24.07.2013 Views

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

SHOW MORE
SHOW LESS

Create successful ePaper yourself

Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.

2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />

መግለጫ ተያት<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

ትግሉ መራራ ቢሆንም በፅናት ለድል እንበቃለን!<br />

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ<br />

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ የተነሳለትን ዓላማ<br />

ለማሳካት የአምባገነኖችን አፈና እየተቋቋመ አባላቱ የህይወትና የንብረት መስዋዕትነት እየከፈሉ<br />

እስከዛሬ ቀን ደርሰዋል፡፡ ዛሬም ገዢው ፓርቲ በአዋጅ በመደገፍ በአካሄደው መንግስታዊ<br />

የጥቃት ዘመቻ ከፍተኛ የፓርቲው አመራሮች፡- (1ኛ) ምክትል ሊቀመንበርና የሕዝብ ግንኙነት<br />

አላፊ አቶ አንዱዓለም አራጌ፣ (2ኛ) የብሔራዊ ምክር ቤት አባል አቶ ናትናኤል መኮንን፣ (3ኛ)<br />

የብሔራዊ ምክር ቤት አባል አቶ ብርሃኑ አሳምነው የማያባራው የግፍ ጥቃት ሰለባ ሆነዋል፡፡<br />

በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስተር መለስ ዜናዊ ባደረጉት ንግግር በተቃዋሚው ጎራ በተለይ<br />

በአንድነት ፓርቲ ላይ የሚደረገው አፈና ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡ ከጥቃት ዘመቻው<br />

በተጨማሪም የፍርድ ቤቱን በትር በህግ ሽፋን እንደሚጠቀሙ በአደባባይ ያለምንም ይሉኝታ<br />

አረጋግጠውልናል፡፡ መንግስት አንድነትን በህግ ሽፋን ስም በጉልበት ለማዳከም መዘጋጀቱን<br />

ያለጥርጥር አረጋግጠውልናል፡፡<br />

ይህ አደገኛ መንግስታዊ ሽብር በፓርቲያችን ላይ እየተፈፀመ ባለበት በአሁኑ ወቅት<br />

የፓርቲያችን ከፍተኛ የስልጣን አካል የሆነው ብሔራዊ ምክር ቤታችን ከጥቅምት 25-<br />

26/2004 ዓ.ም. የአንደኛውን ዙር የመጨረሻ የሥራ ዘመኑን ስብሰባ በታላቅ ቁጭትና ወኔ<br />

ታጅቦ ጉባኤውን አከናውንዋል፡፡<br />

ጉባኤው መንግስት ሕገ-መንግቱን በመጣስ በአባሎቻችን ላይ እየፈፀመ ያለውን የእብሪት<br />

እርምጃ አውግዝዋል፡፡ እንዲሉ በሽብርተኝነት ስም በግፍ<br />

አፍኖ ከማንም ጋር እንዳይገናኙ ሸብቦ ያስራቸው አባሎቶቻችን በአስቸካይ እንዲፈቱ ምክር<br />

ቤቱ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡<br />

ምክር ቤቱ በቀረበለት አጀንዳ ላይ ለሁለት ቀናት ሰፊና ጥልቀት ያለው ውይይት በማድረግ<br />

የኢትዮጵያ ሕዝብ ለነጻነትና ለዴሞክራሲ የሚያደረገውን ሰላማዊ ትግል ወደ ፊት ለማራመድ<br />

የሚያስችሉ ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን አስተላፏል፡፡ በተለይም የፓርቲውን የ2003 ዓ.ም. የሥራ<br />

አፈፃፀምን በተመለከተ ሰፊ ሪፖርት ቀርቦ ደካማና ጠንካራ ጎኖች ተገምግመዋል፡፡<br />

ምክር ቤቱ ከአምስት ወር በፊት ያቋቋመው የጠቅላላ ጉባኤ ጠሪ ኮሚቴ ከአንድ<br />

ወር በኋላ የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ተጠርቶ የስራ ዘመኑን የጨረሰውን ይህን ምክር ቤት<br />

በክብር ያሰናብተዋል፡፡ የሁለተኛው ዙር አዲስ ምክር ቤት በጠቅላላ ጉባኤው በሚደረግ ነፃና<br />

ዴሞክራሳያዊ ምርጫ አዲስ ብሔራዊ ምክር ቤት በመምረጥና የስልጣን ርክክብ ለማድረግ<br />

አንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ም/ቤት መደበኛ ስብሰባውን አካሄደ<br />

