26.05.2017 Views

Amharic (Ethiopia) translation of the Quran

Many more Islamic media to read, listen, print and download at ww.IslamicGlobe.com and at www.QuranReciter.org

Many more Islamic media to read, listen, print and download at ww.IslamicGlobe.com and at www.QuranReciter.org

SHOW MORE
SHOW LESS

You also want an ePaper? Increase the reach of your titles

YUMPU automatically turns print PDFs into web optimized ePapers that Google loves.

82|7|በዚያ በፈጠረህ አካለ ሙሉም ባደረገህ ባስተካከለህም፡፡<br />

82|8|በማንኛውም በሻው ቅርፅ በገጣጠመህ (ጌታህ ምን አታለለህ)፡፡<br />

82|9|ተከልከሉ፤ በእውነቱ በፍርዱ ቀን ታስተባብላላችሁ፡፡<br />

82|10|በእናንተ ላይ ተጠባባቂዎች ያሉባችሁ፤ ስትኾኑ፤<br />

82|11|የተከበሩ ጸሐፊዎች የኾኑ፤ (ተጠባባቂዎች)፡፡<br />

82|12|የምትሠሩትን ሁሉ የሚያውቁ፡፡<br />

82|13|እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በገነት ውስጥ ናቸው፡፡<br />

82|14|ከሓዲዎቹም በእርግጥ በገሀነም ውስጥ ናቸው፡፡<br />

82|15|በፍርዱ ቀን ይገቧታል፡፡<br />

82|16|እነርሱም ከርሷ ራቂዎች አይደሉም፡፡<br />

82|17|የፍርድ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?<br />

82|18|ከዚያም የፍርዱ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?<br />

82|19|(እርሱ) ማንኛይቱም ነፍስ ለሌላይቱ ነፍስ ምንም ማድረግን የማትችልበት ቀን ነው፡<br />

፡ ነገሩም ሁሉ በዚያ ቀን ለአላህ ብቻ ነው፡፡<br />

======================================================<br />

ሱረቱ አል ሙጠፊፉን<br />

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በኾነው<br />

__________________________________________________________________________________________________________________<br />

83|1|ለሰላቢዎች ወዮላቸው፡፡<br />

83|2|ለእነዚያ ከሰዎች ባስሰፈሩ ጊዜ የሚያስሞሉ፡፡<br />

83|3|ለእነርሱም (ለሰዎቹ) በሰፈሩ ወይም በመዘኑላቸው ጊዜ የሚያጎድሉ (ለኾኑት)፡፡<br />

83|4|እነዚያ እነርሱ ተቀስቃሾች መኾናቸውን አያውቁምን?<br />

83|5|በታላቁ ቀን፡፡<br />

83|6|ሰዎች ሁሉ ለዓለማት ጌታ (ፍርድ)፤ በሚቆሙበት ቀን (ተቀስቃሾች መኾናቸውን)፡፡<br />

83|7|በእውነት የከሓዲዎቹ (የሰላቢዎቹ) መጽሐፍ በእርግጥ በሲጂን ውስጥ ነው፡፡<br />

83|8|ሲጂንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?<br />

83|9|የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡<br />

83|10|ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡<br />

83|11|ለእነዚያ በፍርዱ ቀን ለሚያስተባብሉት፡፡<br />

83|12|በእርሱም ወሰን አላፊ ኀጢአተኛ ሁሉ እንጅ ሌላ አያስተባብልም፡፡<br />

83|13|አንቀጾቻችን በእርሱ ላይ በተነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው»<br />

ይላል፡፡<br />

83|14|ይከልከል፤ ይልቁንም በልቦቻቸው ላይ ይሠሩት የነበሩት (ኀጢአት) ደገደገባቸው፡፡<br />

83|15|ይከልከሉ፤ እነርሱ በዚያ ቀን ከጌታቸው (ማየት) ተጋራጆች ናቸው፡፡<br />

83|16|ከዚያም እነርሱ በእርግጥ ገሀነምን ገቢዎች ናቸው፡፡<br />

83|17|ከዚያም «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉበት የነበራችሁት ነው» ይባላሉ፡፡<br />

83|18|በእውነቱ የእውነተኞቹ ምእምናን መጽሐፍ በዒሊዮን ውስጥ ነው፡፡<br />

83|19|ዒሊዮንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?<br />

83|20|የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡<br />

318

Hooray! Your file is uploaded and ready to be published.

Saved successfully!

Ooh no, something went wrong!