24.07.2013 Views

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

SHOW MORE
SHOW LESS

You also want an ePaper? Increase the reach of your titles

YUMPU automatically turns print PDFs into web optimized ePapers that Google loves.

2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />

ዳሰሳ<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

እንጂ ተንቀሳቃሽ ወይም በሃገር ኢኮኖሚ<br />

ውስጥ ተዘዋውሮ ተነግዶበት ለትርፍ<br />

የሚያበቃ አይደለም። በሌላ በኩል ይህ<br />

የተወሰነው የሙስና ተሳታፊ የህብረተሰብ<br />

ከፍል ብዙውን ጊዜ በውድ ቁሳቁሶችና<br />

ጌጣጌጦች በማሸብረቅ ፉክክር ተጠምዶ<br />

ስለሚቀር ለአጓጉል ባህል መጸነስ <strong>ምንጭ</strong><br />

መሆንም ይንጸባረቅበታል።<br />

በርከት ያሉ ጥናቶች<br />

እንዳመለከቱትም ቀልጣፋ ያልሆኑትንና<br />

ውጤታማ ያልሆኑትን (inefficient)<br />

ድርጅቶችን፤ አምራቾችንና ግለሰቦችን<br />

የበላይነት እንዲኖራቸው በማድረግ አገር<br />

ወደ ኋላ እንድትጎተት ያደርጋል።<br />

ሙስና የሕብረተሰብን ንብረት<br />

ወስዶ ለግለሰቦች ያስረክባል። ይህንን<br />

በማድረግም ከሁሉም ይበልጥ የድሀውን<br />

የህብረተሰብ ክፍል በበለጠ ይጎዳል።<br />

ከመንግስት ባለስልጣኖች ጋር ግንኙነት<br />

ያላቸው በሙስና የተዘፈቁት ግለሰቦች<br />

የሕዝቡን ሀብት ለግላቸው ሲያውሉት<br />

የትምህርት ቤት ተቋማትን ለማቋቋም፤<br />

የጤና ጥበቃ ጣቢያዎችን ለመመስረት፤<br />

ለአዉራ ጎዳናና መንገድ ሥራው ሥራዎች፤<br />

ለዉሃ ልማቶች፤ ወ.ዘ.ተ. ሊዉል የሚገባው<br />

ሀብት እንዲባክን ያደርጋል።<br />

ሙስና ከዉጭ አገር<br />

የሚገኘውን እርዳታ ውጤተ-ቢስ<br />

እንዲሆንና እንዲባክን ያደርጋል። ምንም<br />

እንኳ እርዳታው የሚላከው ለድሆች<br />

እንዲደርስ ቢሆንም፤ እርዳታው ለድሆች<br />

እንዳይደርስ፤ በርዳታው ገንዘብ እንዲሰሩ<br />

የተፈለጉት ተቋሞች እንዳይሰሩ ወይም<br />

ብልሹ በሆነ መልክ እንዲሰሩ ያደርጋል።<br />

እኔ እራሴ እንደተገነዘብኩትም፤ በገባያ ላይ<br />

እንዳይሸጡ የተከለከሉ የርዳታ እቃዎች<br />

ሕገ-ወጥ በሆነ መልክ እንዲሸጡ ያደርጋል።<br />

ለዚህ ዋቢም ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ<br />

የሚላከውን የምግብ ዘይት መጥቀስ<br />

ይበቃል።<br />

ፖለቲካንና መንግስታዊ አስተዳደርን<br />

በሚመለከት (በከፊል)፤<br />

ሙስና እየገነነ ሲመጣ በሃገር<br />

ዕድገት መስክ ጉልህ ሚና የሌላቸው በጣም<br />

ጥቂቶች እየከበሩ ይመጡና የመንግስትና<br />

የሕዝብ መገልገያ በሆኑ መሥሪያ ቤቶች<br />

