
በብልጣብልጥነት የከበሩት አላግባብ<br />
መክበራቸውን ስለሚያውቁ አንደኛ<br />
ሃብታቸውን ሁለተኛ ራሳቸውንም<br />
ወደ ውጭ ማሸሽ ይከተላል። ይህ<br />
ተግባር በብዙ አገሮች ውስጥ የተከሰተና<br />
በኢትዮጵያችንም እያቆጠቆጠ ያለ አስፈሪ<br />
ክስተት ነው፤ መባባሱም አያጠራጥርም።<br />
በስልጣን የሚባልጉ<br />
ባለስልጣናትና የሙስና ተባባሪዎቻቸው<br />
ሃብት የሚያካብቱት ባቋራጭና በፍጥነት<br />
ስለሆነ፤ በፋሲካ የተዳረች ሁሌም ፋሲካ<br />
ይመስላታል ነውና፤ ሃብት ሁሉ በዚሁ<br />
መልክ የሚገኝና ምንጊዜም ሊተካ የሚችል<br />
አድርገው ስለሚቆጥሩ በፈጠነ መልክ<br />
ሃብታቸውን እንዲያባክኑ ይገፋፋሉ፤<br />
ይታለላሉ። ባጭር ጊዜ ውስጥ ያገር<br />
ሃብት የሚወድምበት አጋጣሚ ተፈጥሮም<br />
ሃገርና ዜጋ ያለረዳት ይቀራሉ።<br />
ብዙውን ጊዜ በሙስና<br />
የተበከሉ ሰዎች በሕገ-ወጥ መልክ<br />
ያካበቱትን ሀብት የሚያውሉት በድሎትና<br />
በቅምጥል (luxury) ዕቃዎች ላይ ነው።<br />
ከሚገዟቸው ቁሳቁሶች መካከልም፤<br />
ውድ የሆኑ መኪኖች፤ ጌጣጌጦች፤<br />
የቤት ማስጌጫዎች፤ መጠጥና ልብሶች<br />
ተጠቃሾች ናቸው። እንደነዚህ ያሉ<br />
እቃዎችም ባንድ በኩል አላቂና ግላዊ<br />
ስለሆኑ ላገር የሚያስገኙት ጥቅም እጅጉን<br />
ውሱን ነው። የቁሳቁሶቹ ዋጋ ከሌሎች<br />
ቁሳቁሶች ጋር ሲወዳደር ከፍ ስለሚልም<br />
የተገዙበት ንዋይ ተቀማጭ ወይም ታሳሪ
2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />
ዳሰሳ<br />
ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />
እንጂ ተንቀሳቃሽ ወይም በሃገር ኢኮኖሚ<br />
ውስጥ ተዘዋውሮ ተነግዶበት ለትርፍ<br />
የሚያበቃ አይደለም። በሌላ በኩል ይህ<br />
የተወሰነው የሙስና ተሳታፊ የህብረተሰብ<br />
ከፍል ብዙውን ጊዜ በውድ ቁሳቁሶችና<br />
ጌጣጌጦች በማሸብረቅ ፉክክር ተጠምዶ<br />
ስለሚቀር ለአጓጉል ባህል መጸነስ <strong>ምንጭ</strong><br />
መሆንም ይንጸባረቅበታል።<br />
በርከት ያሉ ጥናቶች<br />
እንዳመለከቱትም ቀልጣፋ ያልሆኑትንና<br />
ውጤታማ ያልሆኑትን (inefficient)<br />
ድርጅቶችን፤ አምራቾችንና ግለሰቦችን<br />
የበላይነት እንዲኖራቸው በማድረግ አገር<br />
ወደ ኋላ እንድትጎተት ያደርጋል።<br />
ሙስና የሕብረተሰብን ንብረት<br />
ወስዶ ለግለሰቦች ያስረክባል። ይህንን<br />
በማድረግም ከሁሉም ይበልጥ የድሀውን<br />
የህብረተሰብ ክፍል በበለጠ ይጎዳል።<br />
ከመንግስት ባለስልጣኖች ጋር ግንኙነት<br />
ያላቸው በሙስና የተዘፈቁት ግለሰቦች<br />
የሕዝቡን ሀብት ለግላቸው ሲያውሉት<br />
የትምህርት ቤት ተቋማትን ለማቋቋም፤<br />
የጤና ጥበቃ ጣቢያዎችን ለመመስረት፤<br />
ለአዉራ ጎዳናና መንገድ ሥራው ሥራዎች፤<br />
ለዉሃ ልማቶች፤ ወ.ዘ.ተ. ሊዉል የሚገባው<br />
ሀብት እንዲባክን ያደርጋል።<br />
ሙስና ከዉጭ አገር<br />
የሚገኘውን እርዳታ ውጤተ-ቢስ<br />
እንዲሆንና እንዲባክን ያደርጋል። ምንም<br />
እንኳ እርዳታው የሚላከው ለድሆች<br />
እንዲደርስ ቢሆንም፤ እርዳታው ለድሆች<br />
እንዳይደርስ፤ በርዳታው ገንዘብ እንዲሰሩ<br />
የተፈለጉት ተቋሞች እንዳይሰሩ ወይም<br />
ብልሹ በሆነ መልክ እንዲሰሩ ያደርጋል።<br />
እኔ እራሴ እንደተገነዘብኩትም፤ በገባያ ላይ<br />
እንዳይሸጡ የተከለከሉ የርዳታ እቃዎች<br />
ሕገ-ወጥ በሆነ መልክ እንዲሸጡ ያደርጋል።<br />
ለዚህ ዋቢም ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ<br />
የሚላከውን የምግብ ዘይት መጥቀስ<br />
ይበቃል።<br />
ፖለቲካንና መንግስታዊ አስተዳደርን<br />
በሚመለከት (በከፊል)፤<br />
ሙስና እየገነነ ሲመጣ በሃገር<br />
ዕድገት መስክ ጉልህ ሚና የሌላቸው በጣም<br />
ጥቂቶች እየከበሩ ይመጡና የመንግስትና<br />
የሕዝብ መገልገያ በሆኑ መሥሪያ ቤቶች<br />
በመስራት ብዙ ልምድ ያካበቱና ታማኝ<br />
የሆኑ፤ እንዲሁም ብቃት ያላቸው<br />
የቢሮ ሰራቶኞችን ሥራቸውን ለቀው<br />
እንዲወጡና ቀስ በቀስ ብቃት የሌላቸው<br />
በቦታው እንዲተኩ በር ይከፍታል።<br />
ይህም በሕዝብ መሥሪያ ቤቶች ውስጥ<br />
መልካም ባህርይና ችሎታ ያላቸው መሪዎች<br />
እንዳይበቅሉ ያደርጋል፤ የሃገርን የብቁ ዜጋ<br />
ቋት ያራቁታል። መድረሻ የለንም የሚሉ<br />
ቢኖሩም፡፡<br />
ሙስና ላገራቸውና<br />
ለህዝባቸው ተግተው የሚሰሩ ዜጎችንና<br />
ከፍተኛ የሙያ ትምህርት የቀሰሙ<br />
ሊሂቃንን ለሀገራቸው የሚያደርጉትን<br />
የአገልግሎት ፍላጎት የሚቀንስ ነው።<br />
ሙስናው እየበረታ ሲሄድም የመንግስት<br />
ሥራን እየለቀቁ፤ ለትምህርታቸው<br />
የከፈለላችውን ህዝብ እንደማገልገል<br />
ፋንታ፤የግል ባለህብቶችን/ኩባንያዎችን<br />
ለማገልገል ወይም የራሳቸውን የግል ንግድ<br />
እንዲፈጥሩ ይገፋፋል፤ያስገዳዳልም።<br />
ብዙዎች ባልሰለጠኑበት ሙያ እንዲሰማሩ<br />
እንደሚያስገድድም በብዙ አገሮች ውስጥ<br />
ታይቷል። በኢትዮጵያም እንደዚሁ ባስከፊ<br />
ሁኔታ እየተከሰተ ነው። እያደር ተስፋቸው<br />
እየተሟጠጠ አገራቸውን ጥለው እንዲሄዱ/<br />
እንዲሸሹ የሚገፉ ብዙዎች ለመሆናቸውም<br />
ጥርጥር የለውም። ይህ እየበረከተ ሲሄድ<br />
ደግሞ አገር ምሁር አልባ፤ አዕምሮ አልባ<br />
ትሆናለች። ብዙ ሃብት ጠፍቶ የሰለጠኑ<br />
ምሁራን ለሀብታም አገሮች ሲሳይ (braindrain)<br />
ይሆናሉ። ድሃ አገሮች ደክመውና<br />
ከፍለው ያሰለጠኑት አዕምሮ እየሸሻቸው፤<br />
ያሳደጉትን መሳም ያልቻሉ ደካሞች ሆነው<br />
እንዲታዩም ምክንያት ይሆናል። በአፍሪካ<br />
አህጉር ኢትዮጵያና ጋና በዚህ ረገድ ቀዳሚ<br />
ተጠቃሽ ናቸው። ቀጥተኛ የሆነ የፖለቲካ<br />
ችግር ተጨምሮበት አገራችን ዛሬ ማቆሚያ<br />
በሌለው መልክ የሰለጠነ የአእምሮ ሃብቷ<br />
እየተራቆተ ነው።<br />
በሌላ በኩል በሙስና ምክንያት<br />
ችሎታና ብቃት ያላቸው ባለሙያዎች<br />
ከመንግስታዊ መዋቅሮች ሲለቁ ቦታው ብቁ<br />
ችሎታ በሌላቸው ሰዎች እንዲሞላ ግድ<br />
ይሆናል። ይህም እየቆየ የመንግስት መሥሪያ<br />
ቤቶች እንዲጠሉ ያደርግና ቀስ በቀስ<br />
የመንግስት ትእዛዞች እንዳይከብሩ፤ ብሎም<br />
መንግስት ራሱ እንዲጠላ የራሱን አሉታዊ<br />
ሚና ይጫወታል። በህዝብ የሚጠላ<br />
መንግስት ደግሞ ሕዝባዊ ችግሮችን ሊፈታ<br />
የሚችል አይሆንም።<br />
በሙስና ምክንያት ሌብነት<br />
በዝቶ ድህነት ሲስፋፋ እያደር ዴሞክራሲም<br />
ደብዛው ይጠፋል። ዴሞክራሲ ሲጠፋም<br />
በኤኮኖሚ የማደግ እድል ይቀንሳል፣<br />
በሌላ በኩል በሙስና ምክንያት ችሎታና ብቃት ያላቸው<br />
ባለሙያዎች ከመንግስታዊ መዋቅሮች ሲለቁ ቦታው ብቁ ችሎታ<br />
በሌላቸው ሰዎች እንዲሞላ ግድ ይሆናል። ይህም እየቆየ የመንግስት<br />
መሥሪያ ቤቶች እንዲጠሉ ያደርግና ቀስ በቀስ የመንግስት ትእዛዞች<br />
እንዳይከብሩ፤ ብሎም መንግስት ራሱ እንዲጠላ የራሱን አሉታዊ<br />
ሚና ይጫወታል። በህዝብ የሚጠላ መንግስት ደግሞ ሕዝባዊ<br />
ችግሮችን ሊፈታ የሚችል አይሆንም።<br />
ድህነትንም ያንሰራፋል። የሰብዓዊና<br />
ሌሎችም ዴሞክራሲዊ መብቶች መታጣት<br />
በበኩሉ ለእርስ በርስ ጥልና ንክሻ<br />
ምክንያት ይሆናል። ይህ የሚንጸባረቅበት<br />
ህብረተሰብ ችግርና መከራ እንደ አዙሪት<br />
እየተሽከረከሩበት (vicious circle)<br />
ለመኖር ይገደዳል። ካዙሪቱም መውጣት<br />
አስቸጋሪ ይሆናል።<br />
ሙስና ሲስፋፋ በሥልጣን<br />
ላይ ያሉ ግለሰቦች በሙስናው ይሰክሩና<br />
ያጋልጡናል ብለው የሚፈሯቸውን<br />
ለምሳሌ እንደ ነፃ ፕሬስና ሌሎችም<br />
የሕዝብ መገናኛ ዘዴዎች ባለሙያዎችን<br />
እንዲሁም ንቁ የህብረተሰብ ክፍሎችን<br />
ማፈንና ማሳደድን ስራዬ ብለው ይይዛሉ።<br />
አፋኝ የሆኑ አዳዲስ ሕጎችን እያወጡ ነጻ<br />
አሰራሮችን ያግዳሉ፤ ጋዜጠኞችን ያስራሉ፤<br />
ያሰቃያሉ፤ ያዋክባሉ። በዚህም የተነሳ ነጻው<br />
ፕሬስና የሕዝብ መገናኛው መድረክ ሁሉ<br />
እያደር እየተዳከመ የተልፈሰፈሰ ይሆናል።<br />
ተልፈስፋሽ እንዲሆንም ፍላጎታቸውም፤<br />
ተግባራቸውም ነው። ይኸው ድርጊት<br />
ጠቅላላው ሕብረተሰብ እንዳያውቅ<br />
እንዳይማርና እንዳይጠይቅ ሆኖ የሰጡትን<br />
ብቻ ተቀባይና መስማት የተሳነው እንዲሆን<br />
ያደርጋል። በኢትዮጵያችን ይህ እየሆነ ያለ<br />
ክስተት ይሁን እንጂ ህዝቡ ይባስ ብሎ<br />
ከመንግሥት ለሚተላለፉ መመሪያዎችም<br />
ሆነ ዜናዎች ጆሮ ዳባ ልበስ ካለ ዓመታት<br />
ተቆጥረዋል። ይልቁንም ዕውነትን<br />
ፍለጋ በውጭ መገናኛ ብዙሃን ዘርፎች<br />
ለመጠቀም ተገዷል። ሕዝቡ መንግሥት<br />
ተብዬው ለሚያወጣቸው መመሪያዎች<br />
ቁብ የለውም፤ እንዲለግም የተገደደበት<br />
ሁኔታ ነው የሚታየው። በዚህ ዓይነትም<br />
ፖሊሲዎች በወረቀት ላይ ብቻ ይሆናሉ።<br />
ሕዝብና መንግስትም ሆድና ጀርባ እንደሆኑ<br />
ይቀራሉ።<br />
ማህበረሰባዊ ኑሮን በሚመለከት<br />
(በከፊል)፤<br />
ተደጋግሞ እንደተገለጸው<br />
ሙስና እጅጉን ሲስፋፋ በመንግስት<br />
መዋቅሮች ውስጥ የሚሰሩ በተለይም<br />
በንቃት ሃገራቸውን ሊያገለግሉ የተዘጋጁና<br />
ለስልጠናቸው ብዙ የተደከመባቸው<br />
ወገኖች አእምሯቸው እንዲላሽቅ<br />
ይደረጋል።<br />
ሙስና በትምህርት፤ በሥራ<br />
ልምድና በታታሪነት ኑሮን ከማዳበር<br />
ይልቅ፤ በጓዳና ባቋራጭ መንገድ የመክበር<br />
ፍላጎትንና፡ ስግብግብነትን የሚያበረታታ<br />
ስለሆነ ተጎጂው ሁሌም ንቁና ሀገሩን ወዳዱ<br />
ክፍል ነው። ሙስና ሁሉም ሊከብርና<br />
ኑሮውን ሊያቃና የሚችልበት ሳይሆን<br />
ጥቂቶች ያላግባብ የሚበለጽጉበት በመሆኑ<br />
“እድሉ” ያላጋጠመው አብዛኛው ሁሌም<br />
ብስጭት ላይ ይወድቃል። ኑሮውን<br />
ያማርራል፤ ተስፋ የቆረጠ የህብረተሰብ<br />
አባልን ያበረክታል። ተስፋ በቆረጠ ዜጋ<br />
ሀገር ሊያድግ ከቶውንም አይችልም።<br />
ሙስና በተለይ ድሆችን ጎጂ<br />
ነው፤ ድሆች እንኳን ጉቦ የሚከፍሉት<br />
ሊኖራቸው ቀርቶ ለራሳቸውም የሚበቃ<br />
ሃብት የላቸውምና!<br />
በሃይማኖት በኩልም ቢሆን፤<br />
ሙስና ከኃጢዓት (መቅሰፍት) የሚቆጠር<br />
እንጂ የሚያበረታታ አይደለም። በጉቦ<br />
የተለከፈ ሕብረተሰብ ብርቱ ሞራልና<br />
የወደፊት የረጅም ጊዜ የኑሮ ዕቅድ<br />
የለውም፤የዛሬን የከብሮ ማደር ብቻ ቀዳሚ<br />
ዓላማው ነውና። በሙስና የተጠመዱ ሰዎች<br />
አእምሯቸው ሁሌም የተረበሸና በጥቅም<br />
የተበረዘ በመሆኑ ቀስ በቀስ እንደተላላፊ<br />
በሽታ ሌሎቹንም የሚበክሉ ናቸው።<br />
ለዚህም ነው ሙስና እኩይ ወጥመድ<br />
ነው የሚባለው። በሙስና የተለከፉ ዜጎች<br />
ርህራሄ የጎደላቸውና ከምንም በላይ<br />
ጥቅማቸውን የሚያስቀድሙ በመሆናቸው<br />
የጋራ ሃገር ዕድገት እንቅፋቶች ናቸው።<br />
በሙስና የተጠመዱ ሰዎች ሁሉንም<br />
ለማግበስበስ በሚያደርጉት ሩጫ በተለይ<br />
ድሃው የህበረተሰብ ክፍል በመንግስት<br />
የዕለት ተዕለት አገልግሎቶች እንኳ ሳይቀር<br />
ተጠቃሚ እንዳይሆን የሚያደርጉ ጨካኞች<br />
ናቸው። ሙስና ራሱ ሃጢዓተኛ ነው<br />
የሚባለውም ለዚህ ነው።<br />
ሙስና የህብረተሰብ የእድገት<br />
መስኮችን ሁሉ ገቺና ወደፊት የማያራምድ<br />
ማነቆ ነው። ዕድገትን ሳይሆን ዝቅጠትን<br />
የሚያስከትል አደገኛ የህዝብና የሃገር ነቀርሳ<br />
ነው።<br />
ሙስና ወንጀለኞችን<br />
ያበራክታል፤ ብዙ ጊዜም ድሃ ዜጎች<br />
በሕይወታቸው ደስተኝነትን በማጣት<br />
ሳቢያ ህይወታቸውን እንዲያጠፉ ጭምር<br />
የሚገፋፋ ነው።<br />
3<br />
ሙስና በሰፈነበት አገር<br />
የኢኮኖምም፤ የፖለቲካም የማህበራዊ<br />
ኑሮም አዳዲስ ግኝቶችና ሀሳቦች ማፍለቅ<br />
የሚበረታታበት መድረክ ጎልቶ አይታይም።<br />
ስለሆነም ሙስና የማህበረሰባዊ ዕድገት<br />
ጠንቅ ነው።<br />
ሐ) መደምደሚያና ማጠቃለያ፤<br />
ዉድ ወገኖች፤ ሙስና የአንዲት<br />
አገር ኤኮኖሚን አቆርቋዥ፤ ባህልንና<br />
ሕብረተሰባዊ ትብብርን አኮላሽ፤ መንገሥት<br />
ለሕዝብና ለሃገር ሊያደርግ የሚገባውን<br />
አገልግሎት ቀናሽ ሥለሆነ ሁላችንም<br />
ልንዋጋው ይገባል።<br />
ሙስናን የሚያራምዱ በባህላቸው<br />
የዘቀጡና የባህል ድህነት ያጠቃቸው፤<br />
በተንኮለኝነት አስተሣሰብ የተዘፈቁ፤<br />
በሌብነትና በቀማኛነት የተለከፉ፤ የጥሩ<br />
ሥነ-ምግባር ድሃ የሆኑ፤ የሕብረተሰብንና<br />
ያገር ንብረትን አባካኝ/አጥፊ የሆኑ፤ፀረ-<br />
ሕዝብ ግለሰቦች ናቸው። በሙስና ወረርሽኝ<br />
የተለከፉ ግለሰቦች ከሕብረተሰቡ ጋር<br />
ያላቸው ንክኪም በጣም የበረከተ ስለሆነ<br />
በሽታውን ለጠቅላላው ሕብረተሰብ<br />
የማስፋፋትና የማስለከፍ ችሎታቸው<br />
ከፍተኛ ስለሆነም ከሥልጣናቸው መወገድ<br />
አለባቸው።<br />
በሙስና የተዘፍቁ አግሮች በኢኮኖሚም<br />
ሆነ በባሕል ወደ ኋላ የቀሩ መሆናቸው<br />
በብዙ ጥናቶች የተረጋገጠ ስለሆነ ይህ<br />
ችግር በኢትዮጵያችን በሚያስፈራ መልክ<br />
እያንሠራራ ስለሆነ ይህንን የነቀርሳ<br />
በሽታ ለመዋጋትና መንግሎ ለማውጣት<br />
መተባብር ያስፈልገናል። ከብዙ አገሮች<br />
የተገኘው ልምድ እንደሚያመለክተው ሁሉ<br />
ሙስናን ለመዋጋት በሙስና የተለከፉትን<br />
ግለሰቦች ማጋለጥና መንግሥት ሙስናን<br />
ለመዋጋት የማይተባበር ከሆነም፤ በሕቡዕ<br />
በመደራጀትና በመተባበር መዋጋትን፤<br />
በሙስና የተዘፈቁትንም በምስጢራዊ<br />
ሰነድ አዘጋጅቶ እንደአስፈላጊነቱ ማጋለጥ።<br />
እንደዚህ ያለው አስተዋፅዖና መልካም<br />
ምግባር፤ ለሙስናው መሥፋፋት<br />
ምክንያት የሆነው የአስተዳደር ብልሹነት<br />
እንዲፍረከረክ ያደርገዋል። ተጎጅው<br />
ሕዝብንም እስትንፋስ ይሰጠዋል።<br />
እንደሚታወቀው ባገራችን በኢትዮጵያ<br />
(በየክፍለ ሃገሩ፤ በየከተማው፤ በየንመደሩ፤<br />
በልዩ ልዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች፤<br />
ዱሮ በመንግስት ሥር በነበሩት አሁን ግን<br />
“ለግል ባለ ሀብቶች” በርካሽ በተቸረቸሩት<br />
ተቋማት መካከል፤በግል ሀብቶች መስክ፤<br />
….ወዘተ) ከሙስና ጋር የተያያዘው ችግርና<br />
የሚደረገው ደባ ተዘርዝሮ አያልቅም።<br />
ሙስናው የወረርሽኝ በሽታ ስለሆነ<br />
ከዘራፊዎቹ በስተቀር ሁሉንም ሰው<br />
ይጎዳል። ስለዚህ “የኔ ጉዳይ አይደለም”<br />
ተብሎ የሚተው መሆን የለበትም።<br />
እስካሁን ድረስ በኢትዮጵያ ሕዝብና<br />
በሀገሪቷ ላይ አሁንም እየተፈፀሙ ያሉትን<br />
በደሎችን ብሔራዊ ወንጀሎችን በቀጣይነት<br />
መመዝገብና ማጋለጥ አለብን። የዜግነትና<br />
የሰው ልጅነት ግዴታችንን እንድንወጣ አላህ<br />
(እግዚአብሔር) እንዲረዳን እማፀናለሁ!<br />
በመጨረሻም ሙስና ከሰው ጋር<br />
ያልተፈጠረ ክስተት ስለሆነ ያለጥርጥር<br />
እናሸንፈዋለን! በሙስና የተበከሉ<br />
ግለሰቦች፤ ቡድኖችና የመንግሥት<br />
ባለስልጣኖች የድሃውን ወገናችንን ደም<br />
መጣጭ መዥገሮች ናቸውና መወገድ<br />
አለባቸው!የሁለተኛው የሙስና ክፍል፤<br />
ማለት፤ የመንግሥቱን የሥልጣን አውታር፤<br />
አስተዳደሩን፤ ህጎቹን፤ ወ.ዘ.ተ. በመማረክ<br />
የሚገለፁ የሙስና ጠባዮች (state<br />
capture) በሌላ ጊዜ እስከማቀርብ ድረስ፤<br />
እስከዚያው አላህ ቸር ይበለን።<br />
www.andinet.org.et
4<br />
ፍኖተ -ነፃነት ጋዜጣ ሐምሌ 2ዐዐ3 ዓ.ም<br />
ተመሠረተ፡፡ ፍኖተ ነፃነት በአንድነት ለዴሞክራሲና<br />
ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሥር የሚታተም<br />
በፖለቲካዊ፣ በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ፣ በወቅታዊ ጉዳዮችና<br />
በመዝናኛ ላይ የሚያተኩር የፓርቲው ጋዜጣ ነው፡፡<br />
ጋዜጣችን እንደ ፓርቲ ልሳን ብቻ<br />
ሳይሆን እንደ አንድ ሚዛናዊ የግል<br />
ጋዜጣ ሆኖ ማገልገል ይፈልጋል<br />
የማንኛዉም ሰዉ ሀሳብና አመለካከት<br />
የሚስተናገድበትና የሚንሸራሸርበት<br />
እንዲሆን እንሻለን ሰፊ የሚዲያ<br />
ሽፋን ያለዉ ኢህአዴግም በዚህ ሚዲያ<br />
አቋሙንና ፖሊሲዉን ለማቅረብ ቢፈልግ<br />
ክፍት ነዉ<br />
ዋና አዘጋጅ፡-<br />
አንዳርጌ መሥፍን<br />
አድራሻ፡-<br />
የካ ክ/ከተማ ወረዳ 12<br />
የቤ.ቁ አዲስ<br />
አዘጋጆች፡-<br />
ብዙአየሁ ወንድሙ<br />
ብስራት ወ/ሚካኤል<br />
አምደኞች፡- ዶ/ር ኃይሉ አርዓያ<br />
ኢ/ር ዘለቀ ረዲ<br />
አንዱዓለም አራጌ<br />
ግርማ ሠይፉ<br />
ዳምጠው አለማየሁ<br />
ተስፋዬ ደጉ<br />
በላይ ፍቃደ<br />
ወንድሙ ኢብሳ<br />
ስለሞን ስዩም<br />
ኮምፒውተር ጽሑፍ፡-<br />
የሺ ሃብቴ<br />
ብርቱካን መንገሻ<br />
አከፋፋይ፡-<br />
ነብዩ ሞገስ<br />
አሣታሚው፡-<br />
አንድነት ለዴሞክሲና ለፍትህ ፓርቲ(አንድነት)<br />
አድራሻ፡- አራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 07 የቤ.ቁ አዲስ<br />
አታሚ፡- ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት<br />
አራዳ ክ/ከተማ ቀበሌ 07 የቤ.ቁ 984<br />
የዝግጅት ክፍሉ<br />
ስልክ +251 922 11 17 62<br />
+251 913 05 69 42<br />
+251 118-44 08 40<br />
+251 923 11 93 74<br />
ፖ.ሳ.ቁ፡ 4222<br />
ኢሜይል፡- udjparty@gmail.com<br />
andinet@andinet.org<br />
ፋክስ ቁጥር፡- +251-111226288<br />
www.andinet.org.et<br />
ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />
ርዕሰ አንቀፅ<br />
ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ<br />
ነፃ የሞያ ማህበራት ያስፈልጋሉ!<br />
አገራችን የመድበለ ፓርቲ ሥርዓትን ተቀብላ በሕገ-መንግሥትዋ ካፀደቀች 17 ዓመት ሞላት፡፡ ተግባራዊነቱና<br />
ዕድገቱን ስንመለከት ግን የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት መጀመሩም አጠያያቂ ነው፡፡ ሕገ-መንግሥቱ በተለያየ<br />
ጊዜ በአዋጆች እየተሸረሸረ ነው፡፡ ከፍተኛ የሆነ የሰብአዊ መብት ጥሰት ይፈፀማል፡፡ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት<br />
መገንቢያ ተቋማት ከማስመሰያነት አልዘለሉም፡፡ ዛሬ በአገራችን ነፃ የሲቪክ ድርጅቶች እና ነፃ የሞያ ማህበራት<br />
አሉ ማለት አይቻልም፡፡<br />
በአገራችን ረጅም ታሪክ ያለው የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማሕበር ነበር፡፡ ዛሬ የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማሕበር<br />
ኮንፌዴሬሽንም አለ፡፡ ግን ጥርስ የሌለው አንበሳ ነው፡፡ ከዚህ በፊት ለረጅም ጊዜ የኢትዮጵያ መምህራን ማሕበር<br />
ነበር፡፡ ዛሬም ለስሙ የመምህራን ማሕበር አለ፡፡ ቀደም ሲል ከ30 ዓመት በፊት የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ማሕበር<br />
ነበር፡፡ ዛሬም በቁጥር መብዛት ከሄድን አምስት የጋዜጠኞች ማሕበራት አሉ፡፡ የወጣቶች፣የሴቶች፣የመንፈሳዊ<br />
ድርጅቶች፣የተማሪ ማሕበሮች፣የሰብአዊ መብት ድርጅቶች፣ወ.ዘ.ተ. ነበሩ፡፡ ዛሬም አሉ፡፡ በስም ብቻ መኖራቸው<br />
ግን ፋይዳ የለውም፡፡<br />
ወደ ኋላ መለስ ብለን የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማህበርን በጥቂቱ እናስታውሰው፡፡ በእነ አበራ ገሙ መሪነት<br />
የሠራተኛውን መብትና ጥቅም ለማስከበር ያደረገው እንቅስቃሴ ለዛሬው ኢሠማኮ መፈጠር መሠረት ነው፡፡<br />
የምድር ባቡር ሠራተኞች ማህበር የትግል ታሪክን መጥቀስ ይቻላል፡፡ የሠራተኛውን መብት ለማስከበር ታግለዋል፡<br />
፡ ከነበረው የፊውዳሉ ሥርዓት ጋር ሠላማዊ ትግል አድርገዋል፡፡ መደራጀት መብት መሆኑን አረጋግጠዋል፡<br />
፡ ደርግ ሥልጣን እንደያዘ አካባቢም ቢሆን ቀላል የማይባል መስዋዕትነት ከፍለዋል፡፡ ደርግ ይከተለው<br />
በነበረው ወታደራዊ አመራር የሠራተኛው ተወካዮችና ግንባር ቀደም ተሟጋቾች የቀይ ሽብር ሠለባ ሆነዋል፡፡<br />
መስዋትነታቸው ለሠራተኛው መብትና ጥቅም ሲሉ ቢሆንም ለዛሬው ለመደራጀትም አስተዋጽኦ አድርገዋል፡፡<br />
ደርግ ሥርዓቱን ከተቆጣጠረ በኋላ የሠራተኛ ማህበሩን እንደ አንድ የመንግስት ተቋም እንዲያገለግል<br />
አድርጐታል፡፡ ኢህአዴግ አገሪቱን ከተቆጣጠረ በኋላም ማህበሩን በአዲስ መልክ ለማደራጀት ጥረት ተደርጐ<br />
ነበር፡፡ በዚሁ መሠረት በዘጠኝ ፌዴሬሽኖች የተደራጀው ማህበር የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማህበር ኮንፌዴሬሽን /<br />
ኢሠማኮ/ መሠረተ፡፡ ኢሠማኮ እንደተመሠረተ አካባቢ የሠራተኛውን መብትና ጥቅም የሚያስጠብቁ ጥያቄዎችን<br />
ማንሳት ሲጀምር፡፡ ኢህአዴግ ነፃ ማህበራት እንዳይኖሩ ርምጃ ወሰደ፡፡<br />
እነዚህ ድርጅቶች እያንዳንዳቸው ያሉት እንደ አንድ ነፃ የሲቪክ ድርጅት ወይም እንደ አንድ ነፃ የሞያ ማሕበር<br />
ወይስ እንደ አንድ የመንግሥት ተቋም እያገለገሉ ነው? ብለን ብንጠይቅ መልሱ አጭርና ግልፅ ነው፡፡ እንደ<br />
አንድ መንግሥት ተቋም ሆነው እያገለገሉ ነው ብለን እናምናለን፡፡ ኢመማ ወይም ሌሎች የሞያ ማህበራትንም<br />
ብንመለከት መልሱ ተመሳሳይ ነው፡፡ ምክንያቱም የማሕበሩን አባላት መብትና ጥቅም የሚያስከብር፣በነፃ ምርጫ<br />
በማሕበሩ አባላት ተመርጠው ወደ አመራር በሚመጡ አመራሮች የሚመራ ሳይሆን በድርጅታዊ አሠራርና<br />
ተጽዕኖ ባለበት ምርጫ የሚቋቋሙ አመራሮች ያሉበት ተቋም ሆኖ ይገኛል፡፡ ሥራ አፈጻጸሙም የማሕበሩ አባላት<br />
የሚያነሱዋቸውን ጥያቄዎች በማፈን የሚቆጣጠር ዋና ኃይል ሆኖ የሚያገለግል ነው፡፡ አመራሮቹም ለሞያቸው<br />
ክብር የሚሰጡ፣ለወከሉት ሠራተኛ የቆሙ ሳይሆኑ በአፍቃሬ ኢህአዴግነት ለኢህአዴግ ታማኝ በመሆናቸው<br />
ክብር የሚሰማቸው ናቸው፡፡<br />
የሥርዓቱ ገዢዎች በተደጋጋሚ ሲናገሩ እንደምንሰማው የሠራተኛውን መብትና ጥቅም ለማፈን “ኢንዱስትሪ<br />
ሰላም ነው” ሲሉ ይደመጣሉ፡፡ የማሕበራት ተወካዮችም ይህንኑ ቃል በተደጋጋሚ ያስተጋባሉ፡፡ “የኢንዱስትሪ<br />
ሠላም” ምን ዓይነት ነው? የሠራተኛውን መብትና ጥቅም ወደ ጐን ትቶ የአሠሪውን ጥቅም ብቻ ያስከበረና<br />
የገዢውን የሥልጣን ጥቅም ለማስጠበቅ የታለመ ነው ወይንስ የሠራተኛውን መብትና ጥቅም የሚያስከብር?<br />
መልሱ ሠራተኛው የሥራ ዋስትና አጥቶ ሲበተን የህብረት ስምምነቱ እየተጣሰ መብቱና ጥቅሙ ሲነፈግ፤ ፍትህ<br />
አገኛለሁ ብሎ በየፍ/ቤቱ ሲጉላላ ማህበሩ ዝምታን መርጧል:: በመሆኑም የኢሕአዴግ የእድሜ ክር ቀጣይ እንጂ<br />
የሠራተኛውን መብትና ጥቅም የሚጠብቅ አይደለም፡፡ የይስሙላ “የኢንዱስትሪ ሰላም ነው”<br />
የኢንዱስትሪ ሰላምን በሁለት ከፍሎ ማየት ይቻላል፡፡ ጊዜያዊ ሠላምና ዘላቂ ሠላም ናቸው፡፡ ጊዜያዊ<br />
የኢንዱስትሪ ሠላም የማስመሰያ /አሳሳች/ ሠላም ነው፡፡ የሠራተኛውን ልብ ያልገዛ /የሠራተኛውን ጥቅም<br />
ያልጠበቀ/፣አስተማማኝና ዘላቂ ልማትን የማያመጣ ሠላም ነው፡፡ የመፍጠር ችሎታን የማያበረታታና<br />
ምርታማነትን የማያሳድግ ሠላም ነው፡፡ ዘላቂ የኢንዱስትሪ ሠላም ግን የሠራተኛውን ጥቅምና መብትን<br />
የሚያስከብር፣በሠራተኛው ውስጥ በራስ መተማመንንና መረጋጋትን የሚፈጥር፣የሠራተኛውን የኃላፊነት ስሜት<br />
የሚያስከብር ነው፡፡ ሊኖር የሚገባው ጊዜያዊ ሳይሆን ዘላቂ የኢንዱስትሪ ሠላም ነው፡፡ በሀቅ ላይ የተመሠረተ<br />
ከሆነ የኢንዱስትሪ ሠላም ጥሩ ነው፡፡ ሠላም የሕይወትና የንብረት ዋስትና ይሰጣል፡፡ ሠላም ካለ ልማትና እድገት<br />
አለ፡፡ ሠላም ካለ ቤተሰብ በሰላም ወጥቶ ሠርቶ ይገባል፡፡ ሠላም ከሌለ ሁሉም የለም፡፡ ዛሬ ያለው ሰላም ግን ምን<br />
ዓይነት ሠላም ነው? መብትና ጥቅምን የገፈፈ ሠላም፤የታፈነ ሠላም፤ በቁጭትና በዝምታ የታጀበ ሠላም፤ በፍርሃት<br />
የታጨቀ ሠላም፤አደጋን ያረገዘ ሠላም! እንዲህ ዓይነት ሠላም ውጤቱ የከፋ ስለሚሆን አደጋ ነው፡፡ ጊዜውን<br />
ጠብቆ የሚፈነዳ ሠላም አንሻም፡፡ ጥፋትን በውስጡ አምቆ የያዘ “ሠላም” አያሻንም!<br />
የሚያስፈልገን ሠላም ክፋትንና ጭንቀትን ያስወገደ፣ የዜጐችን መብትና ጥቅም ያስከበረ ሠላም ነው፡፡<br />
የሠራተኛውንና የባለሀብቱን መብትና ጥቅም ፍትሐዊ ያደረገ ሠላም እንሻለን፡፡ የሞያ ማሕበራት የመንግሥት<br />
ጣልቃ ገብነትና ተጽዕኖ የሌለባቸው፣የሥራ ብቻ ሣይሆን ነፃ የምርምር ተቋማት መሆን አለባቸው፡፡ ማህበራት<br />
በነጻነት መደራጀት መቻል አለባቸው፡፡ ይህ እስካልሆነና የማሕብራቱን አባላት መብት እስካላስጠበቀ ድረስ<br />
ኢህአዴግ የሚፈልገው የኢንዱስትሪ ሠላምና የሚመኘው ዕድገት ዘላቂነት አይኖረውም፡፡<br />
የተደራጁት ማሕበራት የአባሎቻቸውን መብት ማስከበር መቻል አለባቸው፡፡ መብታቸውንና ጥቅማቸውን<br />
በመጠየቃቸው አሠሪው ኃይልና መንግሥት በጋራ ሆነው ሠራተኛው ላይ የበቀል ጥቃት ማድረስ መቆም አለበት<br />
ብለን እናምናለን፡፡ ለዚህ ምሳሌ የሚሆነን በዋልዳ ሆጀቶታ ዳንዲ ደራርቱ አርሲ (W H D D A) የቻይና<br />
ሠራተኞች ማሕበር ሠራተኞችና የማሕበሩ አመራሮች ላይ የተወሰደውን ሠራተኞችን ማሰቃየትና የማኅበሩን<br />
የአመራር አባላት የሠራተኛውን መብት እንዳይጠይቁና እንዳያስከብሩ ከሥራቸው በማፈናቀል የተወሰደውን<br />
እርምጃ በጥብቅ እናወግዛለን፡፡ በሌላ በኩልም ጥቃቱም እንዲቆም እንጠይቃለን፡፡ ለደረሰባቸው ጥቃት ካሳ<br />
እንዲከፈላቸው፣ሕክምና እንዲያገኙና መብትና ጥቅማቸው እንዲከበር የሚመለከተው ሁሉ እንዲረባረብ<br />
ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡ እንዲሁም የመደራጀት ጥያቄ አቅርበው የተከለከሉ 120 ሺ መምህራን ጥያቄአቸው<br />
በአግባቡ ሊመለስላቸው ይገባል፡፡<br />
የኢህአዴግ መንግሥት እጁን ከማሕበራት ላይ ያንሳ፡፡ ማሕበራት የመጨቆኛና የማፈኛ ተቋማት መሆን<br />
የለባቸውም ብለን እናምናለን፡፡ በአገሪቱ አስተማማኝ የኢንዱስትሪ ሠላም ኢንዲመጣ ከተፈለገ ሞያ ማህበራት<br />
