26.05.2017 Views

Amharic (Ethiopia) translation of the Quran

Many more Islamic media to read, listen, print and download at ww.IslamicGlobe.com and at www.QuranReciter.org

Many more Islamic media to read, listen, print and download at ww.IslamicGlobe.com and at www.QuranReciter.org

SHOW MORE
SHOW LESS

You also want an ePaper? Increase the reach of your titles

YUMPU automatically turns print PDFs into web optimized ePapers that Google loves.

37|46|ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከኾነች፡፡<br />

37|47|በእርሷ ውስጥም ምታት የለባትም፡፡ እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም፡፡<br />

37|48|እነርሱም ዘንድ ዓይናቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች የኾኑ ዓይናማዎች<br />

አልሉ፡፡<br />

37|49|እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) ዕንቁላል ይመስላሉ፡፡<br />

37|50|የሚጠያየቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ፡፡<br />

37|51|ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ ይላል «እኔ ጓደኛ ነበረኝ፡፡<br />

37|52|«በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን? የሚል፡፡<br />

37|53|«በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ በእርግጥ እንመረመራለን?» (የሚል)፡፡<br />

37|54|እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል፡፡<br />

37|55|ይመለከታልም፤ በገሀነም መካከልም (ጓደኛውን) ያየዋል፡፡<br />

37|56|ይላል «በአላህ እምላለሁ፤ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር፡፡<br />

37|57|«የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር፡፡»<br />

37|58|(የገነት ሰዎች ይላሉ) «እኛ የምንሞት አይደለንምን?<br />

37|59|«የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር፡፡ እኛም የምንቅቀጣ አይደለንምን?»<br />

(ይላሉ)፡፡<br />

37|60|ይህ (ለገነት ሰዎች የተወሳው) እርሱ በእርግጥ ታላቅ ዕድል ነው፡፡<br />

37|61|ለዚህ ብጤ ሠሪዎች ይሥሩ፡፡<br />

37|62|በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?<br />

37|63|እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል፡፡<br />

37|64|እርሷ በገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፡፡<br />

37|65|እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል፡፡<br />

37|66|እነርሱም ከእርሷ በይዎች ናቸው፤ ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው፡፡<br />

37|67|ከዚያም ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅል (መጠጥ) አልላቸው፡፡<br />

37|68|ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው፡፡<br />

37|69|እነሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋልና፡፡<br />

37|70|እነሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና፡፡<br />

37|71|ከእነርሱ በፊትም የቀድሞዎቹ (ሕዝቦች) አብዛኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል፡፡<br />

37|72|በውስጣቸውም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል፡፡<br />

37|73|የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት፡፡<br />

37|74|ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡<br />

37|75|ኑሕም በእርግጥ ጠራን፡፡ ጥሪውን ተቀባዮቹም ምንኛ አማርን!<br />

37|76|እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን፡፡<br />

37|77|ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን፤<br />

37|78|በርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልካም ዝናን) ተውን፡፡<br />

37|79|«በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑሕ ላይ ይኹን፡፡»<br />

37|80|እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡<br />

37|81|እርሱ ከምእምናን ባሮቻችን ነውና፡፡<br />

37|82|ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡<br />

37|83|ኢብራሂምም በእርግጥ ከተከታዮቹ ነው፡፡<br />

231

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!