24.08.2013 Views

የመሬት ቅርምት ለልማት - Ethiopia: A voice for the voiceless

የመሬት ቅርምት ለልማት - Ethiopia: A voice for the voiceless

የመሬት ቅርምት ለልማት - Ethiopia: A voice for the voiceless

SHOW MORE
SHOW LESS

Create successful ePaper yourself

Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.

4<br />

ፍኖተ -ነፃነት ጋዜጣ ሐምሌ 2ዐዐ3 ዓ.ም<br />

ተመሠረተ፡፡ ፍኖተ ነፃነት በአንድነት ለዴሞክራሲና<br />

ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሥር የሚታተም<br />

በፖለቲካዊ፣ በማህበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ፣ በወቅታዊ ጉዳዮችና<br />

በመዝናኛ ላይ የሚያተኩር የፓርቲው ጋዜጣ ነው፡፡<br />

ጋዜጣችን እንደ ፓርቲ ልሳን ብቻ<br />

ሳይሆን እንደ አንድ ሚዛናዊ የግል<br />

ጋዜጣ ሆኖ ማገልገል ይፈልጋል<br />

የማንኛዉም ሰዉ ሀሳብና አመለካከት<br />

የሚስተናገድበትና የሚንሸራሸርበት<br />

እንዲሆን እንሻለን ሰፊና ረዝም የሚዲያ<br />

ሽፋን ያለዉ ኢህአዴግም በዚህ ሚዲያ<br />

አቋሙንና ፖሊሲዉን ለማቅረብ ቢፈልግ<br />

ክፍት ነዉ<br />

ዋና አዘጋጅ፡-<br />

አንዳርጌ መሥፍን<br />

አድራሻ፡-<br />

የካ ክ/ከተማ ወረዳ 12<br />

የቤ.ቁ አዲስ<br />

አዘጋጆች፡-<br />

ብዙአየሁ ወንድሙ<br />

ብስራት ወ/ሚካኤል<br />

አምደኞች፡- ዶ/ር ኃይሉ አርዓያ<br />

ኢ/ር ዘለቀ ረዲ<br />

አንዱዓለም አራጌ<br />

ግርማ ሠይፉ<br />

ዳምጠው አለማየሁ<br />

ተስፋዬ ደጉ<br />

በላይ ፍቃደ<br />

ወንድሙ ኢብሳ<br />

ኮምፒውተር ጽሑፍ፡-<br />

የሺ ሃብቴ<br />

ብርቱካን መንገሻ<br />

አከፋፋይ፡-<br />

ነብዩ ሞገስ<br />

አሣታሚው፡-<br />

አንድነት ለዴሞክሲና ለፍትህ ፓርቲ(አንድነት)<br />

አድራሻ፡- አራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 07 የቤ.ቁ አዲስ<br />

አታሚ፡- ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት<br />

አራዳ ክ/ከተማ ቀበሌ 07 የቤ.ቁ 984<br />

የዝግጅት ክፍሉ<br />

ስልክ +251 922 11 17 62<br />

+251 913 05 69 42<br />

+251 118-44 08 40<br />

ፖ.ሳ.ቁ፡ 4222<br />

ኢሜይል፡- udjparty@gmail.com<br />

andinet@andinet.org<br />

ፋክስ ቁጥር፡- +251-111226288<br />

www.andinet.org.et<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ መስከረም 23 2004 ዓ.ም.<br />

ርዕሰ አንቀፅ<br />

ያለማቋረጥ እያደገ ያለው የዋጋ ንረት<br />

መልህቅ ይበጅለት<br />

ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ የሃገራችን የገበያ ሁኔታ ይበልጥ እየተቃወሰና ከቀን ወደ ቀን እየታመሰ<br />

