26.05.2017 Views

Amharic (Ethiopia) translation of the Quran

Many more Islamic media to read, listen, print and download at ww.IslamicGlobe.com and at www.QuranReciter.org

Many more Islamic media to read, listen, print and download at ww.IslamicGlobe.com and at www.QuranReciter.org

SHOW MORE
SHOW LESS

Create successful ePaper yourself

Turn your PDF publications into a flip-book with our unique Google optimized e-Paper software.

75|20|(ከመጣደፍ) ተከልከል፡፡ ይልቁንም (ሰዎች) ፈጣኒቱን (ዓለም) ትወዳላችሁ፡፡<br />

75|21|መጨረሻይቱንም (ዓለም) ትተዋላችሁ፡፡ (አትዘጋጁላትም)፡፡<br />

75|22|ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፡፡<br />

75|23|ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡<br />

75|24|ፊቶችም በዚያ ቀን ጨፍጋጊዎች ናቸው፡፡<br />

75|25|በርሳቸውም ዐደጋ እንደሚሠራባቸው ያረጋግጣሉ፡፡<br />

75|26|ንቁ (ነፍስ) ብሪዎችን በደረሰች ጊዜ፤<br />

75|27|«አሻሪው ማነው?» በተባለም ጊዜ፡፡<br />

75|28|(ሕመምተኛው) እርሱ (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መልለየት መኾኑን<br />

ባረጋገጠም ጊዜ፡፡<br />

75|29|ባትም በባት በተጣበቀች ጊዜ፡፡<br />

75|30|በዚያ ቀን መነዳቱ ወደ ጌታህ (ፍርድ) ነው፡፡<br />

75|31|አላመነምም አልሰገደምም፡፡<br />

75|32|ግን አስተባበለ፤ (ከእምነት) ዞረም፡፡<br />

75|33|ከዚያም እየተንጎባለለ ወደ ቤተሰቡ ኼደ፡፡<br />

75|34|የምትጠላውን ነገር (አላህ) ያስከትልህ፡፡ ለአንተ ተገቢህም ነው፡፡<br />

75|35|ከዚያም ጥፋት ይጠጋህ ለአንተ የተገባህም ነው፡፡<br />

75|36|ሰው ስድ ኾኖ መትተውን ይጠረጥራልን?<br />

75|37|የሚፈሰስ ከኾነ የፍትወት ጠብታ አልነበረምን?<br />

75|38|ከዚያም የረጋ ደም ኾነ (አላህ ሰው አድርጎ) ፈጠረውም፡፡ አስተካከለውም፡፡<br />

75|39|ከእርሱም ሁለት ዓይነቶችን ወንድና ሴትን አደረገ፡፡<br />

75|40|ይህ (ጌታ) ሙታንን ሕያው በማድረግ ላይ ቻይ አይደለምን?<br />

======================================================<br />

ሱረቱ አል ደህር<br />

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው<br />

__________________________________________________________________________________________________________________<br />

76|1|በሰው ላይ የሚታወስ ነገር ሳይኾን ከዘመናት የተወሰነ ጊዜ በእርግጥ አልፎበታል፡፡<br />

76|2|እኛ ሰውን (በሕግ ግዳጅ) የምንሞከረው ስንኾን ቅልቅሎች ከኾኑ የፍትወት ጠብታ<br />

ፈጠርነው፡፡ ሰሚ ተመልካችም አደረግነው፡፡<br />

76|3|እኛ ወይ አመስጋኝ ወይም ከሓዲ ሲኾን መንገዱን መራነው፤ (ገለጽንለት)፡፡<br />

76|4|እኛ ለከሓዲዎች ሰንሰሎቶችንና እንዛዝላዎችን፣ እሳትንም አዘጋጅተናል፡፡<br />

76|5|በጎ አድራጊዎች መበረዣዋ ካፉር ከኾነች ጠጅ ይጠጣሉ፡፡<br />

76|6|ከእርሷ የአላህ ባሮች የሚጠጡላት (ወደፈለጉበት) ማንቧቧትን የሚያንቧቧት ከኾነች<br />

ምንጭ (ይጠጣሉ)፡፡<br />

76|7|(ዛሬ) በስለታቸው ይሞላሉ፡፡ መከራው ተሰራጪ የኾነንም ቀን ይፈራሉ፡፡<br />

76|8|ምግብንም ከመውደዳቸው ጋር ለድኻ፣ ለየቲምም፣ ለምርኮኛም ለእስረኛም ያበላሉ፡፡<br />

76|9|«የምናበላችሁ ለአላህ ውዴታ ብቻ ነው፡፡ ከእናንተ ዋጋንም ማመስገንንም አንፈልግም፡፡<br />

76|10|«እኛ (ፊትን) የሚያጨፈግግን ብርቱ ቀን ከጌታችን እንፈራለንና፤» (ይላሉ)፡፡<br />

310

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!