የመሬት ቅርምት ለልማት - Ethiopia: A voice for the voiceless
የመሬት ቅርምት ለልማት - Ethiopia: A voice for the voiceless
የመሬት ቅርምት ለልማት - Ethiopia: A voice for the voiceless
Create successful ePaper yourself
Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.
8<br />
www.andinet.org.et<br />
መዝናኛ ከዝናሩ<br />
ሥጦታ<br />
ለአርቲስት ጥላሁን ገሠሠ ማስታወሻ<br />
ከሰሎሞን አድማሱ<br />
ለሀገር ዘፈነ እያለ ሀገሬ<br />
ኩራት ነበርና ሀገር በቀል ፍሬ፤<br />
“መለያየት ሞት ነው” እያለ ዘፈነ<br />
በመሞት ጥያቄ ለመሞት ወሰነ<br />
ጠግበን ሳንጨርሰው ሲለየን ፈጠነ<br />
ሁሉም ነገር በቃ እንደማይሆን ሆነ፡፡<br />
ያ ዘንባባ ማር ዘንጣፋ ሸበላ<br />
ጥላሁን ስንለው ሲሆን ነበር ጥላ<br />
በሱ ተራ ጊዜ ጥላ አጣ ከለላ<br />
ክፉ ሞት ስትወስደው ከጉያ ነጥላ<br />
የዘፈኑ ንጉስ የዛ አርበኛ ገላ<br />
ካፈር ተቀላቅሎ በምስጦች ተበላ<br />
ለካ ሰው ግብዝ ነው ሞኝ ነው ተላላ<br />
እሱን ሲያመው ጠፋን የማዳኛው መላ፡፡<br />
ከልብ ለማይጠፋው ለቁንጮው ስመ-ጥር<br />
ሁላችን ነበረን ፍፁም ልዩ ክብር<br />
ጥሌ ስለሆነ ያገር ኩራት ፍቅር፤<br />
ድምቀት ስለነበር የልብ ውስጥ አበባ<br />
ስጦታ ይሁንና የወገንህ እንባ፤<br />
ብንወድህ ነበረ ጥላሁነን ያልንህ<br />
መጣላት ፈልገን መች ጥል አሁን አልንህ<br />
ዶክተር የራስክን ነፍስ መልሳት እባክህ<br />
ናና ዝፈንልን ትስማ እስትንፋስህ<br />
በአንድ ላይ ነን ዛሬ አንተን ስንጠብቅህ<br />
ከስተሀል ጠቁረሀል እስቲ ትታይ ወዝህ፡፡<br />
ትዝታውን ትቶ እሱ አፈር ለበሰ<br />
ብርቅዬው ድንቅየው ጥላሁን ገሠሠ፤<br />
ውለታ ሳንከፍለው ስለሄደ ድንገት<br />
ሀዘንና ደስታ ባንጎራጎረበት<br />
ጥበብን በድምፁ ገልፆ ባሰማበት<br />
በጥበቧ አዳራሽ አሁን ባለንበት<br />
ቤተሰብ አድናቂው በተገናኘበት<br />
በድምቀት ይከበር የጥልዬ ልደት፡፡<br />
ምንም ሞት ቢነጥቀን ቢለየን በሥጋ<br />
መቼም መቼም መቼም ጥሌ ነው ከኛ ጋ፤<br />
ሁሉን የሚችለው አምላካችን ቸር ነው<br />
ሞገስ ክብራችንን በገነት ያኑረው፡፡<br />
በዚያ አንታለልም<br />
ሙሉነሽ አበባየሁ<br />
መንገዱን ለመስራት ግንብ ለመደርደር፣<br />
ፋሽስቱ ጣሊያንም የሌለው ነው ወደር፡፡<br />
በዚያ ሳንታለል አምስት ዓመት ታግለን፣<br />
ፋሽስቱ ጣሊያንን አስወጣን አባረን፡፡<br />
