24.07.2013 Views

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

ምንጭ - Ethiopia: A voice for the voiceless

SHOW MORE
SHOW LESS

You also want an ePaper? Increase the reach of your titles

YUMPU automatically turns print PDFs into web optimized ePapers that Google loves.

2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.15<br />

ዜና<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ ጥቅምት 28 ቀን 2004 ዓ.ም.<br />

የሠራተኞችን ደሞዝ ለመቀማት ሲል 3ሰው ገድሎ<br />

2 ሰው ያቆሰለው ፖሊስ በቁጥጥር ሥር ዋለ<br />

በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ሰሜን ሸዋ ዞን<br />

የምትገኝኘው የያያ ወረዳ አስተዳደር ሠራተኞች<br />

የጥቅምት ወር ደሞዝ ለመዝረፍ ሦስት ሰው ገሎ<br />

ሁለት ሰው ያቆሰለው የወረዳው ፖሊስ በቁጥጥር<br />

ሥር መዋሉን የዜና ምንጮቻችን በተለይ ለፍኖተ<br />

ነፃነት ጋዜጣ ገለጹ፡፡ እንደ ዜና ምንጮቻችን<br />

ገለጻ ከሆነ “ጥቅምት 20 ቀን 2004 ዓ.ም አንድ<br />

ሚሊዮን ብር ይሆናል የሚባለውን የወረዳውን<br />

የመንግስት ሠራተኖች ደሞዝ ለማምጣት ከወረዳው<br />

ፍቼ ከተማ ንግድ ባንክ ይመጣሉ፡፡ ግንዘቡን<br />

ለማምጣት የመጡት ሦስት ሠራተኞች አንድ<br />

ፖሊስና አንድ ሹፌር በጠቅላላ አምስት ሰዎች<br />

ነበሩ፡፡ ከነዚህ ውስጥ አንዷ ሠራተኛ ነፍሰጡር<br />

ነበረች፡፡ ለጊዜው በባንክ ያለው 12ሺ ብር ብቻ ነው<br />

ባንክ ውስጥ ያለው ተብለው ያንን እንደተሰጣቸው”<br />

ምንጮቻችን ገልፀዋል፡፡<br />

በመቀጠልም የዜና ምንጮቻችን እንደሚሉት<br />

“የተሰጣቸውን ብር 12ሺ ይዘው ወደ ወረዳቸው<br />

ሊንቀሳቀሱ ሲሉ አንድ ሌላ የወረዳው ፖሊስ<br />

ይዛችሁኝ ሂዱ ብሎ ትብብር ይጠይቃቸዋል፡፡<br />

እነሱም እሺ ብለው አሳፈሩት ጉዞ ጀምረው ገጠር<br />

ሲደርሱ ያ በልመና የተሳፈረው ፖሊስ “ሽንት<br />

ሰለያዘኝ አንዴ ሽንቴን ልሽና” ብሎ ጠየቃቸው፡<br />

፡ አሁንም እሺ ብለው መኪና አቆሙለት፡<br />

፡ ከወረደ በኃላ መሣሪያውን አውቶማቲክ ላይ<br />

አድርጐ በቅድሚያ ፖሊሱን ከመታው በኋላ ከዚያ<br />

በተሳፈሩት ላይ በጠቅላላ ጥይት አርከፈከፈባቸው፡<br />

፡ ሁለት ወዲያውኑ ሲሞቱ ሌሎቹ ቆሰሉ፡፡ ገንዘቡን<br />

አንስቶ ለማምለጥ ሞከረ፡፡ ጥይት ጨርሶ ስለነበር<br />

የአካባቢው አርሶ አደሮች ከበው በዱላ ቀጥቅጠው<br />

ከያዙት በኋላ ወዲያውኑ ለፖሊስ አስረክበውታል፡፡<br />