በነጻነት መደራጀት አለባቸው፡፡ ማህበራት የሠራተኛውን መብትና ጥቅም የማስጠበቅ አቅም ሊኖራቸው<br />
ይገባል፡፡ ጥቅማ ጥቅሞቻቸው መጠበቅ አለባቸው፡፡ የሠራተኛው ሞያዊ አቅምና ሥነልቦና መገንባት አለበት፡<br />
፡ ጠንካራ የሠራተኛ ተወካዮችን ከሥራ ገበታቸው ላይ ማፈናቀልና ለጥቃት መዳረግ የለባቸውም፡፡ ይህ አይነቱ<br />
ሠይጣናዊ ርምጃ በአስቸኳይ መቆም አለበት፡፡ ካልቻለ ግን እንደ አንድነት በአጅጉ ያሳስበናል፡፡ የሞያ ማህበራት<br />
የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ መሠረት ናቸው ብለን እናምናለን፡፡ የሞያ ማህበራት በአገሪቱ ፖለቲካዊ<br />
ኢኮኖሚያዊና ማሕበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል፡፡ የማሕበር አባሎቻቸውን መብትና ጥቅም<br />
አሳልፈው ሰጥተው የመጨቆኛ መሳሪያ፤ የሰብዓዊና የዴሞክራሲያዊ መብት ጥሰት ተባባሪ መሆን የለባቸውም፡<br />
፡ የተቋቋሙለትን ዓላማ በተቃራኒው መፈፀም ነው ብለን እናምናለን፡፡ በመጨረሻም ለመድበለ ፓርቲ ሥርዓትና<br />
ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ መጠናከር ነፃ የሞያ ማህበራት በእጅጉ ስለሚያስፈልጉ እነዚህ ማኅበራት<br />
ከኢሕአዴግ የተፅዕኖ ቀንበር ነፃ እንዲወጡ አብረን እንታገል፡፡<br />
ጋዜጣችን “ፍኖተ-ነፃነት” ብለናታል፡፡ “ፍኖት” ማለት መንገድ ማለት ሲሆን ከነፃነት ጋር<br />
ሲጣመር “የነፃነት መንገድ” ማለት ነው!!<br />
ነፃ አስተየት<br />
ታደሰ ፍስሐ<br />
ለማን አቤት<br />
እንበል?<br />
2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />
ኢትዮጵያውያን ብዙ ጮኽን ያዳመጠን ግን የለም፡<br />
፡ ለሰው ጩኽን፤ ለፈጣሪ ጩኽን፤ ለመሬትም ጮህን፤<br />
አንዳች ምላሽ በመሻት፤ ጩኽታችን ግን ለሠማይና<br />
ለምድርም ጮህን፤ ጩኸታችን ግን የቁራ ጩኽት ሆኖ ቀረ፡፡<br />
የተፈረደብን የመከራ ዘመን ከማለቅ ወይ ከመገባደድ ይልቅ<br />
እየጨመረ ሄደ፡፡<br />
በግልፅ የሚታየውን ችግራችንን፣ ከፊታችን ሳይቀር<br />
የሚነበበው ጉስቁልናችን፣ ሚሊዮኖችን ምርኮኝ ያደረገ<br />
ርሃባችን፣ ፀሐይ የሞቀው የርስበርስ ፍጅታችንን ደመናን<br />
ቀርቶ የጎጇችንን ጣሪያ ማለፍ የተሳነው ምህላና ፀሎታችን<br />
ብዙዎች በየቀኑ ሽቅብ የምንረጨው እንባችን፤ ሁሉም<br />
በማንም ዘንድ ተሰሚነት አላገኘም፡፡ አሁንም ለቅሶና<br />
ዋይታችን ተባብሶ እንደቀጠለ ነው፡፡<br />
ተንኮለኞች ያጠመዱትን ወጥመድ የደገሱልን መከራና<br />
የሰቆቃ ድግስ ከዘመናት በፊት በሴራ መክረው ያወጁብን<br />
የጥፋት ዘመን በብሄርና በጎሳ ከፋፍለው የኢትዮጵያን<br />
አንድነት ለመነጣጠል በመካከላችን የከተቱብን የተኩላ<br />
መንጋ ሁሉም እንዳሰቡት ሆኖ ትንቢታቸው ሲይዝላቸውና<br />
ምኞታቸው ሲሳካላቸው በስቃያችን ይደሰታሉ፡፡ በቁስላችን<br />
የጋለ ብረት እየሰደዱ ለቅሷችንን እንደ ጥጋብ፣ ጭንቀት<br />
ጥበታችንን እንደ ደስታ፣ ጦርነታችንን እንደ መዝናኛ፣<br />
መባዘናችንን እንደ በረከት፣ የርስ በርስ እልቂታችንን<br />
እንደሰላም በመቁጠር ያላግጡብናል፡፡ እውነቱን የማያውቁ<br />
ይመስል የላኳቸውን እንደራሴዎች የሚሰሩትን የማይረዱ<br />
ይመስል፡፡ የእኛን መከራና ችግር እንደማያውቁ ሆነው<br />
በመቆለል በጣት የሚቆጠሩ የተሻለ ኑሮ የሚኖሩ በገጠር<br />
በግብርና የሚተዳደሩትን ከተማ ያሉ ሃብታችን በመመልከት<br />
ብቻ ጥሩ ኑሮ ላይ ነን ይላሉ፡፡ እነዚያም ተቀብለው<br />
“ይኽ መቸ አነሳችሁ፤ ጥሩ ኑሮ እየኖራችሁ ነው” በማለት<br />
ይሳለቁብናል፡፡<br />
ጥቂት የምትባል የመናገር፣ የመፃፍ ግድብ (ዴሞክራሲ)<br />
መብት በማየት ብቻ ዴሞክራሲያችን እዚህ ደርሷል<br />
በማለት አዎንታዊ አብነት ወስደው ከእኛ አልፈው<br />
ለሌሎች አገሮች ማስተማሪያ ሊሆን እንደሚገባ ይሰብካሉ፡<br />
፡ ይህ ድርጊታቸው በዴሞክራሲ ላይ ብቻ ሳይሆን በሰው<br />
ልጆችም ላይ እንደማፌዝ የሚቆጠር ከመሆኑም በተጨማሪ<br />
ለይስሙላ ያህል በውሸት በሚያመልኩት በእግዚአብሄርም<br />
ዘንድ በእጅጉ አስነዋሪና ሃጢያት መሆኑን ሊገነዘቡት<br />
ይገባቸው ነበር፡፡ ፈጣሪ የሰውን ልጅ በቀለምና በዘር<br />
በስልጣኔና በመልካም ምድር ልዩነት እየፈጠራችሁ ተፋጁ<br />
(አፋጁ) አላለም፡፡ ከዚህ ነጥብ አኳያ ተምረዋል የተባሉት<br />
አማረዋል፡፡ እነዚህ ወገኖች እየሰሩት ያለው ግፍና በደል<br />
ሲጤን መሰልጠናቸው ሳይሆን መስይጤናቸውንና ፀረ<br />
ሰውም፣ ፀረ ፈጣሪም መሆናቸውን የሚያሳይ ነው፡፡<br />
ሀገራዊም ሆነ አለም አቀፋዊ ሁኔታዎች ለእኛ<br />
ለኢትዮጵያውያን የሚመቹ ባለመሆናቸው ተናግረን<br />
የምንደመጥበት፣ አኩርፈን የምንጠጋበት፣ ፍትህን<br />
የምናገኝበት አንድም አለኝታ የለንም፡፡ ሁሉም ነገር<br />
ያዘነበለው ወደ ገዢዎቻችን በመሆኑ የችግራችን መጠን<br />
ስፋትና ጥልቀት ተነግሮ አያልቅም፡፡ ፈጣሪ ጭምር አስጨናቂ<br />
ዘመን እንድንገፋ የፈረደብን ይመስላል፡፡ ከታሰርንበት<br />
የኑሮ ሰንሰለት ከገባንበት ምድራዊ ሲኦል ነበልባላዊ እቶን<br />
የሚታደገን ከቶ ማነው? ዳዊት በመዝሙሩ አቤቱ ጌታ ሆይ<br />
እስከመቼ ነው የምትተወኝ ያለው ወዶ አይደለም፡፡ እንደኛ<br />
ክፉኛ ቢጨንቀው እንጂ፡፡ በርግጥ መከራ ሲበዛ ያነሆልላል፤<br />
ስቃይ ሲበዛ መፈጠርን ያስረግማል፤ ግፍና በደል ከአንድ<br />
ሰው የመሸከም አቅም ሲያልፍ ራስን ብቻ ሳይሆን ፍጣሪን<br />
ድረስ ሊያስክድ ይደርሳል፡፡<br />
ምንም እንኳን “እረኛ ቢያኮርፍ ምሳው እራት ይሆነዋል”<br />
እንዲሉ አኩራፊ ቢያኮርፍ ከራሱ በላይ የሚጎዳው<br />
ባይኖርም የችግሩ ክረት ፈጣሪን እስከ መውቀስ ቢያደርሰው<br />
ቢያንስ ሊያስነውረው የሚገባ አይመስለኝም፡፡ በክርስቲያኑ<br />
ህይወት እንግልትና የቁም ስቅልን የሚያሳይ አሳር ሲገጥም<br />
በመፅናናት የሚጠቀስ አንድ መፅሐፍ ቅዱሳዊ ምሳሌ ነው፡<br />
፡ የኢዮብ ስቃይ ከእኛ ከኢትዮጵያውያን ስቃይ ማወዳደር<br />
የሚቻል አይመስለኝም፡፡ ለዘመንም ሆነ ከሌሎች መሰል<br />
ፖለቲካዊና ሃይማኖታዊ ችግሮች አንፃር የኢዮብን ከእኛ<br />
አስቸጋሪ ህይወት ላነፃፅር አልችልም፡፡<br />
የመከራ ዶፍ የወረደበት ኢዮብ በደረሰበት ስቃይ<br />
ሰማይ ምድሩ ተደፍቶበት ጭንቅ ውስጥ በነበረበት ወቅት<br />
ከተናገረው ጥቂት እናስታውስና እኛ ከተዘፈቅንበት የችግር<br />
ማጥ አኳያ ብሶት ምን ያህል እንደሚያናግር እንመልከት፡፡<br />
ከችግርና ከረሃብ ብዛት የተነሳ በለሊት ተነስተው ወደ<br />
በረሃ እየሄዱ<br />
ስራ ስሮችን ያኝኩ ነበር፡፡<br />
ጨው ጨው የሚል የበርሃ ቅጠላ ቅጠሎን ይለቅሙ<br />
ነበር፡፡<br />
ሰዎች ሌቦችን እየጮሁ እንደሚያባርሩ<br />
እነርሱም ከህብረተሰቡ መካከል ያባርሯቸው ነበር፡፡<br />
መኖሪያቸውም በየዋሻውና በየገደሉ ስር በተቆፈረ<br />
ጉድጓድ ውስጥ ነበር፡፡<br />
ወደ 10 ዞሯል
2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />
ፖለቲካ<br />
ግርማ ሞገስ<br />
(girmamoges1@gmail.com)<br />
ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />
የዚህ ጽሑፍ ግብ የሰላም ትግል<br />
ለውጥ ማምጫ መንገዶች (Mechanisms<br />
of change) በኢትዮጵያ እንዴት ህዝብን<br />
የመንግስት ስልጣን ባለቤት ሊያደርጉ<br />
እንደሚችሉ በማጥናት በኢትዮጵያ የፖለቲካ<br />
ትግል እና የመንግስት ሽግግር ለማድረግ<br />
ሰላማዊ ትግል ማደረግ እንደሚቻል እና<br />
ተመራጩ የትግል ስልትም እሱ መሆኑን<br />
ማሳየት ነው።<br />
የሰላም ትግላችን ግብ ህዝብን የመንግስት<br />
ስልጣን ባለቤት ማድረግ ነው። ህዝብን<br />
የመንግስት ስልጣን ባለቤት ለማድረግ የሰላም<br />
ትግል በህዝብ እና በአምባገነን መንግስት<br />
መካከል የሚገኘውን የፖለቲካ ኃይል ሚዛን<br />
ግንኙነት ወደ ህዝብ እንዲያደላ ማድረግ<br />
አለበት። የሰላም ትግል ይኽን አስፈላጊ<br />
የሆነ የፖለቲካ ኃይል ሚዛን ግንኙነት<br />
ሽግሽግ (ለውጥ) ተፈጻሚ የሚያደርገው<br />
በአራት መንገዶች እንደሆነ ጅን ሻርፕ<br />
(Gene Sharp) አጥንቶ ለአለም የዲሞክራሲ<br />
ኃይሎች እና ተመራማሪዎች ካበረከተ<br />
ውሎ አድሯል። እነሱም፥ (1ኛ) የመቀየር/<br />
የመለወጥ (Peaceful conversion)፣ (2ኛ)<br />
የመቻቻል (accommodation)፣ (3ኛ)<br />
ሰላማዊ አስገዳጅነት (Peaceful coercion)<br />
እና (4ኛ) ሰላማዊ መፈረካከስ/መበታተን<br />
(Peaceful disintegration) የተባሉት<br />
ናቸው። እነዚህ ሰላማዊ ለውጥ ማምጫ<br />
መንገዶች ከሰላም ትግል መሳሪያዎች ጋር<br />
ዝምድና አላቸው። የሰላም ትግል መሳሪያዎች<br />
ሶስቱ አብይ ክፍሎች (1ኛ) ተቃውሞ እና<br />
ማግባባት (Protest and Persuasion)<br />
እስከዚኽ ድረስ እንዳየነው መቀየር/መለወጥ (Peaceful<br />
conversion) የተባለውን የለውጥ ማምጫ መንገድ ፕላን ቀይሰን<br />
በአግባብ እና በቀጣይነት ከተጠቀምንበት የዲሞክራሲ ትግልን በህብረተሰቡ ውስጥ<br />
ለማስፋፋት እና የህብረተሰቡን የሰላማዊ ትግል አቅምን ለመገንባት ይጠቅማል።<br />
ነገር ግን ይኽ ለውጥ የማምጫ ሰላማዊ መንገድ በአምባገነኖች የፖለቲካ ኃይል<br />
ምንጮች ላይ የሚያደርሰው ቀጥተኛ ጥቃት የለም። ጥቃቱ ተዘዋዋሪ ነው። ለጥቀን<br />
መቻቻል የተባለውን ለውጥ ማምጫ መንገድ እንመልከት።<br />
የሠላም ትግል ለውጥ ማምጫ አማራጭ<br />
መንገዶች በኢትዮጵያ<br />
፣ (2ኛ) ትብብር መንፈግ (noncooperation)<br />
፣ (3ኛ) ጣልቃ መግባት<br />
(intervention) እንደሆኑ እና ዝርዝራቸው<br />
ወደ 200 ግድም እንደሚደርስ በፍኖተ ነፃነት<br />
ቁጥር 13 “የሰላም ትግል መሳሪያዎች” በሚል<br />
ርዕስ ቀርቧል። እነዚኽ አራት ለውጥ ማምጫ<br />
መንገዶች ከሰላማዊ ትግል አቅም ግንባታ<br />
አንስቶ እስከ መንግስት ሽግግር ፍጻሜ ድረስ<br />
እንዴት አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉ ባጭር<br />
ባጭሩ እንመልከት።<br />
(1ኛ) መቀየር/መለወጥ (Peaceful<br />
conversion)<br />
የዲሞክራሲ ኃይሎች ያቀረቡትን የለውጥ<br />
አሳብ ወይንም የለውጥ ጥያቄ መንግስት<br />
ቢቀበል እሱም ተጠቃሚ ሊሆን እንደሚችል<br />
መንግስትን ማሳመን (መቀየር/መለወጥ)<br />
የሚቻልበት ሁኔታዎች (መንገዶች) ሊኖሩ<br />
ይችላሉ። ይኽን በማድረግ የዲሞክራሲ<br />
ኃይሎች ከሚያገኙዋቸው ፋይዳዎች ውስጥ<br />
ጥቂቱ፥ በህዝብ እና በመንግስት ዘንድ<br />
የተቃዋሚ መሪዎችን ህጋዊነት ከፍ ማድረግ፣<br />
ከመንግስት ጋር ሊደረጉ የሚችሉ ግጭቶችን<br />
መቀነስ፣ የሰላማዊ ትግልን የሰው እና የቁሳቁስ<br />
አቅም በረባ ባልረባው ሁሉ እንዳይባክን<br />
ማድረግ ናቸው።<br />
ርግጥ ይኽ መንገድ በመንግስት ላይ<br />
የሚያሳድረው ጫና (ክብደት) በጣም<br />
ዝቅተኛ በመሆኑ የሚያስገኘው ጠቀሜታ<br />
እዚህ ግባ የማይባል ሊሆን ይችላል።<br />
ያም ሆኖ ግን የተመረጠው የለውጥ ጥያቄ<br />
የአምባገነኖችን ስልጣን አደጋ ላይ የማይጥል<br />
እና የጥያቄው አቀራረብ ብልህ እስከሆነ<br />
ድረስ አልፎ አልፎም ቢሆን ጠቃሚ<br />
ውጤት አይገኝም ማለት ያስቸግራል።<br />
ለውጥ የተገኘበት ጊዜ አለ። ምሳሌ፥ እንደ<br />
አውሮፓ አቆጣጠር በ1962 ዓመተ ምህረት<br />
ቀድሞ የእንግሊዝ ቅኝ አገር በነበረችው<br />
በርማ ውስጥ በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን<br />
ላይ የወጣው ወታደራዊ አምባገነን ቡድን<br />
መጀመሪያ ከያዘው አቅዋም ከጊዜ በኋላ<br />
እንዴት እንደተለወጠ እንመልከት።<br />
ስልጣን እንደጨበጠ፣ የእንግሊዘኛ<br />
ቋንቋ ትምህርት በአንደኛ ደረጃ እንዳይሰጥ<br />
አደረገ። በዩንቨርስቲ ደረጃም የሚሰጥ<br />
የእንግሊዘኛ ቋንቋ ዝቅ እንዲል አደረገ።<br />
ወታደራዊው መንግስት ለህዝብ የሰጠው<br />
ሃሰተኛ ምክንያት “እንግሊዘኛ ቋንቋ የቅኝ<br />
ግዛት ዘመን ውርደታችን ማስታወሻ በመሆኑ<br />
መወገድ አለበት” የሚል ሲሆን ሃቀኛው<br />
ምክንያት ግን በመምህርነት ስራ የተሰማሩትን<br />
እና ኗሪ እንግሊዞችን ከአገር በማስወጣት<br />
የበርማን ህዝብ ከውጪው አለም ፖለቲካ<br />
ተጽእኖ ለማፈን (Censorship) ነበር። ይኽ<br />
ፖሊሲ የበርማ ተማሪዎችም ወደ ምዕራቡ<br />
አለም እንደቀድሞው እንደልብ እየወጡ<br />
ከፍተኛ ትምህርት ለመማር በቅድሚያ<br />
ማለፍ ያለባቸውን የእንግሊዘኛ ቋንቋ ፈተና<br />
ማለፍ እንዳይችሉ ማድረግ ጀመረ። በበርማ<br />
እንግሊዘኛ ቋንቋ መናገር የሚችሉ ተወላጅ<br />
የቢሮ አስተዳዳሪዎች ማግኘት አስቸጋሪ<br />
መሆን በመጀመሩ የውጭ አገር ኢንቨስተሮች<br />
ወደ በርማ መምጣት አቆሙ። የአገሪቱ<br />
ኢኮኖሚ ተንኮታኮተ። በዚኽ አይነት<br />
ለስልጣኑ መጠናከር ሲል ለ20 አመቶች<br />
ያህል አለም አቀፍ የቢዝነስ እና የንግድ<br />
ቋንቋ በበርማ እንዲዳከም ካደረገ በኋላ ይኽ<br />
ፖሊሲ በአገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ያስከተለው<br />
አሉታዊ ተጽእኖ ለአምባገነኖቹ ገዢዎች<br />
ወለል ብሎ ይታያቸው ጀመረ። የበርማ<br />
የንግዱ ማህበረሰብ እና የዲሞክራሲ ኃይሎች<br />
በእንግሊዘኛ ቋንቋ ትምህርት ላይ የተጣለው<br />
ገደብ እንዲነሳ ያቀርቡት የነበረውን የለውጥ<br />
ጥያቄ የበርማ አምባገነን መንግስት ተቀበለ።<br />
አምባገነኑ የበርማ መንግስት የለውጡን<br />
ጥያቄ የተቀበለው ለውጥ ቢያደርግ ተጠቃሚ<br />
መሆኑን በመገንዘቡ ነበር።<br />
የሰላም ትግል የመንግስት ባለስልጣኖችን<br />
ብቻ ሳይሆን ህዝብንም በመቀየር/በመለወጥ<br />
ለዲሞክራሲ ትግል መስፋፋት እና አቅም<br />
ግንባታ ጥቅም ይሰጣል። መንግስት በህዝብ<br />
ላይ የሚፈጽማቸው በደሎች፣ ዲሞክራሲ<br />
የሚሰጠው ጠቀሜታ እና ዛሬ በአለም ውስጥ<br />
እየተደረገ ስላለው የለውጥ እንቅስቃሴ<br />
እና ስለመሳሰሉት በሰፊው ማሰራጨት<br />
ህዝብ ለመለውጥ ያግዛል። በአለም ውስጥ<br />
ስለሚሆነው እና በአገር ስለሚፈጸም ሰላማዊ<br />
ሰልፎች፣ ተቃውሞዎች፣ ህዝባዊ ውይይቶች<br />
እና ተመሳሳይ የሰላማዊ ትግል ዜናዎች<br />
የህዝብን ዝንባሌ እንደሚቀይሩ እና ከፍራቻ<br />
ነፃ ለመውጣት እንደሚያግዙ መረሳት<br />
የለበትም። በዚህ ረገድ ድረ ገጾች፣ የህትምት<br />
እና የኤሌክትሮኒክ ሚዲያዎች ከፍተኛ<br />
ሚና አላቸው። ለዚህም ነው አምባገነኖች<br />
የሚያፍኗቸው።<br />
አምባገነኖች በሰላም ትግል ታጋዮች ላይ<br />
የሚፈጽሙት ግፍ እና የሰላም ትግል ታጋዮች<br />
የሚያሳዩት ጀግንነት ህዝብን በመለወጥ<br />
የዲሞክራሲ ትግሉን ያጠናክራል። በዚህ<br />
ረገድ በህዝብ ዘንድ ጀግንነት ተደርገው<br />
የሚወሰዱ ርምጃዎች ሌላውን የመለወጥ<br />
አቅም እንዳላቸውም መረሳት የለበትም።<br />
ምሳሌ፥ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር<br />
በ1950 ዎቹ እና 1960ዎቹ አፍሪካ<br />
አሜሪካውያን መንግስት በሚለቅባቸው<br />
ተናካሽ ውሻዎች መነከሳቸው፣ በእሳት አደጋ<br />
መኪናዎች በሚረጭ ውሃ መደብደባቸው፣<br />
ማታ ማታ በሰላም ትግል መሪዎች ቤቶች<br />
ላይ ይደርስ የነበረው ቃጠሎ፣ የሰላም<br />
ትግል ሰራዊት በሚሰበሰብባቸው ቤተ<br />
ክርስቲያኖች ላይ ይደርስ የነበረው ፈንጂ እና<br />
ቃጠሎ ሳይገታቸው በጀግንነት ለእኩለንት<br />
ያደረጉዋቸው ትግሎች ህዝባቸው ብቻ<br />
ሳይሆን ነጭ አሜሪካውያንን እና የቀረውን<br />
አለም ህዝብ በመለወጥ ከአፍሪካውያን<br />
አሜሪካውያን ጎን እንዲቆም አድርጓል።<br />
ሌላ ምሳሌ፥ ግብጾች መንግስት ሳያስፈቅዱ<br />
በነፃነት አደባባይ መስፈራቸው እና<br />
ነፃነታቸውን ማወጃቸው ብዙ ግብጻውያንን<br />
እንደለወጠ እና ሰላማዊ ትግሉን እንዲቀላቀሉ<br />
እንዳደረገ የምናውቀው ትኩስ ዜና ነው።<br />
እንዲሁም በድስፕሊን የታነጸ የሰላም<br />
ትግል ሰራዊት በአምባገነኖች እየተዋከበ፣<br />
ሳያስር እየታሰረ እና እየተገደለ፤ በጀግንነት<br />
ሰላማዊ ትግሉን በቀጣይነት ሲያኪያሂድ<br />
ሲያዩ የጨቋኙ መንግስት አባላት (የጦር<br />
መኮንኖች፣ ሚንስትሮች፣ ዲፕሎማቶች፣<br />
ወ.ዘ.ተ.) እንዲሁም የተባበሩት መንግስታት፣<br />
የምዕራቡ አለም መሪዎች፣ የመብት ተሟጋች<br />
ድርጅቶች ወ.ዘ.ተ. ሳይቀሩ እየተለወጡ<br />
ሰላማዊ ትግሉን ይቀላቀላሉ። ለምሳሌ<br />
የሊቢያው ጋዳፊ በሰላማዊ መንገድ አደባባይ<br />
ወጥቶ ነፃነቱን በጠየቀ ህዝብ ላይ አረመኒያዊ<br />
ጦርነት ሲያውጅ በጋዳፊ መንግስት ውስጥ<br />
በአገር ውስጥ የነበሩ ባለስልጣኖች እና<br />
ዲፕሎማቶች ሰላማዊ ትግሉን ተቀላቅለዋል።<br />
በየመንም አምባገነኑ የሳላህ መንግስት በሰንዓ<br />
(ለውጥ አደባባይ) እና በታኤዝ ከተሞች<br />
በሰፈረው ሰላማዊ ታጋይ ላይ ግድያ በፈጸመ<br />
ቁጥር ተመሳሳይ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል።<br />
እስከዚኽ ድረስ እንዳየነው መቀየር/<br />
መለወጥ (Peaceful conversion)<br />
የተባለውን የለውጥ ማምጫ መንገድ<br />
ፕላን ቀይሰን በአግባብ እና በቀጣይነት<br />
ከተጠቀምንበት የዲሞክራሲ ትግልን<br />
በህብረተሰቡ ውስጥ ለማስፋፋት እና<br />
የህብረተሰቡን የሰላማዊ ትግል አቅምን<br />
ለመገንባት ይጠቅማል። ነገር ግን ይኽ ለውጥ<br />
የማምጫ ሰላማዊ መንገድ በአምባገነኖች<br />
የፖለቲካ ኃይል ምንጮች ላይ የሚያደርሰው<br />
ቀጥተኛ ጥቃት የለም። ጥቃቱ ተዘዋዋሪ<br />
ነው። ለጥቀን መቻቻል የተባለውን ለውጥ<br />
ማምጫ መንገድ እንመልከት።<br />
(2ኛ) መቻቻል (Peaceful<br />
accommodation)<br />
አንዳንድ ጊዜ አምባገነናዊ መንግስቶች<br />
በዜጎች ዘንድ ላገር አሳቢ መስሎ ለመታየት፣<br />
በውጭ መንግስታት ዘንድ ተቀባይነት<br />
ለማግኘት ወይንም የገጠማቸውን የለውጥ<br />
ጥያቄ ውጥረት ለማርገብ ሲሉ የዲሞክራሲ<br />
ኃይሎችን ጥያቄዎች ይቀበላሉ። ይኽን<br />
የሚያደርጉት መብት አክባሪ እና ትሁት<br />
በመሆናቸው ሳይሆን ለተቃዋሚዎች የለውጥ<br />
ጥያቄ የመቻቻል መፍትሄ ብንሰጥ ስልጣናችን<br />
አይነጠቅም፣ አቅማችንም አይዳከምም ነገር<br />
ግን ከጭቅጭቅ እንድናለን ከሚል እምነት<br />
ነው። ይሁን እንጂ አንድ አምባገነን መንግስት<br />
መቻቻልን እንደመፍትሄ ከወሰደ በስልጣን<br />
ላይ የነበረው ፍጹም የሆነ ቁጥጥር ተቀንሷል<br />
ማለት ነው። በህዝብ እና በአምባገነኖች<br />
መካከል በነበረው የኃይል ሚዛን ግንኙነት<br />
ላይ የተወሰነ ሽግሽግ ተደርጓል ማለት ነው።<br />
ለምሳሌ የስራ ማቆም አድማዎችም ቆመው<br />
ሰራተኞች ወደ ስራ የሚመለሱት በአሰሪና<br />
በሰራተኞች መካከል በሚደረግ መቻቻል<br />
ነው።<br />
5<br />
በአገሮች መካከልም መቻቻል ይደረጋል።<br />
የቻይና መንግስት ጥቂት የፖለቲካ እስረኛ<br />
በመፍታት በምዕራቡ አለም የሚቀርብበትን<br />
የሰብዓዊ መብት ማሻሻል ጥያቄ ለማርገብ<br />
ሲሞክር እናያለን። ምዕራቡም ለጊዜው ዝም<br />
ይላል። በምዕራቡ እና በቻይና መንግስት<br />
መካከል መቻቻል ተደረገ ማለት ነው።<br />
የቻይና መንግስት ይኽን የሚያደርገው<br />
በምዕራቡ አለም ተገዶ (Coerced ሆኖ)<br />
ሳይሆን የቀረበው የመብት ጥያቄ ከምዕራቡ<br />
አለም ጋር ካለው የንግድ እና ሌሎች ጉዳዮች<br />
ጋር እየተወሳሰበ እንደልብ አላራምድ<br />
ስለሚለው ነው። ስለዚኽ ለምዕራቡ ጥያቄ<br />
የመቻቻል ምላሽ በመስጠት ንግዱን እና<br />
ሌሎች የሚጠቅሙትን ነገሮች ያደርጋል።<br />
ምርጫም መቻቻል ነው። በየአምስት<br />
ወይንም አራት አመቶች የሚደረግ ምርጫ<br />
ተቃዋሚ ፓርቲዎች ለሚያቀርቡት የፖለቲካ<br />
ለውጥ ጥያቄ አምባገነን መንግስቶች<br />
የሚሰጡት የመቻቻል መልስ ነው። ይሁን<br />
እንጂ ከተመክሮ ማነስ የተነሳ የተቃዋሚ<br />
ፓርቲ መሪዎች ምርጫው ነፃ እና ፍትሃዊ<br />
ይሆናል፣ ከምርጫው ጋር በተያያዘ<br />
መንግስት የሚፈጽመውን ወከባ ህዝቡ<br />
መቋቋም ይችላል ወይንም አለም አቀፍ<br />
ታዛቢዎች የምርጫውን ድምጽ ቆጠራ<br />
እንዳይሰረቅ ያደርጋሉ ብለው ይገምታሉ።<br />
ይኽ የዋህነት ነው። አምባገነኖች ነጻ ምርጫ<br />
ተደርጎ ስልጣናቸውን በፈቃዳቸው ይለቃሉ<br />
ብሎ መገመት ስህተት ነው። ሳይገደዱ<br />
በፈቃደኛነት ስልጣን ማስረከብ የአምባገነኖች<br />
ጸባይ አይደለም። አምባገነኖች ዲሞክራቶች<br />
አይደሉም። አምባገነኖች ስልጣን ላይ<br />
የሚወጡት በግድያ እና በሽብር ነው።<br />
በስልጣን ለመቆየትም መንግስታዊ ሽብር<br />
ይፈጽማሉ። ምርጫም ከሆነ የሚያግዳቸው<br />
ኃይል ከሌለ ድምጽ ይሰርቃሉ። እንደ<br />
አውሮፓ አቆጣጠር በ2000 ዓመተ ምህረት<br />
በሰርቢያ እና በ2002 ዓመተ ምህረት<br />
በዝንባቡዌ የተደረጉት ምርጫዎች በንፅፅር<br />
ማየት ይጠቅማል። ሁለቱም ምርጫዎች<br />
በስልጣን ላይ በነበሩት አምባገነኖች<br />
ተሰርቀው ነበር። ይሁን እንጂ በሰርቢያ<br />
የህዝብን ድምጽ ማስከበር ሲቻል በዝንባቡዌ<br />
ግን ያን ማድረግ ሳይቻል ቀርቷል። ስለዚኽ<br />
የሁለቱ ምርጫዎች የመጨረሻ ውጤት<br />
ሊለያይ ቻለ። እንመልከት።<br />
በሰርቢያ ተቃዋሚው በመላ አገሪቱ<br />
የምርጫ ታዛቢዎች አሰልጥኖ አሰማራ።<br />
ህዝቡ ንቅል ብሎ ወጥቶ ድምጹን እንዲሰጥ<br />
የሚያነሳሳ እና የሚቀሰቅስ የሰላማዊ የምርጫ<br />
ሰራዊት አሰልጥኖ በመላ አገሪቱ አዘመተ።<br />
መንግስት ድምጽ ቢሰርቅስ ብሎ ቀደም ብሎ<br />
በማሰብ ተቃዋሚው ድምጽ “ለማስከበር<br />
ፕላን ለ” (Plan B) አዘጋጅቶ ነበር። አንድ<br />
መንግስት የህዝብ ድምጽ አላከብርም ካለ<br />
ህዝቡም በበኩሉ ለመንግስት የለገሰውን<br />
የገዢነት ክብር እና ህጋዊነት የመንፈግ መብት<br />
አለው። ስለዚኽ “ፕላን ለ” (Plan B) ድምጽ<br />
ለማስከበር የሚደረግ የፖለቲካ እምቢታ፣<br />
ትብብር የመንፈግ እና የጣልቃ መግባት<br />
የሰላም ትግል መሳሪያዎችን የሚጠቀም<br />
ሰላማዊ ትግል ነው። በየምርጫ ጣቢያው<br />
የተመደቡ የተቃዋሚ ታዛቢዎች በድምጽ<br />
ቆጠራው ላይ በመሳተፍ ቆጠራው እንዳለቀ<br />
በዚያው ምሽት ውጤት በየጣቢያው ይፋ<br />
እንዲሆን አደረጉ። በመጨረሻ በሞሊሶቪች<br />
ይመራ የነበረው አምባገናንዊ መንግስት<br />
የምርጫው ውጤት እንደፈለገው ሳይሆን<br />
በመቅረቱ አይኑን በጨው አጥቦ አሸንፌያለሁ<br />
ቢልም በምርጫው እለት ምሽት በየምርጫ<br />
ጣቢያው ድምጽ ይፋ ተደርጎ ስለነበር ህዝቡ<br />
“ድምጽ ይከበር” አለው። ተቃዋሚው ቀደም<br />
ብሎ ያዘጋጀውን በሚሊዮኖች የሚቆጠር<br />
ወደ 13 ይዞሯል<br />
www.andinet.org.et
6<br />
www.andinet.org.et<br />
በማህበራችሁና በቻይና ኩባንያ በሚሰሩ ዜጐቻችን ላይ ከፍተኛ<br />
በደልና ግፍ እየተፈፀመ ነው ይባላል፡፡ እውነት ነው፡፡ ካለስ<br />
የሚፈፀመው በደል ምንድነው?<br />
- እውነት ነው፡፡ እጅግ አሰቃቂ ግፍ እየተፈጸመብን ነው፡፡<br />
ዋናው ጉዳይ ቻይናውያን በእኛ ሕግ ተዳደሩ ይሉናል፡፡ እኛ<br />
ደግሞ የለም፤ በአገራችን ሕገ-መንግሥትና በአዋጅ 377/96<br />
ሕግ መሠረት እንተዳደር እንላለን፡፡ ሕገ መንግሥቱ አንቀጽ<br />
55/ን/አ/3 የተሰጠን የዜግነት መብት ይከበርልን እንላለን፡<br />
፡ ቻይናውያን ሕገ-መንግሥታችሁንም የአዋጅ ሕጋችሁንም<br />
አናውቅም ብለው በገዛ አገራችን እንደ ዕቃ እየተጫወቱብን<br />
ነው፡፡ በጉልበታችን፤ በጊዜአችንና በሞራላችን ላይ ብቻ ሳይሆን<br />
የሰብአዊና የዴሞክራሲያዊ መብት ጥሰት፣የአካል ጉዳትና በሴት<br />
እህቶቻችን ላይ የፆታ ጥቃት እየተፈፀመ ነው፡፡<br />
የውል ስምምነት የላችሁም? ከሌላችሁስ እንዲኖራችሁ<br />
አልሞከራችሁም?<br />
- በአገራችን ካለው የሥራ እጦት መጀመሪያ ስንቀጠር ሠርተን<br />
እንብላ እያልን ተቀጠርን፡፡ መብታችን አልከበር ሲል፤ጥቃት<br />
ሲደርስብን፤በማህበር ተደራጅተን መብታችንን ለማስከበር<br />
ሞክረን፡፡ የሰራተኛው ብዛት 720 /ሰባት መቶ ሃያ/ ነው፡፡ 3 ጊዜ<br />
ማሕበሩን ለማፍረስ ተሞከረ፡፡ ሆኖም ግን አልቻሉም፡፡ ቀጥሎ<br />
እየነጣጠሉ ማጥቃት ጀመሩ፡፡<br />
የማሕበሩ አመራር በመሆኑ የደረሰ የተለየ የሚባል ጥቃት አለ?<br />
በማስረጃ ሊገልጹልኝ ይችላሉ?<br />
- አዎ፡፡ የማሕበራችን መስራች የሆነው አቶ አረጋኸኝ ተፈሪ<br />
የሚባል የ24 ዓመት ወጣት አለ፡፡ ማሕበሩን ለምን አቋቋምክ?<br />
ለምን አታፈርስም? ብለው ቢያዙት እንቢ በማለቱ የተወሰደበትን<br />
ጥቃት ልንገርህ፡፡ ሚስተር ማ የሚባል ቻይናዊ ከአንድ ሺ<br />
ኪ.ግ በላይ የሆነ የስሚንቶ ማቡኪያ በሃፍቼ ፔን ማሽን ብድግ<br />
ካደረገ በኋላ ከሥር ሆነህ ስሚንቶውን ፈቅፍቅልኝ አለው፡<br />
፡ ይህ ሠራተኛ በታዘዘው መሠረት ከሥር ገብቶ ስሚንቶውን<br />
መፈቅፈቅ ጀመረ፡፡ ማሽኑን አውርዶ አስቀመጠበት፡፡ አረጋኸኝ<br />
ከሥር ሆኖ በሲቃ ሲጮህ ለ49 ደቂቃ በላዩ ላይ አስቀመጠበት፡<br />
፡ አረጋኸኝ ከዚያ ሲወጣ ከሰውነቱ ሦስት አጥንት ወጥቷል፡፡<br />
ሽንቱን መቆጣጠር አልቻለም፡፡ ዛሬ አይነምድሩን እናቱ በጓንት<br />
ያፀዳዱለታል፡፡ የህክምና ፋይሉ ዮርዳኖስ ሆስፒታል ይገኛል፡<br />
፡ ዮርዳኖስ ሆስፒታል 15 ቀን ካስተኙት በኋላ አውጥተው<br />
እንዲሞት ተፈልጐ በአንድ ሆቴል ለ3 ቀን አስተኙት፡፡ ሆኖም<br />
ግን በቤተሰብ ጥረት ተረፈ፡፡ ማህበራችንን ከመሠረቱት ሰባት<br />
ሰዎች አንዱ ነው፡፡ በማህበሩ ውስጥ ንቁ ተሳትፎ ከሚያደርጉ<br />
መካከል አረጋኸኝ ተፈራ ግንባር ቀደም ነበር፡፡ ዛሬ አረጋኸኝ<br />
ሽንቱን መቆጣጠር አይችልም፡፡ የአልጋ ቁራኛ ሆኗል፡፡ ይህ<br />
የደረሰበት ሰው ነኝ፤ አገር አለኝ፤ መብቴን በሕገ-መንግሥቱና<br />
በአዋጁ መሠረት መብቴን አስከብራለሁ፤ መንግሥትም ከጐኔ<br />
ይቆምልኛል ብሎ በማመኑ ነበር፡፡ ነገር ግን አልሆነም፡፡<br />
ወንድሞቹን ያስተምር ነበር እናቱን የሚጦር እሱ ነው፡፡ በአሁኑ<br />
