24.08.2013 Views

የመሬት ቅርምት ለልማት - Ethiopia: A voice for the voiceless

የመሬት ቅርምት ለልማት - Ethiopia: A voice for the voiceless

የመሬት ቅርምት ለልማት - Ethiopia: A voice for the voiceless

SHOW MORE
SHOW LESS

Create successful ePaper yourself

Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.

8<br />

www.andinet.org.et<br />

መዝናኛ ከዝናሩ<br />

ሥጦታ<br />

ለአርቲስት ጥላሁን ገሠሠ ማስታወሻ<br />

ከሰሎሞን አድማሱ<br />

ለሀገር ዘፈነ እያለ ሀገሬ<br />

ኩራት ነበርና ሀገር በቀል ፍሬ፤<br />

“መለያየት ሞት ነው” እያለ ዘፈነ<br />

በመሞት ጥያቄ ለመሞት ወሰነ<br />

ጠግበን ሳንጨርሰው ሲለየን ፈጠነ<br />

ሁሉም ነገር በቃ እንደማይሆን ሆነ፡፡<br />

ያ ዘንባባ ማር ዘንጣፋ ሸበላ<br />

ጥላሁን ስንለው ሲሆን ነበር ጥላ<br />

በሱ ተራ ጊዜ ጥላ አጣ ከለላ<br />

ክፉ ሞት ስትወስደው ከጉያ ነጥላ<br />

የዘፈኑ ንጉስ የዛ አርበኛ ገላ<br />

ካፈር ተቀላቅሎ በምስጦች ተበላ<br />

ለካ ሰው ግብዝ ነው ሞኝ ነው ተላላ<br />

እሱን ሲያመው ጠፋን የማዳኛው መላ፡፡<br />

ከልብ ለማይጠፋው ለቁንጮው ስመ-ጥር<br />

ሁላችን ነበረን ፍፁም ልዩ ክብር<br />

ጥሌ ስለሆነ ያገር ኩራት ፍቅር፤<br />

ድምቀት ስለነበር የልብ ውስጥ አበባ<br />

ስጦታ ይሁንና የወገንህ እንባ፤<br />

ብንወድህ ነበረ ጥላሁነን ያልንህ<br />

መጣላት ፈልገን መች ጥል አሁን አልንህ<br />

ዶክተር የራስክን ነፍስ መልሳት እባክህ<br />

ናና ዝፈንልን ትስማ እስትንፋስህ<br />

በአንድ ላይ ነን ዛሬ አንተን ስንጠብቅህ<br />

ከስተሀል ጠቁረሀል እስቲ ትታይ ወዝህ፡፡<br />

ትዝታውን ትቶ እሱ አፈር ለበሰ<br />

ብርቅዬው ድንቅየው ጥላሁን ገሠሠ፤<br />

ውለታ ሳንከፍለው ስለሄደ ድንገት<br />

ሀዘንና ደስታ ባንጎራጎረበት<br />

ጥበብን በድምፁ ገልፆ ባሰማበት<br />

በጥበቧ አዳራሽ አሁን ባለንበት<br />

ቤተሰብ አድናቂው በተገናኘበት<br />

በድምቀት ይከበር የጥልዬ ልደት፡፡<br />

ምንም ሞት ቢነጥቀን ቢለየን በሥጋ<br />

መቼም መቼም መቼም ጥሌ ነው ከኛ ጋ፤<br />

ሁሉን የሚችለው አምላካችን ቸር ነው<br />

ሞገስ ክብራችንን በገነት ያኑረው፡፡<br />

በዚያ አንታለልም<br />

ሙሉነሽ አበባየሁ<br />

መንገዱን ለመስራት ግንብ ለመደርደር፣<br />

ፋሽስቱ ጣሊያንም የሌለው ነው ወደር፡፡<br />

በዚያ ሳንታለል አምስት ዓመት ታግለን፣<br />

