ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless
ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless
ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless
Create successful ePaper yourself
Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.
2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />
ፖለቲካ<br />
ግርማ ሞገስ<br />
(girmamoges1@gmail.com)<br />
ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />
የዚህ ጽሑፍ ግብ የሰላም ትግል<br />
ለውጥ ማምጫ መንገዶች (Mechanisms<br />
of change) በኢትዮጵያ እንዴት ህዝብን<br />
የመንግስት ስልጣን ባለቤት ሊያደርጉ<br />
እንደሚችሉ በማጥናት በኢትዮጵያ የፖለቲካ<br />
ትግል እና የመንግስት ሽግግር ለማድረግ<br />
ሰላማዊ ትግል ማደረግ እንደሚቻል እና<br />
ተመራጩ የትግል ስልትም እሱ መሆኑን<br />
ማሳየት ነው።<br />
የሰላም ትግላችን ግብ ህዝብን የመንግስት<br />
ስልጣን ባለቤት ማድረግ ነው። ህዝብን<br />
የመንግስት ስልጣን ባለቤት ለማድረግ የሰላም<br />
ትግል በህዝብ እና በአምባገነን መንግስት<br />
መካከል የሚገኘውን የፖለቲካ ኃይል ሚዛን<br />
ግንኙነት ወደ ህዝብ እንዲያደላ ማድረግ<br />
አለበት። የሰላም ትግል ይኽን አስፈላጊ<br />
የሆነ የፖለቲካ ኃይል ሚዛን ግንኙነት<br />
ሽግሽግ (ለውጥ) ተፈጻሚ የሚያደርገው<br />
በአራት መንገዶች እንደሆነ ጅን ሻርፕ<br />
(Gene Sharp) አጥንቶ ለአለም የዲሞክራሲ<br />
ኃይሎች እና ተመራማሪዎች ካበረከተ<br />
ውሎ አድሯል። እነሱም፥ (1ኛ) የመቀየር/<br />
የመለወጥ (Peaceful conversion)፣ (2ኛ)<br />
የመቻቻል (accommodation)፣ (3ኛ)<br />
ሰላማዊ አስገዳጅነት (Peaceful coercion)<br />
እና (4ኛ) ሰላማዊ መፈረካከስ/መበታተን<br />
(Peaceful disintegration) የተባሉት<br />
ናቸው። እነዚህ ሰላማዊ ለውጥ ማምጫ<br />
መንገዶች ከሰላም ትግል መሳሪያዎች ጋር<br />
ዝምድና አላቸው። የሰላም ትግል መሳሪያዎች<br />
ሶስቱ አብይ ክፍሎች (1ኛ) ተቃውሞ እና<br />
ማግባባት (Protest and Persuasion)<br />
እስከዚኽ ድረስ እንዳየነው መቀየር/መለወጥ (Peaceful<br />
conversion) የተባለውን የለውጥ ማምጫ መንገድ ፕላን ቀይሰን<br />
በአግባብ እና በቀጣይነት ከተጠቀምንበት የዲሞክራሲ ትግልን በህብረተሰቡ ውስጥ<br />