ጊዜ ከ6ቱ ወንድሞቹ አራቱ ትምህርታቸውን አቋርጠው ልመና<br />
ገብተዋል፡፡ ለአረጋኸኝ ምግብ ያስፈልገዋል፡፡ አረጋኸኝን<br />
ለሚያስታምሙ እናቱም ምግብ ያስፈልጋታቸዋል፡፡ የቀረነውን<br />
አመራሮች የሚያድን ኃይል ተመድቦብን ሕይወታችን አደጋ<br />
ውስጥ ወድቋል፡፡ በገዛ አገራችን መብታችንን በመጠየቃችን<br />
የሕይወት ዋስትና አጥተን ዛሬ የምንኖረው ተሸሽገን ነው፡<br />
፡ እኛ የጠየቅነው ሕገ መንግሥቱ ይከበር! ሕገ መንግሥስቱ<br />
የሰጠን መብት ይከበርልን ነው፡፡ ሕገ መንግሥቱን ቻይናውያን<br />
አንቀበልም ሲሉ የመንግሥት አካላትም በተገላቢጦሽ እኛን<br />
እንደወንጀለኛ አይተው እያሳደዱን ነው፡፡ እያሳደዱን ያሉት<br />
ሠራዊት ሕጋዊ ሠራዊት መሆኑን እየተጠራጠርን ነው፡፡ በማን<br />
መዋቅር የተደራጀ ሠራዊት በማን እንደሚታዘዝም አልገባንም፡<br />
፡ በዚህ አጋጣሚ የተደቀነብን የሕይወት አደጋ ለሚመለከተው<br />
ሁሉ አሳውቃችሁልን ሕይወታችንን አትርፍልን፡፡<br />
በሌላ አመራር ወይም አባል ላይ እንደዚህ ዓይነት የደረሰ ጉልህ<br />
በደል ይኖር ይሆን?<br />
- 17 አባሎቻችን ከፍተኛ የአካል ጉዳት ደርሶባቸው ለእንግልትና<br />
ለሥቃይ ተዳርገዋል፡፡ ህክምና አጥተው አካላቸው ተበላሽቶ<br />
በቁስል እየተሰቃዩ ናቸው፡፡ ለምን እንዴት ብሎ የሚጠይቅ<br />
ሠራተኛ ካለ በሎደር አፈር ይደፋበታል፡፡ በየዕለቱ በሴት<br />
እህቶቻችን ላይ አስገድዶ መድፈር ይፈፀምባቸዋል፡፡<br />
ለየትኛውም የመንግሥት አካል ብታመለክት መልስ አታገኝም፡፡<br />
ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />
ቆይታ<br />
- “ቻይናውያን ሕገ-መንግሥታችሁንም የአዋጅ<br />
ሕጋችሁንም አናውቅም ብለዋል”<br />
አፍህን ሰብስበህ ሥራህን ሥራ እንባላለን፡፡ ለቻይና እስከሰራችሁ<br />
ድረስ፤ ቻይና ደሞዝ እስከፈለጋችሁ ድረስ፤ በቻይና ሕግ<br />
መተዳደር አለባችሁ ይሉናል፡፡ በቻይና ሕግ ማህበር ማቋቋም<br />
ክልክል ነው፡፡ በቻይና ሕግ ሐሳብን በነጻነት መናገር አይቻልም፡<br />
፡ መሰብሰብ ወንጀል ነው፡፡ ሐሳብን በነጻነት መናገር አይቻልም፡<br />
፡ ጋሻው ጣሰው የተባለ አንድ አባላችን ጥር 7 ቀን 2003 ዓ.ም<br />
በሰርግ ሚስት አገባ፡፡ ጥር 8 ቀን 2004 ዓ.ም አስጠርተው<br />
በሰርግህ ዕለት አንድ ቻይና የሚለብሰው ነጭ ተመሳሳይ ጃኬት<br />
ለምን ለበስክ ብለው ደብድበው የዘር ፍሬውን አበላሽተውታል፡<br />
፡ የዚህን ሠራተኛ የዘር ፍሬ ለማበላሸት የፈፀሙበት ስቃይ<br />
እነዚህ ሰዎች እንደ ሰው የሚያስቡ ናቸው የሚያስኝ ነው? ይህ<br />
ሰራተኛችን አሁንም በአካል አለ፡፡ ልታነጋግሩት ትችላላችሁ፡፡<br />
ከአካል ጉዳትና ከሴቶች መደፈር ሌላስ የሚጠቀስ ጥቃት<br />
ይኖራል?<br />
- እየተፈፀመ ያለው ጥቃት ተዘርዝሮ የሚያልቅ አይደለም፡፡<br />
የብሔራዊና የሃይማኖት በዓላትን እንዳናከብር ተከልክለናል፡፡<br />
በዚሁ ምክንያት 5 የክርስትና፣3 የእስልምና በዓላትን፣የአድዋና<br />
የሜዴይ በዓላትን እንዳናከብር ተከለከልን፡፡ የራሳችንን<br />
ብሔራዊ በዓላት ተከልክለን በአገራችን ተቀምጠን የቻይናን<br />
የጐማ በዓል ተገደን አንድናከብር እየተደረገ ነው፡፡<br />
ይህ ሁሉ በደል ሲፈፀም የት የት አመለከታችሁ? ምን መልስ<br />
ተሰጣችሁ?<br />
- መጀመሪያ አካባቢ የነበረን ግንዛቤ ቻይናውያን<br />
በኢትዮጵያውያን ላይ ለሚያደርሱብን ጥቃት አቤቱታ አቅርበን<br />
ከአንዳንድ የመንግሥት ባለሥልጣናት ፍትህ ስናጣ የመሰለን<br />
የባለሥልጣናት የሙስና ውጤት ነው፤እያልን እሱን ትተን<br />
ወደ ሚቀጥለው ባለሥልጣን እናመለክት ነበር፡፡ በመጨረሻ<br />
ላይ ግን እንደምናየው የመንግሥት አቋም ነው፡፡ መንግሥት<br />
ከቻይናውያን ጥቅም እስካገኘ ድረስ በዜጐች ላይ ምንም<br />
ጥቃት ቢደርስ የፈለገው ግፍ ቢፈጸም ማየትም መስማትም<br />
አለመፈለጋቸውን ነው የተረዳነው፡፡<br />
እንደዚህ ለማለት የሚያበቃችሁ ምንድነው? በቀጥታ ቀርባችሁ<br />
ለመጨረሻ ጊዜ ያነጋገራችሁት ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣን<br />
ማነው? ምንስ መልስ ሰጡዋችሁ?<br />
- ሌላውን ልተወውና ሁለት ቦታዎችን ብቻ ልግለጽልህ፡፡ ለህዝብ<br />
ተወካዮች ም/ቤት ሕግና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ<br />
አመለከትን፡፡ የፓርላማ አባል የሆኑት የተከበሩ አቶ ብርሃኑ<br />
2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />
አቶ ኩራባቸው ፍቅሩ ገ/ማርያም የዋልዳ ሆጀቶታ ዳንዲ ደራርቱ አርሲ (W H D D A) የቻይና ሠራተኞች ማህበር ሊቀመንበር ናቸው፡፡<br />
የቻይና ኩባንያዎች በማሕበራቸውና በዜጐቻችን ላይ እያደረሰ ነው በሚባለው ጉዳይ ላይ ባልደረባችን ብዙአየሁ ወንድሙ አነጋግሮአቸዋል፡፡<br />
አበበ ሥፍራው ድረስ ሄደው ተመልክተዋል፡፡ ሠራተኛው<br />
የደረሰበትን ነገር ሁሉ አስረድቷቸዋል፡፡ ተመልሰው ከሄዱ<br />
በኋላ ትልቅ መፍትሔ እናገኛለን ብለን ተስፋ አድርገን ነበር፡፡<br />
ምንም መልስ አላገኘንም፡፡ ለጠ/ሚኒስትሩ ጽ/ቤት አመልክትን፡<br />
፡ መፍትሄ ስንጠብቅ ያገኘነው ውጤት በተገኘንበት ቦታ ሁሉ<br />
እያሳደዱ እርምጃ መውሰድ ጀመሩ፡፡ ቀይ ሽብራዊ ግርፍ<br />
ተፈጽሞብናል፡፡ ታስረን ተገልብጠን ተገርፈናል፡፡ ሱሪንና<br />
ቡታንታን አስወልቀው እጅና እግርን አስረው ገልብጠው<br />
ሰቅለው መጫወቻ አደረጉን፡፡<br />
እንዲህ ተሰቅላችሁ የተገረፋችሁት የት ነው?<br />
በአርሲ ጮሌ ወረዳ ማኛ ላይ የፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ነው ይህንን የፈፀመብን፡<br />
፡ 51 አባሎቻችን ቀይ ሽብር ግርፍ ተፈጽሞብናል፡፡ በ7 አባሎቻችን ላይ<br />
ደግሞ ለምርመራ ተብለው ተወስደው በራሳቸው ላይ እንዲመሰክሩ<br />
አሰቃይተዋቸዋል፡፡ ኬሚካል ረጭተውባቸዋል፡፡ አእምሮአቸውን እንዲሰቱ<br />
አድርገዋቸዋል፡፡ ጥር 8 ቀን 2003 ዓ.ም ከፍተኛ ተኩስ ተከፍቶብን ሊፈጁን<br />
ሲሉ የሼክ አብዱራህማን ጉቺ የሚባል የእምነት ሥፍራ ያለ ህዝብ ወጥቶ<br />
ነው ያዳነን፡፡<br />
ይህ የተጋነነ ወይም ማስረጃ የሌለው ነገር ነው ማለት አይቻልም?<br />
- ይኸውልህ ከወረዳው መስተዳድር ደብዳቤ አጽፈን በእጃችን<br />
ይገኛል፡፡ ለተፈፀመብን ጥቃት በጠቅላላ የሲዲና የጽሑፍ<br />
ሰነዶቻችን ይኽውልህ፡፡ ሁሉንም አይተህ ማረጋገጥ ትችላለህ፡፡<br />
ሌሎች ሠራተኞችንም አነጋግር፡፡<br />
ቻይናዊያን ይህንን ግፍ ለምን የሚፈጽሙ ይመስልሃል?<br />
ቻይናዊያን እንደሚታወቀው በሰብአዊ መብት ጥሰት በዓለም ላይ የታወቁ<br />
ናቸው፡፡ በተለይ ኢትዮጵያ ከመጡ በኃላ ባለቤትና ከልካይ የሌለው ዜጋ<br />
አገኙ፡፡ እጅግ አድርገው ናቁን፡፡ የዜግንነትና ሉዓላዊ ክብር የሚነካ ስድብ<br />
ይሰድቡናል፡፡ ለመናገር የማይቻል ፀያፍ ስድብ ይሰድቡናል፡፡ በሥራ<br />
ምክንያት ለሚደርስ የአካል ጉዳት ህክምናና ካሳ አገልግሎት መክፈል የለብንም<br />
ብለው ያምናሉ፡፡ በሠራተኛ ማህበር ተደራጅቶ መብትን መጠየቅ ትልቅ<br />
ወንጀል አድርገው ያያሉ፡፡ በሴቶች ላይ የሚፈጽሙትን አስገድዶ መድፈር<br />
እንደመብታቸው ይቆጥሩታል፡፡ በኢትዮጵያ ህግ አንተዳደርም ብለው<br />
አምነዋል፡፡ ከመንግሥት ጋር ያላቸውን ውል አናውቅም፡፡ በአዋጅ 377/96<br />
ተከሰን ለአንድ ሠራተኛ አንድ ሺ ብር ከምንከፍል ለአንድ ባለሥልጣን አንድ<br />
ሚሊዮን ዶላር ሰጥተን ጉዳዩን ብንጨርስ ይሻላል ይላሉ፡፡ ምክንያቱን<br />
ሲገልጹ ለዘላቂ ጥቅም ለወደፊት ዓላማችን ይበጀናል ብለው ያምናሉ፡፡ እረፉ<br />
የሚላቸው ህግም ባለሥልጣንም ባለመኖሩ አጠናክረው ቀጥለዋል፡፡<br />
የኢትዮጵያ መንግስት በቻይናዊያንና በኢትዮጵያኖች መካከል<br />
የሚነሳ አለመግባባቶችን በህግ ለመዳኘት ችግሩ ምንድነው<br />
ይላሉ?<br />
ይህ መንግሥት ካለበት ውጫዊና ውስጣዊ ችግር ምክንያት ይመስለኛል፡፡<br />
መንግስት ከምዕራባዊያንና ከአሜሪካውያን ፊት ስላጣ ሙሉ በሙሉ በሚባል<br />
መልኩ ግንኙነቱን ወደ ቻይና አድርጓል፡፡ ቻይናን እንደ ከለላ መያዣ የፈለገ<br />
ይመስለኛል፡፡ ስለዚህ በምንም መልኩ የቻይናን ኩባንያ በአገሬ ላይ በዜጐች<br />
ላይ ይህንን አትፈጽሙ ለማለት ሞራል አላገኘም፡፡ እንዲያውም ከቻይና ጋር<br />
ግንኙነቱን ካረጋገጠና ካጠናከረ ጀምሮ ራሱ የእኛ መንግሥት በአገሪቱ ውስጥ<br />
ያለው የሰብአዊ መብት ጥሰት በእጅጉ ተጠናክሮ ቀጥሎአል፡፡ ልክ እንደቻይና<br />
ገዢው ፓርቲ ከሚያራምደው አመለካከትና ሐሳብ ውጪ አማራጭ<br />
ሐሳብን ማራመድ ከባድ ውንጀል እየሆነ ነው፡፡ ሚዲያውም የተለየ ሐሳብ<br />
እንዲያንሽራሽር አይፈልግም፡፡ በተጨማሪ ካለብን ድህነት ችግር በዜጐች<br />
ላይ የሚፈጸመውን ግፍና በደል አፍኖ እርዳታና ብድር ማግኘትን መርጧል፡<br />
፡ መንግስት ከዜጐች ይልቅ ገንዘብን የመረጠ ይመስላል፡፡ ምናልባትም የተለየ<br />
ውልና ስምምነትም ሊኖራቸው ይችላል፡፡<br />
በመጨረሻም ያልጠቀስኩት ነገር አለ ካሉ አጠር አድርገው<br />
መግለጽ የሚፈልጉት ሐሳብ ይኖራል?<br />
በመጀመሪያ አሁንም እንደትላንትናው ደግመን ደጋግመን የምንጠይቀው<br />
መንግስት ኃላፊነቱን ይወጣ ነው፡፡ የአገሪቱን ህገመንግስትና ያወጣቸውን<br />
አዋጆች ያስከብር፡፡ የዜጐችን በደልና ግፍ ያድምጥ፡፡ መፍትሄ ይሰጠን<br />
እንላለን፡፡ በሁለተኛ ደረጃ የሰብአዊ መብት ተከራካሪዎች ነን፤ የፆታ ጥቃትን<br />
እንታገላለን፤ የሚሉ ሁሉ ጩኽታችንን ሰምተው ከጐናችን እንዲቆሙ<br />
በሠራተኛው ስም ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡ በገዛ አገራችን እየተፈፀመብን ያለውን<br />
እጅግ ዘግናኝ ግፍና ሰቆቃ በገለልተኛ አካል ተጣርቶ እርምጃ እንዲወሰድ<br />
እንዲደረግልን፤ ህክምና ምግብ አጥተው በስቃይ ላይ ላሉ የጥቃት ሰለባዎች<br />
እርዳታ ድርጅቶችም ሆኑ የመርዳት አቅም ያላቸው ሁሉ እጃቸውን<br />
እንዲዘረጉልን፤ አሁንም በሠራተኛ ማሕበሩ ስም እማፀናለሁ፡፡ በመጨረሻም<br />
መላው ኢትዮጵያውያን ሁሉ በአገሩ ላይ እየተፈፀመ ያለውን ግፍ ይረዳልን<br />
ማለት እውዳለሁ፡፡<br />
እርማት<br />
በፍኖተ ነጻነት ጋዜጣ 2ኛ ዓመት ቅጽ 2 ቁጥር 14 ረቡዕ ጥቅምት 22 ቀን 2004ዓ.ም በወጣው እትም ዝግጅት ክፍላችን ከተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ ጋር ቆይታ ማድረጉ<br />
ይታወቃል፡፡ በገጽ 6 አራተኛው አንቀጽ በስምንተኛው ስንኝ ላይ በሰጡት መልስ “የኢሰፓ አባል ነበርኩ” የሚለው በመቅረፀ ድምጽ ጥራት የተፈጠረ ችግር ስለሆነ<br />
“የኢሠፓ አባል አልነበርኩም” ተብሎ እንዲታረም እየገለጽን ለተፈጠረው ስህተት አንባቢያችንንና የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉን ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡
2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />
በተስፋዬ ደጉ<br />
ወቅታዊ<br />
ሐሙስ ጥቅምት 2 ቀን 2004 ዓ.ም ከጠዋቱ አራት<br />
ሰዓት ላይ በመድረክ ጽ/ቤት ጋዜጣዊ መግለጫ<br />
እየተሰጠ ነው፡፡ በስድስት የተቃዋሚ የፖለቲካ<br />
ፓርቲዎች የተመሰረተው መድረክ፣ ከቅንጅትነት<br />
ወደ ግንባርነት መሸጋገሩን ለማብሰር፡፡ የየፓርቲዎቹ<br />
አመራሮች ጋዜጣዊ መግለጫውን ለመስጠት<br />
መድረኩን ይዘዋል፡፡ የአገር ውስጥም የውጭ አገርም<br />
በርካታ ጋዜጠኞች ሁኔታውን ለመዘገብ በቦታው<br />
ተገኝተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንም ካሜራዎቹን<br />
ደቅኖ ከአንድ ሰዓት በላይ የተካሄደውን ጋዜጣዊ<br />
መግለጫ እየቀረፀው ይታያል፡፡ መግለጫው ተነበበ፡<br />
፡ መድረኩ ለጋዜጠኞች ክፍት ተደረገ፣ ለአመራሮቹ<br />
ጥያቄ እንዲያቀርቡ፡፡<br />
የመጀመሪያዎቹ ሦስት ጥያቄዎች ከጋዜጠኞቹ<br />
ከተሰበሰቡ በኋላ፣ ለጥያቄዎቹ መልሶች መድረኩ ላይ<br />
ያሉት ዶ/ር መረራ ጉዲና መልስ መስጠት ጀምረዋል፡<br />
፡ ለመጀመሪያዎቹ ሁለት ጥያቄዎች በእርጋታ መልስ<br />
ሰጡ፡፡ ሦስተኛውን ጥያቄ ሲመልሱ ግን የተቆጡ<br />
መሰሉ፡፡ “እናንተ የኢሕአዴግ ካድሬዎች ግን<br />
መቼ ነው ፕሮፓጋዳችሁን መንዛት የምታቆሙት?<br />
መቼ ነው የምትተውን?” በማለት ጥያቄውን<br />
ወደ ጠየቃቸው ጋዜጠኛ እንደዋዛ እየተመለከቱ<br />
ጥያቄያቸውን ሰነዘሩ፡፡ ጋዜጠኛውም “ከኢሕአዴግ<br />
ቢሮ አልመጣሁም፡፡ የሬዲዮ ፋና ጋዜጠኛ ነኝ፡<br />
፡” ብሎ ጥያቄቸውን መለሰ፡፡ ዶ/ር መረራም<br />
ሃሳባቸውን ቀጠሉ፡፡ “ጋዜጠኛ ብትሆኑማ ጥሩ ነበር፡<br />
፡ የኢሕአዴግ ካድሬ እየሆናችሁ አስቸገራችሁን<br />
እንጂ፡፡” የሚል ምላሽ ከፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት<br />
ለመጣው ጋዜጠኛ ሰጡ፡፡<br />
ከፋና ብሮድካስት ኮርፖሬት የመጣው ጋዜጠኛ<br />
የጠየቀው ጥያቄ ያጠነጠነው የመድረክ “ግንባርን”<br />
የፈጠሩት ስድስቱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያላቸውን<br />
የአይዲዮሎጂ ልዩነትን የተመለከተ ነው፡፡ ጋዜጠኛው<br />
ስድስቱ ፓርቲዎች ያላቸው ተቃራኒ ሊባል የሚችል<br />
የአይድዮሎጂ ልዩነት “ግንባር” ለመፍጠር<br />
እንደማያስችላቸው ጠቃቅሶ፣ በመካከላቸው ያለውን<br />
የአይዲዮሎጂ ልዩነት የት እንዳደረሱት የሚሞግት<br />
ዓይነት ነበር፡፡<br />
ከመለስተኛዋ መመላለስ በኋላ ዶ/ር መረራ ጉዲና<br />
ለተጠየቀው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በዚህም<br />
ምላሻቸውም አገራችን ኢትዮጵያ አሁን ባለችበት<br />
ዘርፈ ብዙ ችግሮች፤ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓቱ<br />
መገታቱ፣ የኢሕአዴግ አምባገነን ፓርቲ እየሆነ<br />
መሄድ፣ የዜጐች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች<br />
መታፈን፤ የገዢው ፓርቲ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና<br />
የመገናኛ ብዙሃንን ሙሉ በሙሉ በራሱ ቁጥጥር<br />
ሥር ማዋሉና አገራችን ያለችበት አጠቃላይ ቀውስ<br />
በተሰባሰቡት ወቅት በተቃዋሚዎች መካከል<br />
ያለውን የአዲዮሎጂ ልዩነትን በሁለተኛ ደረጃ ላይ<br />
እንዳስቀመጠው ገልፀዋል፡፡ አክለውም መድረክ<br />
በመለስተኛ ፕሮግራሙ ያስቀመጣቸው ነጥቦችም<br />
የጋራ መታገያቸው መሆናቸውን ገልፀው፤ የመድረክ<br />
ዓይነት ግንባር በመፍጠር በጋራ አገር መምራትም<br />
በሰለጠኑት አገራትም ጭምር የተለመደ አካሄድ<br />
መሆኑን የጀርመንና የእስራኤልን ተሞክሮን ዋቢ<br />
አድርገው አብራርተዋል፡፡<br />
ማታ በሁለት ሰዓቱ የአማርኛ ዜና ላይ የመድረክ<br />
ከቅንጅት ወደ ግንባር መሸጋገሩን ከደቂቃዎች<br />
በላይ ባልፈጀ ዜና የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተናገረ፡፡<br />
ሬዲዮ ፋናም በድረ ገጹ ላይ ባንድ መስመር ዜናውን<br />
አስፍሮት ተስተዋለ፡፡<br />
የመገናኛ ብዙሃንና ነፃነት<br />
በማንኛውም አገር ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን<br />
ለመመስረት መገናኛ ብዙሃን የሚያበረክቱት<br />
አስተዋፅኦ ከፍተኛ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ መገናኛ<br />
ብዙሃንም ሊያበረክቱት የሚችሉት አስተዋፅኦም<br />
ባላቸው የነፃነት መጠን ላይ ተንጠልጥሎ ይገኛል፡<br />
፡ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ስንልም የሃሣቦች ብዝሃነት<br />
(plurality of ideas) ዋነኛው አምድ መሆኑን<br />
ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />
የመንግሥት መገናኛ ብዙሃን በሕገ-መንግሥቱ እውቅና የተሰጣቸውን ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብትንና የተለያዩ አስተሳሰቦችን ማስተናገድ ግዴታ እንዳለባቸው ተደንግጓል፡<br />
፡ ዴሞክራሲና መገናኛ ብዙሃን በጣም የተቆራኙ በመሆናቸው፤ አንዱን ከአንዱ ለይቶ ለማየት እስኪያስቸግር ድረስ ተደጋጋፊ ናቸው፡፡ የመንግሥት መገናኛ ብዙሃን ደግሞ<br />
ከየትኛውም የአገራችን የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት በበለጠ፤ ለሕዝብ ዓይንና ጆሮ በመሆን ሕገ-መንግሥቱ በተለያዩ ምክንያቶች ሲጣስ ለሕዝብ የማሳወቅ ግዴታ አለባቸው፡፡<br />
የሕዝብን ፍላጐት ግምት ውስጥ በማስገባት ምላሽ መሰጠት የሚችሉ ፕሮግራሞችን ማዘጋጀትም ሌላው ኃላፊነታቸው ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ላይ መጠነኛ የዳሰሳ<br />
ጥናት ያደረገው ተስፋዬ ደጉ ይሄን ለማድረግ እስካሁ ያልቻሉት “ከገዢው ፓርቲ በኩል የሚሰነዘር ጫና” በመኖሩ መሆኑን ሊያሳየን ተከታዩን ዘገባ አጠናቅሮልናል፡፡<br />
ኢሕአዴግና መገናኛ ብዙሃን<br />
ካሰብን ደግሞ ከኢ-ዴምራሲያዊ ጣልቃ ገብነትና<br />
ተፅዕኖ ነፃ በሆነ መልኩ መደራጀታቸውና ስራቸውን<br />
ማከናወናቸው፤ ዴሞክራሲያዊ ስርዓቱን በአጭር<br />
ጊዜ ለመመስረት የሚያስችል የማይተካ ሚና<br />
እንዳላቸው መረዳት ይቻላል፡፡<br />
መገናኛ ብዙሃን ላይ የተሰሩ በርካታ ጥናቶች<br />
እንደሚያሳዩት ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመመሥረት<br />
በመንገድ ላይ ያሉት በርካታ የአፍሪካ አገሮች<br />
ከመድበለ ፓርቲ ይልቅ ወደ አንድ ፓርቲ አገዛዝ<br />
እየሄዱ መሆኑን ያሳያል፡፡ በየአገራቱ መንግሥት<br />
የሚያስተዳድራቸው ብዙሃን መገናኛዎች በስልጣን<br />
ላይ ያለውን ገዢ ቡድን እንጂ የተለየ ድምፅ<br />
ለማሰማት በራቸውን ዘግተው ተቀምጠዋል፡<br />
፡ በመሆኑም በእነዚህ አገራት የዴሞክራሲያዊ<br />
ሥርዓት ግንባታ ሂደቱ ፈተና ላይ የወደቀው የአንድ<br />
ፓርቲ አገዛዝ ሥርዓት በመመስረቱ ብቻ ሳይሆን<br />
የመንግሥት መገናኛ ብዙሃን ከገዢው ፓርቲ ሃሳቦች<br />
በስተቀር ለሌሎቹ ወይም ለተቃዋሚዎቹ ዕድል<br />
አለመስጠታቸው ነው፡፡ ሲከፋም አሉታዊ ይዘት<br />
ያላቸውን ዘገባዎችን ማቅረብና “የስም ማጥፋት”<br />
ዘመቻዎችም ሲቀርብባቸው ይስተዋላል፡፡ እዚህ<br />
ጋ የዜናዎቹ /የዘገባዎቹ ሚዛናዊነት፣ ትክክለኛነት<br />
ወይም እውነተኛነት የመሳሰሉት የጋዜጠኝነት ስነ-<br />
ምግባር የሚጠይቃቸው እሴቶች አስታዋሽ ያላቸው<br />
አይመስሉም፡፡ እነዚህ ሆን ተብሎ የሚዘነጉ እሴቶች<br />
ደግሞ ለሃሳብ ብዝሃነት (plurality of ideas)<br />
ዋስትና፣ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ደግሞ<br />
መሠረት ናቸው፡፡<br />
ሮኒንግ ሄልግ “The Role of Media in Democracy”<br />
በተባለው መጽሐፍ እንዳስረዱት መገናኛ<br />
ብዙሃን ከመንግስት ወይም ከገዢ ፓርቲ ቀጥተኛ<br />
ጣልቃ ገብነት ነፃ ሆነው መደራጀታቸው በጣም<br />
አስፈላጊ የሚሆነው፤ መንግስት ስልጣኑን አላአግባብ<br />
እንዳይጠቀም ለመከላከል መሆኑን ያስረዳሉ፡፡<br />
ምናልባት የመንግሥትን ስልጣንን የያዙ ግለሰቦች<br />
ስልጣናቸውን ለራሳቸው ግላዊ ጥቅም ቢያውሉት<br />
የህዝብ ዓይንና ጆሮ ሆነው የሚያገለግሉት መገናኛ<br />
ብዙሃን “ስህተቱን” ለሕዝብ ያሳውቃሉ፡፡ መረጃው<br />
የደረሰው ሕዝብም፤ ያጠፉት ወኪሎቹን ማብራሪያ<br />
ከመጠየቅ ጀምሮ ውክልናውን እስከማንሳት የደረሰ<br />
እርምጃ ሊወሰድባቸው ይችላል፡፡ ይህ ሊሆን<br />
የሚችለው ግን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት በመሰረቱት<br />
እንደ አሜሪካና በምዕራብ አውሮፓ ባሉ አገራት<br />
ነው፡፡ በኢትዮጵያስ?<br />
ሁለቱ ወንበሮች<br />
ወንደስን አለሙ (ስሙ ለዚህ ፅሑፍ ተቀይሯል) እንደ<br />
ፖለቲካል ሳይንስ ተማሪነቱ የገዢው ፓርቲን ሁለት<br />
ወንበሮች ለመለየት እንደሚቸግረው ይናገራል፡፡<br />
እንደ ፓርቲ ስለየትኛውም ፖለቲካዊ ጉዳዮች የራሱን<br />
አቋም መያዝ መብቱ መሆኑን የሚቀበለው ቢሆንም፤<br />
የፓርቲውን አቋም ህገ-መንግሥቱን በመጣስ ጭምር<br />
በመንግሥታዊ ጉዳዮች ውስጥ ጣልቃ መግባቱን ግን<br />
አምርሮ እንደሚቃወመው ይናገራል፡፡<br />
የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራር የሆኑት ዶ/ር<br />
ኃይሉ አርአያ “መድበለ ፓርቲ በኢትዮጵያ የወደፊት<br />
ዕጣፋንታ” በሚለው ጥናታቸው ላይ እንደገለፁት<br />
“ከምርጫ 2002 በኋላ ኢሕአዴግ አምባገነናዊ<br />
አውራ ፓርቲ ሆኖ ወጥቷል፡፡ ወደዚህ የደረሰበት<br />
መንገድም ከምርጫ 97 በኋላ በወስዳቸው<br />
ኢ-ዴሞክራሲያዊ እርምጃዎች ነው፡፡” ይላሉ፡<br />
፡ ዝርዝራቸውን ለመቁጠር ወደ ጣቶቻቸው<br />
እየተመለከቱ፡፡ “የመጀመሪያው ነፃው ፕሬስን<br />
ለማዳከም የወጣው የሚዲያ አዋጅ፣ ሲቪክ<br />
ማህበራትን ተሳትፎ ለመቀነስ የወጣው አዋጅ፣<br />
የተቃዋሚ ፓርቲዎችን ደካማ ለማድረግ የወጣው<br />
አዋጅና የፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ” መሆናቸውን<br />
ይገልፃሉ፡፡<br />
ይሄው የዶ/ር ኃይሉ ተመሳሳይ ጥናት<br />
እንደሚያስረዳው ኢሕአዴግ አውራ ፓርቲ ሆኖ<br />
ለመውጣት የቻለው “ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን<br />
በማፈንና ነፃና ፍትሃዊ ባልነበረ ምርጫ በ2002<br />
በማሸነፉ” ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ኢሕአዴግ<br />
በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ “አምባገነናዊ አውራ<br />
ፓርቲ” እንጂ፣ “አውራ ፓርቲ” እንዳልሆነ<br />
ይደመድማሉ፡፡ ሃሳባቸውን በመቀጠልም<br />
“አምባገነናዊ አውራ ፓርቲዎች ባሉበት አገራት<br />
ገዢው ፓርቲንና መንግሥትን መለየት አለመቻል፣<br />
ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ መሰረት<br />
የሆኑ ነፃ የሚዲያ፣ የፍትህ፣ ሲቪክ ማኅበራትና<br />
የምርጫ አስፈፃሚ አካላት አለመኖር፤ ዋና ዋናዎቹ<br />
መገለጫዎቹ” መሆናቸውን አስታውሰው፤<br />
የአገራችን ነባራዊ እውነታም ይሄንኑ እንደሚያሳይ<br />
አስረድተዋል፡፡<br />
የገዢው ፓርቲ ይፋዊ ህትመቶች እንደሚያትቱት<br />
ደግሞ መንግሥት (ኢሕአዴግ ለማለት ነው) የግሉን<br />
የመገናኛ ብዙሃን ዘርፍ፤ “ሊቆጣጠረው” የሚገባው<br />
የአሁኑ ታዳጊ ዴሞክራሲያችን “እንዳይቀለበስ”<br />
ለመጠበቅ ነው፡፡ እነዚህ ይፋዊ ህትመቶችና አልፎ<br />
አልፎም የፓርቲው ሹማምንት እንደሚያስረዱት<br />
“ኢሕአዴግ የጀመረው የዴሞክራሲያዊ ስርዓት<br />
ግንባታ ሊቀለበስ በማይችልበት ደረጃ ላይ<br />
ገና አለመድረሱን ነው፡፡ ለዚህም ክርክራቸው<br />
የሚያቀርቡት ማስረጃም በምርጫ 97 ጊዜ ነፃው<br />
ፕሬስ ከተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጐን<br />
“መሰለፉ” የሚያሳየው ሐቅ ቢኖር፣ “ነፃው ፕሬስ”<br />
ከ “ኢ-ዴሞክራሲያዊ” ኃይሎች ጋር በማበር<br />
“ዴሞክራሲውን” አደጋ ላይ የመጣል አቅም<br />
እንዳለው ማሳየቱን የፓርቲው ህትመቶች ይገልፃሉ፡፡<br />
የዶ/ር ኃይሉ ጥናት የሚያሳየው ግን በሚድያ ህጉ<br />
እንደታየው የኢሕአዴግ ዓላማ ዴሞክራሲያዊ<br />
ስርዓቱን ለማፈን እንጂ ዴሞክራሲያዊ ስርዓቱን<br />
ለመጠበቅ የተሰራ አለመሆኑን ነው፡፡ የምሁሩ ጥናት<br />
እንዲማሳየው የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት በኢትዮጵያ<br />
ለወደፊት የሚኖረውን ዕጣ ፈንታን በተነተኑበት<br />
ፅሁፋቸው እንደደመደሙት ኢህአዴግ በሥልጣን<br />
ላይ እስካለ ድረስ የመነመነ ነው፡፡ እኚህ የአንድነት<br />
ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ከፍተኛ<br />
አመራር እዚህ መደምደሚያ ላይ ያደረሳቸውን<br />
ምክንያት ሲገልፁ ገዢው ፓርቲ ከምርጫ 97<br />
ያልጠበቀው ሽንፈት ወዲህ ያፀደቃቸውን አፋኝ<br />
አዋጆችን ነው፡፡ አዋጆቹም የመገናኛ ብዙሃን<br />
አዋጅ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ማቋቋሚያ አዋጅ፣<br />
የሲቪክ ማኅበራት አዋጅና የፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ<br />
መሆናቸውን ይናገራሉ፡፡ የምሁሩ ጥናታዊ ፅሁፍ<br />
እንደተነተነው እነዚህ አራት አዋጆች በአገራችን<br />
የዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ለማጐልበት እንዲረዱ<br />
በማሰብ ሳይሆን የፀደቁት፣ ይልቁንም ኢህአዴግ<br />
አምባገነናዊ አውራ ፓርቲ ሆኖ እንዲቀጥል፣<br />
ተቺዎቹንና ተቃዋሚዎቹን ከፖለቲካው ጨዋታ<br />
ውጭ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ያሰምሩበታል፡፡<br />
ዶ/ር ነጋሶና አንቀፅ 29<br />
ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ የአንድነት ለዴሞክራሲና<br />
ለፍትህ (አንድነት) ፓርቲ ሊቀመንበር ናቸው፡፡<br />
የኢትዮጵያ ህገ-መንግሥት ከያዛቸው ከመቶ በላይ<br />
አንቀፆች መካከል አንቀጥ 29ን የበለጠ የሚወዷት<br />
ያስመስልባቸዋል፡፡ ፓርቲያቸውን ወክለው<br />
በተገኙበት ቦታ ሁሉ፣ በጋዜጠኞች ቃለ-መጠይቅ<br />
ሲደረግላቸው….. ሁልጊዜም አንቀጽ 29 ሳያነሷት<br />
አያልፉም፡፡<br />
ዶ/ር ነጋሶ “ሃሰብን በነፃነት የመግለጽ መብት ” የህገ-<br />
መንግሥት አርቃቂ ኮሚሽን ውስጥ በነበሩበት ወቅት<br />
የፀደቀ አንቀጽ ነው፡፡ሕገ-መንግስቱም በ1987 ዓ.ም<br />
በርሳቸው የመጨረሻ ፊርማ ፀደቀ፡፡ ፕሬዚዳንት<br />
ስለነበሩ፡፡ ትዝታቸውንና ተስፋቸውን ወደኋላ<br />
ተመልሰው ሲያስታውሱ “ዜጐች የተቃውሞም<br />
ይሁን የድጋፍ ሃሳባቸውን በነፃነት እንዲገልፁ<br />
ዋስትና እንዲሆናቸውና፤ የመንግስት መገናኛ<br />
7<br />
ብዙሃንን ጭምር ተጠቅመው ለሕዝብ ማድረስ<br />
ዕድል ይሰጣቸዋል” በሚል እንደነበር ይናገራሉ፡፡<br />
ሕገ-መንግሥቱ ሥራ ላይ ከዋለ አስራ አምስትና<br />
