ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless
ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless
ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless
You also want an ePaper? Increase the reach of your titles
YUMPU automatically turns print PDFs into web optimized ePapers that Google loves.
2<br />
www.andinet.org.et<br />
የሙስና መስፋፋት<br />
በአንድ አገር ውስጥ በጥቅም ላይ<br />
ሊውል የሚገባውን መዋዕለ-ንዋይ<br />
(Investment) ይሸረሽረዋል። የውጭ<br />
አገር ከበርቴዎችንም ቢሆን በዚያ አገር<br />
የመዋዕለ-ንዋይ (Foreign Investment)<br />
ተግባር እንዳይሳተፉ ተጽዕኖ ያሳድራል።<br />
በዚህ ጉዳይ ላይ ብዙ ጥናቶች ያደረጉ<br />
ተመራማሪዎች ሲገልጹ “አንዳንድ<br />
ባለሃብቶች ወደ አንዳንድ አገሮች፤<br />
በተለይም ወደ አፍሪካ አገሮች ውስጥ<br />
ከሚያስገቡት የውጭ ምንዛሬና መዋዕለ-<br />
ንዋይ ይልቅ ከነዚህ አገሮች ወደ ሀብታም<br />
አገሮች በስርቆት መልክ የሚወጣው<br />
የውጭ ምንዛሬ ይበልጣል” ይላሉ።<br />
(ለምሳሌ በቅርቡ የአለም ባንክ ያወጣው<br />
ጥናታዊ ጽሁፍ ከኢትዮጵያ ተመዝብሮ<br />
ወደ ውጭ ሀገር እንዲሸሽ የተደረገው<br />
ሀብት/ገንዘብ እስከ 11 ቢሊዮን ዶላር<br />
እንደሚደርስ አሳይቷል። የተባበሩት<br />
መንግሥታትም እንደጎርጎረሳውያን<br />
አቆጣጠር ከ1990 ዓ/ም ጀምሮ<br />
ከኢትዮጵያ ወደ ውጭ ሀገሮች ተዘርፎ<br />
የጎረፈው ሀብት ከ8.3 ቢሊልዮን ዶላር<br />
እንደማያንስ አሳይቷል።) አንዳንድ<br />
አበዳሪዎችም በተመሳሳይ ሁኔታ “ያገር<br />
መሪዎች የሃገራቸውን ሃብት ወደውጭ<br />
የሚያሸሹ ከሆነ እኛ ምን ቸግሮን ነው<br />
ወደነዚህ አገሮች መዋዕለ-ንዋያችንን<br />
የምናስገባው?” የሚል ጥያቄ ያነሳሉ።<br />
ለአብነት ለመጥቀስ ያህል በ1997<br />
ዓ/ም በኢትዮጵያ የተካሄደው ምርጫ<br />
በህወሓት/ኢሕአዴግ ከከሸፈ በኋላ<br />
ከኢትዮጵያ ወደ እንግሊዝ አገር የጎረፉት<br />
ሃብቶች በጣም በዝተው እንደነበር<br />
አንዳንድ የእንግሊዝ የዜና ማሰራጫዎች<br />
አጋልጠዋል። በዚያው ሰሞን ሰሚ ያጡ<br />
አቤቱታዎች ከተለያዩ አቅጣጫዎች<br />
መነሳታቸው አልቀረም። ለምሳሌ እ.ኤ.አ.<br />
በ1997 World Development Report<br />