ለማስፋፋት እና የህብረተሰቡን የሰላማዊ ትግል አቅምን ለመገንባት ይጠቅማል።<br />
ነገር ግን ይኽ ለውጥ የማምጫ ሰላማዊ መንገድ በአምባገነኖች የፖለቲካ ኃይል<br />
ምንጮች ላይ የሚያደርሰው ቀጥተኛ ጥቃት የለም። ጥቃቱ ተዘዋዋሪ ነው። ለጥቀን<br />
መቻቻል የተባለውን ለውጥ ማምጫ መንገድ እንመልከት።<br />
የሠላም ትግል ለውጥ ማምጫ አማራጭ<br />
መንገዶች በኢትዮጵያ<br />
፣ (2ኛ) ትብብር መንፈግ (noncooperation)<br />
፣ (3ኛ) ጣልቃ መግባት<br />
(intervention) እንደሆኑ እና ዝርዝራቸው<br />
ወደ 200 ግድም እንደሚደርስ በፍኖተ ነፃነት<br />
ቁጥር 13 “የሰላም ትግል መሳሪያዎች” በሚል<br />
ርዕስ ቀርቧል። እነዚኽ አራት ለውጥ ማምጫ<br />
መንገዶች ከሰላማዊ ትግል አቅም ግንባታ<br />
አንስቶ እስከ መንግስት ሽግግር ፍጻሜ ድረስ<br />
እንዴት አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉ ባጭር<br />
ባጭሩ እንመልከት።<br />
(1ኛ) መቀየር/መለወጥ (Peaceful<br />
conversion)<br />
የዲሞክራሲ ኃይሎች ያቀረቡትን የለውጥ<br />
አሳብ ወይንም የለውጥ ጥያቄ መንግስት<br />
ቢቀበል እሱም ተጠቃሚ ሊሆን እንደሚችል<br />
መንግስትን ማሳመን (መቀየር/መለወጥ)<br />
የሚቻልበት ሁኔታዎች (መንገዶች) ሊኖሩ<br />
ይችላሉ። ይኽን በማድረግ የዲሞክራሲ<br />
ኃይሎች ከሚያገኙዋቸው ፋይዳዎች ውስጥ<br />
ጥቂቱ፥ በህዝብ እና በመንግስት ዘንድ<br />
የተቃዋሚ መሪዎችን ህጋዊነት ከፍ ማድረግ፣<br />
ከመንግስት ጋር ሊደረጉ የሚችሉ ግጭቶችን<br />
መቀነስ፣ የሰላማዊ ትግልን የሰው እና የቁሳቁስ<br />
አቅም በረባ ባልረባው ሁሉ እንዳይባክን<br />
ማድረግ ናቸው።<br />
ርግጥ ይኽ መንገድ በመንግስት ላይ<br />
የሚያሳድረው ጫና (ክብደት) በጣም<br />
ዝቅተኛ በመሆኑ የሚያስገኘው ጠቀሜታ<br />
እዚህ ግባ የማይባል ሊሆን ይችላል።<br />
ያም ሆኖ ግን የተመረጠው የለውጥ ጥያቄ<br />
የአምባገነኖችን ስልጣን አደጋ ላይ የማይጥል<br />
እና የጥያቄው አቀራረብ ብልህ እስከሆነ<br />
ድረስ አልፎ አልፎም ቢሆን ጠቃሚ<br />
ውጤት አይገኝም ማለት ያስቸግራል።<br />
ለውጥ የተገኘበት ጊዜ አለ። ምሳሌ፥ እንደ<br />
አውሮፓ አቆጣጠር በ1962 ዓመተ ምህረት<br />
ቀድሞ የእንግሊዝ ቅኝ አገር በነበረችው<br />
በርማ ውስጥ በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን<br />
ላይ የወጣው ወታደራዊ አምባገነን ቡድን<br />
መጀመሪያ ከያዘው አቅዋም ከጊዜ በኋላ<br />
እንዴት እንደተለወጠ እንመልከት።<br />
ስልጣን እንደጨበጠ፣ የእንግሊዘኛ<br />
ቋንቋ ትምህርት በአንደኛ ደረጃ እንዳይሰጥ<br />