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ /አንድነት/<br />

ብሔራዊ ም/ቤት የመጀመሪያ ዙር የመጨረሻውን የሥራ<br />

ዘመን ጥቅምት 25 እና 26 ቀን 2004 ዓ.ም በጽ/ቤቱ<br />

አዳራሽ መደበኛ ስብሰባውን አካሄደ፡፡<br />

በስብሰባውም በዋነኛነት አራት አጀንዳዎች<br />

ለውይይት የቀረቡ ሲሆን እነኝህም 1ኛ የብሔራዊ ሥራ<br />

አስፈፃሚ ኮሚቴ የሥራ ሪፖርት ማዳመጥ 2ኛ የጠቅላላ<br />

ጉባዔ ጠሪ ኮሚቴ የሥራ ሪፖርት ማዳመጥ 3ኛ የአምስት<br />

ዓመት እቅድና ስትራቴጂ መሠረት በማድረግ የ2004<br />

ዓ.ም በጀት ዕቅድን ማጽደቅ እና 4ኛ ያለፉትን ስብሰባዎች<br />

ቃለ ጉባዔ ማፅደቅ በሚሉ አጀንዳዎች ዙሪያ ነበር፡፡<br />

ብሔራዊ ምክር ቤቱ በአጀንዳዎቹ ላይ<br />

ሰፊ ውይይት በማድረግ አጀንዳዎችን ያፀደቀ ሲሆን<br />

በተለይም በብሔራዊ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የሥራ<br />

ሪፖርት በፓርቲው ሊቀመንበር በዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ<br />

ቀርቧል፡፡<br />

በሪፖርቱ ላይ በእቅዱ መሠረት የተሰሩና<br />

ያልተሰሩ ሥራዎችን መለየት ተችሏል ሲሉ አባላቱ<br />

ገልፀዋል፡፡ በእቅዱ መሠረት ከተሰሩት ውስጥ የፓርቲው<br />

ልሳን “ፍኖተ ነፃነት” ጋዜጣ በየሳምንቱ አሳትሞ<br />

የፓርቲውን እንቅስቃሴ ወቅታዊ የሆኑ ሀገር አቀፍና ዓለም<br />

አቀፍ መረጃዎችን ለሕዝቡ ማድረስ፣በሀገራዊ ወቅታዊ<br />

ጉዳይ ላይ የተለያዩ ምሁራንን ከውጭና ከሀገር ውስጥ<br />

በመጋበዝ ውይይት ማድረግ፣የፓርቲው መመሪያና ደንብ<br />

በሚፈቅደው መሠረት ከመድረክ አቻ ፓርቲዎች ጋር<br />

ሰፊና ጥልቅ ውይይት በማድረግ መድረክን ከቅንጅት<br />

ወደ ግንባር የማሸጋገር ሂደት፣ከብርሃን ለአንድነትና<br />

ለዴሞክራሲ ፓርቲ ጋር ውህደት የመፍጠር ሂደት<br />

ከተሳኩ ተግባራቶች መካከል ጥቂቶቹ ናቸው ተብሏል፡፡<br />

ሌላው ፓርቲው መዋቅሩን በመላው<br />

ሀገሪቱ የማስፋፋትና አሰራሩንም እስከ ወረዳ ድረስ<br />

በመዘርጋት የፓርቲው አባላት በአቅራቢያቸው<br />

እንዲደራጁ ተደርጓል፡፡ ይሁን እንጂ ይህንና ሌላሎች<br />

እቅዶች ሙሉ በሙሉ ተፈፃሚ እንዳይሆኑ የተለያዩ<br />

እንቅፋቶች ተፈጥረው ነበር፡፡ ከችግሮቹም መካከል<br />

ኢህአዴግ የፖለቲካ ምህዳሩን ማጥበብ፣የፓርቲ አባላትን<br />

ማስፈራራት፣ማሰርና መግደል ዋነኞቹ ችግሮች እንደሆኑ<br />

በም/ቤቱ ተጠቁሟል፡፡<br />

በተጨማሪም ፓርቲው በሰው<br />

ኃይል፣በአቅምና በገንዘብ ማነስ ምክንያት በእቅዱ መሠረት<br />

የሚጠበቅበትን አልሰራም ሲሉ ያለፈው ዓመት ስራ<br />

አፈፃፀም ሪፖርትን ም/ቤቱ ገምግሟል ሲል የፓርቲው<br />

ጽ/ቤት ገልጿል፡፡<br />

ለእቅዱ መሳካት ሌሎች ችግሮችም<br />

ተነስተዋል፡፡ እንደ ችግር ከተነሱት መካከል በቂ የገንዘብ<br />

የታሰበውን ያህል ያለማግኘት፣በቂ የሰው ኃይል ያለመኖር<br />

ተጠቅሰዋል፡፡<br />