አስራ ስድስት ዓመታት በኋላና ከኢሕአዴግ የፓርቲ<br />
አባልነት ራሳቸውን ካገለሉ አስር ዓመታት በኋላ<br />
ግን፤ ተስፋቸው አይናቸው እያየ እንደጉም መትነኑን<br />
ይናገራሉ፡፡ ገዢው ፓርቲ ወደለየለት አምባገነንነት<br />
የገባው በዋናነት ከ1993 ወዲህ ሲሆን፣ በተለይ<br />
ግን ከምርጫ 97 ወዲህ መሆኑን ያስምሩበታል፡፡<br />
ለዚህ መከራከሪያም የሚያቀርቡት ማስረጃም ህገ-<br />
መንግሥቱንና የፀረ-ሽብርተኝነት አዋጁን በማነፃፀር<br />
ነው፡፡ “የህገ-መንግሥቱ አንቀጽ 29 ሃሳብን በነፃነት<br />
መግለፅን የሚያበረታታ ሲሆን፣ የፀረ-ሽብርተኝነት<br />
አዋጁ ግን ወንጀል የሚያደርግ ነው፡፡” ይላሉ፡<br />
፡ በኢትዮጵያ ዴሞክራሲዊ ሥርዓት ለመመሥረት<br />
እነዚህ ሁለት ህጐች ሊያበረክቱት የሚችለውን<br />
አስተዋፅኦ ሲያነፃፅሩት ደግሞ “አንቀጽ 29<br />
የሚያበረታታና ገንቢ ነው፡፡ አዋጁ ግን የሚገታ ብቻ<br />
ሳይሆን ዜጐች በፍርሃት እንዲኖሩ የሚያስገድድ<br />
ነው፡፡” በማለት ተናገሩ ፡፡ “የሚያሳዝነው<br />
ደግሞ አዋጁን እየጠቀሱ፤ አንቀጽ 29ን ሲጥሱ<br />
መመልከታችን ነው፡፡ የአንዱዓለም አራጌና<br />
የጋዜጠኛ እስክንድር ነጋም እስር የዚህ ውጤት<br />
ነው፡፡ ሁላችሁም በነበራችሁበት፣ በዚሁ መድረክ<br />
ላይ ሁለቱም ያሉት በአዲሱ ዓመት በ2004 ዓ.ም<br />
በአገራችን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመመሥረት<br />
በሰላማዊና ህጋዊ መንገድ ለመታገል እንዘጋጅ<br />
ነው፡፡ ይህ በህገ-መንግሥቱ የተረጋገጠ መብት<br />
ነው፡፡ ወንጀል አይደለም፡፡ ወንጀል የሚደረገው<br />
በኢሕአዴግ ነው፡፡” በእጃቸው መድረኩን እያሳዩ<br />
ንግግራቸውን ጨረሱ፡፡<br />
እንደምን አመሻችሁ ዲሽ የሌላችሁ<br />
ከአራት ኪሎ ተነስተው ፒያሳ እንደገቡ ቀዝቀዝ<br />
ያለ አየር በሚነፍስበት ጥግ ቀዝቀዝ ያለ ገበያ<br />
ያላቸው ሁለት ሱቆች ይታያሉ። የመጀመሪያው<br />
ሱቅ ስም አልባ ቢሆንም በመስታወቱ ወደ ውስጥ<br />
ዘልቆ አተኩሮ ለተመለከተ የኤሌትሪክ ዕቃዎች<br />
መሸጫ መሆኑን መለየት ይቻላል። ሁለተኛው ሱቅ<br />
አጠገብ ያለው ደግሞ ለብዙ ዓመታት መስታወቱ<br />
ላይ በለጠፈውና የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ድርጅት<br />
ለሚሰጠው አገልግሎት ከደንበኞቹ ክፍያ መቀበያ<br />
መሆኑን የሚገልፀው ማስታወቂያ ያለበት ቢሮ ነው።<br />
ዛሬ ግን አዲስ የሚመስል ነጭ ባነር ላይ “የቴሌቪዥን<br />
ባለቤትነት ማረጋገጫና የቴሌቪዥን አገልግሎት<br />
ክፍያ መሰብሰቢያ” መሆኑን የሚገልፅ ፅሁፍ ሻተሩ<br />
ላይ እንደነገሩ ተንጠልጥሎ ይታያል። በሩ ክፍት<br />
ነው። ሰው ሲገባም ሆነ ሲወጣ አይታይም። ክፍሉ<br />
ውስጥ የሚታየው ደብዘዝ ያለ ብርሃን ክፍሉን<br />
ህይወት አልባና ፈዛዛ ድባብ አላብሶታል። ፒያሳ<br />
ውስጥ ያለ አይመስልም።<br />
በ1957 ዓ.ም የተመሠረተው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን<br />
ዛሬም ድረስ ብቸኛውና በመንግስት ቁጥጥር<br />
ስር ያለ ጣቢያ ነው። ኢሕአዴግ ወደ ስልጣን<br />
እንደመጣ ነፃ ፕሬስ እንዲቋቋም ቢፈቅድም<br />
የኤሌክትሮኒክስ ሚዲያውን ግን ለግል ባለሃብቶች<br />
እንደማይፈቅድ በተደጋጋሚ ሲገልፅ መሰንበቱ<br />
ይታወሳል። ፓርቲው እዚህ አቋም ላይ የደረሰበትን<br />
ምክንያት ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያዎች በባህሪያቸው<br />
ሰፋ ላለው የህብረተሰብ ክፍል በቀላሉ መድረስ<br />
የሚችሉ በመሆናቸው እነሱን ተጠቅሞ የሚደረግ<br />
“ቅስቀሳ” አገሪትዋን ወደ መተላለቅና ወደ መበታተን<br />
ሊያደርሳት መቻሉን ነው። ነፃው ፕሬስስ ? እሱማ<br />
በከተሞች አካባቢና በተማረው የህብረተሰብ<br />
ክፍል ብቻ ተደራሽ በመሆኑ ያን የሚያህል<br />
አቅም አይኖረውም ተብሎ በመታሰቡ ነው።<br />
ይህ የተጠቀሰው የፓርቲው መሠረታዊ ፍልስፍና<br />
ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የተቀየረው ከ1997ቱ<br />
ምርጫ በኋላ ይመስላል።<br />
ወደ 14 ይዞሯል<br />
www.andinet.org.et
8<br />
ከመ/ር ደረጀ መላኩ<br />
www.andinet.org.et<br />
ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />
ኢትዮጵያውያን ሁሉ ኡኡ!<br />
ሪፖርተር ጋዜጣ ጥቅምት<br />
5, 2004 ቅፅ 16.ቁ.5/1197<br />
ግንባር ቀደም ዜናው ላይ<br />
ካራቱሪ የህንድ ገበሬዎችን ሊያሠፍር<br />
ነው በሚል ርእስ ስር ለኢትዮጵያ ህዝብ<br />
መርዶ አሰምቷል፡፡ አስደንጋጩ መርዶ<br />
የሚከተለውን ይመስላል፡፡<br />
ካራቱሬ አዲስ ባወጣው ህግ 20 ሺ<br />
ሄክታር መሬት ላይ የሕንድ ገበሬዎችን<br />
ለማሠራት ወስኗል፡፡ “ከገበሬዎቹ ቀና ምላሽ<br />
አግኝተናል፡፡ መሬቱን እውቀቱ ባላቸው<br />
ገበሬዎች እናለማለን” ሲሉ የኩባንያው ሃላፊ<br />
ገልፀዋል::<br />
“የገቢ ትርፋችን 65 በመቶ ለ35 በመቶ<br />
ሆኖ ከገበሬዎቹ ጋር ገቢውን እንጋራለን”<br />
ሲሉ ለህንዱ ቢዝነስ ስታንዳርድ ጋዜጣ<br />
ገልፀዋል፡፡ ገበሬዎችን ወደ ኢትዮጵያ<br />
የማምጣት ሂደት የሚቀጥል ሲሆን<br />
በሁለተኛው ዙር 50 ሺህ ሄክታር መሬት<br />
ላይ ተጨማሪ ገበሬዎችን እንደሚያስፍሩ<br />
ሀላፊው ተናግረዋል፡፡<br />
የኩባንያው እቅድ እንዳልገባቸው<br />
የጋምቤላ ምክትል ፕሬዜዳንት አቶ ጋነርየር<br />
ሲናገሩ “እኛ የምናውቀው ካራቱሪን<br />
እንጂ የሕንድ ገበሬዎችን አይደለም” ሲሉ<br />
አዲሱ እቅድ ግር እንዳሰኛቸው ገልፀዋል፡<br />
፡ በሌላ በኩል አገዛዙ በፌዴራል ግብርና<br />
ቢሮ ግብርና ኢንቨስትመንት ድጋፍ ሰጭ<br />
ዳይሮክቶሬት ዳይሪክተር በሚል ማዕረግ<br />
የሾማቸውን ግለሰብ ስማቸው አቶ ኢሳያስ<br />
ከበደ ይመስሉኛል አስተያየታቸውን<br />
ለማካተት የጋዜጣው ሪፖርተር ጥረት<br />
አድርጎ እንዳልተሣካለትም አስነብቦናል፡<br />
፡ ከቶ ለመሆኑ ይሄን ትልቅ ሀገራዊ ጉዳይ<br />
በተመለከተ የመአከላዊውን መንግስት አቋም<br />
የሚነግሩን ውጪ ሀገር ለስራ ጉዳይ የሄዱት<br />
ተሻóሚ ብቻ ናቸው? አይሠማም እየተባለ<br />
ነው? ግራም ነፈሰ ቀኝ በኢኮኖሚ ጉዳዮች<br />
ላይ የምታጠነጥ ነው ፎርቹን የእንግሊዝኞ<br />
ጋዜጣ ጥቅምት 5,2004 ዓ.ም እትሟ<br />
ላይ ስለዚሁ አሣሣቢ ጉዳይ ሰፊ ሽፋን<br />
ሰጥታ አስነብባናለች፡፡ አዎ የጋዜጠኞች<br />
ዋነኛ ሥራ እውነተኛ የዜና <strong>ምንጭ</strong> መሆን<br />
አይደል? በእውነቱ ለመናገር የሁለቱም<br />
ጋዜጦች አዘጋጆች አገራዊ ግዴታቸውን<br />
በመወጣታቸው ሊመሠገኑ ይገባል፡፡<br />
ይሄን ካልኩ ቀጥታ ወደ ተነሣሁበት ነጥብ<br />
ልውሰዳችሁ::<br />
እንደ ሥነ ህዝብ ጠበብት ከፍተኛ<br />
ስጋትና ጥናት ከሆነ ሀገሬ ኢትዮጵያ እጅግ<br />
በአጭር ግዜ ውስጥ ከ200 ሚሊዮን በላይ<br />
ህዝብ ይኖርባታል፡፡ አሁን 90 ሚሊዮን<br />
ደርሰናል፡፡ ዛሬ በወጣትነት እድሜ<br />
የሚገኙና ህፃናቶች ወደ እማይቀረው<br />
አለም ከመሄዳቸው በፊት ነው በኢትዮጵያ<br />
መሬት ላይ ከላይ የተጠቀሰው ህዝብ<br />
የሚኖርባት:: ለነገሩ የኢትዮጵያ መሬት<br />
ከተሠራበትና በሀገር ፍቅር ስሜት የነደደ<br />
እንዲሁም የተማረ እና በስልጣን ፍቅር<br />
ያለበደ መሪ ብታገኝ ከ40 ሚሊዮን በላይ<br />
ህዝብ እንደምት መግብ ብዙ ጠበብቶች<br />
የመሠከሩት ጉዳይ ይመስለኛል፡፡ ለዚህ<br />
አልታደልንም:: እና ዝንተ አለም ተመፅዋች<br />
ሆነን ቀርተናል፡፡ ያሳዝናል:: ሌላው ቀርቶ<br />
የሩቁን ትተን የቅርብ ጊዜውን ታሪካችንን<br />
ብንፈትሸው አንገት የሚያስደፋ ነው፡<br />
፡ ቀድሞ በየ አስርተ አመቱ (ከዚያ በላይ)<br />
እየመጣ የሚቀጣን ድርቅና ጠኔ ዛሬ<br />
“የዴሞክራሲ ስርዓት ጀማሪዎች ነን” እያሉ<br />
ሌት ተቀን በተቆጣጠሩት የኤሌክትሮኒክስ<br />
እና የህትመት መሣሪያዎቻቸው ዘወትር<br />
የሚወተውቱት ገዢዎቻችን ቃል እና ተግባር<br />
ያልተገናኙበት ጊዜና ሰዓት ላይ ደርሶናል፡፡<br />
እንደ አሰልቺ ዲስኩራቸው ቢሆን<br />
ኖሮ ሀገሬ ኢትዮጵያ ያልፍላት ነበር፡፡<br />
ከራሷ ልጆች አልፋ ለሌሎች ለተቸገሩ ቀን<br />
ለጨለመባቸው አለም ህዝቦች በደረሰች<br />
ማለት ይገባናል<br />
ነበር፡፡ ይህ ግን ከቶውንም ሲሆን አላየንም<br />
(አልሠማንም)፡፡<br />
በአንፃሩ ዜጎች “የዳቦ ያለህ” እያሉ<br />
ይጠይቃሉ፡፡ ወይንም ፈጣሪያቸውን<br />
ይማፀናሉ፡፡ “ምን አይነት ዘመን መጣን”<br />
በማለት በእውነቱ ለመናገር ካለፉት<br />
20 አመታት ጀምሮ እንደ ትሮይ ፈረስ<br />
የሚጋልቡን የደደቢት በርሃ ጨካኞችና<br />
ጋሻ ጃግሬዎቻቸው ለኢትዮጵያ ህዝብ<br />
ደረቅ ዳቦ እንኳን በስዓቱ ሊያቀርቡለት<br />
አልተቻላቸውም፡፡ ወይንም የስራ ጀግና<br />
የሆኑ ኢትዮጵያውያን በነፃነት ተንቀሳቅሰው<br />
ሊሰሩ የሚችሉበትን ሁኔታ ማመቻቸት<br />
አልቻሉም (አልፈለጉም)፡፡ ኢትዮጵያ እኮ<br />
የወላድ መካን አይደለችም፡፡ ብዙ ምርጥ<br />
ልጆች ሞልተዋታል፡፡<br />
በቅርቡ እንኳን ለአለም አዳጊ አገር<br />
ገበሬዎች መድህን የሆነ የአእምሮ ጭማቂ<br />
ከኢትዮጵያዊው ሣይንቲስት ፕሮፌሰር<br />
እጀታ ጋቢሳ እንደተገኘ አለም ሁሉ<br />
የሚያውቀው እውነት ይመስለኛል፡፡<br />
ኢትዮጵያ ግን ዛሬም ሊያልፍላት አልቻለም፡<br />
፡ ከቶ ለምን ይሆን? የፕሮፌሰሩ የትውልድ<br />
ቦታ ሣይቀር (ሆለታ) ሞልቶ የተረፈው<br />
አይደለም፡፡ መቀመጫቸውን ዴንማርክ<br />
ያደረጉት ፕሮፌሰር ማሞ ሙጬ በቅርቡ<br />
ስለ ኮምፒዮተር እና ኢንተርኔት አስፈላጊነት<br />
በጀርመን ድምፅ ተክሌ ይኋላ ጋር ቃለ<br />
ምልልስ አድርገዋል፡፡ ከቃለ ምልልሱ<br />
ለመረዳት እንደቻልኩት በ21ኛው ክፍለ<br />
ዘመን ያለ ኮምፒዩተር እና ኢንተርኔት<br />
እድገት ፈፅሞ አይታሰብም፡፡ ፕሮፌሰሩ<br />
ያላቸውን ጥልቅ እውቀት ለሀገራቸው<br />
እድገት ማዋል ባለመቻላቸው በሀዘን<br />
ሲናገሩም አድምጫለሁ፡፡ (የተጠቀሰውን<br />
ቴክኖሎጂ በኢትዮጵያ ለማስፋፋት<br />
ሁኔታው አመቺ ባለመሆኑ ለማት ነው)<br />
የደስታ እና አባ ሠንጋ በሽታ ክትባት ግኝት<br />
ባለቤት ፕሮፌሰር ጥላሁን ይልማ የት ገቡ?<br />
ከ30 ሚሊዮን በላይ የቀንድ ከብት ከ50<br />
ሚሊዮን በላይ ዶሮዎች …. ወዘተ ባለቤት<br />
የነበረችው ኢትዮጵያ ዛሬ ያ ሀብቷ አለን?<br />
በቦረና በሌሎች አካባቢዎች በድርቅ<br />
ምክንያት በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ እንስሶች<br />
ወደ ትቢያነት ሲቀየሩ አልሰማንም?<br />
አፍንጫችን ሥር ያለችው ኬንያ ከኢትዮጵያ<br />
ጋር በእንሥሳት ብዛት መወዳደር ቀርቶ<br />
የምትደርስባት አይመስለኝም፡፡ ሆኖም ግን<br />
በአለም ገበያ ላይ ጥራት እና ከፍተኛ ክብደት<br />
ያለው ስጋ እና የሥጋ ውጤቶች (ከኢትዮጵያ<br />
በብዙ የሚልቅ ማለቴ ነው) በየጊዜው<br />
ትልካለች፡፡ ዛዲያ ለምን ለእማማ ኢትዮጵያ<br />
ቀኑ ጨለመባት? ያለ ሥሟ ያለ ምግባሯ<br />
የድሆች ደሀ ብለው ስም አወጡላት?<br />
እንደሚመስለኝ ፕሮፌሰር ጥላሁን እና ሌሎች<br />
ኢትዮጵያውያን ሀገር ቤት እውቀታቸውን<br />
በተግባር እንዳያውሉ በሩ ስለተዘገባቸው<br />
ነው፡፡ በአለምም ሆነ በአፍሪካ ደረጃ በንብ<br />
አንቢነት ከሚተወቁት ሀገራት ኢትዮጵያ<br />
ግንባር ቀደም ሀገር ነበረች፡፡ እውን ዛሬ<br />
ታዲያ ልጆቿ የማር ተጠቃሚዎች ሆነዋል?<br />
መልሱን ለአንባቢ ትቼዋለሁ፡፡ ኬንያ<br />
ከኢትዮጵያ በተሻለ ሁኔታ የተማሩ ዜጎቿን<br />
በማቅረቧ (በመያዟ) ከኢትዮጵያ የተሻለ<br />
እድገት አሣየች፡፡ እኛ ግን ዛሬም እየዳከርን<br />
እንገኛለን፡፡ ታሪክ እንደሚያስተምረን<br />
በንጉሱ ዘመን ብዙ የተማሩ ኢትዮጵያውያን<br />
ሀገራቸውን ለማግለገል ፍላጐት ነበራቸው፣<br />
በደርግ ዘመን ፖለቲካውን ሣይተቹ<br />
በሙያቸው የቀጠሉ መስራት የተከለከሉ<br />
አይመስለኝም፡፡ በእርግጥ የደርግን መጥፎ<br />
ድርጊት በመቃወም ስፍር ቁጥር የሌላቸው<br />
ልጆቿ እንደ ጨው ዘር በአለም ተበትነው<br />
ቀርተዋል፡፡ ዛሬ ደግሞ የጎሣ ፖለቲካ<br />
ተጨምሮበት ከዚህ በፊት ታይቶ ተሠምቶ<br />
በማይታወቅ ሁኔታ ብዙ ምኹራን ሀገር<br />
ለቀው ሄደዋል፡፡ ኢትዮጵያን ከምኹራን<br />
ፍልሰት ለመታደግ ዘላቂ መፍትሄ የተገኘ<br />
አይመስለኝም፡፡ እንዲያውም ጉዳዩን<br />
የሚያባብስ ድርጊት ተፈፅሟል፡፡ ከ1985ቱ<br />
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች አመፅ<br />
በኋላ ከ45 በላይ የዩኒቨርስቲው ነባር<br />
እና ምርጥ መምህራን መባረራቸውን ልብ<br />
ይሏል፡፡<br />
ዛሬ ከሰውነት ደረጃ ዝቅ ብለን እንደ<br />
እንስሳ ዝርያ እየፈለግን መቧደናችን<br />
አሣዛኝም አሣፋሪም ነው፡፡ ከ1983ቱ<br />
የደርግ ውድቀት ወዲህ በእያንዳንዳችን<br />
አእምሮ ውስጥ የተዘራው የጎሳ ፖለቲካ<br />
ውጤት እየታየ ነው፡፡ በወቅቱ 20 አመት<br />
እድሜ የነበረን ዛሬ 40 አመት ሞልቶናል፡<br />
፡ 40 እና ከዚያ በላይ እድሜ የነበራችሁ<br />
ኢትዮጵያውያን የእድሜ ባለ ጸጎች 60<br />
እና ከዚያ በላይ ሆኗችኋል፡፡ ከቶ ምን<br />
ይሰማችሁ ይሆን? ያቺ የወተት እና የማር<br />
ሀገር እንዲህ ስትራብ ስትጠማ? ፍሪምባ<br />
ከቁርጥ አማርጣችሁ የተመገባችሁ እናንተ<br />
ኢትዮጵያውያን፣ በ25 ሣንቲም ክትፎ<br />
የበላችሁ የሀገሩ ሰዎች በእውን ኢትዮጵያ<br />
እንዲህ ነበረች ብሎ ለሚጠይቃችሁ<br />
የአሁኑ ጨለማና አሣፋሪ ጊዜ ሣይሆን<br />
ያኔ ! ጥንት በጃንሜዳ በጥምቀት እለት<br />
የሚደረገው የአንድነትና የፍቅር ዜማ ትዝ<br />
ይላቹህ ይሆን? በደርግ ዘመን እንኳን<br />
የ1975 ዓ.ም አካባቢ ጃንሜዳ ኢዲዩ ቤት<br />
የሚባል ምግብ ቤት ነበር፡፡ ዛሬ ስለመኖሩ<br />
አላውቅም፡፡ ክትፎ ላይ የተጨመረው ቅቤ<br />
አነሰኝ ለሚል ደምበኛ ቅቤ በማንቆርቆሪያ<br />
እየዞረ የሚጨምር እንደነበር በአይኔ<br />
በብረቱ አይቻለሁ፡፡ ለዛውም ንፁህ የሸኖ<br />
ቅቤ፤ ዋጋው ቢበዛ 10 አሊያም ከ15 ብር<br />
አይበልጥም ነበር፡፡ ኢትዮጵያ ሀገራችን<br />
የባህር በሯን በማጣቷ የጂኦ ፖለቲካዊ<br />
ጠቀሜታዋ ከላይዋ ላይ ከተገፈፈ በኋላ<br />
የተፈጠራችሁ ደግሞ 20 አመት እድሜ ላይ<br />
የደረሳችሁ እናንት ሦታ ወጣቶች እኔ ማን<br />
ነኝ? የሚለውን ጥያቄ ለራሳችሁ አቅርባቹሁ<br />
ታውቁ ይሆን? አዎ እናንተ የባለ ታሪክ<br />
ኢትዮጵያ ልጆች መሆናችሁን ለአፍታም<br />
ቢሆን መዘንጋት የለባችሁም፡፡ የጎሳ ፖለቲካ<br />
ሊያጠምቃችሁ የሚፈልገውን እኔ ሰው<br />
ነኝ በማለት መከራከር ይገባችኋል፡፡ በጎስ<br />
ሥርዓት ውስጥ የተፈጠራችሁ በመሆናችሁ<br />
ጎሰኝነት ሊጣባችሁ ይችል ይሆናል፡፡ ግን<br />
ራሳችሁን በራሳችሁ ከቶባችሁ ከጎሳ በሽታ<br />
ተላቀቁ፡፡ የብሮዝ ቲቶ ሀገር የነበረችው<br />
ይጎዝላቪያና የብሬዥኔቭ ሦቬየት ህብረት<br />
እንዴት (ለምን) እንደተፈረካከሱ ታሪክን<br />
መመርመር ተገቢ ነው፡፡ (ታሪክን መርምሩ)<br />
ታላቁ የአፍሪካ ልጅ ኒልሰን ማንዴላ ለምን<br />
አለም አቀፍ እውቅና እና ክብር ተሰጣቸው<br />
ብላችሁ ጠይቁ፡፡<br />
ስማቸውን በወርቅ ቀለም ያፃፉት<br />
የሠላማዊ ትግል አስተማሪዎች የሆኑትን<br />
ማህተም ጋንዲና ማርቲን ሉተር ኪንግን<br />
የህይወት ታሪክ አንብቡ፡፡ እነ ወጣት<br />
አቢቹ፣ ደጃች በላይ ዘለቀ፣ ኮሎኔል አብዲሳ<br />
አጋ፣ ጄኔራል ተሾመ መተኪያ የሌላቸውን<br />
ወድ ህይወታቸውን ለምን ለኢትዮጵያ<br />
ሰውላት ብላችሁ ተመራመሩ፡፡ ጠይቁ?<br />
የትናቷ ኢትዮጵያ ማር ወተት ቅቤ ነበረች፤<br />
ጮማ ነበረች፤ ለዚች ቅዱስ ሀገር ነበር አፄ<br />
ቴዎድሮስ ሽጉጥ ጠጥተው ለክብሯ ሱሉ<br />
ሕይወታቸውን ያሳለፉላት፡፡ የሳቸውን<br />
ፈለግ ተከትለው ሌሎቹም የሚሰውላት<br />
በመሆኑም ይህ ትውልድም የሀገሩ ባለቤት<br />
ለመሆን ራሱን መጠየቅ አለበት፡፡ አለበለዚያ<br />
ጎሰኞች በጀመሩት ዕቅድ የሚገፉበት ከሆነ<br />
(ከመግፋትም አይመለሱም) ከጥቂት<br />
ዓመታት በኋላ የሕንድንና የቻይናን<br />
ቱጃር እያሰፈሩ አገር አልባ አድርገው<br />
እንደሚያስቀሩን ቅንጣት አትጠራጠሩ፡፡<br />
በመሆኑም ጎሳ ሳንለይ እጅ ለእጅ እንያያዝ፡፡<br />
ሰላማዊ ድምፃችንን በኡኡታ! እናሰማ፡፡<br />
የአደባባይ ምስጢሮች<br />
2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />
“ነፃ የሚያወጣኝ<br />
መድረክ ነው<br />
መሰለኝ”<br />
“ኦነግን ሳላውቅ የኦነግ አባል የሆንኩ መሰለኝ” የሚለውን<br />
ቃል የተናገሩት ከዛሬ ዘጠኝ ዓመት በፊት አንድ የዩኒቨርስቲ<br />
መምህር ናቸው፡፡ በ1994 ዓ.ም ክረምት ላይ ጠ/<br />
ሚኒስትር መለስ ዜናዊና አቶ ተፈራ ዋልዋ የከፍተኛ ትምህረት<br />
ተቋም መምህራንን ረዘም ላሉቀናት ያወያዩ ነበር፡፡ አንድ<br />
የዩኒቨርስቲ መምህር የኢህአዴግን የፍረጃ ፖሊሲ ለመግለጽ<br />
ሲሉ የተጠቀሙበት ቃል ነበር፡፡ “እኔ የማንም ድርጅት አባል<br />
አይደለሁም፡፡” አሉ መምህሩ ሲናገሩ “የማንም ድርጅት<br />
አባል ለመሆን እቅድም የለኝም፡፡ ሐሳቤን በነፃነት እሰጣለሁ፡፡<br />
የማላምንበት ነገር በነፃነት እከራከራለሁ፡፡ ኦሮምኛ ቋንቋ ተናጋሪ<br />
ብቻ በመሆኔ የኢህአዴግ አባላት “የኦነግ አባል የኦነግ አባል!<br />
እያሉ አሉኝ፡፡ ኦነግን እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ እንጂ በቅርብ<br />
አላውቀውም፡፡ ኦነግ የእኔን ሐሳብ የሚያራምድ ድርጅት ነው?<br />
ብዬ እንዳስብ እድርጐኛል፡፡ ኦነግን ሳላውቀው የኦነግ አባል<br />
ሆንኩኝ እያልኩ አሰላስላለሁ” በማለት ጠ/ሚኒስትሩ ባሉበት<br />
መናገራቸውን አስታውሳለሁ፡፡<br />
ዛሬ ይህ ትዝ ያለኝ በተለያየ ጊዜ የተለያየ ስም እየተሰጣቸው<br />
ተከሰው በነፃ ስለሚወጡ ሰዎች ሳስብና እንዲሁም ጐንደር<br />
ላይ የገጠመኝ አንድ ገጠመኝ ትዝ ብሎኝ ነው፡፡ ኢህአዴግ<br />
ሥልጣን እንደያዘ አካባቢ አምርረው ኢህአዴግን የተቃወሙ<br />
ደርግ ኢሠፓ ቀይ ሽብር እየተባሉ ወህኒ ወረዱ፡፡ በአንድ ወቅት<br />
ደግሞ መአህድ ሌላ ጊዜ ሌላ ስም እየተሰጠ ይታሰራሉ፡፡ አልፎ<br />
አልፎ የህሊና ዳኛ ሲገጥማቸውም በነጻ ሲለቀቁ እሰማለሁ፡<br />
፡ ዛሬ ደግሞ ጊዜው መድረክ ሆኖአል፡፡ በአንድ ወቅት ደቡብ<br />
ጐንደር ደብረታቦር ከተማ የሰማሁትን ገጠመኝ ላካፍላችሁ፡፡<br />
ከአካባቢው ገጠራማ ቦታ የመጡ አንድ አርሶ አደር አግኝቼ<br />
ተግባባንና ጫወታ ጀመርን፡፡ ስለ ወቅቱ ዝናብ፣ ስለሰብሉ፣<br />
ስለማዳበሪያው ዋጋ ሌላው ሌላውንም አንስተን በመጨረሻው<br />
ወደ ፖለቲካው ገባን፡፡<br />
“ካድሬው አላስቀምጥ አላሰራ አለን፡፡ “አዲሱ እረኛ<br />
ከብትም አያስተኛ” እንደሚባለው አንዱን አውርደው አንዱ<br />
ሲሾም ጥዋት ማታ ሰብስባ ወሬ ጭቅጭቅ ነው፡፡ የተስፋ ወሬ<br />
ነው፡፡ የማዳበሪያው ዋጋ ሰማይ ወጣ ምንም የሚበጀን ነገር<br />
አላገኘንም፡፡ ቅንጅት ይመጣል ብለን ስንጠብቅ በዚያው ቀረ፡<br />
፡ ሰሞኑን ደግሞ መድረክ እየተባለ ነው፡፡ ምናልባት እንግዲህ<br />
መድረክ ነፃ ያወጣን እንደሆነ በተስፋ እየጠበቅን ነው፡፡<br />
አሉኝ እኔም ተገርሜ መድረክ እዚህ አለ እንዴ? አልኳቸው<br />
“ኽረ የለም” ሲሉ መለሱልኝ፡፡ ለእናንተ የሚበጅ ወይም<br />
የማይበጅ መሆኑን እንዴት አወቃችሁ አልኳቸው “ወያኔ ራሷ<br />
ትነግረናለች” አሉኝ፡፡ እንዴት አልኳቸው “ወያኔ ከመጣችበት<br />
ዘመን ጀምሮ የተረፈን ወሬዋ እና ውሸቷ ነው፡፡ የተረፈን፡፡<br />
ያገኘነው፡፡ ድህነትና ውርደት ነው፡፡ ሁሉም ነገር ተወደደ፤<br />
ገንዘብ አምጡ አምጡ ነው፡፡ ሰለቸን፤ የሚያሽንፋቸውና<br />
ለእኛ የሚበጀን ድርጅት ብቅ ሲል ሬዲዮኑም ካድሬውም<br />
ጥዋት ማታ ስም እየጠራ ይሳደባል፡፡ ተጠንቀቁ መጣባችሁ!<br />
ሊያጠፋችሁ ነው! እያለ እንደ ልጅ ሊያታልለን ይሞክራል<br />
ቅንጅት በነበረ ወቅት ቅንጅትን አውሬ አስመስሎ ሲነገረን ነበር፡<br />
፡ ኋላ ላይ ስንሰማ እንዲያ የጠሉት የእኛን ጥያቄ ስለሚያነሳ<br />
ነው አሉ፡፡ አሁን ደግሞ መድረክን እያሉን ነው፡፡ ታዲያ እኛም<br />
ሰማን ሰማንና ጐበዝ ይኽ መድረክ የሚሉት ደግሞ እኛን ነፃ<br />
የሚያወጣን ይሆናል ብለን አመንን፡፡ ለዚህ ነው መድረክ ጥሩ<br />
ነው ያልኩህ” ሲሉ አጫወቱኝ፡፡ “እነሱ ከጠሉት የእኛ ነው<br />
ማለት ነው፡፡” ሲሉ በለሆሳስ ነገሩኝ፡፡
2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />
ከአሸናፊ ደስታ ወንድም አገኘሁ<br />
ወቅታዊ<br />
ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />
ሕወሓት ከደደቢት በረሀ መርሾ<br />
ማሃል አገር ገብቶ ዙፋን ላይ ከተቀመጠበት ጊዜ<br />
ጀምሮ በኢትዮጽያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ ብዙ<br />
ፍንዳታዎች ፈንድተው በብዙ ሚሊዮን ብር<br />
የሚገመት የኢትዮጵያ ሕዝብ ንብረት ወድሟል፡<br />
፡ በሰው ሕይወት ላይም እንዲሁ ብዙ ጉዳት<br />
ደርሷል፡፡<br />
ምንም እንኳን በዩኒበርሲቲው ላይ<br />
የሳት ቃጠሎ ባይደርስበትም፣ “የአገሩን ሠርዶ<br />
በአገሩ በሬ” በሚለው የአበው አባባል፣ባዕዳን<br />
መምህራንን ተክተው ሲያስተምሩ የነበሩ<br />
አንቱ የተባሉ አያሌ እውቅ ፕሮፌሰሮች ከሥራ<br />
ገበታቸው ተባረዋል፡፡ ይህም በራሱ በወቅቱ<br />
በትጉ መምህራን ሽብርና መቅሰፍት ነበር፡፡ በዚያን<br />
ወቅት በዩኒቨርስቲው ውስጥ የተወሰደው ርምጃ<br />
የመንፈስ ስብራት ዛሬም ድረስ ሊቃና አልቻለም፡፡<br />
ያወቅት በጣም አስጊ እና አደጋ<br />
የበዛበት ወቅት ስለነበር፣በወቅቱ የተባበሩት<br />
መንግሥታት ዋና ጸሐፊ የነበሩት የግብፅ ተወላጅ<br />
ቡትሮስ ቡትሮስ ጋሊን ለጉብኝት ወደ አዲስ አበባ<br />
መምጣት ተቃውሞው ሰላማዊ ሰለፍ በወጡ<br />
ተማሪዎች ላይ የጥይት በረዶ ተርከፍክሮባቸው<br />
ተገድለዋል፡፡ ተማሪዎቹ ሰላማዊ ሰልፍ የወጡበት<br />
ምክንያት ግልጽ ስለሆነ፣ከመናገር ተቆጥበን<br />
አልፈነዋል፡፡<br />
ወደ ተነሳሁበት ዋና ነገር ልመለስና<br />
የመጀመሪያው የአዲስ አበባ ነዋሪ ሕዝብ<br />
በሽብር ያናወጠው፣ማቄን ጨርቄን ሳይል<br />
ቤቱን ሳይዘጋ የሌሊት ልብሱን እንደለበሰ፣ቀበሮ<br />
እንደ ገባበት የበግ መንጋ ወደ እየአቅጣጫው<br />
ያስፈረጠጠው፣ከባድ፣እጅግ በጣም ከባድ ፈንዳታ<br />
ነፋስ ስልክ አካባቢ የፈነዳው ፍንዳታ ነበር፡፡<br />
በዚያ አደጋ በተጋለጠ ስፈራ ላይ ያ<br />
ፈንዳታ እንዲፈነዳ የተደረገው በዐፄ ኃ/ሥላሴ<br />
ዘመነ መንግሥት ተገንብቶ አገልግሎት በመስጠት<br />
ላይ የነበረን የሥንቅና ትጥቅ ዴፖ ለማውደም<br />
ሲሆን አጋጣሚ ሆኖ በዚያ አካባቢ ይኖሩ በነበሩ<br />
ነዋሪዎች ላይም በርካታ ቤቶች ተደርምሰዋል፡፡<br />
በቃጠሎ ወድመዋል፡፡ ይህ ነው የማይባል ንብረት<br />
ወድሟል፡፡ የሰው ሕይወት ሳይጠፋ አንዳልቀረም<br />
ተገምቷል፡፡<br />
ከላይ አንብበን እንደመጣነው<br />
ያ ወቅት በሳልና ጠሬውን ለመለየት ወይንም<br />
ማን ምን እንደሆነ ለይቶ ለማወቅ አስቸጋሪ<br />
የሆነበት ወቅት ስለነበር በፈንዳታው ፍንጣሪዎች<br />
ቤቶቻቸው የተደረመሱባቸው፣የተቃጠሉባቸውና<br />
ንብረቶቻቸው የወደሙባቸው አባወራዎችና<br />
እማወራዎች ዋይታ ሲያሰሙና ሲያነቡ<br />
የሚታዩበት ወቅት ነበር፡፡<br />
ስውር ደባ<br />
እነ አጅሬም ፍንዳታው በደረሰበትና<br />
በፍንዳታው በተደረመሱና በቃጠሎው<br />
በነደዱ ቤቶች ዙሪያ ወይም አካባቢ ቁምጣ<br />
ሱሪዎቻቸውን ታጥቀው፣ነጠላ ጫማዎቻቸውን<br />
ተጫምተው አንዳንዶቹ ፎጣቸውን ከአንገታቸው<br />
ላይ ጠምጥመው አንዳንዶቹ ደግሞ ፎጣቸውን<br />
ከራሳቸው ላይ ጠምጥመውና ጠብመንጃቻቸውን<br />
አንግበው፣የዚያን ከባድ ፍንዳታ ውጤት<br />
ለማየት ይርመሰመስ የነበረውን ሕዝብ “ወደዚያ<br />
ሂድ፣ወደዚህ አትጠጋ፣ወደዚህ አትቅረብ” እያሉ<br />
ይገረምሙ ነበር፡፡<br />
ከዚህበላይ ነግረን እንዳመጣነው፣ያ<br />
በከባድ ፈንዳታ የጋየ የሥንቅና ትጥቅ ዴፖ በዐፄ<br />
ኃ/ሥላሴ ዘመን መንግሥት የተገነባ፣ለሠራዊቱ<br />
ሥንቅ እንዲሆን ተዘጋጅተው የተቀመጡ ልዩ<br />
ልዩ የምግብ ዓይነቶች፣ልዩ ልዩ ጥይቶችና ልዩ ልዩ<br />
የጦር መሣሪያዎች የተከማቹበት<br />
ዴፖ ነበር፡፡ ይህም የዚች ሀገር ሀብት እንጂ<br />
የንጉሱ ወይንም የደርግ የግል ሀብት አልነበረም፡<br />
፡ ግን አጋጣሚውን ተጠቅሞ ሰርጎ የገባ<br />
ወይንም ከሕወሓት ጋር ተቀላቅሎ የመጣ ጠላት<br />
አቃጠለው፡፡ መጠነ ሰፊ የሕዝብ ንብረትም<br />
ወደመ፡፡ ይህም በዚያን ጊዜ የከፋና አስደንጋጭ<br />
ሽብር ነበር፡፡<br />
በኢትዮጵያዊነቱ ለሚያምንና<br />
የተከማቸን ብረትን ማውደም፣የአገር ቁርስን<br />
ማውደም መሆኑን ለሚያውቅና ለአገሩ<br />
ተቆርቋሪ ለሆነ ዜጋ፣የዚያ ሁሉ ንብረት<br />
መውደም፣ሳይቆጨውና ሳያንገበግበው<br />
እንደማይቀር ርግጠኛ ሆኖ መናገር ይቻላል፡<br />
፡ ይሁንና፣የፈሰሰ አልታፈሰ ነውና ከሚንቀለቀል<br />
እሣት ውስጥ እንደ ተጣለ ጅማት አሮ ተኮማትሮ<br />
ዝም ከማለት በስቀተር ሌላ መንም ለማድረግ<br />
ስለማይቻል እንደ ጅማቱ አረን ተቀብለነዋል፡፡ ዛሬ<br />
አገራችን ለኛ ባእድ እየሆነች ነው፡፡<br />
እንደሚታወቀው የነፋስ ስልክ አካባቢ<br />
ለአደጋ የተጋለጡ የነዳጅ ማደያዎች፣የእህል<br />
ጐተራዎች፣ከዕለት ጉርሳቸው በስተቀር ሌላ ቋሚ<br />
ንብረት የሌላቸው ባለብዙ ቤተሰብ አባውራዎች<br />
የሚኖሩበትና የኤሌክትሪክ መሥመር የተዘረጋበት<br />
በቀር ወረቀት አያሌ ሕፃናት የሚኖሩበት ት/<br />
ቤቶች ያሉበት በመሆኑ ለሽብር የተጋለጠ ነው፡፡<br />
ስለሆነም ነው የጦር መሣሪያ የተከማቸበት ዴፖ<br />
እንዲቃጠል የተደረገው፡፡<br />
ይህ ሁሉ ሆኖ አልፏል፡<br />
፡ የፈነዳ ፈንድቷል፤የወደመ ንብረትም<br />
ወድሟል፤የተቃጠለም ተቃጥሏል፡፡ የሞተ<br />
ሙቷል፣ግድ የለም፡፡ “በጊዜ ለኩሉ እንዳለው<br />
ቅዱስ ዳዊት” ለሁሉም ጊዜ ስላለው ጊዜው ሲደርስ<br />
