የመሬት ቅርምት ለልማት - Ethiopia: A voice for the voiceless
የመሬት ቅርምት ለልማት - Ethiopia: A voice for the voiceless
የመሬት ቅርምት ለልማት - Ethiopia: A voice for the voiceless
You also want an ePaper? Increase the reach of your titles
YUMPU automatically turns print PDFs into web optimized ePapers that Google loves.
6<br />
ግርማ ካሣ<br />
የሕንድ፣ የቻይናና የሳውዲ ኩባንያዎች በአገራችን<br />
ኢትዮጵያ ለእርሻ ሥራዎች ሰፊ መሬት በሊዝ እንደወሰዱ<br />
መሆናቸው በስፋት ተዘግቧል። የገዢው ፓርቲ<br />
ባለስልጣናት «ሰዎች የማይኖሩባቸው ቦታዎችን ነው<br />
<strong>ለልማት</strong> ስንል ለውጭ አገር ዜጎች የሰጠነው» ይላሉ።<br />
ተቃዋሚዎች በበኩላቸው ያለ ውዴታቸው ዜጎች<br />
እንደተፈናቀሉ ይናገራሉ፡፡ የመሬቱም “ሽያጭ” በርካሽ<br />
ዋጋ፣ እስከ 99 አመታት ላለ ረጅም ጊዜ እንደሆነ<br />
በመግለጽ፣ የገዢው ፓርቲ ኢሕአዴግን እንቅስቃሴ<br />
ጸረ-ሕዝብና የአገርን ጥቅም የሸጠ እንደሆነ አድርገው<br />
ያቀርባሉ።<br />
አንድ ጊዜ፣ ከአዲስ አበባ የመጣ አፍቃሪ<br />
ኢሕአዴግ የሆነን ሰው «መሬት ለ99 አመታት ለውጭ<br />
አገር ዜጎች ይሸጣል ይባላል። እውነት ነው ወይ?»<br />
ብዬ ጠየኩት። ለ99 አመታት ለውጭ አገር ዜጎች<br />
መሬት በሊዝ እንዳልተሸጠ፣ ቢበዛ ለ25 አመታት ብቻ<br />
ሊሆን እንደሚችል ገለጸልኝ። 25 አመት ለምን ሊሆን<br />
እንደሚችል ሲያስረዳኝ «የተሰጠውን ቦታ ኢንቨስተሮች<br />
መጀመሪያ ማልማት አለባቸው። መንገዶች ይሰራሉ።<br />
ለሰራተኞች የሚሆን በአካባቢው ትምህርት ቤቶች፣<br />
መኖሪያ ቤቶች ይሰራሉ። ይሄ አይነት ቅድመ ትርፍ<br />
ሥራዎች ሁሉ፣ ቢያንስ ከአምስት እስከ አሥር አመት<br />
ይፈጃሉ። ትርፍ ሊያገኙ የሚችሉት ከአሥር አመት በኋላ<br />
ቢሆን ነው። ያን ሁሉ ሰርተው፣ ያን ሁሉ ገንብተው፣<br />
ለእነርሱም ትርፍ የሚያገኙበት ሚዛናዊ የሆነ ተጨማሪ<br />
አሥር አሥራ አምስት አመታት መስጠት ያስፈልጋል።<br />
አለበለዚያ ኢንቨስት ላድርግ ብሎ የሚመጣ አይኖርም»<br />
ነበር ያለኝ። ይህ እንግዲህ የአንድ አፍቃሪ ኢሕአዴግ<br />
ቃል ነው። ያለኝን አለኝ እንጂ ውሎች በርግጥ 25<br />
አመታት ብቻ መሆናቸውን፣ የሚያረጋግጥበት አንዳች<br />
አይነት መረጃ አላቀረበልኝም።<br />
ከዚህ ከኢሕአዴግ ደጋፊም ሆነ ከሌላ ምንጮች፣<br />
ለውጭ አገር ዜጎች የሚሰጠው መሬት በምን ሂሳብ፣<br />
ለምን ያህል ጊዜ እንደሆነ በተጨባጭ በመረጃ<br />
የተገለጸበት ቦታ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ላገኝ<br />
አልቻልኩም ነበር።<br />
ሱልጣን ኢብራሂም አሰብን ለጣሊያኖች እንደ<br />
ሸጠ፣ የአገራችን መሬት፣ እኛ በማናውቀው መንገድ<br />
ለውጭ አገር ዜጎች እየተቸበቸበ ይሆን? ከአመታት<br />
በኋላ ኢትዮጵያ የሕንዶችና የቻይናዎች አገር<br />
