26.05.2017 Views

Amharic (Ethiopia) translation of the Quran

Many more Islamic media to read, listen, print and download at ww.IslamicGlobe.com and at www.QuranReciter.org

Many more Islamic media to read, listen, print and download at ww.IslamicGlobe.com and at www.QuranReciter.org

SHOW MORE
SHOW LESS

You also want an ePaper? Increase the reach of your titles

YUMPU automatically turns print PDFs into web optimized ePapers that Google loves.

37|84|ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ (የኾነውን አስታውስ)፡፡፡<br />

37|85|«ለአባቱና ለሕዝቦቹ ምንን ትግገዛላችሁ?» ባለ ጊዜ፡፡<br />

37|86|«ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?<br />

37|87|«በዓለማትም ጌታ ሃሳባችሁ ምንድን ነው?» አለ፡፡<br />

37|88|በከዋክብትም መመልከትን ተመለከተ፡፡<br />

37|89|«እኔ በሽተኛ ነኝም» አለ፡፡<br />

37|90|ከእርሱም የሸሹ ሆነው ኼዱ፡፡<br />

37|91|ወደ አማልክቶቻቸውም ተዘነበለ፡፡ አለም፡- «አትበሉምን?»<br />

37|92|«የማትናገሩት ለናንተ ምን አላችሁ?»<br />

37|93|በኀይል የሚመታቸውም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ፡፡<br />

37|94|ወደእርሱም (ሰዎቹ) እየሮጡ መጡ፡፡<br />

37|95|አላቸው «የምትጠርቡትን ትግገዛላችሁን?»<br />

37|96|«አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲኾን፡፡»<br />

37|97|«ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም» አሉ፡፡<br />

37|98|በእርሱም ተንኮልን አሰቡ፡፡ ዝቅተኞችም አደረግናቸው፡፡<br />

37|99|አለም «እኔ ወደ ጌታዬ ኼያጅ ነኝ፡፡ በእርግጥ ይመራኛልና፡፡»<br />

37|100|ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ፡፡<br />

37|101|ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው፡፡<br />

37|102|ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ<br />

አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ<br />

ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡<br />

37|103|ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)፡፡<br />

37|104|ጠራነውም፤ (አልነው) «ኢብራሂም ሆይ!<br />

37|105|ራእይቱን በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡<br />

37|106|ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡<br />

37|107|በታላቅ ዕርድም (መስዋዕት) ተቤዠነው፡፡<br />

37|108|በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት፡፡<br />

37|109|ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን፡፡<br />

37|110|እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡<br />

37|111|እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው፡፡<br />

37|112|በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡<br />

37|113|በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን፡፡ ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሠሪ አልለ፡፡ ለነፍሱ<br />

ግልጽ በዳይም አለ፡፡<br />

37|114|በሙሳና በሃሩን ላይም በእርግጥ ለገስን፡፡<br />

37|115|እነርሱንም ሕዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን፡፡<br />

37|116|ረዳናቸውም፡፡ እነርሱም አሸናፊዎች ነበሩ፡፡<br />

37|117|በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው፡፡<br />

37|118|ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው፡፡<br />

37|119|በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንላቸው፡፡<br />

37|120|ሰላም በሙሳና በሃሩን ላይ ይሁን፡፡<br />

232

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!