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የታየው ብልጥነት፣<br />
አሮጌን አፋርሶ አንገትን ማስደፋት፣<br />
የልማት ሲናገር መንገድና ፎቁን በቲቪ ማሣየት፡፡<br />
አቅሙን ተረዳው በዚያ አንታለልም፣<br />
አንተንም በማውረድ ወደኋላ አንልም<br />
ሆዴ ባዶ ሆኖ መላወስ ካቃተኝ፣<br />
የአስፋልቱ ስፋት አረምን ሊበጀኝ<br />
መንፈሴ ታውሮ ሲንጣለል አስፋልቱ፤<br />
ፎቆች ተደራርበው ቢሠሩ በብርቱ፣<br />
ለእኔ የማይሆን ነው ለርሃብ ጥማቱ፡፡<br />
ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ መስከረም 23 2004 ዓ.ም.<br />
“ጥሪ አይቀበልም” አዲስ ፊልም<br />
ሊመረቅ ነው!<br />
በሲኒማ ኢትዮጵያ የምሽት የሲኒማ ፕሮግራም ተጀመረ<br />
በአዲስ አበባ ሲኒማ ቤቶች አስተዳደር<br />
በተመልካች ስሜትና ፍላጐት በተመረጡ የአማርኛ<br />
ፊልሞችን ከመስከረም 19 ቀን 2004 ዓ.ም ጀምሮ<br />
ከምሽቱ 2፡30 ለተመልካች እያቀረበ መሆኑ ገለፀ፡፡<br />
ቁጥሩ እየጨመረ የመጣውና የፊልም ስራ እንዲሁም<br />
የወረፋ መጣበብን ለመቅረፍ ያግዛል ተብሎ የተዘረጋ<br />
መሆኑን ዘወትር አርብ ምሽት “ያንቺው ሌባ”<br />
ቅዳሜ በድጋሚ ቀረፃና በባለሙያዎች አስተያየት<br />
ተስተካክሎ የቀረበው “መፈንቅለ ሴቶች” እሁድ<br />
“መካኒኩ” ፊልሞች ለተከታታይ 2 ወራት የሙከራ<br />
እና እንደሚታዩ የሲኒማ ቤቶች አስተዳደር ያገኘው<br />
መረጃ ያመለክታል፡፡ ከዚህ ቀደም ባልተለመደ<br />
አሰራር ከፊልሙ ገቢው 60% ፐርሰንት የፊልሙን<br />
ፕሮዲውሰሮች ቀሪ 40% ፐርሰንት ለሲኒማ ቤቶች<br />
መሆኑን ለማወቅ ችለናል፡፡<br />
ባህል፣ ፌስቲቫልና ባዛር ለዕይታ በቃ<br />
የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ከቢ.ቴክ የማስታወቂያ<br />
ስራ ድርጅት ጋር በመተባበር በአይነቱ ለየት ያለ<br />
የባዛርና የባህል ፌስቲቫል መስከረም 19 ቀን 2004<br />
ዓ.ም ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ታዋቂ<br />
ግለሰቦች አርቲስቶች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች<br />
በተገኙበት በጥቁር አንብሣ በሚገኘው ድላችን<br />
ሀውልት ሲከፈት ከ50 በላይ አገልግሎት ሰጭ<br />
ተቋማት ተሣትፈዋል፡፡ በዚሁ ባዛርና ፌስቲቫል<br />
ላይ የተለያዩ የሙዚቃ ዝግጅቶች የብሔር<br />
ብሔረሰቦች ጭፈራዎች፣ የፎቶ ግራፍ አውደ ርዕይ<br />
