የመሬት ቅርምት ለልማት - Ethiopia: A voice for the voiceless
የመሬት ቅርምት ለልማት - Ethiopia: A voice for the voiceless
የመሬት ቅርምት ለልማት - Ethiopia: A voice for the voiceless
Create successful ePaper yourself
Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.
4<br />
ፍኖተ -ነፃነት ጋዜጣ ሐምሌ 2ዐዐ3 ዓ.ም<br />
ተመሠረተ፡፡ ፍኖተ ነፃነት በአንድነት ለዴሞክራሲና<br />
ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሥር የሚታተም<br />
በፖለቲካዊ፣ በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ፣ በወቅታዊ ጉዳዮችና<br />
በመዝናኛ ላይ የሚያተኩር የፓርቲው ጋዜጣ ነው፡፡<br />
ጋዜጣችን እንደ ፓርቲ ልሳን ብቻ<br />
ሳይሆን እንደ አንድ ሚዛናዊ የግል<br />
ጋዜጣ ሆኖ ማገልገል ይፈልጋል<br />
የማንኛዉም ሰዉ ሀሳብና አመለካከት<br />
የሚስተናገድበትና የሚንሸራሸርበት<br />
እንዲሆን እንሻለን ሰፊና ረዝም የሚዲያ<br />
ሽፋን ያለዉ ኢህአዴግም በዚህ ሚዲያ<br />
አቋሙንና ፖሊሲዉን ለማቅረብ ቢፈልግ<br />
ክፍት ነዉ<br />
ዋና አዘጋጅ፡-<br />
አንዳርጌ መሥፍን<br />
አድራሻ፡-<br />
የካ ክ/ከተማ ወረዳ 12<br />
የቤ.ቁ አዲስ<br />
አዘጋጆች፡-<br />
ብዙአየሁ ወንድሙ<br />
ብስራት ወ/ሚካኤል<br />
አምደኞች፡- ዶ/ር ኃይሉ አርዓያ<br />
ኢ/ር ዘለቀ ረዲ<br />
አንዱዓለም አራጌ<br />
ግርማ ሠይፉ<br />
ዳምጠው አለማየሁ<br />
ተስፋዬ ደጉ<br />
በላይ ፍቃደ<br />
ወንድሙ ኢብሳ<br />
ኮምፒውተር ጽሑፍ፡-<br />
የሺ ሃብቴ<br />
ብርቱካን መንገሻ<br />
አከፋፋይ፡-<br />
ነብዩ ሞገስ<br />
አሣታሚው፡-<br />
አንድነት ለዴሞክሲና ለፍትህ ፓርቲ(አንድነት)<br />
አድራሻ፡- አራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 07 የቤ.ቁ አዲስ<br />
አታሚ፡- ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት<br />
አራዳ ክ/ከተማ ቀበሌ 07 የቤ.ቁ 984<br />
የዝግጅት ክፍሉ<br />
ስልክ +251 922 11 17 62<br />
+251 913 05 69 42<br />
+251 118-44 08 40<br />
ፖ.ሳ.ቁ፡ 4222<br />
ኢሜይል፡- udjparty@gmail.com<br />
andinet@andinet.org<br />
ፋክስ ቁጥር፡- +251-111226288<br />
