24.07.2013 Views

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

SHOW MORE
SHOW LESS

You also want an ePaper? Increase the reach of your titles

YUMPU automatically turns print PDFs into web optimized ePapers that Google loves.

2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

“ ነጋ-እንዴና የግብሩ ...<br />

መስጫ ተቋማት የሚጠየቀውን ጉቦ የሚያስጥለው<br />

ባለመኖሩ ስለ ግብር አከፋፈል ዝቅተኛ እውቀት<br />

ብቻ ሳይሆን ጭርሱንም ላለመክፈል የሚያደርገውን<br />

ድብብቆሽ የሚያባብስበት እንጂ የሚመልስለት<br />

እንደማይሆን እሙን ነው፡፡<br />

ግብር ከፋዩ ዛሬ ግብሩን ከፍሎ ነገ ወደ<br />

አንድ ሕክምና መስጫ ማዕከል ጐራ ቢል ከጎንት<br />

(ግላቭ) ጨምሮ የተለያዩ የህክምና መድኃኒቶችን<br />

በጓሮ በር እያወጡ ለሚቸረችሩ ጥቅመኞች ቀድመው<br />

የተጋለጡ በመሆናቸው ሚስቱ ወይም ልጁ<br />

በግላቭ ወይም ጓንት እጦት ህይወታቸው ሲያልፍ<br />

እየተመለከተና እያዳመጠ ግብር ጠቀሜታው ላንተነው<br />

የሚለውን ፕሮፓጋንዳ እንዴት ሊያዳምጥ ይችላል?<br />

እንዲያዳምጥስ ይጠበቃልን ?፡፡<br />

ታታሪው ግብረኛ አመታዊውን ዜግናታዊ<br />

ግዴታ ተወቶና እፎይ ግብሬን ከፈልኩ ብሎ ለሌላ<br />

ጉዳይ ወደ ሌላ ቢሮ ሲገባ ለመሀንዲስ ትራንሰፖርት<br />

አቅርብ፣ ለልዩ ልዩ ጉዳዮች ማስፈጸሚያ ለምሣሌ እንደ<br />

የሰላም ትግል...<br />

ሰላማዊ የምርጫ ሰራዊት አንቀሳቀሰ። ይኽ ሰላማዊ<br />

ሰልፈኛ “ድምጽ ይከበር” በማለት ፓርላማውን<br />

ያዘ። ወታደሩ እና የፖሊስ ኃይል በምርጫ ፖለቲካ<br />

እንዳይገባ ተቃዋሚው ቀደም ብሎ ህጋዊ ስራ<br />

በመሰራቱ ጣልቃ ከመግባት ተቆጠቡ። የመንግስት<br />

ስልጣን ወደ አሸናፊ ፓርቲዎች ግንባር ተላለፈ።<br />

ይኽ ግንባር በውስጡ 16 ያህል ተቃዋሚ ፓርቲዎች<br />

ነበሩበት። እስቲ የዝንባቡዌን ሁኔታ እንመልከት።<br />

በዝንባቡዌ ተቃዋሚው ፓርቲ ደጋፊዎቹ<br />

በብዛት ወጥተው እንዲመርጡ በማድረግ እንዲሁም<br />

ምርጫው ነፃ እና ፍትሃዊ እንዲሆን አለም አቀፍ<br />

ህብረተሰብ በሙጋቤ አምባገነን መንግስት ላይ ጫና<br />

እንዲያሳርፍ በማድረግ ረገድ ጥሩ ዝግጅት አድርጎ<br />

ነበር። ምርጫውን ከሙጋቤ መንግስት ስርቆት<br />

የሚያድን “ፕላን ለ” (Plan B) ግን ቸል ተብሉ ነበር።<br />

የሙጋቤ መንግስት በምርጫ ሽንፈት ቢደርስበት<br />

ስልጣን እንደማይለቅ የሚጠቁሙ ምልክቶች ቀደም<br />

ብለው ይታዩ ነበር። በምረጡኝ ዘመቻ ወቅት<br />