ቀጥሏል፡፡ የሕብረተሰቡ የኑሮ ሁኔታም ከድጡ ወደ ማጡ እየሆነበት መሠረታዊ የሆኑ የዕለት<br />

ፍላጎቶችን ማሟላት እየቸገረው ነው፡፡<br />

በ1997 ዓ.ም 6.8% የነበረው የዋጋ ንረት በተከታዮቹ ሁለት አመታት 12.3 በመቶ እና 15. 8<br />

በመቶ ደረሰ፡፡ ይህም ማለት የንረቱ እድገት መጠን በሁለት ዓመት ውስጥ 132 በመቶ ሆነ ማለት<br />

ነው፡፡ ከ1999 ዓ.ም በኋላ ያሉት አራት ዓመታት አጠቃላይ የዋጋ ንረት መጠንን ስንመለከት<br />

ደግሞ 1999 ላይ 15.8 በመቶ የነበረው በ2003 ዓ.ም 57 በመቶ ደርሷል፡፡ ይህም አጠቃላይ<br />

የአራት ዓመት የዋጋ ንረት እድገቱን 36ዐ.7 ፕርሰንት መድረሱን ያመላክታል፡፡<br />

ከ1997 ዓ.ም ጀምሮ ያሉትን ስድስት ዓመታት አጠቃላይ የዋጋ ንረት እድገት ስንመለከት<br />

ደግሞ 714% ይሆናል፡፡ ይህም ማለት የገንዘብ የመግዛት አቅም ባለፉት ስድስት ዓመታት በ714<br />

ፕርሰንት ወድቋል ማለት ነው፡፡<br />

በአንፃሩ አማካይ ዓመታዊ ገቢ በ1997 ዓ.ም 165 ዶላር የነበረ ሲሆን አሁን 35ዐ ዶላር<br />

እንደደረሰ የአይኤም ኤፍ ሪፖርት ያመለክታል፡፡ ባለፉት ስድስት ዓመታት አማካይ አመታዊ ገቢ<br />

በ112 በመቶ አድጓል ማለት ነው፡፡<br />

ከላይ ከተመለከቱት መረጃዎች የምንረዳው በስድስት ዓመቱ የገቢ እድገትና የዋጋ ንረት<br />

እድገት መካከል የ602 በመቶ ልዩነት እንዳለ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ<br />