www.andinet.org.et<br />
ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ መስከረም 23 2004 ዓ.ም.<br />
ርዕሰ አንቀፅ<br />
ያለማቋረጥ እያደገ ያለው የዋጋ ንረት<br />
መልህቅ ይበጅለት<br />
ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ የሃገራችን የገበያ ሁኔታ ይበልጥ እየተቃወሰና ከቀን ወደ ቀን እየታመሰ<br />
ቀጥሏል፡፡ የሕብረተሰቡ የኑሮ ሁኔታም ከድጡ ወደ ማጡ እየሆነበት መሠረታዊ የሆኑ የዕለት<br />
ፍላጎቶችን ማሟላት እየቸገረው ነው፡፡<br />
በ1997 ዓ.ም 6.8% የነበረው የዋጋ ንረት በተከታዮቹ ሁለት አመታት 12.3 በመቶ እና 15. 8<br />
በመቶ ደረሰ፡፡ ይህም ማለት የንረቱ እድገት መጠን በሁለት ዓመት ውስጥ 132 በመቶ ሆነ ማለት<br />
ነው፡፡ ከ1999 ዓ.ም በኋላ ያሉት አራት ዓመታት አጠቃላይ የዋጋ ንረት መጠንን ስንመለከት<br />
ደግሞ 1999 ላይ 15.8 በመቶ የነበረው በ2003 ዓ.ም 57 በመቶ ደርሷል፡፡ ይህም አጠቃላይ<br />
የአራት ዓመት የዋጋ ንረት እድገቱን 36ዐ.7 ፕርሰንት መድረሱን ያመላክታል፡፡<br />
ከ1997 ዓ.ም ጀምሮ ያሉትን ስድስት ዓመታት አጠቃላይ የዋጋ ንረት እድገት ስንመለከት<br />
ደግሞ 714% ይሆናል፡፡ ይህም ማለት የገንዘብ የመግዛት አቅም ባለፉት ስድስት ዓመታት በ714<br />
ፕርሰንት ወድቋል ማለት ነው፡፡<br />
በአንፃሩ አማካይ ዓመታዊ ገቢ በ1997 ዓ.ም 165 ዶላር የነበረ ሲሆን አሁን 35ዐ ዶላር<br />
እንደደረሰ የአይኤም ኤፍ ሪፖርት ያመለክታል፡፡ ባለፉት ስድስት ዓመታት አማካይ አመታዊ ገቢ<br />
በ112 በመቶ አድጓል ማለት ነው፡፡<br />
ከላይ ከተመለከቱት መረጃዎች የምንረዳው በስድስት ዓመቱ የገቢ እድገትና የዋጋ ንረት<br />
እድገት መካከል የ602 በመቶ ልዩነት እንዳለ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ<br />
በ1999 ዓ.ም ይኖር የነበረውን ኑሮ ዛሬ ለመኖር እንዲችል የዋጋ ንረቱ ከ14.4 በመቶ መብለጥ<br />
አልነበረበትም ወይም አማካይ አመታዊ ገቢ 1171.5 ዶላር መድረስ ነበረበት፡፡<br />
በሃብታሙና በድሃው ዜጋ መካከል ያለው የሃብት ክፍተት እየሰፋ መሄድ እንዳለ ሆኖ<br />
የኢትዮጵያውያን የድህነት ደረጃ ባለፉት ስድስት ዓመታት በ324.7 በመቶ እንዳደገ መረዳት<br />
ይቻላል፡፡ ይህንን አሰቃቂ ሁኔታ ይበልጥ አስፈሪ የሚያደርገው ገዢው ፓርቲ ችግሩን ለማስወገድ<br />
ቀርቶ ባለበት እንኳን ለማስቆም አለመቻሉ ነው፡፡ እየወሰዳቸው ያሉት ርምጃዎችም አስተውሎት<br />
የጎደላቸው በመሆናቸው ችግሩን የበለጠ ሲያባብሱት እንጂ ሲቀንሱት አልታዩም፡፡<br />
