24.07.2013 Views

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

SHOW MORE
SHOW LESS

Create successful ePaper yourself

Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.

2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />

ፖለቲካ<br />

ግርማ ሞገስ<br />

(girmamoges1@gmail.com)<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

የዚህ ጽሑፍ ግብ የሰላም ትግል<br />

ለውጥ ማምጫ መንገዶች (Mechanisms<br />

of change) በኢትዮጵያ እንዴት ህዝብን<br />

የመንግስት ስልጣን ባለቤት ሊያደርጉ<br />

እንደሚችሉ በማጥናት በኢትዮጵያ የፖለቲካ<br />

ትግል እና የመንግስት ሽግግር ለማድረግ<br />

ሰላማዊ ትግል ማደረግ እንደሚቻል እና<br />

ተመራጩ የትግል ስልትም እሱ መሆኑን<br />

ማሳየት ነው።<br />

የሰላም ትግላችን ግብ ህዝብን የመንግስት<br />

ስልጣን ባለቤት ማድረግ ነው። ህዝብን<br />

የመንግስት ስልጣን ባለቤት ለማድረግ የሰላም<br />

ትግል በህዝብ እና በአምባገነን መንግስት<br />

መካከል የሚገኘውን የፖለቲካ ኃይል ሚዛን<br />

ግንኙነት ወደ ህዝብ እንዲያደላ ማድረግ<br />

አለበት። የሰላም ትግል ይኽን አስፈላጊ<br />

የሆነ የፖለቲካ ኃይል ሚዛን ግንኙነት<br />

ሽግሽግ (ለውጥ) ተፈጻሚ የሚያደርገው<br />

በአራት መንገዶች እንደሆነ ጅን ሻርፕ<br />

(Gene Sharp) አጥንቶ ለአለም የዲሞክራሲ<br />

ኃይሎች እና ተመራማሪዎች ካበረከተ<br />

ውሎ አድሯል። እነሱም፥ (1ኛ) የመቀየር/<br />

የመለወጥ (Peaceful conversion)፣ (2ኛ)<br />

የመቻቻል (accommodation)፣ (3ኛ)<br />

ሰላማዊ አስገዳጅነት (Peaceful coercion)<br />

እና (4ኛ) ሰላማዊ መፈረካከስ/መበታተን<br />

(Peaceful disintegration) የተባሉት<br />

ናቸው። እነዚህ ሰላማዊ ለውጥ ማምጫ<br />

መንገዶች ከሰላም ትግል መሳሪያዎች ጋር<br />

ዝምድና አላቸው። የሰላም ትግል መሳሪያዎች<br />

ሶስቱ አብይ ክፍሎች (1ኛ) ተቃውሞ እና<br />

ማግባባት (Protest and Persuasion)<br />

እስከዚኽ ድረስ እንዳየነው መቀየር/መለወጥ (Peaceful<br />

conversion) የተባለውን የለውጥ ማምጫ መንገድ ፕላን ቀይሰን<br />

በአግባብ እና በቀጣይነት ከተጠቀምንበት የዲሞክራሲ ትግልን በህብረተሰቡ ውስጥ<br />

ለማስፋፋት እና የህብረተሰቡን የሰላማዊ ትግል አቅምን ለመገንባት ይጠቅማል።<br />

ነገር ግን ይኽ ለውጥ የማምጫ ሰላማዊ መንገድ በአምባገነኖች የፖለቲካ ኃይል<br />