በ1999 ዓ.ም ይኖር የነበረውን ኑሮ ዛሬ ለመኖር እንዲችል የዋጋ ንረቱ ከ14.4 በመቶ መብለጥ<br />

አልነበረበትም ወይም አማካይ አመታዊ ገቢ 1171.5 ዶላር መድረስ ነበረበት፡፡<br />

በሃብታሙና በድሃው ዜጋ መካከል ያለው የሃብት ክፍተት እየሰፋ መሄድ እንዳለ ሆኖ<br />

የኢትዮጵያውያን የድህነት ደረጃ ባለፉት ስድስት ዓመታት በ324.7 በመቶ እንዳደገ መረዳት<br />

ይቻላል፡፡ ይህንን አሰቃቂ ሁኔታ ይበልጥ አስፈሪ የሚያደርገው ገዢው ፓርቲ ችግሩን ለማስወገድ<br />

ቀርቶ ባለበት እንኳን ለማስቆም አለመቻሉ ነው፡፡ እየወሰዳቸው ያሉት ርምጃዎችም አስተውሎት<br />

የጎደላቸው በመሆናቸው ችግሩን የበለጠ ሲያባብሱት እንጂ ሲቀንሱት አልታዩም፡፡<br />

የኢኮኖሚ ኃይሎች (ፍላጎትና አቅርቦት) ገበያውን መምራት ሲሳናቸው መንግሥት ጣልቃ<br />

ገብቶ ማረጋጋት እንዳለበት እምነታችን ነው፡፡ ይህ ሲባል ግን መንግሥት የገበያ ኃይሎችን<br />

መቆጣጠር ወይም መተካት አለበት ማለት አይደለም፡፡ በትክክል መሥራት እንዲችሉ የሚረዱ<br />

የፊስካልና የገንዘብ ፖሊሲዎችን ተግባራዊ በማድረግ የኢኮኖሚውን አቅም ያጠናክራል እንጂ፡፡<br />

በእርግጥ ገዢው ፓርቲ ገበያውን ለማረጋጋት የተለያዩ የፖሊሲና የቀጥተኛ ጣልቃ ገብነት<br />

ርምጃዎችን ወስዷል፡፡ እዚህ ላይ የሚነሳው ዋናው ጥያቄ ታዲያ ለምን የዋጋ ንረቱ የበለጠ<br />

እየተባባሰ ሄዴ? የሚለው ነው፡፡<br />

የኢህአዴግ መሠረታዊ ችግር የችግሩን መነሻ ለይቶ ለማወቅ አለመቻሉ ላይ ነው፡፡ ኢህአዴግ<br />

የዋጋ ንረቱ በተከታታይ እየተመዘገበ ያለው የኢኮኖሚ እድገት የፈጠረው ነው ብሎ ያምናል፡፡<br />

እ.ኤ.አ በ1929 በአሜሪካ የተከሰተው የኢኮኖሚ ዝቅጠትን ተከትሎ የተስፋፋው<br />

የኬንዚያውያን (Keynesian) የምጣኔ ኃብት ባለሙያዎች አስተሳሰብ በምጣኔ ኃብት እድገትና<br />

በዋጋ ንረት መካከል ቀጥተኛ ግንኙነት ስለአለ መንግሥት በከፍተኛ ኢንቨስትመንትና የሥራ<br />

ዕድል ፈጠራ ኢኮኖሚውን ሲያሳድግ የሕዝብ ገቢም አብሮ ያድጋል የሚል ነው፡፡ በመሆኑም<br />

የፍጆታ ወጪ መጠን ይጨምራል፡፡ ይህም የሸቀጦችና የአገልግሎት ዋጋ እንዲንር ያደርጋል የሚል<br />

በመሆኑም ኢኮኖሚው ባደገ ቁጥር የዋጋ ንረቱም ይቀጥላል ማለት ነበር፡፡<br />

ይህ አስተሣሰብ በወቅቱ ትክክለኛ የነበረ ቢሆን በ1970ዎቹ የታየው የስራ አጥነትና የዋጋ<br />

ንረት “Stagflation” በተመሣሣይ ጊዜ በመከሰቱ (Stagflation) ውድቅ እንዲሆን አድርጎታል፡፡<br />

በሃገራችን በአሁኑ ሠዓት እየታየ ያለው ክስተትም ከ1970ዎቹ የምዕራባውያን የኢኮኖሚ ቀውስ<br />

ጋር ተመሣሣይነት አለው፡፡<br />

የዋጋ ንረቱ ሥራ አጥነቱ በእጅጉ እየተባባሱ ናቸው፡፡ ከገቢ አንፃር ሲታይም ከላይ<br />

እንደተገለፀው ባለፉት ስድስት ዓመታት ውስጥ የዋጋ ንረት በ714 በመቶ ሲያድግ ዓመታዊ ገቢ<br />

በ112 ፕርሰንት ብቻ ነው ያደገው፡፡ በመሆኑም በሃገራችን ያለው የዋጋ ንረት የኢኮኖሚው እድገት<br />

የወለደው ነው ሊባል ፈፅሞ አይችልም፡፡<br />

በአንድነት ፓርቲ ዕምነት እይታ የዋጋ ንረቱ መሠረታዊ ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው፡-<br />

1. መንግሥት ከፍተኛ ብዛት ያላቸው የገንዘብ ኖቶችን አሣትሞ በኢኮኖሚው ውስጥ<br />

መርጨቱ፣<br />

2. የመንግሥት ወጪ መጠን በከፍተኛ ደረጃ እያደገ መምጣቱ፤ ይህም በሃገር ውስጥ<br />

ምርት አቅርቦት እድገት አለመደገፉ፣<br />

3. በውጭ ምርቶች ላይ መሠረቱን የጣለው አቅርቦትና የውጭ አገር ምርቶች ዋጋ<br />

መናሩ፣<br />

4. የብር ዋጋ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየወደቀ መምጣትና የውጭ ምርት አቅርቦትና ፍላጐት<br />

