24.07.2013 Views

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

SHOW MORE
SHOW LESS

You also want an ePaper? Increase the reach of your titles

YUMPU automatically turns print PDFs into web optimized ePapers that Google loves.

2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />

ከአሸናፊ ደስታ ወንድም አገኘሁ<br />

ወቅታዊ<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

ሕወሓት ከደደቢት በረሀ መርሾ<br />

ማሃል አገር ገብቶ ዙፋን ላይ ከተቀመጠበት ጊዜ<br />

ጀምሮ በኢትዮጽያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ ብዙ<br />

ፍንዳታዎች ፈንድተው በብዙ ሚሊዮን ብር<br />

የሚገመት የኢትዮጵያ ሕዝብ ንብረት ወድሟል፡<br />

፡ በሰው ሕይወት ላይም እንዲሁ ብዙ ጉዳት<br />

ደርሷል፡፡<br />

ምንም እንኳን በዩኒበርሲቲው ላይ<br />

የሳት ቃጠሎ ባይደርስበትም፣ “የአገሩን ሠርዶ<br />

በአገሩ በሬ” በሚለው የአበው አባባል፣ባዕዳን<br />

መምህራንን ተክተው ሲያስተምሩ የነበሩ<br />

አንቱ የተባሉ አያሌ እውቅ ፕሮፌሰሮች ከሥራ<br />

ገበታቸው ተባረዋል፡፡ ይህም በራሱ በወቅቱ<br />

በትጉ መምህራን ሽብርና መቅሰፍት ነበር፡፡ በዚያን<br />

ወቅት በዩኒቨርስቲው ውስጥ የተወሰደው ርምጃ<br />

የመንፈስ ስብራት ዛሬም ድረስ ሊቃና አልቻለም፡፡<br />

ያወቅት በጣም አስጊ እና አደጋ<br />

የበዛበት ወቅት ስለነበር፣በወቅቱ የተባበሩት<br />

መንግሥታት ዋና ጸሐፊ የነበሩት የግብፅ ተወላጅ<br />

ቡትሮስ ቡትሮስ ጋሊን ለጉብኝት ወደ አዲስ አበባ<br />

መምጣት ተቃውሞው ሰላማዊ ሰለፍ በወጡ<br />

ተማሪዎች ላይ የጥይት በረዶ ተርከፍክሮባቸው<br />

ተገድለዋል፡፡ ተማሪዎቹ ሰላማዊ ሰልፍ የወጡበት<br />

ምክንያት ግልጽ ስለሆነ፣ከመናገር ተቆጥበን<br />

አልፈነዋል፡፡<br />

ወደ ተነሳሁበት ዋና ነገር ልመለስና<br />

የመጀመሪያው የአዲስ አበባ ነዋሪ ሕዝብ<br />

በሽብር ያናወጠው፣ማቄን ጨርቄን ሳይል<br />

ቤቱን ሳይዘጋ የሌሊት ልብሱን እንደለበሰ፣ቀበሮ<br />

እንደ ገባበት የበግ መንጋ ወደ እየአቅጣጫው<br />

ያስፈረጠጠው፣ከባድ፣እጅግ በጣም ከባድ ፈንዳታ<br />

ነፋስ ስልክ አካባቢ የፈነዳው ፍንዳታ ነበር፡፡<br />

በዚያ አደጋ በተጋለጠ ስፈራ ላይ ያ<br />