ምንጮች ላይ የሚያደርሰው ቀጥተኛ ጥቃት የለም። ጥቃቱ ተዘዋዋሪ ነው። ለጥቀን<br />

መቻቻል የተባለውን ለውጥ ማምጫ መንገድ እንመልከት።<br />

የሠላም ትግል ለውጥ ማምጫ አማራጭ<br />

መንገዶች በኢትዮጵያ<br />

፣ (2ኛ) ትብብር መንፈግ (noncooperation)<br />

፣ (3ኛ) ጣልቃ መግባት<br />

(intervention) እንደሆኑ እና ዝርዝራቸው<br />

ወደ 200 ግድም እንደሚደርስ በፍኖተ ነፃነት<br />

ቁጥር 13 “የሰላም ትግል መሳሪያዎች” በሚል<br />

ርዕስ ቀርቧል። እነዚኽ አራት ለውጥ ማምጫ<br />

መንገዶች ከሰላማዊ ትግል አቅም ግንባታ<br />

አንስቶ እስከ መንግስት ሽግግር ፍጻሜ ድረስ<br />

እንዴት አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉ ባጭር<br />

ባጭሩ እንመልከት።<br />

(1ኛ) መቀየር/መለወጥ (Peaceful<br />

conversion)<br />

የዲሞክራሲ ኃይሎች ያቀረቡትን የለውጥ<br />

አሳብ ወይንም የለውጥ ጥያቄ መንግስት<br />

ቢቀበል እሱም ተጠቃሚ ሊሆን እንደሚችል<br />

መንግስትን ማሳመን (መቀየር/መለወጥ)<br />

የሚቻልበት ሁኔታዎች (መንገዶች) ሊኖሩ<br />

ይችላሉ። ይኽን በማድረግ የዲሞክራሲ<br />

ኃይሎች ከሚያገኙዋቸው ፋይዳዎች ውስጥ<br />

ጥቂቱ፥ በህዝብ እና በመንግስት ዘንድ<br />

የተቃዋሚ መሪዎችን ህጋዊነት ከፍ ማድረግ፣<br />

ከመንግስት ጋር ሊደረጉ የሚችሉ ግጭቶችን<br />

መቀነስ፣ የሰላማዊ ትግልን የሰው እና የቁሳቁስ<br />

አቅም በረባ ባልረባው ሁሉ እንዳይባክን<br />

ማድረግ ናቸው።<br />

ርግጥ ይኽ መንገድ በመንግስት ላይ<br />

የሚያሳድረው ጫና (ክብደት) በጣም<br />

ዝቅተኛ በመሆኑ የሚያስገኘው ጠቀሜታ<br />

እዚህ ግባ የማይባል ሊሆን ይችላል።<br />

ያም ሆኖ ግን የተመረጠው የለውጥ ጥያቄ<br />

የአምባገነኖችን ስልጣን አደጋ ላይ የማይጥል<br />

እና የጥያቄው አቀራረብ ብልህ እስከሆነ<br />

ድረስ አልፎ አልፎም ቢሆን ጠቃሚ<br />

ውጤት አይገኝም ማለት ያስቸግራል።<br />

ለውጥ የተገኘበት ጊዜ አለ። ምሳሌ፥ እንደ<br />

አውሮፓ አቆጣጠር በ1962 ዓመተ ምህረት<br />

ቀድሞ የእንግሊዝ ቅኝ አገር በነበረችው<br />

በርማ ውስጥ በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን<br />

ላይ የወጣው ወታደራዊ አምባገነን ቡድን<br />

መጀመሪያ ከያዘው አቅዋም ከጊዜ በኋላ<br />

እንዴት እንደተለወጠ እንመልከት።<br />

ስልጣን እንደጨበጠ፣ የእንግሊዘኛ<br />

ቋንቋ ትምህርት በአንደኛ ደረጃ እንዳይሰጥ<br />

አደረገ። በዩንቨርስቲ ደረጃም የሚሰጥ<br />

የእንግሊዘኛ ቋንቋ ዝቅ እንዲል አደረገ።<br />

ወታደራዊው መንግስት ለህዝብ የሰጠው<br />