የኢኮኖሚ ኃይሎች (ፍላጎትና አቅርቦት) ገበያውን መምራት ሲሳናቸው መንግሥት ጣልቃ<br />
ገብቶ ማረጋጋት እንዳለበት እምነታችን ነው፡፡ ይህ ሲባል ግን መንግሥት የገበያ ኃይሎችን<br />
መቆጣጠር ወይም መተካት አለበት ማለት አይደለም፡፡ በትክክል መሥራት እንዲችሉ የሚረዱ<br />
የፊስካልና የገንዘብ ፖሊሲዎችን ተግባራዊ በማድረግ የኢኮኖሚውን አቅም ያጠናክራል እንጂ፡፡<br />
በእርግጥ ገዢው ፓርቲ ገበያውን ለማረጋጋት የተለያዩ የፖሊሲና የቀጥተኛ ጣልቃ ገብነት<br />
ርምጃዎችን ወስዷል፡፡ እዚህ ላይ የሚነሳው ዋናው ጥያቄ ታዲያ ለምን የዋጋ ንረቱ የበለጠ<br />
እየተባባሰ ሄዴ? የሚለው ነው፡፡<br />
የኢህአዴግ መሠረታዊ ችግር የችግሩን መነሻ ለይቶ ለማወቅ አለመቻሉ ላይ ነው፡፡ ኢህአዴግ<br />
የዋጋ ንረቱ በተከታታይ እየተመዘገበ ያለው የኢኮኖሚ እድገት የፈጠረው ነው ብሎ ያምናል፡፡<br />
እ.ኤ.አ በ1929 በአሜሪካ የተከሰተው የኢኮኖሚ ዝቅጠትን ተከትሎ የተስፋፋው<br />
የኬንዚያውያን (Keynesian) የምጣኔ ኃብት ባለሙያዎች አስተሳሰብ በምጣኔ ኃብት እድገትና<br />
በዋጋ ንረት መካከል ቀጥተኛ ግንኙነት ስለአለ መንግሥት በከፍተኛ ኢንቨስትመንትና የሥራ<br />
ዕድል ፈጠራ ኢኮኖሚውን ሲያሳድግ የሕዝብ ገቢም አብሮ ያድጋል የሚል ነው፡፡ በመሆኑም<br />
የፍጆታ ወጪ መጠን ይጨምራል፡፡ ይህም የሸቀጦችና የአገልግሎት ዋጋ እንዲንር ያደርጋል የሚል<br />
በመሆኑም ኢኮኖሚው ባደገ ቁጥር የዋጋ ንረቱም ይቀጥላል ማለት ነበር፡፡<br />
ይህ አስተሣሰብ በወቅቱ ትክክለኛ የነበረ ቢሆን በ1970ዎቹ የታየው የስራ አጥነትና የዋጋ<br />
ንረት “Stagflation” በተመሣሣይ ጊዜ በመከሰቱ (Stagflation) ውድቅ እንዲሆን አድርጎታል፡፡<br />
በሃገራችን በአሁኑ ሠዓት እየታየ ያለው ክስተትም ከ1970ዎቹ የምዕራባውያን የኢኮኖሚ ቀውስ<br />
ጋር ተመሣሣይነት አለው፡፡<br />
የዋጋ ንረቱ ሥራ አጥነቱ በእጅጉ እየተባባሱ ናቸው፡፡ ከገቢ አንፃር ሲታይም ከላይ<br />
እንደተገለፀው ባለፉት ስድስት ዓመታት ውስጥ የዋጋ ንረት በ714 በመቶ ሲያድግ ዓመታዊ ገቢ<br />
በ112 ፕርሰንት ብቻ ነው ያደገው፡፡ በመሆኑም በሃገራችን ያለው የዋጋ ንረት የኢኮኖሚው እድገት<br />
የወለደው ነው ሊባል ፈፅሞ አይችልም፡፡<br />
በአንድነት ፓርቲ ዕምነት እይታ የዋጋ ንረቱ መሠረታዊ ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው፡-<br />
1. መንግሥት ከፍተኛ ብዛት ያላቸው የገንዘብ ኖቶችን አሣትሞ በኢኮኖሚው ውስጥ<br />
መርጨቱ፣<br />
2. የመንግሥት ወጪ መጠን በከፍተኛ ደረጃ እያደገ መምጣቱ፤ ይህም በሃገር ውስጥ<br />