ትሆን ይሆን? አይናችን እያየ በልማት ስም ብሄራዊ<br />
ጥቅማችን እየተሸረሸረ ይሆን? ወይንስ ጥቅም ላይ<br />
ያልዋለ መሬቶችን ጥቅም ላይ በማዋል፣ ለዜጎች የሥራ<br />
እድል የሚከፍቱ፣ እህል በአገራችን ገበያዎች በብዛት<br />
እንዲኖሩ የሚያደርጉ፣ የስንዴም የጤፍ የስኳርን ዋጋ<br />
የሚያስቀንሱ፣ ገጠሪቷ ኢትዮጵያን የሚያለሙ፣ ጸረ-<br />
ድህነትና አገር ጠቃሚ ተግባራት ነው እየተሰሩ ያሉት?<br />
በቅርቡ በሰሜን አሜሪካ የሚንቀሳቀስ የአዲሲቷ<br />
ኢትዮጵያ ሶሊዳሪቲ ንቅናቄ የሚባል የሲቪክ ማህበር፣<br />
እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ለብዙ ጊዜ ማወቅ የምፈልገውን፣<br />
ከላይ ለጠቀስኳቸው ጥያቄዎች አንዳንድ ምላሽ<br />
የሚሰጥን መረጃ ይፋ አድርጓል። የአዲሲቷ ኢትዮጵያ<br />
ሶሊዳሪቲ ንቅናቄ አክቲቪስቶች፣ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ<br />
ሊያውቀው፣ ሊመረምረው፣ መላ ሊፈልግለት<br />
የሚገባውን ይህ አይነቱን ቁልፍ መረጃ አቀናብረው፣<br />
ይፋ ማድረጋቸው በጣም ሊያስመሰግናቸው የሚገባ<br />
ትልቅ ተግባር ነው። እጅግ በጣም ትልቅ ሥራ ነው<br />
የሰሩት።<br />
ያልሆነውን ሆነ በማለት፣ በስሜት በመነዳት ብቻ<br />
መቃወም ሳይሆን፣ ይህ አይነቱን ጥናታዊ፣ በእውነት<br />
ላይ የተመሰረተ፣ ማንም ጥሩ አእምሮ አለኝ የሚል ዜጋን<br />
አእምሮ የሚቆረቁር መረጃዎችን ማሰባሰብና ለሕዝብ<br />
ማሳወቅ፣ ተቃዋሚዎች በዋናነት ሊሰሩት የሚገባ ትልቅ<br />
ተግባር ነው። የአዲሲቷ ኢትዮጵያ ሶሊዳሪቲ ይህንኑ<br />
ነው ያደረገው።<br />
ሶሊዳሪቲ ይፋ ካደረጋቸው መረጃዎች መካከል፣<br />
ምን ያህል መሬት፣ በየትኛው ክልል በሊዝ እንደተሰጠ፣<br />
ለማን እንደተሰጠ፣ በምን ያህል ዋጋ እንደተሰጠ<br />
የሚገልጹ፣ የመንግስት ባለስልጣናት የፈረሙበትና<br />
ማህተማቸውን የመቱበት፣ ሊካዱ የማይችሉ፣<br />
የማያከራክሩ የሕግ ሰነዶች ይገኙበታል።<br />
ለውጭ አገር ዜጎች የተሰጠው መሬት ስፋት<br />
ለኢትዮጵያውያን በሊዝ የተሰጡትን መሬቶች<br />
ለጊዜው ትተናቸው፣ ለውጭ አገር ዜጎች የተሰጡት<br />
www.andinet.org.et<br />
ፍኖተ ነፃነት ማክሰኞ መስከረም 23 2004 ዓ.ም.<br />
መሬቶች ብቻ ብንመለከት፣ ለቻይና ኩባንያ 25000<br />
ሄክታር፣ ለሳውዲ ኩባኒያ 10000 ሄክታር፣ ለሕንድ<br />
ስድስት ኩባንያዎች 246,5012 ሄክታር መሬቶች በሊዝ<br />
ታድሏል።<br />
ይህንን አሃዝ አብዛኞቻችን በሚገባን መልኩ<br />
እንደሚከተለው ለማስቀመጥ እሞክራለሁ፡<br />
1. ወደ አራት ሚሊዮን ሕዝብ የሚኖሩባት የአዲስ<br />
አበባ ከተማ ስፋት 54,000 ሄክታር አካባቢ ነው።<br />
በሌላ አባባል የአዲስ አበባን አምስት ጊዜ የሚያህል<br />
መሬት ነው ለውጭ አገር ዜጎች የተሰጠው።<br />
2. በሕንድ በርካታ ፌደራል ክልሎች አሉ። ከነዚህ<br />
ክልሎች መካከል በደቡብ ምዕራብ የምትገኘው፣ ወደ<br />
34 ሚሊዮን ሕዝብ የሚኖርባት የኬራላ ክልልንና<br />
በሰሜን የምትገኛዋ ወደ 26 ሚሊዮን ሕዝብ የሚኖርባት<br />