ሃሰተኛ ምክንያት “እንግሊዘኛ ቋንቋ የቅኝ<br />

ግዛት ዘመን ውርደታችን ማስታወሻ በመሆኑ<br />

መወገድ አለበት” የሚል ሲሆን ሃቀኛው<br />

ምክንያት ግን በመምህርነት ስራ የተሰማሩትን<br />

እና ኗሪ እንግሊዞችን ከአገር በማስወጣት<br />

የበርማን ህዝብ ከውጪው አለም ፖለቲካ<br />

ተጽእኖ ለማፈን (Censorship) ነበር። ይኽ<br />

ፖሊሲ የበርማ ተማሪዎችም ወደ ምዕራቡ<br />

አለም እንደቀድሞው እንደልብ እየወጡ<br />

ከፍተኛ ትምህርት ለመማር በቅድሚያ<br />

ማለፍ ያለባቸውን የእንግሊዘኛ ቋንቋ ፈተና<br />

ማለፍ እንዳይችሉ ማድረግ ጀመረ። በበርማ<br />

እንግሊዘኛ ቋንቋ መናገር የሚችሉ ተወላጅ<br />

የቢሮ አስተዳዳሪዎች ማግኘት አስቸጋሪ<br />

መሆን በመጀመሩ የውጭ አገር ኢንቨስተሮች<br />

ወደ በርማ መምጣት አቆሙ። የአገሪቱ<br />

ኢኮኖሚ ተንኮታኮተ። በዚኽ አይነት<br />

ለስልጣኑ መጠናከር ሲል ለ20 አመቶች<br />

ያህል አለም አቀፍ የቢዝነስ እና የንግድ<br />

ቋንቋ በበርማ እንዲዳከም ካደረገ በኋላ ይኽ<br />

ፖሊሲ በአገሪቱ ኢኮኖሚ ላይ ያስከተለው<br />

አሉታዊ ተጽእኖ ለአምባገነኖቹ ገዢዎች<br />

ወለል ብሎ ይታያቸው ጀመረ። የበርማ<br />

የንግዱ ማህበረሰብ እና የዲሞክራሲ ኃይሎች<br />

በእንግሊዘኛ ቋንቋ ትምህርት ላይ የተጣለው<br />

ገደብ እንዲነሳ ያቀርቡት የነበረውን የለውጥ<br />

ጥያቄ የበርማ አምባገነን መንግስት ተቀበለ።<br />

አምባገነኑ የበርማ መንግስት የለውጡን<br />

ጥያቄ የተቀበለው ለውጥ ቢያደርግ ተጠቃሚ<br />

መሆኑን በመገንዘቡ ነበር።<br />

የሰላም ትግል የመንግስት ባለስልጣኖችን<br />

ብቻ ሳይሆን ህዝብንም በመቀየር/በመለወጥ<br />

ለዲሞክራሲ ትግል መስፋፋት እና አቅም<br />

ግንባታ ጥቅም ይሰጣል። መንግስት በህዝብ<br />

ላይ የሚፈጽማቸው በደሎች፣ ዲሞክራሲ<br />

የሚሰጠው ጠቀሜታ እና ዛሬ በአለም ውስጥ<br />

እየተደረገ ስላለው የለውጥ እንቅስቃሴ<br />

እና ስለመሳሰሉት በሰፊው ማሰራጨት<br />

ህዝብ ለመለውጥ ያግዛል። በአለም ውስጥ<br />

ስለሚሆነው እና በአገር ስለሚፈጸም ሰላማዊ<br />

ሰልፎች፣ ተቃውሞዎች፣ ህዝባዊ ውይይቶች<br />

እና ተመሳሳይ የሰላማዊ ትግል ዜናዎች<br />

የህዝብን ዝንባሌ እንደሚቀይሩ እና ከፍራቻ<br />

ነፃ ለመውጣት እንደሚያግዙ መረሳት<br />

የለበትም። በዚህ ረገድ ድረ ገጾች፣ የህትምት<br />

እና የኤሌክትሮኒክ ሚዲያዎች ከፍተኛ<br />

ሚና አላቸው። ለዚህም ነው አምባገነኖች<br />

የሚያፍኗቸው።<br />

አምባገነኖች በሰላም ትግል ታጋዮች ላይ<br />

የሚፈጽሙት ግፍ እና የሰላም ትግል ታጋዮች<br />

የሚያሳዩት ጀግንነት ህዝብን በመለወጥ<br />

የዲሞክራሲ ትግሉን ያጠናክራል። በዚህ<br />