የሚጠየቀው አጥፊ ይጠየቃል፡፡ ቢያንስ በታሪክ<br />
እንዲቀመጥ ይደረጋል፡፡ ደባውን ትውልድ<br />
እንዲያውቀው ተጽፎ ይቀመጣል፡፡<br />
ሁለተኛው ከባድ ፍንዳታ በሽሮሜዳ<br />
አካባቢ በአንድ የልዩ ልዩ ቁሣቁሦች ማከማቻ<br />
የፈነዳው ፍንዳታ ነበር፡፡ ምክንያቱ ከመጋዘኑ<br />
ውስጥ የነበሩ ልዩ ልዩ ፈንጂዎችና ሌሎች ልዩ ልዩ<br />
መሣሪያዎች ፈንድተው የአያሌ ሰዎች ሕይወትና<br />
ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሶ አልፏል፡፡<br />
ይህም በዚያን ወቅት የከፋ ሽብር ነበር፡፡<br />
ሦስተኛው ፍንደታ በለደታ<br />
ቤተክርስቲያን ማዶ ከባለወልድ ቤተክርስቲያን<br />
ዝቅ ብሎ ባሉት ቤቶች ውስጥ ከዐፄ ኃ/ሥላሴ<br />
ዘመነ መንግሥት ጀምሮ ጥይት ይከማችባቸው<br />
ስለነበር ያ ሁሉ ጥይት እንዲፈነዳና በአካባቢው<br />
ነዋሪ ሕዝብ ላይ ጉዳት እንዲያደርስ ሆነ ተብሎ<br />
እሳት በመለኮሱና በጥይቶቹና ሌሎች ፈንጂዎችም<br />
በመፈንዳታቸው የጥይቶቹ አረሮችና የሌሉች<br />
ፈንጀዎች ፈንጣሪዎች በሰው ሕይወትና በንብረት<br />
ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል፡፡ ይህም አሳፋሪ<br />
ሽብር ነበር፡፡<br />
ሌላውና አራተኛው ፍንዳታ የደረሰው<br />
ፒያሣ አካባቢ መብራት ኃይል መሥሪያ ቤት በስተ<br />
ጀርባ ትግራይ ሆቴል እየተባለ ይጠራ በነበረውና<br />
የትግሬዎች ዋና መናሐሪያ በነበረው ሆቴል<br />
ውስጥ የፈነዳ ቦመብ ሲሆን፣ሆቴሉ ከምድር<br />
ቤቱ አንስቶ ፎቆ ድረስ በቃጠሎ ወድሟል፡<br />
፡ በዚያ ወቅትም በሆቴሉ ውስጥ ይዝናኑ የነበሩ<br />
በርካታ ዜጎች ሞተዋል፤እንዲሁም ከፎቁ ላይ<br />
ተኝተው በነበረው ከምድር ቤቱ ውስጥ ሲጠጡ<br />
በነበሩትና በአሰላፊዎቹ ላይ ቃጠሎና የሞት<br />
አደጋ ደርሶባቸዋል፡፡ ቤቱም በጣም ወድሞ<br />
ስለነበር፣አሁን ከቦታው ላይ ሌላ ትልቅ ፎቅ<br />
ተሠርቶ ከሆቴል ቤትነት ወደ ሌላ ሸቀጣሸቀጥ<br />
ንግድ ቤትነት ተለውጦ በመሥራት ላይ ይገኛል፡፡<br />
በጣም የሚያስገርምና በጣም<br />
የሚያሳዝነው በዚያ ግዙፍ ሆቴል ላይ ያ ሁሉ<br />
ቃጠሎ ሲደርስ፣ያ ሁሉ ንብረት ሲወድምና በሰው<br />
ሕይወት ላይ የሞት አደጋ ሲደርስ ምክንያቱ ምን<br />
እንደሆነ አይታወቅም፡፡ አለመታወቁ ብቻ ሣይሆን<br />
ለማወቅም ጠረት አለመደረጉ አስገራሚ ድራማ<br />
ነው፡፡ ምኒልክ ዐደባባይ የሚገኘው በእሳት አደጋ<br />
ጣቢያ በወቅቱ ደርሶ ቃጠሎውን ለማጥፋትና<br />
የሰው ሕይወትና ንብረት ለማዳን፣አልሞከረም፡<br />
፡ ከጥፋቶቹ ብርቱ ክንድ ከበስተ ጀርባ እንዳለ<br />
በቂ ማሣያ ነው፡፡ አጥፊው አለመታወቁም በራሱ<br />
ሽብር ነው፡፡<br />
9<br />
ሌላው በጣም አሳዛኝ ወይም ሳይወሳ መታለፍ<br />
የሌለበት አንገብጋቢ ጉዳይ ትምህርቷን ጨርሳ<br />
የመመረቂያ ጊዜዋ ደርሶ ወላጆቿን ጠይቃ<br />
ለመመለስ ወደ ቦሌ በመጓዝ ላይ እንዳለች ውጭ<br />
ጉዳይ ሚኒስቴር ዝቅ ብሎ ቤተ መንግሥት አካባቢ<br />
ስትደርስ ከሚኒባሱ ውስጥ ተጠምዶ የነበረ ቦምብ<br />
ፈንድቶ ካሉት ተሳፋሪዎች ጋር አብራ የተቀሰፈችው<br />
ልጃ ገረድ ናት፡፡ ሌሎችንም፣አሷንም፣ልዑል<br />
እገዚአብሔር ነፍሳቸውን ይማር እንላለን፡፡ ይኸም<br />
በወቅቱ አሣፋሪ ሽብር ነበር፡፡ ብቻ ኢህአዴግ<br />
በሥልጣን ላይ ከወጣ ጀምሮ ከጥፋትና ከሽብር<br />
ወጥተን አናውቅም፡፡ መሸም ነጋም ሽብር ነው፡፡<br />
ዛሬም ከሽብር አልወጣንም፡፡ ነገር፣ኪነጋ ወዲያም<br />
አንወጣም፡፡<br />
ሌላው ሳይወሳ ተዘሎ መታለፍ<br />
የሌለበት ታሪካዊ ጉዳይ በሰማይ ነፈሳቸውን<br />
ይማረውና የመላው አማራ ድርጅት የተባለ<br />
የፖለቲካ ፓርቲ አቋቁመው ባያተርፉት ኖሮ<br />
የብሔርን ትርጉም ጠንቅቀው የማያውቁ ጐሰኞች<br />
የቀበሌ መታወቂያ ላይ “ብሔር አማራ” የሚል<br />
ቅጽል የተሰጠው የኢትዮጵያ ዜጋ መጨረሻው ምን<br />
ይሆን ነበር? የሚል ጥያቄ ማስከተሉ አይቀርም፡፡<br />
በ1984 ዓ.ም የተባለው ድርጅት<br />
ተቋቁሞ የብዙ ንጹሐን ዜጐች ሕይወት<br />
እስከታደገበት ጊዜ ድረስ አያሌ ንጹሐን ዜጐች<br />
ተገድለዋል፤ወደ ገደል ተጥለዋል፤አሰቦት የተባለ<br />
ገዳም ተቃጥሏል፤ገዳሙን ሲያገለግሉ የነበሩ<br />
መነኮሳትም ተገድለዋል፡፡ ይህም በታሪክ ልንረሳው<br />
የማንችለው ክፉ የዘር ሽብር ነበር፡፡ በአማራ<br />
ሕዝብ ላይ የተፈፀመ ሁለገብ ዘመቻ ትውልድ<br />
በክፋቱ ሲያወሳው የሚኖር ከሽብሮች ሁሉ<br />
የከፋው ሽብር ነበር፡፡<br />
በመሠረቱ ሕወሓት አዲስ አበባን<br />
ከረገጠበት ወቅት አንስቶ የተለያዩ ሽብሮች<br />
ተካሒደዋል፡፡ ለነዚያ አያሌ የሰው ሕይወትና<br />
የንብረት ውድመት ለደረሱት ሽብሮች ኃላፊነትን<br />
የወሰደ ግለሰብ፣ቡድን ወይም ድርጅት ግን<br />
እስካሁን ድረስ አልተገኘም፡፡<br />
ስለዚህ ክቡር የሰው ሕይወትና ንብረት እንደ<br />
ወደመ ታፍኖ ይቅር የሚል ሕግ ስለሌለ የሕግ<br />
ልዕልና የሚያከብርና ሐቅን የሚከተል አካል እስከ<br />
ሚገኝ ድረስ ወይም በሌላ አነጋገር ኢህአዴግ<br />
በሥልጣን ላይ እስካለ ድረስ ታፍኖ ይቆያል፡፡<br />
እስከዚያው ግን ከሽብር ማጥ ውስጥ መውጣት<br />
አንችልም፡፡ በመሆኑም ልዑል እግዚአብሔር<br />
እንዲገላግለን እሱን መማፀን ተገቢ ነው፡፡<br />
ከሲኦል ያመለጡ የኢህአዴግ አባላት<br />
ከመ/ር ቀለሙ ሁነኛው<br />
በአንድ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ<br />
ዜናዊ “የኢህአዴግ ስልጣን ዛፍ ላይ ወጥቶ እንደ<br />
ማንቀላፋት ነው ይሉና ፍሬውን ለቅመው ይወርዳሉ”<br />
ሲሉ በተሻDሚዎቻችው ላይ አፊዘው እንደነበር<br />
ሰምቻለሁ፡፡ መዳፈር አይሁንብኝና በራሳቸውም ላይ<br />
ያፌዙ ይመስለኛል፡፡ ፍሬውን የለቀሙት ግን እነማን<br />
ናቸው? በአርግጥም የዛፍ አናት ላይ ቁጢጥ ያሉት<br />
ለበሰለው ፍሬ እጅግ የቀረቡ በመሆናቸው እንዳሻቸው<br />
እጃቸውን እየዘረጉ ለቅመዋል፤እየለቀሙም ነው፡<br />
፡ ከታች ያሉት ተሻሚዎች ደግሞ ከጌቶቻቸው<br />
የተራረፈውን ለመቃረምም ይሁን ከቅንነት በመነጨ<br />
አመለካከት የኢህአዴግን ልማታዊ መንግሥትነት<br />
ለመደስኮር እንደ ክልፍልፍ ውሻ ነጋ ጠባ በየመንደሩ<br />
ሲዘሩ ያተረፉት ቢኖር “ዘመናዊ ቆራሊዮ”የሚል<br />
ስያሜ ነው፡፡ አሁንማ በየወረዳው የተሾሙ<br />
ካቢኔዎችና ግንባር ቀደም ካድሬዎች ውሎአቸው<br />
በየመንደሩ መሆኑ ክፉኛ አማሯቸዋል፡፡ ከዚህ<br />
አንፃር በግምገማም ይሁን በተገኘው ቀዳዳ ሾልከው<br />
መውጣትን ይሻሉ፡፡ በብዛትም እየወጡ ናቸው፡፡<br />
በቅርቡ ከአመራርም ሆነ ከአባልነት የተሰናበቱና<br />
ወደ ቀድሞ ሥራቸው የተመለሱ “ከሲኦል ያመለጡ”<br />
ወጣቶች በግልፅ ይናገራሉ፡፡ ከእስር እንደተፈታ ሰው<br />
ነው ራሳቸውን የሚቆጥሩት፡፡ በየአደባባዩም “እንኳን<br />
ደስ ያለህ/ያለሽ!” ሲባባሉ ይሰማል፡፡ በተለይም በየወሩ<br />
ከደመወዛቸው የሚቆረጠው ገንዘብ፣የጋዜጣና<br />
የመፅሄት ክፍያ በአባላቱ ቋንቋ” የማይደርስ ዕቁብ”<br />
የሚሉት የድርጅቱ ክፍያ፣የሕዳሴው ግድብ መቶ<br />
ፕርሰንት መዋጮ . . . /የሕዳሴው ግድብ መዋጮ<br />
ከኛም ደመወዝ በግዴታ መወሰዱ ሳይዘነጋ/<br />
ኑሮአቸውን ከማቃወሱ ባሻገር በገንዘባቸው ላይ<br />
ማዘዝ የማይችሉ እንደነበረ በምሬት ይገልፃሉ፡<br />
፡ ይበልጥ ደግሞ ፋታ የማይሰጠው የኢህአዴግ<br />
ግምገማ ከሰውነት ተራ አውጥቷቸዋል፡፡ የወጣትነት<br />
ሞራላቸውን ያላሸቀ ግምገማ እጅግ አድርጎ<br />
ከርፍቷቸዋል፡፡ በራስ የመተማመን ስሜታቸውን<br />
ክፉኛ ጎድቶታል፡፡ የዚህ አስተያየት ፀሐፊ እነዚህ<br />
ወጣቶች የስነ ልቡና ሀኪም እንደሚያስፈልጋቸው<br />
ያምናል፡፡<br />
ከሲኦል ካመለጡ ወጣቶች አንዳንዶቹ ካወጉልኝ<br />
ገጠመኞቻቸው መሀከል ባንድ ወቅት የኢህአዴግን<br />
የፖለቲካ መስመር ለመስበክ በየመንደሩ እየዞሩ<br />
በር ሲያንኳኩ አንዲት እማወራ “ኽረ ውሾቹ<br />
እንዳይነክሷቸው” ሲሉ አባወራው ቀበል አድርገው<br />
“ምንነካሽ?! ውሾቹ ከእኛ ይልቅ የሚያውቁት እነሱን<br />
አይአለም እንዴ?!” ያሏቸው ከልብ አስደንቆኛል፡፡<br />
በ2002 ምርጫ ወቅት ጠቅላይ ሚንስትሩ<br />
ሳይቀሩ የኢህአዴግ አባላት ቁጥር ሰባት ሚሊዮን<br />
እንደሚደርስ በኩራት ሲናገሩ ነበር፡፡ “ውስጡን<br />
ለቄስ” እንዲሉ፡፡ አሁን አሁን ግን ይህንን አሀዝ<br />
በእርግጠኝነት ደፍሮ የሚናገር የለም፡፡ የድርጅቱ<br />
ገመና በራሱ የድርጅቱ አባላት ገሀድ እየወጣ ነው፡<br />
፡ በራሱም ጊዜ መፈራረስ ጀምሯል፡፡ “እከሊትን ያየ<br />
በእሳት አይጫወትም” እንዲሉ ከሲኦል ያመለጡትን<br />
የኢህአዴግ አባላት የሞራል ድቀትና ምሬት ያስተዋለ<br />
እንኳን አባልና ደጋፊ ሊሆን አይፈልግም፡፡<br />
የዚህ አስተያየት ፀሀፊ ለዚህ አንድ መረጃ አለው፡<br />
፡ በዚህ ወር እንኳን ከየወረዳው በተባረሩ አመራሮች<br />
መትክ ተረኛ ተዋራጆችን ለመመደብ ድርጅቱ<br />
ያደረገው ጥረት ከንቱ ልፋት ሆኗል፡፡ በየመስሪያ ቤቱ<br />
የሚገኙ አባላቱ በተደጋጋሚ ቢለመኑም አሻፈረን<br />
ብለዋል፡፡<br />
ኢህአዴግ መቼም “አልሞት ባይ ተጋዳይ” ነው፤<br />
አንድ ቀን ጥርስ የሌለው አንበሳ መሆኑ ባይቀርም<br />
/አባባሉ ጋዳፊንም ያስተውሏል/፡፡ ጥቅምት 18<br />
ቀን 2004 ዓ.ም በመዲናችን አዲስ አበባ በሚገኙ<br />
ፕላዝማ ቴሌቪዥን በተዘረጋባቸው ት/ቤቶች<br />
በየወረዳው የሚገኙ አባላትን ለመሰብሰብ ተሞክሮ<br />
ነበር፡፡ የምክትል ከንቲባውና የሌሎች የአዲስ አበባ<br />
መስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ከሥልጣናቸው<br />
መባረር በመጠኑም ቢሆን ኢህአዴግን ያሳስበዋል፡፡<br />
የእያንዳንዳቸው የግንኙነት ሰንሰለት እስከ ወረዳዎች<br />
ወርዶ ተራ አባላትንም ስለሚያካትት የአኩራፊዎቹ<br />
ቁጥር ማሻቀቡ አይቀርም፡፡<br />
በጣም የሚያስገርመው ግን ከመስከረም<br />
15/2004 ጀምሮ የትምህርት ሥርጭት ይጀምራል<br />
የተባለው የፕላዝማ ቴሌቪዥን አስታዋሽና ባለቤት<br />
አጥቶ እስከ ጠቅምት 18/2004 ባልጀመረበት<br />
ሁኔታና የቴክኒክ ችግር እንዳጋጠመ ሲነገር እንዳልቆየ<br />
የኢህአዴግን አባላት ለማወያየት ግን መፍትሄ<br />
ተገኘለት፡፡ በሰበቡም የፕላዝማው ትምህርት<br />
ተጀመረ፡፡ የትምህርት ጥራት ይሏችኋል ይሄ ነው፡፡<br />
ሀሳቤን የምቋጨው በስብከት ነው፡፡ ስብከቱ<br />
ግን ቤተ እምነቶችን አይመለከትም፡፡ በሲኦል ያሉ<br />
ቤተ-ኢህአዴጎችን አይመለከትም-በሲኦል ያሉ<br />
ቤተ-ኢህአዴጎችን እንጂ ሰባኪው እንዲህ ይላል፡፡<br />
“የመዳን ቀን አሁን ነው! በሕይወት ሳሉ እንጂ ከሞት<br />
በኋላ ከሲኦል ማምለጥ አይቻልም፡፡ ቢጤዎቻችሁ<br />
በኢህአዴግ የግምገማ መድረኮች ለራሳቸው የደረጃ<br />
ውጤት “ር” እየሰጡ ከሲኦል አምልጠው ከኢትዮጵያ<br />
ሕዝብ ጋር በንሰሐ እንደተቀላቀሉ ሁሉ መንታ<br />
መንገድ ላይ የቆማችሁ የድርጅቱ አባላትም ጊዜ<br />
አተባክኑ! ፍጠኑ! መዳን ይሆንላችሁ ዘንድ አትፍሩ!<br />
አትፍሩ! “ር” ውጤት ማስመዝገብ የሚያሳፍረው<br />
ለዩኒቨርሲቲ ትምህርት ነው፡፡ በኢህአዴግ ግምገማ<br />
“ር” ማስመዝገብ ግን ጀግንነት ነው፤ “F” ማስመዝገብ<br />
ደግሞ ከጀግንነትም በላይ ጀግንነት ነው!!<br />
ፈጣሪ አምላክ ኢትዮጵያን ይባርክ!<br />
www.andinet.org.et
10<br />
ከብሩክ ከበደ<br />
www.andinet.org.et<br />
ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />
“ ነጋ-እንዴና የግብሩ አብዮት”<br />
ከላይ የተቀመጠውን ርዕስ የተጠቀምኩት<br />
ለቀጣይ ፅሁፌ አንድም ሁለትም<br />
ትርጉም እንዲሰጥልኝ በማሰብ ነው፡<br />
፡ አንደኛው መጠይቂያዊ ወይም ቃል<br />
አጋኖአዊ ትርጓሜ የያዘው የቃላቱ<br />
ዘርፍ ሌሊቱ አልፏአል፣ ነግቷል፣ ፀሐይ ወታለች የሚል<br />
ጥያቄ አዝሎ በመንጋቱ የሚቆጭም፣ የሚደነግጥም፣<br />
የሚደሰትም ሲመስል፤ በሌላ በኩል ደግሞ ነግቷል<br />
ፈጥኜ ለሥራ ጀንበሯን ልቀላቀል የሚል መልህክት<br />
ይይዛል፡፡<br />
ሌላውና ዋነኛው ከዚህ ጋር የተያያዘው<br />
ደግሞ በላቡና ጥረቱ ብቻ ለማደግ የሚጣጣረው<br />
የነጋዴ ክፍል ንጋትን በናፍቆት እንደሚጠብቃት<br />
የታወቀ በመሆኑ አዲስ የሽያጭ ዕቃ ለማስገባት፣<br />
አዲስ ትርፍ ለማግኘት፣ አዲስ ዘርፍ ለመክፈት ካለው<br />
ጉጉት በመነሣት የንጋት ጥያቄና ነጋዴ የሚነጣጠሉ<br />
አይደሉም፡፡ ለዚህም ነው ሳድሶችን በማስወገድ ራሱን<br />
የቻለ ትርጉም የሚሰጥ “ነጋዴ” የሚለውን ሥርወ /ቃል<br />
እንዲያነግስ ያመቻቸሁት፡፡<br />
ይህስ ሆነ ቃሉን ግን እንዲህ ለመሰነጣጠቅ<br />
መልሶም ለማዛመድ ያበቃህ ምንድነው? የሚል ጥያቄ<br />
ሊነሣ ይችላል፡፡ ቢነሣም ተገቢ ነው፡፡ ምክንያቱም<br />
የሰኔ ሰማይ ማጉረምረም ሲጀምር ሁለቱ የቴሌቮዥን<br />
መስመሮች፣ ዋናውን ሬዲዮ ጨምሮ የተለያዩ ኤፍ<br />
ኤም ጣቢያዎች፣ በመንግስት የሥራና በውጭ ቋንቋ<br />
የሚታተሙ የህትመት ውጤቶች፣ በያደባባዩ፣ በተለያዩ<br />
ህዝባዊና መንግስታዊ ተቋማት ደጃፍ የሚሰቀሉ<br />
መፈክሮችና ጥቅሶች ወዘተ ግብር መክፈል ግዴታ<br />
ብቻ ሳይሆን የዜግነት ድርሻ እንደሆነ በሚያስገነዝቡና<br />
በሚያስተምሩ ጽሁፎች ይጥለቀለቃሉ፡፡<br />
በተለይ ዘንድሮ ከመቼውም በተለየ መልኩ<br />
ግብር፣ ክፍያውንና ሂደቱን በተመለከተ ከከፍተኛ<br />
የስራ አላፊዎች እስከመምሪያና ክፍል አለቆች ተራ<br />
ሠራተኞች እስከ አንዳንድ የከተማ ነዋሪዎች ተብለው<br />
እስከሚጠቀሱት ድረስ በየመገናኛ ብዙኃኑ እየቀረቡ<br />
በተቀነባበሩ ቃለምልልሶችና የውይይት መድረኮች<br />
የተነገራቸውን በሰፊው ለማስረዳት ሲጨነቁና<br />
ሲውተረተሩ መመልከት የዘወትር ጸሎት ያህል<br />
የሚደጋገም ነበር፡፡<br />
ግማሹ የመንግስት ተቀጣሪ ሠራተኛ<br />
በአንዳንዱ ነጋዴ ላይ በተጣለው (በተወረወረው)<br />
ከፍተኛ ግብር ባያምንበትም ስራው ደሞዝ<br />
የሚያገኝበት ብቻ በመሆኑ ለከፋዩ ያንያህል ግብር<br />
ለምን እንደተጣለበት ለማሳወቅ በቂ ግንዛቤ ይሁን<br />
በቂ ማብራሪያ መስጠት የተሳነውና እየተውለፈለፈ<br />
ለማን አቤት እንበል...<br />
በየጫካው እየዞሩ እንደዱር አውሬ ይጮሁ ነበር::<br />
በየቁጥቋጦው ስር ተጠግተው ይኖሩ ነበር፡፡<br />
አሁን ግን ልጆቻቸው እየሰደቡኝ ይዘባበቱብኛል::<br />
ተፀይፈውኝ ከእኔ ይርቃሉ<br />
ማምለጫና ኡፎይ የምታሰኘውን “የመንግስት መመሪያ<br />
ነው” የምትለውን ቃል በመሰንዘር የዜጎችን መብትና<br />
ግዴታ እንደግዴታ ብቻ ቆጥሮ “አበቃሁ ጨርሻለሁ”<br />
የሚል ሲቪልሰርቫንት (የመንግስት ተቀጣሪ )<br />
መመልከት ሆነ ሊያጋጥም የሚችለው ይኽችው ሰኔ<br />
ስትመጣ ነው፡፡<br />
ጉዳዩ ይመለከተናል፣ ያገባናል የሚሉት<br />
ተቋማትና ግለሰቦች የሚናገሩትን፣ በማስታወቂያና<br />
ማስጠንቀቂያ ብዛት የሚያጨናንቁትን የግብር<br />
ክፍያ ከተወሰነው በቀር ቁብ ሰቶት የሚከታተላቸው<br />
እምብዛም ነው፡፡ ለምን ቢባል ስር የሰደደው<br />
አንዳንዴም ያልተጠናው እና ያልታሰበበት መልሶም<br />
የሚዘነጋው ጨርሶም ትቼዋለሁ ሊባል የሚችለው ክፍያ<br />
ቀድሞ ግዴታውን የተወጣውን ሲጐዳ እንጂ ሲጠቅም<br />
አለመመልከቱ በህይወት ልምድና ኑሮ ሲያልፍበት<br />
የቆየውነው፡፡ ለዚህም በ1997 ዓ.ም ተፈጥሮ የነበረውን<br />
እና መልሶ የከሰመውን የግብር አብዮት ግብረኛው<br />
በሚገባ የሚያውቀው ብቻ ሳይሆን የተቀጣበትም<br />
ነውና፡፡<br />
ከዚህ ከደነደነ የግብር አከፋፈል ትከሻው<br />
ልምዱ በመነሳት “ደግሞ ይሔ ግብር መጣ !” እያለ<br />
ከመዘባበትና ጊዜው ሳያልቅ ክፈሉ የሚለውን<br />
ማስጠንቀቂያ ችላ በማለት የተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ<br />
ሊያልቅ ሁለት አልያም አንድ ቀን ሲቀረው ከሚደርሰው<br />
መጨናነቅ የዘለለ አዲስ ነገር አይጠበቅም፡፡ ዘንድሮ<br />
ግን ይህን አካሄድ በመጠኑ የሚገለባብጠው አስጨናቂ<br />
ጉዳይ ተፈጥሮ ግብረኛው ማማረር ብቻ ሳይሆን ከፈለጉ<br />
ያሸጉት ሲልም በንግድ ቤቱ ላይ የፈረደበት ይመስላል፡፡<br />
ግብር አስከፋዩን በየጊዜው ገማቾች<br />
የገመቱት ነው በሚለውና አንዳንዴም የተጠና<br />
የማይመስለውን ግብር በከፋዩ ላይ ሲከምረው ከፋዩ<br />
እንዴት እንዲህ ሊሆን ይችላል አስረዱኝ? በሚልበት<br />
ጊዜም መጀመሪያ የተጣለብህን ግማሹን ክፈልና<br />
አቤቱታህን ማቅረብ ትችላለህ የሚል አገር ያለህዝብ<br />
ባዶ መሆኗን ያልቃኘ ምላሽ ይቀርብለታል፡፡ ይህንንም<br />
የሚጠናክርሎት ምላሽ ገንዘብንና ገንዘብን ብቻ ያማከለ<br />
አሰራር እንዲሰሩ የተዋቀሩት የየክፍለ ከተማው ገቢዎች<br />
ሰራተኞች በሚገባዎት ቋንቋ ያስረዳዎታል፡፡ እነዚሁ<br />
በአንዳንድ ክፍለ ከተማ በአንድ ወንበር ላይ ሁለትና<br />
ሦስት ሠራተኞች ሆነው ተደራርበው ሲተረማመሱ<br />
ለሚመለከት ታዛቢ ግብር አስከፋዩ ገንዘብን ብቻ<br />
መሰብሰብ የሚል መመሪያ የሚከተልና ከሰው በፊት<br />
ገንዘብ እንዲቀድም የሚፈልግ ይህንኑም በትጋት<br />
የሚሰብክ ቢመስለው አይፈረድበትም፡፡<br />
እነኚህ በየክፍ ከተማው ያሉ የፋይናንሱ<br />
የስራ ኃላፊዎችና ተራ ሠራተኞች በርካታ ሚሊዮኖችን<br />
ሰብስበው በከፍተኛ የሥራ አለቆቻቸው ለመመስገን<br />
ከገፅ 4 የዞረ<br />
ያለ አንዳች ፍርሃት እፊቴ ምራቃቸውን ይተፋሉ<br />
እግዚአብሄር ሃይሌን አድክሞ ስላዋረደኝ እነርሱም<br />
ልጓሙ እንደወቀለት ፈረስ በላዬ ይፈነጩብኛል፡፡<br />
የኛ ሲቃይም ከላይ ከተጠቀሰው ከኢዮብ<br />
የሰመጉ ጥሪ<br />
ብሎም ዋንጫና የምስክር ወረቀት ከግብር ከፋዩ<br />
በሚሰበሰበው ገንዘብ ድል ያለ ድግስ ደግሰው<br />
ለመቀበልና ለመሸላለም በሚያደርጉት ነፍስ ውጪ ነፍስ<br />
ግቢ አካሄድ ግብር ከፋዩን ህብረተሰብ እስከ ማማረር<br />
የሚደርስ ነው፡፡ በተጨማሪም በተመሣሣይ ስራና ሙያ<br />
ላይ ያለው የግብር አከፋፈል እና አወሳሰን አንዱ ክፍለ<br />
ከተማ ከአንዱ የሚለያይበት አጋጣሚ ስለሚፈጠርም<br />
እርስ በእርሱ የሚነጋገረው ነጋዴ በልዩነቱ ላይ አጥብቆ<br />
ሲማረር ይደመጣል፡፡<br />
ግብርን በወቅቱ ሰብስበን ለመሠረተ ልማት፣<br />
ለዳንድበር ጥበቃ፣ ለደን ልማት ወዘተ እያለ ግብር<br />
አስከፋዩ ተቋም በየጊዜው ቢወተውትም ግብር ከፋዩ<br />
ሕዝብ ግን የሚከፍለው ግብር ለአላስፈላጊ የመንግስት<br />
ተቋማት ልዩ ልዩ ወጪዎች እየዋለ ነው የሚለው<br />
ምክንያት እልባት እስካልተገኘለት ወይም እስካልተሻሻለ<br />
ድረስ ግብርን በትጋት ለመክፈል የሚያበረታታ<br />
አይመስልም፡፡ ይህን አባባል በምሣሌ ለማስረዳት<br />
ካስፈለገም አንድ የገጠር የውስጥ ለውስጥ ጥርጊያ<br />
መንገድን አሊያም ንፁህ የመጠጥ ውሃን ወይንም<br />
አንደኛ ደረጃ ት/ቤትን ለመመረቅ የሚጠሩ እንግዶች<br />
በተናጥል እያግተለተሉ ይዘዋቸው የሚነግዱትን<br />
በሚሊዮኖች የሚቆጠር ግንዘብ የፈሰሰባቸውን<br />
ተሽከርካሪዎች መመልከት ይበቃል፡፡ ጭርሱንማ አሁን<br />
አሁን ያአንዳንድ መስሪያ ቤት ሹመኞች V-8(ቪ-ኤይት)<br />
የተባለውንና ከ3 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣውን<br />
ተሽከርካሪ ካልተገዛልን እያሉ ነው የሚል ጭምጭምታ<br />
እየተሰማ ነው፡፡ ከነሱ የቀደሙትና በእጃቸው ያስገቡት<br />
ግን በከተማችን ውስጥ ሲፈሱበት እየተመለከትናቸው<br />
ነው፡፡<br />
ከዚህ ውጪ ለአዲስ እና ለተጀመሩ<br />
ፕሮጀክቶች ማስፈጽሚያ፣ ለዕቃ ግዢ ወዘተ. እየተባለ<br />
የሚባክነው እና የሚወድመው አንሶ የ----------- መ/<br />
ቤት የስራ ኃላፊ፣ ገንዘብ ያዥ፣ ዕቃ ግዥ----------<br />
ሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ይዞ ተሰወረ፡፡ የ--------<br />
ክፍለ ከተማ የመሬት አስተዳደር ባለሥልጣን ከሁለት<br />
ሚሊዮን ብር በላይ መዘበሩ፡፡ ወዘተ የሚሉና የመሳሰሉ<br />
ዜናዎች መደጋገሙ አገር ብቻ ሳይሆን ግለሰቦችም<br />
የሚለሙት ባንተ ኪስ ነው እየተባለ በተዘዋዋሪ<br />
የሚነገረው ግብር ከፋይ በተለይ ደግሞ ታታሪውና<br />
ሀቀኛው ነጋዴ “ገንዘቤ የበላተኛ ሲሳይ ሆኗአል” እያለ<br />
ዘወትር ቢቆጭና ስለግብር የምሰማበት ጆሮ የለኝም ቢል<br />
ማን ይፈርድበታል?፡፡<br />
ከዚህ ውጪ ሕዝብ ግብር በመክፈሉ፣<br />
ግዴታውን በመወጣቱ የሚደረግለት ተመጣጣኝ<br />
ነገር ባለመኖሩም ቀበሌ ሆነ እስታዲዮም፣ ሆስፒታል<br />
ሆነ አውቶብስ ተራ የሚያጋጥመውን ሰልፍ፣ ጡጫና<br />
ልምጭ፤ በየፖሊስ ጣቢያው፣ ፈርድ ቤት ሕክምና<br />
ወደ 13 ዞሯል<br />
ሲቃይና መከራ ቢበልጥ እንጂ አያንስም ችግራችን<br />
በዝቷል፤ ሸክማችን ከብዷል፤ እንዲቀልልን ለማን<br />
አቤት እንበል?<br />
የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ሰመጉ) በቀድሞው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉበኤ /<br />
ኢሰመጉ/ የቆመው ለህግ ልዕልና፣ ለዲሞክራሲና ለሰብአዊ መብቶች መከበር ነው፡፡ የሰመጉ<br />
አባል ይሁኑ፡፡ ዓላማውን ለማስፈጽም ይችል ዘንድ በገንዘብ ይደግፉ፡፡<br />
ስልክ 011 551-44089/011 551-77-04<br />
አድራሻ ሣህለ ሥላሴ ሕንፃ 8ኛ ፎቅ ከአዲስ አበባ ስታዲየም ፊት ለፊት<br />
2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />
የሰመጉ ይግባኝ በፌዴራል<br />
ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ችሎት<br />
ሊታይ ነው<br />
በቀድሞ አጠራር የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ<br />
(ኢሰመጉ) በአሁኑ የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ሰመጉ)<br />
በበጐ አድራጐት ድርጅቶችና ማህበራት ያለአግባብ<br />
የባንክ አካውንቴ ታግዶአል በማለት ከፍቶት የነበረው<br />
ክስ በፌደራል በከፍተኛ ፍ/ቤት ውድቅ በመደረጉ<br />
ለፌደራሉ ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ችሎት ይግባኝ ጠይቋል፡<br />
፡ ጉዳዩ “በይግባኝ ያሳቀርባል ወይስ አያስቀርብም<br />
በማለት የተመለከተው ሠበር ችሎት ያስቀርባል ወይስ<br />
አያስቀርብም በማለት የተመለከተው ሠበር ችሎት<br />
ያስቀርባል ተብሎ ብይን መስጠቱን” ከሰመጉ ያገኘነው<br />
መረጃ ይገልጻል፡፡<br />
በዚሁ መሠረት በከፍተኛ ፍ/ቤት የተፈጠረውን የህግ<br />
ጥሰት በማንሳት በሰበር ችሎት ለመከራከር ሰመጉ ዝግጅት<br />
እያደረገ መሆኑን” ገልጸዋል፡፡ ከሠመጉ ባገኘነው መረጃ<br />
መሠረት “የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ(ሰመጉ)፣ በቀድሞ<br />
አጠራር የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ)<br />
መንግስታዊ ያልሆነ፤ ከየትኛውም ፖለቲካ ድርጅት<br />
ጋር ያልወገነ ነፃ ድርጅት ነው፡፡ ጉባኤው የቆመው<br />
ለሕግ ልዕልና፤ ለዴሞክራሲ እና ሰብአዊ መብቶች<br />
መከበር ነው፡፡ በቅርቡ ባጋጠመው ችግር ምክንያት<br />
ሥራ እንቅስቃሴው በመድከሙ ጨርሶ ሥራውን ያቆመ<br />
የመሰላቸው በርካታ ሰዎች እንዳሉ ተገንዘበናል፡፡ ሆኖም<br />
ለአላማው ፅኑ እምነት ባላቸው አባላቱ እና ጥቂት<br />
ሠራተኞቹ እየታገዘ አሁንም በመንቀሳቀስ ላይ እንደሆነ<br />
ለደጋፊዎቹ ሁሉ ለማሳወቅ እንፈልጋለን፡፡<br />
ቀደም ሲል ጉባኤው በአብዛኛው ድጋፍ ያገኝ የነበረው<br />
ከውጭ አገር ለጋሾች እንደነበር ይታወሳል፡፡ ሆኖም<br />
አዋጅ 621/2001 በሰብአዊ መብቶች ማስከበር<br />
አኳያ የሚንቀሳቀሱ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች<br />
ከአመታዊ ገቢያቸው ዘጠና በመቶ ማግኘት ያለባቸው<br />
ከአገር ውስጥ ምንጮች መሆን እንዳለበት በመደንገጉ<br />
ገቢው በእጅጉ ቀንሷል፡፡ ከአባላት ሊሰበሰብ የቻለው<br />
ገቢ አነስተኛ ከመሆኑም ሌላ ጉባኤው ለመቋቋሚያ<br />
ብሎ አሥራ ስምንት ዓመታት ሙሉ በማጠራቀም<br />
በባንክ ያስቀመጠው ገንዘብ በበጎ አድራጎት ድርጅቶች<br />
እና ማህበራት ኤጀንሲ ታግዶበት ለማስለቀቅ በክስ ላይ<br />
ይገኛል፡፡<br />
`ሰመጉ` ላለፉት 20 ዓመታት በ12 ቅርንጫፎች እና<br />
ለሰብዓዊ መብት ዴሞክራሲ እና የህግ የበላይነት<br />
መስፈን ፅኑ ፍላጎት ባላቸው ሠራተኞቹ የሰብአዊ<br />
መብት ተጠቂዎች ለጉዳታቸው ድምፅ እንዲያገኙ እና<br />
አጥፊዎቹም እንዲታረሙ በሰፊው ተንቀሳቅሷል፡፡ ከላይ<br />
የተጠቀሰው አዋጅ እስከወጣበት ጊዜም `ሰመጉ` 58<br />
ሠራተመፐች 3 የሥራ ሂደቶች እና 8 ንዑስ የሥራ ሂደቶች<br />
የነበሩት ሲሆን በ2001 ብቻ በ16 የሰብአዊ መብት ጥሰት<br />
መርማሪዎች እና በ12 ቅርንጫፎቹ በመንቀሳቀስ 1723<br />
የሰብአዊ መብት ምርመራዎችን አድርጓል፤ 3 መደበኛ<br />
ሪፖርቶችን እና 6 ልዩ መግለጫዎችን አሳትሟል፡፡<br />
አዋጅ 621/2001 ከወጣ ጊዜ ጀምሮም በተከተለው<br />
አሉታዊ ተጽዕኖ ምክንያት አቅሙ በመዳከሙ ዘጠኝ<br />
ቅርንጫፎቹን ለመዝጋት የተገደደ ሲሆን 85%<br />
ሠራተኞቹንም አጥቷል፡፡ ይህም `ሰመጉ`በመላው<br />
ኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ተጎጂዎችን ጩኽት<br />
በማሰማት እና ከጎናቸው በመቆም ሲያደርግ የነበረውን<br />
የማይተካ ሚና ያስተጓጎለበት ከመሆኑም በተጨማሪ<br />
በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግሥት ማንኛውም ሰው<br />
ለማንኛውም ዓላማ ማህበር የማደራጀት መብት አለው<br />
የሚለው ድንጋጌ ከማጠናከር ይልቅ ውጤት አልባ<br />
የሚያደርግ ነው፡፡ በተለይም የኢትዮጵያ ህዝብ ድምፁን<br />
ከማጠናከር ይልቅ ውጤት አልባ የሚያደርግ ነው፡<br />
፡ በተለይም የኢትዮጵያ ህዝብ ድምፁን ሲያሰማበት<br />
የነበረውን `ሰመጉ`ን በማዳከም ዋናው የህጉ ተጎጅ<br />
`ሰመጉ` ሳይሆን ሲያገለግለው እና ድምፁን ሲያሰማለት<br />
የነበረው ህዝቡ ነው፡፡ ምንም እንኳን ይህ ሁኔታ<br />