ፋሽስቱ ጣሊያንን አስወጣን አባረን፡፡<br />

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የታየው ብልጥነት፣<br />

አሮጌን አፋርሶ አንገትን ማስደፋት፣<br />

የልማት ሲናገር መንገድና ፎቁን በቲቪ ማሣየት፡፡<br />

አቅሙን ተረዳው በዚያ አንታለልም፣<br />

አንተንም በማውረድ ወደኋላ አንልም<br />

ሆዴ ባዶ ሆኖ መላወስ ካቃተኝ፣<br />

የአስፋልቱ ስፋት አረምን ሊበጀኝ<br />

መንፈሴ ታውሮ ሲንጣለል አስፋልቱ፤<br />

ፎቆች ተደራርበው ቢሠሩ በብርቱ፣<br />

ለእኔ የማይሆን ነው ለርሃብ ጥማቱ፡፡<br />

ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ መስከረም 23 2004 ዓ.ም.<br />

“ጥሪ አይቀበልም” አዲስ ፊልም<br />

ሊመረቅ ነው!<br />

በሲኒማ ኢትዮጵያ የምሽት የሲኒማ ፕሮግራም ተጀመረ<br />

በአዲስ አበባ ሲኒማ ቤቶች አስተዳደር<br />

በተመልካች ስሜትና ፍላጐት በተመረጡ የአማርኛ<br />

ፊልሞችን ከመስከረም 19 ቀን 2004 ዓ.ም ጀምሮ<br />

ከምሽቱ 2፡30 ለተመልካች እያቀረበ መሆኑ ገለፀ፡፡<br />

ቁጥሩ እየጨመረ የመጣውና የፊልም ስራ እንዲሁም<br />

የወረፋ መጣበብን ለመቅረፍ ያግዛል ተብሎ የተዘረጋ<br />

መሆኑን ዘወትር አርብ ምሽት “ያንቺው ሌባ”<br />

ቅዳሜ በድጋሚ ቀረፃና በባለሙያዎች አስተያየት<br />

ተስተካክሎ የቀረበው “መፈንቅለ ሴቶች” እሁድ<br />

“መካኒኩ” ፊልሞች ለተከታታይ 2 ወራት የሙከራ<br />

እና እንደሚታዩ የሲኒማ ቤቶች አስተዳደር ያገኘው<br />

መረጃ ያመለክታል፡፡ ከዚህ ቀደም ባልተለመደ<br />

አሰራር ከፊልሙ ገቢው 60% ፐርሰንት የፊልሙን<br />

ፕሮዲውሰሮች ቀሪ 40% ፐርሰንት ለሲኒማ ቤቶች<br />

መሆኑን ለማወቅ ችለናል፡፡<br />

ባህል፣ ፌስቲቫልና ባዛር ለዕይታ በቃ<br />

የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ከቢ.ቴክ የማስታወቂያ<br />

ስራ ድርጅት ጋር በመተባበር በአይነቱ ለየት ያለ<br />

የባዛርና የባህል ፌስቲቫል መስከረም 19 ቀን 2004<br />

ዓ.ም ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ታዋቂ<br />

ግለሰቦች አርቲስቶች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች<br />

በተገኙበት በጥቁር አንብሣ በሚገኘው ድላችን<br />

ሀውልት ሲከፈት ከ50 በላይ አገልግሎት ሰጭ<br />

ተቋማት ተሣትፈዋል፡፡ በዚሁ ባዛርና ፌስቲቫል<br />

ላይ የተለያዩ የሙዚቃ ዝግጅቶች የብሔር<br />

ብሔረሰቦች ጭፈራዎች፣ የፎቶ ግራፍ አውደ ርዕይ<br />