የሃሪያና ክልል ይገኙበታል። ኬራላ ስፋቷ 3,886,300<br />
ሄክታር ስትሆን ሃሪያና 4,421,200 ሄክታር ትሰፋለች።<br />
ለውጭ አገር ኩባንያዎች የተሰጠውን መሬት<br />
ስንመለከት፣ የኬራላን ስድስት በመቶ የሃሪያናን ደግሞ<br />
5.4 በመቶ የሚሆንን መሬት ያህላል። በኬራላ የሕዝብ<br />
ብዛትን በሄክታር ብናሰላው፣ በአገራችን ለውጭ አገር<br />
ዜጎች የተሰጠውን መሬት በሚያክል የኬራላ ክልል ቦታ<br />
2,147,884 ሕዝብ ይኖራል። በሌላ አባባል 2,147,884<br />
ሊያኖር የሚችልን መሬት ነው ለውጭ አገር ዜጎች<br />
የተሰጠው።<br />
3. ሉክሳምበርግ በአውሮፓ፣ ፈረንሳይን በሰሜን<br />
ምእራብ ሆላንድንና ቤልጅየምን በሰሜን የምታዋስን<br />
አገር ናት። ስፋቷ 258,600 ሄክታር መሬት ነው።<br />
ለውጭ አገር ዜጎች በኢትዮጵያ የተሰጠው መሬት<br />
ሉክሳምበርግን የሚያክል መሬት ነው።<br />
4. በመቶ ሺሆች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን በከንቱ<br />
ያለቁበት የባድመ ይገባኛል ጦርነት ነው። የባድመ<br />
ከተማ ከዳር እስከ ዳር ከአንድ ኪሎሜትር አትበልጥም።<br />
በመሆኑም ስፋቷ ከ100 ሄክታር ያነሰ ነው ማለት<br />
ይቻላል። እንደሚታወሰው ከ100 ሄክታር በታች ለሆነ<br />
መሬት ነው፣ ያ ሁሉ የንብረት እልቂት የተከሰተው፣ ያ<br />
ሁሉ ደም የፈሰሰው። ለውጭ አገር ዜጎች የተሰጠው<br />
250,012 ሄክታር መሬት በስፋቱ፣ 2,500 ባድማዎች<br />
እንደተሰጡ የሚያስቆጥር ነው። ለአንድ ባድማ ያን<br />
ያህል መስዋእትነት ሲከፈል ለ2,500 ባድማዎች በቀላሉ<br />
መሬቶች ሲሰጡ ማየት እጅግ በጣም የሚያሳዝንና<br />
እያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ ሊያስቆጣ የሚገባ ጉዳይ<br />
ነው።<br />
ለውጭ አገር ዜጎች የተሰጠው መሬት ለምን ያህል<br />
ጊዜ እንደሆነ<br />
የተሰጠው መሬት ብዛት አሳሳቢነት እንደተጠበቀ<br />
ሆኖ፣ ለምን ያህል ጊዜ ነው ሊዙ የተፈረመው የሚለውን<br />
ጥያቄ ስናነሳ ከአዲስ አበባ መጥቶ ያነጋገርኩት አፍቃሪ<br />
ኢኮኖሚ<br />
2ኛ ዓመት ቅጽ.2 ቁ.10<br />
<strong>የመሬት</strong> <strong>ቅርምት</strong> <strong>ለልማት</strong> ወይንስ<br />
ለአገር ጉዳት?<br />
የሲ.ኤል.ሲ የሕንድ ኩባንያ ለአምሳ<br />
አመታት መሬቱን ከተጠቀመ በኋላ<br />
የሚከፍለው ጠቅላላ ዋጋ ወደ 2<br />
ሚሊዮን ብር ብቻ ሲሆን፣ ይህም<br />
በአዲስ አበባ 0.02 ካሬ ሜት<br />
ለሚያወጣ መሬት የሚከፈል ዋጋ<br />
ነው። ሌላው ከዋጋው ነገር በተገናኘ<br />
ለማንሳት የምፈልገው ሌላ ነጥብ<br />
አለ።በመሬቱ «ሽያጭ» ስምምነቶች<br />
እንደምናየው ኩባንያዎቹ የሚከፍሉት<br />
በውጭ ምንዛሪ በዶላር ወይንም ዩሮ<br />
ሳይሆን በኢትዮጵያ ብር ነው። የብር<br />
ዋጋ ካሽቆለቆለ እነርሱም የሚከፍሉት<br />
ክፍያ የዚያኑ ያህል ያሽቆለቁላል።<br />
ለምሳሌ አገሬን ለቅቄ ስደት ስጀምር፣<br />
አንድ የአሜሪካን ዶላር በ2.07 ብር<br />