አደረገ። በዩንቨርስቲ ደረጃም የሚሰጥ<br />
የእንግሊዘኛ ቋንቋ ዝቅ እንዲል አደረገ።<br />
ወታደራዊው መንግስት ለህዝብ የሰጠው<br />
ሃሰተኛ ምክንያት “እንግሊዘኛ ቋንቋ የቅኝ<br />
ግዛት ዘመን ውርደታችን ማስታወሻ በመሆኑ<br />
መወገድ አለበት” የሚል ሲሆን ሃቀኛው<br />
ምክንያት ግን በመምህርነት ስራ የተሰማሩትን<br />
እና ኗሪ እንግሊዞችን ከአገር በማስወጣት<br />
የበርማን ህዝብ ከውጪው አለም ፖለቲካ<br />
ተጽእኖ ለማፈን (Censorship) ነበር። ይኽ<br />
ፖሊሲ የበርማ ተማሪዎችም ወደ ምዕራቡ<br />
አለም እንደቀድሞው እንደልብ እየወጡ<br />
ከፍተኛ ትምህርት ለመማር በቅድሚያ<br />
ማለፍ ያለባቸውን የእንግሊዘኛ ቋንቋ ፈተና<br />
ማለፍ እንዳይችሉ ማድረግ ጀመረ። በበርማ<br />
እንግሊዘኛ ቋንቋ መናገር የሚችሉ ተወላጅ<br />
የቢሮ አስተዳዳሪዎች ማግኘት አስቸጋሪ<br />
መሆን በመጀመሩ የውጭ አገር ኢንቨስተሮች<br />
ወደ በርማ መምጣት አቆሙ። የአገሪቱ<br />
ኢኮኖሚ ተንኮታኮተ። በዚኽ አይነት<br />
ለስልጣኑ መጠናከር ሲል ለ20 አመቶች<br />
ያህል አለም አቀፍ የቢዝነስ እና የንግድ<br />
ቋንቋ በበርማ እንዲዳከም ካደረገ በኋላ ይኽ<br />
ፖሊሲ በአገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ያስከተለው<br />
አሉታዊ ተጽእኖ ለአምባገነኖቹ ገዢዎች<br />
ወለል ብሎ ይታያቸው ጀመረ። የበርማ<br />
የንግዱ ማህበረሰብ እና የዲሞክራሲ ኃይሎች<br />
በእንግሊዘኛ ቋንቋ ትምህርት ላይ የተጣለው<br />
ገደብ እንዲነሳ ያቀርቡት የነበረውን የለውጥ<br />
ጥያቄ የበርማ አምባገነን መንግስት ተቀበለ።<br />
አምባገነኑ የበርማ መንግስት የለውጡን<br />
ጥያቄ የተቀበለው ለውጥ ቢያደርግ ተጠቃሚ<br />
መሆኑን በመገንዘቡ ነበር።<br />
የሰላም ትግል የመንግስት ባለስልጣኖችን<br />
ብቻ ሳይሆን ህዝብንም በመቀየር/በመለወጥ<br />
ለዲሞክራሲ ትግል መስፋፋት እና አቅም<br />
ግንባታ ጥቅም ይሰጣል። መንግስት በህዝብ<br />
ላይ የሚፈጽማቸው በደሎች፣ ዲሞክራሲ<br />
የሚሰጠው ጠቀሜታ እና ዛሬ በአለም ውስጥ<br />
እየተደረገ ስላለው የለውጥ እንቅስቃሴ<br />
እና ስለመሳሰሉት በሰፊው ማሰራጨት<br />
ህዝብ ለመለውጥ ያግዛል። በአለም ውስጥ<br />
ስለሚሆነው እና በአገር ስለሚፈጸም ሰላማዊ<br />
ሰልፎች፣ ተቃውሞዎች፣ ህዝባዊ ውይይቶች<br />
እና ተመሳሳይ የሰላማዊ ትግል ዜናዎች<br />
የህዝብን ዝንባሌ እንደሚቀይሩ እና ከፍራቻ<br />
ነፃ ለመውጣት እንደሚያግዙ መረሳት<br />
የለበትም። በዚህ ረገድ ድረ ገጾች፣ የህትምት<br />
እና የኤሌክትሮኒክ ሚዲያዎች ከፍተኛ<br />
ሚና አላቸው። ለዚህም ነው አምባገነኖች<br />
የሚያፍኗቸው።<br />
