Amharic (Ethiopia) translation of the Quran
Many more Islamic media to read, listen, print and download at ww.IslamicGlobe.com and at www.QuranReciter.org
Many more Islamic media to read, listen, print and download at ww.IslamicGlobe.com and at www.QuranReciter.org
Create successful ePaper yourself
Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.
51|45|መቆምንም ምንም አልቻሉም፡፡ የሚርረዱም አልነበሩም፡፡<br />
51|46|የኑሕንም ሕዝቦች ከዚህ በፊት (አጠፋን)፡፡ እነርሱ አመጸኞች ሕዝቦች ነበሩና፡፡<br />
51|47|ሰማይንም በኀይል ገነባናት፡፡ እኛም በእርግጥ ቻዮች ነን፡፡<br />
51|48|ምድርንም ዘረጋናት፡፡ ምን ያማርንም ዘርጊዎች (ነን!)<br />
51|49|ትገነዘቡም ዘንድ ከነገሩ ሁሉ ሁለት (ተቃራኒ) ዓይነትን ፈጠርን፡፡<br />
51|50|«ወደ አላህም ሽሹ፤ እኔ ለእናንተ ከርሱ ግልጽ አስጠንቃቂ ነኝና» (በላቸው)፡፡<br />
51|51|ከአላህም ጋር ሌላን አምላክ አታድርጉ፡፡ እኔ ለእናንተ ከእርሱ (የተላክሁ) ግልጽ<br />
አስፈራሪ ነኝና፡፡<br />
51|52|(ነገሩ) እንደዚሁ ነው፡፡ እነዚያን ከእነርሱ በፊት የነበሩትን ከመልክተኛ ማንም<br />
አልመጣቸውም፡፡ (እርሱ) «ድግምተኛ ወይም ዕብድ ነው» ያሉ ቢኾኑ እንጂ፡፡<br />
51|53|በእርሱ (በዚህ ቃል) አደራ ተባብለዋልን? አይደለም፤ እነርሱ ጥጋበኞች ሕዝቦች<br />
ናቸው፡፡<br />
51|54|ከእነርሱም (ክርክር) ዘወር በል፤ (ተዋቸው)፡፡ አንተ ምንም ተወቃሽ አይደለህምና፡፡<br />
51|55|ገሥጽም፤ ግሣጼ ምእመናንን ትጠቅማለችና፡፡<br />
51|56|ጋኔንንና ሰውንም ሊግገዙኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም፡፡<br />
51|57|ከነርሱም ምንም ሲሳይ አልፈልግም፡፡ ሊመግቡኝም አልሻም፡፡<br />
51|58|አላህ እርሱ ሲሳይን ሰጪ የብርቱ ኀይል ባለቤት ነው፡፡<br />
51|59|ለእነዚያም ለበደሉት እንደ ጓደኞቻቸው ፋንታ ብጤ (የቅጣት) ፋንታ አልላቸው፡፡<br />
ስለዚህ አያስቸኩሉኝ፡፡<br />
51|60|ለነዚያም ለካዱት ከዚያ ከሚቀጠሩት ቀናቸው ወዮላቸው፡<br />
======================================================<br />
ሱረቱ አል ጡር<br />
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው<br />
__________________________________________________________________________________________________________________<br />
52|1|በጡር (ጋራ) እምላለሁ፡፡<br />
52|2|በተጻፈው መጽሐፍም፡፡<br />
52|3|በተዘረጋ ብራና ላይ፤ (በተጻፈው)፡፡<br />
52|4|በደመቀው ቤትም፡፡<br />
52|5|ከፍ በተደረገው ጣራም፡፡<br />
52|6|በተመላው ባሕርም እምላለሁ፡፡<br />
52|7|የጌታህ ቅጣት በእርግጥ ወዳቂ ነው፤ (የማይቀር ነው)፡፡<br />
52|8|ለእርሱ ምንም ገፍታሪ የለውም፡፡<br />
52|9|ሰማይ ብርቱ መዞርን በምትዞርበት ቀን (ይኾናል)፡፡<br />
52|10|ተራራዎችም መኼድን በሚኼዱበት (ቀን)፡፡<br />
52|11|ለአስተባባዮችም ያን ጊዜ ወዮላቸው፡፡<br />
52|12|ለእነዚያ እነርሱ በውሸት ውስጥ የሚጫወቱ ለኾኑት፡፡<br />
52|13|ወደ ገሀነም እሳት በኀይል መግገፍተርን በሚግገፈተሩበት ቀን፡፡<br />
274