ፈንዳታ እንዲፈነዳ የተደረገው በዐፄ ኃ/ሥላሴ<br />

ዘመነ መንግሥት ተገንብቶ አገልግሎት በመስጠት<br />

ላይ የነበረን የሥንቅና ትጥቅ ዴፖ ለማውደም<br />

ሲሆን አጋጣሚ ሆኖ በዚያ አካባቢ ይኖሩ በነበሩ<br />

ነዋሪዎች ላይም በርካታ ቤቶች ተደርምሰዋል፡፡<br />

በቃጠሎ ወድመዋል፡፡ ይህ ነው የማይባል ንብረት<br />

ወድሟል፡፡ የሰው ሕይወት ሳይጠፋ አንዳልቀረም<br />

ተገምቷል፡፡<br />

ከላይ አንብበን እንደመጣነው<br />

ያ ወቅት በሳልና ጠሬውን ለመለየት ወይንም<br />

ማን ምን እንደሆነ ለይቶ ለማወቅ አስቸጋሪ<br />

የሆነበት ወቅት ስለነበር በፈንዳታው ፍንጣሪዎች<br />

ቤቶቻቸው የተደረመሱባቸው፣የተቃጠሉባቸውና<br />

ንብረቶቻቸው የወደሙባቸው አባወራዎችና<br />

እማወራዎች ዋይታ ሲያሰሙና ሲያነቡ<br />

የሚታዩበት ወቅት ነበር፡፡<br />

ስውር ደባ<br />

እነ አጅሬም ፍንዳታው በደረሰበትና<br />

በፍንዳታው በተደረመሱና በቃጠሎው<br />

በነደዱ ቤቶች ዙሪያ ወይም አካባቢ ቁምጣ<br />

ሱሪዎቻቸውን ታጥቀው፣ነጠላ ጫማዎቻቸውን<br />

ተጫምተው አንዳንዶቹ ፎጣቸውን ከአንገታቸው<br />

ላይ ጠምጥመው አንዳንዶቹ ደግሞ ፎጣቸውን<br />

ከራሳቸው ላይ ጠምጥመውና ጠብመንጃቻቸውን<br />

አንግበው፣የዚያን ከባድ ፍንዳታ ውጤት<br />

ለማየት ይርመሰመስ የነበረውን ሕዝብ “ወደዚያ<br />

ሂድ፣ወደዚህ አትጠጋ፣ወደዚህ አትቅረብ” እያሉ<br />

ይገረምሙ ነበር፡፡<br />

ከዚህበላይ ነግረን እንዳመጣነው፣ያ<br />

በከባድ ፈንዳታ የጋየ የሥንቅና ትጥቅ ዴፖ በዐፄ<br />

ኃ/ሥላሴ ዘመን መንግሥት የተገነባ፣ለሠራዊቱ<br />

ሥንቅ እንዲሆን ተዘጋጅተው የተቀመጡ ልዩ<br />

ልዩ የምግብ ዓይነቶች፣ልዩ ልዩ ጥይቶችና ልዩ ልዩ<br />

የጦር መሣሪያዎች የተከማቹበት<br />

ዴፖ ነበር፡፡ ይህም የዚች ሀገር ሀብት እንጂ<br />

የንጉሱ ወይንም የደርግ የግል ሀብት አልነበረም፡<br />

፡ ግን አጋጣሚውን ተጠቅሞ ሰርጎ የገባ<br />

ወይንም ከሕወሓት ጋር ተቀላቅሎ የመጣ ጠላት<br />

አቃጠለው፡፡ መጠነ ሰፊ የሕዝብ ንብረትም<br />

ወደመ፡፡ ይህም በዚያን ጊዜ የከፋና አስደንጋጭ<br />

ሽብር ነበር፡፡<br />

በኢትዮጵያዊነቱ ለሚያምንና<br />

የተከማቸን ብረትን ማውደም፣የአገር ቁርስን<br />

ማውደም መሆኑን ለሚያውቅና ለአገሩ<br />

ተቆርቋሪ ለሆነ ዜጋ፣የዚያ ሁሉ ንብረት<br />

መውደም፣ሳይቆጨውና ሳያንገበግበው<br />

እንደማይቀር ርግጠኛ ሆኖ መናገር ይቻላል፡<br />

፡ ይሁንና፣የፈሰሰ አልታፈሰ ነውና ከሚንቀለቀል<br />