በተቃዋሚ ፓርቲ ደጋፊዎች እና ፓርቲ ሰራተኞች<br />

ላይ ወከባዎች፣ ድብደባዎች፣ ግድያ፣ ማሳደድ<br />

እና እስር ቤት የማጎር ተግባራት ይፈጸሙ ነበር።<br />

በምርጫው ቀን ሳይቀር አለም አቀፍ ታዛቢዮች<br />

እየተመለከቱ ድምጽ ለመስጠት የተሰለፉ ዜጎች<br />

ይደበደቡ ነበር። ፖሊስ፣ ደህንነት፣ የጦር ኃይል፣<br />

ካድሬ፣ ሚሊሺያ፣ እና በገንዘብ የተገዙ ቦዘኔዎች<br />

ሳይቀሩ በተቃዋሚ ፓርቲ ደጋፊዎች ላይ አረመኔያዊ<br />

ተግባሮች ፈጸሙ። ተቃዋሚ ፓርቲ የመረጡ ብዙ<br />

ዜጎች ለህይወታቸው በመፍራት መኖሪያቸውን ለቀው<br />

ተሰደዱ። አገር ለቀው ወደ ደቡብ አፍሪካ የጎረፉት<br />

ጥቂት አልነበሩም። ምርጫ ለመታዘብ ከአውሮፓ<br />

ተጋብዘው ከመጡት ውስጥ ምርጫው ሳያልቅ አገር<br />

ለቀው እንዲወጡ የተደረጉ ነበሩ። ባጭሩ ምርጫው<br />

ተሰረቀ። የዝምባቡዌው ሙጋቤ እንደሰርቢያው<br />

ሞሊሶቪች አይኑን በጨው አጥቦ በምርጫው አሸናፊ<br />

መሆኑን አወጀ። የሞሊሶቪች አዋጅ ተቀባይ እንዳጣ<br />

አይተናል። የሙጋቤ አዋጅ ግን ተቀባይ አላጣም።<br />

ምክንያቱም ተቃዋሚው ፓርቲ ምርጫውን ከሙጋቤ<br />

ስርቆት ማዳን ባለመቻሉ። ተቃዋሚው ድምጽ<br />

ለማስከበር የሚያስችል ዝርዝር ፕላን እና የሰላም<br />

ትግል አቅም ስላልነበረው “ምርጫው ነፃ አይደለም፣<br />

ድምጽ ይጣራ፣ ሌላ ምርጫ ይደረግ” የሚሉ ፋይዳ<br />

ቢስ ጩኸቶች ከማሰማት፣ የሙጋቤን መንግስት<br />

በጎ ፈቃደኛነት ከመጠየቅ እና የምዕራቡን አለም<br />

ከመማጸን ባሻገር ምንም ማድረግ ሳይችል ቀረ።<br />

የዝንባቡዌው ተቃዋሚ ፓርቲ እንደ ሰርቢያ “ፕላን<br />

ለ” (Plan B) ያስፈልገው ነበር !!<br />

በምርጫ ሽንፈትን መቀበል ማለት ለገዢው ፓርቲ<br />

በአገር ውስጥ እና በአለም አቀፍ ደረጃ ህጋዊነትን<br />

ማጣት ስለሚሆን በስልጣን ላይ ያሉ አምባገነን<br />

መንግስቶች ሽንፈትን ለመቀበል ዝግጁ አይደሉም።<br />

ተቃዋሚ የዲሞክራሲ ኃይሎችም በምርጫ ያገኙትን<br />

አሸናፊነት ማስከበር ካልቻሉ በአገር ውስጥ እና<br />

በአለም አቀፍ ደረጃ የገዢነት እውቅናን እና ህጋዊነትን<br />

ማግኘት አይችሉም ! ህዝብን የመንግስት ስልጣን<br />

ባለቤት ማድረግ ዋዛ አይደለም።<br />

መታወቂያ ለመሳሰለው ይሄን ያህል ክፈል እየተባለ<br />

በሚጠየቅበት እና በሚከፍለው ግብር ልክ እንኳን<br />

ባይሆን እጅግ አናሳ አገልግሎቶች እንዲያጣ እየተደረገ<br />

ከዓመታት በኃላ ታገኛቸዋለህ ሲለሚባለው ትልልቅ<br />

ፕሮጀክቶች እንዲያስብ ለማድረግ መሞከር በእጅጉ<br />

አስቸጋሪ ነው የሚሆነው፡፡<br />

ከሁሉ በላይ ደግሞ ግብር የሚከፍለውም ሆነ<br />