የቆሰሉት ሦስቱ አዲስ አበባ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል<br />

እንደደረሱ ፖሊሱ በጠና ተጐድቶ ስለነበር<br />

ወዲያውኑ ሲሞት፤ አንዱ ተሽሎት ከሆስፒታል<br />

ሲወጣ ነፍሰጡሯ እስከ አሁን ሆስፒታል በከፍተኛ<br />

ጉዳት ላይ ትገናለች፡፡” ብለዋል፡፡ ስለጉዳዩ መረጃ<br />

እንዲሰጡን የፍቼ ከተማ ዞን ፖሊስ ጠይቀን<br />

ስማቸውን ለመጥቀስ ያልፈለጉ ሰው “የተሟላ መረጃ<br />

ሊነግሩአችሁ የሚችሉት ህዝብ ግንኙነቶች ናቸው፡<br />

፡ እነሱ በአሁኑ ጊዜ የሉም፡፡ ለጊዜው ልሰጣችሁ<br />

ይምችለው መረጃው ተጠናቅሮ ለኦሮሚያ ፖሊስ<br />

ተላልፏል” በማለት መልስ ሰጥተውናል፡፡ በተያያዘ<br />

ዜና በዚህ ዕለት ማለትም ጥቅምት 20 ቀን 2004<br />

ዓ.ም በዚሁ በፍቼ ቆላማው አካባቢ ልዩ ቦታው<br />

ግራር አዲስ ጌ ቀበሌ ገ/ማህበር ውስጥ “አንድ<br />

ታጣቂ ህዝቡን ሰብሰባ ውጡ እያለ በየቤቱ እየዞረ<br />

በዱላ ሲደባደብ በጥይት ተገድሏል” ሲሉ የዜና<br />

ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡ እንደ ዜና ምንጮቻችን<br />

ገለጻ “በግድያ ተጠርጣሪው ነው የተባለው ግለሰብ<br />

ከሦስት ቀን በኋላ ለመንግስት እጁን ሰጥቷል”<br />

ብለዋል፡፡ በዚህም ጉዳይ ያነጋገርናቸው የዞኑ ፖሊስ<br />

“ግጭቱ የተፈጠረው በሁለት ታጣቂዎች መካከል<br />

ነው፡፡ በአካባቢው ማህበራዊ ፍ/ቤት ተካሰው ነበር፡<br />

፡ ተይዞ እንዲቀርብ የተወሰነበት ታጣቂ ቤቱን ዘግቶ<br />

እንቢተኛ በመሆኑ ለማስወጣት ሲሞክሩ ከቤት<br />

ውስጥ በተተኮሰ ጥይት አንድ ታጣቂ ሞቷል፡፡ ቤት<br />

ውስጥ የነበረው ታጣቂ ለጊዜው የተሰወረ ቢሆንም<br />

በህዝብ ትብብርና በፖሊስ ጥረት ተጠርጣሪው<br />

በቁጥጥር ሥር ውሎአል፡፡ ጉዳዩ በምርመራ ላይ<br />

ነው” በማለት መልስ ሰጥተውናል፡፡<br />

የደብረብርሃን ከንቲባና ባለሥልጣናት በሙስና ተጠርጥረው መታሰራቸው ተገለፀ<br />

የዞኑ ደን ልማት ሽያጭ መነጋገሪያ ሆኖአል<br />

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሰሜን ሸዋ<br />

ዞን ዋና ከተማ የሆነችው ደብረ ብርሃን ከተማ ከንቲባ<br />

የሆኑት “አቶ ስዩም ተፈራና በመሬት አስተዳደርና<br />

በልዩ ልዩ የሥራ ኃላፊነት ላይ የነበሩት የዞኑ ከፍተኛ<br />

ባለሥልጣናት ከሙስና ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው<br />

በእስር ላይ እንደሚገኙ” የዜና ምንጮቻችን<br />

በተለይ ለፍኖተ ነጻነት ጋዜጣ ገለጹ፡፡ እንደ መረጃ<br />

ምንጮቻችን ገለጻ ከሆነ “የዞኑ ነዋሪዎች በተለያየ<br />

ጊዜ በመልካም አስተዳደር እጦት ለተለያዩ አካላት<br />

አቤቱታ ቢቀርብም ፍትህ ማግኘት አይቻልም ነበር፡፡<br />