ምርት አቅርቦት እድገት አለመደገፉ፣<br />
3. በውጭ ምርቶች ላይ መሠረቱን የጣለው አቅርቦትና የውጭ አገር ምርቶች ዋጋ<br />
መናሩ፣<br />
4. የብር ዋጋ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየወደቀ መምጣትና የውጭ ምርት አቅርቦትና ፍላጐት<br />
አለመጣጣም፣<br />
5. የመንግሥት የነዳጅ ድጎማ መነሳት፣<br />
6. የመሠረታዊ ዕቃዎች ፍላጎትና አቅርቦት ከፍተኛ ሁኔታ አለመጣጣም፣<br />
7. መንግሥት የግሉን ዘርፍ ተክቶ አቅርቦትና ሥርጭትን ለመቆጣጠር የሚያደርገው<br />
ጥረት፣<br />
8. በግል ባንኮች ላይ ተጥሎ የነበረው የብድር ጣሪያ የአገር ውስጥ ምርትንና ከውጭ<br />
የሚገቡ ሸቀጦችን አቅርቦት መገደቡ፣<br />
9. በግል ባንኮች ላይ የተጣለው የግምጃ ቤት ሰነድ ግዢ ግዴታ የሃገር ውስጥ ምርትንና<br />
ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦች አቅርቦትን የሚገድብ መሆኑ የሚፈጥረው የአቅርቦት እጥረት፣<br />
10. በመሬት ፖሊሲው ምክንያት <strong>የመሬት</strong>ና የገበሬው ምርታማነት መቀነስ፡፡ ይህንንም<br />
ተከትሎ የሃገር ውስጥ ምርት አቅርቦትና ፍላጎት አለመጣጣም፣<br />
11. የመሠረተ ልማት ዝርጋታ ውስንነትና የዜጎች ከክልል ወደ ክልል ተንቀሳቅሶ የመሥራት<br />
መብት መገደብን ተከትሎ የምርትና የሰው ኃብት እንቅስቃሴ መወሰኑ፡፡ በዚህም ምክንያት የሰው<br />
ኃብትና ምትርት ከፍተኛ አቅርቦት ካለበት አካባቢ ወደ ከፍተኛ ፍላጎት ያለበት ቦታ ለመንቀሳቀስ<br />
አለመቻሉ በሃገራችን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ በመምጣት ላይ ላለው የዋጋ ንረትና የኑሮ ውድነት<br />
ዋነኛ ምክንያቶች ናቸው፡፡<br />
እነዚህን ችግሮች በአንክሮ ስንመለከት የሁሉም ምክንያቶች መነሻ የተዛቡ የመንግሥት<br />
ፖሊሲዎችና አስተውሎት የጎደለው የመንግሥት ጣልቃ ገብነት እንደሆነ እንረዳለን፡፡<br />
በመሆኑም መንግሥት ይህን ውስብስብ ችግር ለመፍታት ቁርጠኝነቱ ካለው በመጀመሪያ<br />
ደረጃ የልማት እስትራቴጂውና ፖሊሲዎቹ ላይ መሠረታዊ ለውጥ ሊያደርግና ከግብታዊ ጣልቃ<br />
ገብነት ሊቆጠብ ይገባል፡፡ ይህን የማያደርግ ከሆነ ግን እየተባባሰ ያለው የኑሮ ውድነትና የዋጋ ንረት<br />
ማቆሚያ የሌለው እንደሚሆንና ካሁኑ የባሰ የተወሳሰበ ሰብአዊና ማሕበራዊ ቀውስ ሊያስከትል<br />
እንደሚችል ልብ ሊል ይገባል፡፡<br />
ነፃ አስተያት<br />
2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.10<br />