በተባለው መጽሄት ታትሞ የወጣው<br />
ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />
ጥናት ሲያመለክት እንደ ኢትዮጵያ<br />
በሙስና የተዘፈቁትና ሙስና ያላጠቃቸው<br />
አገሮች ሲወዳደሩ ሙስና ያጠቃቸው<br />
አገሮች በእድገት ወደ ኋላ መቅረታቸውን<br />
ዘግቧል፡፡ እንዲሁም በዚሁ አመት<br />
(National Bureau of Economic<br />
Research) ተብሎ በሚጠራው ጥናታዊ<br />
መጽሄት ያወጣው ጥናት እንደዘገበው<br />
ይህ ሁኔታ በሩቅ ምስራቅ የእስያ አገሮች<br />
እንደተከሰተ ዘግቧል።<br />
ሙስና እንደ ተጨማሪ<br />
ታክስም ስለሆነ የግል ተቋሞችና<br />
ኩባንያዎች እንዳያድጉ ያደርጋል።ሙስና<br />
በግል ተቋማትና በግለሰቦች መካከል<br />
መኖር የሚገባውን ጠቃሚ ውድድር<br />
ይቀንሳል፤ያጫጫል።<br />
ሙስና በጣት የሚቆጠሩ<br />
ሰዎች ብቻ ካለመጠን እንዲከብሩ<br />
ያደርግና በሃብታምና በድሆች መካከል<br />
ልዩነቶችና ቅራኔዎች ያስነሳል። ቅራኔው<br />
ሲገፋም ሀብታሞች ሕጋዊ ባልሆነ መልክ<br />
ያካበቷቸውን ሃብቶች ወደ ሌላ አገር<br />
እንዲያሸሹ ይገፋፋል። ይኸው ድርጊት<br />
በበኩሉ አገር ያራቁታል። ለምሳሌ የዛዬሩ/<br />
የኮንጎው ሞቡቱ ሴሴኮና የፊሊፒኑ<br />
ፈርድናንድ ማርቆስ በሥልጣን ላይ<br />
በነበሩበት ወቅት ያካበቷቸውና በውጭ<br />
አገር ባንኮች ያስቀመጧቸው ንብረቶች<br />
በብዙ ቢሊዮን ዶላር ይቆጠሩ ስለነበር<br />
ዛዬርም/ኮንጎም ሆነች ፊሊፒንስ ለብዙ<br />
ዓመታት የተከማቸባቸውን የውጭ<br />
ብድር በገዛ መሪዎቻቸው የተሰረቀው<br />
ገንዘብ ብድራቸውን ሁሉ ከፍሎ ከዕዳ ነጻ<br />
ሊያደርጋቸው እንደሚችል ተዘግቧል።<br />
ሙስና በአንዲት አገር ውስጥ<br />
የሚገኝን ሕጋዊና ትክክለኛ የንግድ ተግባር<br />
ያዛባል። የፍጆታ ዕቃዎች ትክክለኛ<br />
ዋጋ በተስተካከለ መልክ እንዳይተመን<br />
ያደርጋል። የሸቀጥ እቃዎች እንዲያንሱ<br />
ወይም እንዲጠፉ፤ ብሎም በጓዳ በር<br />
እንዲሸጡ መንገድ ይከፍታል። ዋጋቸው<br />
እንዲንር ያደርጋል፤ ቀስ በቀስም የፍጆታ<br />
ዕቃዎች ዋጋ በጣም ከፍ ይልና ህዝብን<br />
ያስቆጣል። በመንግስትና በነጋዴዎች<br />
መካከል አስፈላጊ ያልሆነ ጠብ እንዲፈጠር<br />
ያደርጋል። ባገራችንም ሆነ በሌሎች<br />
አገሮች እንደተከሰተው፤ መንግስት ነኝ ባዩ<br />
የራሱ መመሪያና ተግባር በፈጠረው ችግር<br />
ነጋዴዎች እንዲከሰሱና እንዲቀጡም<br />