እሣት ውስጥ እንደ ተጣለ ጅማት አሮ ተኮማትሮ<br />

ዝም ከማለት በስቀተር ሌላ መንም ለማድረግ<br />

ስለማይቻል እንደ ጅማቱ አረን ተቀብለነዋል፡፡ ዛሬ<br />

አገራችን ለኛ ባእድ እየሆነች ነው፡፡<br />

እንደሚታወቀው የነፋስ ስልክ አካባቢ<br />

ለአደጋ የተጋለጡ የነዳጅ ማደያዎች፣የእህል<br />

ጐተራዎች፣ከዕለት ጉርሳቸው በስተቀር ሌላ ቋሚ<br />

ንብረት የሌላቸው ባለብዙ ቤተሰብ አባውራዎች<br />

የሚኖሩበትና የኤሌክትሪክ መሥመር የተዘረጋበት<br />

በቀር ወረቀት አያሌ ሕፃናት የሚኖሩበት ት/<br />

ቤቶች ያሉበት በመሆኑ ለሽብር የተጋለጠ ነው፡፡<br />

ስለሆነም ነው የጦር መሣሪያ የተከማቸበት ዴፖ<br />

እንዲቃጠል የተደረገው፡፡<br />

ይህ ሁሉ ሆኖ አልፏል፡<br />

፡ የፈነዳ ፈንድቷል፤የወደመ ንብረትም<br />

ወድሟል፤የተቃጠለም ተቃጥሏል፡፡ የሞተ<br />

ሙቷል፣ግድ የለም፡፡ “በጊዜ ለኩሉ እንዳለው<br />

ቅዱስ ዳዊት” ለሁሉም ጊዜ ስላለው ጊዜው ሲደርስ<br />

የሚጠየቀው አጥፊ ይጠየቃል፡፡ ቢያንስ በታሪክ<br />

እንዲቀመጥ ይደረጋል፡፡ ደባውን ትውልድ<br />

እንዲያውቀው ተጽፎ ይቀመጣል፡፡<br />

ሁለተኛው ከባድ ፍንዳታ በሽሮሜዳ<br />

አካባቢ በአንድ የልዩ ልዩ ቁሣቁሦች ማከማቻ<br />

የፈነዳው ፍንዳታ ነበር፡፡ ምክንያቱ ከመጋዘኑ<br />

ውስጥ የነበሩ ልዩ ልዩ ፈንጂዎችና ሌሎች ልዩ ልዩ<br />

መሣሪያዎች ፈንድተው የአያሌ ሰዎች ሕይወትና<br />

ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሶ አልፏል፡፡<br />

ይህም በዚያን ወቅት የከፋ ሽብር ነበር፡፡<br />

ሦስተኛው ፍንደታ በለደታ<br />

ቤተክርስቲያን ማዶ ከባለወልድ ቤተክርስቲያን<br />

ዝቅ ብሎ ባሉት ቤቶች ውስጥ ከዐፄ ኃ/ሥላሴ<br />

ዘመነ መንግሥት ጀምሮ ጥይት ይከማችባቸው<br />

ስለነበር ያ ሁሉ ጥይት እንዲፈነዳና በአካባቢው<br />

ነዋሪ ሕዝብ ላይ ጉዳት እንዲያደርስ ሆነ ተብሎ<br />

እሳት በመለኮሱና በጥይቶቹና ሌሎች ፈንጂዎችም<br />

በመፈንዳታቸው የጥይቶቹ አረሮችና የሌሉች<br />

ፈንጀዎች ፈንጣሪዎች በሰው ሕይወትና በንብረት<br />

ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል፡፡ ይህም አሳፋሪ<br />

ሽብር ነበር፡፡<br />

ሌላውና አራተኛው ፍንዳታ የደረሰው<br />

ፒያሣ አካባቢ መብራት ኃይል መሥሪያ ቤት በስተ<br />

ጀርባ ትግራይ ሆቴል እየተባለ ይጠራ በነበረውና<br />

የትግሬዎች ዋና መናሐሪያ በነበረው ሆቴል<br />