ማይከፍለው፣ ህገውጡና ወንጀለኛው ነጋዴ ከንፁህና<br />

ታታሪው ነጋዴ ጋር ተደበላልቆ ለትንሹም ለትልቁም<br />

ጉዳይ እኩል ከተጉላላና አንዳንዴም ቅድሚያው<br />

ለህገወጡ ለወንጀለኛው ነጋዴ ሲሰጠው ከታየ ግብር<br />

በመክፈል የሚመጣውን ለውጥና ልዩነት መለፈፉ<br />

ነገሩን ከፈረሱ ጋሪውን ማስቀደም ያስመስላል፡፡<br />

ባለፈው ክረምት ውስጥ የከተማችን ከንቲባ<br />

በቴሌቪዥን መስኮት ብቅ ብለው ግንባራቸውን እንደዛ<br />

ከስክሰው ስለግብር ሲያስረዱ ለተመለከተ ግብር<br />

በዜጐች ቀና አመለካከትና ፈቃደኝነት ፍፁም ለአገርና<br />

ሕዝብ እድገት ተገዢ በመሆን የሚከፈል የንፁህ ነፍስ<br />

ከገፅ 5 የዞረ<br />

የሆነው ሆኖ መቀየር/መለወጥ (Peaceful<br />

conversion) እና መቻቻል (Peaceful<br />

accommodation) የተባሉት ለውጥ ማምጫ<br />

መንገዶች ለገዢው ቡድን ከተቃዋሚዎች የቀረበለትን<br />

ጥያቄ የመቀበል እና ያለመቀበል ምርጫ ይሰጣሉ።<br />

ገዢውን ቡድን ማስገደድ አይችሉም። ሰላማዊ<br />

ማስገደድ (Peaceful coercion) የተባለው ለውጥ<br />

ማምጫ መንገድ ግን ገዢው ቡድን የቀረበለትን<br />

የለውጥ ጥያቄ እንዲቀበል ማስገደድ ይችላል።<br />

እንመልከት።<br />

(3ኛ) ሰላማዊ ማስገደድ (Peaceful coercion)<br />

ሰላማዊው ትግል ማስገደድን ተፈጻሚ ማድረግ<br />

ከሚችልበት ደረጃ ከደረሰ በስልጣን ላይ ያለው<br />

አምባገነናዊ መንግስት አቅም እጅግ ዝቅ ብሏል ማለት<br />

ነው። በአንጻሩ የዲሞክራሲ ኃይሎች የፖለቲካ ኃይል<br />

ከፍ ብሏል ማለት ነው። ጉልህ የፖለቲካ ኃይል ሚዛን<br />

ግንኙነት ሽግሽግ ተደርጓል ማለት ነው። የሆነው ሆኖ<br />

የገዢውን ቡድን ህልውና ላይ ስጋት የሚያሳድሩ<br />

አስገዳጅ ጥያቄዎች ከመቅረባቸው በፊት ግን<br />

ተቃዋሚው ጥንቃቄ የተሞላበት ፕላን መቀየስ እና<br />

ሰፊ የአቅም ዝግጅት ማድረግ ይኖርበታል። ተፈጻሚ<br />

ሊሆኑ የማይችሉ አስገዳጅ ጥያቄዎች ማቅረብ በህዝብ<br />

ዘንድ ተዓማኒነት ያሳጣል። የፕላን አለመጠናቀቅ<br />

ወይንም የትግል አቅም ማነስ ካለ አስገዳጅ ጥያቄዎችን<br />

ከማቅረብ መቆጠብ ወይንም አኪያሄድን ማስተካከል<br />

ይመረጣል። በስልጣን ላይ ያለው አምባገነን መንግስት<br />

የቀረበለትን አስገዳጅ የለውጥ ጥያቄ ፈቃደኛ ሳይሆን<br />

ተገዶ ከተቀበለ ማስገደድ ተሳካ ሊባል ይችላል።<br />

የሰርቢያን እና የዝምባቡዌን ሁኔታዎች እንመልከት።<br />

(4ኛ) (Peaceful disintegration)<br />

ከፍ ብለን እንዳየነው ተቃዋሚው በስልጣን<br />

ላይ ያለውን መንግስት ማስገደድ ከቻለ በገዢው<br />

ቡድንና በህዝብ መካከክል ተጨባጭ የሆነ የስልጣን<br />