ከላይ የተጠቀሱትን ችግሮችን ለመቅረፍ<br />

በ2004 ዓ.ም የተለያዩ የመፍትሄ አቅጣጫዎች የተነሱ<br />

ሲሆን ከነዚህም መካከል በዕውቀትና በቁርጠኝነት<br />

ላይ የተመሰረተ የሰው ኃይል ወደ ፓርቲው እንዲመጣ<br />

መጋበዝ፣ደጋፊዎች ከእውቀትና ከጉልበት በተጨማሪ<br />

በገንዘብም ድጋፍ ማድረግ እንዲችሉ ሕጋዊ የሆኑ<br />

የተለያዩ ስልቶችን መቀየስና ለሕዝቡ ይፋ ማድረግ፣<br />

የሚመጣውም አዲሱ ም/ቤት አባላት በዕውቀትና<br />

በቁርጠኝነት ላይ መሠረት ማድረግ እንዳለበትም ም/ቤቱ<br />

ጠቁሟል፡፡<br />

አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ<br />

አካባቢ ያሉ ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙ የፓርቲው<br />

አባላትንና ሌሎች የፖለቲካና የሕሊና እስረኞችን ጉዳይ<br />

የሚከታተል ልዩ ግብረ ኃይል እንደተቋቋመና ሥራውን<br />

እያከናወነ እንዳለም በሪፖርቱ ገልጿል፡፡<br />

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከ13 ቀናት በፊት<br />

የፓርቲው አባል አቶ ገዛኸኝ ምትኩ በሽብር ተጠርጥሮ<br />

ከሚኖርበት ቂርቆስ ክ/ከተማ በመውሰድ ማዕከላዊ እስር<br />

ቤት እንደሚገኝ ተጠቁሟል፡፡ ባለፈው መስከረም 4 ቀን<br />

2004 ዓ.ም ተጠርጥረው ከታሰሩት መካከል የአንድነት<br />

ፓርቲ ም/ሊቀመንበርና የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ<br />

አንዱዓለም አራጌ ታመው ሆስፒታል ሄደው የሕክምና<br />

እርዳታ እንደተደረገላቸው በሪፖርቱ ላይ የፓርቲው<br />

ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ገልፀዋል፡፡<br />

በስብሰባው ላይ በቀረቡት አጀንዳዎች ዙሪያ ሰፊ<br />

ውይይት ካደረገ በኋላ በአባላቱ ፀድቆ የመጨረሻው<br />

የሥራ ዘመን ጥቅምት 26 ቀን 2004 ዓ.ም ተጠናቋል<br />

ሲል የአንድት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ /አንድነት/<br />

ብሔራዊ ም/ቤት በተለይም ለዝግጅት ክፍላችን ገልጿል፡<br />

፡ይህ በእንዲህ እንዳለ የጉበኤ ጠሪ ኮሚቴ የተሻሻለ<br />

ፕሮግራምና ደንብ ለምክር ቤቱ አቅርቧል፡፡ በአንድነት<br />

15<br />

ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ለምክር ቤቱ አብስሮዋል፡፡ ብሔራዊ ምክር ቤቱ የአንድነት ጠቅላላ<br />

ጉባኤ ህዳር 30 እና ታህሳስ 1/2004 እንዲካሄድ ወስኗል፡፡<br />

ይህንን ተከትሎ ለጠቅላላ ጉባኤ ቀርበው የሚፀድቁትን ልዩ ልዩ የፓርቲው የመታገያ<br />

ሠነዶች ለምክር ቤቱ ቀርበው ከተመረመሩ በኋላ ጠቅላላ ጉባኤው መርምሮ እንዲያፀድቃቸው<br />

ወስኗል፡፡ የፓርቲያችን አዲሱ ሊቀመንበር ከሁሉም አባላት በውድድር በዕጩነት ቀርበው<br />

በጠቅላላ ጉባኤው ፊት አባላት ቀጥተኛ የድምፅ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት እንዲመረጡ<br />