አምባገነኖች በሰላም ትግል ታጋዮች ላይ<br />
የሚፈጽሙት ግፍ እና የሰላም ትግል ታጋዮች<br />
የሚያሳዩት ጀግንነት ህዝብን በመለወጥ<br />
የዲሞክራሲ ትግሉን ያጠናክራል። በዚህ<br />
ረገድ በህዝብ ዘንድ ጀግንነት ተደርገው<br />
የሚወሰዱ ርምጃዎች ሌላውን የመለወጥ<br />
አቅም እንዳላቸውም መረሳት የለበትም።<br />
ምሳሌ፥ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር<br />
በ1950 ዎቹ እና 1960ዎቹ አፍሪካ<br />
አሜሪካውያን መንግስት በሚለቅባቸው<br />
ተናካሽ ውሻዎች መነከሳቸው፣ በእሳት አደጋ<br />
መኪናዎች በሚረጭ ውሃ መደብደባቸው፣<br />
ማታ ማታ በሰላም ትግል መሪዎች ቤቶች<br />
ላይ ይደርስ የነበረው ቃጠሎ፣ የሰላም<br />
ትግል ሰራዊት በሚሰበሰብባቸው ቤተ<br />
ክርስቲያኖች ላይ ይደርስ የነበረው ፈንጂ እና<br />
ቃጠሎ ሳይገታቸው በጀግንነት ለእኩለንት<br />
ያደረጉዋቸው ትግሎች ህዝባቸው ብቻ<br />
ሳይሆን ነጭ አሜሪካውያንን እና የቀረውን<br />
አለም ህዝብ በመለወጥ ከአፍሪካውያን<br />
አሜሪካውያን ጎን እንዲቆም አድርጓል።<br />
ሌላ ምሳሌ፥ ግብጾች መንግስት ሳያስፈቅዱ<br />
በነፃነት አደባባይ መስፈራቸው እና<br />
ነፃነታቸውን ማወጃቸው ብዙ ግብጻውያንን<br />
እንደለወጠ እና ሰላማዊ ትግሉን እንዲቀላቀሉ<br />
እንዳደረገ የምናውቀው ትኩስ ዜና ነው።<br />
እንዲሁም በድስፕሊን የታነጸ የሰላም<br />
ትግል ሰራዊት በአምባገነኖች እየተዋከበ፣<br />
ሳያስር እየታሰረ እና እየተገደለ፤ በጀግንነት<br />
ሰላማዊ ትግሉን በቀጣይነት ሲያኪያሂድ<br />
ሲያዩ የጨቋኙ መንግስት አባላት (የጦር<br />
መኮንኖች፣ ሚንስትሮች፣ ዲፕሎማቶች፣<br />
ወ.ዘ.ተ.) እንዲሁም የተባበሩት መንግስታት፣<br />
የምዕራቡ አለም መሪዎች፣ የመብት ተሟጋች<br />
ድርጅቶች ወ.ዘ.ተ. ሳይቀሩ እየተለወጡ<br />
ሰላማዊ ትግሉን ይቀላቀላሉ። ለምሳሌ<br />
የሊቢያው ጋዳፊ በሰላማዊ መንገድ አደባባይ<br />
ወጥቶ ነፃነቱን በጠየቀ ህዝብ ላይ አረመኒያዊ<br />
ጦርነት ሲያውጅ በጋዳፊ መንግስት ውስጥ<br />
በአገር ውስጥ የነበሩ ባለስልጣኖች እና<br />
ዲፕሎማቶች ሰላማዊ ትግሉን ተቀላቅለዋል።<br />
በየመንም አምባገነኑ የሳላህ መንግስት በሰንዓ<br />
(ለውጥ አደባባይ) እና በታኤዝ ከተሞች<br />
በሰፈረው ሰላማዊ ታጋይ ላይ ግድያ በፈጸመ<br />
ቁጥር ተመሳሳይ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል።<br />
እስከዚኽ ድረስ እንዳየነው መቀየር/<br />
መለወጥ (Peaceful conversion)<br />
የተባለውን የለውጥ ማምጫ መንገድ<br />
ፕላን ቀይሰን በአግባብ እና በቀጣይነት<br />
ከተጠቀምንበት የዲሞክራሲ ትግልን<br />