በመስራት ብዙ ልምድ ያካበቱና ታማኝ<br />

የሆኑ፤ እንዲሁም ብቃት ያላቸው<br />

የቢሮ ሰራቶኞችን ሥራቸውን ለቀው<br />

እንዲወጡና ቀስ በቀስ ብቃት የሌላቸው<br />

በቦታው እንዲተኩ በር ይከፍታል።<br />

ይህም በሕዝብ መሥሪያ ቤቶች ውስጥ<br />

መልካም ባህርይና ችሎታ ያላቸው መሪዎች<br />

እንዳይበቅሉ ያደርጋል፤ የሃገርን የብቁ ዜጋ<br />

ቋት ያራቁታል። መድረሻ የለንም የሚሉ<br />

ቢኖሩም፡፡<br />

ሙስና ላገራቸውና<br />

ለህዝባቸው ተግተው የሚሰሩ ዜጎችንና<br />

ከፍተኛ የሙያ ትምህርት የቀሰሙ<br />

ሊሂቃንን ለሀገራቸው የሚያደርጉትን<br />

የአገልግሎት ፍላጎት የሚቀንስ ነው።<br />

ሙስናው እየበረታ ሲሄድም የመንግስት<br />

ሥራን እየለቀቁ፤ ለትምህርታቸው<br />

የከፈለላችውን ህዝብ እንደማገልገል<br />

ፋንታ፤የግል ባለህብቶችን/ኩባንያዎችን<br />

ለማገልገል ወይም የራሳቸውን የግል ንግድ<br />

እንዲፈጥሩ ይገፋፋል፤ያስገዳዳልም።<br />

ብዙዎች ባልሰለጠኑበት ሙያ እንዲሰማሩ<br />

እንደሚያስገድድም በብዙ አገሮች ውስጥ<br />

ታይቷል። በኢትዮጵያም እንደዚሁ ባስከፊ<br />

ሁኔታ እየተከሰተ ነው። እያደር ተስፋቸው<br />

እየተሟጠጠ አገራቸውን ጥለው እንዲሄዱ/<br />

እንዲሸሹ የሚገፉ ብዙዎች ለመሆናቸውም<br />

ጥርጥር የለውም። ይህ እየበረከተ ሲሄድ<br />

ደግሞ አገር ምሁር አልባ፤ አዕምሮ አልባ<br />

ትሆናለች። ብዙ ሃብት ጠፍቶ የሰለጠኑ<br />

ምሁራን ለሀብታም አገሮች ሲሳይ (braindrain)<br />

ይሆናሉ። ድሃ አገሮች ደክመውና<br />

ከፍለው ያሰለጠኑት አዕምሮ እየሸሻቸው፤<br />

ያሳደጉትን መሳም ያልቻሉ ደካሞች ሆነው<br />

እንዲታዩም ምክንያት ይሆናል። በአፍሪካ<br />

አህጉር ኢትዮጵያና ጋና በዚህ ረገድ ቀዳሚ<br />

ተጠቃሽ ናቸው። ቀጥተኛ የሆነ የፖለቲካ<br />

ችግር ተጨምሮበት አገራችን ዛሬ ማቆሚያ<br />

በሌለው መልክ የሰለጠነ የአእምሮ ሃብቷ<br />

እየተራቆተ ነው።<br />

በሌላ በኩል በሙስና ምክንያት<br />

ችሎታና ብቃት ያላቸው ባለሙያዎች<br />

ከመንግስታዊ መዋቅሮች ሲለቁ ቦታው ብቁ<br />

ችሎታ በሌላቸው ሰዎች እንዲሞላ ግድ<br />

ይሆናል። ይህም እየቆየ የመንግስት መሥሪያ<br />

ቤቶች እንዲጠሉ ያደርግና ቀስ በቀስ<br />

የመንግስት ትእዛዞች እንዳይከብሩ፤ ብሎም<br />

መንግስት ራሱ እንዲጠላ የራሱን አሉታዊ<br />

ሚና ይጫወታል። በህዝብ የሚጠላ<br />

መንግስት ደግሞ ሕዝባዊ ችግሮችን ሊፈታ<br />

የሚችል አይሆንም።<br />

በሙስና ምክንያት ሌብነት<br />

በዝቶ ድህነት ሲስፋፋ እያደር ዴሞክራሲም<br />

ደብዛው ይጠፋል። ዴሞክራሲ ሲጠፋም<br />

በኤኮኖሚ የማደግ እድል ይቀንሳል፣<br />

በሌላ በኩል በሙስና ምክንያት ችሎታና ብቃት ያላቸው<br />

ባለሙያዎች ከመንግስታዊ መዋቅሮች ሲለቁ ቦታው ብቁ ችሎታ<br />

በሌላቸው ሰዎች እንዲሞላ ግድ ይሆናል። ይህም እየቆየ የመንግስት<br />

