Amharic (Ethiopia) translation of the Quran
Many more Islamic media to read, listen, print and download at ww.IslamicGlobe.com and at www.QuranReciter.org
Many more Islamic media to read, listen, print and download at ww.IslamicGlobe.com and at www.QuranReciter.org
You also want an ePaper? Increase the reach of your titles
YUMPU automatically turns print PDFs into web optimized ePapers that Google loves.
56|12|በመጠቀሚያ ገነቶች ውስጥ ሲኾኑ፡፡<br />
56|13|ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡<br />
56|14|ከኋለኞቹም ጥቂቶች ናቸው፡፡<br />
56|15|በተታቱ አልጋዎች ላይ ይኾናሉ፡፡<br />
56|16|በእርሷ ላይ የተመቻቹና ፊት ለፊት የተቅጣጩ ሲኾኑ፡፡<br />
56|17|በእነርሱ ላይ ሁል ጊዜ የማያረጁ ወጣቶች ልጆች ይዘዋወራሉ፡፡<br />
56|18|ከጠጅ ምንጭም በብርጭቆዎችና በኩስኩስቶች በጽዋም (በእነርሱ ላይ ይዝዞራሉ)፡፡<br />
56|19|ከእርሷ የራስ ምታት አያገኛቸውም፤ አይሰክሩምም፡፡<br />
56|20|ከሚመርጡትም ዓይነት በእሸቶች፡፡<br />
56|21|ከሚሹትም በኾነ የበራሪ ሥጋ (ይዞሩባቸዋል)፡፡<br />
56|22|ዓይናማዎች የኾኑ ነጫጭ ቆንጆዎችም አሏቸው፡፡<br />
56|23|ልክ እንደተሸፈነ ሉል መሰሎች የኾኑ፡፡<br />
56|24|በዚያ ይሠሩት በነበሩት ምክንያት ዋጋ ይኾን ዘንድ (ይህንን አደረግንላቸው)፡፡<br />
56|25|በውስጥዋ ውድቅ ንግግርንና መውወንጀልን አይሰሙም፡፡<br />
56|26|ግን ሰላም መባባልን (ይሰማሉ)፡፡<br />
56|27|የቀኝም ጓዶች ምንኛ (የከበሩ) የቀኝ ጓዶች!<br />
56|28|በተቀፈቀፈ (እሾህ በሌለው) ቁርቁራ ውስጥ ናቸው፡፡<br />
56|29|(ፍሬው) በተነባበረ በሙዝ ዛፍም፡፡<br />
56|30|በተዘረጋ ጥላ ሥርም፡፡<br />
56|31|በሚንቧቧ ውሃ አጠገብም፡፡<br />
56|32|ብዙ (ዓይነት) በኾኑ ፍራፍሬዎችም፡፡<br />
56|33|የማትቋረጥም የማትከለከልም የኾነች፡፡<br />
56|34|ከፍ በተደረጉ ምንጣፎችም (ሴቶችም መካከል)፡፡<br />
56|35|እኛ አዲስ ፍጥረት አድርገን (ለእነርሱ) ፈጠርናቸው፡፡<br />
56|36|ደናግሎችም አደረግናቸው፡፡<br />
56|37|ለባሎቻቸው ተሽሞርሟሪዎች እኩያዎች (አደረግናቸው)፡፡<br />
56|38|ለቀኝ ጓዶች (አዘጋጀናቸው)፡፡<br />
56|39|ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡<br />
56|40|ከኋለኞቹም ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡<br />
56|41|የግራ ጓደኞችም ምንኛ (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች! ናቸው፡፡<br />
56|42|በመርዛም ነፋስ በጣም በፈላ ውሃም ውስጥ ናቸው፡፡<br />
56|43|ከጥቁር ጭስም በኾነ ጥላ ውስጥ፡፡<br />
56|44|ቀዝቃዛም መልካምም ያልኾነ፡፡<br />
56|45|እነርሱ ከዚህ በፊት ቅምጥሎች ነበሩና፡፡<br />
56|46|በታላቅ ኀጢአትም ላይ ይዘወትሩ ነበሩና፡፡<br />
56|47|ይሉም ነበሩ፡- «በሞትንና ዐፈር፣ ዐጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ በእርግጥ የምንቀሰቀስ<br />
ነን?<br />
56|48|«የፊተኞቹ አባቶቻችንም?»<br />
56|49|በላቸው፡- «ፊተኞቹም ኋለኞቹም፡፡<br />
56|50|«በተወሰነ ቀን ቀጠሮ በእርግጥ ተሰብሳቢዎች ናቸው፡፡<br />
283