ነበር የሚመነዘረው። አሁን አንድ ዶላር<br />
በ17.5 ብር ይመነዘራል...<br />
ኢሕአዴግ ከነገረኝ ጋር ፈጽሞ የማይሄድ ሆኖ ነው<br />
ያገኘሁት።<br />
ከተሰጡት መሬቶች መካከል 178, 012<br />
(71 በመቶ) ሄክታር መሬት ለአምሳ አመት ነው<br />
የተሰጠው። አሁን ላለው ትውልድ ብቻ ሳይሆን<br />
ለሚቀጥለውም ትውልድ መዘዝ የሚፈጠር ስምምነት<br />
እንደተፈረመ ነው የምናየው።<br />
እንደዚያም ሆኖ ግን በስምምነቶቹ<br />
እንደተቀመጡት የፌዴራል መንግስቱ የተሻለ ሶሲዮ<br />
ኢኮኖሚ ጥቅም ከተገኘ የስድስት ወራት ጊዜ ሰጠቶ<br />
ሊዙን መሰረዝ የሚችልበት ሁኔታ አለ። ለምሳሌ<br />
ከካሩቱሪ የሕንድ ኩባንያ ጋር በተደረገው የስምምነት<br />
ውል አንቀጽ 5.4 “The lessor has exclusive right<br />
to terminate <strong>the</strong> land lease agreement subject<br />
to at least six months prior notice in written<br />
up on <strong>the</strong> Federal Government’s decision <strong>for</strong><br />
any better socio-economic benefit” ይላል።<br />
ስለዚህ ውሉን በተፈለገ ጊዜ መሰረዝ እስከተሻለ<br />
ድረስ የውሉ ዘመን 25 ሆነ አሥር ሆነ ብዙም ስጋት<br />
ውስጥ የሚከት አይመስለኝም።<br />
ለውጭ አገር ዜጎች የተሰጠው መሬት ዋጋው<br />
ምን እንደሆነ<br />
በአሁኑ ጊዜ አዲስ አበባ ውስጥ እንደ ገርጂ<br />
በመሳሰሉ ብዙ ቦታዎች ወደ 200 ካሬ ሜትር (0.02<br />
ሄክታር) ስፋት ያለው ቤት ከሁለት ሚሊዮን ብር ያነሰ<br />
አይገኝም። አንድ ሄክታር መሬት ወደ 67 ሚሊዮን<br />
ብር ነው የሚያወጣው እንደ ማለት ነው። አስቡት …<br />
መቶ ሺህ ሄክታር መሬት ስድስት ትሪሊየን፣ ስድስት<br />
መቶ ቢሊዮን ብር ይደርሳል።<br />
ሲ.ዔል.ሲ ስፔንቴክስ ለተባለው የሕንድ ኩባንያ<br />
100,000 ሄክታር መሬት ለአምሳ አመት የተሰጠበት<br />
ዋጋ ሃያ ብር ( አንድ ዶላር ከሃያ ሳንቲም) ብቻ ነው።<br />
በአሁኑ ጊዜ በአዲስ አበባ በአንድ ተራ ምግብ ቤት፣<br />
ጥቂት ጉርሻ የሚሆን ስጋ ጣል ጣል የተደረገበት አንድ<br />
እንጀራ ወጥ ምግብ ለመመገብ 170 ብር ያወጣል።<br />
የአንድ እንጀራ ምግብ ዋጋ 8.5 ሄክታር ይገዛል።<br />
የሲ.ኤል.ሲ የሕንድ ኩባንያ ለአምሳ አመታት<br />
መሬቱን ከተጠቀመ በኋላ የሚከፍለው ጠቅላላ ዋጋ<br />
ወደ 2 ሚሊዮን ብር ብቻ ሲሆን፣ ይህም በአዲስ<br />
አበባ 0.02 ካሬ ሜት ለሚያወጣ መሬት የሚከፈል<br />
ዋጋ ነው። ሌላው ከዋጋው ነገር በተገናኘ ለማንሳት<br />
የምፈልገው ሌላ ነጥብ አለ።በመሬቱ «ሽያጭ»<br />
ስምምነቶች እንደምናየው ኩባንያዎቹ የሚከፍሉት<br />
በውጭ ምንዛሪ በዶላር ወይንም ዩሮ ሳይሆን<br />
በኢትዮጵያ ብር ነው። የብር ዋጋ ካሽቆለቆለ እነርሱም<br />
የሚከፍሉት ክፍያ የዚያኑ ያህል ያሽቆለቁላል። ለምሳሌ<br />
አገሬን ለቅቄ ስደት ስጀምር፣ አንድ የአሜሪካን ዶላር