መሥሪያ ቤቶች እንዲጠሉ ያደርግና ቀስ በቀስ የመንግስት ትእዛዞች<br />

እንዳይከብሩ፤ ብሎም መንግስት ራሱ እንዲጠላ የራሱን አሉታዊ<br />

ሚና ይጫወታል። በህዝብ የሚጠላ መንግስት ደግሞ ሕዝባዊ<br />

ችግሮችን ሊፈታ የሚችል አይሆንም።<br />

ድህነትንም ያንሰራፋል። የሰብዓዊና<br />

ሌሎችም ዴሞክራሲዊ መብቶች መታጣት<br />

በበኩሉ ለእርስ በርስ ጥልና ንክሻ<br />

ምክንያት ይሆናል። ይህ የሚንጸባረቅበት<br />

ህብረተሰብ ችግርና መከራ እንደ አዙሪት<br />

እየተሽከረከሩበት (vicious circle)<br />

ለመኖር ይገደዳል። ካዙሪቱም መውጣት<br />

አስቸጋሪ ይሆናል።<br />

ሙስና ሲስፋፋ በሥልጣን<br />

ላይ ያሉ ግለሰቦች በሙስናው ይሰክሩና<br />

ያጋልጡናል ብለው የሚፈሯቸውን<br />

ለምሳሌ እንደ ነፃ ፕሬስና ሌሎችም<br />

የሕዝብ መገናኛ ዘዴዎች ባለሙያዎችን<br />

እንዲሁም ንቁ የህብረተሰብ ክፍሎችን<br />

ማፈንና ማሳደድን ስራዬ ብለው ይይዛሉ።<br />

አፋኝ የሆኑ አዳዲስ ሕጎችን እያወጡ ነጻ<br />

አሰራሮችን ያግዳሉ፤ ጋዜጠኞችን ያስራሉ፤<br />

ያሰቃያሉ፤ ያዋክባሉ። በዚህም የተነሳ ነጻው<br />

ፕሬስና የሕዝብ መገናኛው መድረክ ሁሉ<br />

እያደር እየተዳከመ የተልፈሰፈሰ ይሆናል።<br />

ተልፈስፋሽ እንዲሆንም ፍላጎታቸውም፤<br />

ተግባራቸውም ነው። ይኸው ድርጊት<br />

ጠቅላላው ሕብረተሰብ እንዳያውቅ<br />

እንዳይማርና እንዳይጠይቅ ሆኖ የሰጡትን<br />

ብቻ ተቀባይና መስማት የተሳነው እንዲሆን<br />

ያደርጋል። በኢትዮጵያችን ይህ እየሆነ ያለ<br />

ክስተት ይሁን እንጂ ህዝቡ ይባስ ብሎ<br />

ከመንግሥት ለሚተላለፉ መመሪያዎችም<br />

ሆነ ዜናዎች ጆሮ ዳባ ልበስ ካለ ዓመታት<br />

ተቆጥረዋል። ይልቁንም ዕውነትን<br />

ፍለጋ በውጭ መገናኛ ብዙሃን ዘርፎች<br />

ለመጠቀም ተገዷል። ሕዝቡ መንግሥት<br />

ተብዬው ለሚያወጣቸው መመሪያዎች<br />

ቁብ የለውም፤ እንዲለግም የተገደደበት<br />

ሁኔታ ነው የሚታየው። በዚህ ዓይነትም<br />

ፖሊሲዎች በወረቀት ላይ ብቻ ይሆናሉ።<br />

ሕዝብና መንግስትም ሆድና ጀርባ እንደሆኑ<br />

ይቀራሉ።<br />

ማህበረሰባዊ ኑሮን በሚመለከት<br />

(በከፊል)፤<br />

ተደጋግሞ እንደተገለጸው<br />

ሙስና እጅጉን ሲስፋፋ በመንግስት<br />

መዋቅሮች ውስጥ የሚሰሩ በተለይም<br />

በንቃት ሃገራቸውን ሊያገለግሉ የተዘጋጁና<br />

ለስልጠናቸው ብዙ የተደከመባቸው<br />

ወገኖች አእምሯቸው እንዲላሽቅ<br />

ይደረጋል።<br />

ሙስና በትምህርት፤ በሥራ<br />

ልምድና በታታሪነት ኑሮን ከማዳበር<br />

ይልቅ፤ በጓዳና ባቋራጭ መንገድ የመክበር<br />

ፍላጎትንና፡ ስግብግብነትን የሚያበረታታ<br />

ስለሆነ ተጎጂው ሁሌም ንቁና ሀገሩን ወዳዱ<br />

ክፍል ነው። ሙስና ሁሉም ሊከብርና<br />

ኑሮውን ሊያቃና የሚችልበት ሳይሆን<br />

ጥቂቶች ያላግባብ የሚበለጽጉበት በመሆኑ<br />