ሽግሽግ ተደርጓል ማለት ነው። የፖለቲካ ኃይል ሚዛን<br />

ግንኙነት ወደ ተቃዋሚ ማድላቱ በእርግጠኛነት<br />

ከታወቀ የፖለቲካ እምቢተኛነት (Political defiance)<br />

ትብብር መንፈግ (Non-cooperation) እና ጣልቃ<br />

መግባት (Intervention) የተባሉትን የሰላም ትግል<br />

መሳሪያዎች በመጠቀም ስርዓቱን በበርካታ ግንባሮች<br />

ማጥቃት ይቻላል። ይኽ ጥቃት ቀጣይነት ካለው<br />

የፖለቲካ ኃይል ምንጮች እንደሚደርቁ እና መንግስት<br />

ተርቦ እንደሚፈረካከስ መገመት አያዳግትም።<br />

በመጨረሻ በኢትዮጵያ ሰላማዊ ትግል ህዝብን<br />

የመንግስት ስልጣን ባለቤት ማድረግ እንደሚችል<br />

በመተንተን ጥናታችንን እንፈጽማለን። በኢትዮጵያ<br />

ህዝብን የመንግስት ስልጣን ባለቤት ማድረግ<br />

የሚችልባቸው ሁለት አማራጭ ቀዳዳዎች አሉ ማለት<br />

ይቻላል። እነሱም፡-<br />

(1) አንደኛው አማራጭ በሰሜን አፍሪካ እና<br />

በመካከለኛው ምስራቅ የአረቡ ህዝብ የመረጠው<br />

መንገድ ነው። ህዝብ ለመንግስት የሰጠውን የገዢነት<br />

መብት እና ክብር በመንፈግ ህጋዊነቱን ገፍፎ ከስልጣን<br />

ማውረድ ይችላል። ህዝብ በፈለገው ጊዜ የመንግስት<br />

ለውጥ የማድረግ መብት እንዳለው የታወቀ ነው።<br />

የግብጹ ፕሬዘዳንት ሙባረክ የተመረጠበትን የአራት<br />

ከገፅ 10 የዞረ<br />

ስርዓት መገለጫ ሳይሆን ክተት የተዋጀበት ጦርነት<br />

አስመስለው ማቅረባቸው አሁንም ግብርን በተመለከተ<br />

ገዢው ፓርቲ ለራሱ በራሱ ያልገባው ስነልቦናዊ<br />

አመለካከት እንዳለ አስረጂ ነው፡፡ ይህንንም ስል ግብር<br />

መብትም ግዴታም እንደሆነ በሙሉ ልቤ ስለማምንበት<br />

ብቻ ሳይሆን እንደ ሃይማኖታዊ ትዕዛዝ የተቀበልኩት<br />

መሆኔንም ጭምር ለማሳወቅ ነው፡፡<br />

አለመታደል ሆኖ እንጂ ለጉዳይ በምንሄድባቸው<br />

የተለያዩ ህዝባዊ ሆነ መንግሥታዊ ተቋማት፣ ለምርጫ<br />

በቀረብንባቸው የምርጫ ጣቢያዎች፣ ፓርላማ፣<br />

ሆስፒታል ወዘተ ልባችን ሞልተን፣ ደረታችን ነፍተን<br />

እኔእኮ ግብር ከፋይ ነኝ! ያንተን ደሞዝ የምከፍልህ<br />

እኔነኝ ለማለት ቅንጣት ፍርሀትና የዛኛው ወገን አሉታዊ<br />

ምላሽ የምንፈራ ባልሆን ነበር፡፡ ይህን ግን አልሆነም<br />

ለዚህም አልታደልንም ግብር እንዲህ በትንሹ ነገርግን<br />

ትልልቅ ጉዳዮችን ተሸክሞ ባልጠራበት ሁኔታ እየተጓዘ<br />

ገዢው ፓርቲ የኢህአዴግ ደጋፊ ነጋዴዎች ፎረም<br />

የሚል ስያሜ ነጋዴው ላይ በመለጠፍ ነጋዴው እርስ<br />

ወይንም የአምስት አመት የስልጣን ዘመኑን ሳይጨርስ<br />

ከስልጣን እንደተወገደ እናስታውሳለን። ባጭሩ ህዝብ<br />

