26.05.2017 Views

Amharic (Ethiopia) translation of the Quran

Many more Islamic media to read, listen, print and download at ww.IslamicGlobe.com and at www.QuranReciter.org

Many more Islamic media to read, listen, print and download at ww.IslamicGlobe.com and at www.QuranReciter.org

SHOW MORE
SHOW LESS

Create successful ePaper yourself

Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.

37|121|እኛ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡<br />

37|122|ሁለቱም በእርግጥ ከአመኑት ባሮቻችን ናቸው፡፡<br />

37|123|ኢልያስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡<br />

37|124|ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስታውስ)፤ አላህን አትፈሩምን?<br />

37|125|በዕልን ትገዛላችሁን? ከሰዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነውንም አምላክ<br />

ትተዋላችሁን?<br />

37|126|አላህን ጌታችሁንና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁን ጌታ (ትተዋላችሁን)?<br />

37|127|አስተባበሉትም፡፡ ስለዚህ እነርሱ (ለቅጣት) የሚጣዱ ናቸው፡፡<br />

37|128|ንጹሕ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡<br />

37|129|በእርሱ ላይም በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት፡፡<br />

37|130|ሰላም በኢልያሲን ላይ ይሁን፡፡<br />

37|131|እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡<br />

37|132|እርሱ በእርግጥ ከምእመናን ባሮቻችን ነው፡፡<br />

37|133|ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡<br />

37|134|እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳንናቸው ጊዜ (አስታውስ)፡፡<br />

37|135|(በቅጣቱ ውስጥ) ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር፡፡<br />

37|136|ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡<br />

37|137|እናንተም ያነጋችሁ ስትሆኑ በእነርሱ (መኖሪያዎች) ላይ (በቀን) ታልፋላችሁ፡፡<br />

37|138|በሌሊትም (ታልፋላችሁ)፤ ልብም አታደርጉምን?<br />

37|139|ዩኑስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡<br />

37|140|ወደ ተመላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡<br />

37|141|ዕጣም ተጣጣለ፡፡ ከተሸነፉትም ሆነ፡፡<br />

37|142|እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳው ዋጠው፡፡<br />

37|143|እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነም ኖሮ፤<br />

37|144|እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር፡፡<br />

37|145|እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው (በባሕር) ዳርቻ ላይ ጣልነውም፡፡<br />

37|146|በእርሱም ላይ (በአጠገቡ) ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን፡፡<br />

37|147|ወደ መቶ ሺሕ ሰዎችም (ዳግመኛ) ላክነው፡፡ ከቶውንም ይጨምራሉ፡፡<br />

37|148|አመኑም፡፡ እስከ ጊዜ ድረስም አጣቀምናቸው፡፡<br />

37|149|(የመካን ሰዎች) ጠይቃቸውም፡፡ «ለጌታህ ሴቶች ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች<br />

ይኖራልን?»<br />

37|150|ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላእክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን?<br />

37|151|ንቁ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው (የተነሳ) ይላሉ፡-<br />

37|152|«አላህ (መላእክትን) ወለደ፡፡» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፡፡<br />

37|153|በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጥን?<br />

37|154|ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ!<br />

37|155|አትገነዘቡምን?<br />

37|156|ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጅ አላችሁን?<br />

37|157|«እውነተኞች እንደ ሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» (በላቸው)፡፡<br />

233

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!