አለመጣጣም፣<br />

5. የመንግሥት የነዳጅ ድጎማ መነሳት፣<br />

6. የመሠረታዊ ዕቃዎች ፍላጎትና አቅርቦት ከፍተኛ ሁኔታ አለመጣጣም፣<br />

7. መንግሥት የግሉን ዘርፍ ተክቶ አቅርቦትና ሥርጭትን ለመቆጣጠር የሚያደርገው<br />

ጥረት፣<br />

8. በግል ባንኮች ላይ ተጥሎ የነበረው የብድር ጣሪያ የአገር ውስጥ ምርትንና ከውጭ<br />

የሚገቡ ሸቀጦችን አቅርቦት መገደቡ፣<br />

9. በግል ባንኮች ላይ የተጣለው የግምጃ ቤት ሰነድ ግዢ ግዴታ የሃገር ውስጥ ምርትንና<br />

ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦች አቅርቦትን የሚገድብ መሆኑ የሚፈጥረው የአቅርቦት እጥረት፣<br />

10. በመሬት ፖሊሲው ምክንያት <strong>የመሬት</strong>ና የገበሬው ምርታማነት መቀነስ፡፡ ይህንንም<br />

ተከትሎ የሃገር ውስጥ ምርት አቅርቦትና ፍላጎት አለመጣጣም፣<br />

11. የመሠረተ ልማት ዝርጋታ ውስንነትና የዜጎች ከክልል ወደ ክልል ተንቀሳቅሶ የመሥራት<br />

መብት መገደብን ተከትሎ የምርትና የሰው ኃብት እንቅስቃሴ መወሰኑ፡፡ በዚህም ምክንያት የሰው<br />

ኃብትና ምትርት ከፍተኛ አቅርቦት ካለበት አካባቢ ወደ ከፍተኛ ፍላጎት ያለበት ቦታ ለመንቀሳቀስ<br />

አለመቻሉ በሃገራችን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ በመምጣት ላይ ላለው የዋጋ ንረትና የኑሮ ውድነት<br />