ከፍተኛ ጫና ያሣደረብን ቢሆንም ሰመጉ በሰብአዊ<br />
መብት፣ ዲሞክራሲ እና በህግ የበላይነት ፅኑ እምነት<br />
ባላቸው ኢትዮጵያውያን በመታገዝ ሥራዎቹን ቀጥሏል<br />
ለወደፊትም ይቀጥላል፡፡ አሁንም ባሉት ሠራተኞ<br />
በመታገዝ 5 ልዩ መግለጫዎችን እና 1 መደበኛ ሪፖርት<br />
አውጥቷል፡፡<br />
ጉባኤያችን እስካአሁን ሲታገል የቆየው ለህዝብ መብቶች<br />
መከበር እንደመሆኑ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ሊደግፉት<br />
ይገባል የሚል እምነት አለን ስለሆነም ገቢ ለመሰብሰብ<br />
በምናደርገው ጥረት ሁሉ ተካፋይ እንድትሆኑ ከአደራ<br />
ጭምር እናሳስባለን፡፡” ብለዋል፡፡
2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />
ዜና<br />
ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />
የሠራተኞችን ደሞዝ ለመቀማት ሲል 3ሰው ገድሎ<br />
2 ሰው ያቆሰለው ፖሊስ በቁጥጥር ሥር ዋለ<br />
በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ሰሜን ሸዋ ዞን<br />
የምትገኝኘው የያያ ወረዳ አስተዳደር ሠራተኞች<br />
የጥቅምት ወር ደሞዝ ለመዝረፍ ሦስት ሰው ገሎ<br />
ሁለት ሰው ያቆሰለው የወረዳው ፖሊስ በቁጥጥር<br />
ሥር መዋሉን የዜና ምንጮቻችን በተለይ ለፍኖተ<br />
ነፃነት ጋዜጣ ገለጹ፡፡ እንደ ዜና ምንጮቻችን<br />
ገለጻ ከሆነ “ጥቅምት 20 ቀን 2004 ዓ.ም አንድ<br />
ሚሊዮን ብር ይሆናል የሚባለውን የወረዳውን<br />
የመንግስት ሠራተኖች ደሞዝ ለማምጣት ከወረዳው<br />
ፍቼ ከተማ ንግድ ባንክ ይመጣሉ፡፡ ግንዘቡን<br />
ለማምጣት የመጡት ሦስት ሠራተኞች አንድ<br />
ፖሊስና አንድ ሹፌር በጠቅላላ አምስት ሰዎች<br />
ነበሩ፡፡ ከነዚህ ውስጥ አንዷ ሠራተኛ ነፍሰጡር<br />
ነበረች፡፡ ለጊዜው በባንክ ያለው 12ሺ ብር ብቻ ነው<br />
ባንክ ውስጥ ያለው ተብለው ያንን እንደተሰጣቸው”<br />
ምንጮቻችን ገልፀዋል፡፡<br />
በመቀጠልም የዜና ምንጮቻችን እንደሚሉት<br />
“የተሰጣቸውን ብር 12ሺ ይዘው ወደ ወረዳቸው<br />
ሊንቀሳቀሱ ሲሉ አንድ ሌላ የወረዳው ፖሊስ<br />
ይዛችሁኝ ሂዱ ብሎ ትብብር ይጠይቃቸዋል፡፡<br />
እነሱም እሺ ብለው አሳፈሩት ጉዞ ጀምረው ገጠር<br />
ሲደርሱ ያ በልመና የተሳፈረው ፖሊስ “ሽንት<br />
ሰለያዘኝ አንዴ ሽንቴን ልሽና” ብሎ ጠየቃቸው፡<br />
፡ አሁንም እሺ ብለው መኪና አቆሙለት፡<br />
፡ ከወረደ በኃላ መሣሪያውን አውቶማቲክ ላይ<br />
አድርጐ በቅድሚያ ፖሊሱን ከመታው በኋላ ከዚያ<br />
በተሳፈሩት ላይ በጠቅላላ ጥይት አርከፈከፈባቸው፡<br />
፡ ሁለት ወዲያውኑ ሲሞቱ ሌሎቹ ቆሰሉ፡፡ ገንዘቡን<br />
አንስቶ ለማምለጥ ሞከረ፡፡ ጥይት ጨርሶ ስለነበር<br />
የአካባቢው አርሶ አደሮች ከበው በዱላ ቀጥቅጠው<br />
ከያዙት በኋላ ወዲያውኑ ለፖሊስ አስረክበውታል፡፡<br />
የቆሰሉት ሦስቱ አዲስ አበባ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል<br />
እንደደረሱ ፖሊሱ በጠና ተጐድቶ ስለነበር<br />
ወዲያውኑ ሲሞት፤ አንዱ ተሽሎት ከሆስፒታል<br />
ሲወጣ ነፍሰጡሯ እስከ አሁን ሆስፒታል በከፍተኛ<br />
ጉዳት ላይ ትገናለች፡፡” ብለዋል፡፡ ስለጉዳዩ መረጃ<br />
እንዲሰጡን የፍቼ ከተማ ዞን ፖሊስ ጠይቀን<br />
ስማቸውን ለመጥቀስ ያልፈለጉ ሰው “የተሟላ መረጃ<br />
ሊነግሩአችሁ የሚችሉት ህዝብ ግንኙነቶች ናቸው፡<br />
፡ እነሱ በአሁኑ ጊዜ የሉም፡፡ ለጊዜው ልሰጣችሁ<br />
ይምችለው መረጃው ተጠናቅሮ ለኦሮሚያ ፖሊስ<br />
ተላልፏል” በማለት መልስ ሰጥተውናል፡፡ በተያያዘ<br />
ዜና በዚህ ዕለት ማለትም ጥቅምት 20 ቀን 2004<br />
ዓ.ም በዚሁ በፍቼ ቆላማው አካባቢ ልዩ ቦታው<br />
ግራር አዲስ ጌ ቀበሌ ገ/ማህበር ውስጥ “አንድ<br />
ታጣቂ ህዝቡን ሰብሰባ ውጡ እያለ በየቤቱ እየዞረ<br />
በዱላ ሲደባደብ በጥይት ተገድሏል” ሲሉ የዜና<br />
ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡ እንደ ዜና ምንጮቻችን<br />
ገለጻ “በግድያ ተጠርጣሪው ነው የተባለው ግለሰብ<br />
ከሦስት ቀን በኋላ ለመንግስት እጁን ሰጥቷል”<br />
ብለዋል፡፡ በዚህም ጉዳይ ያነጋገርናቸው የዞኑ ፖሊስ<br />
“ግጭቱ የተፈጠረው በሁለት ታጣቂዎች መካከል<br />
ነው፡፡ በአካባቢው ማህበራዊ ፍ/ቤት ተካሰው ነበር፡<br />
፡ ተይዞ እንዲቀርብ የተወሰነበት ታጣቂ ቤቱን ዘግቶ<br />
እንቢተኛ በመሆኑ ለማስወጣት ሲሞክሩ ከቤት<br />
ውስጥ በተተኮሰ ጥይት አንድ ታጣቂ ሞቷል፡፡ ቤት<br />
ውስጥ የነበረው ታጣቂ ለጊዜው የተሰወረ ቢሆንም<br />
በህዝብ ትብብርና በፖሊስ ጥረት ተጠርጣሪው<br />
በቁጥጥር ሥር ውሎአል፡፡ ጉዳዩ በምርመራ ላይ<br />
ነው” በማለት መልስ ሰጥተውናል፡፡<br />
የደብረብርሃን ከንቲባና ባለሥልጣናት በሙስና ተጠርጥረው መታሰራቸው ተገለፀ<br />
የዞኑ ደን ልማት ሽያጭ መነጋገሪያ ሆኖአል<br />
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሰሜን ሸዋ<br />
ዞን ዋና ከተማ የሆነችው ደብረ ብርሃን ከተማ ከንቲባ<br />
የሆኑት “አቶ ስዩም ተፈራና በመሬት አስተዳደርና<br />
በልዩ ልዩ የሥራ ኃላፊነት ላይ የነበሩት የዞኑ ከፍተኛ<br />
ባለሥልጣናት ከሙስና ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው<br />
በእስር ላይ እንደሚገኙ” የዜና ምንጮቻችን<br />
በተለይ ለፍኖተ ነጻነት ጋዜጣ ገለጹ፡፡ እንደ መረጃ<br />
ምንጮቻችን ገለጻ ከሆነ “የዞኑ ነዋሪዎች በተለያየ<br />
ጊዜ በመልካም አስተዳደር እጦት ለተለያዩ አካላት<br />
አቤቱታ ቢቀርብም ፍትህ ማግኘት አይቻልም ነበር፡፡<br />
በጂማ ከተማ የተቃጠለው ውሃ ልማትና ዐቃቤ ህግ ጽ/ቤት<br />
አነጋጋሪ መሆኑ ተገለፀ<br />
በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ጂማ ዞን ዋና ከተማ<br />
በሆነችው ጂማ ከተማ ውስጥ ልዩ ቦታው “ውሃ<br />
ልማት” በሚባል አካባቢ ኖክ ማደያ ፊት ለፊትና<br />
ከፍ/ቤት ጐን የሚገኙት የውሃ ልማትና የዐቃቢ<br />
ህግ ጽ/ቤቶች ሰሞኑን ሙሉ በሙሉ በእሳት ቃጠሎ<br />
መውደማቸው በከተማው አነጋጋሪ ጉዳይ መሆኑን<br />
የዜና ምንጮቻችን ገለጹ፡፡ እንደ ዜና ምንጮቻችን<br />
ገለጻ በ2003 ዓ.ም ለምዕራብ ኦሮሚያ (ጂማ፣ ምዕራብ<br />
ወለጋ፣ ምስራቅ ወለጋና፣ ኢሊባቦር ዞኖች…) በገጠራማ<br />
ሥፍራዎች ለውሃ ቁፋሮ ከፌዴራል መንግስት<br />
ህጋዊ የሆኑ ይዞታዎችን እየነጠቁ ለሚፈልጉት እየሰጡ<br />
ዜጐችን ሲያንከራትቱ፣ ምሪት ቦታዎችን እንዳሻቸው<br />
ለፈለጉት ሲሰጡ ከልካይ አልነበራቸውም፡፡ፍትህ<br />
ሲያዛቡ ጠያቂም አልነበራቸውም፡፡ የአካባቢው<br />
ህዝብ አድማጭ አልነበረውም፡፡ የሚቃወማቸውንና<br />
ልክ አይደለችሁም የሚላቸውን ተለጣፊ ስም እየሰጡ<br />
እያሳሰሩና ከኑሮው እያፈናቀሉ ቆይተዋል፡፡ ዛሬ<br />
ለገዢዎች ባልተመቿቸው ወቅት ጠብቀው ማሰራቸው<br />
የዘገየ እርምጃ ነው” ሲሉ በቁጭትና በሐዘን ገልፀዋል፡፡<br />
በተያያዘ ዜና “ከጣርማ በር መዘዞ ባሽ የሚገኘው<br />
ከተመደበው በጀት ውስጥ 13 ሚሊዮን ብር ጉድለት<br />
በማሳየቱ በባለሥልጣኖች ላይ ክስ ተከፍቶ ጉዳዩን<br />
የፌዴራል ዋናው ኦዲተር መ/ቤት ካሸገው በኋላ ክሱን<br />
የከፈተው የዐቃቢ ህግ ጽ/ቤት ኦዲት ሊደረግ የነበረው<br />
የውሃ ልማት ጽ/ቤት በአንድ ቀንና ሰዓት መቃጠላቸው<br />
እያነጋገር ነው” ሲሉ አብራርተዋል፡፡<br />
የመረጃ ምንጫችን እንደሚሉት “የእሳት<br />
ቃጠሎው ርብርብ አድርጐ ንብረትን፣ ገንዘብንና<br />
ሰነዶችን ማትረፍ ሲቻል ተቃጥሎ እንዲወድም<br />
የተፈለገበት ምክንያት ግልጽ አይደለም፡፡ ካሉ በኋላ<br />
ሰፊ የባህር ዛፍና የጥድ ደን ግልጽነት በጐደለው<br />
ሽያጭ ተሸጦ እየተጨፈጨፈ ነው” ሲሉ አንዳንድ<br />
የአካባቢው ነዋሪዎች ለዝግጅት ክፍላችን ገለጹ፡፡ እንደ<br />
ነዋሪዎቹ ገለጻ “ከጣርማ በር መዘዞ ከመዘዞ መካከል<br />
ባሽ የሚገኘው የሌባ መስቀያ የሚባለው ደን ብቻውን<br />
በእግር ሁለት ሰዓት ያስኬዳል፡፡ ከጣርማ በር እስከ ባሽ<br />
ድረስ በመኪና የአንድ ሰዓት መንገድ ነው፡፡ ይህንን<br />
በ10 ሚሊዮኖች የሚቆጠረውን ደን እንደ ተራ እቃ<br />
በስውር መሸጥ እና ጭፍጨፋ መጀመር አነጋጋሪ ነው”<br />
ሲሉ ያብራራሉ፡፡<br />
ምናልባት ከፍተኛ የመንግስት ባለሥልጣን እጅ<br />
ሳይኖርበት አይቀርም” በማለት ጥርጣሬአቸውን<br />
ገልፀዋል፡፡<br />
በጉዳዩ ላይ አስተያየት እንዲሰጡን የጂማ ከተማ<br />
ፖሊስ ደውለን ነበር፡፡ ስማቸውን ለመጥቀስ ያልፈለጉ<br />
አንድ ግለሰብ ጥያቄያችንን ካዳመጡ በኋላ “ጉዳዩ<br />
በምርመራ ላይ ያለ በመሆኑ አስተያየት ልንሰጣችሁ<br />
አንችልም” በማለታቸው ዜናውን ሚዛናዊ ማድረግ<br />
አልቻልንም፡፡<br />
አርቲስት ደበበ እሸቱ ተጨማሪ ቀነ<br />
ቀጠሮ ተጠየቀበት<br />
በ ”ሽብር” ተጠርጥሮ ማዕከላዊ እስር ቤት የሚገኘው አርቲስት ደበበ እሸቱ ጥቅምት<br />
24 ቀን 2004 ዓ.ም አራዳ ምድብ ችሎት ተቀጥሮ እንደነበር ይታወሳል፡፡<br />
አርቲስት ደበበ በቀጠሮው ቀን ከማዕከላዊ እስር ቤት ወደ ችሎት ቀርቧል፡፡<br />
ችሎቱን ለመከታተልም የተጠርጣሪው ቤተሰብም ሆነ ጋዜጠኞች እንዳይገቡ የተከለከለ<br />
ሲሆን ተጨማሪ የ28 ቀን ቀነ ቀጠሮ ተጠይቆበታል ሲሉ ጠበቃው በተለይም ለዝግጅት<br />
ክፍላችን ገልፀዋል፡፡<br />
ተጠርጣሪውም ጥቅምት 24 ቀን 2004 ዓ.ም ችሎት እስከቀረቡበት ጊዜ<br />
ድረስ በማዕከለዊ እስር ቤት ከጠበቃቸው ጋር እንዲገናኙ ባለመፈቀዱ ጠበቃው ችሎት<br />
ፊት ከደንበኛቸው ጋር እንዲመክሩ በጠየቁት መሠረት ተፈቅዶላቸዋል ሲሉ ምንጮቻችን<br />
ጠቁመዋል፡፡ በዚህም ክቡር ፍ/ቤቱ ተጠርጣሪው ከጠበቃቸው ጋር የመገናኘት ሕገ<br />
መራግሥታዊ መብታቸው መሆኑንና ሊከለከሉ እንደማይገባ ለመርማሪው ፖሊስ<br />
በማሳሰባቸው ጠበቃቸውም ተግባራዊ መሆኑን ለማረጋገጥ ዛሬ ወይም ነገ ማዕከላዊ<br />
እስር ቤት ሄደው ደንበኛቸው አርቲስት ደበበ እሸቱን ለማነጋገር መወሰናቸውን በተለይም<br />
ለዝግጅት ክፍላችን ገልፀዋል፡፡<br />
11<br />
በናይጄሪያ 150 ሰዎች<br />
በአጥፍቶ ጠፊዎች<br />
መገደላቸው ተገለፀ<br />
በሰሜን ናይጄሪያ ደማቱሩ ከተማ 150 ሰዎች<br />
በአጥፍቶ ጠፊዎች ቦምብና በጠብመንጃ በተፈጠረው<br />
ተኩስ ጥቃት ያለፈው ቅዳሜ መገደላቸው ተገለፀ፡፡ ለጥቃቱ<br />
“ይሄነስ” የተባለው እስላማዊ ቡድን እጅ አለበት ብለዋል”<br />
ሲሉ የሀገሪቱን ባለሥልጣናትን ጠቅሶ ቢቢሲ ዘግቧል፡፡<br />
ይህንንም አስመልክቶ የፕሬዘዳንት ጉድላክ<br />
ጆናታን ቃል አቀባይ ሩበን አባቲ ጥቃቱ የተፈፀመው<br />
ከ5 በማያንሱ አጥፋቶ ጠፊዎች እንደሆነና ጉዳዩንም<br />
የሚመለከተው አካል እያጣራ እንዳለ አስታውቀዋል፡<br />
፡ ቃል አቀባዩ አያይዘውም አሁን በአካባቢው ምንም<br />
የፀጥታ ችግር እንደሌለና ጥቃቱን አስተባብረዋል ተብለው<br />
የተጠረጠሩትም በእስር ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል<br />
ሲሉ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙኋን ዘግበዋል፡፡<br />
በኬንያ ቱሪስት መዳረሻ<br />
ኬንያዊ ሾፌር ሲገደል<br />
ስዊዘርላንዳዊ ጐብኚ መቁሰሏ ተገለፀ<br />
በኬንያ ምስራቃዊ ክፍል “ጌም ፓርክ” በተባለው የቱሪስት<br />
መዳረሻ ስዊዘርላንዳዊ ጐብኚዎችን ይዞ የነበረው ኬንያዊ<br />
ሾፌር ባልታወቁ ታጣቂዎች ሲገደል አንድ ስዊዘርላንዳዊት<br />
ጐብኝ መቁሰሏን የፈረንሳይዩ የዜና ወኪል ኤ ኤፍ ፒ<br />
ዘግቧል፡፡<br />
ባለፈው አርብ በተፈፀመ ጥቃት በከፍተኛ ደረጃ የቆሰለችው<br />
ስዊዘርላንዳዊት ቱሪስት ወደ አቅራቢያ ሆስፒታል ሄዳ<br />
የሕክምና እርዳታ እየተደረገላት እንደሆነና አብሯት<br />
የነበረው ስዊዘርላንዳዊ የመቁሰል አደጋ እንዳልገጠመው<br />
የኬንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ስቴፈን ቮን<br />
ቢሎው አስታውቀዋል፡፡<br />
ኬንያ በቱሪዝም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የምታገኝ<br />
ሀገር ስትሆን ከዚህ በፊት በመስከረም ወር እንግሊዛዊ<br />
ጐብኚ ሲገደል ባለቤቱ ታግታ አንደነበር ይታወሳል፡<br />
፡ በተመሳሳይም በጥቅምት ወር አንድ ፈረንሳያዊት እና<br />
ሁለት ስፔይናዊ ዜጐች ጥቃት እንደደረሰባቸው ተዘግቧል፡<br />
፡ ይህንንም አስመልክቶ ኬንያ ከቱሪስት የምታገኛቸው<br />
ገቢዎች እንዳይቀንስ ስጋት የፈጠረ ሲሆን የሀገሪቱ<br />
መንግሥት በበኩሉ ድርጊቱን የሚፈፅሙ ያልታወቁ<br />
ታጣቂዎችን በቅርቡ በቁጥጥር ሥር እንደሚያውል<br />
ገልጿል፡፡<br />
ዓለም አቀፉ የገንዘብ<br />
ድርጅት ለኮትዲቯር<br />
616 ሚሊዮን ዶላር ብድር አፀደቀ<br />
ኮትዲቯር ካለፈው ዓመት ምርጫ ውጤት ጋር<br />
በተያያዘ በተፈጠረ ችግር ከፍተኛ የምጣኔ ሃብት<br />
ውድቀት ተከስቶ እንደነበር ይታወቃል፡፡ ይህ ምጣኔ<br />
ሃብት እንዲያንሰራራ ፕሬዘዳንት ኦታራ ዓለም አቀፍ<br />
አበዳሪ ተቋማትን የተማፀኑ ሲሆን በዚህም መሠረት<br />
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት 616 ሚሊዮን ዶላር ብድር<br />
ያለፈው አርብ ዕለት ማፅደቁ ተጠቁሟል፡፡<br />
በተያያዘ ዜና ባለፈው የኮትዲቯር ምርጫ ተሸንፈው<br />
የነበሩት ሎረንት ባግቦ “ስልጣን አልለቅም” በሚል<br />
በተፈጠረው አለመግባባት 3ሺህ ሰዎች መገደላቸውን<br />
አስመልክቶ በወቅቱ ጥቂት የሀገሪቱ አመራሮች ላይ<br />
የኦታራ መንግስት ክስ መስርቷል፡፡<br />
ከተከሳሾችም መካከል የቀድሞ ፕሬዘዳንት ሎረንት<br />
ባግቦ፣ 24 ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ባለሥልጣናት<br />
እና 57 የሀገሪቱ ወታደራዊ አመራሮች ይገኙበታል ሲል<br />
የፈረንሣዩ የዜና ወኪል ዘግቧል፡፡<br />
www.andinet.org.et
12<br />
ከዳምጠው አለማየሁ<br />
www.andinet.org.et<br />
“ወይ ቶሎ ግደለኝ ወይ እድሌን ባርከው”<br />
“ሊቀደድ ነው ሆዴ ሲርበኝ የማከው”<br />
ድምፃዊ ባሕሩ ቃኘው<br />
“ድህነት ባጭሩ ሲተረጎም የሚበሉትን<br />
ማጣት ወይም መታረዝ ወይም መጠለያ<br />
ማጣት ብቻ ሊመስል ይችላል፡፡ ድህነት<br />
ከሁሉም ይበልጥ ተስፋ ማጣት ነው፣ ክብር<br />
ማጣት ነው፣ በሰዎች መካከል እየተመላለሱ<br />
አለመታየትና መረሳት ነው፡፡ ድህነት<br />
በእያንዳንዱ ቀን ነገን እየፈሩ መኖር ነው፡፡<br />
የኢትዮጵያ ሕዝብ በኢህአዴግ ልማታዊ<br />
መንግስትነት ከላይ በተገለፀው ሁኔታ<br />
ውስጥ የማይኖር ከሆነ ፍርዱ የራሱ ነው፡<br />
፡ ስለሆነም በእኛ ግንዛቤ ዛሬ በኢትዮጵያ<br />
ኢትዮጵያውያንን የሚጠቅም ሰባዊ ልማት<br />
የለም፡፡ ኢኮኖሚው አስርና አስራ አንድ<br />
በመቶ አደገ አላደገ ለሕዝቡ ግን “ያው በገሌ”<br />
እንደተባለው መሆኑን ልብ ይላል፡፡ ይህን<br />
ህዝብ ይፍረድ!!” ከብርሀን ፓርቲ የምርጫ<br />
ቅስቀሳ ሰነድ የተወሰደ፡፡<br />
ሰሞኑን “ድርቅ እንጂ ርሀብ<br />
የለም” በማለት ጠቅላይ ሚኒሰትሩና<br />
ሹማምንቶቻቸው እየተቀባበሉና እየደጋገሙ<br />
ሲናገሩ የምንሰማው እውን በዚህ ሀገር ያለ<br />
ሀቅ ነው?<br />
እንደ እውነቱ ከሆነ ኮሚኒስቶች<br />
ብዙ ጊዜ መፈክሮቻቸውም ሆነ<br />
ዕቅዶቻቸው፤ ህልሞቻቸውም ሆነ የድርጊት<br />
ፕሮግራሞቻቸው ግልፅነት የጎደላቸው<br />
ስለሆኑ ተደናግረው ማደናገር ይወዳሉ፡፡<br />
ረሀብ ትርጉሙ ካልጠፋን በስተቀር<br />
የሚላስ የሚቀመስ ማጣት ብቻ ሳይሆን<br />
በየለቱ በሚቀመሰው ምግብ ውስጥ አማካኝ<br />
የካሎሪ መጠን ማጣት ጭምር መሆኑ<br />
መዘንጋት የለበትም፡፡<br />
ሕወሓት በሽፍትነት ዘመኑ የተከሰተው<br />
ዐይነት ርሀብና የሙት እናቱን ጡት<br />
እየጠባ እነደታየው ህፃን ሰቆቃ፣ “ዋይ ዋይ<br />
ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />
ሲሉ” የሚደመጥ የልጆች እሮሮ ዛሬም ከ<br />
አርባ አመታት በኋላም የምንጠብቅ ከሆነ<br />
የተዋቀርንበት ስርዓት ሰብዓዊ ስርአት መሆኑ<br />
ይቀርና በደመ-ነፍስ የተሰባሰቡ የዓራዊት<br />
ዱለታ ያስመስለዋል፡፡<br />
የሀገራችን ድርቅ እያሰለሰና አብዛኛውን<br />
ጊዜ በየአስር አመቱ የሚመላለስ ክስተት መሆኑ<br />
ባይካድም ረሀብና መራብ ግን የአብዛኛው<br />
ህዝብ የእለት በእለት ኑሮና ቋሚ ህይወት<br />
ነው፡፡ በአስከፊ ድህነት ውስጥ ከሚኖረው<br />
የአብዛኛውን ገበሬ ህይወት እንለፈውና<br />
በመካከለኛ ደረጃ ውስጥ የሚኖረውን ገበሬ<br />
ህይወት እንመርምር፡፡ እንደሚታወቀው<br />
የሀገራችን ገበሬ ተበልቶ ባለቀና በተበጣጠሰ<br />
አነስተኛ ማሳ የሚያመርታት ምርት እጅግ<br />
አነስተኛ ከመሆኑም በላይ በአማካኝ ከአምስት<br />
እስከ ሰባት የሚደርሱ ቤተሰቦቹን ከመመገብ<br />
ጀምሮ ካመረታት ምርት ውስጥ ግማሽ ያህሉን<br />
ይሸጥና…………<br />
1. ግብር ይከፍልበታል<br />
2. የማዳበርያ እዳ ይከፍልበታል<br />
3. ለራሱ ለልጆቹና ለቤተሰቡ<br />
የዓመት ልብስና መጫሚያ እነደአቅሙ<br />
ይገዛል<br />
4. ለልማት መዋጮ እና ለገዢው<br />
ፓርቲ ማጠናከሪያ የግድ ይከፍላል<br />
5. የሚታደሱና ያለቁ የእርሻ<br />
መሳሪያዎችን ይገዛል ለምግብ ማጣፈጫ<br />
ጨው፣በርበሬ፣ዘይት፣ሽሮ፣ስኳር፣ቡና……<br />
ወዘተ ይገዛበታል<br />
6. ማገዶና ሳሙና ወዘተ<br />
የሚያሟላው ከዚሁ ገንዘብ ነው፡፡<br />
በዚህ ሁኔታ በግድ መሟላት<br />
የሚገባቸውን ሸቀጦች ለመግዛት ሲል ወደ<br />
ጎተራው ከገባችው ሰብል የተረፈችው<br />
ምን ያህል ወራት መመገብ እንደምትችል<br />
መገመት አያዳግትም፡፡ በዚህም ምክንያት<br />
የተረፈችው ሰብል ያለጥርጥር ከስድስት<br />
ወራት በላይ ሊመገቧት አይቻላቸውም፡፡<br />
በዚህ አይነት የድህነት አዙሪት ቀለበት ውስጥ<br />
የሚኖረው አብዛኛው የሀገራችን ገበሬ በቂ<br />
ዝናብ ባለባቸው ወቅቶችም እንኳን ከስድስት<br />
ወራት በላይ ሊመግበው የሚያስችለው<br />
ምርት ከቶም ሊያመርት አይችልም፡<br />
፡ ቀሪዎቹ ስድስት ወራት የረሀብ ወራት<br />
ናቸው፡፡ ምክንያቱም እጅግ ኋላ ቀር በሆነ<br />
የአስተራረስ ዘዴ እና ምርታማነቱ ተሟጦ<br />
ባለቀ የተበጣጠሰ አነስተኛ ማሳ ግማሽ ዓመት<br />
የሚመግበው ሰብል ማምረት የሚችል ገበሬ<br />
እጅግ አነስተኛ ሊሆን ይችላል፡፡ በመሆኑም<br />
ረሃብ በአገራችን በማናቸውም ጊዜ በየዓመቱ<br />
ህዝብ እንዲሰደድና እንዲፈናቀል እንዲሁም<br />
ከተሞችን በስራ አጦች ከማጨናነቅ ለማዳን<br />
አልተቻለም፡፡<br />
እንግዲህ ይህ ተጨባጭ የሀገራችን<br />
ሀቅ ረሀብ፣ስደት፣መፈናቀልና ሞት እጣ<br />
ፈንታችን ሆኖ አብሮን የኖረ ነው፡፡ በቅርቡ<br />
በመካከለኛው ምስራቅ ከሊብያ ወደ<br />
አውሮፓ እንዲሁም ከመቋዲሾ ወደ የመን፤<br />
በሶማሌ ላንድ የታገቱና ሞትን ንቀው በስደት<br />
የሚንገላቱ የኢትዮጵያውያን ህይወት ዘግናኝና<br />
አሳዛኝ ነው፡፡ በይበልጥ የሚያሳዝነው ከነዚህ<br />
ውስጥ ከፊሎቹ በጀልባ ሲያቋርጡ የባህር<br />
አውሬ ቀለብ የሆኑ ወገኖቻችን ኢትዮጵያ<br />
ምን ያህል ከሞትም በታች እንደሆነች<br />
የሚያመለክት ነው፡፡<br />
በሌላ በኩል ደግሞ አንድ አለምአቀፍ<br />
የጥናት ማእከል በቅርቡ ይፋ ባደረገው መረጃ<br />
መሰረት ከኢትዮጵያ ህጻናት ግማሽ ያህሉ<br />
በምግብ እጥረት ምክንያት አካላዊ መቀጨጭ<br />
የደረሰባቸው ናቸው፡፡ ይህ ሁኔታ የአእምሮ<br />
መቀጨጭንም ስለሚያስከትል ለማህበራዊ<br />
ልማት ዋና ጉዳይ የሆነው ትምህርትን<br />
የመቀበል አቅማቸውን ከማዳከሙም በላይ<br />
ትውልድ ገዳይ ከሆነው ስርዓተ-ትምህርት<br />
ጋር ተደምረው የኢትዮጵያን ሰብዓዊ ልማት<br />
መካን ያደርገዋል፡፡<br />
በ 1996 ዓ.ም መ.ኢ.አ.ድ. ስለህዝብ<br />
አደረጃጀት ጉዳይ በጎጃም፣ በጎንደርና<br />
በወሎ ታላቅ ፖለቲካዊ ጉዞ መድረጉን<br />
አስታውሳለሁ፡፡ እንዳጋጣሚ ሆኖ ከአዲስ<br />
አበባ የተጓዝን በመሆናችን የገጠሩን<br />
ህዝባችንን ብስቁልና ስንመለከት ሁላችንም<br />
መረበሻችን ትዝ ይለኛል፡፡ በዚያን ግዜ<br />
በደብረታቦር ከተማ ለሚደረገው ታላቅ<br />
ህዝባዊ ስብሰባ ቅድመ ዝግጅት ሲባል<br />
ከተመረጡ አረጋውያንና የአካባቢው<br />
ፖለቲከኞች ጋር የዋዜማው ዕለት አመሻሽ<br />
ላይ በተደረገ ውይይት የመክፈቻ ንግግር<br />
እንዲያደርጉ የተጋበዙት ኢንጂነር ኃይሉ<br />
ሻውል ነበሩ፡፡ ኢንጂነሩም ንግግራቸውን<br />
ከመጀመራቸው ሳግ እየተናነቃቸውና<br />
ንግግራቸውንም እያደናቃቀፈባቸው ያነቡት<br />
እንባ በብርበራ ሰበብ ፊልሙ ካልተዘረፈ<br />
በስተቀር በቪዲዮ ካሜራ የተቀዳ መሆኑ<br />
አይረሳም፡፡ በማግስቱ የዞኑ ህዝብና ከፊል<br />
ፈረሰኛ በቴዎድሮስ አደባባይ ወደሚካሄደው<br />
ህዝባዊ ስብሰባ ከመታደማችን በፊት የዚህ<br />
ጽሁፍ አቅራቢ በማለዳ በመነሳትና በመኝታ<br />
ቤታቸው በመገኘት ትላንትና ማታ ለምን<br />
እንዳለቀሱ ጠየኳቸው፡፡ እርሳቸውም<br />
እስከዛሬ የማይረሳኝንና ጥልቅ ስሜታቸውን<br />
የተገነዘብኩበትን ሃሳባቸውን ገለጹልኝ<br />
እንዲህ በማለት “የወልድያ ወረታ መንገድ<br />
የቻይና ኩባንያ በሚሰራበት ዘመን እኔ<br />
የአውራ ጎዳና ስራአስኪያጅ ነበርኩና መንገዱ<br />
በተሰጠው ንድፍና ደረጃ እየተሰራ መሆኑን<br />
ለመቆጣጠር በተደጋጋሚ እመላለስበት<br />
ነበር፡፡ በዚያን ግዜም በደብረታቦር የነበረ<br />
የሰው ዘር ቁመናው ያማረ፣ ሸበላና መለሎ<br />
ትውልድ አልቆ ትቢያ የመሰለ የደቀቀና<br />
ድውይ ህዝብ ተሰብስቦ ስመለከት ራሴን<br />
መቆጣጠር ተሳነኝ፡፡ ይህንን የተራቆተ መሬት<br />
መልሰን እንዲያገግም ማድረግ እንችላለን፡<br />
፡ ነገር ግን ያለቀውን ዝርያችንንና ወገናችንን<br />
ከየት እናገኘዋለን?” ካሉ በኋላ በመቀጠልም<br />
’’የሰሜን ሸዋን ህዝብ ቢቀጠቅጡት ምኒልክን<br />
የተበቀሉ መስሎአቸው ነው፡፡ የደብረታቦር<br />
ህዝብ ግን ምን አደረጋቸው’’?ማለታቸው<br />
የሚረሳ አይደለም፡፡<br />
ለነገሩማ በአፄ ቴዎድሮስ<br />
“አንድ ሀገር አንድ ንጉሰ ነገስት” የተባለው<br />
የዘመናዊው የኢትዮጵያ አንድነት ታሪክ<br />
ጠንካራ አምድ የተተከለው፤ በፀረ-<br />
ኢምፒሪያሊዝምና በፀረ-ቅኝ አገዛዝ የታነፁና<br />
የአድዋን ጦርነት አይቀሬነት ቀድሞ የተገነዘቡ<br />
ጠንካራዋ የአለማችን የመጀመሪያዋ ሴት<br />
እቴጌ ጣይቱ የተገኙበትና እንዲሁም<br />
በኢትዮጵያ እንደ ቀዳሚ ኢንዱስትሪ አባዮት<br />
የተቆጠረውና ያልዘለቀው ጋፋት የጦር<br />
መሳሪያ ፋብሪካ ማዕከላት ደብረታቦር እና<br />
ጎንደር መሆኑ መቼ ሚረሳ ሆነና ብዬ በልቤ<br />
አሰብኩ፡፡ ደብረታቦርም በፀረ-ኢትዮጵያ<br />
ኃይሎች ኢላማ ውስጥ መግባቱ እንደምን<br />
ያጠራጥራል?<br />
አዲሱ የከተማ ውስጥ ርሃብ!<br />
ድርቅ፣ አስከፊ ድህነትና ኋላ ቀር<br />
ያስተራረስ ዘዴ ያስከትል የነበረው ርሃብና<br />
ሞት በገጠሪቱ ኢትዮጵያ እንደነበረ<br />
አይዘነጋም፡፡ ይሁንና ዛሬዛሬ ርሃብ ባጠቃላይ<br />
2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />
ዕውን በኢትዮጵያ ውስጥ “ድርቅ እንጂ<br />
በዚህ ረገድ እጅግ የሚያሳዝኑ ህፃናት አሉ፡፡ አንዳንዶቹ<br />
ህፃናት ትምህርት ቤት መሄድ እድል ቢያጋጥማቸውም<br />
ምሳ ለመቋጠር ያልታደሉ ወላጆች ስላሉዋቸው ባንዳንድ<br />
የመንግስት ትምህርት ቤቶች ጠኔ የሚጥላቸው ልጆች<br />
መታየት አዲስ ክስተት ነው፡፡ ይህ አስጨናቂ ሀላፊነት<br />
የወደቀው ደግሞ በመምህራንና በየትምህርት ቤቱ<br />
ማህበረሰብ ትከሻ ላይ ነው፡፡ በመሆኑም በአንዳንድ<br />
ትምህርት ቤቶች ጊዜያዊ የመመገቢያ ስፍራዎች<br />
እየተደራጁ ነው፡፡ ቀድሞውኑም ቢሆን ጥቂት የማይባሉ<br />
ህፃናት ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ፣ አልባሳትና<br />
ጥሬ የምግብ ሰብሎች የሚሰጡዋቸው ግብረ ሰናይ<br />
ድርጅቶች አሉ፡፡ በመረጃ አቀራረብ ረገድ መተላለፊያው<br />
ጠባብ ባይሆን ኖሮ በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ እርዳታ<br />
ፈላጊዎች እንደሚኖሩ መገመት አያዳግትም፡፡ በዚህ<br />
አይነት ሰቆቃ በእያንዳንዱ ድሃ ጎጆ ተደፍተው ሚያድሩ<br />
ረሃብተኛ ህፃናት አንጀት የሚበሉ ናቸው፡፡ የዚህ ሀገር<br />
መሪ መሆን እንደመርግ የሚከብድ አበሳ ለመሸከም<br />
ዝግጁ መሆንን እንጂ በመሬት ላይ ካለው ሃቅ ሸሽቶ<br />
’’ድርቅ እንጂ ርሃብ የለም’’ ማለት ይገባል??<br />
ርሃብ የለም ?”<br />
ኢኮኖሚ<br />
በኢትዮጵያ ከተሞችና በተለይ ደግሞ በአዲስ<br />
አበባ ከተማ አዲስ ማህበራዊ ቀውስና<br />
ክስተት ሆንዋል፡፡ የጦር ቁስለኞች፣የኤድስ<br />
ህሙማን፣ጧሪ የሌላቸው አረጋውያን፣<br />
ወላጅ አልባ ህጻናት፣ ቤት አልባና ጎዳና<br />
ተዳዳሪዎች፣ በልመና የሚተዳደሩ ድሆች፣<br />
ስራአጥ ወጣቶች ከግብርናና ከኢንዱስትሪ<br />
ስራ የተገለሉ በርካታ ዜጎች ………ወዘተ<br />
ከተማይቱን በማጨናነቅ ላይ ያሉ ርሃብተኞች<br />
ናቸው፡፡ እነዚህ ሁሉ የአዲሱ የከተማ ውስጥ<br />
ርሃብ ሰለባዎች ናቸው፡፡<br />
በዚህ ረገድ እጅግ የሚያሳዝኑ ህፃናት<br />
አሉ፡፡ አንዳንዶቹ ህፃናት ትምህርት ቤት<br />
መሄድ እድል ቢያጋጥማቸውም ምሳ<br />
ለመቋጠር ያልታደሉ ወላጆች ስላሉዋቸው<br />
ባንዳንድ የመንግስት ትምህርት ቤቶች ጠኔ<br />
የሚጥላቸው ልጆች መታየት አዲስ ክስተት<br />
ነው፡፡ ይህ አስጨናቂ ሀላፊነት የወደቀው<br />
ደግሞ በመምህራንና በየትምህርት ቤቱ<br />
ማህበረሰብ ትከሻ ላይ ነው፡፡ በመሆኑም<br />
በአንዳንድ ትምህርት ቤቶች ጊዜያዊ<br />
የመመገቢያ ስፍራዎች እየተደራጁ ነው፡፡<br />
ቀድሞውኑም ቢሆን ጥቂት የማይባሉ ህፃናት<br />
ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ፣ አልባሳትና<br />
ጥሬ የምግብ ሰብሎች የሚሰጡዋቸው ግብረ<br />
ሰናይ ድርጅቶች አሉ፡፡ በመረጃ አቀራረብ<br />
ረገድ መተላለፊያው ጠባብ ባይሆን ኖሮ<br />
በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ እርዳታ ፈላጊዎች<br />
እንደሚኖሩ መገመት አያዳግትም፡፡ በዚህ<br />
አይነት ሰቆቃ በእያንዳንዱ ድሃ ጎጆ ተደፍተው<br />
ሚያድሩ ረሃብተኛ ህፃናት አንጀት የሚበሉ<br />
ናቸው፡፡ የዚህ ሀገር መሪ መሆን እንደመርግ<br />
የሚከብድ አበሳ ለመሸከም ዝግጁ መሆንን<br />
እንጂ በመሬት ላይ ካለው ሃቅ ሸሽቶ ’’ድርቅ<br />
እንጂ ርሃብ የለም’’ ማለት ይገባል??<br />
ውድ አንባቢያን!<br />
ኢትዮጵያ ያላት ዋና ሀብት መሬት፣ውሃና<br />
ታታሪ ህዝቧ ነው፡፡ ይህንን አቀናጅቶ<br />
በመስራት ሀገራችን ከወደቀችበት አረንቋ<br />
መንጭቆ በማውጣት ድህነትና ርሃብን<br />
መሰናበት ይቻላል፡፡ ተደጋግሞ እንደሚነገረው<br />
በውሃ ሊለማ የሚችል ድንግል መሬት አለን፡<br />
፡ በተለይ በሰባቱ ታላለቅ ተፋሰሶቻችን<br />
ውስጥ ያለው በሚሊዮን ሄክታር የሚቆጠር<br />
ለም መሬት ለማረስና ለማልማት የሚያስችል<br />
በቂ የገንዘብ አቅም እንዳለ ይታወቃል፡<br />
፡ የኢህአዴግ መንግስት በያአመቱ ከአራት<br />
ቢሊዮን ዶላር በላይ በይፋ እርዳታ የሚያገኝ<br />
ከመሆኑም በላይ ይፋ ባልሆነ መንገድ<br />
የዚህን ሶስት እጥፍ እንደሚያገኝ የኢኮኖሚ<br />
ሊቃውንት ይናገራሉ፡፡ ይህ ሁሉ ለልማት<br />
የተትረፍረፈ ሀብት እያለ የሀገሩን ህዝብ<br />
ጩኸት እና ዋይታ ከማዳመጥ ይልቅ ላለም<br />
አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ጆሮ መስጠት<br />
ቀዳሚ አጀንዳ ሆኖዋል ይልቁንም ገንዘብ<br />
ካለን ሸምተን እንበላለን ማለት ይቀናቸዋል፡<br />
፡ በዛሬው አለም የምግብ እህል ዋጋ<br />
መናር አያስጨንቀንም፡፡ እንደ እውነቱ<br />
ከሆነ ኢትዮጵያ ያላትን ለም መሬትና ውሃ<br />
ተጠቅማ ብታርስ የአለምን የምግብ ዋጋ<br />
መናር በማረጋጋት እረገድ የራስዋን ድርሻ<br />
ልታዋጣ ከመቻልዋም በላይ በመቶ ሺህዎች<br />
የሚቆጠሩ የእርሻ ሰራተኞችን በማሰማራት<br />
ይልቁንም ርሃብና ድህነትን ከማስወገድ<br />
ጀምሮ ወደ ብልፅግና በመረማመድ የሀገሪቱን<br />
ገፅታ መለወጥ ይቻላል፡፡ የህንድ ገበሬዎችን<br />
ለማስፈር የመሬት ቅርምትን ከማስፋፋት<br />
ይልቅ የሀገራችንን ህዝብ ችግር እንፍታ፡<br />
፡ በባዶ ፕሮፖጋንዳ የሀገር ገፅታ ግንባታ<br />
አይኖርም!፡፡
2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />
ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />
“ ነጋ-እንዴና የግብሩ ...<br />
መስጫ ተቋማት የሚጠየቀውን ጉቦ የሚያስጥለው<br />
ባለመኖሩ ስለ ግብር አከፋፈል ዝቅተኛ እውቀት<br />
ብቻ ሳይሆን ጭርሱንም ላለመክፈል የሚያደርገውን<br />
ድብብቆሽ የሚያባብስበት እንጂ የሚመልስለት<br />
እንደማይሆን እሙን ነው፡፡<br />
ግብር ከፋዩ ዛሬ ግብሩን ከፍሎ ነገ ወደ<br />
አንድ ሕክምና መስጫ ማዕከል ጐራ ቢል ከጎንት<br />
(ግላቭ) ጨምሮ የተለያዩ የህክምና መድኃኒቶችን<br />
በጓሮ በር እያወጡ ለሚቸረችሩ ጥቅመኞች ቀድመው<br />
የተጋለጡ በመሆናቸው ሚስቱ ወይም ልጁ<br />
በግላቭ ወይም ጓንት እጦት ህይወታቸው ሲያልፍ<br />
እየተመለከተና እያዳመጠ ግብር ጠቀሜታው ላንተነው<br />
የሚለውን ፕሮፓጋንዳ እንዴት ሊያዳምጥ ይችላል?<br />
እንዲያዳምጥስ ይጠበቃልን ?፡፡<br />
ታታሪው ግብረኛ አመታዊውን ዜግናታዊ<br />
ግዴታ ተወቶና እፎይ ግብሬን ከፈልኩ ብሎ ለሌላ<br />
ጉዳይ ወደ ሌላ ቢሮ ሲገባ ለመሀንዲስ ትራንሰፖርት<br />
አቅርብ፣ ለልዩ ልዩ ጉዳዮች ማስፈጸሚያ ለምሣሌ እንደ<br />
የሰላም ትግል...<br />
ሰላማዊ የምርጫ ሰራዊት አንቀሳቀሰ። ይኽ ሰላማዊ<br />
ሰልፈኛ “ድምጽ ይከበር” በማለት ፓርላማውን<br />
ያዘ። ወታደሩ እና የፖሊስ ኃይል በምርጫ ፖለቲካ<br />
እንዳይገባ ተቃዋሚው ቀደም ብሎ ህጋዊ ስራ<br />
በመሰራቱ ጣልቃ ከመግባት ተቆጠቡ። የመንግስት<br />
ስልጣን ወደ አሸናፊ ፓርቲዎች ግንባር ተላለፈ።<br />
ይኽ ግንባር በውስጡ 16 ያህል ተቃዋሚ ፓርቲዎች<br />
ነበሩበት። እስቲ የዝንባቡዌን ሁኔታ እንመልከት።<br />
በዝንባቡዌ ተቃዋሚው ፓርቲ ደጋፊዎቹ<br />
በብዛት ወጥተው እንዲመርጡ በማድረግ እንዲሁም<br />
ምርጫው ነፃ እና ፍትሃዊ እንዲሆን አለም አቀፍ<br />
ህብረተሰብ በሙጋቤ አምባገነን መንግስት ላይ ጫና<br />
እንዲያሳርፍ በማድረግ ረገድ ጥሩ ዝግጅት አድርጎ<br />
ነበር። ምርጫውን ከሙጋቤ መንግስት ስርቆት<br />
የሚያድን “ፕላን ለ” (Plan B) ግን ቸል ተብሉ ነበር።<br />
የሙጋቤ መንግስት በምርጫ ሽንፈት ቢደርስበት<br />
ስልጣን እንደማይለቅ የሚጠቁሙ ምልክቶች ቀደም<br />
ብለው ይታዩ ነበር። በምረጡኝ ዘመቻ ወቅት<br />
በተቃዋሚ ፓርቲ ደጋፊዎች እና ፓርቲ ሰራተኞች<br />
ላይ ወከባዎች፣ ድብደባዎች፣ ግድያ፣ ማሳደድ<br />
እና እስር ቤት የማጎር ተግባራት ይፈጸሙ ነበር።<br />
በምርጫው ቀን ሳይቀር አለም አቀፍ ታዛቢዮች<br />
እየተመለከቱ ድምጽ ለመስጠት የተሰለፉ ዜጎች<br />
ይደበደቡ ነበር። ፖሊስ፣ ደህንነት፣ የጦር ኃይል፣<br />
ካድሬ፣ ሚሊሺያ፣ እና በገንዘብ የተገዙ ቦዘኔዎች<br />
ሳይቀሩ በተቃዋሚ ፓርቲ ደጋፊዎች ላይ አረመኔያዊ<br />
ተግባሮች ፈጸሙ። ተቃዋሚ ፓርቲ የመረጡ ብዙ<br />
ዜጎች ለህይወታቸው በመፍራት መኖሪያቸውን ለቀው<br />
ተሰደዱ። አገር ለቀው ወደ ደቡብ አፍሪካ የጎረፉት<br />
ጥቂት አልነበሩም። ምርጫ ለመታዘብ ከአውሮፓ<br />
ተጋብዘው ከመጡት ውስጥ ምርጫው ሳያልቅ አገር<br />
ለቀው እንዲወጡ የተደረጉ ነበሩ። ባጭሩ ምርጫው<br />
ተሰረቀ። የዝምባቡዌው ሙጋቤ እንደሰርቢያው<br />
ሞሊሶቪች አይኑን በጨው አጥቦ በምርጫው አሸናፊ<br />
መሆኑን አወጀ። የሞሊሶቪች አዋጅ ተቀባይ እንዳጣ<br />
አይተናል። የሙጋቤ አዋጅ ግን ተቀባይ አላጣም።<br />
ምክንያቱም ተቃዋሚው ፓርቲ ምርጫውን ከሙጋቤ<br />
ስርቆት ማዳን ባለመቻሉ። ተቃዋሚው ድምጽ<br />
ለማስከበር የሚያስችል ዝርዝር ፕላን እና የሰላም<br />
ትግል አቅም ስላልነበረው “ምርጫው ነፃ አይደለም፣<br />
ድምጽ ይጣራ፣ ሌላ ምርጫ ይደረግ” የሚሉ ፋይዳ<br />
ቢስ ጩኸቶች ከማሰማት፣ የሙጋቤን መንግስት<br />
በጎ ፈቃደኛነት ከመጠየቅ እና የምዕራቡን አለም<br />
ከመማጸን ባሻገር ምንም ማድረግ ሳይችል ቀረ።<br />
የዝንባቡዌው ተቃዋሚ ፓርቲ እንደ ሰርቢያ “ፕላን<br />
ለ” (Plan B) ያስፈልገው ነበር !!<br />
በምርጫ ሽንፈትን መቀበል ማለት ለገዢው ፓርቲ<br />
በአገር ውስጥ እና በአለም አቀፍ ደረጃ ህጋዊነትን<br />
ማጣት ስለሚሆን በስልጣን ላይ ያሉ አምባገነን<br />
መንግስቶች ሽንፈትን ለመቀበል ዝግጁ አይደሉም።<br />
ተቃዋሚ የዲሞክራሲ ኃይሎችም በምርጫ ያገኙትን<br />
አሸናፊነት ማስከበር ካልቻሉ በአገር ውስጥ እና<br />
በአለም አቀፍ ደረጃ የገዢነት እውቅናን እና ህጋዊነትን<br />
ማግኘት አይችሉም ! ህዝብን የመንግስት ስልጣን<br />
ባለቤት ማድረግ ዋዛ አይደለም።<br />
መታወቂያ ለመሳሰለው ይሄን ያህል ክፈል እየተባለ<br />
በሚጠየቅበት እና በሚከፍለው ግብር ልክ እንኳን<br />
ባይሆን እጅግ አናሳ አገልግሎቶች እንዲያጣ እየተደረገ<br />
ከዓመታት በኃላ ታገኛቸዋለህ ሲለሚባለው ትልልቅ<br />
ፕሮጀክቶች እንዲያስብ ለማድረግ መሞከር በእጅጉ<br />
አስቸጋሪ ነው የሚሆነው፡፡<br />
ከሁሉ በላይ ደግሞ ግብር የሚከፍለውም ሆነ<br />
ማይከፍለው፣ ህገውጡና ወንጀለኛው ነጋዴ ከንፁህና<br />
ታታሪው ነጋዴ ጋር ተደበላልቆ ለትንሹም ለትልቁም<br />
ጉዳይ እኩል ከተጉላላና አንዳንዴም ቅድሚያው<br />
ለህገወጡ ለወንጀለኛው ነጋዴ ሲሰጠው ከታየ ግብር<br />
በመክፈል የሚመጣውን ለውጥና ልዩነት መለፈፉ<br />
ነገሩን ከፈረሱ ጋሪውን ማስቀደም ያስመስላል፡፡<br />
ባለፈው ክረምት ውስጥ የከተማችን ከንቲባ<br />
በቴሌቪዥን መስኮት ብቅ ብለው ግንባራቸውን እንደዛ<br />
ከስክሰው ስለግብር ሲያስረዱ ለተመለከተ ግብር<br />
በዜጐች ቀና አመለካከትና ፈቃደኝነት ፍፁም ለአገርና<br />
ሕዝብ እድገት ተገዢ በመሆን የሚከፈል የንፁህ ነፍስ<br />
ከገፅ 5 የዞረ<br />
የሆነው ሆኖ መቀየር/መለወጥ (Peaceful<br />
conversion) እና መቻቻል (Peaceful<br />
accommodation) የተባሉት ለውጥ ማምጫ<br />
መንገዶች ለገዢው ቡድን ከተቃዋሚዎች የቀረበለትን<br />
ጥያቄ የመቀበል እና ያለመቀበል ምርጫ ይሰጣሉ።<br />
ገዢውን ቡድን ማስገደድ አይችሉም። ሰላማዊ<br />
ማስገደድ (Peaceful coercion) የተባለው ለውጥ<br />
ማምጫ መንገድ ግን ገዢው ቡድን የቀረበለትን<br />
የለውጥ ጥያቄ እንዲቀበል ማስገደድ ይችላል።<br />
እንመልከት።<br />
(3ኛ) ሰላማዊ ማስገደድ (Peaceful coercion)<br />
ሰላማዊው ትግል ማስገደድን ተፈጻሚ ማድረግ<br />
ከሚችልበት ደረጃ ከደረሰ በስልጣን ላይ ያለው<br />
አምባገነናዊ መንግስት አቅም እጅግ ዝቅ ብሏል ማለት<br />
ነው። በአንጻሩ የዲሞክራሲ ኃይሎች የፖለቲካ ኃይል<br />
ከፍ ብሏል ማለት ነው። ጉልህ የፖለቲካ ኃይል ሚዛን<br />
ግንኙነት ሽግሽግ ተደርጓል ማለት ነው። የሆነው ሆኖ<br />
የገዢውን ቡድን ህልውና ላይ ስጋት የሚያሳድሩ<br />
አስገዳጅ ጥያቄዎች ከመቅረባቸው በፊት ግን<br />
ተቃዋሚው ጥንቃቄ የተሞላበት ፕላን መቀየስ እና<br />
ሰፊ የአቅም ዝግጅት ማድረግ ይኖርበታል። ተፈጻሚ<br />
ሊሆኑ የማይችሉ አስገዳጅ ጥያቄዎች ማቅረብ በህዝብ<br />
ዘንድ ተዓማኒነት ያሳጣል። የፕላን አለመጠናቀቅ<br />
ወይንም የትግል አቅም ማነስ ካለ አስገዳጅ ጥያቄዎችን<br />
ከማቅረብ መቆጠብ ወይንም አኪያሄድን ማስተካከል<br />
ይመረጣል። በስልጣን ላይ ያለው አምባገነን መንግስት<br />
የቀረበለትን አስገዳጅ የለውጥ ጥያቄ ፈቃደኛ ሳይሆን<br />
ተገዶ ከተቀበለ ማስገደድ ተሳካ ሊባል ይችላል።<br />
የሰርቢያን እና የዝምባቡዌን ሁኔታዎች እንመልከት።<br />
(4ኛ) (Peaceful disintegration)<br />
ከፍ ብለን እንዳየነው ተቃዋሚው በስልጣን<br />
ላይ ያለውን መንግስት ማስገደድ ከቻለ በገዢው<br />
ቡድንና በህዝብ መካከክል ተጨባጭ የሆነ የስልጣን<br />
ሽግሽግ ተደርጓል ማለት ነው። የፖለቲካ ኃይል ሚዛን<br />
ግንኙነት ወደ ተቃዋሚ ማድላቱ በእርግጠኛነት<br />
ከታወቀ የፖለቲካ እምቢተኛነት (Political defiance)<br />
ትብብር መንፈግ (Non-cooperation) እና ጣልቃ<br />
መግባት (Intervention) የተባሉትን የሰላም ትግል<br />
መሳሪያዎች በመጠቀም ስርዓቱን በበርካታ ግንባሮች<br />
ማጥቃት ይቻላል። ይኽ ጥቃት ቀጣይነት ካለው<br />
የፖለቲካ ኃይል ምንጮች እንደሚደርቁ እና መንግስት<br />
ተርቦ እንደሚፈረካከስ መገመት አያዳግትም።<br />
በመጨረሻ በኢትዮጵያ ሰላማዊ ትግል ህዝብን<br />
የመንግስት ስልጣን ባለቤት ማድረግ እንደሚችል<br />
በመተንተን ጥናታችንን እንፈጽማለን። በኢትዮጵያ<br />
ህዝብን የመንግስት ስልጣን ባለቤት ማድረግ<br />
የሚችልባቸው ሁለት አማራጭ ቀዳዳዎች አሉ ማለት<br />
ይቻላል። እነሱም፡-<br />
(1) አንደኛው አማራጭ በሰሜን አፍሪካ እና<br />
በመካከለኛው ምስራቅ የአረቡ ህዝብ የመረጠው<br />
መንገድ ነው። ህዝብ ለመንግስት የሰጠውን የገዢነት<br />
መብት እና ክብር በመንፈግ ህጋዊነቱን ገፍፎ ከስልጣን<br />
ማውረድ ይችላል። ህዝብ በፈለገው ጊዜ የመንግስት<br />
ለውጥ የማድረግ መብት እንዳለው የታወቀ ነው።<br />
የግብጹ ፕሬዘዳንት ሙባረክ የተመረጠበትን የአራት<br />
ከገፅ 10 የዞረ<br />
ስርዓት መገለጫ ሳይሆን ክተት የተዋጀበት ጦርነት<br />
አስመስለው ማቅረባቸው አሁንም ግብርን በተመለከተ<br />
ገዢው ፓርቲ ለራሱ በራሱ ያልገባው ስነልቦናዊ<br />
አመለካከት እንዳለ አስረጂ ነው፡፡ ይህንንም ስል ግብር<br />
መብትም ግዴታም እንደሆነ በሙሉ ልቤ ስለማምንበት<br />
ብቻ ሳይሆን እንደ ሃይማኖታዊ ትዕዛዝ የተቀበልኩት<br />
መሆኔንም ጭምር ለማሳወቅ ነው፡፡<br />
አለመታደል ሆኖ እንጂ ለጉዳይ በምንሄድባቸው<br />
የተለያዩ ህዝባዊ ሆነ መንግሥታዊ ተቋማት፣ ለምርጫ<br />
በቀረብንባቸው የምርጫ ጣቢያዎች፣ ፓርላማ፣<br />
ሆስፒታል ወዘተ ልባችን ሞልተን፣ ደረታችን ነፍተን<br />
እኔእኮ ግብር ከፋይ ነኝ! ያንተን ደሞዝ የምከፍልህ<br />
እኔነኝ ለማለት ቅንጣት ፍርሀትና የዛኛው ወገን አሉታዊ<br />
ምላሽ የምንፈራ ባልሆን ነበር፡፡ ይህን ግን አልሆነም<br />
ለዚህም አልታደልንም ግብር እንዲህ በትንሹ ነገርግን<br />
ትልልቅ ጉዳዮችን ተሸክሞ ባልጠራበት ሁኔታ እየተጓዘ<br />
ገዢው ፓርቲ የኢህአዴግ ደጋፊ ነጋዴዎች ፎረም<br />
የሚል ስያሜ ነጋዴው ላይ በመለጠፍ ነጋዴው እርስ<br />
ወይንም የአምስት አመት የስልጣን ዘመኑን ሳይጨርስ<br />
ከስልጣን እንደተወገደ እናስታውሳለን። ባጭሩ ህዝብ<br />
እምቢ አልገዛም ካለ መንግስት ሊኖር አይችልም።<br />
የኢትዮጵያ ህዝብ ይኽን አማራጭ ከመረጠ የትግሉ<br />
ባለቤት እራሱ ህዝቡ ነው የሚሆነው። የተቃዋሚ<br />
ፓርቲዎች ሚና ከህዝብ ጎን መቆም ነው የሚሆነው።<br />
(2) ሁለተኛው አማራጭ “ለድምጽ ስርቆት<br />
የማይች ምርጫ ማድረግ” ወይንም በአጭሩ<br />
“የማይሰረቅ ምርጫ” ብለን የምንጠራው ነው።<br />
የኢትዮጵያ ህገ መንግስት በምርጫ ሰላማዊ የመንግስት<br />
ሽግግርን ይፈቅዳል። ይኽ ህገ መንግስታዊ ድንጋጌ<br />
ቢያንስ በወረቀት ላይ ለመንግስት ለውጥ ጥያቄ<br />
ያመቻቻል መልስ ይሰጣል። ነገር ግን በኢትዮጵያ<br />
በስልጣን ላይ ያለው መንግስት በፈጠራቸው የምርጫ<br />
ቦርድ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ ካድሬዎች እና<br />
ሲያስፈልግ ፖሊስ በመጠቀም ምርጫ ስለሚሰርቅ<br />
የኢትዮጵያን ህዝብ የመንግስት ስልጣን ባለቤት<br />
እንዳይሆን ያደርጋል። ይኽን ምርጫ የመስረቅ<br />
ችግር መቋቋም ከተቻለ በህገ መንግስት የተደነገገው<br />
ይመቻቻል መፍትሄው የከፈተውን ቀዳዳ መጠቀም<br />
እንደሚቻል ግልጽ ነው። የመንግስትን ምርጫ<br />
መስረቅ ለመከላከል “ነፃ አውጭ” የተባለ ተቃዋሚ<br />
ቡድን ጫካ ገብቶ የእርስ በርስ ጦርነት መጀመር<br />
የለበትም። ከዚኽ በኋላ የኢትዮጵያ ህዝብ የአዞ እንባ<br />
ረጪ ነፃ አውጪዎች አያስፈልጉትም። ህዝቡ ራሱን<br />
ነፃ ማውጣት አለበት። አብረውት እየኖሩ የሚታገሉ<br />
የሰላማዊ ትግል መሪዎች በሚለግሱት እገዛ ብቻ ራሱ<br />
ህዝቡ የሚያስፈልገውን መስዋዕት በመክፈል ድምጹን<br />
ከስርቆት ተከላክሎ የመንግስት ስልጣን ባለቤት<br />
መሆን ይችላል። ዛሬ ዲሞክራሲ በሆኑ አብዛኛዎቹ<br />
አገሮች ህዝቡ ነው እራሱን በሰላማዊ ትግል ነፃ<br />
ያወጣው። ለዲሞክራሲ ሽግግር አስተማማኙ<br />
መንገድም ይኸው ህዝቡ የተሳተፈበት ሰላማዊው<br />
መንገድ ነው። የኢህአዴግ መንግስት የኢትዮጵያን<br />
ህዝብ ድምጽ አላከብርም ካለ የኢትዮጵያም<br />
ህዝብ በበኩሉ አልገዛልህም ማለት አለበት። ህዝብ<br />
የኢትዮጵያ ህዝብ ድምጹ እንዳይሰረቅ የመጠበቅ<br />
መብትም አለው። ድምጽህን እኛ እንጠብቅልሃለን<br />
የሚሉ የአዞ እንባ ረጪ ካድሬዎችንም ያለማመን እና<br />
በድምጽ አሰጣጥ እና በድምጽ ቆጠራ ላይ በተወካዮቹ<br />
አማካኝነት የመሳተፍ መብትም አለው።<br />
የሆነው ሆኖ የኢትዮጵያ ህዝብ በህገ መንግስቱ<br />
ውስጥ የተጠቀሰውን የምርጫ (መቻቻል) ድንጋጌ<br />
ከ“ፕላን ለ” ጋር አዳቅሎ መጠቀምን ከመረጠ ከህዝቡ<br />
ጋር አብረው የሚኖሩ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ብዙ<br />
ስራ ይጠበቅባቸዋል። በኢትዮጵያ የምርጫ ቦርድ<br />
እና የምርጫ አስፈጻሚዎች ገለልተኛ እንዲሆኑ እና<br />
አለም አቀፍ ምርጫ ታዛቢዎች በብዛት እንዲሰማሩ<br />
ከመደራደር አንስቶ ህዝቡ ድምጹን ከስርቆት<br />
እንዲጠብቅ የማዘጋጀት ኃላፊነት አለባቸው። የሰላም<br />
ትግል ሰራዊት መገንባት ይኖርባቸዋል።<br />
ከፍ ብለው የተመለከቱት ሁለቱም አማራጮች<br />
የሰላም ትግል ሰራዊት ይሻሉ። ለመሆኑ የሰላም ትግል<br />
ሰራዊት ማን ነው? ኢንጅነሮች፣ መምህራን፣ የህግ<br />
ባለሙያዎች፣ የህክምና ባለሙያዎች፣ ተማሪዎች፣<br />
13<br />
በርስ የጎሪጥ እንዲተያይ በአሜት እንዲበላላ መንገድ<br />
ከፍቶለት ይገኛል፡፡<br />
አመታዊውን የሕዝብ ምንዳቸውን በተገቢው መልክ<br />
የሚከፍሉ ሕዝቤና አገሬ አድገው አያቸዋለሁ የሚሉ<br />
እንዳሉ ሁሉ ከባለሥልጣን ጋር በመሞዳሞድ፣ በዘር፣<br />
በቋንቋ፣ በቡድን፣ በኃይማኖት በመጠላላለፍ እና<br />
በመሳሳብ ከሕገወጡ ከኮንትሮባንድ ንግድ ጀምሮ<br />
ሰነድ እስከመደለዝና ማዘጋጀት አልፎ የሕዝብ ንብረት<br />
የሆኑ እንደ መሬት ማምረቻና ማከፋፈያ ተቋማትን<br />
ወደ እራሳቸውን ግብረ አበሮቻቸው የሚያዘዋውሩ<br />
ጥቂት አይደሉም፡፡ የሚያሳዝነው ደግሞ ይህን አደገኛ<br />
አካሄድ የሚቀላቀሉ ግለሰቦች ቁጥር ከእለት ወደ እለት<br />
በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ መምጣቱ ሌላው አደገኛ እና<br />
አሳሳቢ ሁኔታ ነው፡፡ አሁንም የዘንድሮ የግብር ዓመቱ<br />
ጥቅምት 30/2004 ዓ.ም እንደሚገባደድ የታወቀ ነው፡፡<br />
ቢሆንም ግን ምን ያህሉ ከጨዋታ ውጪ እንደሚሆንና<br />
ምን ያህሉም ተፍገምግሞ ምን ያህሉም ተዝናንቶ<br />
እንደሚቀጥል ይለይለታል፡፡<br />
ኢኮኖሚስቶች፣ የባንክ ሰራተኞች፣ የቴሌ፣ የመብራት<br />
ኃይልና የውሃ ሀብት ሠራተኞች አርቲስቶች፣ ታክሲ<br />
ነጂዎች፣ ግንበኞች፣ ሱቅ ነጋዴዎች፣ እናቶች፣<br />
አባቶች፣ የከተማ እና የገጠር ኗሪ ባጠቃላይ የሀገሪቱ<br />
ለውጥ ፈላጊ ዜጎች ሁሉ ሰላማዊ የዲሞክራሲ ኃይል<br />
ናቸው። የሰላም ትግል ሰራዊት አባላት ስራቸውን<br />
ሲጨርሱ ወደ መደበኛ ስራቸው የሚመለሱ ዜጎች<br />
ናቸው። አምባገነን መንግስትን ከስልጣን ለማስወገድ<br />
የሚደረግ ቀጣይነት ያለው የትጥቅ ትግል የሰለጠነና<br />
የተደራጀ መደበኛ የጦር ኃይል ሊኖረው እንደሚገባ<br />
ሁሉ የህዝብ ድምጽ እንዳይሰረቅ ለማድረግም ሆነ<br />
የህዝብ ድምጽ አላከብርም ያለ አምባገነን መንግስትን<br />
በሰላማዊ ትግል ከስልጣን ለማስወገድ የሚደረግ<br />
የሰላም ትግልም የሰለጠነ፣ የተደራጀ እና በድስፕሊን<br />
የታነጸ የሰላም ትግል ሰራዊት ያስፈልገዋል። የሰላም<br />
ትግል ሰራዊት ራሱን ከመንግስት ወሬ አቀባዮች<br />
(in<strong>for</strong>mers) እና ከመንግስት መልክተኛ ቆስቋሾች<br />
በመጠበቅ ረገድም የሰለጠነ ነው። በመኪና ነዳጅ<br />
ውስጥ ውሃ መቀላቀል የመኪና ነዳጅን እንደሚበክል<br />
ሁሉ የሰላም ትግል በካዮችም እንዳሉ የሚያውቅ እና<br />
በጥንቃቄ የሚጓዝ ኃይል ነው። የሰላም ትግል ሰራዊት<br />
ከገዢው ፓርቲ ደጋፊዎች ጋር ግጭት ቀርቶ ክፉ ቃል<br />
መቀያየር እንደማያስፈልግ ያውቃል። የሰላም ትግል<br />
ሰራዊት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የሰለጠኑ አባሎች<br />
ስለሚያሳትፍ የተወሰኑ መሪዎች ቢታሰሩም ትግሉ<br />
ይቀጥላል። አምባገነኖች የአገሪቱን ህዝብ በሙሉ<br />
የሚያስሩበት እስር ቤት የላቸውም።<br />
በፍኖተ ነፃነት ቁጥር 4 በአክሱም ዘመን የነበረው<br />
የመንግስት ሽግግር ባህላችን አስከፊ እንደነበር<br />
ተመልክቷል። ከዘመነ አክሱም ወዲህ ኢህአዴግ<br />
ስልጣን እስከጨበጠበት ድረስም ቢሆን የመንግስት<br />
ሽግግር ታሪካችን ይበልጥ አስከፊ እየሆነ እና ኋላቀር<br />
እያደረገን እንጂ ወደፊት እንድንራመድ አንዲት<br />
ጋት አልረዳንም። በእርስ በርስ ጦርነት የሚደረግ<br />
የመንግስት ሽግግር ቢትዮጵያ ላይ ያደረሰው ኪሳራ<br />
በፍኖተ ነፃነት ቁጥር 12 ቀርቧል። በእርስ በርስ<br />
መገዳደል የሚፈጸም የመንግስት ስልጣን ሽግግር<br />
በኢትዮጵያ መቆም አለበት። ኢትዮጵያ ህዝብ<br />
የመንግስት ስልጣን ባለቤት የሚሆንበት ዘመናዊ<br />
የመንግስት ሽግግር ባህልን ተቀብላ በዘመናዊ<br />
መንግስት መመራት መጀመር አለባት። ለዚህ<br />
አስተማማኙ የፖለቲካ ትግል መንገድ ሰላማዊ ትግል<br />
ነው። ከፍ ብለን ያየናቸው ሁለት አማራጮች የሰላም<br />
ትግል መንገዶች ናቸው። ለዲሞክራሲ የሚደረግ<br />
ትግል በየትም አገር ቢሆን ቀላል ሆኖ አያውቅም።<br />
ይሁን እንጂ ከገዢ አምባገነኖች አቅም ጨቁነው<br />
የሚገዙት ህዝብ አቅም ሚሊዮን ጊዜ እንደሚበልጥ<br />
ላፍታ መዘንጋት የለብንም። ስለዚኽ በረጅሙ<br />
አስፈላጊው ጥናት እና ዝግጅት ከተደረገ፣ አቅም<br />
ከተገነባ፣ ስትራተጂዎች እና ፕላኖች በጥንቃቄ ከተሰሉ<br />
በኢትዮጵያ የሰላም ትግል መስራት ብቻ ሳይሆን<br />
ለኢትዮጵያ ተመራጩ የፖለቲካ እና የመንግስት<br />
ሽግግር ባህል እሱ ብቻ ነው በማለት ጥናታችንን<br />
እንደመድማለን።<br />
www.andinet.org.et
14<br />
ኢሕአዴግና መገናኛ ...<br />
www.andinet.org.et<br />
የግሉን ሚዲያ በተመለከተ ምርጫ 97 ለኢትዮጵያ<br />
ያመጣው መልካምም መጥፎ ነገሮችም አሉ።<br />
የኢትዮጵያ ሚዲያ ላይ ከፍተኛ ጥናት ያደረጉና<br />
ስማቸው እንዳይገለፅ የጠየቁ ምሁር እንደሚሉት<br />
“መልካም ነገር የምለው በአገር ውስጥና በዓለም<br />
ዓቀፍ ጫናዎች ምክንያት ኢሕአዴግ በጭራሽ<br />
ፍቃድ ሊሰጠው የማይፈልገው የነበረውን የሬዲዮ<br />
ፍቃድ መስጠቱ ነው። በእርግጥ ፍቃድ አሰጣጡ<br />
ጥንቃቄ ያልተለየው መሆኑ የሚያስታውቀው፣<br />
የኤፍ.ኤም ሬዲዮ መስመሮች መሆናቸውና ለሦስት<br />
ድርጅቶች ብቻ መፈቀዱ ነው።” ይላሉ። እነዚህ<br />
ሶስት በስራ ላይ ያሉት የኤፍ.ኤም ሬዲዮ ጣቢያዎች<br />
ዛሚ FM 90.7፣ ፋና FM 98.1 እና ሸገር FM 102.1<br />
ናቸው።<br />
በ1999 ዓ.ም የፀደቀው ስለብሮድካስት አገልግሎት<br />
የወጣው አዋጅ በአንቀጽ 23(3) ላይ “የፖለቲካ<br />
ድርጅት ወይም የፖለቲካ ደርጅት ባለአክስዮን<br />
የሆነበት ወይም የፖለቲካ ድረጅት የበላይ አመራር<br />
አባል ባለአክስዮን ወይም በማንኛውም ደረጃ<br />
የአመራር አባል የሆነበት ድርጅት” የብሮድካስት<br />
ፍቃድ እንደማይሰጠው ያውጃል፡፡በኢትዮጵያ<br />
የመገናኛ ብዙሃን ላይ እንደሚያሳየው ዛሬ<br />
በኢትዮጵያ አንድ ሙሉ በሙሉ በመንግሥት<br />
ቁጥጥር ስር ያሉ የቴሌቪዥን ጣቢያና አስር የሬዲዮ<br />
ጣቢያዎች እንዳሉ ይገልፃል፡፡ ይህ ጥናት በግልፅ<br />
እንዳስቀመጠው ስምንቱ ክልላዊ ሽፋን (FM)<br />
ሲኖራቸው፤ ሁለቱ ደግሞ በክልል ደረጃም በአገር<br />
አቀፍ ደረጃም ስርጭት ያስተላልፋሉ፡፡<br />
ምሁሩ ድህረ 97 የተጋረጠ ከባድ ፈተና የሚሉት<br />
ዸግሞ በአጠቃላይ የሚዲያ ተቋማትን የተመለከተ<br />
ቢሆንም፤ እጅግ የከበደው ፈተና ግን ወደ ነፃው<br />
ፕሬስ ማድላቱን ያሰምሩበታል። “ኢሕአዴግ<br />
ከምርጫ 97 በፊት የነፃው ፕሬስ ተፅዕኖ ከቁጥጥሩ<br />
እንደማይወጣ የነበረው እምነት ስህተት መሆኑን<br />
የተረዳው በምርጫው ጊዜ ነበር። ስልጣኑን<br />
ጭምር ሊያሳጡት የሚያስችል አቅማቸውን<br />
በማየቱ ከምርጫው በኋላ በወሰዳቸውና አሁንም<br />
ከሚወስዳቸው እርምጃዎች በቀላሉ ለመረዳት<br />
ይቻላል።” ይላሉ። ለዚህ አባባላቸውም ማስረጃ<br />
አድርገው የሚያቀርቧቸው ዋና ዋናዎቹ የገዢው<br />
ፓርቲ እርምጃዎች በ2001 ዓ.ም የወጣው<br />
የማያላውሰው የሚዲያ ህግንና የአዲስ ነገር ጋዜጣን<br />
እጣ ፈንታ ነው።<br />
የ42 ዓመቱ ሸምሱ ኢቲቪ 3 አልጠራ ብሎት<br />
የቴሌቪዥኑን የውስጥ አንቴና አንዴ ቴሌቪዥኑ<br />
ላይ ይሰካዋል፣ አንዴ ግድግዳው ላይ ይሰካዋል፣<br />
አንዴ ገመድ ቀጥሎበት ከቤቱ ውጭ አጣና አቁሞ<br />
ቢሰቀለውም፤ ጥርት ያለ ምስልና ድምፅ ማግኘት<br />
አልቻለም። ይህን ሁሉ ድካም የሚያይበት ምክንያት<br />
“ኢቴቪ አንድና ሁለት ልዩነት ስለሌላቸው፣ ኢቴቪ<br />
ሦስት የተለየ ነገር ይኖረዋል።” በሚል ተስፋ<br />
መሆኑን ይናገራል። የመስሪያም የመኖሪያም<br />
ስፍራው በሆነችው ትንሿ “ሻይ ቤት” ውስጥ ቀኑን<br />
ሙሉ ተከፍቶ የሚውለው ቴሌቪዥኑ፤ ከኢትዮጵያ<br />
ቴሌቪዥን በስተቀር የሳተላይት ቴሌቪዥን<br />
ፕሮግራሞችን ለመሳብ የሚያስችል መቀበያ ሳህን<br />
ስለሌለው መሆኑን ያስረዳል።<br />
ትንሿ ሻይ ቤቱ በደንበኞች የምትጨናነቀው<br />
በምሳ ሰዓትና በእራት ሰዓታት ነው። በመጠነኛ<br />
ዋጋ የሚሸጣቸው ከሻይ ጀምሮ ያሉት ሌሎች<br />
ምግቦቹን ከኢቴቪ በሚተላለፉት የሰባት ሰዓትና<br />
የምሽት ሁለት ሰዓት ዜናዎች አጅቦ ያቀርባቸዋል።<br />
አብዛኛዎቹ ደንበኞቹ መገናኛ አካባቢ የህንፃ መሳሪያ<br />
በሚሸጥባቸው መደዳ ሱቆች ውስጥ የጉልበት ስራ<br />
የሚሰሩ ሰራተኞች ናቸው። ሲሚንቶና የአርማታ<br />
ብረት የመሳሰሉትን ከመኪና ወደ ሱቆቹ፣ ከሱቆቹ<br />
ወደ መኪና ይጭናሉ፣ ያወርዳሉ። ደንበኞቹን<br />
በከፍተኛ ክብካቤ የሚያስተናግደው ሸምሱ፣<br />
ደንበኞቹ በሁለት ነገሮች ቀልድ እንደማውቁ<br />
ይናገራል። በምግባቸውና በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን።<br />
“አድካሚ የጉልበት ሥራ ስለሚሰሩ፣ ምግባቸውን<br />
በጥራት ብቻ ሳይሆን በፍጥነትም ማቅረብ አለብህ”<br />
ይላል። ከተቀመጠበት እንደነገሩ ወደ ተቀመጠው<br />
ቴሌቪዥን እያማተረ። በምሳና በእራት ሰዓታት<br />
ደምበኞቹ ከምግባቸው ጋር እንዲቀርብላቸው<br />
የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንን የቀትር የሰባት ሰዓትንና<br />
ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />
ከገፅ 7 የዞረ<br />
የምሽት ሁለት ሰዓት ዜናን ነው። ከዜናውም<br />
የስፖርት ዜናውን። የምግብ ቤቷ ደንበኞች፤ የስራ<br />
ልብሳቸውን እንኳን ሳይቀይሩ፣ ሲሚንቶ የጠጣውን<br />
ፀጉራቸውን ሳያራግፉ ቶሎ ምሳቸውን በልተው ወደ<br />
ሥራቸው ለመመለስ ሲጣደፉ ይታያሉ። አንዳንዶቹ<br />
ከላይ ካደረጉት ካኪ ቱታ ሥር የአርሰናል፣ የቼልሲና<br />
የማንቸስተር ዩናይትድ እግር ኳስ ቡድኖች<br />
ማሊያዎችን /ቲ-ሸርቶች/ ማድረጋቸው ይታያል።<br />
ሰባት ሰዓት ሞልቶ የኢቴቪ የዕለቱ ዜና መቅረብ<br />
ቢጀምርም፤ ተመጋቢዎቹ ግድ የሰጣቸው<br />
አይመስልም። ፕሬዝዳንት ግርማ ለሁለቱ ምክር<br />