ውስጥ የፈነዳ ቦመብ ሲሆን፣ሆቴሉ ከምድር<br />

ቤቱ አንስቶ ፎቆ ድረስ በቃጠሎ ወድሟል፡<br />

፡ በዚያ ወቅትም በሆቴሉ ውስጥ ይዝናኑ የነበሩ<br />

በርካታ ዜጎች ሞተዋል፤እንዲሁም ከፎቁ ላይ<br />

ተኝተው በነበረው ከምድር ቤቱ ውስጥ ሲጠጡ<br />

በነበሩትና በአሰላፊዎቹ ላይ ቃጠሎና የሞት<br />

አደጋ ደርሶባቸዋል፡፡ ቤቱም በጣም ወድሞ<br />

ስለነበር፣አሁን ከቦታው ላይ ሌላ ትልቅ ፎቅ<br />

ተሠርቶ ከሆቴል ቤትነት ወደ ሌላ ሸቀጣሸቀጥ<br />

ንግድ ቤትነት ተለውጦ በመሥራት ላይ ይገኛል፡፡<br />

በጣም የሚያስገርምና በጣም<br />

የሚያሳዝነው በዚያ ግዙፍ ሆቴል ላይ ያ ሁሉ<br />

ቃጠሎ ሲደርስ፣ያ ሁሉ ንብረት ሲወድምና በሰው<br />

ሕይወት ላይ የሞት አደጋ ሲደርስ ምክንያቱ ምን<br />

እንደሆነ አይታወቅም፡፡ አለመታወቁ ብቻ ሣይሆን<br />

ለማወቅም ጠረት አለመደረጉ አስገራሚ ድራማ<br />

ነው፡፡ ምኒልክ ዐደባባይ የሚገኘው በእሳት አደጋ<br />

ጣቢያ በወቅቱ ደርሶ ቃጠሎውን ለማጥፋትና<br />

የሰው ሕይወትና ንብረት ለማዳን፣አልሞከረም፡<br />

፡ ከጥፋቶቹ ብርቱ ክንድ ከበስተ ጀርባ እንዳለ<br />

በቂ ማሣያ ነው፡፡ አጥፊው አለመታወቁም በራሱ<br />

ሽብር ነው፡፡<br />

9<br />

ሌላው በጣም አሳዛኝ ወይም ሳይወሳ መታለፍ<br />

የሌለበት አንገብጋቢ ጉዳይ ትምህርቷን ጨርሳ<br />

የመመረቂያ ጊዜዋ ደርሶ ወላጆቿን ጠይቃ<br />

ለመመለስ ወደ ቦሌ በመጓዝ ላይ እንዳለች ውጭ<br />

ጉዳይ ሚኒስቴር ዝቅ ብሎ ቤተ መንግሥት አካባቢ<br />

ስትደርስ ከሚኒባሱ ውስጥ ተጠምዶ የነበረ ቦምብ<br />

ፈንድቶ ካሉት ተሳፋሪዎች ጋር አብራ የተቀሰፈችው<br />

ልጃ ገረድ ናት፡፡ ሌሎችንም፣አሷንም፣ልዑል<br />

እገዚአብሔር ነፍሳቸውን ይማር እንላለን፡፡ ይኸም<br />

በወቅቱ አሣፋሪ ሽብር ነበር፡፡ ብቻ ኢህአዴግ<br />

በሥልጣን ላይ ከወጣ ጀምሮ ከጥፋትና ከሽብር<br />

ወጥተን አናውቅም፡፡ መሸም ነጋም ሽብር ነው፡፡<br />

ዛሬም ከሽብር አልወጣንም፡፡ ነገር፣ኪነጋ ወዲያም<br />

አንወጣም፡፡<br />

ሌላው ሳይወሳ ተዘሎ መታለፍ<br />

የሌለበት ታሪካዊ ጉዳይ በሰማይ ነፈሳቸውን<br />

ይማረውና የመላው አማራ ድርጅት የተባለ<br />

የፖለቲካ ፓርቲ አቋቁመው ባያተርፉት ኖሮ<br />

የብሔርን ትርጉም ጠንቅቀው የማያውቁ ጐሰኞች<br />

የቀበሌ መታወቂያ ላይ “ብሔር አማራ” የሚል<br />

ቅጽል የተሰጠው የኢትዮጵያ ዜጋ መጨረሻው ምን<br />

ይሆን ነበር? የሚል ጥያቄ ማስከተሉ አይቀርም፡፡<br />

