ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless
ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless
ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless
Create successful ePaper yourself
Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.
2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />
መግለጫ ተያት<br />
ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />
ትግሉ መራራ ቢሆንም በፅናት ለድል እንበቃለን!<br />
ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ<br />
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ የተነሳለትን ዓላማ<br />
ለማሳካት የአምባገነኖችን አፈና እየተቋቋመ አባላቱ የህይወትና የንብረት መስዋዕትነት እየከፈሉ<br />
እስከዛሬ ቀን ደርሰዋል፡፡ ዛሬም ገዢው ፓርቲ በአዋጅ በመደገፍ በአካሄደው መንግስታዊ<br />
የጥቃት ዘመቻ ከፍተኛ የፓርቲው አመራሮች፡- (1ኛ) ምክትል ሊቀመንበርና የሕዝብ ግንኙነት<br />
አላፊ አቶ አንዱዓለም አራጌ፣ (2ኛ) የብሔራዊ ምክር ቤት አባል አቶ ናትናኤል መኮንን፣ (3ኛ)<br />
የብሔራዊ ምክር ቤት አባል አቶ ብርሃኑ አሳምነው የማያባራው የግፍ ጥቃት ሰለባ ሆነዋል፡፡<br />
በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስተር መለስ ዜናዊ ባደረጉት ንግግር በተቃዋሚው ጎራ በተለይ<br />
በአንድነት ፓርቲ ላይ የሚደረገው አፈና ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡ ከጥቃት ዘመቻው<br />
በተጨማሪም የፍርድ ቤቱን በትር በህግ ሽፋን እንደሚጠቀሙ በአደባባይ ያለምንም ይሉኝታ<br />
አረጋግጠውልናል፡፡ መንግስት አንድነትን በህግ ሽፋን ስም በጉልበት ለማዳከም መዘጋጀቱን<br />
ያለጥርጥር አረጋግጠውልናል፡፡<br />
ይህ አደገኛ መንግስታዊ ሽብር በፓርቲያችን ላይ እየተፈፀመ ባለበት በአሁኑ ወቅት<br />
የፓርቲያችን ከፍተኛ የስልጣን አካል የሆነው ብሔራዊ ምክር ቤታችን ከጥቅምት 25-<br />
26/2004 ዓ.ም. የአንደኛውን ዙር የመጨረሻ የሥራ ዘመኑን ስብሰባ በታላቅ ቁጭትና ወኔ<br />
ታጅቦ ጉባኤውን አከናውንዋል፡፡<br />
ጉባኤው መንግስት ሕገ-መንግቱን በመጣስ በአባሎቻችን ላይ እየፈፀመ ያለውን የእብሪት<br />
እርምጃ አውግዝዋል፡፡ እንዲሉ በሽብርተኝነት ስም በግፍ<br />
አፍኖ ከማንም ጋር እንዳይገናኙ ሸብቦ ያስራቸው አባሎቶቻችን በአስቸካይ እንዲፈቱ ምክር<br />
ቤቱ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡<br />
ምክር ቤቱ በቀረበለት አጀንዳ ላይ ለሁለት ቀናት ሰፊና ጥልቀት ያለው ውይይት በማድረግ<br />
የኢትዮጵያ ሕዝብ ለነጻነትና ለዴሞክራሲ የሚያደረገውን ሰላማዊ ትግል ወደ ፊት ለማራመድ<br />
የሚያስችሉ ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን አስተላፏል፡፡ በተለይም የፓርቲውን የ2003 ዓ.ም. የሥራ<br />