በህብረተሰቡ ውስጥ ለማስፋፋት እና<br />
የህብረተሰቡን የሰላማዊ ትግል አቅምን<br />
ለመገንባት ይጠቅማል። ነገር ግን ይኽ ለውጥ<br />
የማምጫ ሰላማዊ መንገድ በአምባገነኖች<br />
የፖለቲካ ኃይል ምንጮች ላይ የሚያደርሰው<br />
ቀጥተኛ ጥቃት የለም። ጥቃቱ ተዘዋዋሪ<br />
ነው። ለጥቀን መቻቻል የተባለውን ለውጥ<br />
ማምጫ መንገድ እንመልከት።<br />
(2ኛ) መቻቻል (Peaceful<br />
accommodation)<br />
አንዳንድ ጊዜ አምባገነናዊ መንግስቶች<br />
በዜጎች ዘንድ ላገር አሳቢ መስሎ ለመታየት፣<br />
በውጭ መንግስታት ዘንድ ተቀባይነት<br />
ለማግኘት ወይንም የገጠማቸውን የለውጥ<br />
ጥያቄ ውጥረት ለማርገብ ሲሉ የዲሞክራሲ<br />
ኃይሎችን ጥያቄዎች ይቀበላሉ። ይኽን<br />
የሚያደርጉት መብት አክባሪ እና ትሁት<br />
በመሆናቸው ሳይሆን ለተቃዋሚዎች የለውጥ<br />
ጥያቄ የመቻቻል መፍትሄ ብንሰጥ ስልጣናችን<br />
አይነጠቅም፣ አቅማችንም አይዳከምም ነገር<br />
ግን ከጭቅጭቅ እንድናለን ከሚል እምነት<br />
ነው። ይሁን እንጂ አንድ አምባገነን መንግስት<br />
መቻቻልን እንደመፍትሄ ከወሰደ በስልጣን<br />
ላይ የነበረው ፍጹም የሆነ ቁጥጥር ተቀንሷል<br />
ማለት ነው። በህዝብ እና በአምባገነኖች<br />
መካከል በነበረው የኃይል ሚዛን ግንኙነት<br />
ላይ የተወሰነ ሽግሽግ ተደርጓል ማለት ነው።<br />
ለምሳሌ የስራ ማቆም አድማዎችም ቆመው<br />
ሰራተኞች ወደ ስራ የሚመለሱት በአሰሪና<br />
በሰራተኞች መካከል በሚደረግ መቻቻል<br />
ነው።<br />
5<br />
በአገሮች መካከልም መቻቻል ይደረጋል።<br />
የቻይና መንግስት ጥቂት የፖለቲካ እስረኛ<br />
በመፍታት በምዕራቡ አለም የሚቀርብበትን<br />
የሰብዓዊ መብት ማሻሻል ጥያቄ ለማርገብ<br />
ሲሞክር እናያለን። ምዕራቡም ለጊዜው ዝም<br />
ይላል። በምዕራቡ እና በቻይና መንግስት<br />
መካከል መቻቻል ተደረገ ማለት ነው።<br />
የቻይና መንግስት ይኽን የሚያደርገው<br />
በምዕራቡ አለም ተገዶ (Coerced ሆኖ)<br />
ሳይሆን የቀረበው የመብት ጥያቄ ከምዕራቡ<br />
አለም ጋር ካለው የንግድ እና ሌሎች ጉዳዮች<br />
ጋር እየተወሳሰበ እንደልብ አላራምድ<br />
ስለሚለው ነው። ስለዚኽ ለምዕራቡ ጥያቄ<br />
የመቻቻል ምላሽ በመስጠት ንግዱን እና<br />
ሌሎች የሚጠቅሙትን ነገሮች ያደርጋል።<br />
ምርጫም መቻቻል ነው። በየአምስት<br />
ወይንም አራት አመቶች የሚደረግ ምርጫ<br />
ተቃዋሚ ፓርቲዎች ለሚያቀርቡት የፖለቲካ<br />
ለውጥ ጥያቄ አምባገነን መንግስቶች<br />
የሚሰጡት የመቻቻል መልስ ነው። ይሁን<br />
እንጂ ከተመክሮ ማነስ የተነሳ የተቃዋሚ<br />
ፓርቲ መሪዎች ምርጫው ነፃ እና ፍትሃዊ<br />