በ1984 ዓ.ም የተባለው ድርጅት<br />

ተቋቁሞ የብዙ ንጹሐን ዜጐች ሕይወት<br />

እስከታደገበት ጊዜ ድረስ አያሌ ንጹሐን ዜጐች<br />

ተገድለዋል፤ወደ ገደል ተጥለዋል፤አሰቦት የተባለ<br />

ገዳም ተቃጥሏል፤ገዳሙን ሲያገለግሉ የነበሩ<br />

መነኮሳትም ተገድለዋል፡፡ ይህም በታሪክ ልንረሳው<br />

የማንችለው ክፉ የዘር ሽብር ነበር፡፡ በአማራ<br />

ሕዝብ ላይ የተፈፀመ ሁለገብ ዘመቻ ትውልድ<br />

በክፋቱ ሲያወሳው የሚኖር ከሽብሮች ሁሉ<br />

የከፋው ሽብር ነበር፡፡<br />

በመሠረቱ ሕወሓት አዲስ አበባን<br />

ከረገጠበት ወቅት አንስቶ የተለያዩ ሽብሮች<br />

ተካሒደዋል፡፡ ለነዚያ አያሌ የሰው ሕይወትና<br />

የንብረት ውድመት ለደረሱት ሽብሮች ኃላፊነትን<br />

የወሰደ ግለሰብ፣ቡድን ወይም ድርጅት ግን<br />

እስካሁን ድረስ አልተገኘም፡፡<br />

ስለዚህ ክቡር የሰው ሕይወትና ንብረት እንደ<br />

ወደመ ታፍኖ ይቅር የሚል ሕግ ስለሌለ የሕግ<br />

ልዕልና የሚያከብርና ሐቅን የሚከተል አካል እስከ<br />

ሚገኝ ድረስ ወይም በሌላ አነጋገር ኢህአዴግ<br />

በሥልጣን ላይ እስካለ ድረስ ታፍኖ ይቆያል፡፡<br />

እስከዚያው ግን ከሽብር ማጥ ውስጥ መውጣት<br />

አንችልም፡፡ በመሆኑም ልዑል እግዚአብሔር<br />

እንዲገላግለን እሱን መማፀን ተገቢ ነው፡፡<br />

ከሲኦል ያመለጡ የኢህአዴግ አባላት<br />

ከመ/ር ቀለሙ ሁነኛው<br />

በአንድ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ<br />

ዜናዊ “የኢህአዴግ ስልጣን ዛፍ ላይ ወጥቶ እንደ<br />

ማንቀላፋት ነው ይሉና ፍሬውን ለቅመው ይወርዳሉ”<br />

ሲሉ በተሻDሚዎቻችው ላይ አፊዘው እንደነበር<br />

ሰምቻለሁ፡፡ መዳፈር አይሁንብኝና በራሳቸውም ላይ<br />

ያፌዙ ይመስለኛል፡፡ ፍሬውን የለቀሙት ግን እነማን<br />

ናቸው? በአርግጥም የዛፍ አናት ላይ ቁጢጥ ያሉት<br />

ለበሰለው ፍሬ እጅግ የቀረቡ በመሆናቸው እንዳሻቸው<br />

እጃቸውን እየዘረጉ ለቅመዋል፤እየለቀሙም ነው፡<br />

፡ ከታች ያሉት ተሻሚዎች ደግሞ ከጌቶቻቸው<br />

የተራረፈውን ለመቃረምም ይሁን ከቅንነት በመነጨ<br />

አመለካከት የኢህአዴግን ልማታዊ መንግሥትነት<br />

ለመደስኮር እንደ ክልፍልፍ ውሻ ነጋ ጠባ በየመንደሩ<br />

ሲዘሩ ያተረፉት ቢኖር “ዘመናዊ ቆራሊዮ”የሚል<br />

ስያሜ ነው፡፡ አሁንማ በየወረዳው የተሾሙ<br />

ካቢኔዎችና ግንባር ቀደም ካድሬዎች ውሎአቸው<br />

በየመንደሩ መሆኑ ክፉኛ አማሯቸዋል፡፡ ከዚህ<br />

