24.07.2013 Views

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

SHOW MORE
SHOW LESS

You also want an ePaper? Increase the reach of your titles

YUMPU automatically turns print PDFs into web optimized ePapers that Google loves.

2<br />

www.andinet.org.et<br />

የሙስና መስፋፋት<br />

በአንድ አገር ውስጥ በጥቅም ላይ<br />

ሊውል የሚገባውን መዋዕለ-ንዋይ<br />

(Investment) ይሸረሽረዋል። የውጭ<br />

አገር ከበርቴዎችንም ቢሆን በዚያ አገር<br />

የመዋዕለ-ንዋይ (Foreign Investment)<br />

ተግባር እንዳይሳተፉ ተጽዕኖ ያሳድራል።<br />

በዚህ ጉዳይ ላይ ብዙ ጥናቶች ያደረጉ<br />

ተመራማሪዎች ሲገልጹ “አንዳንድ<br />

ባለሃብቶች ወደ አንዳንድ አገሮች፤<br />

በተለይም ወደ አፍሪካ አገሮች ውስጥ<br />

ከሚያስገቡት የውጭ ምንዛሬና መዋዕለ-<br />

ንዋይ ይልቅ ከነዚህ አገሮች ወደ ሀብታም<br />

አገሮች በስርቆት መልክ የሚወጣው<br />

የውጭ ምንዛሬ ይበልጣል” ይላሉ።<br />

(ለምሳሌ በቅርቡ የአለም ባንክ ያወጣው<br />

ጥናታዊ ጽሁፍ ከኢትዮጵያ ተመዝብሮ<br />

ወደ ውጭ ሀገር እንዲሸሽ የተደረገው<br />

ሀብት/ገንዘብ እስከ 11 ቢሊዮን ዶላር<br />

እንደሚደርስ አሳይቷል። የተባበሩት<br />

መንግሥታትም እንደጎርጎረሳውያን<br />

አቆጣጠር ከ1990 ዓ/ም ጀምሮ<br />

ከኢትዮጵያ ወደ ውጭ ሀገሮች ተዘርፎ<br />

የጎረፈው ሀብት ከ8.3 ቢሊልዮን ዶላር<br />

እንደማያንስ አሳይቷል።) አንዳንድ<br />

አበዳሪዎችም በተመሳሳይ ሁኔታ “ያገር<br />

መሪዎች የሃገራቸውን ሃብት ወደውጭ<br />

የሚያሸሹ ከሆነ እኛ ምን ቸግሮን ነው<br />

ወደነዚህ አገሮች መዋዕለ-ንዋያችንን<br />

የምናስገባው?” የሚል ጥያቄ ያነሳሉ።<br />

ለአብነት ለመጥቀስ ያህል በ1997<br />

ዓ/ም በኢትዮጵያ የተካሄደው ምርጫ<br />

በህወሓት/ኢሕአዴግ ከከሸፈ በኋላ<br />

ከኢትዮጵያ ወደ እንግሊዝ አገር የጎረፉት<br />

ሃብቶች በጣም በዝተው እንደነበር<br />

አንዳንድ የእንግሊዝ የዜና ማሰራጫዎች<br />

አጋልጠዋል። በዚያው ሰሞን ሰሚ ያጡ<br />

አቤቱታዎች ከተለያዩ አቅጣጫዎች<br />

መነሳታቸው አልቀረም። ለምሳሌ እ.ኤ.አ.<br />

በ1997 World Development Report<br />

በተባለው መጽሄት ታትሞ የወጣው<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