ያደርጋል። በዚህ ምክንያት እንግልት፣<br />
እስርና ግድያ ሊከተል ይችላል። የፍጆታ<br />
ዕቃዎች ዋጋዎች ከፍ ሲሉ የፍጆታ<br />
ዕቃዎቹን ሊያገኙ የሚችሉ ሃብታሞችና<br />
ከነሱ ጋር ግንኙነት ያላቸው እንዲሁም<br />
ከሻጮች ጋር ዝምድና ያላቸው ብቻ<br />
ናቸው። ለዘመድና ለጓደኛ ብቻ መሸጥ<br />
ይመጣል። ሻጮች ዋጋ ከፍ አድርገው<br />
ለዘመዶቻቸውና ለጓደኞቻቸው ብቻ<br />
የመሸጣቸው ምክንያትም ለመንግስት<br />
አያጋልጡንም በሚል አስተሳሰብ<br />
ነው። ተራው ዜጋ በተለይም ድሀው<br />
የሕብረተሰብ ክፍል ግን ቁሳቁሶቹን<br />
እንዳያገኝ የገንዘብ አቅሙ የማይፈቅድለት<br />
በመሆኑ እንዲሁም ከሀብታሙም ሆነ<br />
ከሻጩ የሕብረተሰብ ከፍል ጋር የጠበቀ<br />
ግንኙነት ስለማይኖረው ሁሌም ተጎጂ<br />
ነው። እኒህን ዓይነት የሙስና ገጽታዎች<br />
በኢትዮጵያችን በጣም የተንሠራፉ<br />
ስለሆኑ ባንዳንድ ሰዎች አገላለጽ “በአገሪቱ<br />
ውስጥ ዛሬ የሚካሄደው ንግድ ከማፍያ<br />
ድርጊት የማይተናነስ ነው” ብለው<br />
እንደነ ሪፖርተር ያሉ ጋዜጦች ጭምር<br />
ያስገነዝባሉ። በማፍያ መልክ የሚሰራው<br />
ወንጀላዊ የንግድ አሠራር ከመብዛቱም<br />
የተነሣ በድብቅ መነገድና የጥቂቶች ብቻ<br />
መጠቃቀም ባህል ይሆናል፤ ኮንትሮባንድ<br />
ይስፋፋል፤ ዝርፊያ ይጧጧፋል፤<br />
ወንበዴዎች ይፈጠራሉ፤ ይባስ ብለውም<br />
ወንበዴዎች የራሣቸውን ኬላ ይፈጥራሉ፤<br />
እንዳሻቸው ይዘርፋሉ። የሚያሳዝነው ግን<br />
እነዚህን የመሰሉ ክስተቶች በአገራችን<br />
በሰፊው እየታዩ መሆናቸው ነው።<br />
ዳሰሳ<br />
2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />
የሙስና መስፋፋት በኢኮኖሚ፤በፖለቲካና በማህበራዊ ኑሮ<br />
ፕሮፌሰር ሰይድ ሐሰን<br />
መሪ ስቴት ዩኒቨርስቲ (አሜሪካ)<br />
ካለፈው የቀጠለ<br />
ዘርፍ የሚያስከትለው ችግር<br />
ሙስና ሰዎች በትጋት ሰርተው<br />
ሃብታቸውን እንዳያዳብሩ፤ ቤታቸውን<br />
እንዳያቀኑና አገራቸውን እንዳይገነቡ፤<br />
ባንፃሩ ግን ባቋራጭ የመክበር<br />
ፍላጎታቸው እንዲያድግ ያደርጋል። ዜጎች<br />
ለምርት ያላቸውን ዝግጁነት ይቀንሳል<br />
(It distorts incentives)። ይህ<br />
የሚሆንበት ምክንያቱ ብዙ ነው። ለምሳሌ<br />
በበርካታ አገሮች ውስጥ እንደታየውና<br />
እንደተከሰተው፤ ከሙስና ጋር የተሳሰሩ<br />
ድርጅቶችና የንግድ ተቋማት በመልካም<br />
መንገድ ሰርቶ መክበር አይችሉም።<br />
ሁሌም በሙስና መክበርን የሚመርጡ<br />