“ማነው ተው<br />
የሚለኝ?!”<br />
ይድነቃቸው ዐይኔ<br />
አብዛኛዎቻችሁ የዚህን ጽሁፍ ርዕስ ስታዩ የብርሃኑ ተዘራን ማነው<br />
ተው የሚለኝ ማነው? የሚለውን ዘፈን ታስታውሱታላችሁ<br />
ብዬ እገምታለሁ፡፡ ወይም ደግሞ በሰፈራችሁ፣ በአካባቢያችሁ<br />
እና በመንደራችሁ ስፓርታዊ እንቅስቃሴን (በተለይም ክብደት<br />
ማንሳትን) ለፀብ እንጂ ለፀባይ የማይሰሩ በትዕቢት የተሞሉ<br />
ጐረምሶች እና ወጣቶች ማነው ተው የሚለኝ አፍንጫውን<br />
እለዋለሁ፤ የሚለውን አባባል በተደጋጋሚ ስለሚጠቀሙት እነሱ<br />
ትዝ ….. ብለዋችሁ ይሆናል፡፡ እኔ ግን በጽሁፌ ላስታውሳችሁ<br />
የምፈልገው፤ ከሁሉም በላይ አባባሉን በመጠቀም ላይ<br />
ስለሚገኘው እና በተግባር ስለሚያውለው እንዲሁም በዚህ<br />
ድርጊቱ አቻ ስላልተገኘለት አካል ነው፡፡<br />
የመቶ በመቶ የምርጫ ድል (ዘጠና ዘጠኝ ነጥብ ምናምን<br />
የሚለውን ቁጥር ያልተጠቀምኩት አውቄ ነው፡፡ ምክንያቱም ይህ<br />
ገለፃ፤ ምርጫው ሰማንያ በመቶ የማሸነፍ ያህል ያስመስለዋል፡፡<br />
ሥነልቡናዊ ጥቅም አላት፡፡) ከኔ በላይ ለአገሪቱ ተቆርቆሪ ወገን<br />
የለም ብሎ የሚያስብ ገዢ ፓርቲ እና ይህን ሀሳብ የመጨረሻ<br />
እውነት አድርጐ የሚቆጥር የካድሬ ጐርፍ፣ የማያባራ የምሁራን<br />
እና የዜጐች ስደት (ያውም በሬድዮ ጭምር በሚለፍፉ የውጭ አገር<br />
የሥራ ዕድል ማስታወቂያ በሚቀርብበት ሁኔታ ላይ እስክንደርስ፡<br />
፡)፣ በዘፈቀደ የተቀመጠ ግትር ፖሊሲ መቃብራቸውን መማስ፣<br />
የታዋቂ ፖለቲከኞች እና የጋዜጠኞች እስር እና ወከባ እንዲሁም<br />
ተመሳሳይ ሕዝባዊ በደሎች፤ በተጨማሪም የመልካም አስተዳደር<br />
እጦት እና የሙስና መንሰራፋት የተባባሱት እና የተበራከቱት<br />
በሌላ በማንም አይደለም፡፡ ማነው ተው የሚለኝ? ሊጠይቀኝ<br />
የሚችል ከኔ ጋር የተጠጋጋ ኃይል ያለው አካል ከወዴት አለ?<br />
እኔን የሚመጥን ጉልበተኛ ማን አለ? ከኔ በላይ አዋቂ፣ ከኔ በላይ<br />
ብልህ፣ ከኔ በላይ አስተዳዳሪ ለዘበት በሚል መንግስት እንጂ፡፡<br />
ኢሕአዴግ ከጊዜ ወደ ጊዜ ሥር እየሰደደ በመጣው ኃይሉ እና<br />
ባለው የፖለቲካ ሥልጣን ልዕልና በመጠቀም፤ በእያንዳንዱ<br />
እርምጃ እና ድርጊት ያለመጠየቅን ፀጋ ተጐናጽፏል፡፡ ምርጫው<br />
ሙሉ ለሙሉ ሊባል በሚችል መልኩ ማሸነፉን እንደ በጐ<br />
ዴሞክራሲያዊ አካሄድ ማየት፣ የፈለጉትን ሕግ በፓርላማ ማፅደቅ<br />
እና በዚህ ሕግ ሌሎችን ማሸማቀቅ እንዲሁም ማስጨነቅ፣<br />
የሌሎችን ሀሳብ እንደ መናኛ ቆጥሮ የራስን ሀሳብ ብቻ መናገር<br />
እና ማስነገር (የሀገሪቱን ትላልቅ እና ኃይል ያላቸው የመገናኛ<br />