አፈፃፀምን በተመለከተ ሰፊ ሪፖርት ቀርቦ ደካማና ጠንካራ ጎኖች ተገምግመዋል፡፡<br />
ምክር ቤቱ ከአምስት ወር በፊት ያቋቋመው የጠቅላላ ጉባኤ ጠሪ ኮሚቴ ከአንድ<br />
ወር በኋላ የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ተጠርቶ የስራ ዘመኑን የጨረሰውን ይህን ምክር ቤት<br />
በክብር ያሰናብተዋል፡፡ የሁለተኛው ዙር አዲስ ምክር ቤት በጠቅላላ ጉባኤው በሚደረግ ነፃና<br />
ዴሞክራሳያዊ ምርጫ አዲስ ብሔራዊ ምክር ቤት በመምረጥና የስልጣን ርክክብ ለማድረግ<br />
አንድነት ፓርቲ ብሔራዊ ም/ቤት መደበኛ ስብሰባውን አካሄደ<br />
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ /አንድነት/<br />
ብሔራዊ ም/ቤት የመጀመሪያ ዙር የመጨረሻውን የሥራ<br />
ዘመን ጥቅምት 25 እና 26 ቀን 2004 ዓ.ም በጽ/ቤቱ<br />
አዳራሽ መደበኛ ስብሰባውን አካሄደ፡፡<br />
በስብሰባውም በዋነኛነት አራት አጀንዳዎች<br />
ለውይይት የቀረቡ ሲሆን እነኝህም 1ኛ የብሔራዊ ሥራ<br />
አስፈፃሚ ኮሚቴ የሥራ ሪፖርት ማዳመጥ 2ኛ የጠቅላላ<br />
ጉባዔ ጠሪ ኮሚቴ የሥራ ሪፖርት ማዳመጥ 3ኛ የአምስት<br />
ዓመት እቅድና ስትራቴጂ መሠረት በማድረግ የ2004<br />
ዓ.ም በጀት ዕቅድን ማጽደቅ እና 4ኛ ያለፉትን ስብሰባዎች<br />
ቃለ ጉባዔ ማፅደቅ በሚሉ አጀንዳዎች ዙሪያ ነበር፡፡<br />
ብሔራዊ ምክር ቤቱ በአጀንዳዎቹ ላይ<br />
ሰፊ ውይይት በማድረግ አጀንዳዎችን ያፀደቀ ሲሆን<br />
በተለይም በብሔራዊ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የሥራ<br />
ሪፖርት በፓርቲው ሊቀመንበር በዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ<br />
ቀርቧል፡፡<br />
በሪፖርቱ ላይ በእቅዱ መሠረት የተሰሩና<br />
ያልተሰሩ ሥራዎችን መለየት ተችሏል ሲሉ አባላቱ<br />
ገልፀዋል፡፡ በእቅዱ መሠረት ከተሰሩት ውስጥ የፓርቲው<br />
ልሳን “ፍኖተ ነፃነት” ጋዜጣ በየሳምንቱ አሳትሞ<br />
የፓርቲውን እንቅስቃሴ ወቅታዊ የሆኑ ሀገር አቀፍና ዓለም<br />
አቀፍ መረጃዎችን ለሕዝቡ ማድረስ፣በሀገራዊ ወቅታዊ<br />
ጉዳይ ላይ የተለያዩ ምሁራንን ከውጭና ከሀገር ውስጥ<br />
በመጋበዝ ውይይት ማድረግ፣የፓርቲው መመሪያና ደንብ<br />
በሚፈቅደው መሠረት ከመድረክ አቻ ፓርቲዎች ጋር<br />
ሰፊና ጥልቅ ውይይት በማድረግ መድረክን ከቅንጅት<br />
ወደ ግንባር የማሸጋገር ሂደት፣ከብርሃን ለአንድነትና<br />
ለዴሞክራሲ ፓርቲ ጋር ውህደት የመፍጠር ሂደት<br />
ከተሳኩ ተግባራቶች መካከል ጥቂቶቹ ናቸው ተብሏል፡፡<br />
ሌላው ፓርቲው መዋቅሩን በመላው<br />
ሀገሪቱ የማስፋፋትና አሰራሩንም እስከ ወረዳ ድረስ<br />
በመዘርጋት የፓርቲው አባላት በአቅራቢያቸው<br />
እንዲደራጁ ተደርጓል፡፡ ይሁን እንጂ ይህንና ሌላሎች<br />
እቅዶች ሙሉ በሙሉ ተፈፃሚ እንዳይሆኑ የተለያዩ<br />
እንቅፋቶች ተፈጥረው ነበር፡፡ ከችግሮቹም መካከል<br />
ኢህአዴግ የፖለቲካ ምህዳሩን ማጥበብ፣የፓርቲ አባላትን<br />
ማስፈራራት፣ማሰርና መግደል ዋነኞቹ ችግሮች እንደሆኑ<br />
በም/ቤቱ ተጠቁሟል፡፡<br />