ናቸውና። ይህ ደግሞ ባኳያው በትክክልና<br />
በመልካም መንገድ ሥራቸውንና<br />
ሃብታቸውን ለማቃናት የሚጥሩትን ተስፋ<br />
ያስቆርጣል። ቀስ በቀስም በመልካም<br />
መንገድ የሚያካሂዱትን ሥራቸውን<br />
ለቀው ወደመጥፎ ጎዳና እንዲገፉ<br />
ይገደዳሉ፤ ብሎም እነሱም እንደሌሎቹ<br />
ጥቂት ገፋፊዎች በሙስናው እንዲሳተፉ<br />
ይገፋፋሉ። ይህ የስነ-ልቦና ለውጥ እያደር<br />
ለእንያንዳንዱ ዜጋ ይደርሰውና ቀስ በቀስ<br />
አገርና ዜጎች በሙስና ይጠመዳሉ።<br />
ቀደም ሲል ለመጠቆም<br />
እንደተሞከረው በታዳጊ አገሮች ብዙ<br />
መዋዕለ ንዋይ የለም፤ ይባስ ብሎ ያሉትም<br />
ሲዘረፉ ደግሞ አገሮቹ ለበለጠ ድህነት<br />
ይዳረጋሉ። ያገሮቹ ጥቂት ሃብቶች<br />
ወደተወስኑ ግለሰቦችና ድርጅቶች<br />
ወይም ቡድኖች ሲገቡ ደግሞ ያላግባብ<br />
በከበሩ ቡድኖችና በተራው ዜጋ መካከል<br />
መቃቃር ከመከተሉም በላይ የሀብቱ<br />
ልዩነት ይራራቅና ለግጭትና ለብጥብጥ<br />
ይዳርጋል። ይህ ሲሆን በሙስናና<br />
በብልጣብልጥነት የከበሩት አላግባብ<br />
መክበራቸውን ስለሚያውቁ አንደኛ<br />
ሃብታቸውን ሁለተኛ ራሳቸውንም<br />
ወደ ውጭ ማሸሽ ይከተላል። ይህ<br />
ተግባር በብዙ አገሮች ውስጥ የተከሰተና<br />
በኢትዮጵያችንም እያቆጠቆጠ ያለ አስፈሪ<br />
ክስተት ነው፤ መባባሱም አያጠራጥርም።<br />
በስልጣን የሚባልጉ<br />
ባለስልጣናትና የሙስና ተባባሪዎቻቸው<br />
ሃብት የሚያካብቱት ባቋራጭና በፍጥነት<br />
ስለሆነ፤ በፋሲካ የተዳረች ሁሌም ፋሲካ<br />
ይመስላታል ነውና፤ ሃብት ሁሉ በዚሁ<br />
መልክ የሚገኝና ምንጊዜም ሊተካ የሚችል<br />
አድርገው ስለሚቆጥሩ በፈጠነ መልክ<br />
ሃብታቸውን እንዲያባክኑ ይገፋፋሉ፤<br />
ይታለላሉ። ባጭር ጊዜ ውስጥ ያገር<br />
ሃብት የሚወድምበት አጋጣሚ ተፈጥሮም<br />
ሃገርና ዜጋ ያለረዳት ይቀራሉ።<br />
ብዙውን ጊዜ በሙስና<br />
የተበከሉ ሰዎች በሕገ-ወጥ መልክ<br />
ያካበቱትን ሀብት የሚያውሉት በድሎትና<br />
በቅምጥል (luxury) ዕቃዎች ላይ ነው።<br />
ከሚገዟቸው ቁሳቁሶች መካከልም፤<br />
ውድ የሆኑ መኪኖች፤ ጌጣጌጦች፤<br />
የቤት ማስጌጫዎች፤ መጠጥና ልብሶች<br />
ተጠቃሾች ናቸው። እንደነዚህ ያሉ<br />
እቃዎችም ባንድ በኩል አላቂና ግላዊ<br />
ስለሆኑ ላገር የሚያስገኙት ጥቅም እጅጉን<br />
ውሱን ነው። የቁሳቁሶቹ ዋጋ ከሌሎች<br />
ቁሳቁሶች ጋር ሲወዳደር ከፍ ስለሚልም<br />
የተገዙበት ንዋይ ተቀማጭ ወይም ታሳሪ