እምቢ አልገዛም ካለ መንግስት ሊኖር አይችልም።<br />

የኢትዮጵያ ህዝብ ይኽን አማራጭ ከመረጠ የትግሉ<br />

ባለቤት እራሱ ህዝቡ ነው የሚሆነው። የተቃዋሚ<br />

ፓርቲዎች ሚና ከህዝብ ጎን መቆም ነው የሚሆነው።<br />

(2) ሁለተኛው አማራጭ “ለድምጽ ስርቆት<br />

የማይች ምርጫ ማድረግ” ወይንም በአጭሩ<br />

“የማይሰረቅ ምርጫ” ብለን የምንጠራው ነው።<br />

የኢትዮጵያ ህገ መንግስት በምርጫ ሰላማዊ የመንግስት<br />

ሽግግርን ይፈቅዳል። ይኽ ህገ መንግስታዊ ድንጋጌ<br />

ቢያንስ በወረቀት ላይ ለመንግስት ለውጥ ጥያቄ<br />

ያመቻቻል መልስ ይሰጣል። ነገር ግን በኢትዮጵያ<br />

በስልጣን ላይ ያለው መንግስት በፈጠራቸው የምርጫ<br />

ቦርድ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች፣ ካድሬዎች እና<br />

ሲያስፈልግ ፖሊስ በመጠቀም ምርጫ ስለሚሰርቅ<br />

የኢትዮጵያን ህዝብ የመንግስት ስልጣን ባለቤት<br />

እንዳይሆን ያደርጋል። ይኽን ምርጫ የመስረቅ<br />

ችግር መቋቋም ከተቻለ በህገ መንግስት የተደነገገው<br />

ይመቻቻል መፍትሄው የከፈተውን ቀዳዳ መጠቀም<br />

እንደሚቻል ግልጽ ነው። የመንግስትን ምርጫ<br />

መስረቅ ለመከላከል “ነፃ አውጭ” የተባለ ተቃዋሚ<br />

ቡድን ጫካ ገብቶ የእርስ በርስ ጦርነት መጀመር<br />

የለበትም። ከዚኽ በኋላ የኢትዮጵያ ህዝብ የአዞ እንባ<br />

ረጪ ነፃ አውጪዎች አያስፈልጉትም። ህዝቡ ራሱን<br />

ነፃ ማውጣት አለበት። አብረውት እየኖሩ የሚታገሉ<br />

የሰላማዊ ትግል መሪዎች በሚለግሱት እገዛ ብቻ ራሱ<br />

ህዝቡ የሚያስፈልገውን መስዋዕት በመክፈል ድምጹን<br />

ከስርቆት ተከላክሎ የመንግስት ስልጣን ባለቤት<br />

መሆን ይችላል። ዛሬ ዲሞክራሲ በሆኑ አብዛኛዎቹ<br />

አገሮች ህዝቡ ነው እራሱን በሰላማዊ ትግል ነፃ<br />

ያወጣው። ለዲሞክራሲ ሽግግር አስተማማኙ<br />

መንገድም ይኸው ህዝቡ የተሳተፈበት ሰላማዊው<br />

መንገድ ነው። የኢህአዴግ መንግስት የኢትዮጵያን<br />

ህዝብ ድምጽ አላከብርም ካለ የኢትዮጵያም<br />

ህዝብ በበኩሉ አልገዛልህም ማለት አለበት። ህዝብ<br />

የኢትዮጵያ ህዝብ ድምጹ እንዳይሰረቅ የመጠበቅ<br />

መብትም አለው። ድምጽህን እኛ እንጠብቅልሃለን<br />

የሚሉ የአዞ እንባ ረጪ ካድሬዎችንም ያለማመን እና<br />

በድምጽ አሰጣጥ እና በድምጽ ቆጠራ ላይ በተወካዮቹ<br />

አማካኝነት የመሳተፍ መብትም አለው።<br />

የሆነው ሆኖ የኢትዮጵያ ህዝብ በህገ መንግስቱ<br />

ውስጥ የተጠቀሰውን የምርጫ (መቻቻል) ድንጋጌ<br />

ከ“ፕላን ለ” ጋር አዳቅሎ መጠቀምን ከመረጠ ከህዝቡ<br />

ጋር አብረው የሚኖሩ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ብዙ<br />