ረገድ በህዝብ ዘንድ ጀግንነት ተደርገው<br />

የሚወሰዱ ርምጃዎች ሌላውን የመለወጥ<br />

አቅም እንዳላቸውም መረሳት የለበትም።<br />

ምሳሌ፥ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር<br />

በ1950 ዎቹ እና 1960ዎቹ አፍሪካ<br />

አሜሪካውያን መንግስት በሚለቅባቸው<br />

ተናካሽ ውሻዎች መነከሳቸው፣ በእሳት አደጋ<br />

መኪናዎች በሚረጭ ውሃ መደብደባቸው፣<br />

ማታ ማታ በሰላም ትግል መሪዎች ቤቶች<br />

ላይ ይደርስ የነበረው ቃጠሎ፣ የሰላም<br />

ትግል ሰራዊት በሚሰበሰብባቸው ቤተ<br />

ክርስቲያኖች ላይ ይደርስ የነበረው ፈንጂ እና<br />

ቃጠሎ ሳይገታቸው በጀግንነት ለእኩለንት<br />

ያደረጉዋቸው ትግሎች ህዝባቸው ብቻ<br />

ሳይሆን ነጭ አሜሪካውያንን እና የቀረውን<br />

አለም ህዝብ በመለወጥ ከአፍሪካውያን<br />

አሜሪካውያን ጎን እንዲቆም አድርጓል።<br />

ሌላ ምሳሌ፥ ግብጾች መንግስት ሳያስፈቅዱ<br />

በነፃነት አደባባይ መስፈራቸው እና<br />

ነፃነታቸውን ማወጃቸው ብዙ ግብጻውያንን<br />

እንደለወጠ እና ሰላማዊ ትግሉን እንዲቀላቀሉ<br />

እንዳደረገ የምናውቀው ትኩስ ዜና ነው።<br />

እንዲሁም በድስፕሊን የታነጸ የሰላም<br />

ትግል ሰራዊት በአምባገነኖች እየተዋከበ፣<br />

ሳያስር እየታሰረ እና እየተገደለ፤ በጀግንነት<br />

ሰላማዊ ትግሉን በቀጣይነት ሲያኪያሂድ<br />

ሲያዩ የጨቋኙ መንግስት አባላት (የጦር<br />

መኮንኖች፣ ሚንስትሮች፣ ዲፕሎማቶች፣<br />

ወ.ዘ.ተ.) እንዲሁም የተባበሩት መንግስታት፣<br />

የምዕራቡ አለም መሪዎች፣ የመብት ተሟጋች<br />

ድርጅቶች ወ.ዘ.ተ. ሳይቀሩ እየተለወጡ<br />

ሰላማዊ ትግሉን ይቀላቀላሉ። ለምሳሌ<br />

የሊቢያው ጋዳፊ በሰላማዊ መንገድ አደባባይ<br />

ወጥቶ ነፃነቱን በጠየቀ ህዝብ ላይ አረመኒያዊ<br />

ጦርነት ሲያውጅ በጋዳፊ መንግስት ውስጥ<br />

በአገር ውስጥ የነበሩ ባለስልጣኖች እና<br />

ዲፕሎማቶች ሰላማዊ ትግሉን ተቀላቅለዋል።<br />

በየመንም አምባገነኑ የሳላህ መንግስት በሰንዓ<br />

(ለውጥ አደባባይ) እና በታኤዝ ከተሞች<br />

በሰፈረው ሰላማዊ ታጋይ ላይ ግድያ በፈጸመ<br />

ቁጥር ተመሳሳይ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል።<br />

እስከዚኽ ድረስ እንዳየነው መቀየር/<br />

መለወጥ (Peaceful conversion)<br />

የተባለውን የለውጥ ማምጫ መንገድ<br />

ፕላን ቀይሰን በአግባብ እና በቀጣይነት<br />

ከተጠቀምንበት የዲሞክራሲ ትግልን<br />

በህብረተሰቡ ውስጥ ለማስፋፋት እና<br />

የህብረተሰቡን የሰላማዊ ትግል አቅምን<br />

ለመገንባት ይጠቅማል። ነገር ግን ይኽ ለውጥ<br />