አንፃር በግምገማም ይሁን በተገኘው ቀዳዳ ሾልከው<br />

መውጣትን ይሻሉ፡፡ በብዛትም እየወጡ ናቸው፡፡<br />

በቅርቡ ከአመራርም ሆነ ከአባልነት የተሰናበቱና<br />

ወደ ቀድሞ ሥራቸው የተመለሱ “ከሲኦል ያመለጡ”<br />

ወጣቶች በግልፅ ይናገራሉ፡፡ ከእስር እንደተፈታ ሰው<br />

ነው ራሳቸውን የሚቆጥሩት፡፡ በየአደባባዩም “እንኳን<br />

ደስ ያለህ/ያለሽ!” ሲባባሉ ይሰማል፡፡ በተለይም በየወሩ<br />

ከደመወዛቸው የሚቆረጠው ገንዘብ፣የጋዜጣና<br />

የመፅሄት ክፍያ በአባላቱ ቋንቋ” የማይደርስ ዕቁብ”<br />

የሚሉት የድርጅቱ ክፍያ፣የሕዳሴው ግድብ መቶ<br />

ፕርሰንት መዋጮ . . . /የሕዳሴው ግድብ መዋጮ<br />

ከኛም ደመወዝ በግዴታ መወሰዱ ሳይዘነጋ/<br />

ኑሮአቸውን ከማቃወሱ ባሻገር በገንዘባቸው ላይ<br />

ማዘዝ የማይችሉ እንደነበረ በምሬት ይገልፃሉ፡<br />

፡ ይበልጥ ደግሞ ፋታ የማይሰጠው የኢህአዴግ<br />

ግምገማ ከሰውነት ተራ አውጥቷቸዋል፡፡ የወጣትነት<br />

ሞራላቸውን ያላሸቀ ግምገማ እጅግ አድርጎ<br />

ከርፍቷቸዋል፡፡ በራስ የመተማመን ስሜታቸውን<br />

ክፉኛ ጎድቶታል፡፡ የዚህ አስተያየት ፀሐፊ እነዚህ<br />

ወጣቶች የስነ ልቡና ሀኪም እንደሚያስፈልጋቸው<br />

ያምናል፡፡<br />

ከሲኦል ካመለጡ ወጣቶች አንዳንዶቹ ካወጉልኝ<br />

ገጠመኞቻቸው መሀከል ባንድ ወቅት የኢህአዴግን<br />

የፖለቲካ መስመር ለመስበክ በየመንደሩ እየዞሩ<br />

በር ሲያንኳኩ አንዲት እማወራ “ኽረ ውሾቹ<br />

እንዳይነክሷቸው” ሲሉ አባወራው ቀበል አድርገው<br />

“ምንነካሽ?! ውሾቹ ከእኛ ይልቅ የሚያውቁት እነሱን<br />

አይአለም እንዴ?!” ያሏቸው ከልብ አስደንቆኛል፡፡<br />

በ2002 ምርጫ ወቅት ጠቅላይ ሚንስትሩ<br />

ሳይቀሩ የኢህአዴግ አባላት ቁጥር ሰባት ሚሊዮን<br />

እንደሚደርስ በኩራት ሲናገሩ ነበር፡፡ “ውስጡን<br />

ለቄስ” እንዲሉ፡፡ አሁን አሁን ግን ይህንን አሀዝ<br />

በእርግጠኝነት ደፍሮ የሚናገር የለም፡፡ የድርጅቱ<br />

ገመና በራሱ የድርጅቱ አባላት ገሀድ እየወጣ ነው፡<br />

፡ በራሱም ጊዜ መፈራረስ ጀምሯል፡፡ “እከሊትን ያየ<br />

በእሳት አይጫወትም” እንዲሉ ከሲኦል ያመለጡትን<br />

የኢህአዴግ አባላት የሞራል ድቀትና ምሬት ያስተዋለ<br />

እንኳን አባልና ደጋፊ ሊሆን አይፈልግም፡፡<br />

የዚህ አስተያየት ፀሀፊ ለዚህ አንድ መረጃ አለው፡<br />

፡ በዚህ ወር እንኳን ከየወረዳው በተባረሩ አመራሮች<br />

መትክ ተረኛ ተዋራጆችን ለመመደብ ድርጅቱ<br />