ብዙሀንን ለራስ ብቻ በማዋል የሌሎችን ሀሳብ በመገደብ፡፡)፣<br />
ሌሎችን ባለድርሻ አካላት ሳያማክሩ አገሪቷን አደጋ ላይ ሊጥሉ<br />
የሚችሉ ፖለቲካዊ እና ሥነ ምጣኔያዊ ውሳኔዎችን ማስተላለፍ፤<br />
ተው የሚለኝ ካለ፤ ይሞክረኝ! የሚል ሀላፊነት የጐደለው<br />
መልዕክት ማስተላለፍ እንጂ ሌላ ምን ሊሆን ይችላል?<br />
በየወንዙ ዳር መቀደስ<br />
የተኛን ሴጣን ለመቀስቀስ<br />
ይህ አባባል በሁለት መስመር ቃላት ብዙ ማለት ከሚችሉ<br />
ኢትዮጵያውያት ሴቶች ከተናገሯቸው አባባሎች አንዱ እንደሆነ<br />
አምናለሁ፡፡ የእምነት ሰው ነኝ፣ የእግዚአብሄርን ስም ከኔ ወዲያ<br />
ማን ያውቃል? ከኔ በላይስ ክርስቲያን አለ? እንደው ከኔ ወዲያ<br />
ቀዳሽ በአገሪቱ ይኖር ይሆን? ብሎ በእምነት ሳይሆን በትዕቢት<br />
አለፍ ሲልም በሞኝነት የተሞላ ሰው የሚያደርገው አድራጐትን<br />
ይገልፃል አባባሉ የዚህ ሁሉ ቅዳሴ እና የእግዚአብሄርን<br />
ስም መጥራት ሰይጣንን ከመቀስቀስ አልፎ አምላክ ዘንድ<br />
እንደማይደርስ ይገልፃል አባባሉ፡፡<br />
ይህንን አባባል ከተናገሩት ቀደምት ሊቃውንት ሁለቱን መስመር<br />
ተውሼ የሰሞኑን የመንግስታችንን ድርጊት ልመዝን፡፡<br />
የፀረ- ሽብርተኝነት ሕግ አዋጁ እና ዘመቻው ሁሉንም ባለድርሻ<br />
አካላት ባግባብ እና ባሳተፈ መልኩ እንዳልተደረገ ለመናገር<br />
ኢትዮጵያዊ መሆን በቂ ነው፡፡ ከዛ ባለፈ የፓርላማን ውሎ<br />
እና ፓርላማው ነገሮችን በምን ፍጥነት አይቶ በምን ፍጥነት<br />
እንደሚያፀድቅ በቴሌቪዥን መስኮት ማየት ይበቃል፡፡<br />
ፓርቲው የሚያቀርበው ሀሳብ በሙሉ የኔ ሀሳብ ነው፡፡ ፓርቲዬ<br />
የሚያቀርበው ሀሳብ በፍፁም እኔን አደጋ ላይ አይጥለኝም፤ በሚል<br />
የራስን ሀሳብ ገሎ በሌሎች ተጨፍልቆ የማሰብ አዙሪት ውስጥ<br />
በገቡ ሰዎች፤ ስንት ማህበራዊ እና ሀገራዊ አደጋን የሚያስከትሉ<br />
ፖሊሲዎች እና አዋጆች ጸድቀዋል?<br />
በኑሮ ውድነት፣ በአንድ ፓርቲ እና በአንድ ሰው የበላይነት<br />
በዴሞክራሲ እና በብልሹ አስተዳደር እንዲሁም ቀጣይነት<br />
በሌላቸው እና ፖለቲካዊ ዓላማቸውን እስካልሳቱ ብቻ በሚጸድቁ<br />
ፖሊሲዎች የተሰላቸው ህዝብ፣ አነሰም በዛም የሚያውቃቸውን<br />
እና የሚያከብራቸውን ከመንግስት በተቃራኒው የቆሙትን<br />
ፓለቲከኞች እና ጋዜጠኞች በሽብርተኝት ታርጋ ከለላ ወደ<br />
እስር ቤት መወርወር፤ ግለሰቦቹን እና ደጋፊዎቻቸውን ብሎም<br />
ጋዜጣችን “ፍኖተ-ነፃነት” ብለናታል፡፡ “ፍኖት” ማለት መንገድ ማለት ሲሆን ከነፃነት ጋር<br />
ሲጣመር “የነፃነት መንገድ” ማለት ነው!! ወደ 7 የዞሯል