ቀርበዋል ለተከታታይ ቀናት በቆየው ዝግጅት<br />
ላይ በመዝጊያው ስነ-ስርዓት መስከረም 21 ቀን<br />
2004 ዓ.ም ምሽት 1፡00 ሰዓት ጥሪ የተደረገላቸው<br />
እንግዶች በሐርመኒ ኢንተርናሽናል ሆቴል የባህል<br />
ፋሽን ትርዒት ቀርቧል፡፡ የዘንድሮው በአለም አቀፍ<br />
ደረጃ የተከበረው የቱሪዝም ቀን ምክንያት በማድረግ<br />
ቱሪዝም ያስተሣስራል በሚል መሪ ቃል እንደ<br />
ተዘጋጀ አዘጋጆቹ ለዝግጅት ክፍላችን ገልፀዋል፡፡<br />
ለአለም የምሳሌ ዶክመንተሪ የፊልምና የፎቶ<br />
ኤግዚብሽን ተመረቀ<br />
በእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትና ወዛም<br />
ኮሙኒኬሽን ኤንድ ቢዝነስ ኃ.የተ.የግ.ማህበር በጋራ<br />
ማዘጋጃ የኢትዮጵያ ታሪክ የሚገልፅ ዶክመንተሪ<br />
ፊልም በተለያዩ ከ6 በላይ ቋንቋዎች በአማርኛ፣<br />
በእንግሊዘኛ፣ በአረብኛ፣ በፈረንሣይና በኦሮሚኛና<br />
በትግረኛ ቋንቋዎች ተሰርተው ቀረቡ፡፡ መስከረም<br />
በሚዲያ ሀውስ ፊልም ፕሮዳክሽን<br />
በደራሲ ዮሊያን ተ/ማርያም በዳሬክተር<br />
ሚሊዮን ስዩም የተሰራው “ጥሪ አይቀበልም”<br />
የተሰኘ በአይነቱ ለየት ያለ አስቂኝ ልብ<br />
አንጠልጣይ ፊልም የፊታችን እሁድ<br />
መስከረም 28 ቀን 2004 ዓ.ም ሁሉም ሲኒማ<br />
ቤቶች በአዲስ አበባ በሚገኙ ያስመርቃል፡፡<br />
በሲኒማ ሴባስትፖል፣ በሲኒማ<br />
ዮፍታሔ፣ በሲኒማ እምቢልታ፣ ሰበታ<br />
ጂም ሲኒማ፣ በደ/ዘይት ህይወት ሲኒማ እና<br />
በናዝሬት ምርምር ሲኒማ በ8፡00፣ በ10፡00<br />
እና በ12፡00 ሰዓት ለህዝብ እይታ ይበቃል፡<br />
፡ በልዩ ፕሮግራም በሲኒማ ዮፍታሔ በ8፡00<br />
ሰዓት አርቲስቶች ታዋቂ ግለሰቦች ጋዜጠኞች<br />
የኪነ-ጥበብ ወዳጆች በተገኙበት በደመቀ ስነ-<br />
ስርዓት ይመረቃል፡፡ በዚህ ፊልም ላይ ታዋቂ<br />
አርቲስቶች ተውነዋል፡፡ ተዋንያን መስፍን ኃ/<br />
እየሱስ (ጠጆ)፣ ሰለሞን ገብሬ፣ ኤልሳቤት<br />
ጌታቸው (ቀጮ)፣ ፈዮሪ ሀይሌ፣ ዳንኤል<br />
ወንድወሰን ሚኪያስ ታምሬ እና ናርዶስ<br />
በርሄ ሌሎችም ከ25 በላይ ወጣትና አንጋፋ<br />
ተዋንያኖች ተውነውበታል፡፡ የፊልሙ<br />
ርዝመት 1፡39 ደቂቃ ሲወስድ ፊልሙን ሰርቶ<br />
ከማጠናቀቅ 1 ዓመት ከ6 ወር ጊዜ ሲወስድ<br />
ከ450.000 /ከአራት መቶ አምሣ ሺህ ብር<br />
በላይ ሲወስድ የፊልሙ ታሪክ በተለያዩ<br />
ምክንያቶች ከስራ ገበታቸው የተፈናቀሉ<br />
ወጣቶች በአቋራጭ ለመበልፀግ የሚያደርጉት<br />
የሕይወት ውጣ ውረድን ያሳያል፡፡<br />
21 ቀን በሚሊኒየም አዳራሽ የሃይማኖት አባቶች<br />
ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣኖች ጥሪ የተደረገላቸው<br />
እንግዶች ሲከፈት ለተከታይ ቀናቶች በሚቆየው<br />
ኤግዚብሽን ታሪካዊ ቦታዎች በፎቶና በምስል የታገዘ<br />
ስለ ሀይማኖቶች እንደተዘጋጀ በመክፈቻው ዕለት<br />
ተገልፆል፡፡<br />
የአደባባይ ምስጢሮች<br />
ጋሻው<br />
2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.10<br />
የተገላቢጦሽ<br />
አበው ወደ አንድ ቁም ነገር ወዳለው ጉዳይ ለማምራት<br />
ሲፈልጉ “ወግን ወግ ያንጋጋዋል” ይላሉ፡፡ እኔም የዘመኑ ክፋትና<br />
ጭካኔ ጥላ አጥልቶብኝ እየገረመኝ በጥልቀት ስመለከት የበለጠ<br />
ርቄ በሐሳብ እመሰጣለሁኝ፡፡ ብዙ ጊዜ የሚሆነው ሣይሆን<br />
ሲቀርና የማይሆነው ሲሆን ሣይ ሁሉም ነገር የተገላቢጦሽ<br />
ይሆንብኛል፡፡ በልጅነቴ በተወለድኩበት አካባቢ አዛውንቶች<br />
የማይሆንና ያልጠበቁት ነገር ሲሆን ሲያዩ “የተገላቢጦሽ ! ይሉ<br />
ነበር ሼህ ሙሄ” ሲሉ እሰማ ነበር፡፡ ሸህ ሙሄ በተረት መልክም<br />
ይሁን በምሳሌዊ አነጋገር ብቻ በሆነ አጋጣሚ “ሸህ ሙሄ<br />
እንዲህ ብለው ነበር” እየተባለ ይነገራል፡፡ አለቃ ገ/ሐና፣ ሁሴን<br />
ጂብሪል እንዲህ ተናግረው ነበር፡፡ እየተባሉ እንደሚጠቀሱት<br />
ማለት ነው፡፡ እኔም በትዝታ ልጓም ተስቤ ጊዜ ጎትቶ ወስዶ<br />
እኔ ከነበርኩበት ዘመን አልፌ ከሸህ ሜሄ ዘሌ ዘመን በመግባት<br />
በልጅነቴ እሳቸው ተናገሩት የሚባለው ተረት መሰል ቁምነገር<br />
ትውስታ ውሰጥ ገባሁ፡፡<br />
ሸህ ሙሄ ዘሌ የተባሉ አዛውንት ነበሩ፡፡ እኒህ አዛውንት<br />
በረመዳን ፆም ከሚኖሩበት ራቅ ካለ አገር የቅርብ ዘመዳቸው<br />
የሆነ ይሞትና ከዚያ ቀብር ውለው ወደ ቤታቸው ሲመለሱ<br />
“ምሳ አቆይኝ” ከተባለ ቦታ ይደርሳሉ፡፡<br />
ምሳ አቆይኝ እንደ እንጨት የቆመ አቀበት ሲሆን ያንን<br />
የገረረ አቀበት ለመውጣት ወገብን አጉብጦ ሰለሚለቅ ከታች<br />
ከቆላው አገር ውለው ወደ ላይ የሚወጡ መንገደኞች ምሳ<br />
አቆይኝ ሲደርሱ ከድካማቸው ጋር ርሃብም ሰለሚይዛቸው<br />
“ምሳ- አቆይኝ!” ብለው የጥንት አባቶች ስም እንዳወጡለት<br />
ይተረካል፡፡ እውነትም የምሳ አቆይኝ ጋራ ጉልበትን የሚፈትን<br />
ነው፡፡ በተለይም በእድሜአቸው ለገፉ አዛውንቶች በቀላሉ<br />
የሚወጡት አይደለም፡፡ ከምሳም አልፎ ራት አቆይኝ<br />
የሚያስብል ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ምሳ አቆይኝ አካባቢ<br />