በተጨማሪም ፓርቲው በሰው<br />
ኃይል፣በአቅምና በገንዘብ ማነስ ምክንያት በእቅዱ መሠረት<br />
የሚጠበቅበትን አልሰራም ሲሉ ያለፈው ዓመት ስራ<br />
አፈፃፀም ሪፖርትን ም/ቤቱ ገምግሟል ሲል የፓርቲው<br />
ጽ/ቤት ገልጿል፡፡<br />
ለእቅዱ መሳካት ሌሎች ችግሮችም<br />
ተነስተዋል፡፡ እንደ ችግር ከተነሱት መካከል በቂ የገንዘብ<br />
የታሰበውን ያህል ያለማግኘት፣በቂ የሰው ኃይል ያለመኖር<br />
ተጠቅሰዋል፡፡<br />
ከላይ የተጠቀሱትን ችግሮችን ለመቅረፍ<br />
በ2004 ዓ.ም የተለያዩ የመፍትሄ አቅጣጫዎች የተነሱ<br />
ሲሆን ከነዚህም መካከል በዕውቀትና በቁርጠኝነት<br />
ላይ የተመሰረተ የሰው ኃይል ወደ ፓርቲው እንዲመጣ<br />
መጋበዝ፣ደጋፊዎች ከእውቀትና ከጉልበት በተጨማሪ<br />
በገንዘብም ድጋፍ ማድረግ እንዲችሉ ሕጋዊ የሆኑ<br />
የተለያዩ ስልቶችን መቀየስና ለሕዝቡ ይፋ ማድረግ፣<br />
የሚመጣውም አዲሱ ም/ቤት አባላት በዕውቀትና<br />
በቁርጠኝነት ላይ መሠረት ማድረግ እንዳለበትም ም/ቤቱ<br />
ጠቁሟል፡፡<br />
አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የሀገሪቱ<br />
አካባቢ ያሉ ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙ የፓርቲው<br />
አባላትንና ሌሎች የፖለቲካና የሕሊና እስረኞችን ጉዳይ<br />
የሚከታተል ልዩ ግብረ ኃይል እንደተቋቋመና ሥራውን<br />
እያከናወነ እንዳለም በሪፖርቱ ገልጿል፡፡<br />
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከ13 ቀናት በፊት<br />
የፓርቲው አባል አቶ ገዛኸኝ ምትኩ በሽብር ተጠርጥሮ<br />
ከሚኖርበት ቂርቆስ ክ/ከተማ በመውሰድ ማዕከላዊ እስር<br />
ቤት እንደሚገኝ ተጠቁሟል፡፡ ባለፈው መስከረም 4 ቀን<br />
2004 ዓ.ም ተጠርጥረው ከታሰሩት መካከል የአንድነት<br />
ፓርቲ ም/ሊቀመንበርና የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ<br />
አንዱዓለም አራጌ ታመው ሆስፒታል ሄደው የሕክምና<br />
እርዳታ እንደተደረገላቸው በሪፖርቱ ላይ የፓርቲው<br />
ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ገልፀዋል፡፡<br />
በስብሰባው ላይ በቀረቡት አጀንዳዎች ዙሪያ ሰፊ<br />
ውይይት ካደረገ በኋላ በአባላቱ ፀድቆ የመጨረሻው<br />
የሥራ ዘመን ጥቅምት 26 ቀን 2004 ዓ.ም ተጠናቋል<br />
ሲል የአንድት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ /አንድነት/<br />
ብሔራዊ ም/ቤት በተለይም ለዝግጅት ክፍላችን ገልጿል፡<br />
፡ይህ በእንዲህ እንዳለ የጉበኤ ጠሪ ኮሚቴ የተሻሻለ<br />
ፕሮግራምና ደንብ ለምክር ቤቱ አቅርቧል፡፡ በአንድነት<br />
15<br />
ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ለምክር ቤቱ አብስሮዋል፡፡ ብሔራዊ ምክር ቤቱ የአንድነት ጠቅላላ<br />
ጉባኤ ህዳር 30 እና ታህሳስ 1/2004 እንዲካሄድ ወስኗል፡፡<br />
ይህንን ተከትሎ ለጠቅላላ ጉባኤ ቀርበው የሚፀድቁትን ልዩ ልዩ የፓርቲው የመታገያ<br />