ጥናት ሲያመለክት እንደ ኢትዮጵያ<br />

በሙስና የተዘፈቁትና ሙስና ያላጠቃቸው<br />

አገሮች ሲወዳደሩ ሙስና ያጠቃቸው<br />

አገሮች በእድገት ወደ ኋላ መቅረታቸውን<br />

ዘግቧል፡፡ እንዲሁም በዚሁ አመት<br />

(National Bureau of Economic<br />

Research) ተብሎ በሚጠራው ጥናታዊ<br />

መጽሄት ያወጣው ጥናት እንደዘገበው<br />

ይህ ሁኔታ በሩቅ ምስራቅ የእስያ አገሮች<br />

እንደተከሰተ ዘግቧል።<br />

ሙስና እንደ ተጨማሪ<br />

ታክስም ስለሆነ የግል ተቋሞችና<br />

ኩባንያዎች እንዳያድጉ ያደርጋል።ሙስና<br />

በግል ተቋማትና በግለሰቦች መካከል<br />

መኖር የሚገባውን ጠቃሚ ውድድር<br />

ይቀንሳል፤ያጫጫል።<br />

ሙስና በጣት የሚቆጠሩ<br />

ሰዎች ብቻ ካለመጠን እንዲከብሩ<br />

ያደርግና በሃብታምና በድሆች መካከል<br />

ልዩነቶችና ቅራኔዎች ያስነሳል። ቅራኔው<br />

ሲገፋም ሀብታሞች ሕጋዊ ባልሆነ መልክ<br />

ያካበቷቸውን ሃብቶች ወደ ሌላ አገር<br />

እንዲያሸሹ ይገፋፋል። ይኸው ድርጊት<br />

በበኩሉ አገር ያራቁታል። ለምሳሌ የዛዬሩ/<br />

የኮንጎው ሞቡቱ ሴሴኮና የፊሊፒኑ<br />

ፈርድናንድ ማርቆስ በሥልጣን ላይ<br />

በነበሩበት ወቅት ያካበቷቸውና በውጭ<br />

አገር ባንኮች ያስቀመጧቸው ንብረቶች<br />

በብዙ ቢሊዮን ዶላር ይቆጠሩ ስለነበር<br />

ዛዬርም/ኮንጎም ሆነች ፊሊፒንስ ለብዙ<br />

ዓመታት የተከማቸባቸውን የውጭ<br />

ብድር በገዛ መሪዎቻቸው የተሰረቀው<br />

ገንዘብ ብድራቸውን ሁሉ ከፍሎ ከዕዳ ነጻ<br />

ሊያደርጋቸው እንደሚችል ተዘግቧል።<br />

ሙስና በአንዲት አገር ውስጥ<br />

የሚገኝን ሕጋዊና ትክክለኛ የንግድ ተግባር<br />

ያዛባል። የፍጆታ ዕቃዎች ትክክለኛ<br />

ዋጋ በተስተካከለ መልክ እንዳይተመን<br />

ያደርጋል። የሸቀጥ እቃዎች እንዲያንሱ<br />

ወይም እንዲጠፉ፤ ብሎም በጓዳ በር<br />

እንዲሸጡ መንገድ ይከፍታል። ዋጋቸው<br />

እንዲንር ያደርጋል፤ ቀስ በቀስም የፍጆታ<br />

ዕቃዎች ዋጋ በጣም ከፍ ይልና ህዝብን<br />

ያስቆጣል። በመንግስትና በነጋዴዎች<br />

መካከል አስፈላጊ ያልሆነ ጠብ እንዲፈጠር<br />

ያደርጋል። ባገራችንም ሆነ በሌሎች<br />

አገሮች እንደተከሰተው፤ መንግስት ነኝ ባዩ<br />

የራሱ መመሪያና ተግባር በፈጠረው ችግር<br />

ነጋዴዎች እንዲከሰሱና እንዲቀጡም<br />

ያደርጋል። በዚህ ምክንያት እንግልት፣<br />

እስርና ግድያ ሊከተል ይችላል። የፍጆታ<br />

ዕቃዎች ዋጋዎች ከፍ ሲሉ የፍጆታ<br />