ቀርበዋል ለተከታታይ ቀናት በቆየው ዝግጅት<br />

ላይ በመዝጊያው ስነ-ስርዓት መስከረም 21 ቀን<br />

2004 ዓ.ም ምሽት 1፡00 ሰዓት ጥሪ የተደረገላቸው<br />

እንግዶች በሐርመኒ ኢንተርናሽናል ሆቴል የባህል<br />

ፋሽን ትርዒት ቀርቧል፡፡ የዘንድሮው በአለም አቀፍ<br />

ደረጃ የተከበረው የቱሪዝም ቀን ምክንያት በማድረግ<br />

ቱሪዝም ያስተሣስራል በሚል መሪ ቃል እንደ<br />

ተዘጋጀ አዘጋጆቹ ለዝግጅት ክፍላችን ገልፀዋል፡፡<br />

ለአለም የምሳሌ ዶክመንተሪ የፊልምና የፎቶ<br />

ኤግዚብሽን ተመረቀ<br />

በእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትና ወዛም<br />

ኮሙኒኬሽን ኤንድ ቢዝነስ ኃ.የተ.የግ.ማህበር በጋራ<br />

ማዘጋጃ የኢትዮጵያ ታሪክ የሚገልፅ ዶክመንተሪ<br />

ፊልም በተለያዩ ከ6 በላይ ቋንቋዎች በአማርኛ፣<br />

በእንግሊዘኛ፣ በአረብኛ፣ በፈረንሣይና በኦሮሚኛና<br />

በትግረኛ ቋንቋዎች ተሰርተው ቀረቡ፡፡ መስከረም<br />

በሚዲያ ሀውስ ፊልም ፕሮዳክሽን<br />

በደራሲ ዮሊያን ተ/ማርያም በዳሬክተር<br />

ሚሊዮን ስዩም የተሰራው “ጥሪ አይቀበልም”<br />

የተሰኘ በአይነቱ ለየት ያለ አስቂኝ ልብ<br />

አንጠልጣይ ፊልም የፊታችን እሁድ<br />

መስከረም 28 ቀን 2004 ዓ.ም ሁሉም ሲኒማ<br />

ቤቶች በአዲስ አበባ በሚገኙ ያስመርቃል፡፡<br />

በሲኒማ ሴባስትፖል፣ በሲኒማ<br />

ዮፍታሔ፣ በሲኒማ እምቢልታ፣ ሰበታ<br />

ጂም ሲኒማ፣ በደ/ዘይት ህይወት ሲኒማ እና<br />

በናዝሬት ምርምር ሲኒማ በ8፡00፣ በ10፡00<br />

እና በ12፡00 ሰዓት ለህዝብ እይታ ይበቃል፡<br />

፡ በልዩ ፕሮግራም በሲኒማ ዮፍታሔ በ8፡00<br />

ሰዓት አርቲስቶች ታዋቂ ግለሰቦች ጋዜጠኞች<br />

የኪነ-ጥበብ ወዳጆች በተገኙበት በደመቀ ስነ-<br />

ስርዓት ይመረቃል፡፡ በዚህ ፊልም ላይ ታዋቂ<br />

አርቲስቶች ተውነዋል፡፡ ተዋንያን መስፍን ኃ/<br />

እየሱስ (ጠጆ)፣ ሰለሞን ገብሬ፣ ኤልሳቤት<br />

ጌታቸው (ቀጮ)፣ ፈዮሪ ሀይሌ፣ ዳንኤል<br />

ወንድወሰን ሚኪያስ ታምሬ እና ናርዶስ<br />

በርሄ ሌሎችም ከ25 በላይ ወጣትና አንጋፋ<br />

ተዋንያኖች ተውነውበታል፡፡ የፊልሙ<br />

ርዝመት 1፡39 ደቂቃ ሲወስድ ፊልሙን ሰርቶ<br />

ከማጠናቀቅ 1 ዓመት ከ6 ወር ጊዜ ሲወስድ<br />

ከ450.000 /ከአራት መቶ አምሣ ሺህ ብር<br />

በላይ ሲወስድ የፊልሙ ታሪክ በተለያዩ<br />

ምክንያቶች ከስራ ገበታቸው የተፈናቀሉ<br />

ወጣቶች በአቋራጭ ለመበልፀግ የሚያደርጉት<br />

የሕይወት ውጣ ውረድን ያሳያል፡፡<br />

21 ቀን በሚሊኒየም አዳራሽ የሃይማኖት አባቶች<br />

ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣኖች ጥሪ የተደረገላቸው<br />

እንግዶች ሲከፈት ለተከታይ ቀናቶች በሚቆየው<br />

ኤግዚብሽን ታሪካዊ ቦታዎች በፎቶና በምስል የታገዘ<br />

ስለ ሀይማኖቶች እንደተዘጋጀ በመክፈቻው ዕለት<br />

ተገልፆል፡፡<br />

የአደባባይ ምስጢሮች<br />

ጋሻው<br />

2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.10<br />

የተገላቢጦሽ<br />

አበው ወደ አንድ ቁም ነገር ወዳለው ጉዳይ ለማምራት<br />

ሲፈልጉ “ወግን ወግ ያንጋጋዋል” ይላሉ፡፡ እኔም የዘመኑ ክፋትና<br />

ጭካኔ ጥላ አጥልቶብኝ እየገረመኝ በጥልቀት ስመለከት የበለጠ<br />

ርቄ በሐሳብ እመሰጣለሁኝ፡፡ ብዙ ጊዜ የሚሆነው ሣይሆን<br />

ሲቀርና የማይሆነው ሲሆን ሣይ ሁሉም ነገር የተገላቢጦሽ<br />

ይሆንብኛል፡፡ በልጅነቴ በተወለድኩበት አካባቢ አዛውንቶች<br />

የማይሆንና ያልጠበቁት ነገር ሲሆን ሲያዩ “የተገላቢጦሽ ! ይሉ<br />

ነበር ሼህ ሙሄ” ሲሉ እሰማ ነበር፡፡ ሸህ ሙሄ በተረት መልክም<br />

ይሁን በምሳሌዊ አነጋገር ብቻ በሆነ አጋጣሚ “ሸህ ሙሄ<br />

እንዲህ ብለው ነበር” እየተባለ ይነገራል፡፡ አለቃ ገ/ሐና፣ ሁሴን<br />

ጂብሪል እንዲህ ተናግረው ነበር፡፡ እየተባሉ እንደሚጠቀሱት<br />

ማለት ነው፡፡ እኔም በትዝታ ልጓም ተስቤ ጊዜ ጎትቶ ወስዶ<br />

እኔ ከነበርኩበት ዘመን አልፌ ከሸህ ሜሄ ዘሌ ዘመን በመግባት<br />

በልጅነቴ እሳቸው ተናገሩት የሚባለው ተረት መሰል ቁምነገር<br />

ትውስታ ውሰጥ ገባሁ፡፡<br />

ሸህ ሙሄ ዘሌ የተባሉ አዛውንት ነበሩ፡፡ እኒህ አዛውንት<br />

በረመዳን ፆም ከሚኖሩበት ራቅ ካለ አገር የቅርብ ዘመዳቸው<br />

የሆነ ይሞትና ከዚያ ቀብር ውለው ወደ ቤታቸው ሲመለሱ<br />

“ምሳ አቆይኝ” ከተባለ ቦታ ይደርሳሉ፡፡<br />

ምሳ አቆይኝ እንደ እንጨት የቆመ አቀበት ሲሆን ያንን<br />

የገረረ አቀበት ለመውጣት ወገብን አጉብጦ ሰለሚለቅ ከታች<br />

ከቆላው አገር ውለው ወደ ላይ የሚወጡ መንገደኞች ምሳ<br />

አቆይኝ ሲደርሱ ከድካማቸው ጋር ርሃብም ሰለሚይዛቸው<br />

“ምሳ- አቆይኝ!” ብለው የጥንት አባቶች ስም እንዳወጡለት<br />

ይተረካል፡፡ እውነትም የምሳ አቆይኝ ጋራ ጉልበትን የሚፈትን<br />

ነው፡፡ በተለይም በእድሜአቸው ለገፉ አዛውንቶች በቀላሉ<br />

የሚወጡት አይደለም፡፡ ከምሳም አልፎ ራት አቆይኝ<br />

የሚያስብል ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ምሳ አቆይኝ አካባቢ<br />

መንደር የሚባል ስለሌለ ጥቅጥቅ ያለደን በመሆኑ ከመሸ<br />

