26.05.2017 Views

Amharic (Ethiopia) translation of the Quran

Many more Islamic media to read, listen, print and download at ww.IslamicGlobe.com and at www.QuranReciter.org

Many more Islamic media to read, listen, print and download at ww.IslamicGlobe.com and at www.QuranReciter.org

SHOW MORE
SHOW LESS

You also want an ePaper? Increase the reach of your titles

YUMPU automatically turns print PDFs into web optimized ePapers that Google loves.

83|21|ባለሟልዎቹ ይጣዱታል፡፡<br />

83|22|እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በድሎት (ገነት) ውስጥ ናቸው፡፡<br />

83|23|በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው ይመለከታሉ፡፡<br />

83|24|በፊቶቻቸው ላይ የድሎትን ውበት ታውቃለህ፡፡<br />

83|25|ተጣርቶ ከታተመ ጠጅ ይጠጣሉ፡፡<br />

83|26|ማተሚያው ምስክ ከኾነ፤ በዚህም ተሽቀዳዳሚዎች ይሽቀዳደሙ፡፡<br />

83|27|መበረዣውም ከተስኒም ነው፡፡<br />

83|28|ባለሟሎቹ ከእርሷ የሚጠጡላት ምንጭ ናት፡፡<br />

83|29|እነዚያ ያምመጹት በእነዚያ ባመኑት በእርግጥ ይስቁ ነበሩ፡፡<br />

83|30|በእነርሱም ላይ ባለፉ ጊዜ ይጠቃቀሱ ነበር፡፡<br />

83|31|ወደ ቤተሰቦቻቸውም በተመለሱ ጊዜ (በመሳለቃቸው) ተደሳቾች ኾነው ይመለሱ<br />

ነበር፡፡<br />

83|32|ባዩዋቸውም ጊዜ «እነዚህ በእርግጥ ተሳሳቾች ናቸው» ይሉ ነበር፡፡<br />

83|33|በነርሱ ላይ ተጠባባቂዎች ተደርገው ያልተላኩ ሲኾኑ፡፡<br />

83|34|ዛሬ (በትንሣኤ ቀን) እነዚያ ያመኑት በከሓዲዎቹ ይስቃሉ፡፡<br />

83|35|በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው የሚመለከቱ ሲኾኑ (ይስቃሉ)፡፡<br />

83|36|ከሓዲዎች ይሠሩት የነበሩትን (ዋጋ) ተመነዱን? (ይላሉ)፡፡<br />

======================================================<br />

ሱረቱ አል ኢንሺቃቅ<br />

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው<br />

__________________________________________________________________________________________________________________<br />

84|1|ሰማይ በተቀደደች ጊዜ፤<br />

84|2|ለጌታዋም (ትዕዛዝ) በሰማች ጊዜ፤ (ልትሰማ) ተገባትም፤<br />

84|3|ምድርም በተለጠጠች ጊዜ፤<br />

84|4|በውስጧ ያለውንም ሁሉ በጣለችና ባዶ በኾነች ጊዜ፤<br />

84|5|ለጌታዋም በሰማች ጊዜ፤ (መስማት) ተገባትም፤ (ሰው ሁሉ ሥራውን ይገናኛል)፡፡<br />

84|6|አንተ ሰው ሆይ! አንተ ጌታህን (በሞት) እስከምትገናኝ ድረስ ልፋትን ለፊ ነህ፤<br />

ተገናኚውም ነህ፡፡<br />

84|7|መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ፤<br />

84|8|በእርግጥ ቀላልን ምርመራ ይመረመራል፡፡<br />

84|9|ወደ ቤተሰቦቹም ተደሳች ኾኖ ይመለሳል፡፡<br />

84|10|መጽሐፉን በጀርባው ኋላ የተሰጠ ሰውማ፤<br />

84|11|(ዋ! ጥፋቴ በማለት) ጥፋትን በእርግጥ ይጠራል፡፡<br />

84|12|የተጋጋመች እሳትንም ይገባል፡፡<br />

84|13|እርሱ በቤተሰቡ ውስጥ ተደሳች ነበርና፡፡<br />

84|14|እርሱ (ወደ አላህ) የማይመለስ መኾኑን አስቧልና፡፡<br />

84|15|አይደለም (ይመለሳል)፡፡ ጌታው በእርሱ (መመለስ) ዐዋቂ ነበር፤ (ነውም)፡፡<br />

84|16|አትካዱ፤ በወጋገኑ እምላለሁ፡፡<br />

319

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!