ቤቶች “በአሜሪካ የተከሰተውን የኢኮኖሚ …..”<br />
ቢልም ዜና አንባቢው ግድ የሰጣቸው አይመስልም።<br />
በየከበቡት ጠረጴዛና እጃቸውን በየሚሰዱበት<br />
ትሪ ላይ አፍጥጠው፣ አልፎ አልፎ ገልመጥ እያሉ<br />
የተከፈተውን ቴሌቪዥን እየቃኙ የራሳቸው<br />
“ወግ” ይጠርቃሉ። ዜና አቅራቢው “አሁን ለሰዓቱ<br />
ወደያዝናቸው የስፖርት …….” የጀመረውን ዓረፍተ<br />
ነገር ከመጨረሱ በፊት “ስፖርት” የሚለውን ቃል<br />
ሲጠራው፤ ከየጠረጴዛው “ዝም በሉ እስፖርት<br />
እንስማ” የሚሉ ድምፆች መውጣት ጀመሩ።<br />
የቴሌቪዥኑ ድምፅ ከፍ እንዲል ተጠየቀ። ታዛዡ<br />
ሸምሱ ድምፁን ጨመረ።<br />
የአገር ውስጥ የስፖርት ክንውኖች ቀረቡ። የውጭ<br />
አገር ስፖርታዊ ክንውኖች በተለይም እ.ኤ.አ የ2012<br />
የአውሮፓ ዋንጫ ማጣሪያ ግጥሚያዎች በምስል<br />
ተደግፈው በጥሩ ትንታኔ በቴሌቪዥኑ መስኮት<br />
ታዩ። የስፖርት ዜናው አብቅቶ ወደ ዋና ዋና ዜናዎች<br />
መመለሱን ዜና አቅራቢው ከመናገሩ በጫጫታ<br />
ተሞላች። “ፈረንሳይ አለፈች፣ የናስሪን ፔናሊቲ<br />
አመታት አየኸው?”፣ “የክርስቲያኖ ሮናልዶን ጐል<br />
ተመለከትህ?”፣ “ፓርቹጋል መሸነፏ ያሳዝናል።”<br />
ሌላም ሌላም የኳስ ትንታኔም አስተያየትም<br />
እየተሰጣጡ ሻይ ቤቷን ጥለው ወጡ። ምሳቸውን<br />
ከኢቴቪ የስፖርት ዜና ጋር አጣጥመው፣ ለራታቸው<br />
የሚሆን ገንዘብ ለማግኘት ወደ ሥራቸው ተመለሱ።<br />
ሸምሱንና ቴሌቪዥኑን ለብቻቸው ትተው።<br />
ሸምሱም አንዴ የቴሌቪዥኑን የርቀት መቆጣጠሪያ፤<br />
አንዴ ውጭ አጣና ላይ የሰቀለውን አንቴናን<br />
መነካካት ይጀምራል። የኢቴቪ ሦስትን የጠራ<br />
ድምፅና ምስል ለማግኘት። ፍለጋውን ይቀጥላል<br />
እስኪሳካለት ድረስ። ወይም ደምበኞቹ ሁለት ሰዓት<br />
መሙላቱን እስኪነግሩት ድረስ።<br />
ኢሣት ያመጣው ጣጣ<br />
ሰለሞን ቻላቸው በህይወቱ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንን<br />
እንደመመልከት የሚጠላው ነገር ያለ አይመስልም፡<br />
፡ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ሲባል መንገሽገሽ<br />
ይጀምራል፡፡ ቤተሰቡ ውስጥ በአማርኛ ዜና<br />
መመልከት የሚፈልግ ሰው በመኖሩ ግን ዘወትር<br />
ማታ ቴሌቪዥኑ ፊት ማፍጠጥ ግድ ሆኖበታል፡<br />
፡ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ሁለትም ሆነ ሦስት<br />
ወይም አራት ግድ እንደሌለው ይናገራል፡፡ በፊት<br />
በፊት የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን እንዳይከፈት ነበር<br />
ከቤተሰቡ ጋር ሲከራከር የከረመው፡፡ ቀድሞ የሱን<br />
ሃሳብ ደጋፊ የነበረችው ታናሽ እህቱ በእሱ አገላለፅ<br />
“ሌላውን ዓይነት ኢቴቪ” ካልተመለከትኩ እያለች<br />
ታስቸግረዋለች፡፡<br />
ሰለሞን እንደሚለው EBS የተባለውን በዲሽ<br />
የሚተላለፈውን ጣቢያ የኮሌጅ ተማሪ የሆነችው<br />
እህቱ ካላየን ብላ ታስቸግረዋለች፡፡ እንደ ዕምነቱ<br />
EBS የተከፈተው ESAT ጣቢያን ለማስቀየስ ነው፡<br />
፡ በፖለቲካ ጉዳዮች ላይ ንቁ ተሣታፊ መሆኑን<br />
የሚገልፀው ሰለሞን “መንግሥት በፈጠራት በዚች<br />
ትንሽ መሸወጃ” እህቱን ጨምሮ ብዙ ሰዎች ሲሸወዱ<br />
መመልከቱ እንደሚያናድደው እጁን እያወናጨፈ<br />
ይናገራል፡፡አማራጭ ሲያጣ ሸገር ኤፍ ኤምን<br />
ለመስማት መኝታ ቤቱ መደበቅ ብቸኛ መፍትሄው<br />
መሆኑን ያስረዳል ፡፡<br />
የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲና ብቸኛው<br />
የተቃዋሚ ፓርቲ የምክር ቤት አባል የሆኑት<br />
የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ ደግሞ የተለየ ሃሳብ<br />
አላቸው፡፡ “ኢቴቪን ለማየት ምንም የሚያጓጓ<br />
ነገር የለውም፡፡ እንደ ህዝብ ተወካይነታቸው ግን<br />
የመንግሥትን ወቅታዊ አቋሞችና ሃሳቦችን ለማወቅ<br />
ብቻ የሚከታተሉት መሆኑን ገልፀዋል፡፡” አቶ<br />
ግርማ ከዚያ ይልቅ በጣም የሚገርማቸው ጠቅላይ<br />
ሚንስተሩን ጭምር ጠይቀው መልስ ያላገኙለት<br />
ጥያቄ ኢቴቪ አንድ ሆኖ በብቃት መስራት ሳይችል<br />
ሁለትና ሶስት የመሆኑ ሚስጥር ነው፡፡<br />
የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ሚዛናዊነት<br />
አቶ ሰለሞን ኃይለ ማርያም “Trans<strong>for</strong>ming State<br />
Broadcasting in to Public Service Broadcasting<br />
in <strong>Ethiopia</strong>” በሚለው ከ1997 ዓ.ም በፊት<br />
በተሰራው ጥናታቸው እንዳሳዩት የኢትዮጵያ ሬዲዮ<br />
ድርጅት አየር ላይ ካዋላቸው የሁለት ሰዓት ዜናዎች<br />
ውስጥ 74.8% የሚሆኑት ይሰሩ የነበሩት በጣቢያው<br />
ጋዜጠኞች ሳይሆን በኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት<br />
እንደነበር ያስረዳሉ፡፡ ጣቢያው በሁለት ሰዓቱ<br />
የማታ የዜና ክፍለ ጊዜው ያሰራጫቸውን ዜናዎች<br />
በመውሰድ የተደረገው ይህ ጥናት እንደሚያሳየው<br />
የዜናው አንባቢዎች ብቻ ሳይሆኑ፤ የዜና አራሚዎቹ<br />
ጭምር የዜናውን ሚዛናዊነት፣ ትክክለኛነትና ነፃ<br />
መሆን ማረጋገጥ እንደማይችሉ ይገልፃል፡፡<br />
ይኸው ተመሳሳይ ጥናት የደረሰበት ድምዳሜ<br />
እንደሚያሳየው ባለስልጣናት በቃል በሚሰጡት<br />
ትዕዛዝ ምክንያት፣ የጣቢያው ጋዜጠኞች<br />
የተዛባ፣ ትክክል ያልሆነና ሚዛናዊ ያልሆኑ<br />
ዘገባዎችን እንዲያስተላልፉ እንደሚገደዱ ፅፏል፡<br />
፡ በተጨማሪም ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸው፣<br />
በመንግሥት ላይ ሂስ የሚሰነዝሩ ዜናዎች በጣቢያው<br />
ጋዜጠኞች ቢዘጋጁም፤ ብዙ ጊዜ ዕጣ ፈንታቸው<br />
ውድቅ መደረግና ከኢዜአ ወይም ከዋልታ በመጡ<br />
ሌሎች ዜናዎች መተካት እንደነበር አስፍርውታል፡፡<br />
ሌላው የአቶ ሰለሞን ጥናት የደረሰበት ድምዳሜ<br />
እንደሚያሳየው ለአንድ ወር ገደማ የሰበሰባቸውና<br />
የተነተናቸው የኢትዮጵያ ሬዲዮ ዜናዎች<br />
በማጠቃለያቸው ውስጥ እንዳስቀመጡት የተቃዋሚ<br />
የፖለቲካ ፓርቲዎችን በተመለከተ የተሰሩት ዜናዎች<br />
በሙሉ አሉታዊና ሚዛናዊ ያልሆኑ ሲሆኑ ገዢውን<br />
ፓርቲ የተመለከቱት ደግሞ አዎንታዊ ነበሩ፡፡<br />
በመሆኑም አቶ ሰለሞን ሲደመድሙም የተጠቀሰው<br />
ግኝት የሚያደርሰን መደምደሚያ ገዢው ፓርቲ<br />
በቁጥጥሩ ሥር ያሉትን የመንግሥት መገናኛ<br />
ብዙሃንን ፣ሕገ-መንግሥቱን፣ ሌሎች ድንጋጌዎችንና<br />
የዴሞክራሲን መሠረታዊ መርህ በሚጥስ መልክ<br />
እየተጠቀመበት መሆኑን ነው፡፡ መሠረታዊ መርህ<br />
ብለው የጠቀሱትም የተለያዩ ሃሳቦችን ማስተናገድ<br />
(plurality of opinion) መሆኑን ነው፡፡<br />
አቶ ሰለሞን ኃይለማርያም የጥናታቸው ግኝትን<br />
መሠረት በማድረግ የመፍትሄ ሃሳቦችን በመጠቆም<br />
ጥናታቸውን አጠናቀዋል፡፡ ካስቀመጧቸው<br />
የመፍትሄ ሃሳቦችም መካከልም የህገ-መንግሥቱን<br />
አንቀፅ 29(2) መንፈስ የያዘ አዲስ ህግ በፓርላማው<br />
ማውጣት የመንግሥት መገናኛ ብዙሃንን<br />
ወደ Public service Broadcasting ማዞር ፤<br />
የመንግስት መገናኛ ብዙሃን የቦርድ አባላትን ግልፅ<br />
በሆነ መንገድ መሾም፤የመንግሥትን ጣልቃ ገብነት<br />
በህግ መገደብ፤ሚዲያውን ለህዝብ ክፍት ማድረግና<br />
ሙያዊ ጣልቃ ገብነትን ማስወገድ ጋዜጠኞቹ ሙያዊ<br />
ነፃነት እንዲኖራቸው ማድረግ የሚሉ አሉበት፡፡<br />
ኢሕአዴግ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የግንባሩን<br />
አቋም በሚያንፀባርቁት ይፋዊ ህትመቶቹ ውስጥ<br />
በግልፅ እንዳስቀመጠው፣ መገናኛ ብዙሃን<br />
ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ሊያበረክቱት<br />
የሚችሉትን ሚና ከፍተኛ መሆኑን እውቅና<br />
ይሰጣሉ፡፡ ይህ እውቅና ግን “ለማጥፋትም” ትልቅ<br />
አቅም እንዳላቸው ከመግለፅም ባለፈ መልኩ<br />
መንግሥት ሊቆጣጠራቸው እንደሚገባ አፅንኦት<br />
ይሰጣል፡፡ ለዚህም መከራከሪያው በተደጋጋሚ<br />
የሚያነሳው ምሳሌም በምርጫ 97 ወቅት “ነፃው<br />
ፕሬስ” ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር “በመወገን”<br />
በመንግስት፣ በሕዝብና በአገር አንድነትና ፀጥታ ላይ<br />
ሊያደርሱት የነበሩትን “አደጋዎችን” ነው፡፡ ለዚህም<br />
ምክንያቱን ሲገልፅ “የዴሞክራሲያችን ታዳጊነትና<br />
ውስንነት” መሆኑን ይገልፃል፡፡ ይፋዊ ህትመቶቹም<br />
መፍትሄ ብለው የሚሰነዝሩት፣ አሁን በአገራችን<br />
የሌለው የነቃ ሊብራል መካከለኛ መደብ የመገናኛ<br />
ብዙሃን አካሄድን መስመር ማስያዝ የሚችለው<br />
እስኪፈጠር ድረስ በአንድ በኩል የመንግሥት<br />
ቁጥጥር ተገቢ መሆኑን ያሰምርበታል፡፡ በሌላ በኩል<br />
“ታዳጊ ዴሞክራሲያችን” እንዲጐለብት መንግሥት<br />
2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />
የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታው ሂደት ላይ<br />
ርብርብ ማድረግ ለመቀጠል ቁርጠኛ መሆኑን<br />
ይገልፃል፡፡<br />
ሸክሙ የማነው ?<br />
ምርጫ 97 ውጤትን ተከትሎ በኢሕአዴግና<br />
በቅንጅት መካከል ተፈጥሮ በነበረው ውዝግብ<br />
እንደታየው፣ ሁለቱም ፓርቲዎች የተለያዩ የመገናኛ<br />
ብዙሃንን በመጠቀም ከህዝብ ጋር ይገናኙ እንደነበር<br />
ይታወሳል፡፡ ሂዩማን ራይትስ ዎች አውጥቶት<br />
የነበረው አንድ ዘገባ እንደሚያሳየው፤ በምርጫ 97<br />
ሰሞን በኢትዮጵያ ታይቶ የነበረው የነፃው ፕሬስ<br />
በነፃነት ያሰራውን ከባቢ መፈጠሩ በኢትዮጵያ ታሪክ<br />
ተከስቶ እንደማያውቅ ነው፡፡ ይኸው ተመሳሳይ ዘገባ<br />
እንደሚያትተው ከድህረ-ምርጫ 97 በመንግሥት<br />
የተወሰዱ እንደ ጋዜጠኞችን ማሰርና ብዙም<br />
የማያላውስ አዲስ የሚዲያ ሕግ ማውጣት ፕሬሱን<br />
መቀመቅ እንደከተተው ይደመድማል፡፡<br />
ፖለቲካ ፓርቲዎች ውጤት ለማምጣት የመገናኛ<br />
ብዙሃንን እድሎችን አሟጦ መጠቀም፣ ከየፓርቲዎቹ<br />
የቀን ተቀን ስራ እኩል (ምናልባትም የበለጠ?)<br />
ትኩረት እንደሚያስፈልገው ከኢሕአዴግና<br />
ከቀድሞው ቅንጅት በስተቀር በደንብ የተረዳው<br />
ያለ አይመስልም፡፡ የቀድሞው ቅንጅት ምክር ቤት<br />
ለመግባት ወይም ላለመግባት ረጅምና ተከታታይ<br />
ስብሰባዎች አድርጐ፣ በመጨረሻ ላይ የደረሰበት<br />
ውሳኔ የማመቻቸት (Compromise) ነበር፡<br />
፡ ፓርቲው ምርጫ 97 ነፃና ፍትሃዊ ያልነበረ<br />
መሆኑን ቢያምን፣ ለኢሕአዴግ “ስምንት ነጥቦችን”<br />
አቅርቦ ገዢው ፓርቲ ከተቀበለው ምክር ቤት<br />
ሊገባ እንደሚችል መግለጹ ይታወሳል፡፡ ከስምንቱ<br />
ጥያቄዎች ውስጥም የመንግሥት መገናኛ ብዙሃን<br />
ከገዢው ፓርቲ ቁጥጥር ተላቀው፣ ራሳቸውን ችለው<br />
ነፃ ሆነው እንዲቋቋሙ የሚጠይቀው አንዱ ነው፡፡<br />
በሌላ በኩል ኢሕአዴግ በመንግሥት ቁጥጥር<br />
ሥር ያሉትን መገናኛ ብዙሃንን ለሚቃሙ ወገኖች<br />
ለማጋራት ፍቃደኛ አይመስልም፡፡ ይህ ብቻ<br />
አይደለም፡፡ ለተቃዋሚ ፓርቲዎች “በራቸው<br />
ክፍት ነው” ተብለው የሚገመቱ የመገናኛ ብዙሃንን<br />
ከማዳከምም የሚመለስ አይመስልም፡፡ ነፃውን<br />
ፕሬስ ጠንከር ባለ አዋጅ፤ ኢሳትን፣ የአሜሪካንና<br />
የጀርመን ድምፅን በማፈን ይህንን አቁዋሙን<br />
አሳይቱአል፡፡<br />
በምርጫ 2002 ሰሞን እንዳስተዋልነው፤ የአሜሪካን<br />
ድምፅ ሬዲዮን ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳይሰማ<br />
ለማድረግ መንግሥታቸው እንደሚያፍነው<br />
ጠቅላይ ሚንስትር መለስ በግልፅ መናገራቸው<br />
አንድ ማሳያ ተደርጐ ሊወሰድ ይችላል፡፡ በእርግጥ<br />
ኢሳት (ESAT) የተባለውን ከኢትዮጵያ ውጭ<br />
የሚሰራጨውን የሳተላይት ቴሌቪዥንን ኢትዮጵያ<br />
ውስጥ እንዳይደርስ የተደረገው የመንግሥታቸው<br />
እጅ ስለገባበት እንደሆነ ተጠይቀው፤ በጉዳዩ ላይ<br />
አስተያየት መስጠት እንደማይፈልጉ በመግለጽ ፣<br />
ጥያቄውን አለመመለሳቸው ይታወቃል፡፡ የዚህ<br />
ዓይነት መልስ ግን የቴሌቪዥን ፕሮግራሞቻቸው<br />
ኢትዮጵያ ውስጥ ሊታዩ ያልቻሉት ኢሕአዴግ<br />
ስርጭታቸው ላይ እየፈጠረ ባለው ማስተጓጐል<br />
ምክንያት መሆኑን ለሚከሱት የኢሳት ጣቢያ<br />
ኃላፊዎች፣ በቂ መልስ መስጠት የቻለ አይመስልም፡<br />
፡አሁንም ክሳቸውን ቀጥለዋልና ፡፡<br />
አጠቃላዩ የአገራችን የመገናኛ ብዙሃን ነባራዊ<br />
እውነታ፣ በፍፁማዊ የበላይነት በሚያስብል<br />
ደረጃ ኢሕአዴግ ለብቻው ተቆጣጥሮት ባለበት<br />
ሁኔታ ሌሎች ድምፆች የመስተናገዳቸው ዕድል<br />
በጣም ጠባብ ይመስላል፡፡ መድረክ ወደ “ግንባር”<br />
መሸጋገሩን ለማብሰር መድረክ ላይ የወጡት ዶ/ር<br />
መረራም፣ ኢቲቪ አንድና ሁለት ሰልችተውት ኢቲቪ<br />
ሦስትን ሲፈልግ የሚውለው ሸምሱም፣ ኢሳትን<br />
ለመከታተል ያልቻለውና ኢቲቪን ሸሽቶ ማምለጥ<br />
ያቃተው ሰለሞንም የልባቸው በቅርቡ የሚደርስ<br />
አይመስልም፡፡ የምርጫ 97 ውጤት የሆነው<br />
የሸገር ኤፍ.ኤም ሬዲዮ አይነት የቴሌቪዥን ጣቢያ<br />
እንዲመጣ መመኘታቸው አልቀረም፡፡ ምኞታቸው<br />
መቼ እውን እንደሚሆን ግን መገመት እንኳን<br />
አልቻሉም፡፡
2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />
መግለጫ ተያት<br />
ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />
ትግሉ መራራ ቢሆንም በፅናት ለድል እንበቃለን!<br />
ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ<br />
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ የተነሳለትን ዓላማ<br />
ለማሳካት የአምባገነኖችን አፈና እየተቋቋመ አባላቱ የህይወትና የንብረት መስዋዕትነት እየከፈሉ<br />
እስከዛሬ ቀን ደርሰዋል፡፡ ዛሬም ገዢው ፓርቲ በአዋጅ በመደገፍ በአካሄደው መንግስታዊ<br />
የጥቃት ዘመቻ ከፍተኛ የፓርቲው አመራሮች፡- (1ኛ) ምክትል ሊቀመንበርና የሕዝብ ግንኙነት<br />
አላፊ አቶ አንዱዓለም አራጌ፣ (2ኛ) የብሔራዊ ምክር ቤት አባል አቶ ናትናኤል መኮንን፣ (3ኛ)<br />
የብሔራዊ ምክር ቤት አባል አቶ ብርሃኑ አሳምነው የማያባራው የግፍ ጥቃት ሰለባ ሆነዋል፡፡<br />
በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስተር መለስ ዜናዊ ባደረጉት ንግግር በተቃዋሚው ጎራ በተለይ<br />
በአንድነት ፓርቲ ላይ የሚደረገው አፈና ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡ ከጥቃት ዘመቻው<br />
በተጨማሪም የፍርድ ቤቱን በትር በህግ ሽፋን እንደሚጠቀሙ በአደባባይ ያለምንም ይሉኝታ<br />
አረጋግጠውልናል፡፡ መንግስት አንድነትን በህግ ሽፋን ስም በጉልበት ለማዳከም መዘጋጀቱን<br />
ያለጥርጥር አረጋግጠውልናል፡፡<br />
ይህ አደገኛ መንግስታዊ ሽብር በፓርቲያችን ላይ እየተፈፀመ ባለበት በአሁኑ ወቅት<br />
የፓርቲያችን ከፍተኛ የስልጣን አካል የሆነው ብሔራዊ ምክር ቤታችን ከጥቅምት 25-<br />
26/2004 ዓ.ም. የአንደኛውን ዙር የመጨረሻ የሥራ ዘመኑን ስብሰባ በታላቅ ቁጭትና ወኔ<br />
ታጅቦ ጉባኤውን አከናውንዋል፡፡<br />
ጉባኤው መንግስት ሕገ-መንግቱን በመጣስ በአባሎቻችን ላይ እየፈፀመ ያለውን የእብሪት<br />
እርምጃ አውግዝዋል፡፡ እንዲሉ በሽብርተኝነት ስም በግፍ<br />
አፍኖ ከማንም ጋር እንዳይገናኙ ሸብቦ ያስራቸው አባሎቶቻችን በአስቸካይ እንዲፈቱ ምክር<br />
ቤቱ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡<br />
ምክር ቤቱ በቀረበለት አጀንዳ ላይ ለሁለት ቀናት ሰፊና ጥልቀት ያለው ውይይት በማድረግ<br />
የኢትዮጵያ ሕዝብ ለነጻነትና ለዴሞክራሲ የሚያደረገውን ሰላማዊ ትግል ወደ ፊት ለማራመድ<br />
የሚያስችሉ ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን አስተላፏል፡፡ በተለይም የፓርቲውን የ2003 ዓ.ም. የሥራ<br />
አፈፃፀምን በተመለከተ ሰፊ ሪፖርት ቀርቦ ደካማና ጠንካራ ጎኖች ተገምግመዋል፡፡<br />
ምክር ቤቱ ከአምስት ወር በፊት ያቋቋመው የጠቅላላ ጉባኤ ጠሪ ኮሚቴ ከአንድ<br />
ወር በኋላ የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ተጠርቶ የስራ ዘመኑን የጨረሰውን ይህን ምክር ቤት<br />
በክብር ያሰናብተዋል፡፡ የሁለተኛው ዙር አዲስ ምክር ቤት በጠቅላላ ጉባኤው በሚደረግ ነፃና<br />
ዴሞክራሳያዊ ምርጫ አዲስ ብሔራዊ ምክር ቤት በመምረጥና የስልጣን ርክክብ ለማድረግ<br />
አንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ም/ቤት መደበኛ ስብሰባውን አካሄደ<br />
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ /አንድነት/<br />
ብሔራዊ ም/ቤት የመጀመሪያ ዙር የመጨረሻውን የሥራ<br />
ዘመን ጥቅምት 25 እና 26 ቀን 2004 ዓ.ም በጽ/ቤቱ<br />
አዳራሽ መደበኛ ስብሰባውን አካሄደ፡፡<br />
በስብሰባውም በዋነኛነት አራት አጀንዳዎች<br />
ለውይይት የቀረቡ ሲሆን እነኝህም 1ኛ የብሔራዊ ሥራ<br />
አስፈፃሚ ኮሚቴ የሥራ ሪፖርት ማዳመጥ 2ኛ የጠቅላላ<br />
ጉባዔ ጠሪ ኮሚቴ የሥራ ሪፖርት ማዳመጥ 3ኛ የአምስት<br />
ዓመት እቅድና ስትራቴጂ መሠረት በማድረግ የ2004<br />
ዓ.ም በጀት ዕቅድን ማጽደቅ እና 4ኛ ያለፉትን ስብሰባዎች<br />
ቃለ ጉባዔ ማፅደቅ በሚሉ አጀንዳዎች ዙሪያ ነበር፡፡<br />
ብሔራዊ ምክር ቤቱ በአጀንዳዎቹ ላይ<br />
ሰፊ ውይይት በማድረግ አጀንዳዎችን ያፀደቀ ሲሆን<br />
በተለይም በብሔራዊ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የሥራ<br />
ሪፖርት በፓርቲው ሊቀመንበር በዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ<br />
ቀርቧል፡፡<br />
በሪፖርቱ ላይ በእቅዱ መሠረት የተሰሩና<br />
ያልተሰሩ ሥራዎችን መለየት ተችሏል ሲሉ አባላቱ<br />
ገልፀዋል፡፡ በእቅዱ መሠረት ከተሰሩት ውስጥ የፓርቲው<br />
ልሳን “ፍኖተ ነፃነት” ጋዜጣ በየሳምንቱ አሳትሞ<br />
የፓርቲውን እንቅስቃሴ ወቅታዊ የሆኑ ሀገር አቀፍና ዓለም<br />
አቀፍ መረጃዎችን ለሕዝቡ ማድረስ፣በሀገራዊ ወቅታዊ<br />
ጉዳይ ላይ የተለያዩ ምሁራንን ከውጭና ከሀገር ውስጥ<br />
በመጋበዝ ውይይት ማድረግ፣የፓርቲው መመሪያና ደንብ<br />
በሚፈቅደው መሠረት ከመድረክ አቻ ፓርቲዎች ጋር<br />
ሰፊና ጥልቅ ውይይት በማድረግ መድረክን ከቅንጅት<br />
ወደ ግንባር የማሸጋገር ሂደት፣ከብርሃን ለአንድነትና<br />
ለዴሞክራሲ ፓርቲ ጋር ውህደት የመፍጠር ሂደት<br />
ከተሳኩ ተግባራቶች መካከል ጥቂቶቹ ናቸው ተብሏል፡፡<br />
ሌላው ፓርቲው መዋቅሩን በመላው<br />
ሀገሪቱ የማስፋፋትና አሰራሩንም እስከ ወረዳ ድረስ<br />
በመዘርጋት የፓርቲው አባላት በአቅራቢያቸው<br />
እንዲደራጁ ተደርጓል፡፡ ይሁን እንጂ ይህንና ሌላሎች<br />
እቅዶች ሙሉ በሙሉ ተፈፃሚ እንዳይሆኑ የተለያዩ<br />
እንቅፋቶች ተፈጥረው ነበር፡፡ ከችግሮቹም መካከል<br />
ኢህአዴግ የፖለቲካ ምህዳሩን ማጥበብ፣የፓርቲ አባላትን<br />
ማስፈራራት፣ማሰርና መግደል ዋነኞቹ ችግሮች እንደሆኑ<br />
በም/ቤቱ ተጠቁሟል፡፡<br />
በተጨማሪም ፓርቲው በሰው<br />
ኃይል፣በአቅምና በገንዘብ ማነስ ምክንያት በእቅዱ መሠረት<br />
የሚጠበቅበትን አልሰራም ሲሉ ያለፈው ዓመት ስራ<br />
አፈፃፀም ሪፖርትን ም/ቤቱ ገምግሟል ሲል የፓርቲው<br />
ጽ/ቤት ገልጿል፡፡<br />
ለእቅዱ መሳካት ሌሎች ችግሮችም<br />
ተነስተዋል፡፡ እንደ ችግር ከተነሱት መካከል በቂ የገንዘብ<br />
የታሰበውን ያህል ያለማግኘት፣በቂ የሰው ኃይል ያለመኖር<br />
ተጠቅሰዋል፡፡<br />
ከላይ የተጠቀሱትን ችግሮችን ለመቅረፍ<br />
በ2004 ዓ.ም የተለያዩ የመፍትሄ አቅጣጫዎች የተነሱ<br />
ሲሆን ከነዚህም መካከል በዕውቀትና በቁርጠኝነት<br />
ላይ የተመሰረተ የሰው ኃይል ወደ ፓርቲው እንዲመጣ<br />
መጋበዝ፣ደጋፊዎች ከእውቀትና ከጉልበት በተጨማሪ<br />
በገንዘብም ድጋፍ ማድረግ እንዲችሉ ሕጋዊ የሆኑ<br />
የተለያዩ ስልቶችን መቀየስና ለሕዝቡ ይፋ ማድረግ፣<br />
የሚመጣውም አዲሱ ም/ቤት አባላት በዕውቀትና<br />
በቁርጠኝነት ላይ መሠረት ማድረግ እንዳለበትም ም/ቤቱ<br />
ጠቁሟል፡፡<br />
አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ<br />
አካባቢ ያሉ ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙ የፓርቲው<br />
አባላትንና ሌሎች የፖለቲካና የሕሊና እስረኞችን ጉዳይ<br />
የሚከታተል ልዩ ግብረ ኃይል እንደተቋቋመና ሥራውን<br />
እያከናወነ እንዳለም በሪፖርቱ ገልጿል፡፡<br />
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከ13 ቀናት በፊት<br />
የፓርቲው አባል አቶ ገዛኸኝ ምትኩ በሽብር ተጠርጥሮ<br />
ከሚኖርበት ቂርቆስ ክ/ከተማ በመውሰድ ማዕከላዊ እስር<br />
ቤት እንደሚገኝ ተጠቁሟል፡፡ ባለፈው መስከረም 4 ቀን<br />
2004 ዓ.ም ተጠርጥረው ከታሰሩት መካከል የአንድነት<br />
ፓርቲ ም/ሊቀመንበርና የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ<br />
አንዱዓለም አራጌ ታመው ሆስፒታል ሄደው የሕክምና<br />
እርዳታ እንደተደረገላቸው በሪፖርቱ ላይ የፓርቲው<br />
ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ገልፀዋል፡፡<br />
በስብሰባው ላይ በቀረቡት አጀንዳዎች ዙሪያ ሰፊ<br />
ውይይት ካደረገ በኋላ በአባላቱ ፀድቆ የመጨረሻው<br />
የሥራ ዘመን ጥቅምት 26 ቀን 2004 ዓ.ም ተጠናቋል<br />
ሲል የአንድት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ /አንድነት/<br />
ብሔራዊ ም/ቤት በተለይም ለዝግጅት ክፍላችን ገልጿል፡<br />
፡ይህ በእንዲህ እንዳለ የጉበኤ ጠሪ ኮሚቴ የተሻሻለ<br />
ፕሮግራምና ደንብ ለምክር ቤቱ አቅርቧል፡፡ በአንድነት<br />
15<br />
ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ለምክር ቤቱ አብስሮዋል፡፡ ብሔራዊ ምክር ቤቱ የአንድነት ጠቅላላ<br />
ጉባኤ ህዳር 30 እና ታህሳስ 1/2004 እንዲካሄድ ወስኗል፡፡<br />
ይህንን ተከትሎ ለጠቅላላ ጉባኤ ቀርበው የሚፀድቁትን ልዩ ልዩ የፓርቲው የመታገያ<br />
ሠነዶች ለምክር ቤቱ ቀርበው ከተመረመሩ በኋላ ጠቅላላ ጉባኤው መርምሮ እንዲያፀድቃቸው<br />
ወስኗል፡፡ የፓርቲያችን አዲሱ ሊቀመንበር ከሁሉም አባላት በውድድር በዕጩነት ቀርበው<br />
በጠቅላላ ጉባኤው ፊት አባላት ቀጥተኛ የድምፅ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት እንዲመረጡ<br />
ወስኗዋል፡፡<br />
አንድነት በአለፉት ሦስት ዓመታት ከአጋጠሙት መሰናክሎች ትምህርት ወስዶ የራሱን<br />
የትግል ስትራቴጂና የአምስት አመት እቅድ ነድፎ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ የተቀየሰውን<br />
ስትራቴጂ ለመተግበር የሚያስችል አቅም ለመፍጠር ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ነው፡፡<br />
በአዲሱ ዓመት ዜጎች ያለፍርሃት፣ ሳይሸማቀቁ በነፃነት የሚኖሩባት፣ በግል ጥረታቸው<br />
ያፈሩትን ሃብትና ንብረት በግፍ የማይነጠቁባት፤ የዴሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብቶች<br />
የተከበረባት ኢትዮጵያን ለመፍጠር በሚደረገው ትግል ኢትዮጵያዊያን ሁሉ እጅ ለእጅ<br />
ተያይዘን በፅናት እንድንታገል ብሔራዊ ምክር ቤታችን ጥሪውን ያቀርባል፡፡<br />
መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሕገወጦችን አውግዞና፣ ጊዜው የለውጥ መሆኑን ተገንዝቦ<br />
ፓርቲያችን የሰነቀውን ሀገራዊ ራዕይ ደግፎ በዕውቀት ላይ የተመሠረተና የሰለጠነ የመቻቻል<br />
የፖለቲካ መርሆችን ተከትሎ ለነፃነቱ የበኩሉን አስተዋፅኦ እንዲያበረክት የአንድነት ፓርቲ<br />
ብሔራዊ ምክር ቤት ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡<br />
የፖለቲካና የህሊና እስረኞች በአስቸኳያ ይፈቱ!!<br />
ሠላማዊ ትግል ያሸንፋል!!<br />
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት<br />
ጥቅምት 26/2004 ዓ.ም.<br />
አዲስ አበባ<br />
የስብሰባው ተካፋዮች በከፊል<br />
ፕሮግራም ውስጥ እንዲካተቱ ከተደረጉ ጉዳዮች<br />
መካከል አሸባሪነትን በተመለከተና የመሬት ወረራ<br />
ጉዳይን ያካትታል፡፡ ምክር ቤቱ የፓርቲው ፕሮግራም<br />
ውስጥ እንደ አዲስ የተካተቱትን ጉዳዮች በጥልቀት<br />
ተወያይቶበቷል ሲል ምክር ቤቱ ጠቁሟል፡፡<br />
የተሻሻለው የፓርቲው ህገ-ደንብ እንደሚያስረዳው<br />
የፓርቲው ሊቀመንበር በጠቅላላ ጉባኤ የሚመረጥ ሲሆን፣<br />
ሊቀመንበሩ ሌሎች የስራ አስፈፃሚ አባላትን መልምሎ<br />
በዕጩነት ለብሔራዊ ምክር ቤት አቅርቦ ያፀድቃል፡<br />
፡ የፓርቲው መሪ መሆን የሚፈልጉና የተቀመጠውን<br />
መስፈርት የሚያሟሉ አባላት የጠቅላላ ጉባኤ አባላትን<br />
ድጋፍ እንዲያደርጉ በመቀስቀስ መወዳደር እንደሚችሉ<br />
ተገልጿል፡፡ በተመሳሳይም የስራ አስፈፃሚ አባለት ቁጥር<br />
ከ18 ወደ 11 እንዲወርድ ተደርጓል፡፡<br />
ብሔራዊ ምክር ቤቱም የፓርቲውን ጠቅላላ ጉባኤ<br />
በህዳር 30 እና ታህሳስ 01 ቀን 2004 ዓ.ም. እንዲካሄድ<br />
መወሰኑን ምክር ቤቱ በተለይም ለዝግጅት ክፍሉ<br />
ገልጿል፡፡<br />
www.andinet.org.et
16<br />
www.andinet.org.et<br />
ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />
E-mail: udjparty@gmail.com<br />
andinet@andinet.org<br />
2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15