ዕቃዎቹን ሊያገኙ የሚችሉ ሃብታሞችና<br />

ከነሱ ጋር ግንኙነት ያላቸው እንዲሁም<br />

ከሻጮች ጋር ዝምድና ያላቸው ብቻ<br />

ናቸው። ለዘመድና ለጓደኛ ብቻ መሸጥ<br />

ይመጣል። ሻጮች ዋጋ ከፍ አድርገው<br />

ለዘመዶቻቸውና ለጓደኞቻቸው ብቻ<br />

የመሸጣቸው ምክንያትም ለመንግስት<br />

አያጋልጡንም በሚል አስተሳሰብ<br />

ነው። ተራው ዜጋ በተለይም ድሀው<br />

የሕብረተሰብ ክፍል ግን ቁሳቁሶቹን<br />

እንዳያገኝ የገንዘብ አቅሙ የማይፈቅድለት<br />

በመሆኑ እንዲሁም ከሀብታሙም ሆነ<br />

ከሻጩ የሕብረተሰብ ከፍል ጋር የጠበቀ<br />

ግንኙነት ስለማይኖረው ሁሌም ተጎጂ<br />

ነው። እኒህን ዓይነት የሙስና ገጽታዎች<br />

በኢትዮጵያችን በጣም የተንሠራፉ<br />

ስለሆኑ ባንዳንድ ሰዎች አገላለጽ “በአገሪቱ<br />

ውስጥ ዛሬ የሚካሄደው ንግድ ከማፍያ<br />

ድርጊት የማይተናነስ ነው” ብለው<br />

እንደነ ሪፖርተር ያሉ ጋዜጦች ጭምር<br />

ያስገነዝባሉ። በማፍያ መልክ የሚሰራው<br />

ወንጀላዊ የንግድ አሠራር ከመብዛቱም<br />

የተነሣ በድብቅ መነገድና የጥቂቶች ብቻ<br />

መጠቃቀም ባህል ይሆናል፤ ኮንትሮባንድ<br />

ይስፋፋል፤ ዝርፊያ ይጧጧፋል፤<br />

ወንበዴዎች ይፈጠራሉ፤ ይባስ ብለውም<br />

ወንበዴዎች የራሣቸውን ኬላ ይፈጥራሉ፤<br />

እንዳሻቸው ይዘርፋሉ። የሚያሳዝነው ግን<br />

እነዚህን የመሰሉ ክስተቶች በአገራችን<br />

በሰፊው እየታዩ መሆናቸው ነው።<br />

ዳሰሳ<br />

2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />

የሙስና መስፋፋት በኢኮኖሚ፤በፖለቲካና በማህበራዊ ኑሮ<br />

ፕሮፌሰር ሰይድ ሐሰን<br />

መሪ ስቴት ዩኒቨርስቲ (አሜሪካ)<br />

ካለፈው የቀጠለ<br />

ዘርፍ የሚያስከትለው ችግር<br />

ሙስና ሰዎች በትጋት ሰርተው<br />

ሃብታቸውን እንዳያዳብሩ፤ ቤታቸውን<br />

እንዳያቀኑና አገራቸውን እንዳይገነቡ፤<br />

ባንፃሩ ግን ባቋራጭ የመክበር<br />

ፍላጎታቸው እንዲያድግ ያደርጋል። ዜጎች<br />

ለምርት ያላቸውን ዝግጁነት ይቀንሳል<br />

(It distorts incentives)። ይህ<br />

የሚሆንበት ምክንያቱ ብዙ ነው። ለምሳሌ<br />

በበርካታ አገሮች ውስጥ እንደታየውና<br />

እንደተከሰተው፤ ከሙስና ጋር የተሳሰሩ<br />

ድርጅቶችና የንግድ ተቋማት በመልካም<br />

መንገድ ሰርቶ መክበር አይችሉም።<br />

ሁሌም በሙስና መክበርን የሚመርጡ<br />

ናቸውና። ይህ ደግሞ ባኳያው በትክክልና<br />

በመልካም መንገድ ሥራቸውንና<br />