የማምጫ ሰላማዊ መንገድ በአምባገነኖች<br />

የፖለቲካ ኃይል ምንጮች ላይ የሚያደርሰው<br />

ቀጥተኛ ጥቃት የለም። ጥቃቱ ተዘዋዋሪ<br />

ነው። ለጥቀን መቻቻል የተባለውን ለውጥ<br />

ማምጫ መንገድ እንመልከት።<br />

(2ኛ) መቻቻል (Peaceful<br />

accommodation)<br />

አንዳንድ ጊዜ አምባገነናዊ መንግስቶች<br />

በዜጎች ዘንድ ላገር አሳቢ መስሎ ለመታየት፣<br />

በውጭ መንግስታት ዘንድ ተቀባይነት<br />

ለማግኘት ወይንም የገጠማቸውን የለውጥ<br />

ጥያቄ ውጥረት ለማርገብ ሲሉ የዲሞክራሲ<br />

ኃይሎችን ጥያቄዎች ይቀበላሉ። ይኽን<br />

የሚያደርጉት መብት አክባሪ እና ትሁት<br />

በመሆናቸው ሳይሆን ለተቃዋሚዎች የለውጥ<br />

ጥያቄ የመቻቻል መፍትሄ ብንሰጥ ስልጣናችን<br />

አይነጠቅም፣ አቅማችንም አይዳከምም ነገር<br />

ግን ከጭቅጭቅ እንድናለን ከሚል እምነት<br />

ነው። ይሁን እንጂ አንድ አምባገነን መንግስት<br />

መቻቻልን እንደመፍትሄ ከወሰደ በስልጣን<br />

ላይ የነበረው ፍጹም የሆነ ቁጥጥር ተቀንሷል<br />

ማለት ነው። በህዝብ እና በአምባገነኖች<br />

መካከል በነበረው የኃይል ሚዛን ግንኙነት<br />

ላይ የተወሰነ ሽግሽግ ተደርጓል ማለት ነው።<br />

ለምሳሌ የስራ ማቆም አድማዎችም ቆመው<br />

ሰራተኞች ወደ ስራ የሚመለሱት በአሰሪና<br />

በሰራተኞች መካከል በሚደረግ መቻቻል<br />

ነው።<br />

5<br />

በአገሮች መካከልም መቻቻል ይደረጋል።<br />

የቻይና መንግስት ጥቂት የፖለቲካ እስረኛ<br />

በመፍታት በምዕራቡ አለም የሚቀርብበትን<br />

የሰብዓዊ መብት ማሻሻል ጥያቄ ለማርገብ<br />

ሲሞክር እናያለን። ምዕራቡም ለጊዜው ዝም<br />

ይላል። በምዕራቡ እና በቻይና መንግስት<br />

መካከል መቻቻል ተደረገ ማለት ነው።<br />

የቻይና መንግስት ይኽን የሚያደርገው<br />

በምዕራቡ አለም ተገዶ (Coerced ሆኖ)<br />

ሳይሆን የቀረበው የመብት ጥያቄ ከምዕራቡ<br />

አለም ጋር ካለው የንግድ እና ሌሎች ጉዳዮች<br />

ጋር እየተወሳሰበ እንደልብ አላራምድ<br />

ስለሚለው ነው። ስለዚኽ ለምዕራቡ ጥያቄ<br />

የመቻቻል ምላሽ በመስጠት ንግዱን እና<br />

ሌሎች የሚጠቅሙትን ነገሮች ያደርጋል።<br />

ምርጫም መቻቻል ነው። በየአምስት<br />

ወይንም አራት አመቶች የሚደረግ ምርጫ<br />

ተቃዋሚ ፓርቲዎች ለሚያቀርቡት የፖለቲካ<br />

ለውጥ ጥያቄ አምባገነን መንግስቶች<br />

የሚሰጡት የመቻቻል መልስ ነው። ይሁን<br />

እንጂ ከተመክሮ ማነስ የተነሳ የተቃዋሚ<br />

ፓርቲ መሪዎች ምርጫው ነፃ እና ፍትሃዊ<br />

ይሆናል፣ ከምርጫው ጋር በተያያዘ<br />

መንግስት የሚፈጽመውን ወከባ ህዝቡ<br />

መቋቋም ይችላል ወይንም አለም አቀፍ<br />