መንደር የሚባል ስለሌለ ጥቅጥቅ ያለደን በመሆኑ ከመሸ<br />
በኋላ ብቻን ያንን አቀበት ለመውጣት የሚታሰብ አይደለም፡<br />
፡ ጅቦች በየጥጋጥጉ ጉሬቸውን ሠርተው ስላሉ ከመዘነጣጠል<br />
አይመለሱም እየተባለ ይፈራል፡፡ በመሆኑም ሸህ ሙሄ ዘሌ<br />
ከዘመዳቸው ልቅሶ ውለው የማታ ማታ ወደ በመንገድ የደከመ<br />
ጉልበታቸው ከፆም ጋር ተዳምሮ ከስር ሆነው አንጋጠው ያንን<br />
አቀበት ሲመለከቱት አሞታቸው ፍስስ ይላል፡፡<br />
ሸህ ሙሄ ካንድ ዛፍ ስር አረፍ ብለው ያንን የገጠጠ<br />
አቀበት እንዴት እንደሚወጡት ሲያምሰላስሉ አንድ ሐሳብ<br />
ይመጣላቸዋል፡፡ አላህን አጥብቀው ቢማፀኑት ያንን እንደ<br />
እንጨት የቆመ አቀበት አንከብክቦ የሚያ ወጣቸው ሰጋር<br />
በቅሎ እንደሚሰጣቸው! ያምናሉ እናም “ለአላህ ምን<br />
ይገደዋል!” ይሉና በርከክ ብለው፡-<br />
“አላህ አምጣ ግራጫ ያቀበት መውጫ<br />
ዋርዳ በቅሎ አምጣ ይህን አቀበት ይዞ<br />
ሚወጣ! “በማለት በግንባራቸው እየተደፉና<br />
እየተነሱ አላህን ይማፀኑ ጀመር፡፡<br />
አንድ ገበሬ ደግሞ እህል ሸመታ ገበያ ውሎ ባህያውም<br />
ጥርቅ አድርጎ ጭኖ እሱም የተወሰነውን በትከሻው ተሸክሞ<br />
ሲጓዝ አህያውን ከልክ በላይ ጭኖት ስለነበር ይደክምበታል፡<br />
፡ በዚህ ላይ ምሽቱ ይቃረባል፡፡ እንደምንም ያህያውን ቂጥ<br />
እየገፋ፣ አንዳንድ ጊዜም በሽመል እየነረተ አንፏቆ ምሳ አቆይኝ<br />
ይደርሳል፡፡ የምሽቱ ጥላ ጋራውንና የጋራውን ዙሪያ ጥላ<br />
አጥልቶበታል፡፡ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ደግሞ ጅቦች ከያደፈጡበት<br />
ብቅ ብቅ ማለታቸው የማይቀር በመሆኑ እስከነ አህያው<br />
ዝንጥልጥል እንደሚያደርጉት ያውቃል፡፡<br />
“ፈጣሪ የ፤ ፈጥረህ እስከነ አህያዬ ለተራበ ጅብ አትስጠኝ!<br />
ከጉድ አውጣኝ! ቢቻል ጌታ የሌለው ጠብደል አህያ፣ ካልሆነ<br />
ደግሞ የምሳ አቆይኝን ዳገት የሚያወጣኝ አንድ ጠብደል<br />
ጎራዳማን (ወጠምሻ) አምጣልኝ” በማለት እግዚአብሔርን<br />
እየተማፀነ ያህያውን ቂጥ እየገፋ ሸህ ሙሄ ዘሌ ተንበርክከው<br />
ከሚማፀኑበት ይደርሳል፡፡ አህያው በረጅሙ ተነፈሰና ሸህ<br />
ሙሄን ከሽመልና ከጭነት ያድኑኝ የሚል ይመስል ቀጥ ብሎ<br />
ይቆማል፡፡<br />
ሸህ ሙሄ ከኋላቸው ኮቲ ሰምተው መለስ ብለው ሲያዩ<br />
አንድ ሰው አህያ ጭኖ እሱምተሸክሞ ካጠገባቸው ቁሞ ያያሉ፡<br />
፡ ከተንበረከኩበት ይነሱና፡-<br />
“አላህ ሰጋር በቅሎ ስጠኝ ብልህ የተጫነ አህያ<br />
ትሰጠኝ? እንግዲህ ያንተ ስጦታ ከሆነ እቀበላለሁ፤ ይህን<br />
ወደ የዞሯል