ሠነዶች ለምክር ቤቱ ቀርበው ከተመረመሩ በኋላ ጠቅላላ ጉባኤው መርምሮ እንዲያፀድቃቸው<br />
ወስኗል፡፡ የፓርቲያችን አዲሱ ሊቀመንበር ከሁሉም አባላት በውድድር በዕጩነት ቀርበው<br />
በጠቅላላ ጉባኤው ፊት አባላት ቀጥተኛ የድምፅ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት እንዲመረጡ<br />
ወስኗዋል፡፡<br />
አንድነት በአለፉት ሦስት ዓመታት ከአጋጠሙት መሰናክሎች ትምህርት ወስዶ የራሱን<br />
የትግል ስትራቴጂና የአምስት አመት እቅድ ነድፎ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ የተቀየሰውን<br />
ስትራቴጂ ለመተግበር የሚያስችል አቅም ለመፍጠር ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ነው፡፡<br />
በአዲሱ ዓመት ዜጎች ያለፍርሃት፣ ሳይሸማቀቁ በነፃነት የሚኖሩባት፣ በግል ጥረታቸው<br />
ያፈሩትን ሃብትና ንብረት በግፍ የማይነጠቁባት፤ የዴሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብቶች<br />
የተከበረባት ኢትዮጵያን ለመፍጠር በሚደረገው ትግል ኢትዮጵያዊያን ሁሉ እጅ ለእጅ<br />
ተያይዘን በፅናት እንድንታገል ብሔራዊ ምክር ቤታችን ጥሪውን ያቀርባል፡፡<br />
መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሕገወጦችን አውግዞና፣ ጊዜው የለውጥ መሆኑን ተገንዝቦ<br />
ፓርቲያችን የሰነቀውን ሀገራዊ ራዕይ ደግፎ በዕውቀት ላይ የተመሠረተና የሰለጠነ የመቻቻል<br />
የፖለቲካ መርሆችን ተከትሎ ለነፃነቱ የበኩሉን አስተዋፅኦ እንዲያበረክት የአንድነት ፓርቲ<br />
ብሔራዊ ምክር ቤት ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡<br />
የፖለቲካና የህሊና እስረኞች በአስቸኳያ ይፈቱ!!<br />
ሠላማዊ ትግል ያሸንፋል!!<br />
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት<br />
ጥቅምት 26/2004 ዓ.ም.<br />
አዲስ አበባ<br />
የስብሰባው ተካፋዮች በከፊል<br />
ፕሮግራም ውስጥ እንዲካተቱ ከተደረጉ ጉዳዮች<br />
መካከል አሸባሪነትን በተመለከተና የመሬት ወረራ<br />
ጉዳይን ያካትታል፡፡ ምክር ቤቱ የፓርቲው ፕሮግራም<br />
ውስጥ እንደ አዲስ የተካተቱትን ጉዳዮች በጥልቀት<br />
ተወያይቶበቷል ሲል ምክር ቤቱ ጠቁሟል፡፡<br />
የተሻሻለው የፓርቲው ህገ-ደንብ እንደሚያስረዳው<br />
የፓርቲው ሊቀመንበር በጠቅላላ ጉባኤ የሚመረጥ ሲሆን፣<br />
ሊቀመንበሩ ሌሎች የስራ አስፈፃሚ አባላትን መልምሎ<br />
በዕጩነት ለብሔራዊ ምክር ቤት አቅርቦ ያፀድቃል፡<br />
፡ የፓርቲው መሪ መሆን የሚፈልጉና የተቀመጠውን<br />
መስፈርት የሚያሟሉ አባላት የጠቅላላ ጉባኤ አባላትን<br />
ድጋፍ እንዲያደርጉ በመቀስቀስ መወዳደር እንደሚችሉ<br />
ተገልጿል፡፡ በተመሳሳይም የስራ አስፈፃሚ አባለት ቁጥር<br />
ከ18 ወደ 11 እንዲወርድ ተደርጓል፡፡<br />
ብሔራዊ ምክር ቤቱም የፓርቲውን ጠቅላላ ጉባኤ<br />
በህዳር 30 እና ታህሳስ 01 ቀን 2004 ዓ.ም. እንዲካሄድ<br />
መወሰኑን ምክር ቤቱ በተለይም ለዝግጅት ክፍሉ<br />
ገልጿል፡፡<br />
www.andinet.org.et