ወስኗዋል፡፡<br />

አንድነት በአለፉት ሦስት ዓመታት ከአጋጠሙት መሰናክሎች ትምህርት ወስዶ የራሱን<br />

የትግል ስትራቴጂና የአምስት አመት እቅድ ነድፎ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ የተቀየሰውን<br />

ስትራቴጂ ለመተግበር የሚያስችል አቅም ለመፍጠር ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ነው፡፡<br />

በአዲሱ ዓመት ዜጎች ያለፍርሃት፣ ሳይሸማቀቁ በነፃነት የሚኖሩባት፣ በግል ጥረታቸው<br />

ያፈሩትን ሃብትና ንብረት በግፍ የማይነጠቁባት፤ የዴሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብቶች<br />

የተከበረባት ኢትዮጵያን ለመፍጠር በሚደረገው ትግል ኢትዮጵያዊያን ሁሉ እጅ ለእጅ<br />

ተያይዘን በፅናት እንድንታገል ብሔራዊ ምክር ቤታችን ጥሪውን ያቀርባል፡፡<br />

መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሕገወጦችን አውግዞና፣ ጊዜው የለውጥ መሆኑን ተገንዝቦ<br />

ፓርቲያችን የሰነቀውን ሀገራዊ ራዕይ ደግፎ በዕውቀት ላይ የተመሠረተና የሰለጠነ የመቻቻል<br />

የፖለቲካ መርሆችን ተከትሎ ለነፃነቱ የበኩሉን አስተዋፅኦ እንዲያበረክት የአንድነት ፓርቲ<br />

ብሔራዊ ምክር ቤት ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡<br />

የፖለቲካና የህሊና እስረኞች በአስቸኳያ ይፈቱ!!<br />

ሠላማዊ ትግል ያሸንፋል!!<br />

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት<br />

ጥቅምት 26/2004 ዓ.ም.<br />

አዲስ አበባ<br />

የስብሰባው ተካፋዮች በከፊል<br />

ፕሮግራም ውስጥ እንዲካተቱ ከተደረጉ ጉዳዮች<br />

መካከል አሸባሪነትን በተመለከተና የመሬት ወረራ<br />

ጉዳይን ያካትታል፡፡ ምክር ቤቱ የፓርቲው ፕሮግራም<br />

ውስጥ እንደ አዲስ የተካተቱትን ጉዳዮች በጥልቀት<br />

ተወያይቶበቷል ሲል ምክር ቤቱ ጠቁሟል፡፡<br />

የተሻሻለው የፓርቲው ህገ-ደንብ እንደሚያስረዳው<br />

የፓርቲው ሊቀመንበር በጠቅላላ ጉባኤ የሚመረጥ ሲሆን፣<br />

ሊቀመንበሩ ሌሎች የስራ አስፈፃሚ አባላትን መልምሎ<br />

በዕጩነት ለብሔራዊ ምክር ቤት አቅርቦ ያፀድቃል፡<br />

፡ የፓርቲው መሪ መሆን የሚፈልጉና የተቀመጠውን<br />

መስፈርት የሚያሟሉ አባላት የጠቅላላ ጉባኤ አባላትን<br />

ድጋፍ እንዲያደርጉ በመቀስቀስ መወዳደር እንደሚችሉ<br />

ተገልጿል፡፡ በተመሳሳይም የስራ አስፈፃሚ አባለት ቁጥር<br />

ከ18 ወደ 11 እንዲወርድ ተደርጓል፡፡<br />

ብሔራዊ ምክር ቤቱም የፓርቲውን ጠቅላላ ጉባኤ<br />

በህዳር 30 እና ታህሳስ 01 ቀን 2004 ዓ.ም. እንዲካሄድ<br />

መወሰኑን ምክር ቤቱ በተለይም ለዝግጅት ክፍሉ<br />

ገልጿል፡፡<br />

www.andinet.org.et

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!