“እድሉ” ያላጋጠመው አብዛኛው ሁሌም<br />

ብስጭት ላይ ይወድቃል። ኑሮውን<br />

ያማርራል፤ ተስፋ የቆረጠ የህብረተሰብ<br />

አባልን ያበረክታል። ተስፋ በቆረጠ ዜጋ<br />

ሀገር ሊያድግ ከቶውንም አይችልም።<br />

ሙስና በተለይ ድሆችን ጎጂ<br />

ነው፤ ድሆች እንኳን ጉቦ የሚከፍሉት<br />

ሊኖራቸው ቀርቶ ለራሳቸውም የሚበቃ<br />

ሃብት የላቸውምና!<br />

በሃይማኖት በኩልም ቢሆን፤<br />

ሙስና ከኃጢዓት (መቅሰፍት) የሚቆጠር<br />

እንጂ የሚያበረታታ አይደለም። በጉቦ<br />

የተለከፈ ሕብረተሰብ ብርቱ ሞራልና<br />

የወደፊት የረጅም ጊዜ የኑሮ ዕቅድ<br />

የለውም፤የዛሬን የከብሮ ማደር ብቻ ቀዳሚ<br />

ዓላማው ነውና። በሙስና የተጠመዱ ሰዎች<br />

አእምሯቸው ሁሌም የተረበሸና በጥቅም<br />

የተበረዘ በመሆኑ ቀስ በቀስ እንደተላላፊ<br />

በሽታ ሌሎቹንም የሚበክሉ ናቸው።<br />

ለዚህም ነው ሙስና እኩይ ወጥመድ<br />

ነው የሚባለው። በሙስና የተለከፉ ዜጎች<br />

ርህራሄ የጎደላቸውና ከምንም በላይ<br />

ጥቅማቸውን የሚያስቀድሙ በመሆናቸው<br />

የጋራ ሃገር ዕድገት እንቅፋቶች ናቸው።<br />

በሙስና የተጠመዱ ሰዎች ሁሉንም<br />

ለማግበስበስ በሚያደርጉት ሩጫ በተለይ<br />

ድሃው የህበረተሰብ ክፍል በመንግስት<br />

የዕለት ተዕለት አገልግሎቶች እንኳ ሳይቀር<br />

ተጠቃሚ እንዳይሆን የሚያደርጉ ጨካኞች<br />

ናቸው። ሙስና ራሱ ሃጢዓተኛ ነው<br />

የሚባለውም ለዚህ ነው።<br />

ሙስና የህብረተሰብ የእድገት<br />

መስኮችን ሁሉ ገቺና ወደፊት የማያራምድ<br />

ማነቆ ነው። ዕድገትን ሳይሆን ዝቅጠትን<br />

የሚያስከትል አደገኛ የህዝብና የሃገር ነቀርሳ<br />

ነው።<br />

ሙስና ወንጀለኞችን<br />

ያበራክታል፤ ብዙ ጊዜም ድሃ ዜጎች<br />

በሕይወታቸው ደስተኝነትን በማጣት<br />

ሳቢያ ህይወታቸውን እንዲያጠፉ ጭምር<br />

የሚገፋፋ ነው።<br />

3<br />

ሙስና በሰፈነበት አገር<br />

የኢኮኖምም፤ የፖለቲካም የማህበራዊ<br />

ኑሮም አዳዲስ ግኝቶችና ሀሳቦች ማፍለቅ<br />

የሚበረታታበት መድረክ ጎልቶ አይታይም።<br />

ስለሆነም ሙስና የማህበረሰባዊ ዕድገት<br />

ጠንቅ ነው።<br />

ሐ) መደምደሚያና ማጠቃለያ፤<br />

ዉድ ወገኖች፤ ሙስና የአንዲት<br />

አገር ኤኮኖሚን አቆርቋዥ፤ ባህልንና<br />

ሕብረተሰባዊ ትብብርን አኮላሽ፤ መንገሥት<br />

ለሕዝብና ለሃገር ሊያደርግ የሚገባውን<br />

አገልግሎት ቀናሽ ሥለሆነ ሁላችንም<br />

ልንዋጋው ይገባል።<br />

ሙስናን የሚያራምዱ በባህላቸው<br />

የዘቀጡና የባህል ድህነት ያጠቃቸው፤<br />

በተንኮለኝነት አስተሣሰብ የተዘፈቁ፤<br />

በሌብነትና በቀማኛነት የተለከፉ፤ የጥሩ<br />

ሥነ-ምግባር ድሃ የሆኑ፤ የሕብረተሰብንና<br />

ያገር ንብረትን አባካኝ/አጥፊ የሆኑ፤ፀረ-<br />

ሕዝብ ግለሰቦች ናቸው። በሙስና ወረርሽኝ<br />