ዋነኛ ምክንያቶች ናቸው፡፡<br />

እነዚህን ችግሮች በአንክሮ ስንመለከት የሁሉም ምክንያቶች መነሻ የተዛቡ የመንግሥት<br />

ፖሊሲዎችና አስተውሎት የጎደለው የመንግሥት ጣልቃ ገብነት እንደሆነ እንረዳለን፡፡<br />

በመሆኑም መንግሥት ይህን ውስብስብ ችግር ለመፍታት ቁርጠኝነቱ ካለው በመጀመሪያ<br />

ደረጃ የልማት እስትራቴጂውና ፖሊሲዎቹ ላይ መሠረታዊ ለውጥ ሊያደርግና ከግብታዊ ጣልቃ<br />

ገብነት ሊቆጠብ ይገባል፡፡ ይህን የማያደርግ ከሆነ ግን እየተባባሰ ያለው የኑሮ ውድነትና የዋጋ ንረት<br />

ማቆሚያ የሌለው እንደሚሆንና ካሁኑ የባሰ የተወሳሰበ ሰብአዊና ማሕበራዊ ቀውስ ሊያስከትል<br />

እንደሚችል ልብ ሊል ይገባል፡፡<br />

ነፃ አስተያት<br />

2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.10<br />

“ማነው ተው<br />

የሚለኝ?!”<br />

ይድነቃቸው ዐይኔ<br />

አብዛኛዎቻችሁ የዚህን ጽሁፍ ርዕስ ስታዩ የብርሃኑ ተዘራን ማነው<br />

ተው የሚለኝ ማነው? የሚለውን ዘፈን ታስታውሱታላችሁ<br />

ብዬ እገምታለሁ፡፡ ወይም ደግሞ በሰፈራችሁ፣ በአካባቢያችሁ<br />

እና በመንደራችሁ ስፓርታዊ እንቅስቃሴን (በተለይም ክብደት<br />

ማንሳትን) ለፀብ እንጂ ለፀባይ የማይሰሩ በትዕቢት የተሞሉ<br />

ጐረምሶች እና ወጣቶች ማነው ተው የሚለኝ አፍንጫውን<br />

እለዋለሁ፤ የሚለውን አባባል በተደጋጋሚ ስለሚጠቀሙት እነሱ<br />

ትዝ ….. ብለዋችሁ ይሆናል፡፡ እኔ ግን በጽሁፌ ላስታውሳችሁ<br />

የምፈልገው፤ ከሁሉም በላይ አባባሉን በመጠቀም ላይ<br />

ስለሚገኘው እና በተግባር ስለሚያውለው እንዲሁም በዚህ<br />

ድርጊቱ አቻ ስላልተገኘለት አካል ነው፡፡<br />

የመቶ በመቶ የምርጫ ድል (ዘጠና ዘጠኝ ነጥብ ምናምን<br />

የሚለውን ቁጥር ያልተጠቀምኩት አውቄ ነው፡፡ ምክንያቱም ይህ<br />

ገለፃ፤ ምርጫው ሰማንያ በመቶ የማሸነፍ ያህል ያስመስለዋል፡፡<br />

ሥነልቡናዊ ጥቅም አላት፡፡) ከኔ በላይ ለአገሪቱ ተቆርቆሪ ወገን<br />

የለም ብሎ የሚያስብ ገዢ ፓርቲ እና ይህን ሀሳብ የመጨረሻ<br />

እውነት አድርጐ የሚቆጥር የካድሬ ጐርፍ፣ የማያባራ የምሁራን<br />

እና የዜጐች ስደት (ያውም በሬድዮ ጭምር በሚለፍፉ የውጭ አገር<br />

የሥራ ዕድል ማስታወቂያ በሚቀርብበት ሁኔታ ላይ እስክንደርስ፡<br />

፡)፣ በዘፈቀደ የተቀመጠ ግትር ፖሊሲ መቃብራቸውን መማስ፣<br />

የታዋቂ ፖለቲከኞች እና የጋዜጠኞች እስር እና ወከባ እንዲሁም<br />

ተመሳሳይ ሕዝባዊ በደሎች፤ በተጨማሪም የመልካም አስተዳደር<br />

እጦት እና የሙስና መንሰራፋት የተባባሱት እና የተበራከቱት<br />

በሌላ በማንም አይደለም፡፡ ማነው ተው የሚለኝ? ሊጠይቀኝ<br />

የሚችል ከኔ ጋር የተጠጋጋ ኃይል ያለው አካል ከወዴት አለ?<br />

እኔን የሚመጥን ጉልበተኛ ማን አለ? ከኔ በላይ አዋቂ፣ ከኔ በላይ<br />

ብልህ፣ ከኔ በላይ አስተዳዳሪ ለዘበት በሚል መንግስት እንጂ፡፡<br />

ኢሕአዴግ ከጊዜ ወደ ጊዜ ሥር እየሰደደ በመጣው ኃይሉ እና<br />

ባለው የፖለቲካ ሥልጣን ልዕልና በመጠቀም፤ በእያንዳንዱ<br />

እርምጃ እና ድርጊት ያለመጠየቅን ፀጋ ተጐናጽፏል፡፡ ምርጫው<br />