በኋላ ብቻን ያንን አቀበት ለመውጣት የሚታሰብ አይደለም፡<br />

፡ ጅቦች በየጥጋጥጉ ጉሬቸውን ሠርተው ስላሉ ከመዘነጣጠል<br />

አይመለሱም እየተባለ ይፈራል፡፡ በመሆኑም ሸህ ሙሄ ዘሌ<br />

ከዘመዳቸው ልቅሶ ውለው የማታ ማታ ወደ በመንገድ የደከመ<br />

ጉልበታቸው ከፆም ጋር ተዳምሮ ከስር ሆነው አንጋጠው ያንን<br />

አቀበት ሲመለከቱት አሞታቸው ፍስስ ይላል፡፡<br />

ሸህ ሙሄ ካንድ ዛፍ ስር አረፍ ብለው ያንን የገጠጠ<br />

አቀበት እንዴት እንደሚወጡት ሲያምሰላስሉ አንድ ሐሳብ<br />

ይመጣላቸዋል፡፡ አላህን አጥብቀው ቢማፀኑት ያንን እንደ<br />

እንጨት የቆመ አቀበት አንከብክቦ የሚያ ወጣቸው ሰጋር<br />

በቅሎ እንደሚሰጣቸው! ያምናሉ እናም “ለአላህ ምን<br />

ይገደዋል!” ይሉና በርከክ ብለው፡-<br />

“አላህ አምጣ ግራጫ ያቀበት መውጫ<br />

ዋርዳ በቅሎ አምጣ ይህን አቀበት ይዞ<br />

ሚወጣ! “በማለት በግንባራቸው እየተደፉና<br />

እየተነሱ አላህን ይማፀኑ ጀመር፡፡<br />

አንድ ገበሬ ደግሞ እህል ሸመታ ገበያ ውሎ ባህያውም<br />

ጥርቅ አድርጎ ጭኖ እሱም የተወሰነውን በትከሻው ተሸክሞ<br />

ሲጓዝ አህያውን ከልክ በላይ ጭኖት ስለነበር ይደክምበታል፡<br />

፡ በዚህ ላይ ምሽቱ ይቃረባል፡፡ እንደምንም ያህያውን ቂጥ<br />

እየገፋ፣ አንዳንድ ጊዜም በሽመል እየነረተ አንፏቆ ምሳ አቆይኝ<br />

ይደርሳል፡፡ የምሽቱ ጥላ ጋራውንና የጋራውን ዙሪያ ጥላ<br />

አጥልቶበታል፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ደግሞ ጅቦች ከያደፈጡበት<br />

ብቅ ብቅ ማለታቸው የማይቀር በመሆኑ እስከነ አህያው<br />

ዝንጥልጥል እንደሚያደርጉት ያውቃል፡፡<br />

“ፈጣሪ የ፤ ፈጥረህ እስከነ አህያዬ ለተራበ ጅብ አትስጠኝ!<br />

ከጉድ አውጣኝ! ቢቻል ጌታ የሌለው ጠብደል አህያ፣ ካልሆነ<br />

ደግሞ የምሳ አቆይኝን ዳገት የሚያወጣኝ አንድ ጠብደል<br />

ጎራዳማን (ወጠምሻ) አምጣልኝ” በማለት እግዚአብሔርን<br />

እየተማፀነ ያህያውን ቂጥ እየገፋ ሸህ ሙሄ ዘሌ ተንበርክከው<br />

ከሚማፀኑበት ይደርሳል፡፡ አህያው በረጅሙ ተነፈሰና ሸህ<br />

ሙሄን ከሽመልና ከጭነት ያድኑኝ የሚል ይመስል ቀጥ ብሎ<br />

ይቆማል፡፡<br />

ሸህ ሙሄ ከኋላቸው ኮቲ ሰምተው መለስ ብለው ሲያዩ<br />

አንድ ሰው አህያ ጭኖ እሱምተሸክሞ ካጠገባቸው ቁሞ ያያሉ፡<br />

፡ ከተንበረከኩበት ይነሱና፡-<br />

“አላህ ሰጋር በቅሎ ስጠኝ ብልህ የተጫነ አህያ<br />

ትሰጠኝ? እንግዲህ ያንተ ስጦታ ከሆነ እቀበላለሁ፤ ይህን<br />

ወደ የዞሯል

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!