ታዛቢዎች የምርጫውን ድምጽ ቆጠራ<br />

እንዳይሰረቅ ያደርጋሉ ብለው ይገምታሉ።<br />

ይኽ የዋህነት ነው። አምባገነኖች ነጻ ምርጫ<br />

ተደርጎ ስልጣናቸውን በፈቃዳቸው ይለቃሉ<br />

ብሎ መገመት ስህተት ነው። ሳይገደዱ<br />

በፈቃደኛነት ስልጣን ማስረከብ የአምባገነኖች<br />

ጸባይ አይደለም። አምባገነኖች ዲሞክራቶች<br />

አይደሉም። አምባገነኖች ስልጣን ላይ<br />

የሚወጡት በግድያ እና በሽብር ነው።<br />

በስልጣን ለመቆየትም መንግስታዊ ሽብር<br />

ይፈጽማሉ። ምርጫም ከሆነ የሚያግዳቸው<br />

ኃይል ከሌለ ድምጽ ይሰርቃሉ። እንደ<br />

አውሮፓ አቆጣጠር በ2000 ዓመተ ምህረት<br />

በሰርቢያ እና በ2002 ዓመተ ምህረት<br />

በዝንባቡዌ የተደረጉት ምርጫዎች በንፅፅር<br />

ማየት ይጠቅማል። ሁለቱም ምርጫዎች<br />

በስልጣን ላይ በነበሩት አምባገነኖች<br />

ተሰርቀው ነበር። ይሁን እንጂ በሰርቢያ<br />

የህዝብን ድምጽ ማስከበር ሲቻል በዝንባቡዌ<br />

ግን ያን ማድረግ ሳይቻል ቀርቷል። ስለዚኽ<br />

የሁለቱ ምርጫዎች የመጨረሻ ውጤት<br />

ሊለያይ ቻለ። እንመልከት።<br />

በሰርቢያ ተቃዋሚው በመላ አገሪቱ<br />

የምርጫ ታዛቢዎች አሰልጥኖ አሰማራ።<br />

ህዝቡ ንቅል ብሎ ወጥቶ ድምጹን እንዲሰጥ<br />

የሚያነሳሳ እና የሚቀሰቅስ የሰላማዊ የምርጫ<br />

ሰራዊት አሰልጥኖ በመላ አገሪቱ አዘመተ።<br />

መንግስት ድምጽ ቢሰርቅስ ብሎ ቀደም ብሎ<br />

በማሰብ ተቃዋሚው ድምጽ “ለማስከበር<br />

ፕላን ለ” (Plan B) አዘጋጅቶ ነበር። አንድ<br />

መንግስት የህዝብ ድምጽ አላከብርም ካለ<br />

ህዝቡም በበኩሉ ለመንግስት የለገሰውን<br />

የገዢነት ክብር እና ህጋዊነት የመንፈግ መብት<br />

አለው። ስለዚኽ “ፕላን ለ” (Plan B) ድምጽ<br />

ለማስከበር የሚደረግ የፖለቲካ እምቢታ፣<br />

ትብብር የመንፈግ እና የጣልቃ መግባት<br />

የሰላም ትግል መሳሪያዎችን የሚጠቀም<br />

ሰላማዊ ትግል ነው። በየምርጫ ጣቢያው<br />

የተመደቡ የተቃዋሚ ታዛቢዎች በድምጽ<br />

ቆጠራው ላይ በመሳተፍ ቆጠራው እንዳለቀ<br />

በዚያው ምሽት ውጤት በየጣቢያው ይፋ<br />

እንዲሆን አደረጉ። በመጨረሻ በሞሊሶቪች<br />

ይመራ የነበረው አምባገናንዊ መንግስት<br />

የምርጫው ውጤት እንደፈለገው ሳይሆን<br />

በመቅረቱ አይኑን በጨው አጥቦ አሸንፌያለሁ<br />

ቢልም በምርጫው እለት ምሽት በየምርጫ<br />

ጣቢያው ድምጽ ይፋ ተደርጎ ስለነበር ህዝቡ<br />

“ድምጽ ይከበር” አለው። ተቃዋሚው ቀደም<br />

ብሎ ያዘጋጀውን በሚሊዮኖች የሚቆጠር<br />

ወደ 13 ይዞሯል<br />

www.andinet.org.et

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!