ያደረገው ጥረት ከንቱ ልፋት ሆኗል፡፡ በየመስሪያ ቤቱ<br />

የሚገኙ አባላቱ በተደጋጋሚ ቢለመኑም አሻፈረን<br />

ብለዋል፡፡<br />

ኢህአዴግ መቼም “አልሞት ባይ ተጋዳይ” ነው፤<br />

አንድ ቀን ጥርስ የሌለው አንበሳ መሆኑ ባይቀርም<br />

/አባባሉ ጋዳፊንም ያስተውሏል/፡፡ ጥቅምት 18<br />

ቀን 2004 ዓ.ም በመዲናችን አዲስ አበባ በሚገኙ<br />

ፕላዝማ ቴሌቪዥን በተዘረጋባቸው ት/ቤቶች<br />

በየወረዳው የሚገኙ አባላትን ለመሰብሰብ ተሞክሮ<br />

ነበር፡፡ የምክትል ከንቲባውና የሌሎች የአዲስ አበባ<br />

መስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች ከሥልጣናቸው<br />

መባረር በመጠኑም ቢሆን ኢህአዴግን ያሳስበዋል፡፡<br />

የእያንዳንዳቸው የግንኙነት ሰንሰለት እስከ ወረዳዎች<br />

ወርዶ ተራ አባላትንም ስለሚያካትት የአኩራፊዎቹ<br />

ቁጥር ማሻቀቡ አይቀርም፡፡<br />

በጣም የሚያስገርመው ግን ከመስከረም<br />

15/2004 ጀምሮ የትምህርት ሥርጭት ይጀምራል<br />

የተባለው የፕላዝማ ቴሌቪዥን አስታዋሽና ባለቤት<br />

አጥቶ እስከ ጠቅምት 18/2004 ባልጀመረበት<br />

ሁኔታና የቴክኒክ ችግር እንዳጋጠመ ሲነገር እንዳልቆየ<br />

የኢህአዴግን አባላት ለማወያየት ግን መፍትሄ<br />

ተገኘለት፡፡ በሰበቡም የፕላዝማው ትምህርት<br />

ተጀመረ፡፡ የትምህርት ጥራት ይሏችኋል ይሄ ነው፡፡<br />

ሀሳቤን የምቋጨው በስብከት ነው፡፡ ስብከቱ<br />

ግን ቤተ እምነቶችን አይመለከትም፡፡ በሲኦል ያሉ<br />

ቤተ-ኢህአዴጎችን አይመለከትም-በሲኦል ያሉ<br />

ቤተ-ኢህአዴጎችን እንጂ ሰባኪው እንዲህ ይላል፡፡<br />

“የመዳን ቀን አሁን ነው! በሕይወት ሳሉ እንጂ ከሞት<br />

በኋላ ከሲኦል ማምለጥ አይቻልም፡፡ ቢጤዎቻችሁ<br />

በኢህአዴግ የግምገማ መድረኮች ለራሳቸው የደረጃ<br />

ውጤት “ር” እየሰጡ ከሲኦል አምልጠው ከኢትዮጵያ<br />

ሕዝብ ጋር በንሰሐ እንደተቀላቀሉ ሁሉ መንታ<br />

መንገድ ላይ የቆማችሁ የድርጅቱ አባላትም ጊዜ<br />

አተባክኑ! ፍጠኑ! መዳን ይሆንላችሁ ዘንድ አትፍሩ!<br />

አትፍሩ! “ር” ውጤት ማስመዝገብ የሚያሳፍረው<br />

ለዩኒቨርሲቲ ትምህርት ነው፡፡ በኢህአዴግ ግምገማ<br />

“ር” ማስመዝገብ ግን ጀግንነት ነው፤ “F” ማስመዝገብ<br />

ደግሞ ከጀግንነትም በላይ ጀግንነት ነው!!<br />

ፈጣሪ አምላክ ኢትዮጵያን ይባርክ!<br />

www.andinet.org.et

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!