Amharic (Ethiopia) translation of the Quran
Many more Islamic media to read, listen, print and download at ww.IslamicGlobe.com and at www.QuranReciter.org
Many more Islamic media to read, listen, print and download at ww.IslamicGlobe.com and at www.QuranReciter.org
You also want an ePaper? Increase the reach of your titles
YUMPU automatically turns print PDFs into web optimized ePapers that Google loves.
87|11|መናጢውም ይርቃታል፡፡<br />
87|12|ያ ታላቂቱን እሳት የሚገባው፡፡<br />
87|13|ከዚያም በእርሷ ውስጥ አይሞትም ሕያውም አይኾንም፡፡<br />
87|14|የተጥራራ ሰው በእርግጥ ዳነ፡፡<br />
87|15|የጌታውንም ስም ያወሳና የሰገደ፡፡<br />
87|16|ይልቁንም ቅርቢቱን ሕይወት ትመርጣላችሁ፡፡<br />
87|17|መጨረሻይቱ (ሕይወት) በላጭ ሁል ጊዜ ዘውታሪም ስትኾን፡፡<br />
87|18|ይህ በፊተኞቹ መጻሕፍት ውስጥ ያልለ ነው፡፡<br />
87|19|በኢብራሂምና በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ፡፡<br />
======================================================<br />
ሱረቱ አል ጋሺያህ<br />
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው<br />
__________________________________________________________________________________________________________________<br />
88|1|የሸፋኝቱ (ትንሣኤ) ወሬ መጣህን?<br />
88|2|ፊቶች በዚያ ቀን ተዋራጆች ናቸው፡፡<br />
88|3|ሠሪዎች ለፊዎች ናቸው፡፡<br />
88|4|ተኳሳን እሳት ይገባሉ፡፡<br />
88|5|በጣም ከፈላች ምንጭ ይጋታሉ፡፡<br />
88|6|ለእነርሱ ዶሪዕ ከሚባል (እሾሃም) ዛፍ እንጅ ሌላ ምግብ የላቸውም፡፡<br />
88|7|የማያሰባ ከረኃብም የማያብቃቃ ከኾነው፡፡<br />
88|8|ፊቶች በዚያ ቀን ተቀማጣዮች ናቸው፡፡<br />
88|9|ለሥራቸው ተደሳቾች ናቸው፡፡<br />
88|10|በከፍተኛ ገነት ውስጥ ናቸው፡፡<br />
88|11|በውስጧ ውድቅን ነገር አይሰሙም፡፡<br />
88|12|በውስጧ ፈሳሾች ምንጮች አልሉ፡፡<br />
88|13|በውስጧ ከፍ የተደረጉ አልጋዎች አልሉ፡፡<br />
88|14|በተርታ የተኖሩ ብርጭቆዎችም፡፡<br />
88|15|የተደረደሩ መከዳዎችም፡፡<br />
88|16|የተነጠፉ ስጋጃዎችም (አልሉ)፡፡<br />
88|17|(ከሓዲዎች) አይመለከቱምን? ወደ ግመል እንዴት እነደተፈጠረች!<br />
88|18|ወደ ሰማይም እንዴት ከፍ እንደ ተደረገች!<br />
88|19|ወደ ተራራዎችም እንዴት እንደ ተቸከሉ!<br />
88|20|ወደ ምድርም እንዴ እንደተዘረጋች (አይመለከቱምን?)<br />
88|21|አስታውስም፤ አንተ አስታዋሽ ብቻ ነህና፡፡<br />
88|22|በእነርሱ ላይ ተሿሚ (አስገዳጅ) አይደለህም፡፡<br />
88|23|ግን (ከእውነት) የዞረና የካደ ሰው፤<br />
88|24|አላህ ታላቁን ቅጣት ይቀጣዋል፡፡<br />
88|25|መመለሻቸው ወደእኛ ብቻ ነው፡፡<br />
88|26|ከዚያም ምርመራቸው በእኛ ላይ ብቻ ነው፡፡<br />
322