በጂማ ከተማ የተቃጠለው ውሃ ልማትና ዐቃቤ ህግ ጽ/ቤት<br />

አነጋጋሪ መሆኑ ተገለፀ<br />

በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ጂማ ዞን ዋና ከተማ<br />

በሆነችው ጂማ ከተማ ውስጥ ልዩ ቦታው “ውሃ<br />

ልማት” በሚባል አካባቢ ኖክ ማደያ ፊት ለፊትና<br />

ከፍ/ቤት ጐን የሚገኙት የውሃ ልማትና የዐቃቢ<br />

ህግ ጽ/ቤቶች ሰሞኑን ሙሉ በሙሉ በእሳት ቃጠሎ<br />

መውደማቸው በከተማው አነጋጋሪ ጉዳይ መሆኑን<br />

የዜና ምንጮቻችን ገለጹ፡፡ እንደ ዜና ምንጮቻችን<br />

ገለጻ በ2003 ዓ.ም ለምዕራብ ኦሮሚያ (ጂማ፣ ምዕራብ<br />

ወለጋ፣ ምስራቅ ወለጋና፣ ኢሊባቦር ዞኖች…) በገጠራማ<br />

ሥፍራዎች ለውሃ ቁፋሮ ከፌዴራል መንግስት<br />

ህጋዊ የሆኑ ይዞታዎችን እየነጠቁ ለሚፈልጉት እየሰጡ<br />

ዜጐችን ሲያንከራትቱ፣ ምሪት ቦታዎችን እንዳሻቸው<br />

ለፈለጉት ሲሰጡ ከልካይ አልነበራቸውም፡፡ፍትህ<br />

ሲያዛቡ ጠያቂም አልነበራቸውም፡፡ የአካባቢው<br />

ህዝብ አድማጭ አልነበረውም፡፡ የሚቃወማቸውንና<br />

ልክ አይደለችሁም የሚላቸውን ተለጣፊ ስም እየሰጡ<br />

እያሳሰሩና ከኑሮው እያፈናቀሉ ቆይተዋል፡፡ ዛሬ<br />

ለገዢዎች ባልተመቿቸው ወቅት ጠብቀው ማሰራቸው<br />

የዘገየ እርምጃ ነው” ሲሉ በቁጭትና በሐዘን ገልፀዋል፡፡<br />

በተያያዘ ዜና “ከጣርማ በር መዘዞ ባሽ የሚገኘው<br />

ከተመደበው በጀት ውስጥ 13 ሚሊዮን ብር ጉድለት<br />

በማሳየቱ በባለሥልጣኖች ላይ ክስ ተከፍቶ ጉዳዩን<br />

የፌዴራል ዋናው ኦዲተር መ/ቤት ካሸገው በኋላ ክሱን<br />

የከፈተው የዐቃቢ ህግ ጽ/ቤት ኦዲት ሊደረግ የነበረው<br />

የውሃ ልማት ጽ/ቤት በአንድ ቀንና ሰዓት መቃጠላቸው<br />

እያነጋገር ነው” ሲሉ አብራርተዋል፡፡<br />

የመረጃ ምንጫችን እንደሚሉት “የእሳት<br />

ቃጠሎው ርብርብ አድርጐ ንብረትን፣ ገንዘብንና<br />

ሰነዶችን ማትረፍ ሲቻል ተቃጥሎ እንዲወድም<br />

የተፈለገበት ምክንያት ግልጽ አይደለም፡፡ ካሉ በኋላ<br />

ሰፊ የባህር ዛፍና የጥድ ደን ግልጽነት በጐደለው<br />

ሽያጭ ተሸጦ እየተጨፈጨፈ ነው” ሲሉ አንዳንድ<br />

የአካባቢው ነዋሪዎች ለዝግጅት ክፍላችን ገለጹ፡፡ እንደ<br />

ነዋሪዎቹ ገለጻ “ከጣርማ በር መዘዞ ከመዘዞ መካከል<br />

ባሽ የሚገኘው የሌባ መስቀያ የሚባለው ደን ብቻውን<br />

በእግር ሁለት ሰዓት ያስኬዳል፡፡ ከጣርማ በር እስከ ባሽ<br />

ድረስ በመኪና የአንድ ሰዓት መንገድ ነው፡፡ ይህንን<br />

በ10 ሚሊዮኖች የሚቆጠረውን ደን እንደ ተራ እቃ<br />

በስውር መሸጥ እና ጭፍጨፋ መጀመር አነጋጋሪ ነው”<br />

ሲሉ ያብራራሉ፡፡<br />

ምናልባት ከፍተኛ የመንግስት ባለሥልጣን እጅ<br />

ሳይኖርበት አይቀርም” በማለት ጥርጣሬአቸውን<br />

ገልፀዋል፡፡<br />