የተለከፉ ግለሰቦች ከሕብረተሰቡ ጋር<br />

ያላቸው ንክኪም በጣም የበረከተ ስለሆነ<br />

በሽታውን ለጠቅላላው ሕብረተሰብ<br />

የማስፋፋትና የማስለከፍ ችሎታቸው<br />

ከፍተኛ ስለሆነም ከሥልጣናቸው መወገድ<br />

አለባቸው።<br />

በሙስና የተዘፍቁ አግሮች በኢኮኖሚም<br />

ሆነ በባሕል ወደ ኋላ የቀሩ መሆናቸው<br />

በብዙ ጥናቶች የተረጋገጠ ስለሆነ ይህ<br />

ችግር በኢትዮጵያችን በሚያስፈራ መልክ<br />

እያንሠራራ ስለሆነ ይህንን የነቀርሳ<br />

በሽታ ለመዋጋትና መንግሎ ለማውጣት<br />

መተባብር ያስፈልገናል። ከብዙ አገሮች<br />

የተገኘው ልምድ እንደሚያመለክተው ሁሉ<br />

ሙስናን ለመዋጋት በሙስና የተለከፉትን<br />

ግለሰቦች ማጋለጥና መንግሥት ሙስናን<br />

ለመዋጋት የማይተባበር ከሆነም፤ በሕቡዕ<br />

በመደራጀትና በመተባበር መዋጋትን፤<br />

በሙስና የተዘፈቁትንም በምስጢራዊ<br />

ሰነድ አዘጋጅቶ እንደአስፈላጊነቱ ማጋለጥ።<br />

እንደዚህ ያለው አስተዋፅዖና መልካም<br />

ምግባር፤ ለሙስናው መሥፋፋት<br />

ምክንያት የሆነው የአስተዳደር ብልሹነት<br />

እንዲፍረከረክ ያደርገዋል። ተጎጅው<br />

ሕዝብንም እስትንፋስ ይሰጠዋል።<br />

እንደሚታወቀው ባገራችን በኢትዮጵያ<br />

(በየክፍለ ሃገሩ፤ በየከተማው፤ በየንመደሩ፤<br />

በልዩ ልዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች፤<br />

ዱሮ በመንግስት ሥር በነበሩት አሁን ግን<br />

“ለግል ባለ ሀብቶች” በርካሽ በተቸረቸሩት<br />

ተቋማት መካከል፤በግል ሀብቶች መስክ፤<br />

….ወዘተ) ከሙስና ጋር የተያያዘው ችግርና<br />

የሚደረገው ደባ ተዘርዝሮ አያልቅም።<br />

ሙስናው የወረርሽኝ በሽታ ስለሆነ<br />

ከዘራፊዎቹ በስተቀር ሁሉንም ሰው<br />

ይጎዳል። ስለዚህ “የኔ ጉዳይ አይደለም”<br />

ተብሎ የሚተው መሆን የለበትም።<br />

እስካሁን ድረስ በኢትዮጵያ ሕዝብና<br />

በሀገሪቷ ላይ አሁንም እየተፈፀሙ ያሉትን<br />

በደሎችን ብሔራዊ ወንጀሎችን በቀጣይነት<br />

መመዝገብና ማጋለጥ አለብን። የዜግነትና<br />

የሰው ልጅነት ግዴታችንን እንድንወጣ አላህ<br />

(እግዚአብሔር) እንዲረዳን እማፀናለሁ!<br />

በመጨረሻም ሙስና ከሰው ጋር<br />

ያልተፈጠረ ክስተት ስለሆነ ያለጥርጥር<br />

እናሸንፈዋለን! በሙስና የተበከሉ<br />

ግለሰቦች፤ ቡድኖችና የመንግሥት<br />

ባለስልጣኖች የድሃውን ወገናችንን ደም<br />

መጣጭ መዥገሮች ናቸውና መወገድ<br />

አለባቸው!የሁለተኛው የሙስና ክፍል፤<br />

ማለት፤ የመንግሥቱን የሥልጣን አውታር፤<br />

አስተዳደሩን፤ ህጎቹን፤ ወ.ዘ.ተ. በመማረክ<br />

የሚገለፁ የሙስና ጠባዮች (state<br />

capture) በሌላ ጊዜ እስከማቀርብ ድረስ፤<br />

እስከዚያው አላህ ቸር ይበለን።<br />

www.andinet.org.et

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!