ስራ ይጠበቅባቸዋል። በኢትዮጵያ የምርጫ ቦርድ<br />

እና የምርጫ አስፈጻሚዎች ገለልተኛ እንዲሆኑ እና<br />

አለም አቀፍ ምርጫ ታዛቢዎች በብዛት እንዲሰማሩ<br />

ከመደራደር አንስቶ ህዝቡ ድምጹን ከስርቆት<br />

እንዲጠብቅ የማዘጋጀት ኃላፊነት አለባቸው። የሰላም<br />

ትግል ሰራዊት መገንባት ይኖርባቸዋል።<br />

ከፍ ብለው የተመለከቱት ሁለቱም አማራጮች<br />

የሰላም ትግል ሰራዊት ይሻሉ። ለመሆኑ የሰላም ትግል<br />

ሰራዊት ማን ነው? ኢንጅነሮች፣ መምህራን፣ የህግ<br />

ባለሙያዎች፣ የህክምና ባለሙያዎች፣ ተማሪዎች፣<br />

13<br />

በርስ የጎሪጥ እንዲተያይ በአሜት እንዲበላላ መንገድ<br />

ከፍቶለት ይገኛል፡፡<br />

አመታዊውን የሕዝብ ምንዳቸውን በተገቢው መልክ<br />

የሚከፍሉ ሕዝቤና አገሬ አድገው አያቸዋለሁ የሚሉ<br />

እንዳሉ ሁሉ ከባለሥልጣን ጋር በመሞዳሞድ፣ በዘር፣<br />

በቋንቋ፣ በቡድን፣ በኃይማኖት በመጠላላለፍ እና<br />

በመሳሳብ ከሕገወጡ ከኮንትሮባንድ ንግድ ጀምሮ<br />

ሰነድ እስከመደለዝና ማዘጋጀት አልፎ የሕዝብ ንብረት<br />

የሆኑ እንደ መሬት ማምረቻና ማከፋፈያ ተቋማትን<br />

ወደ እራሳቸውን ግብረ አበሮቻቸው የሚያዘዋውሩ<br />

ጥቂት አይደሉም፡፡ የሚያሳዝነው ደግሞ ይህን አደገኛ<br />

አካሄድ የሚቀላቀሉ ግለሰቦች ቁጥር ከእለት ወደ እለት<br />

በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ መምጣቱ ሌላው አደገኛ እና<br />

አሳሳቢ ሁኔታ ነው፡፡ አሁንም የዘንድሮ የግብር ዓመቱ<br />

ጥቅምት 30/2004 ዓ.ም እንደሚገባደድ የታወቀ ነው፡፡<br />

ቢሆንም ግን ምን ያህሉ ከጨዋታ ውጪ እንደሚሆንና<br />

ምን ያህሉም ተፍገምግሞ ምን ያህሉም ተዝናንቶ<br />

እንደሚቀጥል ይለይለታል፡፡<br />

ኢኮኖሚስቶች፣ የባንክ ሰራተኞች፣ የቴሌ፣ የመብራት<br />

ኃይልና የውሃ ሀብት ሠራተኞች አርቲስቶች፣ ታክሲ<br />

ነጂዎች፣ ግንበኞች፣ ሱቅ ነጋዴዎች፣ እናቶች፣<br />

አባቶች፣ የከተማ እና የገጠር ኗሪ ባጠቃላይ የሀገሪቱ<br />

ለውጥ ፈላጊ ዜጎች ሁሉ ሰላማዊ የዲሞክራሲ ኃይል<br />

ናቸው። የሰላም ትግል ሰራዊት አባላት ስራቸውን<br />

ሲጨርሱ ወደ መደበኛ ስራቸው የሚመለሱ ዜጎች<br />

ናቸው። አምባገነን መንግስትን ከስልጣን ለማስወገድ<br />

የሚደረግ ቀጣይነት ያለው የትጥቅ ትግል የሰለጠነና<br />

የተደራጀ መደበኛ የጦር ኃይል ሊኖረው እንደሚገባ<br />

ሁሉ የህዝብ ድምጽ እንዳይሰረቅ ለማድረግም ሆነ<br />

የህዝብ ድምጽ አላከብርም ያለ አምባገነን መንግስትን<br />

በሰላማዊ ትግል ከስልጣን ለማስወገድ የሚደረግ<br />