ሃብታቸውን ለማቃናት የሚጥሩትን ተስፋ<br />

ያስቆርጣል። ቀስ በቀስም በመልካም<br />

መንገድ የሚያካሂዱትን ሥራቸውን<br />

ለቀው ወደመጥፎ ጎዳና እንዲገፉ<br />

ይገደዳሉ፤ ብሎም እነሱም እንደሌሎቹ<br />

ጥቂት ገፋፊዎች በሙስናው እንዲሳተፉ<br />

ይገፋፋሉ። ይህ የስነ-ልቦና ለውጥ እያደር<br />

ለእንያንዳንዱ ዜጋ ይደርሰውና ቀስ በቀስ<br />

አገርና ዜጎች በሙስና ይጠመዳሉ።<br />

ቀደም ሲል ለመጠቆም<br />

እንደተሞከረው በታዳጊ አገሮች ብዙ<br />

መዋዕለ ንዋይ የለም፤ ይባስ ብሎ ያሉትም<br />

ሲዘረፉ ደግሞ አገሮቹ ለበለጠ ድህነት<br />

ይዳረጋሉ። ያገሮቹ ጥቂት ሃብቶች<br />

ወደተወስኑ ግለሰቦችና ድርጅቶች<br />

ወይም ቡድኖች ሲገቡ ደግሞ ያላግባብ<br />

በከበሩ ቡድኖችና በተራው ዜጋ መካከል<br />

መቃቃር ከመከተሉም በላይ የሀብቱ<br />

ልዩነት ይራራቅና ለግጭትና ለብጥብጥ<br />

ይዳርጋል። ይህ ሲሆን በሙስናና<br />

በብልጣብልጥነት የከበሩት አላግባብ<br />

መክበራቸውን ስለሚያውቁ አንደኛ<br />

ሃብታቸውን ሁለተኛ ራሳቸውንም<br />

ወደ ውጭ ማሸሽ ይከተላል። ይህ<br />

ተግባር በብዙ አገሮች ውስጥ የተከሰተና<br />

በኢትዮጵያችንም እያቆጠቆጠ ያለ አስፈሪ<br />

ክስተት ነው፤ መባባሱም አያጠራጥርም።<br />

በስልጣን የሚባልጉ<br />

ባለስልጣናትና የሙስና ተባባሪዎቻቸው<br />

ሃብት የሚያካብቱት ባቋራጭና በፍጥነት<br />

ስለሆነ፤ በፋሲካ የተዳረች ሁሌም ፋሲካ<br />

ይመስላታል ነውና፤ ሃብት ሁሉ በዚሁ<br />

መልክ የሚገኝና ምንጊዜም ሊተካ የሚችል<br />

አድርገው ስለሚቆጥሩ በፈጠነ መልክ<br />

ሃብታቸውን እንዲያባክኑ ይገፋፋሉ፤<br />

ይታለላሉ። ባጭር ጊዜ ውስጥ ያገር<br />

ሃብት የሚወድምበት አጋጣሚ ተፈጥሮም<br />

ሃገርና ዜጋ ያለረዳት ይቀራሉ።<br />

ብዙውን ጊዜ በሙስና<br />

የተበከሉ ሰዎች በሕገ-ወጥ መልክ<br />

ያካበቱትን ሀብት የሚያውሉት በድሎትና<br />

በቅምጥል (luxury) ዕቃዎች ላይ ነው።<br />

ከሚገዟቸው ቁሳቁሶች መካከልም፤<br />

ውድ የሆኑ መኪኖች፤ ጌጣጌጦች፤<br />

የቤት ማስጌጫዎች፤ መጠጥና ልብሶች<br />

ተጠቃሾች ናቸው። እንደነዚህ ያሉ<br />

እቃዎችም ባንድ በኩል አላቂና ግላዊ<br />

ስለሆኑ ላገር የሚያስገኙት ጥቅም እጅጉን<br />

ውሱን ነው። የቁሳቁሶቹ ዋጋ ከሌሎች<br />

ቁሳቁሶች ጋር ሲወዳደር ከፍ ስለሚልም<br />

የተገዙበት ንዋይ ተቀማጭ ወይም ታሳሪ

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!