ይሆናል፣ ከምርጫው ጋር በተያያዘ<br />
መንግስት የሚፈጽመውን ወከባ ህዝቡ<br />
መቋቋም ይችላል ወይንም አለም አቀፍ<br />
ታዛቢዎች የምርጫውን ድምጽ ቆጠራ<br />
እንዳይሰረቅ ያደርጋሉ ብለው ይገምታሉ።<br />
ይኽ የዋህነት ነው። አምባገነኖች ነጻ ምርጫ<br />
ተደርጎ ስልጣናቸውን በፈቃዳቸው ይለቃሉ<br />
ብሎ መገመት ስህተት ነው። ሳይገደዱ<br />
በፈቃደኛነት ስልጣን ማስረከብ የአምባገነኖች<br />
ጸባይ አይደለም። አምባገነኖች ዲሞክራቶች<br />
አይደሉም። አምባገነኖች ስልጣን ላይ<br />
የሚወጡት በግድያ እና በሽብር ነው።<br />
በስልጣን ለመቆየትም መንግስታዊ ሽብር<br />
ይፈጽማሉ። ምርጫም ከሆነ የሚያግዳቸው<br />
ኃይል ከሌለ ድምጽ ይሰርቃሉ። እንደ<br />
አውሮፓ አቆጣጠር በ2000 ዓመተ ምህረት<br />
በሰርቢያ እና በ2002 ዓመተ ምህረት<br />
በዝንባቡዌ የተደረጉት ምርጫዎች በንፅፅር<br />
ማየት ይጠቅማል። ሁለቱም ምርጫዎች<br />
በስልጣን ላይ በነበሩት አምባገነኖች<br />
ተሰርቀው ነበር። ይሁን እንጂ በሰርቢያ<br />
የህዝብን ድምጽ ማስከበር ሲቻል በዝንባቡዌ<br />
ግን ያን ማድረግ ሳይቻል ቀርቷል። ስለዚኽ<br />
የሁለቱ ምርጫዎች የመጨረሻ ውጤት<br />
ሊለያይ ቻለ። እንመልከት።<br />
በሰርቢያ ተቃዋሚው በመላ አገሪቱ<br />
የምርጫ ታዛቢዎች አሰልጥኖ አሰማራ።<br />
ህዝቡ ንቅል ብሎ ወጥቶ ድምጹን እንዲሰጥ<br />
የሚያነሳሳ እና የሚቀሰቅስ የሰላማዊ የምርጫ<br />
ሰራዊት አሰልጥኖ በመላ አገሪቱ አዘመተ።<br />
መንግስት ድምጽ ቢሰርቅስ ብሎ ቀደም ብሎ<br />
በማሰብ ተቃዋሚው ድምጽ “ለማስከበር<br />
ፕላን ለ” (Plan B) አዘጋጅቶ ነበር። አንድ<br />
መንግስት የህዝብ ድምጽ አላከብርም ካለ<br />
ህዝቡም በበኩሉ ለመንግስት የለገሰውን<br />
የገዢነት ክብር እና ህጋዊነት የመንፈግ መብት<br />
አለው። ስለዚኽ “ፕላን ለ” (Plan B) ድምጽ<br />
ለማስከበር የሚደረግ የፖለቲካ እምቢታ፣<br />
ትብብር የመንፈግ እና የጣልቃ መግባት<br />
የሰላም ትግል መሳሪያዎችን የሚጠቀም<br />
ሰላማዊ ትግል ነው። በየምርጫ ጣቢያው<br />
የተመደቡ የተቃዋሚ ታዛቢዎች በድምጽ<br />
ቆጠራው ላይ በመሳተፍ ቆጠራው እንዳለቀ<br />
በዚያው ምሽት ውጤት በየጣቢያው ይፋ<br />
እንዲሆን አደረጉ። በመጨረሻ በሞሊሶቪች<br />
ይመራ የነበረው አምባገናንዊ መንግስት<br />
የምርጫው ውጤት እንደፈለገው ሳይሆን<br />
በመቅረቱ አይኑን በጨው አጥቦ አሸንፌያለሁ<br />
ቢልም በምርጫው እለት ምሽት በየምርጫ<br />
ጣቢያው ድምጽ ይፋ ተደርጎ ስለነበር ህዝቡ<br />
“ድምጽ ይከበር” አለው። ተቃዋሚው ቀደም<br />
ብሎ ያዘጋጀውን በሚሊዮኖች የሚቆጠር<br />
ወደ 13 ይዞሯል<br />
www.andinet.org.et