በጉዳዩ ላይ አስተያየት እንዲሰጡን የጂማ ከተማ<br />

ፖሊስ ደውለን ነበር፡፡ ስማቸውን ለመጥቀስ ያልፈለጉ<br />

አንድ ግለሰብ ጥያቄያችንን ካዳመጡ በኋላ “ጉዳዩ<br />

በምርመራ ላይ ያለ በመሆኑ አስተያየት ልንሰጣችሁ<br />

አንችልም” በማለታቸው ዜናውን ሚዛናዊ ማድረግ<br />

አልቻልንም፡፡<br />

አርቲስት ደበበ እሸቱ ተጨማሪ ቀነ<br />

ቀጠሮ ተጠየቀበት<br />

በ ”ሽብር” ተጠርጥሮ ማዕከላዊ እስር ቤት የሚገኘው አርቲስት ደበበ እሸቱ ጥቅምት<br />

24 ቀን 2004 ዓ.ም አራዳ ምድብ ችሎት ተቀጥሮ እንደነበር ይታወሳል፡፡<br />

አርቲስት ደበበ በቀጠሮው ቀን ከማዕከላዊ እስር ቤት ወደ ችሎት ቀርቧል፡፡<br />

ችሎቱን ለመከታተልም የተጠርጣሪው ቤተሰብም ሆነ ጋዜጠኞች እንዳይገቡ የተከለከለ<br />

ሲሆን ተጨማሪ የ28 ቀን ቀነ ቀጠሮ ተጠይቆበታል ሲሉ ጠበቃው በተለይም ለዝግጅት<br />

ክፍላችን ገልፀዋል፡፡<br />

ተጠርጣሪውም ጥቅምት 24 ቀን 2004 ዓ.ም ችሎት እስከቀረቡበት ጊዜ<br />

ድረስ በማዕከለዊ እስር ቤት ከጠበቃቸው ጋር እንዲገናኙ ባለመፈቀዱ ጠበቃው ችሎት<br />

ፊት ከደንበኛቸው ጋር እንዲመክሩ በጠየቁት መሠረት ተፈቅዶላቸዋል ሲሉ ምንጮቻችን<br />

ጠቁመዋል፡፡ በዚህም ክቡር ፍ/ቤቱ ተጠርጣሪው ከጠበቃቸው ጋር የመገናኘት ሕገ<br />

መራግሥታዊ መብታቸው መሆኑንና ሊከለከሉ እንደማይገባ ለመርማሪው ፖሊስ<br />

በማሳሰባቸው ጠበቃቸውም ተግባራዊ መሆኑን ለማረጋገጥ ዛሬ ወይም ነገ ማዕከላዊ<br />

እስር ቤት ሄደው ደንበኛቸው አርቲስት ደበበ እሸቱን ለማነጋገር መወሰናቸውን በተለይም<br />

ለዝግጅት ክፍላችን ገልፀዋል፡፡<br />

11<br />

በናይጄሪያ 150 ሰዎች<br />

በአጥፍቶ ጠፊዎች<br />

መገደላቸው ተገለፀ<br />

በሰሜን ናይጄሪያ ደማቱሩ ከተማ 150 ሰዎች<br />

በአጥፍቶ ጠፊዎች ቦምብና በጠብመንጃ በተፈጠረው<br />

ተኩስ ጥቃት ያለፈው ቅዳሜ መገደላቸው ተገለፀ፡፡ ለጥቃቱ<br />

“ይሄነስ” የተባለው እስላማዊ ቡድን እጅ አለበት ብለዋል”<br />

ሲሉ የሀገሪቱን ባለሥልጣናትን ጠቅሶ ቢቢሲ ዘግቧል፡፡<br />

ይህንንም አስመልክቶ የፕሬዘዳንት ጉድላክ<br />

ጆናታን ቃል አቀባይ ሩበን አባቲ ጥቃቱ የተፈፀመው<br />

ከ5 በማያንሱ አጥፋቶ ጠፊዎች እንደሆነና ጉዳዩንም<br />

የሚመለከተው አካል እያጣራ እንዳለ አስታውቀዋል፡<br />

፡ ቃል አቀባዩ አያይዘውም አሁን በአካባቢው ምንም<br />

የፀጥታ ችግር እንደሌለና ጥቃቱን አስተባብረዋል ተብለው<br />

የተጠረጠሩትም በእስር ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል<br />

ሲሉ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙኋን ዘግበዋል፡፡<br />

በኬንያ ቱሪስት መዳረሻ<br />

ኬንያዊ ሾፌር ሲገደል<br />