ሙሉ ለሙሉ ሊባል በሚችል መልኩ ማሸነፉን እንደ በጐ<br />

ዴሞክራሲያዊ አካሄድ ማየት፣ የፈለጉትን ሕግ በፓርላማ ማፅደቅ<br />

እና በዚህ ሕግ ሌሎችን ማሸማቀቅ እንዲሁም ማስጨነቅ፣<br />

የሌሎችን ሀሳብ እንደ መናኛ ቆጥሮ የራስን ሀሳብ ብቻ መናገር<br />

እና ማስነገር (የሀገሪቱን ትላልቅ እና ኃይል ያላቸው የመገናኛ<br />

ብዙሀንን ለራስ ብቻ በማዋል የሌሎችን ሀሳብ በመገደብ፡፡)፣<br />

ሌሎችን ባለድርሻ አካላት ሳያማክሩ አገሪቷን አደጋ ላይ ሊጥሉ<br />

የሚችሉ ፖለቲካዊ እና ሥነ ምጣኔያዊ ውሳኔዎችን ማስተላለፍ፤<br />

ተው የሚለኝ ካለ፤ ይሞክረኝ! የሚል ሀላፊነት የጐደለው<br />

መልዕክት ማስተላለፍ እንጂ ሌላ ምን ሊሆን ይችላል?<br />

በየወንዙ ዳር መቀደስ<br />

የተኛን ሴጣን ለመቀስቀስ<br />

ይህ አባባል በሁለት መስመር ቃላት ብዙ ማለት ከሚችሉ<br />

ኢትዮጵያውያት ሴቶች ከተናገሯቸው አባባሎች አንዱ እንደሆነ<br />

አምናለሁ፡፡ የእምነት ሰው ነኝ፣ የእግዚአብሄርን ስም ከኔ ወዲያ<br />

ማን ያውቃል? ከኔ በላይስ ክርስቲያን አለ? እንደው ከኔ ወዲያ<br />

ቀዳሽ በአገሪቱ ይኖር ይሆን? ብሎ በእምነት ሳይሆን በትዕቢት<br />

አለፍ ሲልም በሞኝነት የተሞላ ሰው የሚያደርገው አድራጐትን<br />

ይገልፃል አባባሉ የዚህ ሁሉ ቅዳሴ እና የእግዚአብሄርን<br />

ስም መጥራት ሰይጣንን ከመቀስቀስ አልፎ አምላክ ዘንድ<br />

እንደማይደርስ ይገልፃል አባባሉ፡፡<br />

ይህንን አባባል ከተናገሩት ቀደምት ሊቃውንት ሁለቱን መስመር<br />

ተውሼ የሰሞኑን የመንግስታችንን ድርጊት ልመዝን፡፡<br />

የፀረ- ሽብርተኝነት ሕግ አዋጁ እና ዘመቻው ሁሉንም ባለድርሻ<br />

አካላት ባግባብ እና ባሳተፈ መልኩ እንዳልተደረገ ለመናገር<br />

ኢትዮጵያዊ መሆን በቂ ነው፡፡ ከዛ ባለፈ የፓርላማን ውሎ<br />

እና ፓርላማው ነገሮችን በምን ፍጥነት አይቶ በምን ፍጥነት<br />

እንደሚያፀድቅ በቴሌቪዥን መስኮት ማየት ይበቃል፡፡<br />

ፓርቲው የሚያቀርበው ሀሳብ በሙሉ የኔ ሀሳብ ነው፡፡ ፓርቲዬ<br />

የሚያቀርበው ሀሳብ በፍፁም እኔን አደጋ ላይ አይጥለኝም፤ በሚል<br />

የራስን ሀሳብ ገሎ በሌሎች ተጨፍልቆ የማሰብ አዙሪት ውስጥ<br />

በገቡ ሰዎች፤ ስንት ማህበራዊ እና ሀገራዊ አደጋን የሚያስከትሉ<br />

ፖሊሲዎች እና አዋጆች ጸድቀዋል?<br />

በኑሮ ውድነት፣ በአንድ ፓርቲ እና በአንድ ሰው የበላይነት<br />

በዴሞክራሲ እና በብልሹ አስተዳደር እንዲሁም ቀጣይነት<br />

በሌላቸው እና ፖለቲካዊ ዓላማቸውን እስካልሳቱ ብቻ በሚጸድቁ<br />

ፖሊሲዎች የተሰላቸው ህዝብ፣ አነሰም በዛም የሚያውቃቸውን<br />

እና የሚያከብራቸውን ከመንግስት በተቃራኒው የቆሙትን<br />

ፓለቲከኞች እና ጋዜጠኞች በሽብርተኝት ታርጋ ከለላ ወደ<br />

እስር ቤት መወርወር፤ ግለሰቦቹን እና ደጋፊዎቻቸውን ብሎም<br />

ጋዜጣችን “ፍኖተ-ነፃነት” ብለናታል፡፡ “ፍኖት” ማለት መንገድ ማለት ሲሆን ከነፃነት ጋር<br />

ሲጣመር “የነፃነት መንገድ” ማለት ነው!! ወደ 7 የዞሯል

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!