የሰላም ትግልም የሰለጠነ፣ የተደራጀ እና በድስፕሊን<br />

የታነጸ የሰላም ትግል ሰራዊት ያስፈልገዋል። የሰላም<br />

ትግል ሰራዊት ራሱን ከመንግስት ወሬ አቀባዮች<br />

(in<strong>for</strong>mers) እና ከመንግስት መልክተኛ ቆስቋሾች<br />

በመጠበቅ ረገድም የሰለጠነ ነው። በመኪና ነዳጅ<br />

ውስጥ ውሃ መቀላቀል የመኪና ነዳጅን እንደሚበክል<br />

ሁሉ የሰላም ትግል በካዮችም እንዳሉ የሚያውቅ እና<br />

በጥንቃቄ የሚጓዝ ኃይል ነው። የሰላም ትግል ሰራዊት<br />

ከገዢው ፓርቲ ደጋፊዎች ጋር ግጭት ቀርቶ ክፉ ቃል<br />

መቀያየር እንደማያስፈልግ ያውቃል። የሰላም ትግል<br />

ሰራዊት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የሰለጠኑ አባሎች<br />

ስለሚያሳትፍ የተወሰኑ መሪዎች ቢታሰሩም ትግሉ<br />

ይቀጥላል። አምባገነኖች የአገሪቱን ህዝብ በሙሉ<br />

የሚያስሩበት እስር ቤት የላቸውም።<br />

በፍኖተ ነፃነት ቁጥር 4 በአክሱም ዘመን የነበረው<br />

የመንግስት ሽግግር ባህላችን አስከፊ እንደነበር<br />

ተመልክቷል። ከዘመነ አክሱም ወዲህ ኢህአዴግ<br />

ስልጣን እስከጨበጠበት ድረስም ቢሆን የመንግስት<br />

ሽግግር ታሪካችን ይበልጥ አስከፊ እየሆነ እና ኋላቀር<br />

እያደረገን እንጂ ወደፊት እንድንራመድ አንዲት<br />

ጋት አልረዳንም። በእርስ በርስ ጦርነት የሚደረግ<br />

የመንግስት ሽግግር ቢትዮጵያ ላይ ያደረሰው ኪሳራ<br />

በፍኖተ ነፃነት ቁጥር 12 ቀርቧል። በእርስ በርስ<br />

መገዳደል የሚፈጸም የመንግስት ስልጣን ሽግግር<br />

በኢትዮጵያ መቆም አለበት። ኢትዮጵያ ህዝብ<br />

የመንግስት ስልጣን ባለቤት የሚሆንበት ዘመናዊ<br />

የመንግስት ሽግግር ባህልን ተቀብላ በዘመናዊ<br />

መንግስት መመራት መጀመር አለባት። ለዚህ<br />

አስተማማኙ የፖለቲካ ትግል መንገድ ሰላማዊ ትግል<br />

ነው። ከፍ ብለን ያየናቸው ሁለት አማራጮች የሰላም<br />

ትግል መንገዶች ናቸው። ለዲሞክራሲ የሚደረግ<br />

ትግል በየትም አገር ቢሆን ቀላል ሆኖ አያውቅም።<br />

ይሁን እንጂ ከገዢ አምባገነኖች አቅም ጨቁነው<br />

የሚገዙት ህዝብ አቅም ሚሊዮን ጊዜ እንደሚበልጥ<br />

ላፍታ መዘንጋት የለብንም። ስለዚኽ በረጅሙ<br />

አስፈላጊው ጥናት እና ዝግጅት ከተደረገ፣ አቅም<br />

ከተገነባ፣ ስትራተጂዎች እና ፕላኖች በጥንቃቄ ከተሰሉ<br />

በኢትዮጵያ የሰላም ትግል መስራት ብቻ ሳይሆን<br />

ለኢትዮጵያ ተመራጩ የፖለቲካ እና የመንግስት<br />

ሽግግር ባህል እሱ ብቻ ነው በማለት ጥናታችንን<br />

እንደመድማለን።<br />

www.andinet.org.et

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!