ስዊዘርላንዳዊ ጐብኚ መቁሰሏ ተገለፀ<br />

በኬንያ ምስራቃዊ ክፍል “ጌም ፓርክ” በተባለው የቱሪስት<br />

መዳረሻ ስዊዘርላንዳዊ ጐብኚዎችን ይዞ የነበረው ኬንያዊ<br />

ሾፌር ባልታወቁ ታጣቂዎች ሲገደል አንድ ስዊዘርላንዳዊት<br />

ጐብኝ መቁሰሏን የፈረንሳይዩ የዜና ወኪል ኤ ኤፍ ፒ<br />

ዘግቧል፡፡<br />

ባለፈው አርብ በተፈፀመ ጥቃት በከፍተኛ ደረጃ የቆሰለችው<br />

ስዊዘርላንዳዊት ቱሪስት ወደ አቅራቢያ ሆስፒታል ሄዳ<br />

የሕክምና እርዳታ እየተደረገላት እንደሆነና አብሯት<br />

የነበረው ስዊዘርላንዳዊ የመቁሰል አደጋ እንዳልገጠመው<br />

የኬንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ስቴፈን ቮን<br />

ቢሎው አስታውቀዋል፡፡<br />

ኬንያ በቱሪዝም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የምታገኝ<br />

ሀገር ስትሆን ከዚህ በፊት በመስከረም ወር እንግሊዛዊ<br />

ጐብኚ ሲገደል ባለቤቱ ታግታ አንደነበር ይታወሳል፡<br />

፡ በተመሳሳይም በጥቅምት ወር አንድ ፈረንሳያዊት እና<br />

ሁለት ስፔይናዊ ዜጐች ጥቃት እንደደረሰባቸው ተዘግቧል፡<br />

፡ ይህንንም አስመልክቶ ኬንያ ከቱሪስት የምታገኛቸው<br />

ገቢዎች እንዳይቀንስ ስጋት የፈጠረ ሲሆን የሀገሪቱ<br />

መንግሥት በበኩሉ ድርጊቱን የሚፈፅሙ ያልታወቁ<br />

ታጣቂዎችን በቅርቡ በቁጥጥር ሥር እንደሚያውል<br />

ገልጿል፡፡<br />

ዓለም አቀፉ የገንዘብ<br />

ድርጅት ለኮትዲቯር<br />

616 ሚሊዮን ዶላር ብድር አፀደቀ<br />

ኮትዲቯር ካለፈው ዓመት ምርጫ ውጤት ጋር<br />

በተያያዘ በተፈጠረ ችግር ከፍተኛ የምጣኔ ሃብት<br />

ውድቀት ተከስቶ እንደነበር ይታወቃል፡፡ ይህ ምጣኔ<br />

ሃብት እንዲያንሰራራ ፕሬዘዳንት ኦታራ ዓለም አቀፍ<br />

አበዳሪ ተቋማትን የተማፀኑ ሲሆን በዚህም መሠረት<br />

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት 616 ሚሊዮን ዶላር ብድር<br />

ያለፈው አርብ ዕለት ማፅደቁ ተጠቁሟል፡፡<br />

በተያያዘ ዜና ባለፈው የኮትዲቯር ምርጫ ተሸንፈው<br />

የነበሩት ሎረንት ባግቦ “ስልጣን አልለቅም” በሚል<br />

በተፈጠረው አለመግባባት 3ሺህ ሰዎች መገደላቸውን<br />

አስመልክቶ በወቅቱ ጥቂት የሀገሪቱ አመራሮች ላይ<br />

የኦታራ መንግስት ክስ መስርቷል፡፡<br />

ከተከሳሾችም መካከል የቀድሞ ፕሬዘዳንት ሎረንት<br />

ባግቦ፣ 24 ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት ባለሥልጣናት<br />

እና 57 የሀገሪቱ ወታደራዊ አመራሮች ይገኙበታል ሲል<br />

የፈረንሣዩ የዜና ወኪል ዘግቧል፡፡<br />

www.andinet.org.et

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!